Professional Documents
Culture Documents
32269
32269
ጥር 5 ቀን 2002 ዓ.ም
ሐጐስ ወልዱ
ሂሩት መለሰ
ታፈሰ ይርጋ
ዓልማው ወሌ
ፍርድ
በዚህ መዝገብ ለቀረበው የሰበር አቤቱታ መነሻ የሆነው ጉዳይ አባትነት ይረጋገጥልኝ በሚል
የተጀመረው በማህበራዊ ፍ/ቤት ሆኖ ልጅነት ይረጋገጥልኝ ክስ ያቀረበችው ተጠሪ ናት፡፡ ተጠሪ ህፃን
1
ያቀረበችው የማህበራዊ ፍ/ቤቱ ህፃን ሕይወት የአቶ ታፈረ ስብሐት ልጅ ነች በማለት ሲወስን በዚህ
ላይ ይግባኝ የቀረበለት የወረዳ ፍ/ቤት ግን ህፃንዋ የአቶ ታፈረ ስብሐት ልጅ አይደለችም በማለት
ወስኖአል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ተጠሪ ለከፍተኛ ፍ/ቤት ይግባኝ በማቅረብዋ በዚህ ደረጃም ክርክሩ
ከተሰማ በኋላ የወረዳው ፍ/ቤት ውሳኔ ተሽሮ የማህበራዊ ፍ/ቤት ውሳኔ ፀንቶአል፡፡ በመጨረሻም
በአመልካቾች በኩል ለትግራይ ብ/ክ/መ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ችሎት አቤቱታ የቀረበ ሲሆን ችሎቱ
የተፈጸመ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የለም ብሎአል፡፡ የአሁኑ የሰበር አቤቱታ የቀረበው በዚህ ላይ ነው፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የሰበር አቤቱታው ከተመረመረ በኋላ በሥር ፍ/ቤቶች ውሳኔ የተፈጸመ መሠረታዊ
የሕግ ስህተት የለም ተብሎ መዝገቡ ተዘግቶ የነበረ ሲሆን በድጋሚ ሊንቀሳቀስ የቻለው አመልካቾች
መጋቢት 19 ቀን 2000 ዓ.ም በተጻፈ ቃለ መሃላ ዳኝነት እንደገና ይታይልን የሚል አቤቱታ
በማቅረባቸው ነው፡፡
እኛም የቀረበውን አቤቱታ መሠረት በማድረግ ተጠሪን አስቀርበን በግራ ቀኝ ወገኖች በኩል
ያለውን ሃሳብ ሰምተናል፡፡ ተጠሪ ዳኝነት በድጋሚ የሚታይበት ምክንያት የለም በማለት ስትከራከር
አመልካቾች ደግሞ የቀድሞ ውሳኔ የተሰጠው በሐሰት የተዘጋጁት ማስረጃዎች መሠረት በማድረግ
በመሆኑ ዳኝነቱ በድጋሚ ቢታይ ውሳኔው እንደሚሻር እርግጠኞች ነን የሚል መከራከሪያ አቅርበዋል፡፡
መሠረት ዳኝነት እንዲታይ የቀረበው ጥያቄ አግባብነት የሚመለከት ነው፡፡ አመልካቾች ጥያቄውን
ሳይሆን በሐሰት የተዘጋጁ ማስረጃዎች በመቅረባቸው ምክንያት ነው፡፡ ማስረጃዎቹ በሐሰት የተዘጋጁ
መሆናቸውን ያረጋገጥነውም ጉዳዩ እስከ ሰበር ችሎት ድረስ ከሄደ በኋላ ነው የሚል ምክንያት
ውሳኔ ሊታረም ይገባል በሚል ለሰበር ችሎቱ አቤቱታ ከቀረበ በኋላ ነው፡፡ ይህ በመሆኑም የዳኝነት
ይታይ አቤቱታ በዚህ ደረጃ ሊቀርብ ይችላል ወይ? የሚል ጥያቄ ተነስቶ ችሎቱ ተመልክቶታል፡፡ በሰበር
መ/ቁ 43821 በቀረበው ክርክር የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁ.6 አተረጓጐም በሚመለከት ችሎቱ ተገቢ ነው
2
ያለውን ትርጉም ሰጥቶአል፡፡ በዚህም የቀድሞ ውሳኔ ይግባኝ ይባልበትም አይባልበት በሐሰተኛ ማስረጃ
እና ወንጀል ቀመስ በመሆኑ ተግባሮች ላይ ተመስርቶ የተሰጠ ነው የሚል አቤቱታ እስከቀረበበት ድረስ
ተመልክቶአል፡፡ የሰበር ችሎቱ በዚህ ረገድ የሰጠው የሕግ ትርጉም ከዚህ በኋላ ገዢ (አስገዳጅ) በመሆኑ
3
ውሳኔ
ወገኖች ክርክር ከሰማ በኋላ ተገቢውን ውሳኔ እንዲሰጥ ጉዳይ ይመለስለት ብለናል፡፡
መዝገቡ ይመለስ፡፡
ፀ/መ