Professional Documents
Culture Documents
581719307
581719307
ችግሮች
1
መግቢያ
ሙስና በየትኛውም የአለም አገራት የሚከሰት ክስተት ነው፡፡ መጠኑ ይለያይ እንጅ ሙስና የሌለበት አገር የለም፡
እንደ ተራነሰፓርንሲ ኢንተርናቲናል (TI) የ 2013 ጥናት 177 አገሮች የሙስና ሁኔታ ጥናት
እንደሚያመለክተው ጥናቱ ከተደረገባቸው 70% ያህሉ አሳሳቢ የሆነ የሙስና ችግር እንዳለባቸው ያሳያል ፡፡
በተመሳሳይ በኢትዮጵያ ሙስና በከፍተኛ ሁኔታ ተንሰራፍቶ እንደሚገኝ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ እንደ 2006 ግሎባል
ኢንተግሪቲ ሪፖርት ሙስና በኢትዮያ የፖለቲካ፤ ኢኮኖሚ እና ማህበረሰብ ውስጥ ስር ሰዶ የሚገኝ አሳሳቢ
ችግር ነው ፡፡ ‘’ትራንስፓረንሲ ኢንተርነሽናል’’ የተባለው ዓለም አቀፍ የበጎ አድራጎት ድርጅት እኤአ ከ 2012
ጀምሮ የዓለም ሀገራትን የሙስና ቅኝት ጥናት እያጠና በየዓመቱ ለሀገሮች ደረጃ የሚያወጣ ሲሆን ሀገራችን
ኢትዮጵያ በድርጅቱ የቅኝት ጥናት መለኪያዎች መሰረት በ 2019 ከ 180 ሀገሮች 37% በማግኘት 96 ኛ ደረጃ
የነበረች ስትሆን በ 2020 ከ 180 ሀገሮች 38% በማግኘት 94 ኛ ደረጃ በመቀመጥ በነጥብም ይሆን በደረጃ አንፃራዊ
መሻሻል አምጥታለች፡፡
በስፋት ከሚታዩ ችግሮች የተለመደዉና ዋናዉ የሰራተኞች በስራ ገበታቸዉ አለመገኘት ነዉ፡፡ ይህ ችግር አጅግ
አሳሳቢ እየሆነ የመጣ ነዉ፡፡ ጊዜ ሕይወት ነዉ፡፡ በአግባቡ ከተጠቀሙበት ጊዜ ሕይወት ይታደጋል፣ ካልሆነ ግን ሰዉ
ሊሞት ይችላል፡፡ ከችግሮቹ መካከል አንዳንዶቹ የሚከተሉት ናቸዉ፡- አርፍዶ ስራ መግባት፣ የሥራ ሰዓት
ሳይጠናቀቅ ቀድሞ መውጣት፣ ያለምክንያት ከስራ ገበታ መቅረትና ጊዜን በአግባቡ ለሥራ አለማዋል ፣ተቋሙ
ዉስጥም ሁኖ አለመስራት፣ በወሬና በጨዋታ ማሳለፍ፣ የግል ስራ በመስራት፣ ከስራ ጋር ግንኙነት የሌላቸዉ
ተገልጋይን በማስተናገድ ረግድ ከባለሙያ ከማይጠበቁ አፀያፊ ድርጊቶች አንዳንዶቹ ቀጥሎ የቀረቡት ናቸዉ፡-
አዋራጅ ባህሪ ፤ ማስፈራራት፤ ለሰራተኞችና ባለጉዳዮች መዋሸት፣ ሃላፊነትን ባግባቡ አለመወጣት፣ ከባለጉዳይ ጋር
ስጦታዎችንና ግብዣዎች መቀበል፣ ማታለል፣ ታማኝ አለመሆን፣ ቅን ባህሪን አለማሳየት፣ ቸልተኝነት፣ ማጉላላት፣
መሳደብ፣ ማመናጨቅ፣ መቆጣት፣ መገልመጥና ማዋከብ፣ አድልኦ መፈጸም፣ በዘመድ አዝማድና በጓደኛነት ቀረቤታ
መስራት፣ የማያስፈልግ እንዲያደርግ ማስገደድ፣ ተገቢ ያልሆነ ዋጋ መጠየቅ እና የመሳሰሉ ችግሮች ይታያሉ፡፡
2
በተለይ የመድሎና የዝምድና ስራ፣ዘረኝነት እና ጎጠኝነት በአገልግሎት አሰጣጥ የሚስተዋል ችግር ነው፡፡ የተለያዩ
በአንድ ጥናት ግብር ከፋዮች እንደገለፁት ግብር ሲወስኑ ተመጣጣኝ አይደለም በስራው ሳይሆን በትውውቅ
ስለሚወስኑ ወይም አድልኦ አለው፡፡ አንዳንድ ጊዜ የገቢዎች ሰራተኞች /ባለሙያዎች/ለግል ጥቅም ፍላጐት
ምክንያት የቀን ገቢ ጥናቱን በትክክል ያለማጥናት ወይም በገበያ እንቅስቃሴ መረጃ ሳይሆን በግምታዊ አሰራር
መሆን በተመሳሳይ ስራ የተራራቀ ግብር ስለሚወስኑ ብዙውን ጊዜ ነጋዴዉ እውነቱን ለመደበቅ ስለሚሞክር ነው
ከፍተኛ የንግድ እንቅስቃሴ ያላቸው አነስተኛ ግብር ሲጣልባቸው አነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴ ያላቸው ከፍተኛ
ግብር ይጣልና ንግዳቸውን እስከ መዝጋት ይደርሳሉ፡፡ ባብዛኛው አጥኝ ኮሚቴ ባጠናው አይሄዱም ገቢ መ/ቤቱ
በራሱ ነው በግምት የሚደለድለው የግብር ሒሳብ ውድቅ ያደርጉና በቀን ግምት አጋነው ይገምታሉ፣በግምት
ስለሚጠና የማዳላት ክፍተት አለ፣ በስም ብቻ ብዙ ግብር ይጥላሉ ፡፡በቀበሌ ደረጃ መታወቂያ አሰጣጥ እጅግ በጣም
ይህ የሙስና መገለጫ ወንጀል መገለጫዉቹም ሐሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀትና መጠቀም፤ ሰነዶችን መሰረዝ፣ መደለዝ፣
መቅደድና ማጥፋት፤ ቀሪና በራሪ ደረሰኝን ማበላለጥ፣ ገቢና ወጭን አለመመዝገብ፤ ለኢንሹራንስና ለግብር
እንደተከፈለ አድርገዉ መሰነድ እንዲሁም የተጋነነ ቁጥር ሪፖርት ማቅረብና የመሳሰሉት ናቸዉ፡፡ እነዚህ
ሰራተኞችና አመራሮች፣ በአቅራቢ ድርጅቶች እና በሌሎች ተገልጋዮች ነዉ ፡፡ በጨረታ፣ ሐሰተኛ ፋክቱር በማቅረብ
የሃሰት የወጭ ረሲት ማቅረብና ማወራረድ፣ የተሳሳተ የግዥ ማስረጃ ማቅረብ፣ላልተገዙ ቁሶች የግዥ ሰነድ
ማቅረብ፣ የሀሰት ሰነዶችን ማዘጋጀት፣ ሃሰተኛ የትምህርት ማስረጃ፣ የሥራ ልምድ፣ መታወቂያ ወረቀት ወይንም
ማንኛውንም ሃሰተኛ ማረጋገጫ መስጠት በስፋት የሚታዩ የማጭበርበር የሙስና ወንጀሎች ናቸው፡፡
ጉዳይ ከመጀመሩ በፊትና በኋላ ክፍያ፣ ጀርባ መደገፍ፣ ማጣፈጫ፣ ማፋጠኛና ማለስለሻ፣ ንግድ ማመቻቸት)፡
የኮንትራትና የግንባታ ፈቃድ ለማግኘት፣ የህክምና መድሃኒቶችን፣ ቁሳቁሶችንና አገልግሎቶችን ለማቅረብ፣
የኮንትራት ዉልን ቀጣይነትን ለማረጋገጥ፣ ሰነድና መረጃዎችን ለመቀየር፣ ለማሳሳት፣ ለማዛባት፣ ከህግ ግዴታና
ተጠያቂነት ለማምለጥ፣ ዉሳኔን ለማፋጠን ወዘተ በሚል የሚሰጥ ነዉ፡፡
3
ውሳኔዎችን ለሚወስኑ የስራ ሃላፊዎች ውሳኔያቸው ለተወሰነ ሰው ወይም ቡድን ተስማሚ እንዲሆን ለማድረግ
ከሚሰጥ ትልልቅ ጉቦ ጀምሮ በተለምዶ ስራን ለማቀላጠፍ በሚል ለበታች ሰራተኞች የሚሰጠውን ትንንሽ ጉቦ
ይመለከታል፡፡
በመሬት አስተዳደር አገልግሎት ውስጥ ግቦ በመስጠት እና ግቦ በመቀበል የተለያዩ ህገወጥ ድርጊቶች ይፈጸማሉ ፡፡
ለመቀየር፣ የይዞታ መሬቱን በህገወጥ መንገድ መጠኑን ለማሳደግ፣የስመ ንብረት ዝውውር ለማድረግ የማይገባ
ጥቅም መጠየቅ፣የመሬት አጠቃቀም እቅዱን ያልተከተለ ግንባታ ሲገነባ በግቦ ዝም ብሎ ማለፍ፣ የመሬት ቅየሳ
መስጠት የተለመደ ነው፡፡ በህገወጥ መንገድ መሬት፣ ፍትህ፣ ጨረታ፣ ወዘተ ለማግኘት በርካታ ነጋዴዎች
ታማኝ ያልሆኑት “ግብር ከፋዮች” በማጭበርበር ወይም ጉቦ(መደለያ) በመስጠት መንግስት ሊያገኝ የሚገባውን
ወይም ከደረጃ በታች የሆኑ ምርቶችን በመመሳጠር በማስገባት መሸጥ፣ የጉሙሩክ ኬላዎች ላይ መደራደር፣የግብር
እፎይታ እና ከቀረጥ ነፃ የሚገቡ እቃዎች ለሌላ አላማ ማዋል የሚሉት ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
ግብር ከፋዩ ግብሩን አጠቃሎ ከመክፈሉ በፊት በመደራደር ግዴታውን ላልተወጣ ግብር ከፋይ ክሊራንስ መሥጠት፣
መግለጽ፣ (የአዋቂ ልብስ የሆነው የህጻን፣3 ፒስ ሆነው 2 ፒስ ሲባል…ወዘተ) በኮንትሮባንድ ከሚያስገቡ ሰዎች ጋር
በመደራደር የኮንትሮባንድ ነጋዴዎች ሰው ከተኛ በኋላ ለሊት እንዲመጡ በመንገር ቀረጥ ሳይከፍሉ በጉቦ እንዲያልፉ
ማድረግ፡፡
ግለሰቦች መታወቂያ እንዳያገኙ በማጉላላት ኢ-ፍትሃዊ ጥቅም ማካበት፡፡ በቀላሉ የሚገኙ መዝገቦች የሉም
ወንጀል ሠርተው ለማምለጥና የቅጣት ጊዜያቸውን ለማሳጠር ለፖሊስና ለፍርድ ቤቶች (ዳኞችና ዓቃብያነ ሕግ)
የሚከፍሉ አሉ፡፡
4
በሆስፒታሎች የተሻለ አልጋ ለማግኘት ግቦ መክፈል የተለመደ ነው፣ ያለወረፋ ለመታከም፣ ለጥሩ እንክብካና የተሻለ
አንድ ግንባታ የሚያከናዉን ኮንትራክተር ከስታንዳርድ በታች የወረደ ግንባታ በመገንባቱና ተቆጣጣሪ መሃንዲሱ
በማየቱ ሪፖርት እንዳይደረግበትና የክፍያ ማረጋገጫ አልፈርምም እንዳይል በማሰብ ጉቦ ሊሰጥ ይችላል፡፡
በአጋጣሚ የግንባታዉን ሁኔታ ለማየት ሲመጡ ኮንትራክተሩ ድል ያለ መስተንግዶ ሊያቀርብ ይችላል፡፡ በአጠቃላይ
ግቦ ኢ-ፍትሃዊ የአገልግሎት ክፍፍልን ያስከትላል፣ ሙስና በተንሰራፋባቸው አከባቢዎች የመብራትና ዉሃ አገልገሎት
ለማግኘት ጉቦ መክፈል የግድ ይላል፡፡ ማለት ከጊዜ፤ከጉልበትና ከገንዘብ አንጻር ጥራት ያለው አገልግሎ ለማግኘት
ግቦ መክፈል ግዴታ ይሆናል (ማሳለጫ)፡፡ በአሁኑ ወቅት ዜጎች ማግኘት የሚገባቸውን አገልግሎት ያለ እንግልትና
ያለአድልኦ ማግኘት ፈታኝ እየሆነባቸው መጥቷል፡፡ ዜጎች በተለያዩ የመንግስት ተቋማት አገልግሎቶችን ለማግኘት
እየተቸገሩ እንደሆነ እየታየ ነው፡፡ይህ መንገላታት ምንጩ በአግባቡ አገልግሎት መስጠት ያለበት አካል ከሚቆረጥለት
ምንዳ ያለፈ ጥቅም ለማግኘት የመፈለጉ ምክንያት ነው፡፡
ባለው ቀረቤታ በመጠቀም ወይም በቀጥታ በሃላፊነት እንዲጠብቃቸው የተሰጠውን ንብረቶች “በጓሮ በር እያወጡ
በመንግስት ንብረትና ሃብት አጠቃቀም ለብክነትና ለሙስና ሊጋለጡ የሚችሉ አካባቢዎች የሚባሉት የሚከተሉት
የመንግስትን ንብረት አለዓግባብ ማባከን እና እንደ ራስ ንብረት አለማየት በበርካታ መስሪያቤቶች ይስተዋላል፡፡
በተለያዩ ተቋማት ውስጥ የመንግስት ሀብትና ንብረት እየተበላሸ፣ ያለአግባብ ወጭ እየሆነና ጥቅም ላይ እየዋለ
መሳሪያዎች ስርቆትና ግዴለሽ ወይም የተዝረከረከ አስተዳደር ነዉ፡፡ እነዚህ የሙስና ተዋናዮች ለጤና ተቋማት
የማያስፈል መድሐኒትና የህክምና መገልገያ መሳሪያ በተደጋጋሚ ይገዛሉ፡፡ ይሕ ለግል የጤና ድርጅቶች ለመሸጥና
5
በከፍተኛ ወጭ የተገዙ ዘመናዊ የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች ያለተበላሽተዉ መቀመጣቸዉም ሌላዉ የዘርፉ
መለያ ባህሪ ነዉ፡፡ ሕሙማንም እንደታከሙበት በማስመሰል ሐሰተኛ ሰነድ ተሰንዶ መድሐኒቶች እና የሕክምና
በህክምናው ዘርፉ ከሚስተዋሉ ሕብረተሰቡን ያማረሩ የሥነ-ምግባር ጥሰቶች እና ሕገወጥ ድርጊቶች መካከል
የሚከቱት ጥቂቶቹ ናቸዉ፡-መድሀኒቶችን ከመንግስት ጤና ተቋማት አዉጥቶ ለግል የጤና ድርጅቶች መሸጥና
ህብረተሰቡን ለብዝበዛ መዳረግ፣ የህክምና መሳሪያዎችን መሰወር፣ መደበቅ ወይም ሆን ብሎ ማበላሸት፣ የሕክምና
መሳሪያዎች ሳይበላሹ ተበላሽቷል በማለት ታካሚዎች ወደ ግል የጤና ድርጅቶች እንዲሄዱ በማድረግ ለከፍተኛ
ተቋም እየሰሩ እንደ ራጅ፣ አልትራሳዉንድ፣ ሲቲ ስካን እና የመሳሰሉትን የሆስፒታልን የህክምና መገልገያ
ያልተጠናቀቁና ደረጃቸዉን ያልጠበቁ ግንባታዎች መረከብ ፣ተገቢውን የግንባታ ብረት አለመጠቀም ወይም
ከተፈላጊ ደረጃ በታች የሆኑ ግንባታ ተግባሮች (substandard building practices) መፈጸም ከግንባታ ጋር ተያይዞ
የውሸት ሪፖርት ማቅረብ፡፡ የግንባታ ፕሮጀክቶች አለማጠናቀቅና እንደተጠናቀቁ አድርጎ ማወራረድ፣ ያልተሰራን
እንደተሰራ አድርጎ ሪፖርት ማቅረብ ፤ግንባታዎችን ስንከታተል የሌለን ግንባታ ወይም የሚፈለገው ደረጃ
ከስፔስፍኬሽን ወይም ከውል ስምምነት በታች (ጥራት የሌለው) አገልግሎት ሲቀርብ በጉቦ ወይም በሌላ ሥጦታ
አማካኝነት ዝም ተብሎ ሊታለፍና ርክክብ ሊፈፀም ይችላል፤ ግንባታው በግዜው ሳይጠናቀቅ ሲቀር፤ በሚፈለገው
6
በሙስና ሰበብ ለማህበራዊ አገልግሎት ለትምህርትና ለልዩ ልዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ግንባታ መዋል የሚገባው
የመንግስት ሃብት ለጥቂቶች እንዲውል ስለሚደያደርግ፣ አብዛኛው ህብረተሰብ የመሠረተ ልማት ተጠቃሚ መሆን
የፍትህ ተቋሙ ቀልጣፋ የምርመራና የማስረጃ አያያዝና አቀራረብን ተግባራዊ በማድረግ የወንጀል ተጠርጣሪዎችና
ተጠቂዎች ፈጣን ፍትህ የማግኘት መብታቸውን ማረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ ይሁንና አንዳንድ ጊዜ ሥነምግባር
በጎደላቸው የተቋሙ አባላት የሚፈጸም ሙስና ተቋሙ ሃላፊነቱን እንዳይወጣ እንቅፋት የሚሆኑበት አጋጣሚዎች
ይፈጠራሉ፡፡
ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የሙስና መከሰቻ አጋጣሚዎች ሥነምግባር በጎደላቸው የተቋሙ አባላት ሊፈጸሙ
የሚችሉ የሙስና አጋጣሚዎች ናቸው፡፡ እነዚህንና መሰል አጋጣሚዎች እንዴት ሊፈጠሩ እንደሚችሉ በመነጋገር፤
አሰራርን በመፈተሽ፣ መፍትሄ ወይም መከላከያ በማፈላለግ ተቋሙን ከሙስና የጸዳ ማድረግ ይገባል፡፡
ማስረጃዎችን ሆን ብሎ በማጥፋት፣
በህገወጦች ወይም በህገወጥ ነጋዴዎች የሚሰሩትን ስራ አይቶ እንዳላየ በመሆን ቋሚ የሆነ የገንዘብ ምንጭ
ሊገኙ ይችላሉ፤
7
የተያዙ ኮንትሮባንድ እቃዎችን ለራስ መውሰድ፣
በቀጥታ ወንጀል እና የተደራጀ ወንጀል ላይ ተሳታፊ መሆን (ለምሳሌ አደንዛዥ እፅ ማዘዋወር፣ ግለሰቦችን
ስልጣን መከታ በማድረግ የቂም በቀል እርምጃ መውሰድ እንደሚችል መዛት፣ማስፈራራት ወይም የበቀል
ተጠርጣሪ በጣቢያ የታሰረበት ጊዜ ሲጠይቅ ሆነ ብሎ ቀኑን ጨምሮ ወይም ቀንሶ ማስረጃ መስጠት
የንግዱ አለም ስራ በዕጅጉ ውስብስብ ነው፡፡ የሁለት ወገኖችን ፍላጎት /የገዥና ሻጭ/ ፍላጎት የሚያስተሳስር ብቻ
አይደለም፡፡ በትስስሩ ውስጥ አንዱ ወገን በሌላኛው ላይ በደል መፈፀም የሚያስችል አጋጣሚ የሚፈጥር ነው፡፡
ንግድን በስራ መስክነቱ የመረጠው ወገን ነግዶ የማትረፍ ወይም ጥቅም የማግኘት መብትና ነፃነት አለው በሌላ
በኩል የንግዱ አገልግሎት ተቀባይ የሆነው ወገን የሚፈልገውን ነገር በተመጣጣኝ ዋጋና በተገቢ ጥራት ማግኘት
ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ንግድ አርቆ አስተዋይነትን ይጠይቃል፡፡ ማለትም ታማኝነት፣ በኃላፊነት ስሜት መንቀሳቀስ፣
ትክክለኛነት፣ ግልፅነት፣ አክብሮት፣ ትህትና፣ ቅንነት…ወዘተ ያሉ መልካም ነገሮች ገቢያን የሚያሞቁና የሚያደምቁ
በመሆናቸው ለንግድ ግንኙነት ቁልፍ ሚና አላቸው፡፡ ነገር ግን የአገራችን የንግድ ግንኙነት የሚፈለግበትን ስነ
አንዳንድ ነጋዴዎች በአጭር ግዜ ያለብዙ ወጭና ድካም ለመበልፀግ ባላቸው ጉጉት የተነሳ በወገኖች ላይ
ጉዳት ያደርሳሉ፡፡ የተለያዩ ባዕድ ነገሮችን ተፈላጊ ከሆኑ ምርቶች ጋር በመደበላለቅ የሚሸጡ ወገኖች አሉ፡፡
8
ለምሳሌ ቅቤን ከሙዝ፣ ከድንችና ከመሳሰሉት ነገሮች ጋር ይቀላቅላሉ፡፡ ዘይትን በእግር ከተረገጠ ፋጉሎ
ጨምረው በመጭመቅ ለገቢያ አቅርበው ይሸጣሉ፡፡ በርበሬን ከቀይ አፈር ጋር ቀላቅሎ በማስፈጨት ለገቢያ
ዱቄትን ከበአድ ነገር ጋር በመቀየጥ የሚሸጡ አሉ፡፡ ግዜ ያለፈበት ምርት የሚሸጡም አሉ፡፡ ሚዛን
ሆቴል ቤቶችም በመጠኑም ሆነ በጥራቱ ደረጃውን ያልጠበቀ ምግብ ማቅረብ፣ ምግብን ለጤና ጠንቅ በሆኑ
የመገልገያ እቃዎችና ቦታዎች ማዘጋጀት፣ ለምግብ ዝግጅት ደረጃውን ያልጠበቁ ግብአቶችን መጠቀም፣
በተገልጋዮች መካከል አድሎ መፈፀም፣ ፅዳት የሌላው የመኝታ ክፍልና አልጋ ማከራየት፣ ከተሰጠው
ከዚህ በተጨማሪ በአሁኑ ሰአት በአገራችን ውስጥ አንዱ የሆነው አርቴፈሻል የገቢያ ስርአት ለመፍጠር
እያደረጉ ያሉት የኢኮኖሚ አሻጥር ይጠቀሳል፡፡ በዚህም አንዳንዶች በመሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች ላይ ሆን
ተብሎ እጥረት እንዲፈጠር በማሰብ ሸቀጦች ሲሰወሩ ይስተዋላል፡፡ ሌሎች ደግሞ አጋጣሚውን
ተጠቅመው የማይገባ ትርፍ ለማጋበስ ሲሉ መሰረታዊ ሸቀጦችን በማከማቸት ገበያው ተፈጥሮዊ ሂደቱን
እንዲያጣ ያደርጋሉ፡፡ በተጨማሪም አንዳንድ ነጋዴዎች ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡
በአሁኑ ሰአት በተለያዩ ቦታዎች ምርቶችን በመጋዝን አከማችተው ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ
በሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይ ቁጥጥር እየተደረገ ነው፡፡ እርምጃ የመውሰድ ስራውም ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
ህብረተሰቡም በአገርና በህዝብ ላይ እየተፈፀመ ያለውን ይህን እኩይ ሴራ በማጋለጥ መብቱን ማስጠበቅና
ለዚህም ተገቢውን መረጃ ለሚመለከተው አካል በመስጠትም የኢኮኖሚ «ሳቦታጅ» ፈፃሚዎችን ድርጊት
ለሽያጭ በሚቀርቡ ማለትም ከውጭ ሀገር የገቡ ወይም በሀገር ውስጥ የተመረቱ ማንኛውም እቃዎች፣
የግብርና ምርቶች፣ የምግብ እና መሰል ሸቀጣሸቀጦች ላይ የማይገባ ዋጋ መጨመር በህግ የተከለከለ ነው፡፡
በተጨማሪም ምርት መደበቅ እና ማከማቸት፣ ምርትን ከባዕድ ነገር ጋር መቀላቀል፣ ሚዛን ማዛባት፣ ግዜ
ያለፈባቸው ምርቶች ለገቢያ ማቅረብ፣ ደረሰኝ በሚያስፈልጉ የንግድ ቦታዎች ላይ ያለደረሰኝ መገበያየት፣
እና ሌሎችም በህግ የተከለከሉ ድርጊቶችን መፈፀም በንግድ ህግ የሚያስቀጣ በመሆኑ ነጋዴዎች ጥንቃቄ
ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
ከሁሉም በላይ ግን ሁሉም ነጋዴ ከስግብግብና እራስ ወዳድ አመለካከት በመራቅ ለማህበረሰብ ፍትሀዊ
9
ከትራንስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ
ከትራንስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ በዕቃ መጫኛ ተሽከርካሪዎች ሰዎችን መጫን፣ ከተሽከርካሪ አቅምና ከተፈቀደው
በላይ ሰው መጫን፣ ከተፈቀደ ታሪፍ በላይ ለሰውም ሆነ ለእቃ ማስከፈል፣ በመንገድ ላይ በቂ ባልሆኑ ምክንያቶች ተገልጋዩን
ማቆየት ወይም ግዜውን ማባከን፣ ከሰው ጋር እንሰሳትንና /ለምሳሌ ደሮ፣ በግ ወዘተ/ የተለያዩ አደገኛ ነገሮችን /ለምሳሌ
በርበሬ፣ ነዳጅ፣ አልኮል…ወዘተ/ መጫን ወዘተ ምክንያት ተገልጋዩ ላልተፈለገ እንግልት እና የጤና ጠንቅ እየተጋለጠ ነው፡፡
የሊዝ ቦታ አሰጣጥ ስርአቱ በተመለከተ ወጥነት የጎደለው እና ለበርካታ ብልሹ አሰራር የተጋለጠ መሆን፣ መሬት
ለልማታዊ ባለሀብቶች ከመስጠት ይልቅ ለማልማት አቅም ለሌላቸውና መሬት ለሚሸጡ ግለሰቦች መስጠት፣
ምትክ ቦታ ሲጠየቅ ባለሥልጣኑ ማዘጋጀት ሲገባው ጠቁሙ ማለትና የተጠቆመውንም ቦታ ጥያቄውን ላላቀረበ
ባለሀብት አሳልፎ መስጠት፣መሬትን በሊዝ በድርድር ምንም ቅድመ ሁኔታ ላላሟሉ በዝምድናና በመሳሰሉት
ግንኙነቶች መስጠት፣ የሊዝ ዋጋ ግምት በጣም ዝቅተኛ እንዲሆን ማድረግ፣ በአንድ አካባቢ በአንድ ደረጃ ላይ
ለሚገኙ ቦታዎች የተለያየ የሊዝ ዋጋ ማውጣት፣ አቅም እያላቸው መሬት ያላገኙ ልማታዊ ባለሀብቶች
ሕጋዊ ላልሆኑ ይዞታዎች የይዞታ ማረጋገጫ ካረታ እና ሌሎች መረጃዎችን መስጠት፣ የተቋሙ ሰራተኞች
ከደላሎችና ላንድ ስፔኩሌተርስ ጋር በመመሳጠር የተለያዩ የመሬት መረጃዎችን በህገወጥ በማዘጋጀትና መሬቱን
በመሸጥ ወይም ህገወጥ ጥቅም በማግኘት የመንግስትና የህዝብ ሃብት ይመዘብራሉ፡፡ደላሎች በከተማው ውስጥ
የሚገኙ የተለያዩ ክፍት የመንግስት መሬቶችን መረጃ ስላላቸው ከተቋሙ ሰራተኞች ጋር በመመሳጠርና ህገወጥ
መረጃዎችን በማዘጋጀት መሬት በህገወጥ ሲያስተላልፉ ይታያሉ፡፡በተለይ ተቋሙ በቂና ጥራት ያለው የመሬት
መረጃ ስርአት ስለሌለው ለደላሎች በቀላሉ የመሬት መረጃውን ለማጭበርበር እድል ይፈጥርላቸዋል፡፡
ከይዞታ ለሚነሱ ሰዎች ካሳ አከፋፈል፣ ተተኪ ቦታ አሰጣጥ፣ ወዘተ በብልሹ አሰራር ውስጥ መገኘት፡፡ በከተሞች
ማስፋፊያ አካባቢ የሚገኙ አርሶ አደሮች ከነበሩበት ይዞታ ከከተማ መስፋፋት እና ዕድገት ጋር ተያይዞ ሚመጣው
ልማት ምክንያት ከይዞታቸው ለሚፈናቀሉ አርሶ አደሮች የንብረት ካሳ ግመታ እንደአከባቢዉ ተጨባጭ ሁኔታ
የሚለያይ ቢሆንም በጥናት ወቅት ከተሰበሰቡ መረጃዎች ለመረዳት እንደተቻለዉ አፈጻጸሙ የዜጐችን ንብረት
መልሶ መተካት በሚያስችል መልኩ ወቅታዊ የገበያ ዋጋ ተመን መሰረት ግልጽነትና ተጠያቂነት ባለው አሠራር
የተጠናከረ አይደለም፡፡ ለምሳሌ በክልላችን ያለው የካሳ ግመታ አሠራር ወጥነት የሌለው ከከተማ ከተማ የተለያየ
ነው፡፡ አንድ ጥናት እንዳመላከተው በሃዋሳ ከተማ የነበረው አሠራር ሲታይ በአንድ ወቅት ከአንድ ሄክታር
10
ለሚፈናቀሉ 1 እጣ የተሰጠበት፣ በሌላ ወቅት ለተመሳሳይ ይዞታ 5 እጣ የተሰጠበት ሁኔታ ሲኖር በሌላ ከተማ
ከ 200 ካ.ሜ 500 ካ.ሜ ፣በሌላ አካባቢ ደግሞ የንብረት ግመታ ክፍያ ተፈጽሞ ተተኪ ቦታ የሚሰጥበት ሁኔታ
ይታያል፡፡
በተጨማሪ በከተማ አስተዳደር በመሬት ልማት አስተዳደር ከዋጋ ግመታ ጋር በተያያዘ የነበረዉ አሰራር የጓሮ
ንብረት ዋጋ በግብርና ባለሙያ፣ የቤት ግምት በማዘጋጃ ቤት ባለሙያ የሚገመት ሲሆን ከስም ዝዉዉር ጋር
በተያያዘ የቤት ግምት ወይም የታክስ ግመታ በታክስ ባለስልጣን ባለሙያ የሚፈጸምበት አሰራር በመሆኑ አፈጻጸሙ
ወጥ በሆነ መለኪያ የተበጀለት ካለመሆኑ ጋር ተያይዞ በሰዎች በጎ ፈቃድ ላይ የተመሰረተ እንድሆን አድርጎታል፡፡
ለባለሀብቶች ወይም ለምሃበራት ቦታ ከመስጠት በፊት ቦታዉ /ይዞታዉ/ ከማንኛውም የይገባኛል ጥያቄ ነጻ
ሳይሆን፣ ለመንግሥት ወይም ለቀበሌ ቤት ወይም በቦታው ለነበሩ አርሶ አደሮች ተገቢ ካሳ ሳይከፈል ሕግና ደንብ
ከሚፈቅደው ውጭ ተሰጥቶ ህጋዊ ባለሀብቶች ሳይት ኘላን ይዘው ለችግር መጋለጥ፣ይህም በሥራ ላይ ጫና
እያሳደረ ይገኛል፡፡
የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ (ምስክር ወቀረት) አሰጣጥ ተጠያቂነትንና ግልፅነትን የተከተለ አለመሆን፡፡ የመሬት
ልማትና አስተዳደር ባለሥልጣን ከሚሰጣቸው ዋና ዋና ተግባራት አንዱ የቦታና ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ አሰጣጥ
ነው፡፡ ይህን ሥራ በተገቢው ሁኔታ ለመወጣት ተጠያቂነትና ግልጽነትን የተከተለ ባለመሆኑ በማህበር ተደራጅተው
መሬት ለመውሰድ ጥያቄ ላቀረቡ ተገልጋዮች በአንድ ሰው ስም ካርታ በመስጠት ህገ ወጥ ተግባር መፈፀም፣ በአንድ
ቦታ ላይ ለሁለት ሰዎች ካርታ መስጠት፣ መሀንዲሶች ሲለኩ ባዶ ቦታ መተውና በህገወጥ መንገድ እንዲያዝ
በሚያመች ሁኔታ ካርታ መስራት፣ በካርታ ላይ ካርታ በመስራት፣ ተገልጋዮችን ለአላስፈላጊ ችግር መዳረግና ፍትህን
ማዛባት፣ የመንግስትን ቤት ተከራይተው ለሚኖሩ ግለሰቦች ማስፋፊያ አግባብ በሌለው መንገድ መስጠት፣ የቀበሌ
ቤት በግል ይዞታ ማዞር ለዚህም የግል ማህደር ማጥፋትና በግለሰብ እንዲቀየር ማድረግ፣ ክፍትና ለመናፈሻ
የሚሆኑ ቦታዎችን ለግለሰቦች በመስጠት የይዞታ ማረጋገጫ እንዲኖራቸው ማድረግ፣ ለአንድ ግለሰብ ከአራት ቦታ
በላይ ለመኖሪያ ቦታ መስጠት፣ በውጭ ድርጅቶች ለቆሻሻ ማስወገጃ የተሠራውን ቦታ በጥቅማጥቅም ለግለሰብ
መስጠትና በአካባቢው ነዋሪ ላይ የጤናና ማህበራዊ ችግሮችን ከሚያስከትሉ ነገሮች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
የመንግስት ቤቶች በመድሎ ለሚፈልጉት ሰው መስጠት የግል ቤት እያላቸው በመንግስት ቤት ወይም በቀበሌ ቤት
መኖር
11
የመኖሪያ ቤት እጥረት ለማቃለል የመኖሪያ ቤት የሌላቸው ሰዎች በሕጋዊ መንገድ በግል ወይም በማህበር
ተደራጅተው የመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታ የሚያገኙበት አሠራር ያለ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ቤት ለመሥራት
ስለመኖሩ ይታወቃል፡፡
ሆኖም በአንዳንድ አካባቢ በነበረዉ ብልሹ አሰራር ግማሹ የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ጠይቆ የማያገኝበት አሠራር
ሲታይ ሌላዉ ደግሞ በአንድ ከተማ ውስጥ ከሁለት በላይ የመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታ እየወሰደ፣ እየሸጠ እና ቤቱን
ለሌላ ሰዉ በማከራየት እሱ በመንግሥት ቤት በመሆን ተጠቃሚ የሚሆንበት ሁኔታ መኖሩ በህዝብ በተደጋጋሚ
መዝገብ ቤት በማንኛዉንም መስሪያ ቤት እጅግ ጠቀሜታ ያለዉ የስራ ዘርፍ ነዉ፡፡ እንዲያዉም ለሙስና ሊጋለጡ
ከሚችሉ አደገኛ ቦታዎች አንዱ እንደሆነ በዘርፉ ጥናት ያደረጉ ምሁራን ይስማማሉ፡፡ ስለሆነም መዝገብ ቤትን ህገ
የተለያዩ ጥናቶች እንዳመላከቱት አብዛኛው የመሬት ፋይል የተቀመጠው በዘፈቀደ እንደሆነ የሚሰሩበት ቢሮም
ጣራው ክፍተት መሆኑ ማንም ሰው በጣራው ገብቶ መዝገቡን ማውጣት የሚችልበት ሲሆን የፋይል ቅብብሎሽም
አንድ አንድ ግለሰቦች እንደሚገልፁት ከሆነ ደላሎች እያንዳንዱን ማስረጃ የህግ እውቅና ከተሰጠው ተቋም
ገቢ እንዲደረግ እና የመሬቱ ባለቤት ህጋዊ እውቅና እንዲያገኝ የሚያደርጉበት አቅጣጫ አለ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ቀድሞ
በነበሩ የተቋሙን ሰራተኞች መሃተም እና ፊርማ በመጠቀም የሃሰት የመሬት የይዞታ ማረጋገጫ ማስረጃዎችን
በፋይሎች ላይ ለተለያዩ ችግር ሊያጋጥም የሚቻልበት ሁኔታ እንዳለ መታዘብ ይቻላል ማለትም የፋይል መጥፋት፣
የሠነድ መቀየር፣ መበላሸት/መቀደድ/ ሰፊ ከመሆኑም በላይ ጥንቃቄ የጎደለው የፋይል እንቅስቃሴ እንዳለ እና በዚህ
በከተሞች የይዞታ ማህደር አደረጃጀት እና አስተዳደር ለዘርፈ ብዙ ችግሮች ተጋልጦ የቆየ መሆኑ ይታወቃል፡፡
የይዞታ ማህደር መሰወር፣መጥፋት እና ለተለያየ ብልሽት መጋለጥ ወ.ዘ.ተ.የሚታዩ ችግሮች ናቸዉ፡፡ በዚህም የተነሳ
12
ተገልጋዩ ለከፍተኛ እንግልት እና ዉጣ ዉረድ ተጋልጧል፡፡ ችግሩን ይበልጥ አሳሳቢ የሚያደርገዉ ደግሞ ክፍተቱ
የመረጃ አያያዝ ችግር አለ፡፡ በአብዛኛው ተገልጋዮች ጉዳይ ለማስፈጸም የቤት ሰነዳቸውን በሚፈልጉበት ጊዜ
በቀላሉ አይገኝም ወይም ከናካቴው ይጠፋል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ጊዜው ያለፈባቸው ፋይሎች (dead files)
በሌላ በኩል የፋይሎች አያያዝና አቀማመጥ ጉዳይ በአብዛኛው ችግር ያለበት ነው፡፡ ፋይሎች በአይጥ የመበላት
ሁኔታ አለ፡፡ አንዳንዶች የተሻለ አቀማመጥ ያላቸው አንዳንዶች በተሻለ ሁኔታ ፋይል ቆልፈው የሚያስቀምጡም
ያሉ ሲሆን አንዳንዶች ደግሞ ቦታው በተገቢው ብርሃናማ ያልሆነ በመሆኑ ቀኑን ሙሉ መብራት እያበሩና ወደ
ውስጥ ገባ ብለው ፋይል ለማምጣትም ሞባይል እያበሩ የሚንቀሳቀሱበትን ሁኔታ ከመኖሩም በላይ ካለው ፋይል
ከተሞች እየተስፋፉና በዙሪያው የሚገኙ የገጠር ቀበሌያት ወደ ከተማነት እያደጉና እየተጠቃለሉ ያሉበት ሁኔታ
በአሁን ወቅት በግልጽ የሚታይ ጉዳይ ነው፡፡ በተለይም የከተማና ድንበር በመሬት ላይ ያረፈ ግልጽ አዋሳኝ ባለመኖሩ
በከተሞች አዋሳኝ አካባቢ የሚገኘው የመሬት ሀብት በሕገ ወጥ መንገድ በወረራ እየተያዘ፣ ከኘላን ውጭ የሆኑ
ግንባታዎች እየተበራከቱ ሽንሽኖ አልባ በሆኑ ይዞታዎች፣ ደረጃቸውን ባልጠበቁ ግንባታዎች የከተማ ውበት
ከማበላሸቱም በተጨማሪም የተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ለመካሄድ እንቅፋት የሆነበት ሁኔታ ሲኖር በሌላ
በኩል ደግሞ በሕገ ወጥ መንገድ ያአግባብ ለመሬት ግዥ እና ግንባታ እየተፈፀመ ገንዘብ ለብክነት እንድጋለጥ
ሲሆኑ “በዚህ ትልቅ መንገድ ይወጣል“ ፣ “በዚህ አከባቢ ገበያ ልቆም ነዉ፣“ ወዘተ.. እያሉ ነዋሪዉን አርሶ አደር
አንዳንድ ባለሀብቶች የመንግሥት ቤቶች እና ክፍት ቦታዎችን በማስፋፊያ ስም ከአቅም በላይ እየጠየቁ እና
እየተፈቀደ ወደ አንድ ይዞታ ካጠቃለሉ በኋላ በተፈቀደው ጊዜ ውስጥ ወደ ልማት ባለመግባታቸው መንግሥት
13
ከቦታው ማግኘት ያለበትን ገቢ እንዳያገኝ፣ ህብረተሰቡም በልማቱ ተጠቃሚ እንዳይሆን በማድረግ የተወሰኑ
ግለሰቦች ከተማውን በመቆጣጠር ባዶ ቦታ እየከለሉ እየሸጡ ህገ ወጥ ጥቅም እያገኙ ስለመሆኑ ግንዛቤ ተወስዷል፡፡
በሊዝ የተላለፉ ቦታዎች በብዛትና በስፋት ታጥረው የተቀመጡና አንዳንዶቹም የተባለው ግንባታ ሳይገነባ
ተከራይተው ለሌላ አገልግሎት የሚውሉበት ሁኔታ/ለብሎኬት ማምራቻ፣ ለሻይ ቡና መሸጫ፣ መኖሪያ ቤቱን
ለዘይት መጭመቂያ ወዘተ/ እንዳለ ተረጋግጧል፡፡ ግንባታ ያልተጀመረባቸው የሊዝ ቦታዎችም ማስተላለፊያ ዋጋው
ከፍተኛ በመሆኑ ውስጥ ለውስጥ በሚደረግ ሂደት ተሽጠውና ተገንብተው ከ 2 አመት አገልግሎት በኋላ በዝቅተኛ
ዋጋ ስመ ንብረት ዝውውር የሚፈፀምበት ሁኔታ እንዳለ በጥናት ታይቷል፡፡ በንግድና በመኖሪያ የሊዝ ቦታ የወሰዱ
ሰዎች ቦታውን ለመውሰድ የሚያደርጉትን የነቃ እንቅስቃሴና ተሳትፎ ቢኖርም ቦታው በተሰጣቸው ጊዜ ገንብተው
ለተባለው አገልግሎት እንዲውል በማድረግ እረገድ ጉድለቶች መኖራቸውና ከታለመላቸው አላማ ውጭ እየዋሉ
መሆኑ ተረጋግጧል፡፡
ሕጋዊ የሆነ ከተሞች መሪ ኘላን ተዘጋጅቶ ለመንግሥታዊ ተቋማት፣ ለማህበራዊ አገልግሎት፣ ለአረንጓዴ ተክል
የሚውሉ መናፈሻዎች፣ እንደ አገልግሎቱ አይነት፣ በመንገድ ተለይተው በዚሁ መሰረት የሚመሩበት ሥርዓት
እንዳለ ይታወቃል፡፡
የከተማ መሪ ኘላን ለመንገድ፣ ለአረንጓዴ መናፈሻ እና ለተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎቶች የሚውሉ በታዎች
ለመኖሪያና ለንግድ ተሽንሽኖ የሚሰጥበት አሠራር ስለመኖሩ ይገለጻል፡፡ ችግሩ የጐላ ባይሆንም በአንዳንድ ከተሞች
በፊት ለግሪን ኤሪያ ተብሎ የተተው ቦታዎች በመሸንሸን የክፍል ከተማ ማዘጋጃ ጽ/ቤት፣ የትምህርት ተቋማት፣
የጤና ተቋማት እና የተለያዩ ግንባታ ተከናውኖ አገልግሎት እየሰጠ ያለበት ሁኔታ ስለመኖሩ ተጠቅሷል፡፡ ከተማ
በማካተት የሚዘጋጅበት እና እንደገና ማሻሻያ የሚደረግበት አሠራር የተጠናከረ ያለመሆን ተጠቃሽ ምክንያት ነው፣
በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንዱስትሪ ለተደራጁ ማህበራት የመሥሪያ ቦታ ለ 5 ዓመት የሊዝ ዘመን የሚሰጥ ስለመሆኑ
ተጠቅሷል፡፡ ሆኖም ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንዱስትሪ ለተደራጀ ማህበራት የተሰጡ ቦታዎች በመሸንሸን ወደ ግል
14
ከተማ አስተዳደር ጋር በተደረገዉ ዉይይት በጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት ስም ለተደራጁ ስራ አጦች በተሰጡ
ቦታዎች ላይ ስራ አጥ ያልሆኑ ከአመራር ጀምሮ ለሌሎች ሰዎች ተሰጥቶ ያሉበት ሰለመሆኑ ያረጋገጡበት ሁኔታ
አለ፡፡
የግንባታ ማጠናቀቂያ ጊዜ ካለፈ በኃላ ምንም ዓይነት ግንባታ ሳይፈጸም መሬት ለሶስተኛ ወገን ማስተላለፍ
ማንኛውም በሊዝ ኪራይ ለኢንቨስትመንት መሬት የወሰደ ወደ 3 ኛ ወገን በሽያጭ ለማስተላለፊ የስም ዝውውር
ጥያቄ ሲቀርብ በአፈጻፀም መመሪያ ቁጥር 2/97 አንቀጽ 2.4.5 እና ደንብ ቁጥር 27/97 አንቀጽ 13/1/ መሠረት
የዋናው ቤት ግንባታ ወይም የህንጻ ግንባታ 51% እና ከዚያ በላይ በማጠናቀቅ ልዩ ልዩ ክፍያዎች በአግባቡ
ስለመከናወኑ ተረጋግጦ መፈጸም እንዳለበት ተገልጿል፡፡ በተጨማሪም በአዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀጽ 24፣ ደንብ
ቁጥር 103/2004 አንቀጽ 34 እና የአፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 1/05 አንቀጽ 64 ስር ማንኛዉም የሊዝ ባለይዞታ
የግንባታ ማጠናቀቂያ ጊዜ ከማለፉ በፊት የሊዝ መብቱን ለሶስተኛ ወገን ማስተላለፍ እንደሚቻል ተደንግጓል፡፡
ሆኖም በጥናት ወቅት ከተሰበሰቡ መረጃዎች ለመረዳት እንደተቻለዉ በርካታ ቦታዎች ምንም አይነት ግንባታ
ለተለያዩ ኢንቨስትመንቶች የሚሰጡ ቦታዎች ለፕሮጀክቱ በቂ ስለመሆናቸዉ ሳይጣራ የሚሰጥበት አሰራር መኖር
በከተማ ውስጥ የሚገኙ ቁልፍ የሆኑ ቦታዎች ለተለያዩ ኢንቬስትመንቶች ከመሰጠቱ በፊት የተጠየቀው የቦታ
ስፋት፣ በቦታው የሚካሄደው የግንባታ ዓይነት፣ የሚያርፍበት ስፍራ፣ ለተሽከርካሪ ማቆሚያ የሚሆን ቦታ
እንዲሁም ኘሮጀክቱ የሚያስገኘውን ፋይዳ እና በአካባቢዉ ላይ የሚያስከትለው ጉዳት መኖር አለመኖሩ በሚገባ
ተጠንቶ መሰጠት እንዳለበት ይታወቃል፡፡ ሆኖም በአንዳንድ ከተሞች ለኢንቨስትመንት የሚሆን የቦታ ጥያቄ
በሚቀርብበት ወቅት ተገቢ የሆነ ጥናት ሳይደረግ የሚፈቀድበት አሠራር በመኖሩ ግንባታ ከተጀመረ በኋላ
የተሽከርካሪ ማቆሚያ፣ ለሴፍት ታንከር፣ ለኩሽና ለመጸዳጃ ወ.ዘ.ተ የሚሆን በቂ ቦታ ሳይቀር ግንባታ
የሚፈፀምበት ሁኔታ በመኖሩ ባለሀብቱ ይህንን ክፍተት በመጠቀም በጐን የሚገኘውን ተጨማሪ ቦታ እንዲጠይቅ
ሁኔታ በማመቻቸት አጠገቡ የሚገኘን የመንግሥት ቤት ወይም ቦታ ያለ ውድድር የሚወስድበት አሠራር በመኖሩ
የሀሰተኛ ሠነድ ባለጉዳዩ እንዲያዘጋጅ የተመቻቸ ሁኔታ መኖር፣ በቀበሌ በአግባቡ የማረጋገጥ ሥራ አለማከናወን፣
ፍ/ቤት የባለቤትነት ማረጋገጫ ሲጠይቅ አንዳንድ ቀበሌና የመሬት አስተዳደር ባለሥልጣናት ሀሰተኛ መረጃ
15
በመስጠትና ውሳኔዎችን በማዛባት ካርታ እንዲያገኙ ማድረግ፣ የተጭበረበረ ሠነድ ማዘጋጀትና ህግን የማስከበር
በመንግስት ተቋማት ውስጥ በሀሰተኛ ማስረጃ የመጠቀም / የመቀጠርና የደረጃ እድገት የማግኘት / ሁኔታ
እየተፈጠረ ነው፣የሃሰት የመሬት ማስረጃዎች ባስመሳይነት በተፈጠሩ ፎቶግራፎች አማካኝነት የመሬት የይዞታ
ማረጋገጫ ካርታ ይዘጋጃል፣ ሀሰተኛ የመኖሪያ ቤቶች ህብረት ሥራ ማህበራትን በማቋቋም የማህበሩ አባለት
የስ/ጎ/ዞ/ስ/ጸ/ሙ/ኮ በያመቱ በርካታ ሀሰተኛ የመሬት ማስረጃ ሰነዶችን ይመረምራል፡፡እነዚህን የሃሰት የመሬት
ማስረጃዎች ባስመሳይነት በተፈጠሩ ፎቶግራፎች አማካኝነት የመሬት የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ይዘጋጃል፡፡
ት/ቤቶች፤ ኮሌጆች፤ ዩንቨርስቲዎች በቂና በሞያ ብቃታቸው አስተማማኝ መምህራን አይኖሩትም ስለዚህ
ተማሪዎች ሲመረቁ በቂ እውቀት ጨብጠው እይወጡም ፡፡ ሙስና በተንሰራፋበት ማህበረሰብ ውስጥ የትምህርት
ደረጃን በገንዘብ መግዛት ወይንም በሃሰት ማዘጋጀት ስለሚቻል ችሎታና አቅም ያላቸው፤ ዘመድና ገንዘብ
የሌላቸው ወጣቶች ስራ የማግኘት እድላቸው የተመናመነ ይሆናል፡፡
ተጫራቾች በቡድን በመደራጀትና ከቡድናቸው ውስጥ አንዱ እንዲያሸንፍ ለማድረግ ልዩ ልዩ ዘዴዎችን መጠቀምን
ይመለከታል፤ ይህም በሁለት ዓይነት መንገድ ሊፈጸም ይችላል፤ አንደኛው ተጫራጮች በመመካከር አሸናፊ
የሚሆኑ ቡድኖችን ተራ በማስያዝ፤ አንተ መጀመሪያ አሸናፊ ትሆናለህ አንተ ደግሞ ቀጥሎ በመባባል ሲሆን፣
ሌላው ደግሞ የመጫረቻ ዋጋን ሆን ብሎ ከፍ በማድረግ ከአሸናፊ ተጫራች የተወሰነ ገንዘብ የሚከፋፈሉበት ዘዴ
ነው፡፡
የሚወገዱ ንብረቶች ለዚያ መስሪያ ቤት አገልግሎት የማይሰጡ ቢሆንም የህዝብ ሃብት ናቸውና ባግባቡ ሊወገዱ
ይገባል፡፡ በመሆኑም ግዥ በውል ሲፈጸም እንደሚደረገው ሁሉ፣ የሚወገዱ ንብረቶችንም የማስወገድ ሂደት
በእቅድና የገንዘብን ዋጋ ባገናዘበ መልኩ መሆን ይገባዋል፡፡ በማስወገድ ሂደትም የሚፈጠሩ የሙስና አጋጣሚዎችን
ለመከላከል በሚያስችል መልኩ መሆን ይገባቸዋል፡፡ ከዚህ በታች የተገለጹት ንብረትን በማስወገድ ሂደት ሊከሰቱ
16
የሚገለገሉበትን ንብረት አገልግሎት በማሳነስ( የማይሰራ በማስመሰል) ከሚወገዱ እቃዎች ውስጥ እንዲመደብ
ሊፈጠር ይችላል፤ የሚወገዱ የህክምና መሳሪያዎች፤መድሃኒቶች በጨረታ በማስወገድ ሂደት ለእጩ ተወዳዳሪዎች
አንዳንድ መስሪያ ቤቶች ሰራተኞችን መምረጥ፣ ቅጥር፣ እድገትና የሙያ ማሻሻያ ጉዳይ ላይ ተገቢ የሆኑ
ስርአቶችን፣ ህግና ደንቦችን አላስቀመጡ ይሆናል፡፡ ቢኖሩም አንዳንድ ጊዜ እየታወቁ ሊዘነጉና ሊጣሱ ይችላሉ፡፡ ይህ
ከሆነ በዚህ ዘርፍ ዉስጥ የሚከተሉት እንዲከሰቱ ያደርጋል፡-የተሳሳተና ህገ ወጥ የሆነ የሰራተኛ ቅጥርና
ሰራተኛ መቅጠር፣በሁሉም ደረጃ የስራ ብቃትና ጥራት መዉደቅ፣መርህንና የስራ መስፈርትን በመጣስ ወጣ ገባ
እድገትና የስራ ማሻሻያ፣ የሚገባቸዉ ባለሙያዎችና ሰራተኞች የሙያዊ ልማት ተጠቃሚ አለመሆን፡፡
ከፍተኛ መደቦችንና ሹመቶችን በኔትወርክ፣ በጥቅማጥቅምና በሥልጣን ቀረቤታ በመስጠት የሚፈፀሙ የሙስና
በሆነ አስተዳደር የስራተኛውን እድገት ቅጥርና ጥቅማ ጥቅም ችሎታን መሰረት ባደረገ መንገድ ባለማከናወንና
ምቹ የሥራ ሁኔታ እንዳይኖር በማድረግ የሰራተኛውን የሥራ ፍላጎትና ሞራል እጅጉን እንዲጎዳና የሥራ
ለሙስና በከፍተኛ ደረጃ ከተጋለጡ የስራ ዘርፎች ዉስጥ ግዥና ጨረታ አንዱ ነዉ፡፡ከግዥ ጋር የተያያዙ የሙስና
ከሚገባው በላይ የተጋነነ መሆን፣ ተመሳስለው በተሰሩ ፎርጅድ እቃዎች በርካታ ገንዘብ ይባክናል፣ ስለሆነም ይህንን
ችግር ለመግታት የግዥና ጨረታ ሂደት ስነ ስርአቶች ግልጽና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ የሚተገበሩ መሆን አለባቸዉ፡፡
የተጋለጡ ናቸዉ፡፡ ለዚህ ምክንያቱም በመስሪያ ቤቱ የተቀመጡ መመሪያዎች በዚህ አካባቢ የሚሰሩ ሰራተኞች
ወይንም ሃላፊዎች ልዩ የመወሰን ስልጣን የሰጣቸዉ በመሆኑ ነዉ፡፡ ልዩ የሆኑ ለአንድ ግለሰብ የሚሰጡ የመወሰን
17
ስልጣኖች ለሙስናና ስልጣንን አላግባብ መገልገል ወንጀል መፈጠር ምክንያት ይሆናሉ፡፡ በዚህ ሁኔታ ለሙስና
በተለይ በየክፍለከተማው እና ቀበሌው የመታወቂያ አሰጣጥ ስርአት ለበርካታ የሙስና ወንጀል የተጋለጠ ነው፡፡
ወጭ ለመቆጣጠር ብዙ ጊዜ ከባድ ነዉ፡፡ ምክንያቱም ባብዛኛዉ በግለሰብ ደረጃ የሚፈጸም ስለሆነ ነዉ፡፡ በዚህ
በኩል የሚባክነዉና የሚጭበረበረዉ ገንዘብ እጅግ ብዙ ነዉ፡፡ በፊልድ ስራ የሚወጣዉ ገንዘብ ላይ አላግባብ
የመገልገልና የሙስና እድሎች በማንኛዉም ደረጃ ማለትም ከጉዞ በፊትና በኋላ ሊከሰቱ ይችላሉ፡፡ እነዚህ እድሎች
የሚፈጠሩባቸዉ ምክንያቶች፡-
ኃላፊዎች የውሎ አበል መስክ ሣይሄዱ ወይም ሣይወጡ ሁሉ አበል የሚያወራርዱ እንዳሉ በተጠኝዎች ተጠቅሷል፣
ሰኔ በረረች ብሎ ያለአግባብ በጀቱን ማባከን ሲሉ አንድ ተጠኝ ገልጸዋል፣በመስክ ሥራ ወቅት ላልተሠራ ሥራ ክፍያ
መክፈልና ቀን ጨምሮ የማወራረድ ሁኔታ ሠራተኛውን ጨምሮ በብዛት ከፍተኛ አመራሩ ዘንድ በከፍተኛ ሁኔታ
በጉዞ ክፍያ ላይ የሚታዩ ሌሎች አላግባብ መገልገሎች ፡-ያልተፈቀደ ከጸደቀዉ ጋር ልዩነት ያለዉ የጊዜ ቆይታ፣ለጉዞ
የሚፈለገዉ ገንዘብ ሳይጸድቅ ቀድሞ መሰጠት፣የተሰጠዉ ገንዘብ ከጉዞ በፊት መባከን (ወጭ) መሆን፣ሃሰት የዉጭ
መንግሥት ለኢንቨስትመንትና ለንግድ መስፋፋት እጅግ አስፈላጊ የሆኑ መሠረተ ልማቶችን ለምሳሌ፡- የኃይል
በብዛት ለመዘርጋት ገንዘብ ያስፈልገዋል፡፡ በመሆኑም እነዚህን ተግባራት ለማከናወን የሚያስችል ወጪ የሚገኘው
ከተለመዱት የመንግሥት ገቢዎች መካከል በፐርሰንት ሲሰላ ትልቁን ድርሻ የሚይዘው ከግብር የሚገኝ እንደሆነ ልብ
ይሏል፡፡ ከዚህ በመነሳት በታክስ ላይ የሚፈጠር ሙስና ለልማት እንቅፋት እንደሚሆን መገመት አያዳግትም፡፡
18
የግብር አሰባሰብ ሥርዓትንና ደንብን በማዛባት ከገቢ ግብር እና ልዩ ልዩ የታክስ ገቢዎች ለመንግስት መግባት
የሚገባውን የገቢ መጠን በመቀነስ በቂና አስፈላጊ የሆኑ አገልግሎት መስጫ ተቋማት እንዳይፈጠሩ እንቅፋት
በመሆን፣
የገቢ ሂሳብን በማምታታት ወይም ሌላ ህገወጥ ዘዴዎችን በመጠቀም የታክስ ክፍያን መቀነስ ወይም ፈጽሞ
ለማስቀረት የሚደረግ የተሳካ ወይም ያልተሳካ ሙከራ ነው፡፡ ታክስ ሰዋሪዎች ትክክለኛ ገቢያቸውንና ትርፋቸውን
ግብር ስወራ የሚመለከተው በስህተት ምክንያት ወይም አቅም በማጣት የታወቀ የግብር ግዴታ ሳይከፈል ለሚቀር
ግብር ሳይሆን ሆነ ተብሎና እያወቁ የተለያዩ የማታለያ፣ የተንኮልና አሳሳች ነገሮች በመፈጸም ሊከፈል የሚገባ
በዚህም ባለፉት አመታት ግብር ከፋዮች ሃሰተኛ ደረሰኝ በማቅረብ፣ ገቢን አሳንሶ በማሳወቅ፣ ኪሳራን
“ግብር መሰወር መዋረድ ነው” በሚል አንድ ግብር ከፋይ ተናግረዋል፡፡ ሌላው ግብር ከፋይ ”አንዱ በትክክል እየከፈለ
አንዱ የሚሰውርበት አካሄድን መከላከል ካልተቻለ ሌላውም እንዳይከፍል ያደርጋል” የሚል ሃሳብ ሰጥተዋል።
አንድ ለተጨማሪ እሴት ታክስ ስብሳቢነት የተመዘገበ ነጋዴ የዕቃ ወይም የአገልግሎት ማቅረብ ሥራ በማከናወን
በዚህ ግብይት የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ሰብስቦ እያለ የሰበሰበው የተጨማሪ እሴት ታክስ ሙሉ በሙሉ
ለግብር ሰብሳቢው መሥሪያ ቤት ላለመክፈል የፈጸመው የሽያጭ መጠን ዝቅ አድርጐ ሊያሳውቅ ይችላል፡፡ ይህንን
ለማድረግ የፈጸማቸውን ሽያጮች በተወሰነ መልኩ ለመደበቅ ያለደረሰኝ ግብይት መፈጸም(ደረሰኝ አለመስጠት) ፣
የተጭበረበረ ደረሰኝ መጠቀም፣የተሰበሰበን ተጨማሪ እሴት ታክስ በወቅቱ ገቢ አለማድረግ ፣ ሐሰተኛ የሒሳብ
መዝገብ የማደራጀት ወይም የተፈጸሙ ሽያጮች በሒሳብ መዝገብ ያለመመዝገብ ድርጊት ሊፈጽም ይችላል፡፡
የሽያጩ መጠን ዝቅ ከተደረገ (ከተደበቀ) ደግሞ ባልተገለጸው ሽያጭ ላይ የተሰበሰበ የተጨማሪ እሴት ታክስ ለራስ
በማስቀረት የግብር መሰወር ድርጊት ይፈጽማል፡፡ ይህም በአገራችንም ሆነ በሌሎች አገሮች ላይ በታክስ አሰባሰቡ
ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እየፈጠረ ያለ ሕገወጥ ድርጊት ነው፡፡ ለምሳሌ በ 2010 በመጀመሪያዉ ሩብ ዓመት ብቻ
ካለደረሰኝ ሲገበያዩ የተገኙ 90 ድርጅቶች መኖራቸዉን እና ከዚህ ጋር ተያይዞ ከ 131 ግለሰቦች በፍታብሄር እና
19
የሰበሰቡትን ታክስ (VAT) ለመንግሥት አለመክፈል፡፡ ይህም ከላይ በተገለጹት ድርጊቶች አማካይነት ሊፈጸም
የሚችል ሲሆን፣ በሌላ መልኩ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፈጸሙአቸው ግብይቶች የሚሰበስቡ ነጋዴዎች አስቀድሞ
በተሰላ ሁኔታ ድርጅታቸው ኪሳራ ሳይገጥመው ሆነ ተብሎ የመክሰር ውሳኔ በማሰጠት አስቀድሞ የተሰበሰበ ቫት
ሳይከፈል የሚቀርበት ሁኔታ አለ፡፡ በሌላ በኩል አንዳንድ ነጋዴዎች ለተጨማሪ እሴት ታክስ ሰብሳቢነት በመመዝገብ
ከፈጸሙአቸው ግብይቶች ቫት ሰብስበው ለመንግሥት ሳይከፍሉ ይዘውት የመጥፋት ድርጊት (Missing trader
fraud) በአገራችን እንዲሁም በሌሎች አገሮች በስፋት የሚታይ የግብር ስወራ ዓይነት አለ፡፡
በ 2010 400 ሽያጭ መመዝገቢያ ማሽኖች ደብዛቸው ጠፍቷል፡፡ እነዚህ ማሽኖች ከመሥሪያ ቤቱ የመረጃ ቋት
ዕቃዎቹ በሕገወጥ መንገድ ከገቡ ግን በእነዚህ ዕቃዎች ላይ ሊከፈል ይችል የነበረው ቀረጥና የተጨማሪ እሴት ታክስ
ጨምሮ ሌሎች በገቢ ዕቃዎች የሚከፈሉ ታክሶች ሳይከፈሉ እንዲቀሩ ያደርጋል፡፡ በሕገወጥ መንገድ የገቡ ዕቃዎች
ተገቢው ቀረጥና ታክስ ሳይከፈልባቸው መግባታቸው ብቻ ሳይሆን በአገር ውስጥ ገበያ ላይ የሚሸጡት ከሌሎች
እንደሚያስከትል በርካታ የጥናትና ምርምር ግኝቶች አረጋግጠዋል፡፡ ከዚህ ቀጥሎ እያንዳንዱን በዝርዝር እናያለን።
2.1. የመንግስት ገንዘብ እና ንብረት በከፍተኛ ሁኔታ እየባከነ ይገኛል፣
የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ከሚጠይቁት በላይ ወጭ ይኖራቸዋል፣ወጭዎች ባልታቀዱ ፐሮጀክቶች፣
ፕሮግራሞች ላይ ይዉልና ከፍተኛ ብክነትን ያስከትላል፣የመንግስት ሃብት ወደግል ንብረት በቀላሉ የሚቀየርበት
ሁኔታም ይፈጠራል፣በመንግሥት ገንዘብ በውድ ዋጋ ተገዝተው የሚገቡ እቃዎች ትክክለኛነት የሚረጋገጥበት
(የጥራትቁጥጥር) ስርዓት ወጥነት የሌለው፣ቀልጣፋ ያልሆነ እና አስተማማኝነት የጎደለው መሆኑ ሌላው ችግር
ሆኖ ቆይቷል።
20
ለኢኮኖሚ እድገት የተነደፉ የልማት ፕሮጀክቶች ለህብረተሰቡ የጎላ ጥቅም በማይሰጡ ፕሮጀክቶች እንዲተኩ
በማድረግ፣ የመንግስት በጀት ለተገቢው እና ቅድሚያ ሊሰጠው ለሚገባው ተግባር እንዳይውል በጥቂቶች
የአገርን ሃብት ጥቂት ባለስልጣናትና ባለሃብቶች እንዲቀራመቱት ሁኔታዎችን በማመቻቸት አብዛኛውን ህዝብ
ለድህነት፣ ለችግርና ለከፋ የጉስቁልና ኑሮ መዳረግ፡፡ ሙስና በፈጠረዉ ሚዛናዊ ባልሆነ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ
ምክንያት ድህነትና የሃብት ልዩነት መጠን ስለሚሰፋ ድግግሞሹ በበዛ አዙሪት ዉስጥ ግለሰቦችና አገር እጅግ በከፋ
ሁኔታ እንዲራቆቱ ያደርጋል፡፡ ምሁራኖች ይህንን "paradox of plenty or Dutch disease" በማለት ያብራሩታል፡፡
የመጀመሪያዉ ጽንሰ ሃሳብ የሚገልጸዉ የተትረፈረፈ ሃብት እያላቸዉ ህዝባቸዉን በቀን 3 ጊዜ መመገብ
ያቃታቸዉን ሲሆን፣ ሁለተኛዉ የሚገልጸዉ ደግሞ የኢኮኖሚ እድገቱ የተዛባና ኢ-ፍትሃዊ የሆነ መሆኑን ነዉ፡፡
ከፍተኛ የውጪ ኢንቨስተሮችን /ባለሃብቶችን/ ገንዘብና እውቀታቸውን በአገር ኢኮኖሚ እድገትና ልማት ላይ
ለማዋል የሚያስችል አገልግሎቶችን ለማግኘት ጉቦ እንዲከፍሉ በመጠየቅ ወደ አገር ውስጥ ገብተው ገንዘብና
እንቅስቃሴን ይገድባል፡፡
21
ሙስና ሰብአዊ መብትን ይጥሳል ፤ በሙስና የተሰደዱ፣የሞቱ፣ያበዱ፣የድሀድሀ የሆኑ ዜጎች አሉን፡፡
ሙስና የሰዉል ጅሰ ብአዊነትና ክብርን የሚሸረሽር ምሁራዊ ስንፍናን እና ወሬኛነትን የሚያሰፋ፣ እያወቁ እዉነታን
መደበቅና ማዛባትን፣ችላ ባይነትንና ደንታቢስነትን፣ትኩረት አለመስጠትን የሚያባብስ፣የፈጠራ ችሎታን
የሚገድልና የእዉቀት ስድትን የሚያመጣ ነዉ፡፡
ሙስና ጥራትና ደረጃዉን የጠበቅ የህክምና አገልግሎት እንዳይኖር በማድረግ፣ በጀት ጉድለት በመፍጠር፣ የህክምና
በጨረታ ተገዝተዉ የሚላኩ መድሃኒቶች ደረጃቸዉ የወረደ፣የሚገዙ የህክማ ቁሳቁሶች ጥራት ደረጃቸዉ የወረደ
በመሆኑ አገልግሎት ሳይሰጡ በቀላሉ መበላሸት፣ለወረዳ የሚመደቡ መድሃኒቶች ከተማ ላይ በድብቅ የሚከማቹ፣
ጊዜ ያለፈባቸዉና ጉዳት የሚያደርሱ መድሃኒቶች በብዛት መሸጥ፣ ለወሊድ አገልግሎት የመጡ አንቡላንሶች
የህዝብ ትራንስፖርት መገልገያ ሆነዉ የግለሰቦች መጠቀሚያ መሆን፣ዉድ የሆኑመድሃኒቶች በየቦታዉ በስፋት
መዘረፍ፣ ወጥተዉ መሸጥ በጥቅሉ መንግስት በጤናው ዘርፍ የሚያደርገውን ጥረት አደጋ ላይ ይጥላሉ፡፡
2.7. የፍትህ ጉዳት
ሙስና የህግ የበላይነት እንዲዛባ ያደርጋል፡፡ኪሚያመጣቸዉ ጉዳቶች ዉስጥ ዋና ዎቹ የህግና ስርአት
መፈራረስ፣የህግና ፖሊሲዎች አለመተግበር፣ፍትህን ለማግኘት አለመቻል፣መጓተትና መከልከል፣ችግር ያለበት የህግ
አፈጻጸም፣በህግ ስርአቱ ያለዉ የህዝብ መተማመነት ናእምነት እንዲቀንስ፣ስጋት እንዲጨምር፣ህገ ወጥነት
እንዲበዛ ያደርጋል፡፡
ሙስና በህግ እኩል የመዳኘትንና የመንግስት አገልግሎት ጥራትን ስለሚቀነስ የሕግ የበላይነት ስሜትን ከህብረተሰቡ
ዘንድ በማጥፋት ማህበረሰቡን ላልተረጋጋ ህይወት በመዳረግ ዋልጌነት፣ ጥፋተኛነትና ሥርዓተ አልበኝነት
22
2.8. ለሌሎች ወንጀሎች መከሰት ምክንያት ይሆናል
ሙስና ሌላሙስና ይወልዳል( corruption breeds corruption)፣ሙስና ማፍያዎች የተደራጀ ወንጀል እንዲፈጠሩ
ያደርጋል፣ፖሊስ ደካማ እንዲሆንና ወንጀለኞች የመያዛቸው እድል ደካማ እንዲሆን ያደርጋል፣ የአደገኛ
መድሃኒቶችና እጾች፣የመኪና አደጋዎች መበራከት፣የጦር መሳሪያዎች ዝዉዉር፣ወዘተ..እንዲበራከት ያደርጋል፡፡
በህብረተሰቡ ውስጥ አንቱ የተባሉ ሰዎች በሙስና ውስጥ የሚዘፈቁ ከሆነ በህብረተሰቡ ዘንድ ያለውን የጨዋነት
መመዘኛ ከማዛባቱም ባሻገር ለሌሎች የሥ-ነምግባር ብልሹነት እና ለሙስና ተግባር እንደመከላከያ (ማጣቀሻ)
ተደርገው ሊቀርቡ ይችላል፡፡ “እነ እገሌም እንዲህ ያደርጉ የለም እንዴ” የሚል አመለካከት እንዲዳብር
ከማድረጉም ባሻገር ስርዓተ አልበኝነት፣ ህገወጥነት እንዲስፋፋና የአገር ሰላምና መረጋጋት አደጋ ውስጥ
ሙስና ህዝብ በመንግስትና በሕግ የበላይነት ላይ አመኔታ እንዲያጣና በዲሞክራሲ ሥርዓት ላይ ጥርጣሬ
እንዴት?
የመንግስት ሥራዎች ከተገቢው አሰራርና ከሕግ ውጪ እንዲከናወኑ በማድረግ፣ ሙስና ዜጐች በሀገራቸው
ብሔራዊ ሃብት ተጠቃሚ እንዳይሆኑ መብታቸው እንዲነካና አድሎ እንዲፈጸምባቸው ስለሚጋብዝ ህዝቦች
በመንግስት ላይ የሚኖራቸው እምነት እንዲሸረሸርና በሚኖሩበት ሀገር ውስጥ የቤተኝነት ስሜት እንዳይሰማቸው
በማድረግና በዚህም የተነሳ በመንግስትና በህዝብ ዘንድ ትልቅ ክፍተት እንዲፈጠር ያደርጋል፣
በአንድ አገር ውስጥ የፖለቲካ መረጋጋት እንዲጠፋ በማድረግ ነፃና ፍትሀዊ ምርጫ እንዳይኖር በማድረግ ለህገ ወጥ
ሹም ሽር እንዲጋለጥ ምክንያት ይሆናል፣ የመልካም አስተዳደር ችግር መንግስት በህዝብ ዘንድ አመኔታ በማሳጣት
አገርን ወደ ፖለቲካዊ አለመረጋጋት እንዲያመራ ከማድረግ ባሻገር የሕግ የበላይነትን በማደብዘዝ ስርዓተ
የህግ የበላይነት መደብዘዝና ሥርዓተ አልበኝነት መንገስ ደግሞ ሕዝብ የተረጋጋ ኑሮ እንዳይመራ ከማድረግ ባሻገር
23
የሙስና በአንድ አገር ውስጥ መንሰራፋት የአገር ደህንነት ላይ የራሱ የሆነ አሉታዊ ተጽእኖ ይፈጥራል። በተለይም
ሙስና በሚያስከትለው ያልተመጣጠነ የሃብት ክፍፍል በአንድ አገር ውስጥ ግጭቶችና አልፎ ተርፎም የእርስ በርስ
በሌላ በኩል ሙስና በአንድ አገር ውስጥ የመንግስት አለመረጋጋት ስለሚፈጥር የአገርን ህልውና ጥያቄ ውስጥ
ይከታል፡፡ ለዚህም ጥሩ ምሳሌ የሚሆነው ሙስና በአውሮፖዋ ሀገር ጣሊያን ተደጋጋሚ የካቢኔ መበተን እንዲደርስ
ማድረጉን በዋቢነት ማንሳት ይቻላል:: በአፍሪካም በሴራሊዩን፣ በላይቤሪያ፣ በኮንጐ፣ በሶማሊያ የደረሰው መጠነ
ሙስና ለአገሮች ሁለንተናዊ እድገት ማነቆ ከመሆኑም በላይ ህልውናቸውንም በመፈታተን ሰላምና የፖለቲካ
መረጋጋት እንዳይኖር ያደርጋል፡፡ ይህም ማለት ሙስና ለሃገሮች የፖለቲካ አለመረጋጋትና ለርስ በርስ ጦርነቶችና
ግጭቶች መንስኤ ሊሆን ይችላል፡፡ ይህ በአብዛኛው ጊዜ የሚስተዋለው የተወሰነ የህብረተሰብ ክፍልን መሰረት
በማድረግ አላስፈላጊ የሆነ የጥቅም ትስስር በሚኖርበት ወቅት በድርጊቱ የተወሰኑ ቡድኖች ብቻ የሚጠቀሙበት
ሲሆን ነው፡፡ ከሥርዓቱ ወይንም ከአገዛዙ ምንም አይነት አልያም ጥቂት ጥቅም የሚያገኘው ቡድን ራሱን
በማንቀሳቀስ እኩል ወይም የተሻለ ድርሻ ለማግኘት የሃይል አማራጭን በመከተል ትግል ይጀምራል፡፡ በዚህ ወቅት
ሙሰና የእርስ በርስ ጦርነትን እንደሚያመጣ ሁሉ የእርስ በርስ ጦርነትም የሙስና ወንጀል የበለጠ እንዲስፋፋና
እንዲወሳሰብ በር ይከፍታል፡፡ ይኸውም አንድ አገር በእርስ በርስ ጦርነት ስትታመስ ሌሎች አገሮች በሁኔታው
እነዚህ አገራት ጦርነቱ እንዳይበርድ በማድረግ በእዛ ሃገር ውሰጥ የሚገኘውን የማእድን፣የነዳጅና ሌሎችን ሃብቶች
የሙስና መንሰራፋት የተለያዩ እቅዶች እንዳይተገበሩና ያልተስተካከለ እድገት እንዲኖር በማድረግ በመንግስት ላይ
የተለያዩ ተቃውሞዎችና ጥያቄዎች እንዲነሱ በማድረግ በከፋ መልኩም ለጐሳ ግጭቶች፣ ለብሔርና ለኃይማኖት
ጦርነቶች በር በመክፈት፣
ሙስና የዲሞክራሲ ሥርዓት መሠረት የሆኑትን የግልጽነትና የተጠያቂነት መርሆዎችን የሚያፋልስ የሰዎችን
ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን የሚገድብ ተግባር በመሆኑ ሕዝብ በዲሞክራሲ ሥርዓት ላይ ጥርጣሬ
እንዲኖረውና ለሥርዓቱ ግንባታ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዳያደርግ እንቅፋት በመሆን በዚህም ህዝብ መንግስት
24
ሙስና ለመንግስት መዳከም፣ ለፖለቲካ አለመረጋጋትና ለደም አፋሳሽ ብጥብጥ አንዱና ዋነኛዉ መንስኤ ነዉ
የሚለዉ ነበር፡፡ በአንድ አገር ዉስጥ ያቆጠቆጠ ሙስና መንግስትን የሚያዳክመዉ በአንድ ቀን ጀንበር ሳይሆን ቀስ
በቀስ ተቋማትንና የመንግስትን የአካሄድ ስርአቶችን እና የህግ የበላይነት በመሸርሸር ነዉ፡፡ በጊዜ መቆጣጠር
ካልተቻለ እንደካንሰር ይስፋፋና ግላዊ ጥቅሞች ከአገራዊ ጥቅሞች በላይ መሄድ ይጀምራሉ፡፡ የግል ጥቅም
መንግስትን የሚቆጣጠር ከሆነ መንግስት ይዳከምና መንግስታዊ ተግባሩን መወጣት ተስኖት የመዳከም ምልክት
በሙስና እና በመንግስታት መዳከምና አለመረጋጋት መካከል ግንኙነት ለመፍጠር ዋነኛ ትኩረት የሚሆነው ስር
የሰደደና የተስፋፋ ሙስና ነው፡፡ የዚህ አይነት ሙስና የመንግስት ተቋማት በአግባቡ ተግባራቸውን እንዳይወጡ፣
ማህበራዊ አገልግሎቶችን ጤና፣ ትምህርት፣ ደህንነት /ባግባቡ እንዳይሰጡ ያደርጋል፡፡ የመንግስት ቁልፍ ተግባራት
የሚባሉት የግዛት ቁጥጥር፣ ሰላምና ደህንነት፣ የመንግስት ሀብትና ንብረትን የማስተዳደር የተጎዱ የህ/ክፍሎችን
የሙስና እድሎች በሰፉባቸዉ አገሮች ዘርፎ የመያዝ እድል ዝቅተኛ ስለሚሆን ባለስልጣን ሆኖ ሲዘርፉ ለመኖር እና
ባለስልጣን ሆኖ ለመዝረፍ የሚፈልጉ ሰዎችና ቡድኖች እንዲበዙ ያደርጋል፡፡ በዚህም የፖለቲካ ስልጣን ለመያዝ
የሚደረግ ዉድድር ጤናማ ያልሆነ፣ በተንኮልና በሸፍጥ የተሞላ፣ ለብጥብጥና ግጭት በር የሚከፍት ይሆናል፡፡ ለዚህ
አይነት አደጋ የተጋለጡ ብዙዎቹ አገሮች ሰፊ የተፈጥሮ ሃብት ያላቸዉ አገሮች ኮንጎ፣ ሴራሊዮን፣ ላይቤሪያ፣ ሱዳን፣
ሙስና ስር በሰደደባቸው አገሮች ነፃና ሚዛናዊ በሆነ ምርጫ የፖለቲካ ስልጣን መያዝ ስለማይቻል የምርጫ ሂደቱ
የተጭበረበረ፣ በገንዘብ የተገዛ እንዲሆንና የምርጫ ማጭበርበር ክሶች በጉቦ እንዲዘጉና ላቅ ያለ ጥቅም ያቀረበ
ስልጣን እንዲይዝ ያደርጋል፡፡ በምርጫ ስልጣን የመያዝ እድሉ ቢጠፋ ሁለተኛዉ አማራጭ ማለትም ብጥብጥ
ሲጠቃለል ሙስና የህዝብን እምነት ያጣ ስልጣን ላይ ያለ መንግስት በስልጣን የመቆየት እድሉን ያሰፋለታል፡፡
በገዥዎች አማካኝነት ስር የሰደደና የሰፋ ሙስና ገዥዎች ለግልፅነት፣ ለተጠያቂነትና ለፖለቲካዊ ሙስና
ጆሮአቸውን እንዲደፍኑ፣ ሚስጥራዊ ግንኙነቶች ደግሞ በህ/ሰቡ ውስጥ እንዲሰፉ በማድረግ አለመረጋጋቱን
ያባብሰዋል፡፡
አንድ የተረጋጋ የፖለቲካ ስርኣት በራሱና በማህበረሰቡ ወይም በጥቂት ማ/ሰብ ክፍሎች፣ በመንግስት ውስጥ ባሉ
ቡድኖች መካከል የሚፈጠር ግጭትን /አለመግባባትን/ በቀላሉ መፍታት ይችላል፡፡ ፖለቲካዊ ሙስና ወይንም
የፖለቲካው በሙሰኞች የመበረዝ ሁኔታ ተቋማዊ አገልግሎት አሰጣጡን የሚያዳክም፣ የፖለቲካ ለውጥ ሂደቱን
25
የሚያበላሽ፣ የህግ የበላይነትን የሚሸረሽር፣ የግጭት መፍቻ ዘዴዎች ውጤታማ እንዳይሆኑ የሚያደርግ ነው፡፡
በዚህም ሰዎች አለመግባባትን ለመፍታት ወደ ፍርድ ቤት ወይንም አስተዳደራዊ ስነርዓቶች ከመሄድ ይልቅ ሀይልና
መንግስት በራሱ አለመግባባቱን መፍታት ሲሳነው ህገ ወጥ ወደሆነ ሀይል የመጠቀም መንገድን በመከተል ስርዓት
ለማስጠበቅ ይሞክራል፡፡ ግጭትና አለመግባባትን ለመፍታት /በጉልበት ሀይል ላይ መተማመን ሀይል መጠቀም እድል
ያለው የማ/ሰብ ክፍል በጉልበት ስልጣን ላይ ያለውን መንግስት ይቀናቀናል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሙስና መልካም
አስተዳደርን በማዳከም መንግስታዊ ገቢ እንዲቀንስ በማድረግ መሰረታዊ አገልግሎቶች ማነቆ በመሆን መንግስት
እንዲዳከምና እንዳይረጋጋ ያደርጋል፡፡ እንዲሁም አቅማቸው የደከመ ያልተረጋጉ መንግስቶች በራሳቸው ሙስና
እንዲጎለብት ያደርጋሉ፡፡ ይህ የሆነው የህግ የበላይነት መዳከም፣ ከሙስና ጋር የተያያዙ አቤቱታና ቅሬታዎችን
ሙስና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ በመፍጠር የአገር ልማት እንዲቀጭጭ፣ የኢኮኖሚ እድገት እንዲገታ፣ ኪሣራና
ውድቀት እንዲፋጠን እና ድህነት በከፍተኛ ደረጃ እንዲስፋፋ በማድረግ ዜጎች ወደ ከፋ የኑሮ አዘቅት ውስጥ
እንዲወድቁ ያደርጋል፡፡
ለህዝብ የሚቀርቡ የፍጆታ ዕቃዎች መጠንና ጥራትን በመቀነስ የግብይትን ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ በማናር ህዝብን
ሙስና በሰፈነበት አገር በዋነኛነት ሰፊው ህብረተሰብ የችግሩ ተጠቂ በመሆኑ በሚያጋጥመው የኢኮኖሚ ቀውስ
ሳቢያ አብዛኛው ህዝብ ለድህነት ይዳረጋል፡፡ ሰርቼ የተሻለ ኑሮ አኖራለሁ ብሎ የሚመኘው ህዝብ ለሥራ አጥነት፣
ለጎዳና ተዳዳሪነት እና ለሴተኛ አዳሪነት ይጋለጣል፣ እጅግ ሲከፋም ለስደት እንዲዳረግ ምክንያት ይሆናል፡፡
2.11. በሃቀኛ የገበያ ተፎካካሪዎች ላይ የሚያስከትለው ተጽእኖ
ሙሰኛ ተጫራቾች ማእቀብ ካልተደረገባቸውና ሁሌም አሸናፊ ከሆኑ በጥራት፣ በአዳዲስ ፈጠራና በተመጣጣኝ ዋጋ
በማቅረብ ኢኮኖሚውን ሊደግፉ የሚችሉ ታማኝ ተፎካካሪዎች ከገበያ እየወጡ እንዲሄዱ ምክንያት ይሆናል፡፡ሙስና
ከነጻና ፍትሃዊ ዉድድር ዉጭ የሆኑ ጥቂት ጥገኛ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ብቻ ተጠቃሚ እንዲሆኑና ህጋዊ
26
ሙስና ተፎካካሪነትን ስለሚቀንስ የፈጠራ ስራ እንዲዳከም ምክንያት ይሆናል፡፡ በሙስና የሚተማመኑ አቅራቢዎች
ሃብታቸውን በፈጠራ ላይ በማዋል የተሻለ ነገር ይዞ ከመቅረብ ይልቅ የተለመደውን እቃ ወይም አገልግሎት ይዘው
መቅረብን ይመርጣሉ፡፡
2.12. እዳ ለቀጣዩ ትውልድ እንዲተላለፍ ምክንያት ይሆናል
አገሮች ውስጥ የበጀት እጥረት /ዴፊሲታቸው/ ከፍተኛ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ በመሆኑም መንግሥት
ገቢውን ለማሳደግ ብድርን ጨምሮ ሌላ አማራጭ እንዲፈልግ ይገደዳል፡፡ ይህ ደግሞ መንግሥትን ከብድር አዘቅት
ውስጥ እንዲገባ በማድረግ በጉዳዩ ውስጥ የሌለበት መጪው ትውልድ የእዳ ተሸካሚ እንዲሆን ያስገድደዋል፡፡
2.13. በግልና በቤተሰብ የሚደርስ ጉዳት
አንድ ሰው በሙስና ወንጀል ተጠርጥሮ ሲፈረድበት በእሱና በቤተሰቡ ላይ ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም
ስነልቦናዊ ጉዳት ይደርሳል፡፡ ሰዎች ከሚወዱት ቤተሰብ ይለያሉ፣ ከስራ ገበታቸው ይፈናቀላሉ፤ በዚህ ምክንያትም
የቤተሰብ ኢኮኖሚ ይናጋል፤ ልጆች ትምህርት ቤት ሊያቋርጡ ይችላሉ፤ከሚኖሩበት አካባቢም በመፈናቀል
ማህበራዊ ኪሳራ ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ፤ በሙስና መያዙ በራሱም በግለሰቡ እና በቤተሰቡ ላይ የሚያደርሰው ስነ
ልቡናዊ ጉዳት ቀላል አይደለም፡፡
2.14. ሙስና የተፈጥሮ ሚዛንን ያዛባል
በማዛባት ከባቢያዊ ሁኔታዎችን የሚያዛቡ ተግባሮችን በመፈጸም የሰውን ልጅ የመኖር ህልውና የሚፈታተኑ
ጉዳቶችን ያስከትላል፡፡
እንዴት ?
የተፈጥሮ ሃብቶች ከማንኛውም ሃብት ባልተናነስ መልኩ ለሙስና የተጋለጡ ናቸው። ይህም በሁለት መንገድ ሲሆን
አንደኛው የተፈጥሮ ሃብቶችን ኃላፊነት በጐደለው መንገድ መመዝበር ነው::ሁለተኛው ደግሞ ለአካባቢ ብክለት
ከፍተኛ ሚና የሚኖራቸውን፣ የአካባቢ ዑደትን ሊያዛቡ የሚችሉ አደገኛ የኬሚካል ተረፈ ምርቶችን በየብስ፣
በሙስና ግንኙነት ለደን የተከለሉ የደን ልማት ቦታዎች እንዲጨፈጨፉ፣ ነዳጅና የተፈጥሮ ሃብቶች አንዲሰረቁ፣
ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡና ጥቅም ላይ እንዳይውሉ የተከለከሉ ኬሚካሎች ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡና ጥቅም
ላይ እንዲውሉ በመፍቀድ የአገር የተፈጥሮ ሃብት ያለአግባብ እንዲባክን በማድረግ፣ በዚህም ለአከባቢ አየር
ከህገ ወጥ የመሬት ወረራ ጋር ተያይዞ ከተሞች ማስተር ፕላናቸውን ጠብቀው ለልማትና ለእድገት አመቺ የሆነ
27
በአካባቢ የተፈጥሮ ሃብቶች ላይ ከሚፈጸሙ የሙስና ወንጀሎች በቀዳሚነት ሊጠቀስ የሚችለው የሕግ ወጥ የደን
ቆረጣ ሲሆን ፣ለምሳሌ በካምቦዲያ በ 1997 ዓ.ም ለመንግስት ባለስልጣናት የተሰጠ ጉቦ ወደ 200 ሚሊዮን ዶላር
የሚጠጋ ሲሆን፣ ይህ የካምቦዲያ መንግስት በህጋዊ መንገድ ከተፈጥሮ ደን ሽያጭ ካገኘው በ 13 እጥፍ ይበልጣል፡፡
በኢንዶኔዥያም በሃገሪቱ ጥቅም ላይ የእንጨት ውጤቶች ከ 50-70 በመቶ በሕገ-ወጥ መንገድ የሚመረት ሲሆን
ይህም የሃገሪቱን የደን ሃብት በዓመት ከሁለት ሚሊዮን ሄክታር በላይ እንዲወድም ያደርጋል፡፡ በተመሳሳይ በሩሲያ
በኢኮኖሚ ዘርፍ በግል ሴክተሩ የንግድ እንቅስቃሴ ወጭን ያጋንናል፡፡ የንግድ ባለቤቶች የሚከፍሉት ጉቦ፣ ለድርድር
የሚያወጡት ወጭ፣ ወይንም ህግን በመጣስ ወይንም መጣሳቸዉ እንዳይታወቅ በማሰብ የሚከፍሉት ክፍያ ከፍተኛ
ይሆናል፡፡ እንዲሁም የኢንቬስትሜንት እድሎችን በመዝጋት፣ አመች የንግድ ከባቢ እንዳይኖር በማድረግ፣ በሙሰኛ
ባለስልጣናት ምክንያት አዳዲስ ያልተጻፉ ደንቦች እና መጓተቶች ይፈጠሩና ንግዱን ክፉኛ የሚጎዱ ይሆናሉ፡፡
ሙስና በከፍተኛ መንግስታዊ ድክመትንና አለመረጋጋትን የሚያመጣባቸዉ መንገዶች ከላይ ያየናቸዉ ሶስት
መሰረታዊ ጉዳዮች ቢሆኑም፤ ከዚሁ ጋር የተያያዘ ሌላዉ የሙስና መዘዝ ጥቂት ስልጣን ያሉ አካላትና የስልጣኑ
ተጠቃሚ የሆኑ ቡድኖች በሙስና ከተዘፈቀች አገር በሙስና የሰበሰቡትን ሃብት በህገ ወጥና ምስጢራዊ በሆነ
መንገድ ወደሌሎች አገሮች ማሻገር ነዉ፡፡ ምስጢራዊ የገንዘብ ፍሰት ማለት ህገወጥ በሆነ መንገድ የተገኘ (በስፋት
ምስጢራዊ የገንዘብ ፍሰትን በአንድ አገር ውስጥ ወይንም ድንበር ዘለል ሊሆን ይችላል፡፡ ድንበር ዘለል ከሆነ ሀብቱ
ከአገራዊ ህግ ተጠያቂነት የራቀና ለማስመለስ ቢሞከር የማይቻል ይሆናል፡፡ በማደግ ላይ ባሉ አገሮች ከምስጢራዊ
ገንዘብ ፍሰት ውጤቶች ዉስጥ ዋናዉ በምስጥር ወደ ውጭ የሚወጣው ሀብት ለነዚህ አገሮች ድጋፍ ከሚመጣው
ገንዘብ ይበልጣል፡፡ እንደዚሁም ድርጊቱ እርዳታ ላይ ጥገኛ በሆኑ ድሀ አገሮች ላይ ስለሚፈፀም በድህነት አሮንቋ
ተዘፍቀዉ እንዲኖሩ ትልቁን ድርሻ ይወስዳል፡፡ በተጨማሪም በመንግስታት የኢኮኖሚያዊና የመልካም አስተዳደር
አፈፃፀም ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ሙስናን የመዋጋት አቅማቸዉን ይሸረሽራል፣ ለዉስጥና ለዉጭ ሃይሎች
እንዲጋለጡ ያደርጋል፡፡
28
እንደ አለም አቀፍ የፋይናንስ ኢንተግሪቲ ሪፖርት (GFI) መሰረት ከ 2005 – 2014 ባሉት አመታት ከኢትዮጵያ
1,259-3,153 ቢሊየን ዶላር) በምስጢር ወደ ውጭ ወጥቷል፡፡ በተጨማሪም አገሪቱ ከ 2000- 2009 11.7 ቢሊዮን
ዶላር አጥታለች፡፡ በ 2009 ብቻ 3.26 ቢሊየን ዶላር ያጣች ሲሆን ይህ በ 2008 አገሪቱ ከዉጭ እርዳታ ካገኘችዉ
829 ሚሊዮን ዶላር የሚበልጥ ነዉ፡፡ ምስጢራዊ የገንዘብ ፍሰት የአገሪቱ የ GDP እድገት 22% እንዲቀንስ
አድርጓል፡፡ ከ 55 እስከ 80% የሚሆነዉ ምስጢራዊ የገንዘብ ዝውውር የመነጨው በሀሰት የውጭ ንግድ ደረሰኝ
ምክንያት ነው፡፡ ይህ በየዓመቱ ወደ ውጭ የሚወጣው የአገሪቱን 11% - 29% የሚሆነውን የንግድ መጠን
የሚሸፍን፣ ከ 40 - 97% ወደ አገሪቱ የሚገባዉን የገንዘብ ድጋፍ የሚያክል፣ ከ 10% - 30% የሚሆነው የኢትዮጵያ
መንግስትን ጥቅል በጀት የሚሸፍን ነዉ (OECD 2016፣ GFI 2017)፡፡ ስለሆነም ሙስና ኢኮኖሚዉን በማራቆት፣
የመንግስትን አቅም በማሽመድመድ አጥፊ ወደሆነ አለመረጋጋትና ብጥብጥ እንድታመራ እንዳደረገ ያሳያል
ትምህርት ሶስት
የመፍትሄ እርምጃዎች
አስከፊ ጉዳት የሚያደርሰዉን የሙስና ወንጀል ለመግታት መወሰድ የሚገባቸዉ እርምጃዎች ምንድን ናቸዉ? ማን
ነው ተጠያቂው?
በሙስና ላይ የሚደረገዉ ጦርነት የእያንዳንዱ ሰዉ ብሄራዊ ግዴታ ነዉ፡፡ በማህበረሰብ ዉስጥ ያለ ሁሉም አባል የጸረ
ሙስናዉ ወታደር መሆን አለበት (Mwai Kibaki) ፡፡ ሙስናን ለመዋጋት a multi-pronged approach የሚጠይቅ
ነዉ፡፡ በአለም አቀፍ፣ በአህጉር፣ በአገር፣ በክልል ደረጃ ችግሩን ለመግታት የሚደረገዉ ጥረት እንዳለ ሆኖ ትግሉን ወደ
የሥነምግባር ትምህርትን በስፋት በመስጠት ሙስናን ሊሸከም የማይችል ዜጋ መፍጠር ፤የሙስና ወንጀልንና
ብልሹ አሰራርን መከላከል ፤ ሙሰኞችን ማጋለጥ ፤ መክሰስና መመርመር ውጤታማነት ማሻሻል፡፡
በመንግስታት መካከል ሙስናን የመዋጋት ቁርጠኝነትንና ትብብርን ለማጠናከር በርካታ አለምአቀፋዊና ከህግ
ታራሚ ድንጋጌዎች ስራ ላይ ውለዋል፡፡ ለምሳሌ የመንግስታቱ ድርጅት የፀረ ሙስና ኮንቬንሽን እና የአፍሪካ የፀረ
29
ሙስና ኮሚሽን በዋነኛነት ይጠቀሳሉ፡፡ የነዚህ ኮንቬንሽኖች ዋነኛ ትኩረቶች፡ ሙስናን አስቀድሞ መከላከል፣
ሙሰኞችን የሚቀጣ ጠንካራ የህግ ማዕቀፍ ማዉጣት፣ የተመዘበረና የተሻገረ ሃብትን ማስመለስና አለአቀፋዊና
አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከር ናቸዉ፡፡ ብዙዎቹ የአፍሪካ አገራት ኢትዮጵን ጨምሮ እነዚህን ኮንቬሽኖች
ነገር ግን አሁንም ድረስ ሙሰኞችን ለፍርድ በማቅረብ የዘረፉትን ሀብት በማስመለስ ረገድ ሰፊ ክፍተቶች አሉ፡፡
በመንግስት እና በሲቪክ ማህበረሰቦች አመራር ውስጥ ሙስናና ብልሹ አሰራርን የመዋጋት ቁርጠኝነት በጋራ
በሚሰሩ የፀረ ሙስና አደረጃጀቶች እየተደገፉ የሙስና ድርጊትን ለመቀነስ ያስችላሉ፡፡ የፖለቲካ ተቋማትና
ፓርቲዎች የበለጠ ተጠያቂነትንና ግልፅነትን የሚጠይቁና የሚፈጽሙ ከሆነ የማህበረሰቡን ሙስናን የመዋጋት
አቅምን ያጠነክራል፡፡ ይህ ማለት የፖለቲካ ሰዎችና ድርጅቶች የፀረ ሙስና አቋማቸው ጠንካራና ለድርድር
የአመራር ቁርጠኝነት ማለት በአንድ አገር ዉስጥ ያሉ አመራሮችና ሰራተኞች ለመንግስቱ ቁልፍ ስትራቴጂዎችና
ፖሊሲዎች (አገራዊ የጸረ ሙስና ትግልን ጨምሮ) ስኬትና ዉጤታማነት ያላቸዉን አፋዊና ተግባራዊ እንቅስቃሴ
ይህ አስትራቴጅ ተቋማት በባለቤትነት መንፈስ የሚያደርጉት ቀጥተኛ ተሳትፎ ነው፡፡ ሙስናን መከላከል የአንድ
ተቋም/የሥራ ክፍል ጉዳይ ሳይሆን የሁሉም አካላት ድርሻ ነው፣ በዚህም ሙስናና ብልሹ አሠራርን ከመከላከል
አንጻር በእያንዳንዱ ተቋም ያለውን ተጨባጭ የሆነ ቁርጠኝነት ማረጋገጥ ይጠይቃል፡፡ ‹‹ሳይቃጠል በቅጠል››
ሙስናን የመዋጋት ስራ ለአንድ ተቋም ብቻ የሚተው ሳይሆን የመንግስትን የሲቪክ ማህበራትንና የዜጎችን
ትብብርና አጋርነት የሚጠይቅ ነው፡፡ መንግስት ህግ በማውጣትና የፀረ ሙስና ተቋም በመፍጠር ላይ ሲያተኮር
የሲቪክ ማህበራት ደግሞ የፀረ ሙስና ዘመቻን በተሻለ በማስፋት፣ በሙስና ላይ ጥናት በማካሄድና አካባቢያዊ የፀረ
ሙስና ልምዶችን ለመንግስት በማጋራት የፖሊሲ መነሻ እንዲሆኑ ሊረዱ ይችላሉ፡፡ ሌላው ዜጋ ደግሞ በግልም ሆነ
30
የፀረ ሙስና ትግሉ የሁሉንም አከላት ርብርብ የሚጠይቅ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በተለይ ፍ/ቤቶችና ሌሎች
የፍትህ ተቋማት፣ ዋና ኦዲተር መ/ቤት፣የህዝብ ቅሬታ ሰሚ ወዘተ ያሉ መ/ቤቶች ይገኙበታል፡፡ እነዚህ አካላት
ሙስናን በመታገል ረገድ ያላቸውን ሚና በውል ተገንዝበው ተልዕኳቸውን በአግባቡ እንዲወጡ አስፈላጊውን
ይህ ማለት ህዝቡ መንግስት ሙስናን ለመከላከል በዘረጋቸው ስርአቶች ውሰጥ ተሳትፎ ማድረግ፣ሁሉም ዜጋ
ደግሞ በግልም ሆነ እንደየ አደረጃጀቱ የሙስና ድርጊትን በማጋለጥና በመጠቆም ድጋፉን ሊገልፅ ይገባል፣የሙስና
ወንጀሎችን መጠቆም፣ ፍርድ ቤት ቀርበው ምስክርነት መስጠት፣ የሙስና ወንጀል የሚፈጽሙትን መኮነን፣ በፀረ
ሙስና ትግሉ ተሳትፈው ውጤት ያመጡትን ማወደስ ከህዝቡ የሚጠበቁ ተግባራት ናቸው፡፡
ነገር ግን በአሁኑ ሰዓት ያለው ነባራዊ ሁኔታ እንደሚያሳየው የሥነ-ምግባርም ሆነ የግብረ-ገብ ትምህርት ቀድሞ
በነበረበት ልክ አይደለም፡፡ በአንድ በኩል የእምነቱ ተቋማት ስነ ምግባር ማጎልበት ሚናቸዉን በአግባቡ እንዳይወጡ
የሚያደርጉ ሁኔታዎች መፈጠር፣ በሌላ በኩል ደግሞ የእምነቱ ተከታዮችን በግብረገብ ትምህርት የማነጽ
ሃላፊነታቸዉን በቃልም በተግባርም እንዳይወጡ አድርጎአቸዋል፡፡ ስለሆነም የእነሱን ሚና ማጎልበት ተገቢ ነዉ፡፡
ሙስናን በመዋጋትና በመግታት ረገድ የግሉ ዘርፍ በተለይም የንግዱ ማህበረሰብ አይነተኛ ሚና ይጫወታሉ፡፡ የግሉን
ዘርፍ ከሙስና ማጽዳት ማለት የመንግስት ሴክተሮች ከሙስና እንዲጸዱ ማድረግ ስለሆነ በዚህ በኩል በያገባኛል
ስሜት ሃላፊነታቸዉ እንዲወጡ ማድረግ ይገባል፡፡ የንግዱ ማ/ሰብ ሙስና እና ብልሹ አሰራር ዋጋ እንደሚያሰከፍል
አውቆ ማንኛወንም የሙስና ወንጀሎች በማጋለጥ፣ በመቆምና በመካላከል ከህግ አስከባሪ አካላት ጋር ብትብብር
እና በቅንጅት መስራት፣ ውድድርን የሚገድብና ሀገርና ህዘብን የሚጎዳ ህገወጥ ንግድ ሲካሄድ ዝም አለማለት
ይገባል፡፡
ዜጎች ሙስና ምንድን ነው? እንዴት ሊከሰት ይችላል? በምን መንገድ መዋጋት ይቻላል? የሚለውን ማወቅ
እስከቻሉ ድረስ ሙስናን የመዋጋት ድርሻቸውን ለመወጣት ወደ ኋላ ሊሉ አይችሉም፡፡ እንደዚሁም ሰዎች በሙስና
ድርጊት መሳተፍን እንዴት ሊያርቁ እንደሚችሉ ተግባራዊ ክህሎት ካዳበሩ ራሳቸዉ በሙስና ድርጊት ባለመሳተፍ፣
31
ሌሎች በሙስና ድርጊት እንዳይሳተፉ በማድረግ ከተሳተፉም ደግሞ በመጠቆም አብዛኛውን የሙስና ድርጊት
መግታት ይቻላል፡፡ በዚህ በኩል ት/ተቋማት፣ የሙያ ማህበራት፣ ብዙሃን መገናኛ ድርጅቶች ስለ ስነ ምግባር
ጠቀሜታ፣ ስለ ሙስና አስከፊ ጉዳት ደጋግመዉ ህዝቡ መረጃ እንዲደርሰዉ ማድረግ ከቻሉ ችግሩን በዘላቂነት
መቅረፍ ይቻላል፡፡
ይህ የእድሜ ክልል ከበሰለ አእምሮ ይልቅ ስሜታዊነት አይሎ የሚገኝበት ወቅት ሲሆን ሁለት ነገሮችን ከፊታቸው
እንዳሉ ማወቅ ተገቢ ነው፡፡ አንዱ አካላዊ እና ቁሳዊ ፍላጎቶች በሚፈጥሩት ስሜት እና ግፊት ፣ጫና እና ጉጉት
ምክንያት የተሳሳተ መንገድ በመምረጥ የወደፊት እድል የሚሰናከልበት ነው፡፡ ሌላው መልካም ነገርን በመጎናጸፍ
ወደ ተሻለ ህይወት የሚወስደውን ትክክለኛ መንገድ መምረጥ ነው፡፡ ስለዚህ ከግብረገብ አንጻር ወጣቶች
በስነ-ምግባርና ሞራል እሴቶች እና ሙስና መከላከል ላይ በሀገሪቱ ያሉ የ 2 ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ የኮሌጆች
በመንግስት ሰራተኛው ዘንድ የሚስተዋሉ ከልክ ያለፈ እራስ ወዳድነት እና ግለኝነት ማስወገድበስራ ላይ የሚታይ
ግዴለሽነት(ምን አገባኝ)፣ በአቋራጭ የመክበር ፍላጎት እና ስስታምነት፣ ሀቀኝነት፣ ታማኝነት እሴቶች መሸራረፍና
በአጭበርባሪነት መተካት፤ከልክ ያለፈ የሃገር ፍቅር መሸርሸር፣ የሕዝብን ጥቅም አለማስቀደም …የመሳሰሉት
ለፌዴራልና ለክልሎች የመንግስት መስሪያ ቤቶች፣ የልማት ድርጅቶች፤ ህዝባዊ ድርጅቶች የስነ-ምግባር መከታተያ
ለክልል ስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አመራርና ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት፤ በመንግስት
መስሪያ ቤቶች ፣ በልማት ድርጅቶች እና በህዝባዊ ድርጅት ለሚሾሙ ተሚዎች ስራ ከመጀመራቸው በፊት
ለኮሚሽኑ አመራርና ሰራተኞች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ስልጠና መስጠት፤ ለሲቪክ ማህበራት አመራሮችና
32
ለሀገራዊ ፍቅር መቀዛቀዝ በዋናነት የሚጠቀሰው የግለኝነት እኩይ በሽታ እየተስፋፋ በመምጣቱ እንደሆነ በየ
መድረኩ ሲነገር ይደመጣል፡፡ የግለኝነትና የስግብግብነት መርዛማ በሽታ መንስኤዎች ዘረኝነት፣ ጎጠኝነትና
አልጠግብ ባይነት በመሆናቸው ሀገራዊ ፍቅር በእጅጉ አንዲቀዘቅዝ እና ሙስና እንዲሰራፋ አድርገዋል ፡፡
ቸ) በ 2013 በጀት ዓመት የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል በዚህም የተለያዩ ውጤቶች ተመዝግበዋል
በሀገር አቀፍ ደረጃ ያሉ የመንግስትና የግል ትምህርት ተቋማት መረጃዎችን መሰብሰብ ፣ ማደራጀት
እና ወቅታዊ ማድረግ፤
ደረጃ ለሚማሩ ተማሪዎች በስነ ምግባርና በሞራል እሴቶች ላይ የተማሪዎች የጥያቄና መልስ
ውድድር ማካሄድ፤
ግንቦት 16/2013 ዓ.ም በሀገር ደረጃ በሁሉም ክልሎች፣ ዞን እና ወረዳ ድረስ በመንግስትና በግል
በአሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚገኙ የ 1 ኛና የ 2 ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና ኮሌጆች ሁለት በመቶ (2%)
33
በሁሉም ክልሎች የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ የመንግስትና የግል ኮሌጆች፣
ክልሎች በትምህርት ቤት የሥነ-ምግባር ክበባት ዙሪያ የተሻሉ ምርጥ ተሞክሮ ሊሆኑ የሚችሉ
ክልሎች የመንግስትና የግል አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ያሳተፈ የተማሪዎች የሥነ-ምግባርና
ሞራል እሴቶች ግንባታ ላይ የጥያቄና መልስ ውድድር እንዲያካሂዱ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ፤
በሁሉም የአንደኛ ደረጃና የ 2 ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና ኮሌጆች ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀንን
የስነ ምግባርና ሞራል እሴቶች ግንባታ እና የሙስና መከላከል መልዕክቶችን በተለያዩ ማህበራዊ
በየሩብ ዓመቱ የሀገሪቱን የፀረ ሙስና ትግል እንቅስቃሴ የሚያሳዩ መረጃዎችንና የአፈፃፀም
በስነ ምግባርና ሞራል እሴቶች ግንባታና በሙስና መከላከል ስራ እንቅስቃሴ ላይ በየሳምንቱ በሀገሪቱ
በስነ ምግባርና ሞራል እሴቶች ግንባታ እና ሙስና መከላከል ዙሪያ በአማረኛና በእንግሊዘኛ
34
በስነ ምግባርና ሞራል እሴቶች እና ሙስና መከላከል ዙሪያ 74 ቃለ ምልልስ፣ ፕረስ ሪሊዝ፣ ፕሬስ
ኮንፍረስ ማዘጋጀት፤
በስነ ምግባርና ሞራል እሴቶች እና ሙስና መከላከል ዙሪያ 115 ስነ ምግባር መፅሔት፣ ዜና
በስነ ምግባርና ሞራል እሴቶች ግንባታ እና ሙስና መከላከል ዙሪያ የተዘጋጁትን ወቅታዊ የሆኑ
አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን በዓልን የድርጊት መርሀ ግብር በማዘጋጀት በሀገር አቀፍ ደረጃ በዓሉ
እንዲከበር ማድረግ፤
ለሚዲያ አመራሮችና ባለሙያዎች በስነ ምግባርና ሞራል እሴቶች ግንባታና ሙስና መከላከል ላይ
ስልጠና መስጠት፤
እና በክልል የመንግስት ተቋማት እና የልማት ድርጅቶች 4667 የስነ ምግባር መከታተያ ክፍሎች
ሁሉም ክልሎች ከክልል እስከ ወረዳ ተቋማቶች ድረስ ባለ የመንግስት መዋቅር የሥነ-ምግባር
ሰራተኞች ስራ ከመጀመራቸው በፊት የስነ ምግባርና ሞራል እሴቶችና ሙስና መከላከል ስልጠና
ለሁሉም የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍሎች የበጀት ዓመት መነሻ ዕቅድ ማዘጋጀትና የእቅድ
የአሰራር ስርዓት ጥናት በማካሄድ የማሻሻያ ሀሳቦችን እንዲተገበር ክትትልና ድጋፍ ማድረግ፤
35
በተቋማት ስነ-ምግባር መከታተያ ክፍሎች በተቋሞቻቸው የአስቸኳይ ሙስና መከላከል እንዲሰሩ
ተችሏል፡፡
የተመዘገበን የሀብት ምዝገባ መረጃ ለተደራሽነት ዝግጁ ማደረግና መረጃውን ለመረጃ ጠያቂዎች
ተደራሽ ማድረግ፤
ሀብት አስመዝጋቢዎች መረጃ ላይ የመረጃ ትክክለኛነት ማረጋገጥ ተገቢ የህግ እርምጃ እንዲወሰድ
ማድረግ፤
አስቸኳይየሙስናመከላከልማለትበተቋማትውስጥሙስናለመፈፀምየሚያስችልዝግጅትእየተደረገመሆኑንሲጠረጠር
ወይምጥቆማሲደርስድርጊቱከመፈፀሙበፊትአስቸኳይየሙስናመከላከልስራበመስራትሂደቱእንዲቋረጥወይምአስፈ
ላጊውንየማስተካከያእርምጃእንዲወሰድየማድረግተግባርነው፡፡
36
የመንግሥትንና የህዝብ ሀብት ለመመዝበር፣ ለማጭበርበር፣ ለመስረቅ፣ ለመዝረፍ በሀሳብ ደረጃ የተጠነሰሰ ወይም
በአሠራር ደረጃ የተዘጋጀ የጥፋት አቅምን በማምከን ሙስናን የወንጀል ድርጊት ከመሆኑ በፊት ወይም አስቀድሞ
አመላካች ነገሮች ሲኖሩ ለአስቸኳይ ሙስና ለመከላከል የሚያስችል የጥቆማ መቀበያ ዘዴን መዘርጋት
ተገቢ በመሆኑ፣
ሙስና ለመፈፅም የታቀደውን ድርጊት በማምከን የሙስና መከላከል ስራን ውጤታማ ማድረግ
ስለሚያስፈልግ፣
በአስቸኳይ የሙስና መከላከል ተግባር ሙስና ለመፈፀም ሃስብ የሌላቸው ግን በእውቀት እና በልምድ
ማነስ ወደ ስህተት የሚገቡ አመራሮችንና ሰራተኞችን እንዲሁም የመወሰን ስልጣን የተሰጣቸውን አካላት
በመሆኑ፣
ሆነ ብለው ሙስና የመፈፀም ሃስብ ያላቸው አካሎች ድርጊቱን ከመፈፀማቸው እና የህዝብ ሃብት
ከመዝረፋቸው በፊት ማስቀረት፤
ሙስና የመፈፀም ዝግጅት እንዴት እየተደረገ እንደሆነ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በማወቅ ለስነምግባር
ግንባታ እና ለስልጠና ግብአት እንዲሆን ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፤
ስለሆነም የሥነምግባርና የፀረ ሙስና መከታተያ ክፍሎች በተቋም ውስጥ አስቸኳይ የሙስና መከላከል ተግባርን
የጥቆማ መቀበያ ሣጥኖችን በተቋሙ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች እንዲቀመጥ ማድረግ፡፡ የጥቆማ ሣጥኑ
በቀላሉ ከቦታው የማይነሰና ጠንካራ የመቆለፊያ ቁልፍ ያለው ቢሆን ይመረጣል፡፡ የጥቆማ መቀበያ ሳጥኑ
ለሥነምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ክፍል ብቻ አገልግሎት የሚሰጥና ቢያንስ በቀን አንድ ጊዜ ሣጥኑ
በአካል ቀርበው ጥቆማ ለሚሰጡ አቅራቢዎች ወይም የሙስና ጥቆማ ለመቀበል የተመቻቸ ሊሆን ይገባል፡፡
ጥቆማ አቅራቢዎች ሳይሸማቀቁ ነፃነት ተሰምቷቸው የሙስና መከላከል ጥቆማዎችን ለብቻቸው ሆነው
37
ለመቀበል የጥቆማ የማቅረቢያ ቅጽ በማዘጋጀትና የጥቆማው ቀን፣ ጥቆማው የቀረባበት ዋና ጉዳይ፣
ሙስናን ለመፈጸም እንቅስቃሴ እየተደረገ ያለው የሥራ ክፍል፣ እንደአስፈላጊነቱ የጠቋሚው ስም ያየዘ
በተቋም ደረጃ የሚቻል ከሆነ ነፃ የጥቆማ መቀበያ የስልክ አገልግሎት ማመቻቸትና ማስተዋወቅ ካልሆነ
ደግሞ ጠቋሚዎች ጥቆማዎች ለማቅረብ የሚያስችለውን የስልክ አገልግሎት ቁጥር በተቋም ውስጥ
በሚታዩ ቦታዎች ላይ ሙስና ከተጠያቀችሁ በዚህ የስልክ ቁጥር መጠቆም ትችላለችሁ የሚሉ
መልዕክቶችን በመለጠፍ በግልጽ ማስታዋወቅ፡፡ የቀረበውን ጥቆማ ከላይ በተገለጸ መሠረት የጥቆማው
የቀረባበትን ቀን፣ ጥቆማ የቀረበባትን ጉዳይ ጭብጥ ወዘተ.. በአግባቡ መዝግቦ መያዝ ፡፡
የሙስና መከላከል ጥቆማዎችን በፖስታ ቤት ወይም በፋስክ ለመቀበል የፖስታ ቤቱንና የፋስክ ቁጥር
ለጠቋሚዎች ግልጽ በሆነ ቦታ ላይ ማስቀመጥ፣ በምን አግባብ ጥቆማ ማቅረብ እንደሚችሉ ማስተዋወቅና
o የአመራር ቁርጠኝነት
በየደረጃዉ የሚገኙ የተቋማት አመራሮች ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን የመከላከል ተግባራትን ማከናወን
የስራቸዉ ዋነኛ አካል መሆን አለበት፡፡ በመሆኑም ለሚከናወኑት የአስቸኳይ ሙስና መከላከል ስራ አስፈላጊዉን
ድጋፍ ማድረግ አለባቸዉ፡፡ ከዚህ አንጻር በስነምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ሥራ ክፍሎች ለሚቀርቡት የአስቸኳይ
ሙስና መከላከል ስራዎች ጋር በተያያዘ ጥያቄዎች በአፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ድርጊቱ እንዲቆም ማድረግ፣ የስራ
ክፍሎች የተለያዩ ማስረጃዎች ሲጠየቁ እንዲሰጡ ማድረግና የሚሰጡ ዉሳኔዎችን ተግባራዊ ማድረግ
ይጠበቅባቸዋል፡፡
የአሰራር ስርአት ጥናት
የአሰራር ስርአት ጥናት በአንድ ተቋም ውስጥ ሙስናና ብልሹ አሰራር ተከስተው ከፍተኛ ጉዳት
ከማድረሳቸው በፊት ለችግሩ ክፍተት የሚፈጥሩ ሁኔታዎችን መርምሮ በማውጣት የመፍትሄ ሃሳቦችን
በማቅረብ ችግሮች ከወዲሁ እንዲቀረፉ ለማድረግ የሚያስችል ጥናት በመሆኑ ሙስና ተከስቶ ወይም
የተባባሰ ደረጃ ላይ ደርሶ ሊፈጠር የሚችለውን ኪሳራ በማስወገድ ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ ግልጽ የሆነ የአሰራር ስርአት በመዘርጋት የሚፈጠሩ የሙስናና ብልሹ አሰራር ችግሮች በቀላሉ
ውስጥ የአሰራር ስርዓት ጥናትእንዲያካሂዱ ማድረግ የተሻለ አማራጭ ነው፡፡ የሥነምግባርና የጸረሙስና
38
መከታተያ ክፍሎች ለሙስና እና ብልሹ አሠራር የሚያጋልጡ አሰራሮችን በመለየት ሙስናን ለመከላከል
ሥራዎችን ማስፋፋት
በሀገሪቱ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በራሳቸው አቅም የጥናትና ምርምር
ስራ እንዲሰሩ ማድረግ፤
በተቋማት ለሙስና እና ብልሹ አሰራር ተጋላጭ የሆኑ ተግባር ተኮር 48 የአሰራር ስርዓት ጥናቶችን
ለተለዩ የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች በኮሚሽኑ ዓመታዊ መነሻ ዕቅድ ላይ የዕቅድ ኦረንቴሽን
ለሀይማኖት ተቋማት የስነ ምግባርና ሞራል እሴቶች ግንባታን መሰረት ባደረገ መልኩ የኮሚሽኑን
ዓመታዊ ዕቅድ እና የሀይማኖት ተቋማት መነሻ ዕቅድ ላይ ኦረንቴሽን መስጠት፣ ዓመታዊ ዕቅድ
በስነ ምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ላይ ወቅታዊ በሆኑ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ከሀይማኖት ተቋማት
በስነ ምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ላይ ወቅታዊ በሆኑ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ከሲቪክ ማህበረሰብ
39
የማቋቋሚያ አዋጅ 1236/2013 በህዝብ ተወካዮች በማስፀደቅ ወደ ስራ የተገባ ሲሆን ይህን አዋጅ
ከአዋጅ እስከ አፈፃፀም መመሪያ ድረስ አስፀድቀው ወደ ስራ እንዲገቡ ድጋፍና ክትትል ማድረግ ፤
ክልሎች በዞን፣በወረዳና በከተማ መስተዳደር ደረጃ የሥነ-ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን መምሪያ
ድጋፍ ማድረግ፤
የክልል የሥነ-ምግባርና መከታተያ ክፍሎች ለተቋም ሰራተኞችና አመራሮች የአቅም ግንባታ ስልጠና
5.4. ክልሎች ዓለም አቀፍ የጸረ ሙስና ቀንን በሁሉም የመንግስት ተቋማት የልማት ድርጅትና ህዝባዊ ድርጅቶች
ከክልል እስከ ቀበሌ ድረስ በደመቀ ሁኔታ በተለያዩ ዝግጅቶች እንዲያከብሩ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ፤
40