Professional Documents
Culture Documents
Company Name: Document No.
Company Name: Document No.
ማውጫ
1. መግቢያ...................................................................................................................................................2
2. የአቅም ግንባታ ሥራዎች..............................................................................................................................5
2.1 ስልጠና፣..........................................................................................................................................5
2.2 ተሞከሮዎች ቅመራ፣............................................................................................................................5
2.3 የአሰራርስርዓት፣.................................................................................................................................5
2.4 ማኑዋሎችና የሕግ ማዕቀፍ ዝግጅት......................................................................................................5
3. የዓበይት ተግባራት የ 12 ወር ዕቅድ አፈጻጸም፤...................................................................................................6
3.1 የፕሮጀክቶች ዝርዝር የ 12 ወር አፈጻጸም ሪፖርት.......................................................................................7
4. የማዕከሉ ተቋማዊ ለውጥዕቅድ አፈጻጸም፤.......................................................................................................14
4.1 የወርክ ፋሲሊቴሽ (የ 1 ለ 5 ውይይት)...................................................................................................14
4.2 ካይዘንና ትግበራው፣/ Kaisen Training /..........................................................................................14
4.3 የሴቶች ጉዳይና ተሳትፎ.....................................................................................................................14
የአፕሬይዛልና ሪስክ ማኔጅመንት ዕቅድ አፈፃፀም...................................................................................................15
5. ያጋጠሙ ችግሮች፣ የተወሰዱ የመፍትሄ እርምጃዎችና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ፤.......................................................15
5.1 ያጋጠሙ ችግሮች.............................................................................................................................15
5.1.1 የቢሮ መገልገያ ዕቃዎች ማሟላት.............................................................................................................15
5.1.2 የሰዉ ሐይል ማሟላት...................................................................................................................15
5.2 የተወሰዱ የመፍትሄ እርምጃዎች...........................................................................................................17
6. በአባሪገፅ፡..............................................................................................................................................18
7. ማጠቃለያ፤.............................................................................................................................................18
1
በኢ.ኮ.ሥ.ኮ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከል የ 2010 በጀት አመት የ 12 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
1. መግቢያ
በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ዋና መሥሪያ ቤት የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከል
ለዋና ሥራ አስፈፃሚ ተጠሪ በመሆን በአዲስ መልክ በመደራጀት ቀደም ሲል ያልነበሩ አዳዲስ ተግባራት እና
ኃላፊነቶች ማለትም የፕሮጀክት ማኔጅመንት አገልግሎት፣የፕሮጀክት አፕሬይዛልና ምህንድስና፣ የፕሮጀክት ክትትልና ድጋፍ
እንዲሁም ፐርፎርማንስ ማኔጅመንት፣ ኮንትራት ፎርሙሌሽን እና ሪስክ ማኔጅመንት ኃለፊነቶችን እንዲወጣ ሀላፊነት
ተሰጥቶታል፡፡ ማዕከሉ እራሱን የቻለ አደረጃጀት ያለው ሆኖ በ 2010 በጀት ዓመት ስራ እንዲጀምር ተደርጓል፡፡ ይህ
ማዕከል በቀጣይ ኮርፖሬሽኑ የሚገነባቸውን እንዲሁም በሌሎች አካላት የሚገነቡ የግንባታ ፕሮጀክቶችን የባለቤትነት ድርሻ
ውል (ኮንትራት) እየወሰደ ያስተዳድራል፤ የፕሮጀክት አመራር አገልግሎት ይሰጣል፡፡
ሥለሆነም በቀጣይ በዚህ ማዕከልአማካኝነት እየተከናወነ ያለዉን አፈፃፀም በላቀ ደረጃ በማሳደግ ለኮርፖሬሽኑ አጠቃላይ
ኢኮኖሚያዊ እድገት ከፍተኛ ሚና መጫወት የሚጠበቅበት ሲሆን፤ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከሉም ይህንኑ
በመገንዘብ ተልእኮውን በብቃት ለመወጣት የሚያስችለው አደረጃጀት በመፍጠር፤ የ 12 ወር ዕቅድ ስራዎችን ማከናወኑ
ይታወቃል፡፡
በ 2010 በጀት ዓመት ማዕከሉ ዋና ዋና ግቦችን እና ዝርዝር ተግባራትን ያካተተ ዕቅድ እና ክንዉኖችን እንዲሁም በማዕከሉ
ስር በተደራጀው የፕሮጀክት ማኔጅመንት አገልግሎት በኩል በባለቤትነት ተረክቦ የሚያስተዳድራቸዉን መንግስታዊ
ፕሮጀክቶችን አፈጻጸም ሪፖርት ያዘጋጀ ሲሆን፤ የዕቅድ አፈፃፀም መርሃ-ግብሩም በዚሁ መሠረት በዝርዝር ቀርቧል፡፡ ይህ
ሪፖርት የበጀት ዓመቱን የ 12 ወርዕቅድ አፈፃፀም የሚያሳይ ነው፡፡
2
በኢ.ኮ.ሥ.ኮ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከል የ 2010 በጀት አመት የ 12 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
በዚህም መሰረት በኮርፖሬሽኑ ሥር የሚገኘው የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከልና በሥሩ በሚገኙት መምሪያዎች እና
ቡድኖች የሚከናወኑ ሥራዎችን በመደበኛዕቅድክለሳ መሰረት የ 12 ወር የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርቧል፡፡ ስለሆነም
በዕቅዱ ከተያዙት የግንባታ ፕሮጀክቶች ዉስጥ፡
ሀ). ከተለያዩ መንግስታዊ ተቋማት ጋር የፕሮጀክት ማኔጅመንት አገልግሎት ውል ስምምነት ተመስርቶባቸው እየተከናወኑ
ከሚገኙ መንግስታዊ ፕሮጀክቶች መካከል፡-
በጥቅሉ በ 12 ወር ግዜ ዉስጥ በዕቅዱ ከተያዙት ተግባራት መከካል የተከናወኑቱ በሪፖርቱ ውስጥ እንዲካተቱ
ተደርጓል፡፡
3
በኢ.ኮ.ሥ.ኮ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከል የ 2010 በጀት አመት የ 12 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
4
በኢ.ኮ.ሥ.ኮ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከል የ 2010 በጀት አመት የ 12 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
የፕሮጀክቶቹን ዲዛይንና ግንባታ ስራ ለማከናወን ይቻል ዘንድ፤ የዲዛይንና supervision ስራው አሸናፊ
ድርጅት (ዮሐንስ አባይ አማካሪ አርኪቴክቶችና መሐንዲሶች ድርጅት) ስራውን ከየካቲት ወር
5
በኢ.ኮ.ሥ.ኮ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከል የ 2010 በጀት አመት የ 12 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
2010 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት በ 6 ወራት ጊዜ ውስጥ እንዲያጠናቅቅ በታሰረው ውል መሰረት የዲዛይን
ስራው የተጀመረ ሲሆን ከዚህ ቀደም የመጀመሪያው/inception report/ ተጠናቆ ቀጣዩ የ/Schematic
Design Report/ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ይህም ሪፖርት በማዕከሉ ባለሙያዎች ተገምግሞና ተተችቶ
አስፈላጊው ግብረ መልስ ለአማካሪ ድርጅቱ በተሠጠው መሠረት በአሁኑ ወቅት ሪፖርቱ ተስተካክሎ
የተመለሰ ሲሆን ይህንኑም ተከትሎ በተደረገው የጋራ ውይይት መሰረት ቀጣይ የዲዛይን ሥራውን
ለማጠናቀቅ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
3.1.2 የፐብሊክ ሰርቪስ ሰራተኞች ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት ዋና መ/ቤት ህንጻ የአዋጭነት ጥናት፡
በኮርፖሬሽኑና በጠቅላይ ሚ/ር ጽ/ቤት መካከል በተፈረመው የግንባታ ውል ስምምነት መሰረት የቦታ
ርክክቡ ቢፈጸምም ፕሮጀክቱ የሚከናወነው ከፍተኛ የሆነ የጸጥታ ቁጥጥር በሚደረግበት አካባቢ
ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በፕሮጀከቱ ባለቤት በኩል አንዳንድ ሁኔታዎች እስኪሟሉ ድረስ አጥር ከማጠርና
በአንዱ ህንጻ ላይ ስራዎችን ከማከናወን በዘለለ አሁንም ድረስ መሰረታዊ በሆነ መልኩ ፕሮጀክቱን
በሙሉ ኃይል ለመጀመር ያልተቻለበት ሁኔታ እንዳለ ይታያል፡፡
ሥለሆነም እስካሁን ድረስ ሊከናወኑ ከሚገባቸው የስራ ክፍሎች ማለትም (Office Building,
Waiting Area, Parking Building, Guard Post, Inspection, Check Point, Fence, Site
Sanitary, Site Electrical, Civil Work) መካከል በሙሉ ሀይል መጀመር የተቻለው የዋናውን ህንጻ
ብቻ ሲሆን ይህም ህንጻ በአሁኑ ወቅት የመሰረት ስራው (Substructure work) እየተጠናቀቀ ይገኛል፡፡
6
በኢ.ኮ.ሥ.ኮ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከል የ 2010 በጀት አመት የ 12 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
በጨረታው ላይም 7/ሰባት/ አለም አቀፍ ድርጅቶች ሰነድ ማስገባታቸው ተከትሎ የቴክኒክ ሰነድ
ግምገማው ተከናውኗል፡፡ ከቴክኒክ ግምገማ ውጤቱ ለመገንዘብ እንደተቻለውም 3 ድርጅቶች ብቻ
ዝቅተኛ የቴክኒክ ምዘና መስፈርቱን አሟልተው ወደ ቀጣዩ ዙር ውድድር አልፈዋል፡፡ ይህም ውጤት
ለሁሉም ተወዳዳሪዎች በጽሁፍ ተገልጿል፡፡ ይህንኑም ተከትሎ 2 ድርጅቶች በተሰጣቸው ውጤት ላይ
ቅሬታ እንዳላቸው በመግለጽ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡ በዚህም መሰረት ለ 2 ቱም
ድርጅቶች በቂ ማብራሪያ በጽሁፍ ተዘጋጅቶ እንዲደርሳቸው ተደርጓል፡፡
3.1.5 በጠቅላይ ሚ/ር ጽ/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ እየተከናወነ የሚገኘው የባስኬት ቦልና የሜዳ ቴኒስ
መጫወቻ ሜዳ ግንባታ፡
7
በኢ.ኮ.ሥ.ኮ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከል የ 2010 በጀት አመት የ 12 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
በተለይም ሁለት አማካሪ ድርጅቶች ያቀረቡት የፋይናንስ ሰነድ በግልጽ ዋጋቸውን ለመገምገም እጅግ
አሻሚና አስቸጋሪ ሆኖ በመገኘቱና ከጨረታ ውድድር ውጪ ለማድረግም የህግ አግባብ ባለመኖሩ
ምክንያት ውድድሩን ማጠናቀቅ አልተቻለም፡፡
ሥለሆነም ይህንኑ በመገንዘብ የቴክኒክ ኮሚቴው የጨረታ ሂደቱ ውድቅ ተደርጎ ጨረታው በድጋሚ
ይወጣ ዘንድ ለምህንድስና ጉዳዮች ጨረታ አጽዳቂ ኮሚቴው ባቀረበው የውሳኔ ሀሳብ መሰረት
ጨረታው ተሰርዞ ድጋሚ ሌላ ጨረታ እንዲወጣ በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት የጨረታ ሰነዱና
ማስታወቂያው ተዘጋጅቶ ለኮርፖሬት ግዢና ንብረት አስተዳደር ዋና መምሪያ ተልኳል፡፡ ሥለሆነም
ጨረታው እደተሸጠና ከተጫራቾች ለሚቀርቡ ማብራሪያዎች መልስ እየተሠጠ ይገኛል፡፡
ለስራው የሚያስፈልገው ዲዛይንና የስራ ዝርዝር በህንፃ ቴክኖሎጂና ኮንስትራክሽን ዘርፍ በኩል
ተከናውኖ ቀርቧል፡፡ ይህንኑም ተከትሎ ለስራው የሚያስፈልገው የዋጋ ዝርዝር በዘርፉ በኩል ተዘጋጅቶ
የቀረበ ሲሆን የቀረበውን ዋጋም በማእከሉ ባለሙያዎች አማካኝነት በመገምገምና ከወቅቱ የገበያ ዋጋ
አንጻር የዋጋ ማስተካከያ ሊደረግባቸው ይገባል ተብለው በተለዩ የስራ አይነቶች ላይ ተገቢው የዋጋ
ማስተካከያ ተደርጎና ከስምምነት ላይ ተደርሶየመጨረሻ ውሳኔ ይሰጥበት ዘንድ ለሚመለከተው አካል
ተላልፏል፡፡
8
በኢ.ኮ.ሥ.ኮ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከል የ 2010 በጀት አመት የ 12 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
ለዚህ ግንባታ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ ግንባታ ሥራውን ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ በአሁኑ ወቅት
ግንባታው ከውሃና ከመጸዳጃ አገልግሎት ውጪ ያሉት ስራዎች በሙሉ መሰረታዊ ሊባል በሚችል ደረጃ
የተጠናቀቁ ስለሆነ ፕሮጀክቱን በከፊል በመረከብ ህንጻዎቹን ለአገልግሎት ማዋል ተችሏል፡፡
የህንጻው የሴፕቲክ ታንክ ግንባታ ስራም በአሁኑ ወቅት በተወሰነ ደረጃ ተጀምሯል፡፡
በዚህ አመት የኮርፖሬት ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና ዳታ ቤዝ ልማት መምሪያ የዳታ ሴንተር ዲዛይን
እንዲሰራለት ለማእከሉ ባቀረበው ጥያቄ መሰረት ፍላጎቱን በማጥናት በማዕከሉ ሥር በሚገኘው
የፕሮጀክት አፕሬይዛልና ምህንድስና መምሪያ፣የምህንድስና እና ኮንትራት ፎርሙሌሽን ቡድን የዳታ
ሴንተር ዲዛይንና የግንባታ ዝርዝር ስራ ከዋጋ ትመና አገልግሎት ጋር ሙሉ በሙሉ በማከናወን የጥናት
ሰነዱን ፍላጎቱን ላቀረበው መምሪያ መላክ ተችሏል፡፡ በመምሪያው በኩል ግንባታው እንዲ ጀመር
ውሳኔ ሲሰጥ የዋጋ ድርድር ተደርጎ ውል የሚታሰር ይሆናል፡፡
3.1.13. የ 5 የግድብ አስተዳደርማዕከላትሕንፃ ሰነድን በተመለከተ
9
በኢ.ኮ.ሥ.ኮ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከል የ 2010 በጀት አመት የ 12 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
በ 2010 የበጀት አመት የ 5 የግድብ አስተዳደደር ማዕከላት ለመገንበት በታቀደው እቅድ መሰረት የሰነድ
ዝግጅቱ ተጠናቅቋል፡፡ የሕንፃ ቴክኖሎጂና ኮንስትራክሽን ዘርፍ የመስሪያ ዋጋውን እንዲያቀርብ ተደርጎ
የቀረበው ዋጋም በባለሙያዎች ተገምግሞ ተቀባይነትን አግኝቷል፡፡
ይህንኑም መሰረት በማድረግ ቀጣይ ውል ከመታሰሩ በፊትበግድብና መስኖ ኮ/ፕ/ፕ/ማ ዘርፍ፡ የግድብ
ኦፕሬሽን ጥገናና የተፋሰስ ሪሃብሌሽን መምሪያ የአስተዳደደር ማዕከላቱ የዲዛይን ይዘትካለው ፍላጎት
ጋር ስለ መጣጣሙና ለግንባታው በቂ በጀት ስለመያዙ ማረጋገጫ እንዲሰጥ በጽሁፍ ተጠይቋል፡፡
ሥለሆነም ይህ ሂደት ሲጠናቀቅ ውል ታስሮ ግንባታው የሚጀመር ይሆናል፡፡
የ 12 ወር ገቢ የማሰባሰብ ስራዎች
ኮርፖሬሽኑለኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሙያዊ አገልግሎት እንዲሰጥ በሁለቱ ተቋማት መካከል የጋራ
መግባባት ላይ ተደርሶ ለጊዜው በሁለት ፕሮጀክቶችላይ ስራ መጀመሩ ይታወቃል፡፡
በዚህም መሰረት የመጀመሪያው ፕሮጀክት ለሆነው ለሴካ እርሻ የግድብ ግንባታ ወጪ ግምት ሙያዊ
አገልግሎት ለመስጠት በኮርፖሬሽኑ በኩል ለአገልግሎቱ ከተጠየቀው ጠቅላላ ብር 502,632.31 ውስጥ
ለጊዜው የመጀመሪያ ዙር ክፍያ ብር 251,316.10 (ሁለት መቶ ሀምሳ አንድ ሺህ ሦስት መቶ አስራ
ስድስት ሺህ ብር ከ 10 ሳንቲም) በኮርፖሬሽኑ ሂሳብ ቁጥር ገቢ ስለመደረጉ መረጃ መገኘቱን ተከትሎ
ለስራው ባለሙያዎችን ወደ ፕሮጀክቱ በመላክ በፕሮጀክቱ አስፈላጊውን የልኬት ሥራ /as-built
reading / መውሰድ ተችሏል፡፡ በመሆኑ ይሄው የተጠናቆ የመጀመሪያ ሪፖርት / Draft
report /ተዘጋጅቷል፡፡ ይሄው ይበልጥ ተገምግሞና ዳብሮ ለባንኩ በቅርቡ የሚላክ ይሆናል፡፡
በተመሳሳይ መልኩም ባንኩ በአንድ አልሚ የቀረበለትን አንድ የአለም አቀፍ የጨረታ ሰነድ
(የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት) በኮርፖሬሽኑ በኩል እንዲገመገምለት በጠየቀው መሰረትኮርፖሬሽኑ
ለአገልግሎቱ የጠየቀው ገንዘብ ብር 83,211.70 (ሰማኒያ ሶስት ሺ ሁለት መቶ አስራ አንድ ብር ከ 70
ሳንቲም) በኮርፖሬሽኑ የሂሳብ ቁጥር ገቢ ስለመደረጉ መረጃ በመገኘቱ ምክንያት ስራውን በማከናወን
ውጤቱ ለኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሪፖርት ተደርጓል፡፡
10
በኢ.ኮ.ሥ.ኮ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከል የ 2010 በጀት አመት የ 12 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
የኢፌድሪ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የአርባ ምንጭ ፈጥኖ ደራሽ መንገድ ስራ ፕሮጀክት፡
የፌዴራል ፖሊስ በአርባምንጭ ከተማ የ 1.154 ኪ.ሜ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ለማከናወን በስራ
ተቋራጮች የቀረበለትን ዋጋ ተገቢነት ኮርፖሬሽኑ እንዲገመግምለት በጠየቀው ሙያዊ ትብብር መሰረት
አስፈላጊው ሙያዊ ድጋፍና ትብብር በሙሉእጅግ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተደርጎለታል፡፡
የኢ.ፌ.ድ.ሪ. የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በአይሲቲ ፓርክ እያከናወነ ለሚገኘው የዋና
መ/ቤቱ ህንጻ የፕሮጀክት ማኔጅመንት አገልግሎት ለማግኘት ባቀረበው ጥያቄ መነሻነት ወርሃዊ
የአገልግሎት ክፍያችንን በጽሁፍ አሳውቀናል፡፡ ሥለሆነም ከሚ/ር መ/ቤቱ ጋር በወርሃዊ የአገልግሎት
ክፍያው ተመን ላይ ከስምምነት ከተደረሰ በቀጣይ አገልግሎቱ የሚሰጥ ይሆናል፡፡
ከላይ ለመግለጽ እንደተሞከረው ማዕከሉ ለሚሰጠው ሙያዊ አገልግሎት ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ገቢ
ከተደረገለት ጠቅላላ ገንዘብ ብር 334,527.8 (ሶስት መቶ ሰላሳ አራት ሺህ አምስት መቶ ሀያ ሰባት
ብር ከ 80 ሳንቲም) በተጨማሪ ለተለያዩ መንግስታዊ ተቋማት ከተሰጠ የፕሮጀክት ማኔጅመንት
አገልግሎት ማለትም ፡-
11
በኢ.ኮ.ሥ.ኮ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከል የ 2010 በጀት አመት የ 12 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
ማዕከሉ እንደ አዲስ በመደራጀት ላይያለ እንደመሆኑ መጠን በስሩ ለሚደራጁት የስራ ክፍሎች የሰዉ
ሐይል፤የቢሮዎች እና የቢሮ መገልገያ እቃዎች ፍላጎት በ 2011 ዕቅድ ለበጀት ዓመቱ ደረጃ በደረጃ
ለማሟላት ዝግጅቱ ተጠናቆ ለሚመለከታቸው ክፍሎች ሪፖርት ተደርጓል፡፡
የካይዘንን ፍልስፍና በመተግበር በስራ ላይ ውጤታማ ከመሆን አንጻር በተለይምየስራ ቦታን ለሰራተኞች
ምቹ ከማድረግ አንጻር በጥቅሉ አበረታች ሊባሉ የሚችሉ ስራዎች በዚህም ግዜ ውስጥ ተሰርተዋል፡፡
በአጠቃላይ ከፕሮጀክት አፈጻጸምና ትግበራ አኳያ በዋናነት የስጋትና ሪስክ ተጋላጭ የሆኑት ጉዳዮች
ከፕሮጀክት መተግበሪያ ጊዜ (Project Schedule)፤ከስራ ደህንነት (Project Safety) ከፕሮጀክት ስኮፕ
(Project Scope)እና ፕሮጀክት ዋጋ(Project Cost) እንዲሁም ውጫዊ ሁኔታዎች (External factors)ጋር
የተያያዙት ጉዳዮች ሊሆኑ እንደሚችሉ ታሳቢ በማድረግ በእነዚህ ጉዳዮች ላይ “ Focused” ሆኖ
በጥልቀት ለመስራት ጥረት ተደርጓል፡፡
12
በኢ.ኮ.ሥ.ኮ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከል የ 2010 በጀት አመት የ 12 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
በበጀት ዓመቱ በማዕከሉ ስር ለተመደቡ አዳዲስ ባለሙያዎች የሚሆን የቢሮ መገልገያ እቃዎችን ደረጃ
በደረጃ በግዥ ለመሟላት ጥረት የተደረገ መሆኑ ባይካድም በተለይም ለማዕከሉ ስራ እጅግ አንገብጋቢ
ከሆኑት የቢሮ መገልገያ እቃዎች መካከል እንደ ዴስክ
ቶፕኮምፒውተር፣ላፕቶፕ፣ፕሪንተር፣ፕሮጀክተር፣ፎቶኮፒ ማሽንና የተለያዩ ጠረዼዛዎችና
ወንበሮችንአሁንም ድረስ በቂ በሆነ ደረጃ ለማሟላት አልተቻለም፡፡ይህም በመሆኑ ምክንያት በጥቅሉ
በማዕከሉ የስራ እንቅስቃሴ ላይ ጫናን ፈጥሯል፡፡
ይህን ችግር ለማስተካካል በማቀድም የማቴሪያልና አገልግሎት ፍላጎት ክፍተቱን በመለየት በ 2011
በጀት ዓመት እቅድ ውስጥ ምላሽ እንዲያገኝ ጥያቄውን ከወዲሁ ለሚመለከተው የስራ ክፍል
ለማቅረብ ተሞክሯል፡፡
13
በኢ.ኮ.ሥ.ኮ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከል የ 2010 በጀት አመት የ 12 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
ከዚህም በተጨማሪ በፕሮጀክት ባለቤት መ/ቤቶች አካባቢ ከሚነሳ የፍላጎት መለዋወጥ ጋር ተያይዞ
ፕሮጀክቶችን አስቀድሞ በተያዘላቸው እቅድ መሰረት ለማከናወን አስቸጋሪ የሆነበት ሁኔታም ይታያል፡፡
14
በኢ.ኮ.ሥ.ኮ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከል የ 2010 በጀት አመት የ 12 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
በዚህም መሰረት የኮርፖሽኑን የዳታ ሴንተር ግንባታ ለማከናወን የሚያስችል ዝርዝርና የተሟላ ዲዛይን
እንዲሁም “Specification & Bill of quantities” የተዘጋጀ ስለሆነ ቀጣይ የትግበራ ውሳኔን ተከትሎ
ለትግበራ ምዕራፉ ዝግጁ የማድረግ ስራ በዕቅድ ተይዟል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ መለስተኛ መሰብሰቢያ አዳራሽና ወላድ እናት ሰራተኞች በስራ ላይ በሚሆኑበት
ጊዜ ህጻናቶቻቸውን የሚያቆዩበት ጊዜያዊ ማረፊያ ሕንጻ በዋና መ/ቤታችን ቅጥር ጊቢ ውስጥ
ለመገንባት የሚያስችል የዲዛይንና የስራ ዝርዝር በማዘጋጀት ለቀጣይ ትግበራ ዝግጁ ለማድረግ
አንዳንድ ቅድመ ዝግጅቶች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡
በተመሳሳይ መልኩም የሞጆ ማሰልጠኛ ማዕከሉን ግንባታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ትኩረት
ተሰጥቶት የሚሰራ ይሆናል፡፡
የህዝብ ተወካዮች ምክር-ቤት ህንጻ ግንባታ ሂደትንም የማስጀመር ስራው ትኩረት ተሰጥቶት
የሚከናወን ይሆናል፡፡
ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጋር በተያያዘም የቀረውን የአንድ ፕሮጀክት ውጤት በማጠናቀቅ ለባንኩ
ሪፖርት ለማድረግ ጥረት የሚደረግ ይሆናል፤ በተመሳሳይ መልኩም ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክና
ለኢ.ፌ.ድ.ሪ. የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በተሰጠው የፋይናንሺያል ፕሮፖዛል ላይ
በጎ ምላሽ ከተገኘ ይህንንም ስራ በፍጥነት ለመጀመር ተገቢው ዝግጅት ተደርጓል፡፡
6. አባሪ ገፅ፡
የማዕከሉ የ 12 ወር የአፈጻጸም ውጤት፤
የመደበኛ ሥራዎች ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ማቅረቢያ ቅፅ ተያይዟል፡፡
15
በኢ.ኮ.ሥ.ኮ የፕሮጀክት ዴቨሎፕመንት ማዕከል የ 2010 በጀት አመት የ 12 ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት
7. ማጠቃለያ፤
በማዕከሉ በኩል በ 2010 የበጀት አመት ዕቅድ ውስጥ የተያዙት የመንግስታዊ የግንባታ ፕሮጀክቶች ከላይ
በዝርዝር የተቀመጡት ናቸዉ፡፡ ይሁን እንጂ ፍላጎትን መሰረት በማድረግ ወደ ፊት ወደ ማዕከሉ
በሚመጡት ተጨማሪ ፕሮጀክቶች መሰረት አፈፃፀሙ እያደገ የሚሔድ እንደሆነ ይታመናል፡፡
ሥለሆነም በጥቅሉ ባለፉት 12 ወራት ጊዜ ውስጥ በማዕከሉ በኩል በመደበኛነት ሊከናወኑ የታቀዱ ዋና
ዋና ስራዎች የፕሮጀክቶቹን የኮንትራት አስተዳደር ስራዎችን መስራት፤ የዲዛይንና የግንባታ ነባራዊ
መረጃ የማሰባሰብ እንዱሁም የፕሮጀክቶቹን የፕሮጀክት ማኔጅመንት 2011 በጀት ዓመት ዝርዝር
መርሃ ግብር ዕቅድ መሰረትና ከዚህ በፊት የታዩትን ክፍተቶች በማስወገድ መፈጸምና የፕሮጀክት
አፕሬይዛል ስራዎችን ማከናወን ሲሆን ይህም ተስፋ ሰጪ በሆነ መልኩ የሚከናወን ይሆናል፡፡
16