Download as pdf or txt
Download as pdf or txt
You are on page 1of 159

የብልጽግና ፓርቲ

የአሥር ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅድ


(ከ2015 - 2024 ዓ.ም)

ሰኔ 2014 ዓ.ም
ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት
አዲስ አበባ
ማውጫ

ምዕራፍ አንድ፡ መንደርደሪያ ............................................ 4


1.1. መግቢያ ................................................... 4
1.2. የብልፅግና ፓርቲ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ አስፈላጊነት (Rationale) ............ 6
1.3. የፖሊሲ ክለሳና ለውጥ (Policy Review) ......................... 7
ምእራፍ ሁለት፡- የዕቅዱ መነሻዎች ...................................... 11
2.1. ፖለቲካ ፓርቲዎችና ስትራቴጂክ እቅድ............................... 11
2.1.1. ፖለቲካና የፖለቲካ ፓርቲ ምንነት .............................. 11
2.1.2. የፖለቲካ ፓርቲዎች ስትራቴጂክ እቅድ ............................ 13
2.2. በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሁኔታ ............................... 15
2.2.1. የፖለቲካ ፓርቲዎች ታሪክ በኢትዮጵያ ............................ 15
2.2.2. የተፎካካሪ ፓርቲዎች ወቅታዊ ሁኔታ ............................ 18
2.3. የኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ታሪክ ........................... 19
2.4. ሀገራዊ የህግና የፖሊሲ ማዕቀፎች ................................. 21
2.5. የ10 አመት የመንግስት የልማት እቅድ .............................. 22
2.6. ቀጠናዊና አለም አቀፋዊ ሁኔታዎች ................................. 24
2.7. ሀገራዊ ለውጥና የብልፅግና ፓርቲ ዉልደት ........................... 27
2.8. የብልፅግና ፓርቲ ሁኔታ ........................................ 30
2.8.1. የብልፅግና ፕሮግራምና መተዳደሪያ ደንብ ......................... 30
2.8.2. የአመራርና አባላት ሁኔታ .................................... 32
2.8.3. የብልፅግና ፓርቲ አንደኛ ጉባዔ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ............... 33
2.9. የስድስተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ እንድምታዎች ........................... 35
ምዕራፍ ሦስት፡- የብልፅግና ፓርቲ ርዕይ፣ ተልዕኮ፣ እሴቶችና መርሆዎች .............. 37
3.1. የብልጽግና ፓርቲ ርዕይ (Vision) ............................... 37
3.2. የብልፅግና ፓርቲ ተልዕኮ (Mission) ............................. 37
3.3. የብልፅግና ፓርቲ ሀላፊነት (Mandate) እና መዋቅር ................... 37
3.4. የብልፅግና ፓርቲ እሴቶች (Core Values) ......................... 40
3.5. የብልፅግና ፓርቲ መርሆዎች (principles) ........................ 42
3.6. የብልፅግና ፓርቲ መዋቅር (structure) .......................... 42
3.7. የብልፅግና ፓርቲ መዋቅራዊ ቻርት ................................ 44
ምዕራፍ አራት፡- የተቋማዊና ዉጫዊ ሁኔታና የባለድርሻ አካላት ትንተና .............. 45
4.1. የተቋማዊና ዉጫዊ ሁኔታ ትንተና ................................. 45
4.1.1. ውስጣዊ ጥንካሬና ድክመት .................................. 45
4.1.2. ውጫዊ እድሎችና ስጋቶች ................................... 47
4.2. የተገልጋይና ባለድርሻ አካላት ትንተና................................ 54
ምዕራፍ አምስት፡- ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች፣ ስትራቴጂያዊ ግቦችና እይታዎች ............ 61
5.1. ስትራቴጂያዊ ጉዳዮችና ግቦች .................................... 61
5.2. እይታዎች ................................................. 71
ምዕራፍ ስድስት፡ የውጤት አመላካቾችና መለኪያዎች .......................... 87
ምዕራፍ ሰባት፡ ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች .................................. 97
ምዕራፍ ስምንት፡ ስትራቴጂን ወደፈጻሚ ማውረድ (cascading) ............... 119
ምዕራፍ ዘጠኝ፡- የክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ ሥርዓት እና ታሳቢዎች ............... 121
9.1. የክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ ሥርዓት ............................... 121
9.2. የዕቅዱ ታሳቢዎች ........................................... 122
ዋቢዎች ...................................................... 123
ሰንጠረዦች
Table 1 ተቋማዊ ውስጣዊ ሁኔታ 50
Table 2 ዉጫዊ ሁኔታ 52
Table 3 የተገልጋዮችና ባለድርሻ አካላት ፍላጎትን መለየት 55
Table 4 የተገልጋዮችና የባለድርሻ አካላት ቁልፍ ፍላጎቶች ትንተና 58
Table 5 እይታዎና ተቋማዊ ስትራቴጂዎች ግቦች 72
Table 6 ስትራቴጂያዊ ግቦች ትንተና 75
Table 7 ስትራቴጂያ ግቦች፣ መለኪያዎችና ኢላማዎች 87

3
ምዕራፍ አንድ፡ መንደርደሪያ

1.1. መግቢያ

ኢትዮጵያ ረጅም የመንግሥት ታሪክ ካላቸዉ ጥቂት የዓለማችን ሀገሮች አንዷ ነች። ዘመናዊ

መንግሥት ከመሠረተች ጀምሮ የተለያዩ ፈተናዎች ቢገጥሟትም ሉዓላዊነቷን አስከብራ ቅኝ ገዥዎችን

በማንበርከክ ጭምር ለጥቁር ህዝቦች የነፃነት ተምሳሌትና ኩራት ሆና ዘልቃለች። ኢትዮጵያ በመልክዓ

ምድራዊ አቀማመጧ፤ በህዝብ ብዛቷ፤ ለግብርና ስራ ባላት ምቹነትና በእምቅ የተፈጥሮ ሀብቷ

በዓለምም ሆነ በአፍሪካ ቀንድ ልዩ ስፍራ የሚሰጣት ሀገር ነች። በዲፕሎማሲው መስክም ሊግ ኦፍ

ኔሽንንና የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን ከመሰረቱ ሀገራት ውስጥ አንዷ ከመሆኗም በላይ ዛሬም

ድረስ የተለያዩ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ተቋማት መቀመጫና የዲፕሎማሲ ማዕከል በመሆን

እያገለገለች ትገኛለች።

ይሁን እንጂ ለረጅም ጊዜ የተካሄዱ ጦርነቶችና ኋላቀር የመንግሥት አስተዳደር ሥርዓቶች ህዝቦቿን

ለጉስቁልና፣ ሀገሪቱንም ለቁልቁለት ጉዞ ዳርገዋት ቆይተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ያጋጠሙ ግጭቶችና

መከራዎች ስሪታቸው ፖለቲካዊ ነው፡፡ ጤናማና ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ስርዓት ባለመገንባቱ እስከ

አሁን ድረስ የዘለቀ ፖለቲካዊ አለመረጋጋትና ቀውስ እያስተናገደች ትገኛለች፡፡ ከዚህም ሌላ ለረጅም

ጊዜ በዘለቀው አፄአዊና ወታደራዊ አገዛዝ ምክንያት የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ሽታ ሳይኖር ረጅም

ዘመን አሳልፋለች፡፡

በአንድ የፖለቲካ ሥርዓት ግንባታ ውስጥ ፖለቲካ ፓርቲዎች ራሳቸውን ባልጠበቁትና እጅግ

ውስብስብ ነባራዊ ሁኔታ ውስጥ ማለፍና መውደቅ የተለመደ እውነታ ነው፡፡ ነባራዊ ወቅታዊ

ሁኔታውን ማስተናገድ ያቃታቸው ፓርቲዎች ሲከስሙ፣ አዲሱ ሲመጣ፣ አዲሱ በተራው አሮጌ ሆኖ

በሌላኛው ሲተካ ማየት የለውጥ ተፈጥሯዊ ሂደትና ክስተት ነው፡፡

የብልፅግና ፓርቲ ምስረታ ለዘመናት ያልተመለሱ የህዝብ ጥያቄዎችን ለመመለስ የሚያስችል እድል

መፍጠር ብቻ ሳይሆን ተጨባጭ ውጤቶችንም እያስመዘገበ ይገኛል፡፡ በኢትዮጵያ እውነተኛ ህብረ-

ብሔራዊ ፌደራላዊ ስርዓት ለመዘርጋት መሰረት የጣለ ፓርቲም ነው፡፡ የዴሞክራሲ ምህዳሩን

4
ለማስፋት የተወሰዱ እርምጃዎች በሀገራችን ለዘመናት የቆየውን የጠላት-ወዳጅ ፍረጃ እና የጥላቻና

የመጠላለፍ ፖለቲካ አስወግዶ አዲስ የዴሞክራሲ ባህልን ለመገንባት መሰረት የጣለ ነው፡፡ ከተቋማት

ግንባታ አንፃርም ህያው የሆኑ መንግስታዊ አገልግሎት ሰጪ መዋቅሮችን የመፍጠርና ያሉት

ተቋማትም ከሶስተኛ ወገን ጫና ተላቀው የተሰጣቸውን ተልዕኮ በብቃት የሚፈፅሙበትን ሁኔታ

ተመቻችቷል፡፡ መዋቅራዊ የሆኑ የኢኮኖሚ ችግሮችን ለመፍታትና ማህበራዊ መዛነፎችን ለማስተካከል

የተወሰዱ እርምጃዎችም የማይናቅ ውጤት የተገኘባቸው ናቸው፡፡

ብልፅግና ፓርቲ እስካሁን ያስመዘገባቸውን ስኬቶች ጠብቆና አጠናክሮ ለመዝለቅ፤ እንዲሁም የረጅም

ጊዜ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊና የውጪ ግንኙነት ፕሮግራሞቹን ለማሳካት የሚያስችለውን

ይህን የ10 አመት የፓርቲ ስትራቴጂክ እቅድ አዘጋጅቷል፡፡

የስትራቴጂክ ማኔጂመንት ምሁሩ ጆን ብራይሰን ስትራቴጂክ እቅድን ሲያብራራ በእውቀትና በስርዓት

ላይ ተመስርቶ የአንድን ተቋም ምንነት፣ ምን እንደሚሰራና እንዴት እንደሚሰራ መሰረታዊ ብያኔ

ለመስጠትና ለመተግበር የሚደረግ ጥረት ነው ይለዋል፡፡1 ፒተርሰን በበኩሉ አንድ ተቋም የራሱን

ወቅታዊ ሁኔታ፣ አካባቢያዊ የወደፊት ሁኔታዎችን የሚፈትሽበትና ከዚህ ተነስቶ የተቀናጀ የአፈፃፀም

ስልት፣ ፖሊሲና ስርዓት የሚያበጅበት በእውቀት ላይ የተመሰረተ ሂደት ነው ብሎታል፡፡2 ላቻፔሌ

ባሰፈረው ፅሁፍም ስትራቴጂክ እቅድ ከእለታዊ የድርጊት መርሃ ግብሮች በዘለለ ስለአንድ

ድርጅት/ተቋም ማንነት፣ ምን ላይ መድረስ እንደሚፈልግና በምን መልኩ ካሰበው እንደሚደርስ

በግልፅ ለማወቅ የሚያስችል ግልፀኝነትን ይፈጥራል ይላል፡፡3

በዚሁ መሰረት የዚህ ስትራቴጂክ እቅድ አላማ ብልፅግና ፓርቲ ከራዕይ፣ ተልዕኮውና እሴቶቹ

በመነሳት በ10 ዓመት ምን ላይ እንደሚደርስ መበየንና ይህንኑ ለማሳካት ስትራቴጂክ አቅጣጫዎችን

በስትራቴጂያዊ ዕቅድ ማመላከት ነው፡፡

1
Bryson, John M. and Alston, Farnum K., (2011). Creating your Strategic Plan, Third Edition.
2
Peterson, M.W. 1980. ‘Analyzing Alternative Approaches to Planning’. Improving Academic
Management. San Francisco: Jossey-Bass Publishers. p. 114.
3
Lachapelle, P.R., McCool, S.F., & Patterson, M.E. (2003). Barriers to Effective Natural Resource Planning
in a “Messy” World. Society and Natural Resources, 16, 473-490.
5
ስትራቴጂክ እቅዱ በስምንት ምዕራፎች ተደራጅቷል፡፡ የመጀመሪያው ምዕራፍ የመነሻ ሁኔታዎችን

ይተነትናል፡፡ በዚህ ምዕራፍ ስር ለስትራቴጂክ እቅዱ መነሻ የሆኑ ሀገራዊ፣ ቀጠናዊና አለም አቀፋዊ

ነባራዊ ሁኔታዎችና ታሪካዊ ዳራዎች ተተንትነዋል፡፡ ምዕራፍ ሁለት የዕቅዱን ርዕይና ተልዕኮ

ያስቀምጣል፡፡ በተጨማሪም የብልፅግና መገለጫ የሆኑትን እሴቶችና መርሆዎችን ይዘረዝራል፡፡

የፓርቲው መዋቅርም በስዕላዊ መግለጫ ተደግፎ ቀርቧል፡፡ ምዕራፍ ሶስት የብልፅግና ፓርቲ

ተቋማዊ ውስጣዊና ውጫዊ ሁኔታዎች እንዲሁም የባለድርሻ አካላት ሁኔታ በዝርዝር የተተነተነበት

ክፍል ነው፡፡ ለሁኔታዎች ትንተና የጥንካሬ፣ ድክመት፣ እድሎችና ስጋቶች ትንተና (SWOT) እና

የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ፣ ቴክኖሎጂ፣ አካባቢያዊና ህጋዊ ሁኔታዎች ትንተና (PESTEL)

ሞዴሎች በጋራ ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡

የስትራቴጂክ እቅዱ ማዕከል የሆኑት ስትራቴጂያዊ ጉዳዮችና ስትራቴጂያዊ ግቦች በምዕራፍ አራት

ተቀምጠዋል፡፡ በዚሁ ስር ያሉት እይታዎች የግቦቹን ይዘትና ወሰን እንዲሁም የሚጠበቁ ውጤቶችን

ያብራራሉ፡፡ የእነዚህ ውጤቶች አመላካቾችና መለኪያዎች በቀጣዩ ምዕራፍ ላይ በሰንጠረዥ ተደግፈው

ቀርበዋል፡፡ ምዕራፍ ስድስት በእቅዱ ዘመኑ የሚወሰዱ ስትራቴጂያዊ እርምጃዎች የተዘረዘሩበት ነው፡

፡ እነዚህ እርምጃዎች በተቋሙ የአፈጻጸም መነሻ እና በተቀረጹት ዒላማዎች መካከል ያለውን ክፍተት

ለመሙላት የሚቀረጹ አስቻይ ፕሮግራሞችን፣ ፕሮጀክቶችንና ዋና ዋና ተግባራትን ይዘዋል፡፡

ምዕራፍ ሰባት ስትራቴጂውን በየደረጃው ላሉ ፈፃሚ አካላት በማውረድ ሂደቱ ታሳቢ ሊደረጉ የሚገባቸውን

አቅጣጫዎችና የአሰራር መርሆዎች አስቀምጧል፡፡ የመጨረሻው ምዕራፍ የስትራቴጂክ እቅዱን የክትትል፣

ድጋፍና ግምገማ ስርዓቱንና የእቅዱን ታሳቢዎች አመላክቷል፡፡

1.2. የብልፅግና ፓርቲ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ አስፈላጊነት (Rationale)

ፖለቲካ ፓርቲዎች ማህበረሰባዊ ፍላጎቶችን ማሟላትና ዴሞክራሲያዊ ሽግግሮች በስኬት መፈፀም

የሚችሉት ዘላቂና መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ፣ ተደራሽ እና የረጅም ጊዜ አላማዎች ያሉት

ስትራቴጂክ እቅድ ቀርፀው መተግበር ሲችሉ ነው፡፡ ስኬቶቻቸውን ጠብቀውና አጠናክረው ለረጅም

ጊዜ ለመዝለቅ እንዲችሉ፣ መድረስ የሚፈልጉበትን ግብ እና ይህንኑ እንዴት እንደሚያሳኩት

ለተገልጋይና ባለድርሻዎች በግልፅ ማሳወቅ ይጠበቅባቸዋል፡፡

6
ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት ሁለት አመታት አመታዊ እቅዶችን በማውጣትና እንደየአስፈላጊነቱም

በመከለስ ሀገርና ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራትን ሲያከናውን ቢቆይም የረጅም ጊዜ ስትራቴጂክ

እቅድ አልነበረውም፡፡ በፓርቲው እሳቤዎች፣ በመሰረታዊ ባህሪዎቹና በመዳረሻዎቹ ላይ በተለያዩ

መልኮችና ወቅቶች ሰነዶች የተዘጋጁና ስልጠናም የተሰጠባቸው ቢሆንም በሚለኩ ስትራቴጂያዊ

ግቦች የተሰፈሩ እና በተወሰነ የጊዜ ገደብ ውስጥ የሚተገበሩ ዝርዝር ተግባሮች ያላቸው አይደሉም፡

፡ በሌላ በኩል በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የኢፌዴሪ መንግስትም የ10 አመት የልማት እቅድ

አውጥቶ በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡ በመሆኑም በአንድ ገፅታው የፓርቲ ተቋማዊ መዋቅሩን

ለማጎልበት በሌላ በኩል ለሚመራው መንግስት ብቃት ያለው ፖለቲካዊ አመራር ለመስጠት

የሚያስችለውን ስትራቴጂያዊ እቅድ መንደፍ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

በዚሁ መሰረት ፓርቲው ከራዕይ፣ ተልዕኮውና እሴቶቹ በመነሳት በ10 ዓመት ምን ላይ እንደሚደርስ

የሚበይንና ይህንኑ ለማሳካት ምን አይነት ስትራቴጂክ አቅጣጫዎችን እንደሚከተል የሚያመለክት

የረጅም ጊዜ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊና የውጪ ግንኙነት ፕሮግራሞቹን ለማሳካት

የሚያስችለውን የ10 አመት የፓርቲ ስትራቴጂክ እቅድ አዘጋጅቷል፡፡

1.3. የፖሊሲ ክለሳና ለውጥ (Policy Review)

ጊዜ ያለፈባቸው ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ከአዳዲስ ሀገራዊ ህጎችና ደንቦች ጋር እንዲሁም አዲስ

ከሚፈጠሩ ቴክኖሎጂዎችና የአሰራር ስርዓቶች ጋር ተጣጥሞ ያለመሄድ ችግር ያጋጥማቸዋል፡፡ ይህ

ብቻ ሳይሆን ተቋምን አደጋ ውስጥ የሚጥሉበት ሁኔታም ይፈጠራል፡፡ፖሊሲን መከለስ ወይም

መቀየር ከፖለቲካ ስርዓት ለውጥ ጋር ብቻ የሚተሳሰር አይደለም፡፡ በተረጋጋ የፖለቲካና የኢኮኖሚ

ስርዓት ውስጥ ሆኖም አዝማሚያዎችን በመገምገምና ወደፊት ሊያጋጥሙ የሚችሉ አደጋዎችን

አስቀድሞ ለመቀልበስ ሲባልም ይፈፀማል፡፡ ስለሆነም በየጊዜውና በመደበኛነት ፖሊሲን መከለስና

መቀየር ይመከራል፡፡4 ይህ እንዳለ ሆኖ አመታዊ የፖሊሲ ግምገማዎች እና መሰረታዊ የሚባሉ

4
Power DMS, Why it is important to review policies and procedures? December 22, 2020.

7
የተቋም የሽግግር ወቅቶች ፖሊሲን በመቀየር ወይም በመከለስ ራስን ለማደስና የትኩረትና የስራ

ስምሪት አቅጣጫን ከወቅቱ ጋር ለማስተካከል እንደ መልካም አጋጣሚ ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡5

የብልፅግና ፓርቲ ምስረታ በፊት በነበሩት የአስተሳሰብ፣ የአሰራርና የአተገባበር ፖሊሲዎችና

አቅጣጫዎች ላይ መሰረታዊ ለውጦችን አስከትሏል፡፡ ከዚህ አንፃር ቀድሞ የሚነሳው የመደመር

እሳቤ ሀገራዊ ለውጡ የሚመራበት ፍኖተ ካርታ ሆኖ መምጣቱ ነው፡፡ የመደመር ዕሳቤ ከመበታተን

ወደ መሰባሰብ የሚወስድ፣ የጋራ የሆኑትን ዕሴቶች የሚያጎለብት፣ ሀገረ መንግስቱ የማይነቃነቅ

መሰረት እንዲኖረው የሚያደርግ፣ በአጠቃላይም የትስስር ትርክቶችንን እያጠነከረ የሚሄድ እና

መቀራረብን፣ መመካከርን፣ መረዳዳትን፣ አብሮ መፍትሔ መፈለግን ለማላመድ መንገድ የሚከፍት

ዕሳቤ ነው።6

የመደመር ፍኖተ ካርታ ይዞት የመጣው አንዱ መሰረታዊ የፖሊሲ ለውጥ ፕራግማቲክ እይታ ነው፡

፡ በፕራግማቲክ ፖለቲካ ተአማኒነትን የሚያገኝ ማንኛው የፖለቲካ አማራጭ ሁሌም በተግባር

የተፈተነ፣ ተጨባጭና የተረጋገጠ ውጤታማነት ያለው መሆን ይጠበቅበታል። በመሆኑም ብልፅግና

ለአንድ የፖለቲካ እይታ እስረኛ በመሆን በሌላው የመፍትሄ አማራጭ የሚቀርቡ አካሄዶችን

ካለመቀበል የረጅም ጊዜ የፖለቲካ ባህል ራሱን በማራቅ ታማኝነቱ ሊያሳካው ለሚያልመው

የፖለቲካ-ኢኮሚያዊ ግብ እንጂ ለርዕዮት ዓለም እንዳይሆን አድርጓል። የመደመር ፕራግማቲዝም

የትኩረት ነጥብ እንደሀገር የምናልማቸውንና ልናሳካቸው የምንጓጓላቸው የጋራ የብልጽግና ራዕዮች

እንጂ ውስን የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ወይም የፖሊሲ አማራጮች አይደሉም።

ሌላው መሰረታዊ ለውጥ የተካሄደበት የፓርቲ ፖሊሲ የዴሞክራሲ እና የኢኮኖሚ ስርዓቱን

የተመለከተው ነው፡፡ ብልፅግና የሚከተለው የዴሞክራሲ አቅጣጫ ትብብርና ድርድር ላይ

የተመሠረተ፣ ለብዙሃነትና ህብረ ብሔራዊነት የተለየ ቦታ የሚሰጥ ኮንሶንሰሽናል ዴሞክራሲ

(Consonsational Democracy) ነው፡፡ የሚገነባው የኢኮኖሚ ሥርዓት ደግሞ በገበያ

የሚመራ ነገር ግን የዜጐችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ማዕከል ያደረገ የመንግሥት ጣልቃ ገብነትን

5
Kimberly D. Gray, (2018) The Importance of Reviewing Policies and Procedures: Resourcing Edge.
6
ወቅታዊ ሁኔታችንን መሻገሪያ ትልሞች፤ የስልጠና ማንዋል፤ ነሀሴ 2012 ዓ.ም
8
የሚፈቅድ የኘሮግረሲቭ ካፒታሊዝም (progressive capitalism) ስርዓት ነው፡፡ የፖለቲካ

ስርዓቱ በህገ መንግስቱ ላይ የተመለከተውን እውነተኛ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ሊያሳካ የሚችል

ሲሆን የኢኮኖሚ ስርዓቱ ደሃ ተኮር የሆኑ ፖሊሲዎችን በመንደፍ ዕድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ

የሚያስችል ነው፡፡ በእነዚህ የፖሊሲ ማሻሻያዎቹ ብልፅግና በፖለቲካም ሆነ በኢኮኖሚ ስርዓቱ

ከርእዮተ ዓለም ጽንፈኝነት ርቆ ማዕከላዊውን መንገድ እንደተከለ ማስቀመጥ ይቻላል፡፡7

በሀገራችን ከ1950ዎቹ ጀምሮ የሐሳብ ልዩነትን በቀና ወይም ሰላማዊ መንገድ አለማስተናገድ፣ በሐሳብ

የተለየን ሁሉ እንደ ጠላት ወይም የጠላት አጋር አድርጎ መሳል አብሮን የኖረ ነው ማለት ይቻላል። አማካይ

መንገድን መያዝ እንደ ወላዋይነትና አቋም የለሽነት ሲፈረጅ የኖረ ነው። ይህ የሐሳብ ልዩነትን ያለማስተናገድ

ባህል በፖለቲከኞቹ አማካኝነት በአጠቃላይ በሀገራችን የፖለቲካ ባህል ላይ አሻራውን በማሳረፉ ምክንያት፣

የፅንፈኝነት ዝንባሌ በወጣቶቹ ልቦና ሳይቀር እየሰረፀ መጥቷል። ብልፅግና ፓርቲ ይህን ታሪካዊ እውነታ

በመረዳት በሀገራችን የመጀመሪያው የመሐል ፖለቲካ አራማጅ ሆኖ መጥቷል። ሀገራዊ ማንነትንና የብሔር

ማንነትን አጣጥሞ የሚሄድና ልዩነቶችን በመደማመጥና በመመካከር ለመፍታት ዝግጁ የሆነ አዲስ የፖሊሲ

አቅጣጫን ተከትሏል፡፡ የእኔ ሐሳብ ብቻ ልክ ነው፤ የሌላው በሙሉ ሀገር አጥፊ ነው ከሚል የፅንፈኝነት

አዝማሚያ ወጥቶ፣ በንግግርና በምክክር የፖለቲካ ችግሮቻችንን የሚያስታርቅ መንገድን ተከትሏል።

ብልፅግና ይዞት የመጣው የፖሊሲ ለውጥና የዚሁ የመሃል ፖለቲካ መገለጫ የሆነው ሌላው ጉዳይ

ከዋልታ ረገጥነትና ከብሔር ፅንፈኝነት የተላቀቀ መንገድን መከተሉ ነው፡፡ ፅንፍ በመያዝና በግትርነት

የሚገለጥ ዋልታ ረገጥነትና የብሔር ፅንፈኝት ሁለንተናዊ ብልፅግናን እውን ለማድረግ፣ እውነተኛ

ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በሀገራችን ለመገንባት እና ብሔር ብሔረሰቦች በእኩልነት የሚከበሩባት ኅብረ

ብሔራዊ የሆነች ኢትዮጵያ ለመፍጠር የሚደረገውን ጥረት የሚያደናቅፍ አካሄድ ነው። ስለሆነም

ብልፅግና ከዚህ የፖለቲካ ባህል ለመውጣት ጎራ የለሽ የልኬት ዕይታን የሚያዳብር፣ ነገሮችን

ለመረዳት የፈጠርናቸው የተቃርኖ ምድቦች አስተሳሰባችንን እንዳይቀፈድዱት የሚያደርግ መሰረታዊ

7
ርእዮት-ዓለሞች እና አንድምታቸው፤ የስልጠና ማንዋል፤ ህዳር 2012

9
የሆነ የአስተሳሰብ ሽግግር ማድረግ እና በውይይትና ክርክር ባህላችን መካከል ሚዛን መጠበቅን

እንደ መፍትሔ አስቀምጧል።8

8
ወቅታዊ ሁኔታችንን መሻገሪያ ትልሞች፤ የስልጠና ማንዋል፤ ነሀሴ 2012 ዓ.ም
10
ምእራፍ ሁለት፡- የዕቅዱ መነሻዎች

2.1. ፖለቲካ ፓርቲዎችና ስትራቴጂክ እቅድ

2.1.1. ፖለቲካና የፖለቲካ ፓርቲ ምንነት

ሃሮልድ ላስዌል ፖለቲካን “ማን፣ ምን፣ መቼና እንዴት አገኘ?” የሚል ትርጉም ይሰጠዋል፡፡ በዚህ

ትርጓሜና በሌሎች ፀሃፊዎች ብያኔ መሰረት ፖለቲካ ቁሳዊና ቁሳዊ ያልሆነ ሃብትን ለማከፋፈል

የሚደረግ ፉክክር ነው፡፡ የአንድን ወገን የሃብት፣ የደረጃ ወይም የሃይል ሚዛን ለማሳደግ በግለሰቦችና

በቡድኖች ደረጃ ውሳኔዎችን ከማሳለፍ ጋር ይተሳሰራል፡፡ በሰዎች ወይም በቡድኖች መካከል የሃይል

ሚዛንን ለማስጠበቅ ወይም ለማጎልበት የሚደረግ ትግልና ይህንኑ ለማሳካት ደጋፊዎችን በጎን

የማሰለፍም ሂደት ነው ፖለቲካ፡፡ ሰፋ ብሎ ሲተረጎም ደግሞ ሰዎች በጋራ ለመኖር የሚወስኗቸውን፣

የሚያሻሽሏቸውንና የሚያከብሯቸውን አጠቃላይ ህጎች ይመለከታል፡፡ ከአንድ ሀገር ወይም የተወሰነ

አካባቢ አስተዳደር ጋር ተያይዞ ባሉ ጉዳዮች ዙሪያ በተለያዩ ሃይሎች መካከል የሚደረጉ ክርክሮችና

ውይይቶችንም ይመለከታል፡፡ የመንግስትን ስልጣን የያዙ ግለሰቦች እንቅስቃሴም በጥቅሉ ፖለቲካ

ነው፡፡ ፖለቲካ ከድርጊቶች ባለፈ አንድ አካል መንግስት ምንና እንዴት ሊሰራ እንደሚገባው

የሚይዘውን ግንዛቤና የሚሰጠውን አስተያየትም ያካትታል፡፡

ሳርቶሪ ስለ ፖለቲካ ፓርቲዎች ምንነት ሲያብራራ ፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ሂደት አካል የሆኑና

በመደበኛ መርሃ ግብር ለስልጣን ተፎካካሪ እጩዎችን የሚያቀርቡ በህግ እውቅና የተሰጣቸው

የፖለቲካ ቡድን ናቸው ይላቸዋል፡፡9 ፖለቲካ ፓርቲዎች የሚቋቋሙት በምርጫ ተወዳድረው

ለማሸነፍ፣ መንግስት ለመምራት እና በሀገራዊ ፖሊሲዎች ላይ ተፅዕኖ ለማሳረፍ በሚደራጁ ከሞላ

ጎደል ተመሳሳይ የፖለቲካ አስተሳሰብና እምነት ባላቸው ግለሰቦች ነው፡፡

በብዙ ፀሃፍት እንደሚታመነው ፖለቲካ ፓርቲዎችና የዴሞክራሲ አይነተኛ መገለጫ ሆኖ የሚወሰደው

ምርጫ ሊነጣጠሉ የማይችሉ ብቻ ሳይሆኑ የፖለቲካ ስርዓት ጤንነት የሚመዘንባቸው መስፈርቶችም

9
Institute of Developing Economies: Japan External Trade Organization (JETRO), (n.d) Hazama Yasushi.
Political Parties and Elections: Minimal conditions for democracy.
11
ሆነው ያገለግላሉ፡፡ በፅኑ መሰረት ላይ የተገነባ ዴሞክራሲ (consolidated democracy)

ሰፍኗል የሚባለው በእጩዎች ህዝባዊ ተቀባይነት ወይም በመራጮች ልዩ ፍላጎት ላይ ተመስርቶ

በሚካሄድ ምርጫ ሳይሆን ምርጫው ፖለቲካ ፓርቲዎች ለውድድር በሚያቀርቡት ሃሳብና ፖሊሲ

ላይ ተመስርቶ እውነተኛ ውድድር መካሄድ ሲችል ነው፡፡10

የፖለቲካ ፓርቲዎች ለዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ያላቸው ሚና ግን በምርጫ ወቅት ብቻ የሚገለፅ

አይደለም፡፡ ዜጎች የፖሊሲ አማራጮች ቀርበውላቸውና መክረውባቸው የሚበጃቸውን የሚወስኑትና

በዚህም መንግስታዊ አስተዳደርን የመምራት መብትና ብቃታቸውን የሚያረጋግጡት በፓርቲዎች

በመወከል ነው፡፡ ዜጎች በራሳቸውና በጋራ የሀገራቸው ጉዳዮች ላይ በግልፅና በፍትሃዊ መንገድ

የሚወያዩበትና የሚወስኑበት ሁኔታ መኖር ለዴሞክራሲ ባህል ማበብ መሰረት ነው፡፡ ተሳትፎ

ተቋማዊ መልክ ወይም አደረጃጀት ከሌለው ግን ውጤት አልባና ትርምስ ከመሆን አልፎ በብዙዎች

ድካም የጥቂቶችን ጥቅም ብቻ የሚያረጋግጥ መሆኑ አይቀርም፡፡ ስለሆነም የዜጎችና ቡድኖች

የመደራደር፣ የመደራጀት የመሰባሰብ፣ ወዘተ… ተሳትፎ በአግባቡና በውጤታማነት ሊፈፀም

የሚችለው በፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ በሚኖራቸው ተሳትፎ ጭምር ነው፡፡11

በተጨማሪም ፖለቲካ ፓርቲዎች እንደ ድልድይ ሆነው ህዝብንና መንግስታዊ አስተዳደሩን የሚያገናኙ

ቁልፍ የዴሞክራሲ ተቋማት ናቸው፡፡ የህዝብን ፍላጎትና ቅሬታ ወደ መንግስት ይወስዳሉ፤

መንግስትም ለፖሊሲና ፕሮግራሙ ህዝባዊ ድጋፍና ተቀባይነት ለማግኘት የሚጥረው በፓርቲው

አማካኝነት ነው፡፡ ዜጎች የፖለቲካ ፓርቲዎችን በአባልነት ሲቀላቀሉ፣ ጊዜያቸውንና ገንዘባቸውን

ሲለግሱና መሪዎቹን ሲመርጡ መሰረታዊ የዴሞክራሲ መብታቸውን እየተገበሩ እንደሆኑ ይታመናል፡

፡ በምርጫ አሸንፎ ስልጣን የሚይዝ ፓርቲ መንግስትን ሲመሰርት ያላሸነፉት ፓርቲዎች ደግሞ

መንግስትን የመሰረተውን ፓርቲ አፈፃፀም በትኩረት በመከታተልና በመተቸት ህዝቡ የተሻለ

መንግስታዊ አገልግሎት ማግኘቱን ያረጋግጣሉ፡፡ እንደ አስፈላጊነቱም አማራጭ ሃሳቦችን በማቅረብ

10
Institute of Developing Economies: Japan External Trade Organization (JETRO), (n.d) Hazama
Yasushi. Political Parties and Elections: Minimal conditions for democracy.
11
Michael, Johnston. (n.d) Political Parties and Democracy in Theoretical and Practical Perspectives.
National Democratic Institute For International Affairs (NDI), pdf.
12
የተረጋጋ ስርዓት እንዲፈጠር ያግዛሉ፡፡ ስለዚህም የጤነኛ ተፎካካሪ ፓርቲዎች መኖር ለስኬታማ

ዴሞክራሲ አስፈላጊ ነው፡፡

2.1.2. የፖለቲካ ፓርቲዎች ስትራቴጂክ እቅድ

በማንኛውም የፖለቲካ ስርዓት ውስጥ በቋሚነት የሚኖር ነገር ቢኖር ለውጥ ነው፡፡ ፖለቲካ

ፓርቲዎች የሚንቀሳቀሱት በውስብስብ፣ ተለዋዋጭና የማይገመት ከባቢያዊ ሁኔታ ውስጥ ነው፡፡

የአመራሮች፣ አባላትና ባለሙያዎች መቀያየር፣ የበጀት ማነስና መጨመር፣ የህገ መንግስትና ሌሎች

ህጎች መሻሻል፣ የመራጮች ፍላጎት፣ የኢኮኖሚ ቀውስ፣ የተፎካካሪ ፓርቲዎች ማንሰራራት ወይም

መዳከም ሁሉ የለውጥ ሁኔታዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ለውጦችና ተግዳሮቶች ፓርቲውን ሊያጠነክሩት

ወይም ሊያዳክሙት፣ ግቦቹን እንዲያሳካ ሊያግዙት ወይም እንቅፋት ሊሆኑት፣ አነስተኛ ጫና

ሊያሳድሩበት ወይም ጭራሹኑ ህልውናውን ሊያከስሙት ይችላሉ፡፡ እነዚህ ሁኔታዎች ተሻግሮ ስኬታማ

ለመሆን በፓርቲው እሳቤዎች፣ በመሰረታዊ ባህሪዎቹ፣ በመዳረሻዎቹና የአተገባበር ስልቶቹ ላይ

በፓርቲው ሁሉም መዋቅሮች መካከል የጋራ አመለካከት መያዝ ያስፈልጋል፡፡ ከፖለቲካ ፓርቲዎች

ስትራቴጂክ እቅድ አስፈላጊነት ጀርባ ያለው አመክንዮም ይሄው ነው፡፡

ተቋም ተኮር ስትራቴጂክ እቅድን ማዘጋጀት የተጀመረው በ1950ዎቹ እና በ1960ዎቹ መጀመሪያ

አካባቢ ነው፡፡12 በኢንዱስትሪ አብዮት ውስጥ ባለፉ የአውሮፓ ሀገራት ያሉ ኩባንያዎች በዙሪያቸው

ያለው ፈጣን ተለዋዋጭ ሁኔታ (ስጋቶችና መልካም እድሎች) በተለመደው የእለት ተዕለት እቅድ

ሊስተናገድ እንደማይችል ሲገነዘቡ ሁኔታውን የሚመጥን የተለየ እቅድ መቅረፅ እንደጀመሩ ይነገራል፡

፡ ሆኖም ስትራቴጂክ እቅድ ለግል ድርጅቶች/ ኩባንያዎች እና እንደ ፖለቲካ ፓርቲ ወይም ሌላ

ህዝባዊ ተቋም ያሉ ለትርፍ ያልተቋቋሙ ድርጅቶች የሚኖረው ትርጉምና ፋይዳ የተለያየ ነው፡፡

ከግል ሴክተሩ በተለየ መልኩ በህዝባዊ ተቋማትና በፖለቲካ ፓርቲዎች የሚዘጋጁ እቅዶች ግብ

ማህበራዊ እሴቶችን ማበልፀግ እና ለዚህ ስኬትም መንግስታዊና ፖለቲካዊ ስልጣንን ጥቅም ላይ

ማዋል እንደሆነ ያብራራሉ፡፡13 ማርክ ሙር እንደሚለው የንግድና ፋይናንስ ተቋማት ስትራቴጂክ

12
Crol, J.B., (1999). ‘Het Belang van Strategisch Denken in het Bedrijfsleven’, Beleid en Maatschappij,,
pp. 163–9.
13
Ombati, Kepta. (20008). Strategic Planning Practices among Political Parties in Kenya. School of
Business, University of Nairobi.
13
እቅድ የመጨረሻ መዳረሻ የባለ አክስዮኖችን ድርሻ ማሳደግ ነው፡፡ ለትርፍ ያልተቋቋሙ የህዝባዊ

ድርጅቶች እቅድ የመጨረሻ ግብ ግን ሌሎች ማህበራዊ ተልዕኮዎችን ማሳካት ነው፡፡14 የእቅድ

አፈፃፀማቸውም ሲገመገምም የግል ድርጅቶች በፈጠሩት የፋይናንስ አቅም መጠን ሲለኩ ህዝባዊ

ተቋማት ደግሞ የያዙትን ማህበረሰባዊ ተልዕኮ ሲፈፅሙ ባሳዩት በዉጤታማነትና ቅልጥፍና

ይመዘናሉ፡፡ የእነዚህ የህዝብ ተቋማት ግብና የሃብት ምንጭ ከግል ድርጅቶች የተለየ እስከሆነ ድረስ

የተለየ የስትራቴጂክ እቅድ አነዳደፍ ስልት መከተል ይገባቸዋል፡፡

ስትራቴጂክ እቅድ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር እንዴት እንደሚተሳሰር በዝርዝር ማየት ተገቢ ነው፡፡

ቫን ደንበርግ እንደሚለው ስትራቴጂ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በብዙ መልኩ ተሳስሮ ጥቅም ላይ

ይውላል፡፡ ከሁሉ ቀድሞ በሰው አዕምሮ የሚመጣው ግን ፓርቲዎች በምርጫ ወቅት የመራጫቸውን

ህዝብ ቁጥር ለማሳደግ የሚከተሉት ስትራቴጂ ነው፡፡ ይህም ማለት የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም

መራጮች ጋር በመድረስ በተቻለ መጠን ብዙ መራጭ ድምፁን እንዲሰጠው የማሳመን ተልዕኮ

ካለው የፖለቲካ ፓርቲዎች የምረጡኝ ቅስቀሳ ዘመቻ ጋር የተሳሰረ ይሆናል፡፡ ይሄ አንዱ ቁልፍ

የፖለቲካ ፓርቲዎች የስትራቴጂክ እቅድ መገለጫ መስክ መሆኑ ባይካድም ብቸኛው ነው ማለት

ግን አይደለም፡፡ ፓርቲዎች ከምርጫ ቅስቀሳ ስትራቴጂ ባለፈ የስራ ዘርፎቻቸውን ወደ አንድ የጋራ

እይታና ውጤት የሚያስተሳስር ተቋም ተኮር ስትራቴጂም ያስፈልጋቸዋል፡፡15

ብዙውን ጊዜ ፖለቲካ ፓርቲዎች በአጭርና የድንገተኛ ጊዜ የቀውስ ጉዳዮች ወይም የዘመቻ ስራዎች

ላይ እንዲያተኩሩ ሁኔታዎች ያስገድዷቸዋል፡፡ በተለይም በታዳጊ ዴሞክራሲ ውስጥ እንዲህ አይነት

ተለዋዋጭ የፖለቲካ ምህዳሮች የፖለቲካ ፓርቲዎችን ህዝባዊ ቅቡልነት ብሎም ዘለቄታዊ

ህልውናቸውን ይፈታተኗቸዋል፡፡ ፓርቲዎች ለእነዚህ ማህበረሰባዊ ፍላጎቶች እና ዴሞክራሲያዊ

ሽግግሮች ራሳቸውን በብቃት ማዘጋጀት የሚችሉት የሩቁን አቅርበው ማየት ሲችሉና እድገትን

ሲያልሙ ብቻ መሆኑን ቫን ደንበርግ ይመክራል፡፡

14
Moore, M.H., (2000). ‘Managing for Value: Organizational Strategy in For-profit, Non-profit, and
Governmental Organizations’, Nonprofit and Voluntary Sector Quarterly, 29/1.
15
Caspar F. van den Berg. Strategic Planning for Political Parties: A Practical Tool. Netherlands Institute
for Multiparty Democracy (NDI).
14
ቫን ደንበርግ እና ኦምባቲ ስትራቴጂክ እቅድ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ያለውን ፋይዳ በሚከተሉት

መንገዶች ዘርዝረዋል፡፡

• ከእለት ተዕለት አጀንዳዎች ፈቀቅ ብለው መሰረታዊና ዘላቂ ጉዳዮች ላይ እንዲጨነቁ እድሉን

ይሰጣቸዋል፡፡

• የተቋማቸውንና የመዋቅራቸውን ጥንካሬ የሚያጎለብቱ ተደራሽ የረጅም ጊዜ አላማዎችን

የሚቀርጹበትን አካሄድ ይፈጥርላቸዋል፡፡

• ወዴት መድረስ እንደሚፈልጉ በግልፅ ለማየት እንዲችሉና የትኞቹ የተግባር አጀንዳዎች

ተቋማዊ አቅማቸውን በማጎልበት የፈለጉበት ቦታ እንደሚያደርሷቸው እንዲረዱ ያግዛቸዋል፡

፡16

• የተጠያቂነት አሰራርን ለመዘርጋትና የፓርቲውን አፈፃፀም በተጨባጭ መለኪያዎች ላይ

ተመስርቶ ለመመዘን ያስችላቸዋል፡፡17

ከዚህ አንፃር ሲታይ ብልፅግና ፓርቲ መሰረታዊና ዘለቄታዊ የህዝብና የሀገር ፍላጎትን የሚያሟሉ

ተግባሮች ላይ ያተኮረ የረጅም ጊዜ እቅድና የአፈፃፀም ስትራቴጂ መቅረፅ ያስፈልገዋል፡፡

2.2. በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሁኔታ

2.2.1. የፖለቲካ ፓርቲዎች ታሪክ በኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ ካላት የረጅም ዘመን ታሪክ አንፃር የፓርቲ ፖለቲካ የቅርብ ጊዜ ክስተት ተደርጎ የሚወሰድ

ነው፡፡ በተመሳሳይ የዴሞክራሲያዊ ስርዓት አስኳል በሆነው ምርጫ ላይ ያላቸው ተሳትፎም እንዲሁ

የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው፡፡

በንጉሳዊ አስተዳደር ዘመን በ1948 ዓ.ም የተሻሻለው ሕገ መንግስት አንዳንድ የዲሞክራሲ

መብቶችን ለይስሙላ ቢፈቅድም በተግባር ግን ለፖለቲካ ፓርቲዎች ምስረታ የፈየደው ነገር

አልነበረም። ስለሆነም በሀገራችን የፓርቲ ፖለቲካ ቅርፅ መያዝ የጀመረው የ1960ዎቹን አብዮት

16
Caspar F. van den Berg. Strategic Planning for Political Parties: A Practical Tool. Netherlands Institute
for Multiparty Democracy (NDI).
17
Ombati, Kepta. (20008). Strategic Planning Practices among Political Parties in Kenya. School of
Business, University of Nairobi.
15
ተከትሎ ነው ማለት ይቻላል፡፡ በአብዮቱ ወቅትና ከዛም በኋላ የተለያዩ የፖለቲካ ሃይሎች እንደ

ንቅናቄ፣ ግንባር፣ ድርጅት፣ ቅንጅት፣ ፓርቲ የመሳሰሉ ስሞችን በመያዝ ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ

ገብተዋል፡፡ በደርግ ዘመን የነበሩት የፖለቲካ ስብስቦች ግን በከፊል ህጋዊነት፤ በሕቡዕና፤ ከሕጋዊ

እውቅና ውጪ ተሰባስበው የሚንቀሳቀሱ ነበሩ፡፡ ለዚህም ዋናው ምክንያት ደርግ ከራሱ ፈቃድና

ይሁንታ ውጭ ተደራጅተው ለመንቀሳቀስ የሞከሩትን የፖለቲካ ኃይሎች በሙሉ በጥርጣሬ ይመለከት

ስለነበር ነው፡፡ ይህ አዝማሚያ በሂደት ኢሠፓ የተባለውን ብቸኛ ሕጋዊ ድርጅት በማቋቋምና ከዚህ

ውጪ ሌላ የፖለቲካ ቡድን ሕጋዊ እውቅና ሊኖረው እንደማይችል በመደንገግ ተቋጭቷል። ደርግን

በማስወገድ አስቀድሞ በሽግግር መንግስት ቀጥሎም በምርጫ ወደ ስልጣን የወጣው የኢህአዴግ

ስርዓት መገለጫ የሚሆነው በርካታ መጠን ያላቸው ብሄር ተኮርና ሀገር አቀፍ ፓርቲዎችን መፍጠሩ

ነው፡፡ የፓርቲዎቹን አይነትና መጠን መብዛትን ስርዓቱ የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን መስርቻለሁ

ለሚል ፕሮፓጋንዳ ሊያውለው ቢሞክርም በተግባር ስርዓቱ የሚታወቀው ግን በአግላይነትና

በአፋኝነት ነበር፡፡ ሰፊ ሕዝባዊ መሰረት አላቸው ተብለው የሚገመቱ ፓርቲዎችን በማግለል

የተጀመረው የአንድ ፓርቲ ፈላጭ ቆራጭነት በርካታ ፓርቲዎች ወደ ትጥቅ ትግል እንዲያቀኑ

በመግፋት ጤናማ የፓርቲ ፖለቲካ ምህዳር እንዳይፈጠር አድርጓል። በአጭሩ ከንጉሳዊ ወደ ወታደራዊ

አስተዳደር የተደረገው የስልጣን ሽግግር ከፓርቲ አልባነት ወደ አንድ ፓርቲ ህልውና መረጋገጥ

ያዘነበለ ሲሆን ከደርግ ወደ ኢህአዴግ የተላለፈው የፖለቲካ ስርዓት ደግሞ በነቢብ የመድብለ ፓርቲ

በተግባር ግን አውራ ፓርቲ የመገንባት ነበር ማለት ይቻላል፡፡18

በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ የተጀመረው በአፄ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት በ1923 ዓ.ም

በተካሄደው የዘውድ ምክር ቤት አባላት ምርጫ ነው፡፡ በ1923 ዓ.ም የመጀመሪያው የተጻፈ ህገ

መንግሥት ተረቆ የመጀመሪያው ፓርላማ ተቋቋመ፡፡ በሁለቱም ምርጫዎች መራጩ ህዝቡ ሳይሆን

ንጉሡ ራሣቸው ነበሩ፡፡ በ1935 ዓ.ም የተቋቋመው ፖርላማም እንደፊተኛው የህግ መምሪያና

የህግ መወሰኛ ምክር ቤቶች ነበሩት፡፡ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት አባላትም በንጉሠ ነገሥቱ

18
አበበ አሠፋ እና ክቡር እንግዳወርቅ (2012) ዲሞክራሲያዊ የለውጥ እርምጃዎች እንድምታዎች እና
አማራጮቻቸው በኢትዮጵያ (ቅጽ አንድ)፤ ሕገ-መንግስት፣ ብሔር-ተኮር ፌደራሊዝም፣ የፖለቲካ
ፓርቲዎች እና ሕዝባዊ ምርጫ፤ ፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ
16
የተመረጡ ሲሆን የህግ መምሪያ አባላት ግን የአገር ሽማግሌዎች በየወረዳቸው ተሰብሰበው

የሚመርጡዋቸው ባላባቶች እንዲሆኑ ተደረገ፡፡ ከ1948 ዓ.ም ጀምሮ ህዝቡ ራሱ እንደራሴዎቹን

በቀጥታ እንዲመርጥ ተፈቀደ፡፡ ከ1948-1967 ዓ.ም በየአራት ዓመቱ አምስት ተከታታይ

ምርጫዎች ተካሂደዋል፡፡ ንጉሱን አስወግዶ ስልጣንን በሃይል የያዘው ደርግ እስከ 1979 ዓ.ም

ድረስ ሀገር ሲመራ የቆየው ከልዩ ልዩ ወታደራዊ ክፍሎችና መሥሪያ ቤቶች የተውጣጡ 6ዐ ሰዎችን

ባቀፈ የመማክርት ጉባኤ ነበር፡፡ በ1979 ዓ.ም 835 አባላት ያሉት ባለ አንድ ሸንጎ ምክር ቤት

በምርጫ ቢሰየምም ዕጩዎችን የሚጠቁመውም፣ የሚያስመርጠው ራሱ የኢትዮጵያ ሠራተኞች

ፓርቲ /ኢሠፓ/ ነበር፡፡ ኢህአዴግ ሥልጣን ከተቆጣጠረ በኃላ የሸግግር መንግሥት በመመስረት

እስከ 1984 ዓ.ም ድረስ አስተዳድሯል፡፡ በ1984 ዓ.ም የብሔራዊ፣ ክልላዊ፣ የዞን እና የወረዳ

ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ ተካሄደ፡፡ የኢፌዴሪ ህገ መንግስት ፀድቆ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ

ቦርድ በህገ መንግሥቱ መሰረት ከተቋቋመ ጀምሮ ደግሞ ስድስት ጠቅላላ ምርጫዎች ተካሂደዋል፡

፡19

በንጉሡና በደርግ አስተዳደር እንዲሁም በኢህአዴግ የስልጣን ዘመን የተካሄዱት እነዚህ ምርጫዎች

የሕዝብን ትክክለኛ ተወካይነት የሚያረጋግጡና የዜጎችን ትክክለኛ ፍላጎት በዲሞክራሲያዊ መንገድ

የሚያስተናግዱ አልነበሩም፡፡ የየምርጫዎቹ አላማ ለየሥርዓቶቹ የሕጋዊነት ሽፋን ለመስጠትና

የህዝብና አለም አቀፍ ድርጅቶችን ቅቡልነት ለማግኘት እንጂ የዜጎችን ተገቢና አሳማኝ ፍላጎቶችን

የሚያሟላ አማራጭ ያላቸውን የፖለቲካ ሃይሎች ወደ ስልጣን ለማውጣት አይደለም፡፡

በ2010 ዓ.ም የመጣው ሀገራዊ ለውጥ ከወሰዳቸው ዘርፈ ብዙ የለውጥና የፖሊሲ ማሻሻያ

እርምጃዎች ቀዳሚው ለረጅም አመታት በድባቴ ውስጥ የኖረውን የሀገሪቱን የፓርቲ ፖለቲካ እንደገና

እንዲያንሰራራ የሚያስችሉ ዉሳኔዎችን ማሳለፍና መተግበር ነው። የአፋኝ ህጎች መሻሻል፣ የምርጫ

ቦርድ በፓርቲዎች ተሳትፎ ጭምር እንደገና መዋቀር፣ የታገዱና በሽብርተኝነት የተፈረጁ የፖለቲካ

19 ሰዋሰው (ከዚህም ከዚያም) (2021) የምርጫ ታሪክ በኢትዮጵያ፤ ከዘውዳዊው ስርዓት እስከ
ኢፌዴሪ፤ ከተለያዩ ምንጮች የተገኙ መጣጥፎች

17
ድርጅቶች እንደገና እውቅና ማግኘት እና በፖለቲካዊ አመለካከታቸው የተነሳ የታሰሩ የፖርቲ

አመራሮችና አባላት መፈታት ተጠቃሽ እርምጃዎች ናቸው፡፡20

2.2.2. የተፎካካሪ ፓርቲዎች ወቅታዊ ሁኔታ

በሀገራችን የተመዘገበው ለውጥ ለፓርቲ ፖለቲካ መዳበር ሁነኛ አስተዋፆ አበርክቷል፡፡ በሀገራችን

ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ገዥው ፓርቲ ብልፅግና ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ተቀራርቦ

ለመስራት ያስቻሉትን እርምጃዎች ወስዷል፡፡ ተፎካካሪ ፓርቲዎች በዋናዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ

እንዲመክሩና የውሳኔ አካል እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች በከፍተኛ የመንግስት

ስልጣን ቦታዎች ተመድበው በሀገር መምራት ሂደቱ ላይ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ በሀገሪቱ ያለው የፖለቲካ

ምህዳር በጥቅሉ በመግባባት፣ በመተማመንና በመተባበር ላይ ተመስርቶ እንዲጓዝ ብልፅግና

የሚጠበቅበትን ሃላፊነት ሁሉ እየተወጣ ይገኛል፡፡

እነዚህ እርምጃዎች በተፎካካሪ ፓርቲዎች ዘንድ በጎ ተቀባይነትን አስገኝተዋል፡፡ አሁን ላይ ተፎካካሪ

ፓርቲዎች በጭፍን የመንግስትን ውሳኔዎች የሚያጥላሉ ሳይሆኑ ምክንያታዊ የሆነ የድጋፍና የልዩነት

ሃሳባቸውን በነፃነት የሚሰጡ፤ አለፍ ሲልም አብረው ለመስራት ተነሳሽነት የሚወስዱ ናቸው፡፡ ይህ

የፓርቲዎች ቁርጠኝነት በህልውና ማስከበር ዘመቻው ወቅትና ቀደም ብሎም ስድስተኛውን ዙር

ሀገራዊ ምርጫ በኮቪድና ሌሎች ምክንያቶች ጊዜውን ለማሸጋገር በተደረገው ውሳኔ ወቅት በገሃድ

የታየ ነው፡፡

ይህ እንዳለ ሆኖ በቁጥራቸው ጥቂት የሆኑ ፓርቲዎች ግን አሁንም ድረስ ቀድሞ በነበረው ልምድ

ህጋዊና ህገ ወጥ መንገድን እያጣቀሱ የመሄድና ሀገራዊ ለውጡንና የመንግስትን እያንዳንዱን

እንቅስቃሴ በፈጠራ ወሬዎች በማጠልሸት ህዝብን ለማደናገር የሚሰሩ ሆነው ቀጥለዋል፡፡ ማህበራዊ

ሚዲያውን በመጠቀም ህዝቡን በሀሰት ወሬዎች ለማደናገርና የህዝቡን ብሶት በመቀስቀስ ለአመፅ

ለማነሳሳት የሚጥሩ ፓርቲዎች አሉ፡፡ ሀገራዊ ምክክር ለማካሄድ እየተከናወኑ ባሉ የዝግጅት ስራዎች

20
አበበ አሠፋ እና ክቡር እንግዳወርቅ (2012) ዲሞክራሲያዊ የለውጥ እርምጃዎች እንድምታዎች እና
አማራጮቻቸው በኢትዮጵያ (ቅጽ አንድ)፤ ሕገ-መንግስት፣ ብሔር-ተኮር ፌደራሊዝም፣ የፖለቲካ
ፓርቲዎች እና ሕዝባዊ ምርጫ፤ ፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ
18
ላይ ከሞላ ጎደል ሁሉም ፓርቲዎች ድጋፋቸውን ገልፀው እየተሳተፉ የቆዩ ቢሆኑም የዝግጅት ሂደቱ

በመገባደድ ላይ ባለበት ወቅት አንዳንዶቹ ያለ በቂ ምክንያትና ሰበብ ፍለጋ በሚመስል መልኩ

ሂደቱን ለማስተጓጎል ሲጥሩ ይታያሉ፡፡

ከዚህ በተጨማሪም አሁን ላይ በሀገራችን የሚታየው የፖለቲካ ፓርቲዎች ቁጥር ብዛት የሀገሪቱ

የፓርቲ ፖለቲካ መሰረቱ የፖለቲካ አስተሳሰብ ወይም የመደብ ልዩነት ሳይሆን በወቅታዊ ስሜቶች

ላይና በቡድኖች ልዩ ፍላጎቶች ላይ የተመሰረተ መሆኑን ለመረዳት አይከብድም፡፡ ምንም እንኳን

ይህ ክስተት ከለውጡ በኋላ የተፈጠረ አዲስ ክስተት ባይሆንም ብልፅግና በሃሳብ ላይ የተመሰረተ

ጤነኛ ዴሞክራሲን ለመፍጠር ቃል በገባው መሰረት ችግሩን የሚቀርፉ ስትራቴጂያዊ ርምጃዎችን

መውሰድ ይኖርበታል፡፡ በመሆኑም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች አንፃር ያለውን ጉራማይሌ እንቅስቃሴ

ግምት ውስጥ በማስገባት ሁኔታዎችን የሚመጥን የፖለቲካ ስራ መሥራት እንደመነሻ ተወስዷል፡፡

2.3. የኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ታሪክ

ኢትዮጵያ ረጅም የመንግሥት ታሪክ ካላቸዉ ጥቂት የዓለማችን ሀገሮች አንዷ ነች። ዘመናዊ ሀገረ

መንግሥት ከመሠረተች ጀምሮ የተለያዩ ፈተናዎች ቢገጥሟትም ሉዓላዊነቷን አስከብራ ቆይታለች።

በ19ኛዉ ክፍለ ዘመን መጨረሻ አካባቢ በአድዋ ጦርነት የጣሊያንን ወራሪ ሃይል በማንበርከክ

ጭምር ለጥቁር ህዝቦች ሁሉ የነፃነት ተምሳሌትና ኩራት ለመሆን በቅታለች።

ከአድዋ ጦርነት በፊትም ሆነ በኋላ ኢትዮጵያዉያን ባደረጉት አኩሪ ተጋድሎ ኢትዮጵያ የማትደፈር

የነፃነት ዓርማ መሆኗን አስጠብቀው ቆይተዋል። በዚህም በዓለም ፊት በኩራት የሚራመዱ ህዝቦች

መሆናቸዉን አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ በመልክዓ ምድራዊ አቀማመጧ፥ በህዝብ ብዛቷ፥ ለግብርና

ስራ ባላት ምቹ መሬት፥ ውሃን ጨምሮ ባላት እምቅ የተፈጥሮ ሀብት እንዲሁም በቀጠናዊ ፀጥታና

ደህንነት ጉዳዮች በሚኖራት ሚና በአፍሪካ ቀንድ ልዩ ስፍራ የሚሰጣት ሀገር ነች። በዲፕሎማሲው

መስክም ሀገራችን ሊግ ኦፍ ኔሽንንና የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን ከመሰረቱ ሀገራት ውስጥ አንዷ

ነች፡፡ ዛሬም ድረስ የተለያዩ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ተቋማት መቀመጫ የዲፕሎማሲ ማዕከል

በመሆን እያገለገለች ትገኛለች።

19
ረጅም ሀገረ መንግሥት፥ ታሪክና ቱባ ባህል ያላትና እምቅ የተፈጥሮ ሀብት ባለቤት የሆነችዉ

ኢትዮጵያ፥ አፍሪካዊት የነፃነት ምልክት ብትሆንም ከዉስጥም ሆነ ከዉጪ በተከታታይ በገጠሟት

ችግሮች ምክንያት የብልፅግና ተምሳሌት መሆን አልቻለችም። ዘመናትን ባስቆጠሩ የፖለቲካ ታሪክ

ዉስጥ ኢትዮጵያ የተለያዩ የፖለቲካ ሥርዓቶችና ርዕዮተ ዓለሞች ተፈራርቀዉባታል። ዘዉዳዊ የአገዛዝ

ሥርዓት፥ የሶሻሊዝም አገዛዝና አብዮታዊ ዲሞክራሲ የአስተዳደር ሥርዓቶችን በቅደም ተከተል

አስተናግዳለች። አንዱን ሥርዓት በሌላዉ ለመተካት ተደጋጋሚ መፈንቅለ መንግሥትና የትጥቅ

ትግሎች ተካሂደዋል፡፡ እነዚህ በባህሪያቸው አብዮታዊ የሆኑ ህዝባዊ ንቅናቄዎች ህዝቦቿን ለጉስቁልና፣

ሀገሪቱንም ለቁልቁለት ጉዞ ዳርገዋል፡፡

በ1960ዎቹ አጋማሽ የተካሄደው የተማሪዎች ንቅናቄ የህዝቡን ጥያቄዎች መልክ በማስያዝ

የመሬት/የኢኮኖሚ፥ የዴሞክራሲ እና የብሔር እኩልነት ጥያቄዎች የትግል አቅጣጫ ሆነው

እንዲቀጥሉ አድርገዋል።

ወቅታዊ ሁኔታውን ተጠቅሞ ስልጣን የተቆጣጠረው የደርግ አስተዳደር መሬት ለአራሹን በማወጅ

የመሬት ጥያቄን ለመመለስ ቢሞክርም መሬት ለህዝቦች ዘላቂ የኢኮኖሚ ብልፅግና መሰረት

የሚሆንበትን የተሟላ ምላሽ መስጠት ሳይችል ቀርቷል፡፡ በተለይም ደግሞ የደርግ መንግስት የብሔር

ጥያቄን ለመመለስ በማቅማማቱ ስርዓቱ ፈርሷል። ደርግን ተክቶ በሃይል ስልጣን የያዘው ኢህአዴግ

የብሔሮችን መብቶች ለመመለስ ረጅም ርቀት ተጉዟል ማለት ይቻላል፡፡ አተገባበሩ ግን የሀገርን

አንድነትን የህዝቦችን አብሮነት የመሸርሸር አደጋ ያደረሰ ነበር፡፡ ኢህአዴግ የብሄር እኩልነት ጥያቄን

በሕገ መንግስት ደረጃ ምላሽ በመስጠት መልካም ጅምሮችን ቢያሳይም ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ

መብቶችንና እውነተኛ ፌዴራሊዝምን በቁርጠኝነትና በሙሉ ልብ ለመተግበር ባለመቻሉና የመሬት

ጥያቄም የመጨረሻ እልባት ሳያገኝ በመዝለቁ ፍፃሜው ህልውናውን ማጣት ሆኗል፡፡

ከአንዱ ወደ ሌላው ስርዓት ሲካሄዱ በነበሩት ሽግግሮች ሂደት ዉስጥ ተቋማት ተገንብተዋል፤

ተቋማት ፈርሰዋል። የለውጥ ሃይሎቹ በርዕዮተ ዓለምና ሌሎች ትናንሽ አጀንዳዎች ስምምነት ላይ

መድረስ አቅቷቸው እርስ በርስ ተዋግተዋል፥ ሀገረ መንግሥቱም መረጋጋት ተስኖት አሁን ላይ

ደርሰናል። በኢትዮጵያ የፖለቲካ ስርዓት ውስጥ በተለያየ ጊዜ የተፈጠሩ የፖለቲካ ምስቅልቅሎች

ህዝቡን ወደመበተን አደጋ አድርሰውት በነበረበት ሁኔታ ነው ብልጽግና የተወለደው፡፡

20
ብልፅግና ፓርቲ ይህን የሀገረ መንግስት ግንባታ ሂደትና ታሪክ በመረከብ በተሟላ መደላድል ላይ

የማሳረፍና ለቀጣዩ ትውልድ የማሳለፍ ሃላፊነት አለበት፡፡ የሀገረ መንግስት ግንባታ በአጭር ጊዜና

ታክቲካዊ ርምጃዎች የሚሳካ ሳይሆን የረጅም ጊዜ ስትራቴጂክ እቅድ እና የማስፈፀሚያ ስልት

ያስፈልገዋል፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ የሀገረ መንግስት ግንባታ ታሪክ የስትራቴጂክ እቅዱ አንዱ

መነሻ ተደርጎ ተወስዷል፡፡

2.4. ሀገራዊ የህግና የፖሊሲ ማዕቀፎች

በኢፌዴሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 38 መሰረት ማንኛውም ሰው በቀለም፣ በብሔር፣ በጾታ፣ በቋንቋ፣

በሃይማኖት፣ በፖለቲካ ወይም በሌላ አመለካከት ወይም አቋም ላይ የተመሰረተ ልዩነት ሳይደረግበት

የፖለቲካ ድርጅቶች አባል የመሆን፣ የመምረጥና የመመረጥ መብቶች አሉት፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ

የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 መሰረት በህገ

መንግስቱ እግድ ከተጣለባቸው ዜጎች (ዳኛ፣ የመከላከያ ሰራዊት አባል እና የፖሊስ አባል) በስተቀር

ማንኛውም እድሜው 18 ዓመትና ከዚያ በላይ የሆነ ኢትዮጵያዊ የፖለቲካ ድርጅቶች አባል መሆን

ይችላል፡፡

የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ የፖለቲካ ፓርቲዎች የገቢ ምንጭ ከአባላት መዋጮ፣

ከኢትዮጵያውያን ግለሰቦችና ኩባንያዎች ከሚገኝ ስጦታ እና ከመንግስት ድጎማ ብቻ እንደሚሆን

ያስቀምጣል፡፡

ሀገራችን እየተከተለች ያለችው የምርጫ ስርዓት በአንድ የምርጫ ክልል ውስጥ ከሌሎች ተወዳዳሪዎች

መካከል አብላጫ ድምጽ ያገኘ ተወዳዳሪ ለምክር ቤት አባልነት አሸናፊ የሚሆንበት (Plurality

system) ነው፡፡ በህገ መንግሥቱ መሰረት በየአምስት ዓመቱ ምርጫ እንደሚደረግ በግልፅ

ተደንግጓል፡፡ከዚህ በተጨማሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ወንበር ድልድል የሕዝብ ብዛትንና

በልዩ ትኩረት ውክልና የሚሰጣቸው በቁጥር አናሳ ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ቁጥር መሰረት በማድረግ

እንደሚፈፀም በህገ መንግስቱ እንዲሁም በምርጫ ህጉ ላይ ተደንግጓል፡፡ በብልፅግና ፓርቲ ህገ

ደንብ መሰረት ከጉባኤ እስከ ጉባኤ ፓርቲውን የሚመራ ከፍተኛ አካል የሆነው የፓርቲው ማዕከላዊ

ኮሚቴ ምርጫ ሲካሄድም ይህንኑ በሚያንፀባርቅ መልኩ የህዝብ ብዛትን፣ የአባላት ብዛትንና

21
በቁጥር አናሳ የሆኑ ብሔሮችን ታሳቢ ባደረገ መስፈርት የሚፈፀም መሆኑ በህገ ደንባችን ተደንግጓል፡

ፓርቲዉ በህገ ደንቡ ብቻ ሳይሆን በፕሮግራሙም ፖለቲካዊ፥ ኢኮኖሚያዊ፥ ማህበራዊ እና ዉጪ

ጉዳይ ፖሊሲዎች አካታችነትን የተላበሱ እንዲሆኑ አድርጓል። ብልፅግና የሚከተላዉ ዲሞክራሲ

በትብብርና ዉድድር ላይ የተመሠረተ የመግባባት ዲሞክራሲ ነዉ።

በኢኮኖሚው ረገድ የምንከተለው እሳቤም የዜጎችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ማዕከል ያደረገና የመንግስትን

ጣልቃ ገብነት የሚፈቅድ አካታች ካፒታሊዝም ነው፡፡ በውጭ ግንኙነት ረገድ ብልጽግና የሚከተለው

እሳቤ በትብብርና በፉክክር መካከል ሚዛን የሚጠብቅ፣ ለዜጎች ክብር ቅድሚያ የሚሰጥ፣ ብሔራዊ

ጥቅምን የሚያስጠብቅና ለጎረቤት አገራት ቅድሚያ የሚሰጥ ነው፡፡ ከሀገራዊ ደህንነትና የውጪ

ግንኙነት አንፃር የተቀመጡትም የመንግስት የፖሊሲ አቅጣጫዎች በዚህ መንገድ የተቃኙ ናቸው፡፡

በሀገሪቱ ስራ ላይ ያሉ የህግ ማዕቀፎች ለፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ምቹ ምህዳር የሚፈጥሩ

ናቸው፡፡ ብልፅግና ፓርቲ በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ ሆኖ የራሱን መለያ የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና

የውጪ ግንኙነት ፖሊሲዎችንና አቅጣጫዎች ቀርፆ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ እነዚህ ፖሊሲዎችና

አቅጣጫዎች በስትራቴጂክ እቅዱ ውስጥ በአግባቡ እንዲንፀባረቁና በሚለኩ ግቦች ተዘርዝረው እንዲታዩ

ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

2.5. የ10 አመት የመንግስት የልማት እቅድ

የኢፌዴሪ መንግስት ከ2013 እስከ 2022 ዓ.ም የሚፈፀም የ10 አመት የልማት እቅድ አውጥቶ

በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡ የ10 አመቱ እቅድ ሀገራዊና የዘርፍ ፖሊሲዎችን፣ የአንደኛውና የሁለተኛው

የእድገትና ትራስፎርሜሽን እቅዶችን አፈፃፀም፣ ሀገራዊ ለውጡንና የኢኮኖሚ ሪፎርሙን፣ በሀገሪቱ

የታዩ መልካም ውጤቶችንና ያጋጠሙ ፈተናዎችን፤ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ስምምነቶችንና

ሁኔታዎችን መነሻ አድርጎ ወስዷል፡፡

ኢትዮጵያ በአንደኛውና በሁለተኛው የእድገትና ትራስፎርሜሽን ወቅትና ከዚያ በፊት ባሉ ዓመታት

ፈጣንና ተከታታይ ዕድገት ማስመዝገቧ ይታወሳል፡፡ ይሁን እንጂ እድገቱ በመንግስት ከፍተኛ ወጪ

በተስፋፋ የመሠረተ ልማት ዕድገት አማካኝነት የተመዘገበ ነው። ይህ የመንግስት የመሰረተ ልማት
22
ወጪ በከፍተኛ ብድር እና እርዳታ የተሸፈነ ነው። በመሆኑም እድገት እያለም ሀገራዊ ቀውስ

እንዲፈጠር ሆኗል፡፡

የውጭ ክፍያ ሚዛን እና በቁጠባና ኢንቨስትመንት መካከል ያለው ሚዛን መዛባት፣ የዋጋ ግሽበትን

አለማረጋጋት፣ የሥራ አጥ ቁጥር መጨመር፣ አዝጋሚ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጥ እና ደካማ

የዘርፎች ትስስር፣ ሀብት የማሰባበስብ ዝቅተኛ አቅም፣ የፋይናንስ ድርጅቶች ተደራሽ አለመሆን

በአጠቃላይ ጥራት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገብ አለመቻል የኢኮኖሚ ስርዓቱ መገለጫ

ሆነው ቆይተዋል፡፡

የማህበራዊ አገልግሎቶችና የመሠረተ ልማት አቅርቦት እጥረትና የጥራት ጉድለት መኖር እንዲሁም

የመንግሥት የማስፈጸም አቅም ውስንነትና ብልሹ አሰራር መስፈኑ ሀገራዊ ቀውሱ እንዲባባስ

አድርገውታል፡፡ የ10 አመቱ ዕቅድ እነዚህን በአንደኛውና ሁለተኛው የእድገትና ትራስፎርሜሽን

ወቅትና ከዚያ በፊት የነበሩ የኢኮኖሚ ስብራቶችን በመሰረታዊነት ለመለወጥ ያለመም ነው፡፡

የልማት ዕቅዱ በ2022 ዓ.ም ኢትዮጵያን የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት ሆና ማየትን ያለመ ነው፡

፡ ርዕዩን ለማሳካት በማክሮ ኢኮኖሚ 10 በመቶ አማካይ ዓመታዊ እድገት በማስመዝገብ የድህነት

ምጣኔን በ2012 በጀት ዓመት ከነበረበት 19 በመቶ በ2022 በጀት ዓመት ወደ 7በመቶ መቀነስ፣

ጠቅላላ የመንግስት ገቢን በ2012 በጀት ዓመት ከነበረበት 395 ቢሊዮን ብር በአማካይ በየዓመቱ

በ26.1 በመቶ በማሳደግ በ2022 በጀት ዓመት ወደ 3.9 ትሪሊዮን ብር ማድረስ፣ ጠቅላላው

የመንግስት ወጪ ከጠቅላላው የሀገር ውስጥ ምርት የሚኖረውን ድርሻ በ2022 በጀት ዓመት ወደ

23.4በመቶ ለማሳደግ ታቅዷል። ይህም ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ገቢ የጠቅላላ ወጪን 88.7

በመቶ እንደሚሸፍንና ጠቅላላ የመንግሥት ወጪ በዕቅድ ዘመኑ ብር 19.3 ትሪሊዮን ማድረስን

ታሳቢ ያደርጋል፡፡

ከማህበራዊ ዘርፍ አንፃር እቅዱ ለሥነ ሕዝብና ለሰው ኃብት ልማት ልዩ ትኩረት ሰጥቷል። የሥነ

ሕዝብ ሽግግርን ማፋጠን እና የሥነ ሕዝብ ትሩፋትን አዎንታዊ በሆነ አግባብ መጠቀም፤ የቤተሰብ

ምጣኔ አገልግሎት ተደራሽነትን ማሳደግ፤ የሴቶችን የትምህርት ተሳትፎ እንዲሁም ውጤታማነት

እንዲጎለብት ማድረግ፤ ወቅታዊ የሥነ ሕዝብ መረጃዎችን ተደራሽነትና ተጠቃሚነት ማሳደግ፤ ከገጠር

23
ወደ ከተማ እንዲሁም ከትናንሽ ወደ ትላልቅ ከተሞች የሚደረግ ፍልሰት በስርዓት እንዲመራ

ማስቻል እና የአካባቢ ደህንነት ማሻሻል የትኩረት አቅጣጫዎቹ ናቸው።

ሁለንተናዊ የሰው ሀብት አቅምን ይበልጥ ለማዳበር የጤናና የትምህርት ፍትሃዊ ተደራሽነትን፣

ጥራትንና አግባብነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ በእቅዱ ተመላክቷል። በሽታ

መከላከል ላይ ያተኮረ የማይበገር የጤና ሥርዓት በመገንባት የእናቶችንና የህጻናትን ሞት መግታት፤

ተላላፊ እና ተላላፊ ባልሆኑ በሽታዎች ሳቢያ የሚደርስ ህመምና ሞትን መከላከልና መቀነስ እና

ዜጎችን ከድንገተኛ የጤና አደጋዎች መጠበቅ ሌሎች የእቅዱ አላማዎች ናቸው።

የማህበራዊ ፍትህ እና ዋስትና ልማት ዋና ዋና ዓላማዎች የሴቶችን፣ የህፃናትን፣ የወጣቶችን፣

የአረጋዊያንን፣ የአካል ጉዳተኞችን እና ተጋላጭ የሆኑ ዜጎችን ሁለንተናዊ ብቃት በማሳደግ በሀገሪቱ

በኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና ባህላዊ ልማት እንቅስቃሴዎች ውስጥ በተደራጀና በተቀናጀ አኳኋን የነቃና

ግንባር ቀደም ተሳትፎ እንዲያደርጉና ከውጤቱም በተገቢው መንገድ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ

ናቸው።

የብልፅግና ፓርቲ የ10 አመት እቅድ ይህ የመንግስት የልማት እቅድ የተያዙለትን ግቦች እንዲያሳካ

ተገቢውን የፖለቲካ አመራር፤ ክትትልና ድጋፍ ማካሄድ አስፈላጊ መሆኑን እንደ አንድ የእቅድ መነሻ

ወስዷል፡፡ በመሆኑም የዕቅድ አፈጻጸም ክትትልና ግምገማ ቅንጅትን ማጠናከር፣ በክትትልና ግምገማ

ዙሪያ የተሟላ አመለካከት መፍጠር፣ የክትትልና ግምገማ አሠራሩን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንዲታገዝ

ማድረግ፣ የአፈፃፀም መመዘኛዎችን ከሂደትና ውጤት ይልቅ ስኬት ተኮር ማድረግ፣ የግልፅነትና

ተጠያቂነት ሥርዓትን መዘርጋት የእቅዱ አቅጣጫዎች ናቸው፡፡

2.6. ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎች

ዓለም ከ250-260 ዓመት አንዴ የሚያጋጥም ከፍተኛ የሆነ ለውጥ ውስጥ ትገኛለች፡፡ ለውጡ

በዋናነት የሚያጠነጥነው በልዕለ ኃያላን ሽግግር ላይ እንደሚሆን ቢያንስ ሦስት ነገሮች አመላካች

ናቸው፡፡ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ የልዕለ ኃያላኑ ሽኩቻ በኃይል ጭምር የሚገለፅ መሆኑ ዓለምን

ወደ ባለ ብዙ ዋልታ ሊቀይራት የሚችል ዕድል ያለው ነው፡፡ ይህ ከሆነ እንደኛ ያሉ ድሃ ሃገራት

እንደሚጠቀሙ ብዙዎች ይስማማሉ፡፡ ሁለተኛው የለውጥ ገጽታ ደግሞ ዓለምን በጣጥሶ መንግስት
24
አልባ ሀገራትን በማብዛት በጎበዝ አለቆች እንድትመራ እድል የሚሰጥ ነው፡፡ ምክንያቱም በርካታ

ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ወይም ቡድኖች /Non-State actors/ እየተፈጠሩ በመታየታቸው

ነው፡፡ ይህን ጉዳይ አንድ ምሳሌ ወስዶ ማየት ግልጽ ሊያደርገው ይቻላል፡፡

ኤሎን ማስክ የተባለ አሜሪካዊ ቱጃር 91 ሚሊየን የፌስቡክ ተከታዮች ያሉት ግለሰብ ነው፡፡ እሱን

የሚከተለው ህዝብ ከጀርመን ህዝብ በላይ ነው፡፡ ምን አልባት በአፍሪካ ጥቂት ሀገሮች ቢቀድሙት

ነው፡፡ ፌስቡክን የሚከተል ማህበረሰብ ደግሞ የተለያዩ ማህበራዊ መሰረት አለኝ ብሎ ከሚኩራራ

የፖለቲካ ፓርቲ በላይ አስተማማኝነት ያለው ነው፡፡ ምክንያቱም የፌስቡክ ተከታይ ማለት ወዶ

ፈቀዶ ጽዕኑ ደጋፊ የሆነ፣ በመረጃው የሚጠቀም በመሆኑ ይህን ያህል ተከታይ ማለት ዓለምን

የሚያንቀጠቅጥ ኃይል መሆኑን ልብ ይሏል፡፡

የዚህን ግለሰብ ተፅዕኖ ፈጣሪነት በሌላ ገፅታው ደግሞ እንየው፡፡ ግለሰቡ በአሁኑ ሰዓት 279

ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ባለቤት ነው፡፡ ይህ ሃብት አፍሪካ በአንድ ዓመት ከምትበጅተው በላይ

ነው፡፡ ነገሮች በሃብት ሚዛን በሚቀያየሩበት ዓለም ውስጥ ግለሰቦች ወይም ቡድኖች ሃብታም

እየሆኑ መሄድ ፖለቲካዊ ፍላጎታቸውን በዚያው ልክ ለማሳካት በጀት ይመድባሉ ማለት ነው፡፡

ግለሰቡ ባለው ተከታይና ሃብት ብቻ ሳይሆን አሁን በተጨባጭ እያደረገ ያለውን መመልከት ደግሞ

ጉዳዩን የበለጠ ግልፅ ሊያደርገው ይችላል፡፡ ይህ ግለሰብ አሁን ላይ በራሺያና ዩክሬን ጦርነት ውስጥ

እጁን በሰፊው አስገብቷል፡፡ ኤስ ፒ ኤክስ የሚባለው የግለሰቡ ካምፓኒ ሳተላይትን የመቆጣጠር

አቅም ስላለው በኢንተርኔት የሚሰሩ ማሽነሪዎችን መቆጣጠር ጀምሯል፡፡ ጦርነቱ ሲጀመር የበላይነቷን

እያረጋገጠች የነበረችው ራሺያ አሁን ላይ በኢንተርኔት የሚሰሩ ጦር መሣሪያዎችን እንደልብ

መጠቀም አልቻለችም፡፡ የጦርነቱ ሚዛንም እየተቀየረ ይመስላል፡፡ ስለሆነም ግለሰቡ በዚህ ደረጃ

የዓለምን ልዕለ ኃያላን ሚዛን እያዛባ መሆኑን ልብ ይሏል፡፡

ሶስተኛው ግን ደግሞ በስሱም ቢሆን ሊከሰት ይችላል ተብሎ የሚጠበቀው ዓለም አንድ

ወጥ/Unipolar/ ሆና የመቀጠል እድል አላት የሚለው ጉዳይ ነው፡፡ አሜሪካ እስከ አሁን ባለው

መሪነቷን ያስቀጠለች ልዕለ ኃያል ሀገር ነች፡፡ ከሷ ቀጥላ ያለችውን ቻይናን ወስደን ብናይ ከአሜሪሪካ

ጋር በዓመታዊ ገቢም ሆነ የጦር ዝግጅት ብቃት በእጅጉ ይለያያሉ፡፡ ብዙዎች እንደሚስማሙበት

ቻይና ከአሜሪካ ጋር ለመስተካከል አሜሪካ 25 ዓመት ቆማ መጠበቅ አለባት፡፡ ይህንን ልዩነት


25
የምትረዳው አሜሪካ በቻይና የውስጥ ጉዳይ እጇን ማስገባት የፈለገች ይመስላል፡፡ በቅርቡ እንኳን

ቻይና ታይዋን ላይ ተጨማሪ እርምጃ ብትወስድ አማሪካ የጦር ጣልቃ ገብነት እንደምታደግ

ዝታለች፡፡ ይህ ሁኔታ እየተባባሰ ከቀጠለ ሶስተኛው የዓለም ጦርነት ላይጀመር ዋስትና የለም፡፡

ሶስተኛው የዓለም ጦርነት ቢፈጠር ምን ተከትሎ ሊከሰት ይችላል የሚለውን ለመረዳት የአንደኛው

እና የሁለተኛው የዓለም ጦርነቶች የዓለም ሚዛን እንዳዛቡት መመልከት በቂ ነው፡፡ ሶስተኛ የዓለም

ጦርነት ከተከሰተ ከዚህ በፊት እንደነበሩት ዓይነት ሳይሆን በእጅጉ ከቴክኖሎጂ ጋር የተያያዘ መሆኑ

ግልጽ ነው፡፡

ከዚህ በተጨማሪ እንደ አራተኛ ውጤት ተደርጎ የሚወሰደው የፖለቲካ ኮሚኒኬሽን አብዮት ሊፈጠር

ያለበት ነባራዊ ሁኔታ ነው፡፡ ይህ ሁኔታ የተቀላቀለ /Hybrid/ ፣የተበጣጠሰ/ fragmented/

ወይም ጫፍ የረገጠ/Pollarzed/ ነባራዊ ሁኔታ ያለው አዝማሚያ ነው፡፡ ሁኔታው በ250

ዓመት ውስጥ አንድ ጊዜ የሚፈጠር ክስተት እንደሆነ የመስኩ ባለሙያዎች ጥናት ያሳያል፡፡ አሁን

ዓለም ያለችበት የፖለቲካ ኮሙኒኬ በነዚህ በአንዱ ቢቋጭ አለምን በእጅጉ የሚጎዳ ነው፡፡

እኛ ያለንበት ቀጠና ሁኔታ ሲታይ ከላይ ካነሳናቸው ጉዳዮች ጋር በእጅጉ ይያያዛል፡፡ በአንደኛው

የአለም ጦርነት ወቅት ልዕለ ኃያል የነበሩ የጣልያን፣ ኔዘርላንድ፣ እንግሊዝና አሜሪካ በሁለቱ የዓለም

ጦርነቶች ምክንያት የልዕለ ሀያልነት ሸግግር አድርገዋል፡፡ አትላንቲክ ውቅያኖስን መሰረት ያደረገው

የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት ፍሎሬንስና ቬነስ የተባሉ የጣሊያን ልዕለ ሀያላን ሀገራት በኔዘርላንድ

የበላይነት ልዕለ ኃያልነታቸው ተወስዶባቸዋል፡፡ ሽግግሩ ከጣሊያን ወደ ኔዘርላንድ ተደረገ ማለት

ነው፡፡ የፓስፊክ ውቅያኖስ መሰረት አድርጎ የተካሄደው ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ደግሞ የእንግሊዝን

ልዕለ ሀያልነት በአሜሪካ ተክቶ አልፏል፡፡

ሶስተኛው የአለም ጦርነት ከተከሰተ ሚዛኑ ከምዕራቡ ወደ ምስራቅ የመሸጋገር እድሉ ሰፊ እንደሆነ

ትንበያዎች ያሳያሉ፡፡ ይህ የሶሶተኛው የዓለም ጦርነት የስበት ኃይል ደግሞ ቀይ ባህርና ህንድ

ውቅያኖስ ናቸው፡፡ ምክንያቱም የዓለም ንግድ አርባ በመቶ በላይና ነዳጅ ዘጠና በመቶ በላይ በዚህ

ቀጠና ስለሚተላለፍ ነው፡፡ ለዚህም ነው አሜሪካ፥ ቻይና፥ ራሽያ፣ ቱርክ እና የገልፍ ሃገራት ሀይሎች

በቀጠናዉ የሚያካሂዱት ፉክክርና ፍልሚያ እየሰፋና እየከረረ የሔደው፡፡

26
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሀይል ሚዛን ጨዋታ ዉሰጥ ከፍተኛ ድርሻ ያላት ሀገር ናት፡፡

በዚህም የቀጠናዉ የደህንነትና የፀጥታ ጉዳዮች በእጀጉ የሚመለከታት መሆኑን በቀላሉ መገንዘብ

ይቻላል፡፡ አገራችን የዓለምን ትኩረት የሳበውን የህዳሴ ግድብ መገንባቷ እና የባህር ሃይል በአዲስ

መልክ ማጠናከሯን ተከትሎ ምዕራባዉያን በቀና ከማየት ይልቅ ለግብፅ በመወገን በሀገራችን ላይ

ያልተገባ ፖሊሲ እንዲያራምዱ አድርጓቸዋል። ይህን ተከትሎ ባለፉት አራት ዓመታት ኢትዮጵያን

ከዉስጥም ከሩቅም ፖለቲካዊ፥ ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ ጫና በእጅጉ ፈትኗታል። ምዕራባዉያን

ድብቅ ፍላጎታቸዉን ለማሳካት በትግራይ ክልል የተፈጠረዉን ሁኔታና በህዳሴ ግድብ ግንባታ

ምክንያት የግብፅና ሱዳን ክስን እንደ ሰበብ አድርገው ጣልቃ በመግባት ኢትዮጵያን ለማዳከም

ተደጋጋሚ ሙከራዎችን አድርገዋል። ጫናዎቹ በመንግሥታት፥ በዓለም አቀፍ ተቋማት እና በሚዲያ

የሚካሄድ ዘመቻ ነዉ።

በመሆኑም የአስር አመቱ የፓርቲያችን እቅድ ከላይ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበና በፎክክክርና

በትብብር መካከል ሚዛኑን በመጠበቅ ማዕከላዊ ወይም ፕራግማቲክ ሆነን በዓለም ሜዳ ውስጥ

መጫወት እንዳለብን የግድ ይላል፡፡ ስትራቴጂያዊ እቅዱ ከወቅታዊ ዓለም አቀፋዊና ቀጠናዊ

ተለዋዋጭ ሁኔታዎች አንጻር በየጊዜው እየተቃኘ ሊሄድ የሚገባው መሆኑ እንዳለ ሆኖ ያለንበትን

ስትራቴጂክ ጂኦፖሊቲካዊ ሁኔታ መሰረት ያደረገ የረጅም ጊዜ እይታና ግብ ሊኖረው ይገባል፡፡

2.7. ሀገራዊ ለውጥና የብልፅግና ፓርቲ ዉልደት

የ1997ቱ ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ህዝብ ስርዓቱ የሚበጀው እንዳልሆነና በዴሞክራሲያዊ ምርጫ

ተሸንፎ ስልጣኑን ለማስረከብ ዝግጁ እንዳልሆነ በግልፅ የተረዳበት ጊዜ ነው፡፡ ከዚህ ጊዜ አንስቶ

በሀገራችን ህዝቦች ዘንድ በኢህአዴግ ላይ የመረረ ጥላቻና የለውጥ ፍላጎት አቆጥቁጧል፡፡ ከ10

አመት በኋላ በ2007 ዓ.ም የተካሄደው ሃገራዊ ምርጫና ውጤቱ ደግሞ ሀገራችን በሁሉም መስክ

እንደ ሀገር የመቀጠል አደጋ ጥያቄ ውስጥ የገባበትን ሁኔታ ፈጥሯል፡፡ አፈናና ኢ-ፍትሐዊነት

ያንገሸገሸው የኢትዮጵያ ሕዝብ በእነዚህ አመታት በሰላማዊ መንገድ ስርዓቱን ለመቀየር በየጊዜው

ያደረጋቸው ትግሎች የስርዓቱን ልክ አልባ አምባገነንነት ገሃድ እያወጡ ሄደዋል፡፡ ኢህአዴግ ለሕዝቡ

27
ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት ወይም ደግሞ የህዝቡን የለውጥ ፍላጎት መቀበል ያልቻለበት ሁኔታ

ተፈጥሯል፡፡

ይህ በአንድ በኩል የከረረ የህዝብ ምሬትና የለውጥ ፍላጎት፤ በሌላ በኩል ደግሞ አፈናን ምላሽ

ያደረገ ስርዓት የተፋጠጡበት የትግል ምዕራፍ በጎኑ ሶስተኛ የሃይል ሚዛን ፈጥሯል፡፡ በራሱ

በኢሕአዴግ ውስጥ የለውጥ ፍላጎት ያለው ሃይል የፍርሐት ቆፈኑን ገፍፎ የኢትዮጵያ ሕዝብ

ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ትግሉን አቀጣጥሏል፡፡ ምላሽ ያላገኘው የህዝብ ጥያቄና ፀረ ህዝብ

የሆነው የኢህአዴግ ምላሽ ተካርሮ ሀገራዊ ቀውስ ሊፈጠር ቋፍ ላይ በደረሰበት ጊዜ በራሱ በድርጅቱ

ውስጥ የተፈጠረው የለውጥ አመራር ህዝባዊ ጥያቄውን ፖለቲካዊ ቅርፅና አቅጣጫ በማስያዝ

ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ ጉልበቱን ቀስ በቀስ እያጠናከረ ህዝቡን ከጥፋት ሀገሪቱንም ከብተና የታደጉ

የሪፎርም እርምጃዎችን መውሰድ ጀምሯል፡፡ ውስጣዊ ለውጡን መቀበልም ሆነ ጫናውን መቋቋም

ያልቻለው ሕወሓት ሀገራዊ ለውጡን ለማደናቀፍ አቅሙ የፈቀደለትን ያክል ቢረባረብም የለውጥ

ኃይሉ ሀገራቱን ከቡድናዊ አምባገነኖች መንጋጋ በማላቀቅ ኢትዮጵያን ወደ አዲስ ምዕራፍ

አሸጋግሯል።

በወርሃ መጋቢት 2010 ዓ.ም ወደ ስልጣን የወጣው የለውጡ አመራር ሀገራችን የጀመረችውን

የመበታተን የቁልቁለት ጉዞ በመግታት በሪፎርም ማዕቀፍ ወደ አዲስ የለውጥ ምሕዋር እንድትሸጋገር

ያስቻሉ በርካታ እርምጃዎችን ወስዷል፡፡ የኢህአዴግ አባል እና አጋር የነበሩ ስምንት የፖለቲካ

ድርጅቶች ራሳቸውን አክስመው ብልፅግና ፓርቲን ለመመስረት የስምምነት ፊርማቸውን ያኖሩበት

ህዳር 2012 ዓ.ም ደግሞ የዚህ ሀገራዊ ለውጥ ልዩ ገፅታ ነው፡፡ ሀገራዊ የሆነ እና ሁሉንም

ብሄሮች ያቀፈው የብልፅግና ፓርቲ ምስረታ የለውጡ የከፍታ ጫፍ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡

ብልፅግና ፓርቲ ኢህአዴግን የመሠረቱትን ሶስት ፓርቲዎች እና ከተሟላ የፖለቲካ ተሳትፎና ከውሳኔ

ሰጪነት ተገልለው የነበሩ አጋር ፓርቲዎችን በማቀፍ የተፈጠረ ዉህድ ሃገራዊ ፓርቲ ነዉ። ዉህደቱ

የብሔሮችና ብሔረሰቦች መብቶችና ጥቅሞችን በተሟላ ሁኔታ ለማስጠበቅ እና እውነተኛ ህብረ-

ብሔራዊ ፌደራላዊ ስርዓት ለመዘርጋት መሰረት የተጣለበት ነው። በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ አንድ

28
ሀገራዊ ፓርቲ ተመስርቶ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በጠላትነት መተያየትን በማስቀረት አብሮ

የመስራት ልምድ የፈጠረ በሞዴልነቱ የሚጠቀስ ፓርቲ ነው ብልፅግና፡፡

ብልፅግና ቁልፍ ሀገራዊ ተቋማት ነጻና ገለልተኛ ሆነው እንዲደራጁ በህግ ማዕቀፍ ጭምር እንዲታገዝ

በማድረግ በተቋም ግንባታ መስክ መሰረታዊ ለውጦችን እያስመዘገበ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር የጸጥታና

ደህንነት ተቋማት፣ የፍትህ ተቋማት እና የዴሞክራሲ ተቋማት ሪፎርም ጎልቶ የሚታይ ነው፡፡

ከለውጡ በፊት ሀገራችን ከገጠሟት ችግሮች አንደኛው ህዝባዊ አገልግሎታቸውን በነፃነት መስጠት

ይገባቸው የነበሩ እነዚህ ተቋማት የአንድ ፖለቲካ ቡድን ፍላጎት ማስፈፀሚያ ሆነው ማገልገላቸው

ነው፡፡ በለውጡ ተቋማቱ ከሶስተኛ ወገን ያልተገባ ጣልቃ ገብነትና ጫና ተላቀው የተሰጣቸውን

ተልዕኮ ከህገ መንግስትና ከህዝብ ወገንተኝነት በመነጨ ሁኔታ ብቻ ለመፈፀም የሚያስችሏቸው

ማስተካከያዎች ተደርገዋል፡፡

ሌላኛው የለውጡ ስኬት በዲፕሎማሲ መስክ የተመዘገበው ነው፡፡ ብልፅግና ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ

አቅጣጫ በመከተሉ በውጭ ሃገራት በአስከፊ የሰብአዊ አያያዝ ውስጥ ለነበሩ ዜጎቻችን መድረስ

ተችሏል፡፡ በውጪ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሀገር ባለቤትነት መንፈስ

ለሀገራቸው ሁለንተናዊ ድጋፍ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ፡፡ ጎረቤት ተኮር የሆነው የውጪ ግንኙነት

ፖሊሲያችንም መልካም ውጤት ማስመዝገብ ጀምሯል፡፡ በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል የተፈጠረው

መልካም ጉርብትና በሁለቱ ሀገራት መካከል በትብብር ላይ የተመሰረተ አዲስ ግንኙነት እንዲፈጠር

ከማስቻሉ በዘለለ በቀጠናው ባሉ ሀገራት መካከልም አዎንታዊ ግንኙነት እንዲፈጠር መሰረት ጥሏል፡

ሀገራዊ ለውጡ የተጠቀሱትንና ሌሎች በርካታ ውጤቶች ማስመዝገብ የቻለው በግዙፍ ተግዳሮቶች

ውስጥ እያለፈ ነው፡፡ ባለፉት አመታት ሀገራችን ከገጠሟት አደጋዎች ቀዳሚው አሸባሪው የህወሃት

ቡድን ለውጡን ለመቀልበስና ሀገር ለማፍረስ ሲያደርግ የነበረው እኩይ እንቅስቃሴ ነው፡፡ ህወሃት

የኢትዮጵያን ብልፅግና ማየት ለማይፈልጉ የውጪ ሃይሎች ተላላኪ በመሆንና በሀገር ውስጥ

በፅንፈኝነት ከናወዙ ቡድኖች ጋር በማበር በሀገር መከላከያ ሰራዊታችን ላይ የክህደት ተግባር

ከመፈፀም ጀምሮ ሀገራችን የህልውና አደጋ ደቅኖብናል፡፡ በህዝባችን የተባበረ ክንድ የህልውና

አደጋውን መቀልበስ የተቻለ ቢሆንም ችግሩን ከስር መሰረቱ በዘላቂነት መፍታት የሚጠይቅ ነው፡፡
29
ከዚሁ በተያያዘ ኢትዮጵያ በቀጠናው የፈጠረችውን በትብብር ላይ የተመሰረተ የሃይል ሚዛንና

ቀጠናዊ ትብብር ለማኮላሸትና የህዳሴ ግድቡን ግንባታ ለማስተጓጎል የሚደረገው የአንዳንድ ሀገራት

ጫናም እንደ ተግዳሮት ሊወሰድ የሚችል ነው፡፡

የሀገራችን የፖለቲካ ምህዳር ሰፍቶ በሰለጠነ መንገድ በሰላማዊ ሁኔታ የሃሳብ ትግል የሚደረግበት

ሁኔታ ቢመቻችም ልዩነትን በሃይልና በሴራ እንጂ በንግግር የመፍታት ልምዳችን አልዳበረም፡፡ ዋልታ

ረገጥ የፖለቲካ አስተሳሰብን ጨምሮ በሁሉም መስክ የሚታይ ጽንፈኝነት እየተቀረፈ ካልመጣና

ሕብረብሔራዊ የወንድማማችነትና እህትማማችነት አስተሳሰብ ካልጎለበተ በስተቀር ሀገራዊ ለውጡ

የተሟላ ብልፅግናን ማረጋገጥ አይቻለውም:: የዋጋ ግሽበት፣ የኑሮ ውድነት፣ ስራ አጥነትና ተያያዥ

ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች እንዲሁም እንደ የኮሮና ወረርሽኝ፣ የአንበጣ መንጋ እና ሌሎችም

ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች በህዝቡ ላይ የፈጠሩት ጫና በጣም ከፍተኛ ነው፡፡ የለውጥ

ጉዞውም የሚጠበቅበት ያህል ውጤት እንዳያስመዘግብ እንቅፋት ሆነው ቆይተዋል፡፡

በመሆኑም ለውጡን የተጋረጡበትን ችግሮች የማስወገድና የተገኙ ድሎችን በማስፋት የህዝብና

የሀገርን ዘለቄታዊና ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚያረጋግጡ ስትራቴጂያዊ ግቦችን ቀርፆ የመተግበር

አስፈላጊነት ለዚህ ዕቅድ በመነሻነት ተወስዷል፡፡

2.8. የብልፅግና ፓርቲ ሁኔታ

2.8.1. የብልፅግና ፕሮግራምና መተዳደሪያ ደንብ

ብልፅግና ፓርቲ የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ፕሮግራም ቀርጾ ወደ ተግባር የገባ ፓርቲ

ነው፡፡ ብልጽግና የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ እንዲሁም የዲፕሎማሲ አቅጣጫዎች አስቀምጦ

በተጨባጭ የህዝቡን መሰረታዊ ቸግሮች ለመቅረፍ ቁርጠኛ አቋም ያለው ፓርቲ ነው፡፡

የብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካ ፕሮግራም ጠንካራና ቅቡልነት ያለውን የብሔር ማንነትና ሀገራዊ

አንድነትን ሚዛን የጠበቀ ዘላቂ ሀገረ መንግስት መገንባት ነው፡፡ የህዝቦች ልማት፣ ነጻነትና እኩልነት

ፍላጎቶች ተረጋግጦ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸው ተከብሮላቸው

የሚኖሩባት፣ ህብረ-ብሔራዊ እንድነቷ የተረጋገጠ፣ ፌዴራላዊት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ጽኑ

30
መሰረት ላይ ማቆም ነው፡፡ የብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካ ግቦችም ጠንካራ ቅቡል ሀገረ መንግስት

በጽኑ መሰረት ላይ ለመገንባት የሚያስችል ሀገራዊ መግባባት መፍጠር፤ በተቋማትና ሕዝባዊ ባህል

ላይ የቆመ የዴሞክራሲ ስርዓት መገንባት እና ዘላቂና አዎንታዊ ሰላም ማረጋገጥ ነው፡፡

የፓርቲው ኢኮኖሚ ፕሮግራም ልማትና ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ አካታች የኢኮኖሚ

ስርዓት መገንባት ሲሆን ግቦቹ ደግሞ የብዙሃ ዘርፍ ኢኮኖሚ መዋቅር መገንባት፣ጥራት ያለው

ኢኮኖሚ ልማት እና ምርታማነትን መሰረት ያደረገ ማህበራዊ ፍትህ ማረጋገጥ፣ ሀብት ፈጠራን

የሚያሳድግ ዕውቀት መር ኢኮኖሚ መገንባት እና ከተሜነትና የከተማ ልማት በማስፋፋት የህዝቦችን

መሰረታዊ ፍላጎቶች በዘላቂነት ለመሟላት የሚያሰችል ሁለተናዊ ብልፅግና ማረጋገጥ ነው፡፡

በማኅበራዊ ዘርፍ ሁለንተናዊ ብልጽግናን የሚረጋግጥ አካታች ማህበራዊ ልማት እውን ማድረግ

ሲሆን ግቦችም ፍትሃዊነት፣ ጥራት፣ አካታችነት እና አግባብነት ያለው የትምህርት ስርኣት ማረጋገጥ፣

መከላከልና ሀክሞ የማዳን መሰረት ያደረገ የጤና ስርዓት መዘርጋት፣ የሀገራችንን አቅም ያገናዘበ

የማህበራዊ ጥበቃ ስርዓት መዘርጋት እና የሴቶችና ወጣቶችን የፖለቲካና ኢከኖሚ ተሳትፎና

ተጠቃሚነት ማጎልበት ነው፡፡

ፓርቲው በውጭ ግንኙነት ፕሮግራሙ ሀገራዊ ክብር ማዕከል ያደረገ የውጭ ግንኙነት የሚከተል

ሆኖ ሀገራዊ ክብርን የሚያረጋግጥ የውጭ ግንኙነት፣ ለትብብርና ለጋራ ተጠቃሚነት ትኩረት

በመስጠት አጋሮቻችንን ማስፋት፣ የብዙዮሽ ትብብር ተቋማት ተሰሚነት መጨመርና ፖለቲካዊ

ነጻነትን ማስከበር፣ ለጎረቤት ሀገራት ትኩረት በመስጠት ዘርፈ ብዙ የጋራ ተጠቃሚነት ማረጋግ፣

ኢትዮጵያውያንና ትውልድ ኢትዮጵያውያን ተሳትፎ ማሳደግና ሃገራዊ ክብርንና ጥቅም የሚያስጠብቅ

የውጭ ግንኙነት የመፈጸም አቅም መገንባት ግብ ያደረገ ነው፡፡ ስለሆነም የብልጽግና የፖለቲካ፣

የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊና የውጭ ዲፕሎማሲ ዓላማዎችን በዝርዝር ያካተተው ፕሮግራም በአንደኛ

መደበኛ ጉባኤ ጽድቆ ሥራ ላይ መዋሉ እንደመነሻ ተወስዷል፡፡

የብልጽግና መተዳደሪያ ደንብ በየደረጃ ባለው መዋቅር ውስጥ የሚሠሩ አመራርና አባላት ተግባርና

ኃላፊነት፣ የውሳኔ አሰጣጥና አፈፃፀም ሂደት እንዲሁም መዋቅሮቹ የሚጠቀሙባቸው የአሠራርና

የአመራር መርሆዎችንና እሴቶች በዝርዝር በማስቀመጥ ህጋዊና ተቋማዊ ሥርዓት ያለው እና

ዓላማዎችን በአስተማማኝ ሁኔታ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ነው፡፡


31
የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ አስተማማኝ ዴሞክራሲያዊ ሁኔታ በመፍጠር ለዳበረ የሀሳብ አንድነት

የሚያበቁ መሰረታዊ አምዶች የተቀመጡበት በመሆኑ መላ የመዋቅሩ አካላትና አባላት በሚገባ

እንዲገነዘቡትና ለተግባራዊነቱ መታገል እንዲችሉ እንደመነሻ ተወስዷል፡፡ የእቅድ ትግበራ ሂደቱም

በፓርቲው ህግና ደንብ መሰረት የሚፈፀም መሆኑ በየጊዜው ማረጋገጥ ስለሚገባ የስትራቴጂክ

እቅዱ የክትትልና ድጋፍ ስርዓት ይህንኑ ታሳቢ ማድረግ ይኖርበታል፡፡

2.8.2. የአመራርና አባላት ሁኔታ

አመራሩ በሕዝብ ግፊትና በውስጠ ድርጅት ትግል የተገኘውን ለውጥ ለማስቀጠል የተለያዩ ተግባራትን

እያከናወነ ነው፡፡ የተለያዩ የጥፋት ዘመቻ ቢከፈትበትም በአገራችን እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶች በግንባር

ቀደም እየመራ የሚገኝ ሃይል ነው፡፡ አገሪቱን ወደ ሰላማዊ፤ ዴሞክራሲያዊና በህዝብ ዘንድ ተአማኒነትን

ያተረፈ 6ኛውን አገራዊ ምርጫ በማሳካት መንግስትን የመምራት ዕድል እንዲያገኝ የመሪነት ሚናውን

ተጫውቷል፡፡ ይሁን እንጂ በከፍተኛ አመራሩ መካከል የአመለካከትና የተግባር አንድነት አለመኖር፤

የጠራ አመለካከት በሚፈልጉ ሀገራዊ ጉዳዮችና በፓርቲው እሳቤዎች ላይ የጋራ መግባባት

አለመፍጠር፤ ህብረ-ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነትን ለማጠናከር ከመስራት ይልቅ ልዩነት ተኮር

መሆን፤ ለስልጣን ያለ የተዛባ እይታ፣ ሌብነትና ብልሹ አሰራር በእጅጉ ይፈትኑታል፡፡ በተጨማሪም

አመራሩ ራሱን ከህዝበኝነትና አክራሪነት ማላቀቅ አቅቶት የአክቲቭስት ሚና የተጠናውተው መሆኑ፣

ለችግሮች ቀድሞ ፓለቲካዊ ትርጉም በመስጠት የመረዳትና የመተንተን እንዲሁም ችግሮችን

በሙሉነታቸው አይቶ ቀጣይነት ያለው የፓለቲካ ስራዎች ያለመስራት ችግሮች፣ ይፈትኑታል፡፡

አባላችን በርካታ ተግባራትን በተለይ ከጸጥታና ሰላም ጋር በተያያዘ ለመስራት የሚያደርጋቸው ጥረቶች

አሉ፡፡ የአባላችን ቁጥር በአሁኑ ወቅት ከ11 ሚሊዮን በላይ መሆኑ አቅሙ ከተገነባ ብዙ ለውጥ

ማስመዝገብ የሚችል ኃይል ነው፡፡ ይሁን እንጂ የብዛቱ ያሕል ጥራት የሌለው ሃይል መሆኑን

በተደጋጋሚ የታየ ጉዳይ ነው፡፡ የጎራ መደበላለቅ፣ በህገወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርና ህገወጥ

ግንባታን የመሳተፍ፣ ከጠላት ጋር መወገን፣ ጽንፈኝነት፣ ወዘተ የሚታይበት ነው፡፡

በአባላትና በአመራሩ የሚየታዩ ጥንካሬዎችና ድክመቶች በፓርቲው እቅድ አፈፃፀም ውስጥ ቀጥተኛ

ተፅዕኖ ያሳድራሉ፡፡ በመሆኑም በስትራቴጂክ እቅዱ ውስጥ በአመራሩ መካከል፣ በአመራሩና በአባላት

32
መካከልና በተቋማት መካከል የተጠናከረና የተናበበ ግንኙነት እንዲኖር፣ አመራሩ ውስጥ የሚታዩ የስነ

ምግባር፣ የአቅምና የአመለካከት ጉድለቶችን ማረምና ለላቀ ውጤታማነት የሚያበቃ የግንባታ ስራ

መፈፀም ታሳቢ ተደርጓል፡፡

2.8.3. የብልፅግና ፓርቲ አንደኛ ጉባዔ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች

ከየካቲት 28 እስከ መጋቢት 3 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ከፈተና ወደ ልዕልና በሚል መሪ ሃሳብ

ሲከናወን የቆየው የመጀመርያው የብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ ባለፉት አራት የለዉጥ ዓመታት በተመዘገቡ

ድሎችና ባጋጠሙ ተግዳሮቶች ላይ በጥልቀት መክሮ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል፡፡

ስኬት ከተመዘገበባቸዉ ጉዳዮች ዉስጥ፥ የብልጽግና ምስረታ፣ ለለዉጡ ወሳኝ የሆኑ የተቋማት

ግንባታ፣ ስኬታማ ምርጫ በማካሄድ በህዝብ ዘንድ ቅቡልት ያለው መንግስት መመስረት፣ አረንጓዴ

አሻራ ልማት፣ ለብዝሀ ኢኮኖሚ ልማት የተሰጠው ትኩረት፣ የኢትዮ ኤርትራ ግንኙነትና የቀጠናው

ትብብር፣ ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ፣ የታላቁ ህዳሴ ግድብ አፈጻጸምና የተገኘው ዉጤት ይገኙበታል።

በሌላ መልኩ ደግሞ የህዝባችንን አኗኗር በእጅጉ ያወሳሰበውና በአገረ መንግስቱ ቀጣይነት ላይ

የህልውና ስጋት ሆኖ የነበረው የአሸባሪው ኃይል ጥፋት፣ ጽንፈኝነት፣ የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት እና

የተፈጥሮ አደጋዎች የፈጠሩት አሉታዊ ጫና እና የኑሮ ውድነት እንደዋነኛ ተግዳሮት ተለይተው በስፋት

ተመክሮባቸዋል፡፡ ከህዝብ አገልግሎት ጋር በተያያዘ የሚነሱ ቅሬታዎች እና የመልካም አስተዳደር

ችግሮች በተለይም ከሌብነት እና ከስርቆት ጋር ህዝቡን ያማረሩ ጉዳዮችና በየአካባቢ የሚስተዋሉ

የጸጥታ ችግሮች በጥልቀት ተገምግመዋል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም የውስጠ ፓርቲ ፖለቲካዊ ጤንነት

መጓደል፣ የአመራርና አባላት ጥራት ችግር በሀገራችንና ህዝባችን ላይ ያስከተለው አሉታዊ ተፅዕኖ

ተገምግሞ ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል፡፡ የብልጽግና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ አቅጣጫ

ለውጡን ማጽናት ላይ መሰረት ያደረገ ነው፡፡ ለውጡ በባህሪው ነባሩን የፖለቲካ አካሄድና አደረጃጀት

የሕዝብ ፍላጎትን በሚያሟላ መልኩ ለማስተካከል አዳዲስ አካሄዶችና አደረጃጀቶችን ማለማመድ፣

ማስረጽ እና ማዋሐድ የሚፈልግ ረጅም ሂደት ነው።

በመሆኑም ለውጡን ለማጽናት ታሳቢ የተደረጉ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች፡-

33
➢ ጠንካራ ፓርቲ ለመገንባት የዓላማ እና የተግባር አንድነትን ማጠናከር፤ የውስጠ ድርጅት

ዴሞክራሲውን በማጠናከር የፓርቲ የህልውናው አዕማዶች የሆኑትን ሐሳቦቹን፣ አደረጃጃቱን

እና አባላቱን ለማጥራት በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ በተጨማሪም

የተፎካካሪ ፓርቲዎችን ለመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ካላቸው ሁለንተናዊ አስተዋጽዖ አንጻር፣

በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ መሥራት እንደ አቅጣጫ ተይዟል።

➢ ዘላቂ ሰላም ግንባታ እና ሀገራዊ አንድነትን ለማጠናከር ፓርቲው ካለፉት ታሪኮቻችን

ውስጥ መልካሞቹን እንደ ወረት በማካበት የተሠሩ ስሕተቶችን ደግሞ በማረም ለቀጣዩ

ትውልድ የበለጸገች ኢትዮጵያን ማሰረከብ ግብ አድርጎ ይሰራል፡፡ በመሆኑም ያለፉትን

ቁርሾዎቻችንና ቅያሜያችንን በዕርቅና በይቅርታ ለመሻገር፣ በኢትዮጵያውያን መካከል

ብሔራዊ መግባባት ለመፈጠር እንደሚሰራ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

➢ በውጤት የሚገለጽ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት ነባር ጅምሮችን በማስፋት ሕዝብን

በከፍተኛ ምሬት ውስጥ እየከተቱ ያሉ አስተዳደራዊ ችግሮችን በማረምና፣ መልካም የሕዝብ

አስተዳደርና የመልማት መብቶችን በተጨባጭ በመመለስ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ

ማጠናከር በቁልፍነት ተወስዷል፡፡

➢ ኢኮኖሚያዊ መልሶ መቋቋምና የ10 ዓመት ዕቅድ ትግበራ በተመለከተ በዕቅዱ በተቀመጠው

አቅጣጫ መሰረት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጠናክሮ በመተግበር ኢኮኖሚውን በፈጣን

የዕድገት ምሕዋር ውስጥ በመክተት የሕዝብን መሠረታዊ የኢኮኖሚ ጥያቄዎች ለመመለስ

ፓርቲው አቅጣጫ አስቀምጣል፡፡ ለዚህም ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት

ለማድረግ ሁሉም አመራር ዕቅዱን በተቀናጀ ሁኔታ እንዲተገበር ውጤታማ የሆነ የክትትልና

የምዘና ሥራ መሥራት እንደሚዘረጋ ግልጽ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

➢ ሉዓላዊነትና ድህረ-ጦርነት ሰላምን ለማስጠበቅ በድህረ ጦርነቱ በመልሶ ግንባታ ውስጥ

ዘላቂ ሀገር ግንባታ ስራዎችን በመስራትና ጫናን ተቋቁሞ ሉዓላዊነትን ለማጽናት የሚያስችል

የዲፕሎማሲ ዐቅም በመገንባት፤ ጫናዎችን እና ትንኮሳዎችን በመመከት ኢትዮጵያ ሉዓለዊነቷ

እና ግዛታዊ እንደነቷ ለሁል ጊዜም ተጠብቆ እንዲኖር ማድረግ በፓርቲው ጉባኤ

ተሰምሮበታል፡፡

34
በአጠቃላይ ጉባኤው ያስቀመጣቸው የውስጠ ፓርቲ ጉዳዮች፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና

ዓለማቀፋዊ ባህሪ ያላቸው አቅጣጫዎች ለአስር ዓመቱ የፓርቲው ስትራቴጂያዊ ዕቅድ የመጀመሪያ

ሁለትና ሶስት አመታት የአፈፃፀም አቅጣጫዎች እንደ መነሻ ተደርገው የሚወሰዱ ይሆናሉ፡፡ በእነዚህ

አፈፃፀሞች ላይ ተመስርተውና አዳዲስ ውሳኔዎችን በማከል የሚካሄዱ ሌሎች ተከታታይ የፓርቲው

ጉባዔዎች የ10 አመቱን እቅድ ዘመን በመሸፈን መነሻ ሆነው ያገለግላሉ፡፡

2.9. የስድስተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ እንድምታዎች

በኢፌዴሪ ህገመንግሥት መሠረት የመንግሥት ሥልጣን የሚመነጨዉ በህዝቡ ነፃ ፈቃድ ብቻ

እንደሆነ ተደንግጓል። 6ኛዉ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በሀገራችን ለረጅም ዓመታት ሲንከባለል

የቆየዉን የዲሞክራሲ ጥያቄ መልስ የሰጠ ክስተት ሆኖ አልፏል፡፡ ይህ ምርጫ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ

ጊዜ በሠላማዊ፥ ዲሞክራሲያዊ የተመረጠ መንግሥት እንዲኖራት በማድረግም ታሪካዊ ነበር።

6ኛዉ ሀገራዊ ምርጫ ሠላማዊ፥ ዲሞክራሲያዊና በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነትን ያረጋገጠ እንዲሆን

ወሳኝ የሆኑ የቅድመ ምርጫ እርምጃዎች ተወስደዋል። የፖለቲካ እስረኞች መፈታትና ዉጪ የሚገኙት

ተፎካካሪ ፓርቲዎች ወደ ሀገራቸዉ ገብተዉ በሠላማዊ መንገድ እንዲታገሉ፥የተዘጉት ሚዲያች

ተከፍተዉ በነፃነት እንዲዘግቡ፥ ለፖለቲካ ነፃ እንቅስቃሴ አሳሪ የሆኑ ህጎች አንዲሻሻሉ ተደርገዋል።

በዚሁ በተፈጠረዉ ምቹ ሁኔታ የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫው ሂደት በነፃነት ተሳትፈዋል። ነፃና

ፍትሐዊ ምርጫ በማድረግ ህዝቡ የሚፈልጋቸዉን መሪዎቹን ወደ ሥልጣን የሚያመጣበትን ምቹ

ሁኔታ ለመፍጠር ነፃና ገለልተኛ ምርጫ ቦርድ ተቋቁሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫዉ ያለምንም

ተፅኖ የያዙትን የፖሊሲ አማራጮች ለህዝቡ እንዲያቀርቡ ሆነዋል።

በዚህ 6ኛዉ ሀገራዊ ምርጫ ላይ የህዝቡ ተሳትፎ በሀገራችን ታርክ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ

ለዝናብ ብርድና ፀሐይ ሳይበገር ረጃጅምና አሰልቺ ሰልፎችን እስከ ለሊት ድረስ ተቋቁሞ በከፍተኛ

ትዕግሥትና ተነሳሽነት ይወክለኛል ያለዉን ፓርቲ መርጧል። ይህ የህዝቡ የነቃ ተሳትፎ በሀገራችን

የዲሞክራሲ መሠረት እንዲጣል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ከማበርከቱም አልፎ ከዉጪ እና ዉስጥ

በመቀናጀት የምርጫን ሂደት በማደናቀፍ የሀገራችንን ህልዉና ስፈታተኑ ለነበሩት ሃይሎች ከፍተኛ

ትምህርት የሰጠም ነበረ።

35
ብልፅግና እንደ ገዥ ፓርቲነቱ ምርጫን በተመለከተ ያስቀመጣቸዉ ሁለት ዋና ዋና ግቦች ማለትም፥

በሀገራችን ታርክ ነፃ፥ ፍትሐዊና ተዓማኒ ምርጫ እንዲሆን እና ከሌሎች ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር

በእኩልነት ተወዳድሮ አብላጫ ወንበር በማግኘት መንግሥትን በመመሥረት ራዕዩን እዉን ማድረግ

ነበረ።ከዚህ አንፃር በኢትዮጵያ ታርክ ዲሞክራሲያዊ ምርጫን በማሳካት አድስ ምዕራፍ ተመዝግቧል።

ፓርቲያችን ፕሮግራሙንና ፖሊሲዎቹን የያዘ ማኒፌስቶ ለህዝቡ በማቅረብ የምርጫ ሂደቶችን ሁሉ

በማለፍ ከፍተኛ የህዝብ ድምፅ በማግኘት ሀገር የመምራት ሀላፍነትን ተረክቧል። ራዕዩንም ተፈፃሚ

ለማድረግ ትልቅ ዕድልና አጋጣሚ መፈጠሩ ለዕቅዱ እንደ መነሻነት ተወስዷል።

36
ምዕራፍ ሦስት፡- የብልፅግና ፓርቲ ርዕይ፣ ተልዕኮ፣ እሴቶችና
መርሆዎች

3.1. የብልጽግና ፓርቲ ርዕይ (Vision)

ሀ/ በ2024 ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት ማድረግ የሚችል ፓርቲ ሆኖ ማየት፣

ለ/በ2024 ኢትዮጵያን አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት ማድረግ የሚያስችል ድርጅታዊ ጥንካሬና

ብቃት የተላበሰ በትብበር መርህ የሚሰራ የሀጉራችን ቀዳሚ ፓርቲ ሆኖ ማየት፣

ሐ/

3.2. የብልፅግና ፓርቲ ተልዕኮ (Mission)

የውስጠ ፓርቲ አንድነትና ዴሞክራሲን በማጠናከር እና የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚያረጋግጡ

የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና የውጭ ግንኙነት እቅዶችን ብቃት ባለው አመራር በመፈፀም

በኢትዮጵያ ህዝቦች ዘንድ ቅቡልነት ያለው ዴሞክራሲያዊ ህብረ-ብሔራዊ የፌደራላዊ ሥርዓት

መገንባት፤

3.3. የብልፅግና ፓርቲ ሀላፊነት (Mandate) እና መዋቅር

የብልፅግና ፓርቲ የተረጋጋና ጊዜዉን የዋጀ ጠንካራ አደረጃጀትና አሠራርን እንዲሁም ዉስጠ ፓርቲ

ዲሞክራሲን በማረጋገጥ ስትራቴጂውን በዉጤታማነት እንዲፈፀም ማስቻል፤ ጠንካራ የአመራር

ስምርትን ማረጋገጥ፤ ብቃት ያላቸዉ ተቋማት እንዲፈጠሩ ማድረግ፣ የሀገር ግዛትና ሉዓላዊነት፤

የዜጎች ክብር፤ ያደገ የዲሞክራሲ ባህል የጠበቀ ትሥሥርና የተዋሄደ ማህበረሰብ እዉን እንዲሆን

በማድረግ ዘላቂ ሠላም፤ልማትና መልካም አስተዳደር በሀገሪቱ እንዲሰፍን የማስቻል ተልዕኮ የተሸከመ

ፓርቲ ነዉ።

በዚህ መሠረትም ከፖለቲካ ፕሮግራሙ አንጻር በህገ-መንግስቱ የተደነገገውን የዲሞክራሲ

መርሆዎችን እና እውነተኛ የመድበለ ፓርቲ ስርዓት እውን ማድረግ ሲሆን ለሁሉም ዜጎች

የምትስማማ ሁሉንም ኢትዮጵያዊያን የምትመስል የበለጸገች የብሔሮችን መብት ከግለሰብ መብቶች

37
ጋር አጣጥማ የምታስጠብቅ ጠንካራ ፌደራላዊት፤ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን የመገንባት’

ሀላፊነት ተጥሎበታል።

ኢኮኖሚን በሚመለከትም ጥራት ያለው፤ ዘላቂና ፍትሐዊ የኢኮኖሚ እድገትና ልማት ማምጣት፤

ትውልድን ከፍፁም ድህነት ወደ ፍፁም ብልፅግና ማሻገር ነው፡፡ የኢኮኖሚ ጥራት በአሳታፊነቱና

በቀጣይነቱ ይገለፃል፡፡ አሳታፊነት ሲባል ፍትሐዊ የልማት ተጠቃሚነት፤ ፍትሐዊ የስራ ዕድል

እንዲሁም ፍትሐዊ የገቢ ክፍፍል የሚመለከት ሲሆን ቀጣይነት ደግሞ ዕድገት የአንድ ወቅት ክስተት

ከመሆን አልፎ የመጪው ትውልድን ብልፅግና ሳያጓድል ትውልድን ከፍፁም ድህነት ወደ ፍፁም

ብልፅግና የሚያሻግር ሀላፊነት አለበት፡፡

ማህበራዊ ዘርፉ ዜጎች እምቅ ችሎታቸውን በመጠቀም ሀብትን በመፍጠርና በፍትሐዊነት ለመጠቀም

የሚያስችላቸውን የትምህርት፤ የጤና እና ሌሎች አገልግሎቶች በእያሉበት በጥራት እንዲደርሳቸው

ማድረግ፤በማህበራዊ ልማት መስክ መልካም ሀገራዊ እሴቶችና ባህሎች በማዳበር፤ በስነ-ምግባር

የታነጸ ትውልድ ማፍራት፤ ለኑሮ ምቹ የሆነ አከባቢን እንዲፈጠር የማድረግ ሃላፊነት አለበት።

የህግ መሠረቱ ሲታይም በኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-

ምግባር አዋጅ 1162/2011ዓ.ም ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተሰጠው ስልጣን መሰረት ለብልፅግና

ፓርቲ ሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ታህሳስ 11/2012ዓ.ም ተሰቶታል፡፡ በዚህ

አዋጅ መሰረት ፓርቲው መብት እና ግዴታ ተጥሎበታል፡፡ የኢፈዴሪ ህገመንግሥት አንቀፅ 29

ማንኛዉም ሰዉ ያለ ማንም ጣልቃ ገብነት ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ ነፃነት እንደለዉ ይደነግጋል።

ህገመንግሥቱ ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት እና የመገናኛ ብዙሃን ነፃነት ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት

ግንባታ ያላቸዉን ልዩ ቦታ ከግምት ዉስጥ በማስገባት የተለየ ከለላ ወይም የህግ ጥበቃ

እንደሚደረግላቸዉ ያስቀምጣል።የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃን ህግጋት ከኢፌዴሪ ሕገመንግሥት፤

አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የሰብዓዊ መብት ስምምነቶችና ሰነዶች የተጣጣሙ መሆን እንዳለባቸዉ፤

እንዲሁም መንግሥት የሚወስዳቸዉ ማናቸዉም እርምጃዎች ከነዚሁ ህግጋቶች ጋራ የተጣጣሙ

መሆናቸዉን ማረጋገጥ እንዳለበት በመገናኛ ብዙሃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 ተደንግጓል።

38
ምርጫን በተመለከተ የመገናኛ ብዙሃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 እንዳስቀመጠዉ፤ ማንኛዉም

የብሮድካስት ባለፈቃድ አግባብ ባለዉ ህግ መሠረት ተመዝግበዉ ለሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች

በምርቻ ወቅት ዓላማቸዉንና ፕሮግራማቸዉን ለህዝብ እንዲያስተዋዉቁ፤ መግለጫ እንዲያስተላልፉ

የምርጫ ቦርድ በሚሰጠዉ መመሪያ/አቅጣጫ መሠረት ነፃ የአየር ጊዜ በፍትሃዊነት እንዲመድቡ

ተደንግጓል። የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ወቅትን ሳይጠብቁ በማናቸዉም ጊዜ በልዩ ልዩ ጉዳዮች

ላይ ያላቸዉን ሃሳብና አመለካከት እንዲያንሸራሽሩ በተለይም በሕዝብ መገናኛ ብዙሃን በፍትሃዊነት

እንዲስተናገዱ በአዋጁ ተካቷል። በአዋጁ አንቀፅ 71(2) መሠረት ማንኛዉም የብሮድካስት

አገልግሎት ባለፈቃድ በምርጫ ወቅት የሚያቀርቧቸዉ የዜና ዘገባዎች፤ ትንታኔዎች፤የዉይይት

መሰናዶዎች ሚዛናዊና የተሟላ እይታ እንዲኖራቸዉ፤ የመራጮችንና የፖለቲካ ፓርቲዎችን ድምፅ

በአግባቡ ማካተት እንደሚኖርባቸዉ ያስቀምጣል።

በአዋጁ አንቀፅ 71(10) መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎች ወይም የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎች የምርጫ

ማስታወቂያዎቻቸዉና በነፃ የአየር ጊዜ የሚያስተላልፏቸዉ መልዕክቶች የምርጫ ህግና ደንብን

ያከበረ ስለመሆኑ የማረጋገጥ ሃላፊነት ከተጠያቂነት ጋር ይኖርባቸዋል በሚል ተደንግጓል።

በመተዳደሪያ ደንቡ በሚወሰነው መሠረት የፖለቲካ ሥራውን የሚመሩ፣ ውሣኔ የሚሰጡ እና

የሚያስፈፅሙ አካላት ማቋቋምና የአመራር አካላት መምረጥ፣ ፓርቲው ሥራውን ለማካሄድ በሀገሪቱ

ውስጥ በየትኛውም ቦታ ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤት ሊያቋቁም እንደሚችል በህግ ሥልጣን ተሰጥቶታል፡

ፓርቲው የአባላቱን ብዛት፣ የፆታ ስብጥር፣ ዓመታዊ ሪፓርትና የኦዲት ሪፖርት ማቅረብ፣ የፓርቲውን

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ማሳወቅ፣ ግንባር ለመፍጠር ወይም ለመዋሃድ ወይም ለመቀናጀት

የሚደረጉ ስብሰባዎች ሲኖሩ ቦርዱ በስብሰባው ላይ እንዲገኝ የማሳወቅ፤ ፓርቲው እንደየአግባብነቱ

በኦዲተር ወይም በሂሳብ ባለሙያ የተረጋገጠ የሃብትና ዕዳ መግለጫ በፓርቲው መሪ ፊርማ

ለቦርዱ የጽሑፍ ሪፖርት የማቅረብ ግዴታ እንዳለበት ተደንግጓል፡፡ ሆኖም የብልጽግና ሴትና ወጣት

ሊጎች ከብልፅግና ፓርቲ ጋር ያላቸውን ግንኙነትና ተጠሪነት የሚያሳይ የህግ ማዕቀፍ አልተቀመጠም፡

39
3.4. የብልፅግና ፓርቲ እሴቶች (Core Values)

የዜጎችና የህዝቦች ክብር

የዜጎችና የህዝቦች ክብር ሲባል ማንኛውም ቡድን ወይም ግለሰብ ከሌሎች የተለየ ተጠቃሚ አሊያ

ተጎጂ እንዳይሆን መሥራት ማለት ነው፡፡ ብልፅግና በዋነኝነት በሀገር ውስጥ የፍትሕና የብልፅግና

ጥያቄዎችን በመመለስ እንዲሁም ከሀገር ውጭ የኢትዮጵያውያንን ደኅንነትና መብት በማስከበር

ኢትዮጵያውያን በሀገራቸውና በማኅበረሰባቸው ክብር እንዲሰማቸው ማድረግ ነው። በዜግነት ክብር

የኢትዮጵያን ስም ከፍ ማድረግ፤ ከፍ ያለች ሀገር በመገንባት ደግሞ የዜግነትን ክብርን ወደ ላቀ

ደረጃ ማድረስ እንደሚገባ ብልጽግና ፓርቲ ያምናል፡፡

ነፃነት

ነፃነት ሲባል አንድ ሰው የፈለገውን እንዲያምን፣ እንዲያመልክ፣ ሐሳቡን እንዲያሠራጭ፣ ከፈለገው

ጋር እንዲሰባሰብና እንዲደራጅ ነጻነት አለው ማለት ነው። ስለሆነም ብልፅግና ፓርቲ የኢትዮጵያን

ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታት ይቻል ዘንድ ነጻነትን አንዱ ዕሴት

አድርጎ ይንቀሳቀሳል፡፡

ፍትሕ

ፍትህ ሲባል ሁሉም ኢትዮጵያውያንን በእኩል ዓይን የሚያይና የሚዳኝ፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሕግ

ፊት በእኩል የሚታዩበትና በፍትሐዊነት ተጠቃሚ የሚሆኑበት፣ የብዙኃንም ሆነ አነስተኛ ቁጥር

ያላቸው ብሔሮች መብትና ነጻነት የሚከበርበት፣ ሰው በሰውነቱ በእኩል የሚታይበት፣ ከበደልና

ጭቆና ነጻ መሆን ማለት ነው፡፡

የሕግ የበላይነትን ማስፈን፣ ሐቀኛ የፍትሕ ሥርዓት መገንባት፣ መሠረታዊ ሰብአዊ መብቶችን

ማክበር፣ ማኅበራዊ ፍትሕን ማረጋገጥ የብልፅግና ፓርቲ ዕሴት ነው፡፡

ህብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት

40
ኅብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት፣ የሚከፋፍሉ እና የሚያጣሉ ትርክቶችን ከማጉላት

ይልቅ የሚያቀራርቡና የሚያስተሣሥሩንን እውነታዎች በማጉላት፣ ከትናንት ጠቃሚ ትምህርቶችን

በመውሰድ እንዲሁም ዛሬና ነገ ላይ በማተኮር ወንድማዊና እህታዊ ኅብረትን ማጠናከርን፣ ብዙ

ሆነን አንድ፣ አንድ ሆነንም ብዙ የምንሆንበት፣ ለጋራ ግብና ዓላማ የምንደመርበት እንደሆነ

ብልጽግና ፓርቲ ያምናል፡፡ ስለሆነም ብልጽግና ፓርቲ በሀገራችን ህብረብሔራዊ ወንድማማችነትና

እህትማማችነት እንዲጠነክር ዋልታ ረገጥ አስተሳሰቦች እንዲወገዱ በእሴትነት ይዞ የሚሰራ ፓርቲ

ነው፡

መከባበርና መቻቻል

መከባበርና መቻቻል ማለት አንዱ የሌላውን ሀሳብ ፣ እሴትና ልዩነት ማክበር፣ ልዩነት ባላቸው

ሐሳቦች ላይ አሉታዊ አመለካከት አለማሳየት ማለት ነው፡፡ በኢትዮጵያሁሉም ብሔር ብሔረሰቦችና

ህዝቦች ተከባበረውና ተቻችለው አንዱ የበላይ አንዱ የበታች ሳይሆን በእኩልነት የሚተያዩበትና

የሀገራቸውን ዕድገት በጋራ ተልመው እንዲፈጽሙ ብልፅግና ፓርቲ ያምናል፡፡ ስለሆነም በህዝቦች

ዘንድ መከባበርና መቻቻል እንዲፈጠር ሁሉም ተከባብሮና ተቻችሎ የሚኖሩባት ኢትዮጵያን እውን

እንዲትሆን ፓርቲው በእሴትነት ይዞ የሚታገል ይሆናል፡፡

ህብረ-ብሔራዊ አንድነት

ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ብዝኃነትን እንደ ጸጋ የሚመለከት ለሁሉም ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች

ዕውቅና የሚሰጥ ነው፡፡ ህብረ ብሔራዊ አንድነት፣ ማንነታችን እርስ በርሱ የተጋመደ፣ የተሠናሠለ

እና የተዋሐደ መሆኑን በመገንዘብ ለጋራ ዓላማና ግብ አብረን መቆም፣ አብረን መሥራት፣ መደጋገፍ

እና መተጋገዝ እንደሚገባን የሚያስገነዝብ አመለካከት ነው። ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ታሪካዊና

ነባራዊ በደሎችን ከማድበስበስ ይልቅ ታርመው እንዲሄዱ፣ ይህም ለቁርሾ ሳይሆን ወዳጅነትን

ለማጠናከር እንዲውል የሚያደርግ አካሄድ በመሆኑ ፓርቲያችን የሚታገልበት አንዱ እሴት ነው።

41
አሳታፊነት

ብልጽግና ፓርቲ ሁሉም ዜጋ በዋናዋናየሀገሪቱጉዳዮችማለትም በፖለቲካ፣ በልማት፣በመልካም

አስተዳደር ጉዳዮች፣ የሀገር ሉኣላዊነት በማስከበር ሂደት ተሳታፊ እንዲሆንበዕሴትነት ይዞ ይሰራል፡፡

ተሳታፊነት ሲባል የይስሙላ ተሳትፎ ሳይሆን ሁለንተናዊ ተሳትፎ እንደሆነና ለዚህም የሚታገል

ፓርቲው ነው ብልፅግና፡፡

ግልጸኝነትና ተጠያቂነት

ግልፀኝነት ተግባራትንና ድርጊቶችን ግልፅ በሆነ ሁኔታ፣በአሰራርና በህግ መሠረት መፈጸም ሲሆን

ተጠያቂነት ማለት ደግሞ ለድርጊቱ ወይም ለተግባሩ ኃላፊነት መውስድ ማለት ነው፡፡ ስለሆነም

ብልጽግና ፓርቲም የመንግሥትም ሆነ የፓርቲ አገልግሎቶች፣ ውሳኔዎችና አፈጻጸሞች ግልጸኝነትና

ተጠያቂነት በተረጋገጠበት እንዲሆን በእሴትነት ይዞ ይታገላል፡፡

3.5. የብልፅግና ፓርቲ መርሆዎች (principles)

• ህዝባዊነት

• ዴሞክራሲያዊነት

• የህግ የበላይነት

• ልማትና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት

• ተግባራዊ እውነታ

• አገራዊ አንድነትና ህብረ ብሄራዊነት

3.6. የብልፅግና ፓርቲ መዋቅር (structure)

የፓርቲው ድርጅታዊ አወቃቀር የሀገሪቱን ህገመንግስታዊ ፌዴራላዊ አወቃቀር የተከተለ ነው፡፡

አወቃቀሩ ከፌዴራል እስከ ህዋስ ድረስ ሆኖ የሚከተሉት ተቋማዊ አደረጃጀቶች አሉት፡፡

ሀ. ጉባኤ

42
ለ. ማዕከላዊ ኮሚቴ

ሐ. ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ

መ.የፌዴራልና የክልል የፓርቲ አመራሮች የጋራ መድረክ

ሠ.ፕሬዝዳንት

ረ. ምክትል ፕሬዝዳንቶች

ሰ. የኢንስፔክሽንና ስነ-መግባር ኮሚሽን

ሸ. የፓርቲው ዋና ጽህፈት ቤት

ቀ. የፓርቲው የክልል ቅርጫፍ ጽህፈት ቤቶች

በ. የብልፅግና ሴቶች ሊግ

ተ. የብልፅግና ወጣቶች ሊግ

ቸ. የፓርቲው መሰረታዊ ድርጅትና ህዋስ ሲሆኑ የእነዚህን መዋቅር ሃላፊነትና ተግባራት

በግልጽ የተቀመጡ በመሆኑ ፓርቲችን ህጋዊ አሰራርን የተለከተለ ነው፡፡

43
3.7. የብልፅግና ፓርቲ መዋቅራዊ ቻርት

የብልፅግና
ፓርቲ ጉባዔ
ኢንስፔክሽንና ስነ
ምግባር ኮሚሽን

---------------------------------
ማዕከላዊ ኮሚቴ -------------------

የፓርቲ ሴቶች እና
ፕሬዝዳንት ወጣቶች ሊጎች

ስራ አስፈፃሚ

የብልፅግና ዋና ምክትል
ፅ/ቤት ፕሬዝዳንቶች

የፌዴራልና የክልል
ፓርቲ አመራሮች
የጋራ መድረክ

የፓርቲው የክልል የአ/አበባና የድሬዳዋ


ቅርንጫፍ ከተማ አስተዳደር ፓርቲ
ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች
ፅ/ቤቶች

44
ምዕራፍ አራት፡- የተቋማዊና ዉጫዊ ሁኔታና የባለድርሻ አካላት
ትንተና

4.1. የተቋማዊና ዉጫዊ ሁኔታ ትንተና

4.1.1. ውስጣዊ ጥንካሬና ድክመት

4.1.1.1. ጠንካራ ጎን

• ፓርቲው አዲስ ሀገር በቀል የመደመር እሳቤ ይዞ የተነሳ ፅንፈኝነትን የሚታገል፥ ሀገራዊ

አንድነትንና የብሔር ማንነትን ሚዛን የጠበቀ የመሐል ፖለቲካን የሚያራምድ ወጥ ሀገራዊ

ፓርቲ መሆኑ፤

• ፓርቲው ፕሮገራሞቹን፣ ፖሊሲዎቹንና እሳቤዎቹን በተሻለ ሁኔታ የቀረጻቸው መሆኑ፥

በአብዛኛዉ ኢትዮጵያዉያን ዘንድ ተቀባይነት ስለማግኘቱ በ6ኛዉ ሀገራዊ ምርጫ ጭምር

የተረጋገጠ መሆኑ፣

• ፓርቲዉ ባደረገዉ የመጀመሪያ ጉባኤ የፓርቲውን ማዕከላዊ ኮሚቴ፣ ሥራ አስፈጻሚ እና

ኢንስፔክሽንና ሥነ-ምግር ኮሚሽን በጉባኤ ማደራጀቱና ተግባርና ኃላፊነታቸውን መወሰኑ፣

• ፓርቲዉ ሁሉንም የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች አቅፎ ያያዘ ግዙፍ ሀገራዊ ፓርቲ፥

ልምድ ያለውና ራሱን ከነባራዊ ሁኔታው አኳያ እያደሰ የሚሄድ (ፕራግማቲክ) መሆኑ፤

• ፓርቲው ሰፊ የአባል ቁጥር ያለውና፤ በአደረጃጀትና አሰራር መመሪያ መሰረት አደረጃጀቶች

እስከ ቀበሌ/ህዋስ ድረስ በአዲስ መልክ እንዲደራጁ መደረጉ፤

• ፕሮግራሙን ሊያፈጽም የሚያስችለው የሰው ኃይል እና ሌሎች ሀብቶች ያሉት መሆኑ፤

• ፓርቲው ሀገራዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲዎችን

በመንግሥት በሪፎረምና የ10 ዓመት ዕቅድ እንካት በማድረግ እየመራ መሆኑ፣

4.1.1.2. ድክመት

• በየደረጃው ጠንካራና ብቃት ያለዉ የፓርቲ ተቋም አለመፍጠር

• ብቃት ያለው የአደረጃጀትና አሰራር ሥርዓት የመዘርጋት ውስንነት

45
• በክልሎች መሐል የአደረጃጀት፥ አሠራር እና ተግባር አፈፃፀም አለመናበብ፥

• የግልጸኝነትና የተጠያቂነት ችግር ያለ መሆኑ፤

• የፓርቲ የመረጃ አያያዝ ሥርዓት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ያልተደገፈ መሆኑ፣

• በፓርቲው ራዕይ፥ፕሮግራም እና ዕሳቤዎች ዙሪያ በአመራሩና አባሉ ዘንድ ከፍተኛ

የአመለካከትና ግንዛቤ ክፍተቶች ያሉ መሆኑ፤

• በአመራሩና በአባሉ የአመለካከትና የተግባር አንድነት አለመኖር፤ የጠራ አመለካከት

በሚፈልጉ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት አለመፍጠር፤

• ህብረ-ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነትን ለማጠናከር ከመስራት ይልቅ ልዩነት ተኮር መሆን፤

• ከፍተኛ የሆነ የአመራርና የአባላት የብቃትና ጥራት (አስተሳሰብ፥ዕዉቀት፥ክህሎት፥ጥበብ)

ችግር ያለ መሆኑ፤

• የፓርቲውን መሰረታውያን፣ እሴቶች እና መርሆዎች ላይ በቂ የተግባቦት ሥራ ባለመሰራቱ

በእሴቶቹ ያለመገዛት የዲስፕሊን ችግር መኖሩ፤

• የአባላት ምልመላ የጥራትና የአግባብነት፣ ስምሪትና ግንባታ ችግር ያለበት መሆኑ፣

• ችግሮችን ቀድሞ ፓለቲካዊ ትርጉም ሰጥቶ የመረዳትና የመተንተን እንዲሁም ችግሮችን

በሙሉነታቸው አይቶ ቀጣይነት ያለው የፓለቲካ ስራዎች አለመስራት፤

• ለረጅም ጊዜ ያገለገሉ አመራሮች የአመራር ሽግሽግ እና የአመራር ስንብት ራሱን የቻለ

ግልጽ የሆነ ስርዓት አለመኖር፤

• የፖለቲካ ስራዎች በጥናትና ምርምር የተደገፈ አለመሆኑ፣

• የፓርቲው ውስጠ ዴሞክራሲ አለመጠናከርና ፀረ-ዴሞክራሲያዊነት እያደገ መምጣቱ፤

• የፓርቲን እና የመንግስትን ሚና በአግባቡ ለይቶ ከመምራት አኳያ ከፍተኛ ችግር ያለ

መሆኑ፤

• ስልጣን ህዝብን የማገልገያ መሳሪያ መሆኑ ቀርቶ የግል ፍላጎት ማስፈጸሚያ ከመሆኑ የተነሳ

ሌብነትና ብልሹ አሰራር መበራከት፤

• የተፎካካሪ ፓርቲዎች አያያዝና ግንኙነት በመርህና አሰራር ላይ ያልተመሰረተ መሆኑ፣

46
4.1.2. ውጫዊ እድሎችና ስጋቶች

4.1.2.1. ውጫዊ እድሎች

• ሀገሪቱ ህገ-መንግስትን ጨምሮ የሚያሰሩ የህግ ማዕቀፎች፣ ስትራቴጅዎችና ፖሊሲዎች ያላት

መሆኑ፤

• የቀጣይ 10 ዓመት ሀገራዊ የልማት እቅድ መኖሩ፤

• በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ፍላጎት ያላቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች መኖራቸው፤

• ነፃና ገለልተኛ የዴሞክራሲ ተቋማት እየተገነቡ መሆናቸው፤

• የኢትዮጵያ ህዝብ የሀገር አንድነት፤ ሉአላዊነትና ነፃነት፤ ሰላምና ደህንነት እንዲሁም የመልማት

ፅኑ ፍላጎት ያለው መሆኑ፤

• ረጅም የሀገረ መንግስት ግንባታና የዲፕሎማሲ ታሪክ ያለን፤ የተባበሩት መንግስታት እና

የአፍሪካ ህብረት መስራች መሆናችን፤

• ዓለም ከባለ አንድ ዋልታ ወደ ብዙ ዋልታነት እየመጣች መሆኑ፣

• ፓርቲያችን የሚከተለው የአረንጓዴ ኢኮኖሚ አቅጣጫ አለም አቀፍ ተቀባይነት እያገኘ መሆኑ፤

• ዓለማ ዓቀፋዊ ጫናን ተቋቁሞና የነበረበትን ውስጣዊ ተቋማዊ ችግር ፈትቶ ህዳሴ ግድብን

ሥራ ማስቀጠል በመቻሉ ህዝቡ ላይ አዎንታዊ እይታ እና ድጋፍ መፈጠሩ፣

• ከጥቂት ዘርፎች ተኮር ወደ ብዙሀን ዘርፎች የኢኮኖሚ ስርአት ሽግግር እየተደረገ መሆኑ፤

• ከልዩነቶች ይልቅ የሚያስተሳስሩን ሀገራዊ ባህላዊ፣ ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ዕሴቶች መኖር፣

• የትምህርት ተደራሽነትና መከላከልን መሰረት ያደረገው የጤና ልማት ሰፊ የተማረና ጤናው

የተጠበቀ ሰው ሃይል ማፍራቱ፤

• ሀገራዊ የዘመናዊ የቴክኖሎጂ ውጤቶች አጠቃቀም እድገት እየታየ መሆኑ፣

• ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የተተገበሩ የሪፎርም ስራዎች ውጤት እያስገኙ መሆናቸው፣

• ሀገራዊ ምክክርና ውይይት የማድረግ ሂደቱ ሰፊ ህዝባዊና ፖለቲካዊ ተቀባይነት ያገኘ መሆኑ፣

4.1.2.2. ውጫዊ ስጋቶች

• በህገ መንግሥቱ፥ በሀገረ-መንግስትና ብሔረ መንግሥት ግንባታ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ

መግባባት ያለመኖር፤

47
• ሀገራዊ የሰላም፣ የደህንነትና የህግ የበላይነት ያለመከበር ችግሮች መኖራቸው፤

• የሀሳብ የበላይነትን መሰረት አድርጎ ፓለቲካን ከማራመድ ይልቅ አክራሪነትና ጽንፈኝነት ላይ

መሰረት ያደረገ የፖለቲካ እንቅስቃሴ፤

• በምክንያት የመደገፍና የመቃወም የሰለጠነ የፖለቲካ አስተሳሰብ ልምድ አለመዳበር፣

• የነፃና ገለልተኛ ዴሞክራሲያዊ ተቋማት አለመጠናከር፤

• የጥናት፣ የምርምርና የሃሳብ ማፍለቂያ (thinktank) ጠንካራ ሀገራዊ ተቋማት አለመኖር፤

• ጎረቤት ሀገራት ጠንካራ ፓርቲና መንግሥት የሌላቸው፤ የእርስ በእርስ ግጭት የሚበዛባቸው

እና የውጫዊ ሀይሎች ጣልቃ ገብነት ያለባቸው መሆኑ፤

• አለም አቀፍ ተሰሚነታችንን ወደ ላቀ ደረጃ የሚወስድ ጠንካራ የዲፕሎማሲና የተግባቦት

ሥራ አለመኖር፤

• ሀያላን ሀገራት የአፍሪካ ቀንድ ቀጠናን ለመቆጣጠር የሚያደርጉት ፉክክር እያየለ መምጣቱ፤

• ኢ-ተገማች የሆነ አለም አቀፋዊ ሁኔታ መኖር፤

• ከጎረቤት ሀገሮች ጋር ለግጭት መነሾ የሚሆኑ ያልተቋጩ ጉዳዮች መኖር (የድንበር ጉዳይ፤

የውሃ ፓለቲካ)፤

• በክልሎች የሚነሱ የወሰንና የማንነት ጉዳዮች እልባት ያላገኙ መሆናቸው፤

• የፌደራል መንግሥቱንና የክልል መንግሥታትን ግንኙነት የሚያሳልጥ የህግ ማዕቀፍና አሰራሮች

ተግባራዊ አለመደረጋቸው፣

• በትልልቅ ከተሞች ያለው የፖለቲካ ትኩሳት መልክ አለመያዝ፤

• ሀገራዊ የማስፈጸም አቅም ችግር መኖሩ፣

• በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆንና ጫናዎችን መቋቋም የሚችል የግል ኢኮኖሚ ዘርፍ

አለመገንባቱ፣

• የምርታማነትና የተወዳዳሪነት ችግር መኖር፣

• የመንግሥትና የግሉ ሴክተር የቅንጅት ችግር መኖር፣

• የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት አሉታዊ ውጤቶች (የዋጋ ንረት፣ እዳ ጫና፣ የምንዛሬ እጥረት፤

ስራ አጥነት…) ሀገራዊ እድገቱን እየፈተኑት መሆናቸው፤

• የኢኮኖሚ አሻጥርና ሌብነት መኖር፣

48
• ነባር ታሪካዊ፤ ባህላዊና ሀይማኖታዊ እሴቶች እየተሸረሸሩ መምጣታቸው፤

• የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አቅምና ልምድ አናሳ መሆን እና በቂ መሰረተ ልማቶች አለመዘርጋት፣

• ቴክኖሎጂ ለበጎ አላማ ከማዋል ይልቅ ለአፍራሽ ተግባር መጠቀም፣

49
Table 1 ተቋማዊ ውስጣዊ ሁኔታ

ዋና ዋና በጥንካሬ
ጉዳዮች
• ፓርቲው አዲስ ሀገር በቀል የመደመር እሳቤ ይዞ የመጣ
ፅንፈኝነትን የሚታገል የመሐል ፖለቲካን የሚከተልፓርቲ
መሆኑ፤
ፖሊሲዎችና • ፓርቲው ፕሮገራሞቹን፣ እሳቤዎቹን በተሻለ ሁኔታ
አቅጣጫዎች የቀረጻቸውና በኢትዮጵያዉያን ዘንድ ተቀባይነት ያለዉ
መሆኑ፣ በምርጫ ጭምር ተቀባይነቱ የተረጋገጠ መሆኑ፤
• የፓርቲው፤ሀገራዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊና፤
የውጭ;ጉዳይ፤ፖሊሲዎችን በመንግሥት 10 ዓመት ዕቅድ
ትግበራ ላይ መሆኑ
• በተነፃፃሪ ልምድ ያለውና ራሱን ከነባራዊ ሁኔታው አኳያ
እያደሰ የሚሄድ(ፕራግማቲክ) ፓርቲ መሆኑ፤
• በቁጥር አነስተኛ ቢሆኑም ለውጡን ሊመሩ የሚችሉ
አመለካከት፤ የጠራ አመለካከት ያላቸው አመራር መኖራቸው፣
ዕዉቀትና • ለመነሻ የሚሆን ልምድና ተነሳሽነት ያላቸዉ የአመራር
ክህሎት መኖር፣
• ለአጠቃላይ ፓርቲዉ ዓላማ መሳካት የአባላት ፍላጎት
መኖር፣

5
በድክመት

• በፓርቲዉ ራዕይ፤ ተልዕኮ፤ ፕሮግራሞችና ህሳቤዎች ላይ ከፍተኛ የአመለካከትና


የግንዛቤ ክፍተት መኖሩ
• ፓርቲዉ ሁሉም ኢትዮጵያዉያንን አቅፎ የያዘ ግዙፍ ፓርቲ ቢሆንም ከማዕከል
እስከ ታችኛዉ አደረጃጀት ድረስ ጉዳዮችን በተቀናጀና በተናበበ ሁኔታ የመምራት
ችግር ያለበት መሆኑ

• ከፍተኛ የሆነ የአመራርና የአባላት የብቃትና የጥራት ችግር


• በዉስጠ፤ፓርቲ፤ብሔርተኝነትና፤ፅንፈኝነት የጎላ ችግር ሆኖ መቀጠሉ
• የፓርቲውን፤መርሆዎች፤እሴቶች ህሳቤዎች፤ላይ በዉስጠ ፓርቲ ተግባቦት
አለመፈጠር
• የተዛባ፤የሥልጣን፤እይታ፤ሌብነት፤የዲስፕልን ችግር
• ችግሮችን ቀድሞ ፓለቲካዊ ትርጉም ሰጥቶ የመረዳትና የመተንተን ቀጣይነት
ያለው የፓለቲካ ስራዎች ለመሥራት ተቋማዊ አቅም ችግር፤
• ሰፊ የአፈፃፀም አቅም ክፈተቶችና የተረጋጋ የአመራር ሁኔታ መፍጠር አለመቻል
• በየደረጃዉ ባለዉ ከፍተኛ አመራር የሚሰጡ ዉሳኔዎች የብስለት፤ያለመናበብና
ተጠያቂነት ችግር ያለበት መሆኑ

50
• የፓርቲውን፤ማዕከላዊ ኮሚቴ፣ ሥራ;አስፈጻሚ፤እና
ኢንስፔክሽንና ሥነ-ምግር ኮሚሽን በጉባኤ ማደራጀቱና
ተግባርና;ኃላፊነታቸው ግልፅ መደረጉ፣
አደረጃጀትና • በአደረጃጀትና አሰራር መመሪያ መሰረት አደረጃጀቶች
አሠራር እስከ ቀበሌ/ህዋስ ድረስ በአዲስ መልክ እንዲደራጁ
አቅጣጫ መኖሩ፤

• ፓርቲው ሰፊ የአባል ቁጥር ያለው መሆኑ፤


• ፕሮግራሙን ሊያፈጽም የሚያስችለው ተነፃፃሪ የሰው
ሀብት/ግብዓ ኃይል፤ቢሮዎች እና ሌሎች ሀብቶች ያሉት መሆኑ፤

5
• በየደረጃው ጠንካራ ተቋም አለመፍጠር፤
• ብቃት ያለው የአሰራር ሥርዓት ችግር
• የዉስጠ ፓርቲ ዲሞክራሲ፤ የግልጸኝነትና የተጠያቂነት ችግር
• የአባላት ምልመላ የጥራትና የአግባብነት፣ ስምሪትና ግንባታነ ችግር
• የአመራር ሽግሽግ እና የአመራር ስንብት ግልጽ የሆነ ስርዓት አለመኖር፤
• የፓርቲ የመረጃ አያያዝ ሥርዓት ዘመናዊ አለመሆን(MIS)
• የፓርቲው ውስጠ ዴሞክራሲ እሴት አለመጠናከር
• የዕቅድ፤የክትትል፤የሪፖርትና ምዘና ችግር
• የፓርቲዉ ቅሬታ አፈታት ሥርዓት ችግ መዳከም፡ ፀረ ዴ/ሲያዊነት ማገንገን

• የሠራተኛዉ የእዉቀት፤ክህሎትና ተነሳስነት(ስታፍ፤ምልመላ፤አስተዳደር፤


የትምህርት፤ሥልጠና፤ዕድገት) ችግር
• የሰዉ ሀብት ሥምርት/ምደባ/ ችግር
• የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ችግር(MIS)
• ሀብት/ገቢ የመሰብሰብና የመበጀት ችግር
• የሀብት አጠቃቀምና ቁጥጥር ችግር

51
Table 2 ዉጫዊ ሁኔታ

ዕድሎች
• ሀገሪቱ፤ህገመንግሥት፤የህግ ማዕቀፎች፣ፖሊሲዎች፤
ስትራቴጅዎች ያላት መሆኑ፤
• የቀጣይ 10 ዓመት ሀገራዊ የልማት እቅድ ወደ
ትግበራ መግባቱ
• በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ፍላጎት ያላቸው፤
የፖለቲካ፤ፓርቲዎች መኖራቸው፤
ፖለቲካዊ
• የኢትዮጵያ ህዝብ የሀገር አንድነት፤ ሉአላዊነትና
ሁኔታ
ነፃነት፤ ሰላምና ደህንነት እንዲሁም የመልማት
ፅኑ ፍላጎት ያለው መሆኑ፤
• ነፃና ገለልተኛ የዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታ
ጅማሮ መኖሩ
• ረጅም የሀገረ መንግስት ግንባታና የዲፕሎማሲ
ታሪክ ያለን፤
• ዓለም ከባለ አንድ ዋልታ ወደ ብዙ ዋልታነት
የመምጣት ዕድል መኖሩ፣
• የዲያስፖራዉ ሀገራዊ ፖለቲካ ተሳትፎ
መጨመር

• ከጥቂት ዘርፎች ተኮር ወደ ብዙሀን ዘርፎች


የኢኮኖሚ ስርአት ሽግግር መደረጉ
• የአረንጓዴ ኢኮኖሚ አቅጣጫ ተቀባይነት እያገኘ
መሆኑ፤
ኢኮኖሚያዊ • የ10 ዓመት የልማትና ዕድገት ዕቅድ ተግባራዊ
ሁኔታ መደረጉ

5
ስጋቶች
• በህገ መንግሥቱና በሀገረ-መንግስት ግንባታ መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ
መግባባት ያለመኖር፤
• ሀገራዊ የሰላም፣ የደህንነትና የህግ የበላይነት ችግር፤
• የፓርቲዎች መብዛትና አክራሪነትና ጽንፈኝነት ላይ መሰረት ያደረገ የፖለቲካ
እንቅስቃሴ፤የበላይነት መኖር
• በህብረተሰቡ ዘንድ በምክንያት የመደገፍና የመቃወም የሰለጠነ የፖለቲካ
አስተሳሰብ ልምድ አለመዳበር፣
• በኢልቶችና አክቲቪስቶች የሚዘወር አሻጥር የበዛበት የፖለቲካ እንቅስቃሴ
• በዉስጥና ዉጪ ሃይሎች የተቀናጀ የሠላምና ደህንነት አደጋ መኖሩ
• የነፃና፤ገለልተኛ፤ዴሞክራሲያዊ፤ተቋማት አለመጠናከር፤
• ጎረቤት ሀገራት አለመረጋጋት የእርስ በእርስ ግጭት የሚበዛባቸው እና የውጫዊ
ሀይሎች ጣልቃ ገብነት
• አለም አቀፍ ተሰሚነታችንን ከፍ የሚያደርግ ጠንካራ የዲፕሎማሲና የተግባቦት
ሥራ አለመኖር፤
• በቀጠናዉ የሃያላን ፉክክር እያየለ መምጣቱ፤
• ኢ-ተገማች የሆነ አለም አቀፋዊ ሁኔታ መኖር፤
• ከጎረቤት ሀገሮች ጋር ያልተቋጩ የድንበር ጉዳዮችና የቀጠናዉ ውሃ ፓለቲካ፤
• በክልሎች የሚነሱ የወሰንና የማንነት ጉዳዮች አለመፈታት
• የፌደራል፤መንግሥቱንና፤የክልል መንግሥታትን፤ግንኙነት የሚያሳልጥ የህግ
ማዕቀፍና ችግር
• በትላልቅ ከተሞች ያለው የፖለቲካ ትኩሳት መልክ አለመያዝ፤
• ፖሊሲን የማስፈጸም አቅም(ቢሮክራሲ) ችግር መኖሩ፣
• የግል ሴክተር ኢኮኖሚ ዘርፍ አለመገንባቱ፣
• የምርታማነትና የተወዳዳሪነት ችግር መኖር፣
• የመንግሥትና የግሉ ሴክተር የቅንጅት ችግር
• የዓለም ኢኮኖሚ መዋዠቅ፤የሃያላን ፍጥጫ ትልቅ አደጋ መደቀኑ፤በተለይም
የምግብ፤ ነዳጅ፤ማዳበሪያ ሸቀጦች ላይ

52
• በህዳሴ ግድብ ግንባታ የተጠናከረ ህዝባዊ
ድጋፍና ተሳትፎ መኖሩ፣

• ከልዩነቶች;ይልቅ የሚያስተሳስሩን ሀገራዊ


ባህላዊ፣ ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ዕሴቶች መኖር፣
• የተሻለ;የትምህርት;ተደራሽነት
ማህበራዊ
ሁኔታ • መከላከልን መሰረት ያደረገው የጤና ልማት
መሠረት መጣሉ
• እምቅ የቱርዝም ሀብት መኖር
• ትኩስ አምራች ሃይል መኖር

ቴክኖሎጂ • የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ግንባታ ጅማሮ


መኖር
• የሰዉ ሃይል የማፍራት ጅማሮ መኖሩ
የህግ ማዕቀፍ • የሚያሰራ የፓርቲዎች የምዝገባና ምርጫ
አሠራር መኖር

5
• የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት አሉታዊ ውጤቶች (የዋጋ ንረት፣ እዳ ጫና፣
የምንዛሬ እጥረት፤ ስራ አጥነት…)
• የህዝቡ የመግዛት አቅም ማሽቆልቆልና የምግብ እጥረት ፈተና መደቀኑ
• የኢኮኖሚ አሻጥርና ሌብነት መኖር፣
• የማይገመቱ የተፈጥሮ አደጋዎች በተደጋጋሚ መከሰትና የመቋቋም አቅም
ማነስ
• ነባር ታሪካዊ፤ ባህላዊና ሀይማኖታዊ እሴቶች እየተሸረሸሩ መምጣታቸው፤
• የህዝብ ፍልሰት በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩ በተለይም ለከተሞች ፈታኝ
ሁኔታ መፍጠሩ
• የዓለም አቀፍ ሰብዓዊ ዕርዳታ መቀነስና ፖለቲካዊ መልክ መያዝ
• የሥራ አጥነት ቁጥር ማደግ ለሀገሪቱ አለመረጋጋት አስተወፅኦዉ ከፍተኛ
መሆኑ
• የሥራ ባህላችን ደካማ መሆን፣
• በየጊዜው የሚፈጠር ያልተጠበቁ የተፈጥሮ አዳጋ፣
• የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አቅምና ልምድ አናሳ መሆን እና በቂ መሰረተ
ልማቶች አለመዘርጋት፣
• ቴክኖሎጂ ለበጎ አላማ ከማዋል ይልቅ ለአፍራሽ ተግባር መጠቀም፣
• በህጎች ላይ የተሟላ ግንዛቤ አለመኖር፣
• ለህግ ያለው ተገዥነት አናሳ መሆን፣

53
4.2. የተገልጋይና ባለድርሻ አካላት ትንተና

የብልፅግና ፓርቲ ዋና ዋና ተገልጋዮች በየደረጃው የሚገኘው አመራርና መላ አባላቱ ሲሆኑ ባለድርሻ

አካላት ደግሞ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ናቸው፡፡ እነሱም፡-

1) የኢትዮጵያ ህዝብ ( ባለሀብት፣ አርሶ አደር፣ አርብቶ አደር፣ የከተማ ነዋሪ፣ ምሁራን፣ ወጣቶችና

ሴቶች)

2) መንግስት(ህግ አውጭ፣ ሕግ አስፈጻሚና ህግ ተጓሚ)፤

3) የመንግስት ሰራተኛና ላባደር፤

4) የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች፤

5) የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት.

6) የሲቨክ ማህበራት፤

7) የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ፤

8) የውጭ ሀገራት ወዳጅ ፓርቲዎች እና

9) የዴሞክራሲ ተቋማት ናቸው፡፡

54
Table 3 የተገልጋዮችና ባለድርሻ አካላት ፍላጎትን መለየት

ተገልጋዮችና የተገልጋዮችና ባለድርሻ አካላት ፓርቲው ከተ


ባለድርሻ ፍላጎት አካላት
አካላት

ዋና ዋና የአቅም ግንባታና ሥልጠና፣ አሰራሮችና ደንብና መመሪያ አ


ተገልጋዮች መመሪያዎች እንዲኖሩት፣ የልምድ ዴሞክራሲያ ግንኙነ
ልውውጥ፣ የክትትልና ድጋፍ፣ ሐሳብ የፓርቲው ውሳኔዎች
የማመንጨት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ የፓርቲውን እሴቶች
የፓርቲው እንዲኖር፣ የሥራ ዋስትና እንዲያደርጉ፣ የአመ
አመራር አንድነት እንዲኖራቸ
ዕቅድ ማቀድ፣ ሪፖ

የአቅም ግንባታና ሥልጠና፣ አሰራሮችና የተሟላ ሥነ-ምግባ


መመሪያዎች እንዲኖሩት፣ በክትትልና ውጤታማነት፣ ታማ
አባላት
ድጋፍ ማሳተፍ፣ ሐሳብ ማመንጨት መርሆዎች ማክበር
የሚያስችል ምቹ ሁኔታ እንዲኖር፣ የሥራ
ዋስትና

- ምቹ የሥራ ሁኔታ የፓርቲውን ህጎችና


- አቅም ግንባታ የሥራ ውጤታማነት
የዋና
- የሥራ ዋስትና የባለቤትነት መንፈስ
ጽ/ቤትና - በቂ ደመወዝና ጥቅማጥቅም የተከተለ ተሳትፎና
ቅ/ጽ/ቤቶ - አሳታፊነትና/ፍትሃዊነት እቅድና ተግባር እን
ች - ወቅታዊ መረጃ
ማመንጨት፣
- ፈጣን ምላሽ

5
ተገልጋዮችና ባለድርሻ ተገልጋዮችና ባለድርሻዎች የተፅዕኖ
የሚጠብቀው በፓርቲው ላይ አሉታዊ ደረጃ
ተፅዕኖ የሚያሳድሩባቸው
ጉዳዮች

አክብረው እንዲሰሩ ፣ ደንቦችንና መመሪያዎችን ጠብቆ


ነት እንዲኖራቸው፣ በቁርጠኝነትና በተነሳሽነት በጣም
ችን ተግባራዊ እንዲያደርጉ፣ አለመስራት፣ ሌብነትና ብልሹ ከፍተኛ
ችንና መርሆዎችን ተግባራዊ አሰራር መስፋት፣ የብቃት
መለካከትና የተግባር ማነስ፣ በፓርቲው እሳቤዎች ላይ
ቸው፣ ሀሳብ ማመንጨት የግንዛቤ እጥረት፣ የፅንፈኝነት
ፖርት ማድረግ፣ ዝንባሌ ማደግ፣

ባር፣ ተሳትፎ፣ እምነት መቀነስ/መሸርሸር፣


ማኝነት ፣ ደንብ እሴቶች የአመለካከት ዝንፈት፣ ብቃት በጣም
መቀነስ፣ ሌብነት፣ የተሳትፎ ከፍተኛ
ማነስ፣ ፅንፈኝነት ማደግ

መመሪያዎች ማክበር፣ - መቆዘምና የተሳትፎ


ት፣ ታማኝነት፣ ታታሪነት፣ ማነስ/ዝምታ
በጣም
ስ/ሀሳብ፣ ግልፅና መርህን - የስራ ተነሳሽነት ማጣት፣
ከፍተኛ
ትችት፣ ውሳኔዎች ወደ - ፅንፈኝነት፣
ንዲቀየሩ ማድረግ እና ሀሳብ - የአመራር መቀያየር፣
- ተቋሙን ለቆ መሄድ

55
አመራርና
ሰራተኛ

የብልጽግና መተዳደሪያ ደንቡ ተጠብቆ ተግባራዊ የፓርቲ አቅጣጫዎች


ጉባኤ፣ መደረጉ፣ የተቀመጡ አቅጣጫዎችና ልዩ ልዩ አገራዊና ፓ
ማዕከላዊ ውሳኔዎች ተግባራዊ መሆናቸውን መርምሮ ውሳኔ እን
ኮሚቴ፣ ማረጋገጥ፣ መመሪያዎችና አሠራሮች እንዲፀድቅ
ሥራ መጠበቅ፣ በአገሪቱ ሰላም፣ ልማት፣ እና
አስፈጻሚ፣ መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን አቅጣጫ
የፌደራልና ማስቀመጥ
የክልል
የፓርቲ
አመራሮች
የጋራ
መድረክ

የፓርቲው የተጠቃለለ ዕቅድ፣ መረጃና - ውጤታማ ጥናት


ሪፖርት፣የዋና ጽ/ቤቱንና የቅርንጫፍ ቁጥጥር ሥራ ማ
ጽ/ቤቶች የሥራ አፈፃፀምና የፋይናንስ መስጠት፣
ኢንስፔክሽን የሀብት አጠቃቀም ሪፖርት፣ ፕሮግራምና - ውሳኔዎችን ለፓ
እና ሥነ- ህገ-ደንብና መመሪያ በትክክለኛው አቅርቦ ማስመር
ምግባር አቅጣጫ መተግበር፣ በፓርቲው የሚፈጠሩ
ኮሚሽን ቅሬታዎችን መመርመርና ማረም፣ ነፃ እና
ገለልተኛ አካል ሆኖ መስራት

ባለድርሻ - ወቅታዊ መረጃ - ህግ አክባሪነት


- ታማኝነት/ወጥነት - በመረጃ ላይ የተ
ዎች
- ሰላምና ዲሞክራሲ - የምርጫ ድጋፍ

5
ችና ውሳኔዎች እንዲከበሩ ፣ የብልፅግና እሳቤዎች ላይ
ፓርቲያዊ አጀንዳዎችን የሚፈጠር ክፍተት፣ አጠቃላይ
ንዲተላለፍ፣ ዕቅድና በጀት የተግባር መውደቅ/መዳከም፣
በጣም
ያልተጠና ውሳኔና አገራዊ
ከፍተኛ
ቀውስ፣ የፓርቲው የመፍረስ
አደጋ

ት፣ ክትትል፣ የኢንስፔክሽንና - የውስጠ ዲሞክራሲ


ማከናወንና ግብረ-መልስ መዳከምና ፓርቲው በአባላት
ዘንድ እምነት ማጣት
ፓርቲው የተለያዩ አካላት - የችግሮች በወቅቱ በጣም
ርመርና ማፀደቅ አለመስተካከልና እየተባባሱ ከፍተኛ
መሄድ
- ተከታታይና በመረጃ ላይ
አለመመሥረት፣

- ህግ አለማክበር /ስርአት
ተመሰረተ ድጋፍና ትችት አልበኝነት/ በጣም
- የድጋፍ መዋዠቅ፣ ከፍተኛ

56
- ተሳትፎ - ተከባብሮ መኖር
- ፈጣን ምላሽ - ሁለንተናዊ ተሳት
የኢትዮጵያ - ፍትሃዊ አገልግሎት - እሴቱን እንዲጠብ
ህዝብ - ወንድማማችነትና እህታማማችነት
- ባህል፣ ቋንቋውና ሀይማኖቱ
እንዲከበርነት
- ፍትሃዊ ልማት
- ለልማቱ ምቹ ሁኔታ/ፖሊሲ - ቀና አስተሳሰብ
- ሰላምና ፀጥታ - ህግ አክባሪነት
- ተሳታፊነትና ተአማኒነት - በወቅቱ ግብር መ
ባለሀብት - ፈጣን ውሳኔ - የፋይናንስና ማቴ
- አወንታዊ ድጋፍ - ለምርጫ የድምጽ

በዴሞክራሲ ጉዳዮች በአጋርነት መስራት፣ በአሠራር ላይ የተመ


የወቅታዊ መረጃ ተደራሽነት፣ ግንኙነት ማድረግ፣
የዲሞክራሲ
ሚዛናዊነት መጠበቅ
ተቋማት
እንዲሆን

በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ መሳተፍና ህጋዊና ሰላማዊ ትግ


መወያየት፣ ቋሚ መድረክ እንዲፈጠር ላይ የተመሰረተ ው
የተፎካካሪ
በአዳዲስ ውሳኔዎችና አዋጆች ዙሪያ እንዲያደርጉ፣ በአገራ
ፓርቲዎች
ማብራሪያ ማግኘት፣ ኃላፊነትን መጋራት ላይ በኃላፊነት ስሜ
መፈለግ፣

ተባባሪ የልምድ ልውውጥና ተሞክሮ ማግኘት፣ ስትራቴጂያዊ የአጋር


አካላት በፓርቲው ወቅታዊ ውሳኔዎች ላይ መረጃ ልውውጥና ተሞክሮ
እንዲኖራቸው መፈለግ፣ ስትራቴጂያዊ አጋርነት፣
አጋርነት፣

5
- የእሴት መሸርሸር
ትፎ፣ - ድምፅ መንፈግ፣
ብቅ፣ - ፅንፈኝነትና ወደ ሌላ ፓርቲ
ማማተር

- ዕምነት መቀነስ
- ተሳትፎ መቀነስ
ከፍተኛ
መክፈል - ድጋፍ መቀነስ
ቴሪያል ድጋፍ - ድምፅ መንፈግ
ጽና የሎጂሰቲክስ ድጋፍ ወደሌላ ማማተር

መሠረተ ዴሞክራሲያዊ አመኔታ ማጣትና ፅንፈኛ


የዴሞክራሲ አጋርነት አስተሳሰብ እንዲበራከት እድል በጣም
ቅ፣ መረጃ ተደራሽ መስጠት፣ የተዛባ መረጃ ከፍተኛ
ስርጭት፣ የሥርዓት ለውጥ
እንዲመጣ መፈለግና መደገፍ

ግል እንዲያደርጉ፣ በመርህ ህጋዊና ሰላማዊ እንቅስቃሴዎችን


ውይይትና ክርክር አለማድረግ፣ከፀረ ሰላም ኃይሎች
ራዊ ዋና ዋና አጀንዳዎች ጋር መተባበር፣ በጋራ መድረክ
ሜት እንዲንቀሳቀሱ አለመሳተፍ፣ ህጋዊና ህገወጥነትን ከፍተኛ
ማደበላለቅ፣ገዥ ፓርቲ ብቻ
መኮነንና ማጥላላት

ርነትና ወዳጅነት የልምድ - ተሞክሮ ማጣት፣


ሮ ማግኘት፣ስትራቴጂያዊ - ተስፋ መቁረጥ፣
መካከለኛ
- የታማኘነት መጓደል፣
- የግንኙነት መላላት፣

57
የውጭ
ወዳጅ
ፓርቲዎች

ሲቪክ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ መሳተፍና በመርህ ላይ የተመ


ማህበራት መወያየት፣ ቋሚ መድረክ እንዲፈጠር እንዲያደርጉ፣ በሀገራ
በአዳዲስ ውሳኔዎችና አዋጆች ዙሪያ ላይ በኃላፊነት ስሜ
ማብራሪያ ማግኘት፣

Table 4 የተገልጋዮችና የባለድርሻ አካላት ቁልፍ ፍላጎቶች ትንተና

ተገልጋዮች/ የሚፈልጉት/የሚጠብቁ የ
ባለድርሻ ት አገልግሎት ጠቀሜታ ጥራት
አካላት (Customer (Function) (Qualit
(Custome services)
r
segment)
የልሳናትና ፖለቲካዊ ሰነዶች የተገነባ ፖለቲካዊ ፍላጎትና አቅር
ዋና ሥርጭት፣ አቅም ግንባታ/ አቅም፣ የተፈቱ ተኮር መሆን፣
ተገልጋዮች ሥልጠና፣የፋይናንስና ችግሮች/እንቅፋቶች ደረጃውን የጠ
የሎጅስቲክስ ድጋፍ፣ የሀገር ፣ የተገኙ አገልግሎት፣
አመራርና ውስጥና የውጭ የሥራ ልምዶች፣ ችግር-ፈቺ
አባላት ልምድ ተሞክሮ ልውውጥ፣ የወንድማማችነትና አገልግሎት፣
የፋሲሊቲ አገልግሎት፣ እህትማማችነት ነባራዊ ሁኔታ
ግንኙነት፣ ያገናዘበ ችግር
ፈች ፖለቲካዊ
ድጋፍ

5
መሰረተ ውይይትና ክርክር ህጋዊና ሰላማዊ እንቅስቃሴዎችን
ራዊ ዋና ዋና አጀንዳዎች አለማድረግ፣ከፀረ ሰላም ኃይሎች ከፍተኛ
ሜት እንዲንቀሳቀሱ፣ ጋር መተባበር፣

የአገልግሎት መገለጫዎች
ጊዜ/ወቅታዊነ ዋጋ/ወጪ ግንኙነትና ገፅታ
ty) ት (Price/c ሸፋን (Image)
(Timelines ost (relations
s) hip)

ርቦት በተቀመጠው ከልሳን ክፍያ ቀጣይነት እና


፣ መርሃግብርና በስተ ቀር አስተማማኝ አስተማማኝ
ጠበቀ ስምምንነት በነፃ የሆነ፣ ፍትሃዊ የፓርቲ
መሰረት ተጠቃሚ ገጽታ
የሚያደርጉና
ተሸጋጋሪ በሆኑ
ታ አሠራሮች ላይ
ር ማተኮር፣

58
ቁልፍ ወቅታዊ መረጃዎች፣ ጥራት የሕዝብ አመኔታ ተሳታፊነት፣
ባለድርሻ ያለውና ፍትሐዊ መጨመር፣ ተግባራዊነት፣
አካላት አገልግሎት፣ የፓርቲው እርካታ
የኢትዮጵያ አስተማማኝ ሰላም፣ ቅቡልነት ማደግ፣
ህዝብ የሕዝብ ተሳትፎ
ማደግ፣

ተልዕኮን ተሳታፊነት፣
የብልጽግና ለመወጣት ተግባራዊነት፣
ጉባኤ፣ የሚያስችል አቅም ችግር ፈቺ
ማዕከላዊና ይፈጠራል ፖለቲካዊ ድጋ
ሥራ ክትትል፣ የአቅ
አስፈጻሚ፣
ግንባታ
ኢንስፔክሽን
የሥልጠናና
ና ሥነ-
የአቅርቦት
ምግባር አገልግሎት፣
አሳታፊነት
ምርጫ የሀገሪቱ ሕጎች መከበር፣ ለሕግ በሕጉ መሰረት
ቦርድ የፓርቲው ሕገ-ደንብ የበላይነትና አገልግሎት
መከበር፣ የፋይናንስና ኦዲት ዴሞክራሲያዊነት ማግኘት
ሪፖርት ማቅረብ ፣
በምርጫ ተወዳዳሪ እጩዎች
መረጃ መስጠት፣
በዴሞክራሲ ጉዳዮች ዴሞክራሲያዊ
በአጋርነት ተሳታፊ መሆንና ተሳትፎ፣ የዴሞክራሲ
የዲሞክራሲ መሥራት፣ወቅታዊ መረጃ፣ ግልጸኝነት፣ ስርጸት
ተቋማት በሚመለከታቸው ጉዳይ አሳታፊነት፣
በጋራ መወያየትና መስራት፣ ዴሞክራሲያዊ
የፓርቲውን አቅጣጫዎችና አጋርነት
5
እንዳስፈላጊነቱና ነፃ ስትራቴጂያዊና አስተማማኝ
በቀጣይነት፣ በቋሚነት፣ ና ችግር
ድጋፍና ተቋማዊ ፈች
አገልግሎት ተቋማዊ
መስጠት ብቃት፣
የልቀት
ማዕከል
መሆን
አጀንዳዎች ላይ ነፃ ስትራቴጂያዊና አስተማማኝነ
ባተኮረ፣ በቋሚነት፣ ትና ችግር
በተቀመጠው ተቋማዊነት ፈችነት፣
ጋፍና አሰራርናፍላጎትን ተቋማዊ
ቅም መሰረት ብቃት፣
በማድረግ

ት በዕቅድ መሰረት ነጻ ተቋማዊነት ሕጋዊ


በጠየቁበት ተቋም
ጊዜ፣ ሆኖ
መታየት

በቀጣይነት ነጻ ስትራቴጂያዊና ግልጸኝነት


በቋሚነት

59
ውሳኔዎች መግለጫ
መስጠት
ለልማት ምቹ ሁኔታዎች የልማትና ፓርቲ ፓርቲያዊ ድጋ
መፈጠር፣ተሳታፊነትና አጋርነት፣
ባለሃብት ተደማጭነት፣የቅሬታዎቻቸው
ተሰሚነት፣ ውሳኔ ማግኘት፣

በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ዴሞክራሲያዊ የሰለጠነ የፓር


ተፎካካሪ መሳተፍና መወያየት፣ ሥርዓት እንቅስቃሴ
ፓርቲዎች ቋሚ መድረክ እንዲፈጠር፣ ማጠናከር፣ ሕገ-
በአዳዲስ ውሳኔዎችና ወጥ እንቅስቃሴ
አዋጆች መቀነስ፣
ዙሪያ ማብራሪያ ማግኘት፣
ተባባሪ የልምድ ልውውጥና አጋርነትና ልምድ የሰፋና ያደገ
አካላት ተሞክሮ ማግኘት፣ ልውውጥ ትስስር
በፓርቲው ወቅታዊ
የውጭ
ውሳኔዎች ላይ መረጃ
ወዳጅ
እንዲኖራቸው መፈለግ፣
ፓርቲዎች
ስትራቴጂያዊ አጋርነት፣

ሲቪክ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ የተረጋጋ ፖለቲካዊ መግባባት


ማህበራት መሳተፍና መወያየት፣ ቋሚ ሁኔታ
መድረክ እንዲፈጠር
በአዳዲስ ውሳኔዎችና
አዋጆች ዙሪያ ማብራሪያ
ማግኘት፣

6
ጋፍ በቋሚነት ነጻ በመርህ ላይ አመኔታ
የተመሰረተ
ግንኙነት

ርቲ ነጻ በመርህ ላይ
በቋሚነት የተመሰረተ አሳታፊነት
ግንኙነት

በቋሚነት ነጻ በመርህ ላይ
የተመሰረተ መተማመን
ግንኙነት

በቋሚነት ነጻ በመርህ ላይ
የተመሰረተ ምህዳር
ግንኙነት መስፋት

60
ምዕራፍ አምስት፡- ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች፣ ስትራቴጂያዊ ግቦችና
እይታዎች

5.1. ስትራቴጂያዊ ጉዳዮችና ግቦች

ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች የስትራቴጂያዊ ዕቅዱን ርዕይና ተልዕኮ ለማሳካት ቅድሚያ ትኩረት

ተሰጥቷቸው መፈታት ያለባቸው ቁልፍ ጉዳዮች ናቸው፡፡ እነዚህ ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ሲለዩ

እንደመመዘኛ የተወሰደው ዓላማና ግቦችን በማሳካት ወደ ርዕዩ ለመድረስ በሚደረገው ሂደት

ከፍተኛ እንቅፋት የሆኑት ተዘርዝረው ሲያበቃ ከነዚህ ውስጥ ቁልፍ ችግሮች ቢፈቱ ሌሎች አብረው

ሊፈቱ የሚያስችሉ ቁልፍ ጉዳዮችን በመለየት ነው፡፡ የዚህ ዕቅድ ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች የተቀረጹት

ርዕይ፣ ተልዕኮና የዳሰሳ ጥናትና የተገልጋይ/ባለድርሻ አካላት ፍላጎት ትንተና መነሻ ተደርጎ ነው፡፡

በነዚህ መስፈርቶች በመመዘን ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ተለይተዋል፡፡

የብልፅግና ፓርቲ የአስር ዓመት ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ውስጣዊና ውጫዊ ተብለው ሊከፈሉ ይችላሉ፡

፡ ውስጣዊ ገጽታው በአመራሩ መካክል፤ በአመራሩና አባላት መካከል፤ በፓርቲው የውስጥ

አደረጃጀቶች መካከል ሊኖር የሚችለውን መስተጋብር የሚመለከት ነው፡፡ የፓርቲው ውጫዊ ጉዳዮች

ሲባል ከፓርቲው አደረጃጀት፣ አሠራር፣ አመራርና አባላት ውጭ ያለ ጉዳይ ሆኖ ፓርቲው በኃላፊነት

ወይም ተባባሪነት ሊተገብራቸው የሚገቡትን መሰረታዊ ጉዳዮች የያዙ ናቸው፡፡

ብልፅና ፓርቲ የኢትዮጵያ ሕዝብ እውቅናና ድጋፍ ሳይሰጠው ራዕዩን ሊያሳካና ቀጣይነቱን ሊያረጋግጥ

አይችልም፡፡ ሕዝብ እውቅና የሰጠው ፓርቲ ደግሞ መንግሥት መስርቶ ሀገር ያስተዳድራል፡፡

መንግሥት የሚመሰረተው አሸናፊ በሆነው ገዥ ፓርቲ ቢሆንም የመንግሥትና የፓርቲ ሚና መለየት

አለባቸው፡፡ በውጭም ሆነ በሀገር ውስጥ ያሉ ፓርቲዎች ደግሞ በብልፅግና ፓርቲ ላይ ቀጥተኛ

ወይም ተዘዋዋሪ ተፅዕኖ ያላቸው ናቸው፡፡ ስለሆነም ውጫዊ ጉዳዮችን በብቃት መርቶ ጠንካራ

ፓርቲ ሆኖ እንዲቀጥል ውጫዊ ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች በዚህ እቅድ ተለይተዋል፡፡

የብልፅግና ፓርቲ የአስር ዓመት ስትራቴጂያዊ ግቦች የብልፅግና ፓርቲ ዋና ዋና ተግባራትን

የሚገልጹና የትኩረት አቅጣጫዎችን የሚያመላክቱ የስኬት ዓምዶች ሲሆኑ ተልዕኮውንና ራዕዩን

61
ዕውን ከማድረግ አኳያ ውጤት የሚያስገኙ አመራርና አባሉ ሙሉ ትኩረት ሊያደርግባቸው የሚገቡ

መሠረታዊ ጉዳዮች ናቸው፡፡ ስትራቴጂያዊ ግቦች በዕቅድ ዘመኑ መፈታት በሚገባቸው ቁልፍ

ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ላይ ርብርብ በማድረግ የተቀረጸውን ተልዕኮና ርዕይ ለማሳካት ታስበው

የተዘጋጁ ግቦች ናቸው፡፡ በመሆኑም ለእያንዳንዱ ስትራቴጂያዊ ጉዳይ ስትራቴጂያዊ ግቦች

ተለይተዋል፡፡

ስትራቴጂ ጉዳይ አንድ፡ የብልጽግና ፓርቲ ተቋማዊ ግንባታ ማረጋገጥ

የፓርቲ ተቋማዊ ግንባታ ስንል ፓርቲው በዕሳቤዎቹ ጥራት፣ በአደረጃጀቱና አሰራሩ አስተማማኘነት፣

በአመራሮቹና በአባላቱ ጥንካሬና ውጤታማነት የሚገለፅ ሆኖ የተረጋጋና የማይዋዥቅ ባህሪ ያለው

እና ለአገርና ለሕዝብ ፋይዳው የጎላ፣ በሕዝቡ አእምሮ በተጨባጭ ተግባሩና ስኬቱ የሚታወስ ፓርቲ

መገንባት ማለታችን ነው፡፡ ስለሆነም የፓርቲውን ተቋማዊ ግንባታ ለማረጋገጥ የፓርቲውን ውስጣዊ

ተቋማዊ ጥራትና ጥንካሬ ማጎልበት፣ ውስጠ ፓርቲ ዲሞክራሲ ማረጋገጥና በሚወክለው ሕዝብ

ዘንድ ቅቡል እንዲሆን በማድረግ ቀጣይነቱን አስተማማኝ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

የብልፅግና ፓርቲ ውጤታማነትና ስጋት ዋነኛ ምንጭ የሆነው በአመራሩ መካክል፤ በአመራሩና

አባላት መካከል፤ በፓርቲው የውስጥ አደረጃጀቶች መካከል ሊኖር የሚችለው የአመለካከትና

የተግባር አንድነት ጉዳይ ነው፡፡ በዚህ መሰረት ይህ ስትራቴጂያዊ ጉዳይ ከሚመለከታቸውና

ከሚመልሳቸው ውስጥ አመራሩ በብልፅግና እሳቤ በትርጉምና በአረዳድ ደረጃ ወጥነትና እውቀት

እንዲኖረው፣ በመስኩ የሚፈለገውን ክህሎት እንዲያሟላ ማድረግና ከአመራር የሚጠበቀውን

ስነምግባር እንዲላበስ ማስቻል ነው፡፡ የብልጽግና ፓርቲ አባላት ስብስብ በትውልድ ቅብብሎሽ

ውስጥ እንደመምጣቱ በአመለካከቱና አሁን ብልፅግና አሳካለሁ በሚለው እሳቤው/ርዕዩ ዙሪያ በቂ

አረዳድና መግባባት በመፍጠር የጠራ አመለካከት እንዲኖረው ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ግንኙነትም

ረድፋዊና የግንዮሽ ባህሪ ያለው ነው፡፡

በዚህ ስትራቴጂ ፓርቲው ሊሰራበት የሚገባው ሌላው ጉዳይ ፓርቲው ወጥና ውህድ ፓርቲ

እንደመሆኑ መጠን በአባላት መካከል እውነተኛ ወንድማማችነት/እህትማማችነት የሚረጋገጥበት

ማድረግ ነው፡፡ ይህንንም ለመፈፀም በየደረጃው ያለው አመራር የብቃት ደረጃ እና ቁርጠኝነት

62
እንዲረጋገጥ ማድረግ ሲቻል ነው፡፡ አመራሩ በየጉባኤው የሚቀመጡትንም ሆነ በመተዳደሪያ ደንቡ

ላይ የሰፈሩትን ለመተግበር ቁርጠኝነቱ መረጋገጥ አለበት፡፡ አስራ ሁለት ሚሊዮን አባል ያለው

ብልፅግና ፓርቲ በጥብቅ ዲሲፕሊን የሚመራ ወንድማማችነትና እህትማማችነት ባህል የሆነበት አባል

መኖሩን ካላረጋገጠ ይህ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ሊሳካ አይችልም፡፡ ስለሆነም ያለውን አመራርና አባል

ጥራት ማስጠበቅና በትውልዶች መካከል ልዩነት በማጥበብ ለአንድ ሀገራዊ አላማ ዝግጁ ማድረግ

ነው፡፡

የፓርቲው ውስጣዊ የስጋት ምንጭ ሊሆን የሚችለው ሌላው ጉዳይ በማዕከል ደረጃ በተደራጀው

ፓርቲ ጽ/ቤትና ቅርንጫፎች መካከል ያለው ግንኙነት አለመናበብ ነው፡፡ እያንዳንዱ ቅርንጫፍ

ጽህፈት ቤት ከዋናው ጽህፈት ቤትና ከሌላው ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ጋር የሚያደርገው ግንኙነት

ከፍተኛ ችግር ያለበት ነው፡፡

ይህን ስትራቴጂያዊ ጉዳይ በውጤታማነት ለመፈጸም ስትራቴጂዊ ግቦችን አንጥሮ ማውጣት

ያስፈልጋል፡፡ በዚህ መሰረት ቀጥሎ የተመላከቱት ስትራቴጂያዊ ግቦች ተለይተዋል፡፡

ስትራቴጂያዊ ግብ 1፡- ተከታታይነት ያለው የአቅም ግንባታ ሥራዎችን በመተግበር፣ በግልፅ

የተልዕኮ ስኬት ላይ የተመሰረተ የምደባ ስርዓት በመዘርጋት እና የምዘናና እውቅና ስርዓት እውን

በማድረግ የአመራሩና አባሉን የአመለካከትና የተግባር አንድነት፣ ጥራት እና ቁርጠኝነት ማረጋገጥ፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ የአላማና የተግባር አንድነት እና ጥራት ያለው አመራርና አባል፣

ስትራቴጂያዊ ግብ 2፡- የውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲ በዘላቂነት በመትከል በአመራሩ መካከል፣

በአመራሩና በአባሉ መካከል እና በፓርቲው የተለያዩ ትውልዶችና መዋቅሮች መካከል

ወንድማማችነትና እህትማማችነትን ማጎልበት፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ ግልፅነት፣ ተጠያቂነትና ውስጠ ዴሞክራሲ፣

ስትራቴጂያዊ ግብ 3፡ የፓርቲው የአደረጃጀትና የአሰራር መመሪያዎችን በጥናትና ምርምር ላይ

ተመስርቶ በማዘመንና ተግባራዊ በማድረግ የፓርቲውን ተቋማዊ ጥንካሬ ማረጋገጥ

63
የሚጠበቅ ውጤት፡ ተቋማዊ ጥንካሬ፣

ስትራቴጂያዊ ግብ 4፡- በፓርቲው ህገ ደንብና አሠራር መሰረት የአመራርና አባላት ምልመላ

በማድረግና አባላትን ሃምሳ በመቶ በማሳደግ የፓርቲውን መሠረት ማስፋት፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ መሠረቱ የሰፋ ፓርቲ (አስተማማኝነት)፣

ስትራቴጂያዊ ግብ 5፡- በፓርቲው ህገ ደንብና አሠራር መሰረት የአባላትና አመራር ምደባ፣ ስምሪት፣

ግንባታና ስንብት በማከናወን የአመራርና አባሉን ብቃትና ጥራት ማረጋገጥ፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ ጥራትና ብቃት፣

ስትራቴጂያዊ ግብ 6፡ የውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊነትን የሚያረጋገጥ፣ በመላ አባላቱ ዘንድ

ተቀባይነት ያለው በየደረጃው የውስጥ ምርጫ በማካሔድ የፓርቲውን ዲሞክራሲያዊነትና አመራር

ማረጋገጥ፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ ውስጠ ፓርቲ ዲሞክራሲና ጠንካራ አመራር

ስትራቴጂያዊ ግብ 7፡ የፓርቲ አመራር የጋራ መድረኮችን በውጤታማነት በመፈጽም የፓርቲው

ጽ/ቤቶችና አደረጃጀቶች በመርህ ላይ የተመሰረተና ተጠያቂነት ያለበት ውጤታማ ግንኙነት

እንዲኖራቸው ማድረግ፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ የሚናበብ ተቋማዊ ግንኙነት፣ ተቋማዊ የሆነ የፖለቲካ፣ የአደረጃጀት፣ የህዘብ

ግንኙነት እና የጥናትና ምርምር ሥራ፣

ስትራቴጂያዊ ግብ 8፡ የወጣትና ሴት ሊግ አደረጃጀቶችን ማጠናከር

የሚጠበቅ ውጤት፡ የተናበበና የተደራጀ አመራር

ስትራቴጂያዊ ግብ 9፡ የፓርቲውን የገቢ አቅም ማሳደግና አጠቃቀሙን ዉጤታማና ቀልጣፋ

ማድረግ፣

64
የሚጠበቅ ውጤት፡- የፓርቲው ተቋማዊ ጥንካሬ፣

ስትራቴጂያዊ ግብ 10፡ ብቃት ያለው የኮሙኒኬሽን ሥርዓት በመዘርጋት አመራሩ፣ አባሉና

ባለድርሻዎች የተሟላ መረጃ እንዲደርሳቸውና የጋራ አቋም እንዲይዙ ማድረግ፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ ያደገ እውቀትና የጋራ አረዳድ፣

ስትራቴጂያዊ ግብ 11፡ ውቅቱን የዋጀ ሐሳብ በማመንጭት፣ በየጊዜው የሚጋጥሙ ስህተቶችን

በማረም፣ በውጤታማ የተግባር አፈጻጸም ስኬቶችን በማስቀጠልና በማሳደግ የፓርቲውን ቀጣይነት

ማረጋገጥ፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ የፓርቲው ቀጣይነት፣

ስትራቴጂያዊ ግብ 12፡ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫዎችን በፓርቲ ዲሲፕሊን መፈጸም የሚችል

የፓርቲ አቅም መገንባት.

የሚጠበቅ ውጤት፡- ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ታማኒነት ያለው ምርጫ፣

ስትራቴጂያዊ ግብ 13፡ ውጤታማ ድጋፍና ክትትል ሥርዓት በመዘርጋት በመረጃ ላይ የተመሰረተ

ውሳኔ ተግባራዊ ማድረግ፣

የሚጠበቅ ውጤት፡- አዎንታዊ የዕቅድ አፈጻጸም ውጤት፣ የተሸሻለ የአመራር ብቃት፣ የተሸሻለ

ተግባቦትና የተገልጋይ እርካታ፣ የፓርቲና የመንግስት ሥራ ቅንጅት፣ በመረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ

ስትራቴጂያዊ ጉዳይ ሁለት፡ ውጤታማ የሕዝብና የባለድርሻ አካላት ግንኙነት


ማረጋገጥ

ከፓርቲው ተቋማዊ ጥንካሬ ቀጥሎ የአንድን ፓርቲ ህልውና ከሚወስኑ ጉዳዮች አንዱና መሰረታዊዩ

ማህበራዊ መሰረቱና በአጠቃላይ በህዝቡ ዘንድ ያለው ቅቡልነት ነው፡፡ ቅቡልነቱ ደግሞ የገባውን

ቃል ወይም የተሰጠውን አደራ ሳያንጠባጥብ በመፈጸም ብቃቱ ይለካል፡፡ ስለሆነም የፓርቲው እና

የህዝቡ ግንኙነት ከፓርቲው ውስጣዊ ሁኔታ ቀጥሎ የሚመጣ ስትራቴጂካዊ ጉዳይ ነው፡፡

65
በሚቀጥሉት 10 ዓመታት የአካባቢና የሀገራዊ ምርጫዎች የሚካሄዱ በመሆኑ ስትራቴጅክ ዕቅዱ

የህዝቡን ሁኔታ በአፅንኦት የሚመለከተው ይሆናል ማለት ነው፡፡ ስለሆነም ይህን ስትራቴጂያዊ ጉዳይ

በውጤታማነት ለመፈጸም የኢትዮጵያ ሕዝቦች የስትታቴጂው አካል ናቸው፡፡

የብልጽግና ባለድርሻ አካላት ከሆኑት መሰረታውያን መካከል የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ድርሻ

ከፍተኛ ነው፡፡ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ባህል የጠልፎ መጣል ባህል ነው፡፡ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ኮሙኒቲ

በውል ተፈጥሯል ማለት አይቻልም፡፡ ቢያንስ ሦስት ዓይነቶች አሉ፡፡ አንደኛው ማንኛውንም ለውጥ

በጠመንጃ አፈሙውዝ ማምጣ የሚፈልግ በግልፅ ጦርነት አውጆ የሚንቀሳቀስ ቡድን ነው፡፡ ይህ

ዓይነቱ ለፓርቲያችን ከፍተኛ ተግዳሮት እየሆነ ያለ እውነታ ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ በምርጫና

በህዝባዊ ግርግር ስልጣን መያዝ የሚከጅል ነው፡፡ ይህ አይነቱ ፓርቲ ደግሞ ከተመቸው በማነኛውም

ማህበራዊ እንቅስቃሴ ወይም ማዕበል ብልፅግናን ማስወገድ የሚፈልግ ነው፡፡ ሦስተኛው አይነት

የሀገራችን ፓርቲ ደግሞ በምርጫ ተወዳድሮ መሸፍ የቆረጠ የሚመስል ግን ወቅቱ ሲመቸው

ከተፎካካሪነት ወደተቃዋሚነት የሚያዘነብል ነው፡፡ በጥቅሉ ሲታዩ ሁሉም የኢትዮጵያ ፖለቲካ

ፓርቲዎች ስልጣንን በተመለከተ የትም ፍጭው ዱቄቱን አምጪው ዓይነት ብሂል አላቸው፡፡ ይህም

ማለት የሰናፍጭ ቅንጣት ያህክል የሚያወሩትን ያክል ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብና ተግባር የላቸውም፡

፡ ብልፅግና እንደ መሃል ፓርቲነቱና እንደ ገዥ ፓርቲነቱ እንዲሁም ለህዝቡ የዴሞክራሲ ስርዓት

ግንባታን እውን ለማድረግ እንደ ገባው ቃል፤ ፖለቲካ ፓርቲዎች ሰላማዊውን መንገድ ብቻ

ተጠቅመው ስልጣን መያዝ የሚችሉበትን የዴሞክራሲ ልምምድ በ10 ዓመቱ ዕቅዱ ውስጥ እንደ

አንድ አብይ ጉዳይ አድርጎ ወስዶታል፡፡ ይህንንም ለማድረግ በሁለትዮሽና በባለብዙ ዘርፍ ግንኙነት

በኩል አበክሮ መስራት አለበት፡፡ ይህ ዕቅድ እውን እንዲሆን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ መድረክ

እንደ መሰረታዊ የልምምድ መድረክ በመጠቀም ዓላማውን ማሳካት አለበት፡፡ ከፖለቲካ ፓርቲዎች

ጋር ብልፅግና ሊኖረው የሚገባው ግንኙነት ለኢትዮጵያ የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ እውን

መሆን ብቻ ሳይሆን ልሂቃኑ በአገራቸው ጉዳይ ዙሪያ መግባባት የሚችሉባቸውን አውዶች ለመፍጠር

ሁነኛ መንገድ ተደርጎ መወሰድ ስላለበት ነው፡፡

ከባለድርሻ አካላት ሌላው ትኩረት የሚሰጣቸው የዲሞክራሲ ተቋማት ናቸው፡፡ ከፖለቲካ ፓርቲዎች

ጋር የሚደረገውን ግንኙነት ሚዛናዊ ለማድረግ የተለያዩ የዲሞክራሲ ተቋማት ሚና ከፍተኛ ነው፡፡

66
ብዙሃንና ሙያ ማህበራት፣ ሲቪክ ማህበራት፣ ምርጫ ቦርድና ሚዲያ በዚህ ዘርፍ ውስጥ የሚታዩ

ናቸው፡፡ የብዙሃንና ሙያ ማህበራት በተለያየ ደረጃ ያለውን ማሀበረሰብ ይወክላሉ፡፡ የሴቶችና

ወጣቶች ማህበራትና ፌደሬሽኖች፣ የአሰሪዎችና ሰራተኛ ማህበራት፣ የመምህራን ማህበር ጨምሮ

የተማረውን አካል የሚያሳትፉ የሙያ ማህበራትና የባለሃብቶች ዘርፍ ማህበራት ልዩ ትኩረት

ይሰጣቸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድና የሚዲያ ተቋማት እንደ አንድ

የዲሞክራሲ ተቋማት በሀገራችን ያለው የተዛባ የፖለቲካ ፓርቲዎች ግንኙነት በህግ፣ በማጋለጥና

ወደ መሥመር በማሥገባት ሚናቸው የጎላ ነው፡፡

በአመራሩ ለሚሰራው የኮሙኒኬሽን ሥራ ደግሞ ሚዲያዎች የሚጫወቱት ድርሻ ከፍተኛ ነው፡፡

የአገራችንን ወይም የፓርቲያችንን ራዕይ፣ ዕሴቶች፣ ተልዕኮዎች፣ ፕሮገራሞች፣ ስኬቶች መሰረት

ያደረገ የተግባቦት ሥራ ተራ ጉዳይ ሳይሆን የአመራር ድርሻ ነው፡፡ ስለሆነም ኮሙኒኬሽን ስንል

ስትራቴጂያዊ ለውጥ ለማምጣት፣ በታላላቅ የጋራ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር፣ ባለ

ድርሻ አካላትን በራዕያችንና ተልዕኳችን ዙሪያ ለማሰለፍ፣ በመንግሥት/በፓርቲና በህዝብ መካከል

መተማመንን ለመፍጠር እና ራዕይና ተልዕኳችንን ለማሳት አይነተኛ መሳሪያ ነው፡፡ በመረጃ

የታጠቁ ዜጎችን በመፍጠር መብትና ግዴታውን የሚያውቅ ትውልድ ለመገንባትና እዚያው ሳለ

የፖለቲካ ፓርቲዎችን ሚናና ተሳትፎ ለማጎልበት እንዲሁም ነጻ፣ ገለልተኛና ብቃት ያላቸው ተቋማት

እንዲገነቡ ለማስቻል የሚዲያና ኮሙኒኩሽን ሚና ተኪ የሌለው ነው፡፡

የብልፅግና ፓርቲ እንደ ምሶሶ ካስቀመጣቸው ዋና ዋና ፕሮግራሞች መካከል ከውስጥ ወደ ውጭ

እየሰፋ የሚሄድ፤ ለጎረቤት አገራት ቅድሚያ የሚሰጥ የውጭ ግንኙነት ነው፡፡ ምንም እንኳን

ፓርቲው ገዥ ሆኖ ሳለ የውጭ ግንኙነት ስራዎችን የሚያካሂደው በመንግስት በኩል መሆኑ የተጠበቀ

ቢሆንም እያንዳንዱ መንግስት (የውጭ መንግስታትም) የሚዘወሩት በሚመራቸው ፓርቲ(ዎች)

በኩል እንደሆነ ይታወቃል፡፡ እንደ ገዥ ፓርቲ የመንግስት የውጭ መልካም ግንኙነት እና ቅቡልነት

ለፓርቲው ወይም በፓርቲው ድካም የተገኘ እንደመሆኑ ፓርቲያችንም ከመንግስት ውጭ ፓርቲ

ለፓርቲ ሊኖር የሚገባውን ግንኙነት በእጅጉ በሚታይና በሚጨበጥ መንገድ መስራትን እንደ ጉዳይ

አድርጎ መንቀሳቀስ አለበት፡፡ ፓርቲው በፍልስፍና ከሚመሳሉትም ሆነ ከማይመሳሰሉት ጋር

የሚወያይበት፤ ድጋፍ ለማሰባብ ሎቢ የሚያደርግበት የግንኙነት መስመሩ አድርጎ መውሰድ መቻል

67
አለበት፡፡ ኢትዮጵያን ወደ መንታ መንገድ የሚገፉ መንግስታት በስተጀርባ የፓርቲ አመራሮች ድጋፍ

መኖሩ ጥርጥር የለውም፡፡ ይህ አደጋ በውል ተረድቶ እንደ አንድ የ10 አመት ስትራቴጂካዊ ጉዳይ

ተመላክቶ የሚሰራበት ይሆናል፡፡ ከላይ የተቀመጠውን ስትራቴጂያዊ ጉዳይ ውጤታማ ለማድረግ

የሚከተሉት ግቦች ተቀምጠዋል፡፡

ስትራቴጂያዊ ግብ 1፡ ፓርቲው በሕዝብ የተሰጠውን ኃላፊነት በተደራጀ የሕዝብ ተሳትፎና

በውጤታማ የአሰራር ሥርዓት ልማት በማረጋገጥ፣ መልካም አስተዳደር በማስፈንና የሕዝብን

ጥያቄዎች በመመለስ የህዝብ አመኔታና እርካታ ማረጋገጥ፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ የሕዝብ እርካታ፣

ስትራቴጂያዊ ግብ 2፡ በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮችና በፓርቲው እሳቢዎች ላይ ያተኮሩ ሕዝባዊ

መድረኮች በመፍጠር ሕዝቡ በብልጽግና ዕሳቤ ላይ ግልጸኝነት እንዲኖረው ማድረግ፣፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ ሕዝባዊ እውቅናና ተቀባይነት፣

ስትራቴጂያዊ ግብ 3፡ የብሔረ መንግሰት (Nation building) ግንባታን ስትራቴጂያዊ በሆነ

አግባብ እውን በማድረግ ኢትዮጵያን ለዜጎቿ ምቹና ተፈቃሪ ሀገር ማድረግ፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ የጠነከረ የጋራ ማንነት፣ አስተማማኝ የሆነ የጋራ አመለካከትና ተሻጋሪና ባህል

የሆነ የጋራ እሴት፣

ስትራቴጂያዊ ግብ 4፡ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና በሕዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለው

ምርጫ በማካሔድ በአብላጫ ድምጽ ማሸነፍ፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ በብልፅግና የሚመራ መንግሥትና የሕዝብ አመኔታ

ስትራቴጂያዊ ግብ 5፡ ከተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የፉክክርና ትብብር መርህን የተከተለ

ግንኙነት ማጠናከርና ማሳደግ፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ ያደገ የፓርቲዎች ግንኙነት፣


68
ስትራቴጂያዊ ግብ 6፡ ከሲቪክ ማህበራትና የዴሞክራሲ ተቋማት ጋር ግልፅና ተከታታይ የግንኙነት

ስርዓት በመዘርጋት የመድብለ ፓርቲ ሥርዓቱን ማጠናከር፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ ብሔራዊ መግባባትና ጠንካራ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት፣

ስትራቴጂያዊ ግብ 7፡ የዲሞክራሲ ተቋማትን በመገንባትና ዲሞክራሲን በመትከል ለመብቱ

የሚታገል የሰለጠነ ማህበረሰብ መገንባት፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ የነቃና የተደራጀ ማህበረሰብ፣ እኩልነት፣ ነጻነትና የህግ የበላይነት

ስትራቴጂያዊ ግብ 8፡ የወጣትና ሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ ያገደ ተሳትና እርካታ

ስትራቴጂያዊ ግብ 9፡ ለወዳጅ ሀገራትና የመሃል ፖለቲካ ከሚያራምዱ ሌሎች ፓርቲዎች ቅድሚያ

በመስጠት ከውጭ ሀገር ፓርቲዎች ጋር ጠንካራ ትስስር መፍጠርና ማጠናከር፤

የሚጠበቅ ውጤት፡ ብሄራዊ ጥቅማችንንና ሉዓላዊነታችንን የሚያስከብሩ ትብብሮችና ስምምነቶች

ስትራቴጂያዊ ግብ 10፡ በጠንካራ የዲፕሎማሲ ተቋማት በየሀገራቱ ያሉ ዜጎቻችንን የዜግነት ክብር

ማረጋገጥ፤

የሚጠበቅ ውጤት፡ የዜጎች ክብር

ስትራቴጂያዊ ጉዳይ ሦስት፡ ጠንካራና ነፃነቱ የተጠበቀ መንግስት የመገንባት


ስትራቴጂ

ብልፅግና እንደ እሳቤ ከተንደረደረባቸው መካከል በአገራችን ከፍተኛ የሆነ የነፃ ተቋማት ግንባታ

ስብራት መኖሩን በማመላከት ነው፡፡ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የአመራር ታሪካዊ ዳራ ውስጥ

ገዥ ፓርቲው የመንግስት ተቋማትን ያለ ገደብ የሚጠቀምበት፤ ተቋማቱ ተልፈስፍሰው ግለሰቦች

የሚገኑነበት፤ ግለሰቦቹ ከአመራርነት በተነሱ ቁጥር ተቋማቱ ዘጭ እንቦጭ እያሉ የሚቀጥሉበት፤

69
በአጠቃላይ በመንግስትና በፓርቲ መካከል ድንበሩ ያለየበት፤ ይህም እያንዳንዱ ፓርቲ የሚመሰርተው

ሁሉ እንደ ገዥ ፓርቲ የህዝብን ሃብት የሚያማትርበት፤ የመንግስት ስልጣን አቋራጭ የመክበሪያ

መንገድ የሆነበትን እንደፈጠረ ይታሰባል፡፡ በተያያዘም የመንግስት ተቋማት ከፍተኛ ቀጣሪ በሆኑበት

ልማታዊ የመንግስት ግንባታ ውስጥ ተቀጣሪው ከፓርቲ ነፃና ገለልተኛ ሊሆን ባልቻለበት አድሎ፤

መድሎ፤ ማን አለበኝነት፤ ዝቅተኛ አፋፃፀም እያስመዘገበ ሳይቀር በህዝብ ወንበርና ሃብት ላይ እንደ

መዥገር ተጣብቆ እንዲኖር ይፈቅድለታል፡፡ ይህንን በመንግስትና በፓርቲ መካከል ያለውን ግንኙነት

በውል ተረድቶ ድንበር ማበጀት አንድ ውነኛ ስትራቴጂካዊ ጉዳይ ነው፡፡

የመንግሥትን አመራር የመፈጸም አቅም ስትራቴጆያዊ በሆነ አካሄድ ማሳደግ የፓርቲው አንድ

ጉዳይ ሆኖ የሚታይ ሲሆን ፐብሊክ ሰርቪሱን ማብቃትና ማሰማራት ያለበት ደግሞ መንግሥት

ነው፡፡ ስለሆነም ብልጥግና ፓርቲ ፐብሊክ ሰርቪሱ ከፖለቲካ ነፃ ሆኖ በየትኛውም ሥርዓት ሳይዋዥቅ

የሚቀጥል ማድረግ ታሪካዊ ኃላፊነት አለበት፡፡

በምንከተለው አካታች ሥርዓትና በምናልመው ብልፅግና የግል ባለሃብቱ ሚና የራሱ ድርሻ ያለው

ነው፡፡ በሥርዓቱ ከተደገፈ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ልማት በማረጋገጥ የማይተካ ሚና ያለው

ሲሆን በሥርዓቱ ካልተገራ ደግሞ የኪራይ ሰብሳቢነት ምንጭ በመሆን ማህበራዊ ምስቅልቅል

ሊያስከት ይችላል፡፡ ስለሆነም ብልፅግና ፓርቲ የግል ሴክተሩን መምራት፣ መደገፍና መግራት

ስለሚኖርበት የስትራቴጂው አካል አድርጎታል፡፡

ከላይ የተጠቀሰውን ስትራቴጂያዊ ጉዳይ ተግባራዊ ለማድረግ የሚከተሉት ግቦች ተቀምጠዋል፡፡

ስትራቴጂያዊ ግብ 1፡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፖሊሲዎችን በብቃት

ማቀድና መፈፀም የሚችል ኮር አመራር በየደረጃው ማፍራትና ማብቃት፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ ብቃት ያለው የመንግሥት አመራር፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ የተሳለጠ የተግባር አፈጻጸምና የሕዝብ እርካታ

ስትራቴጂያዊ ግብ 2፡ በጠንካራ ድጋፍና ክትትል የመንግሥት የልማት ዕቅድ በውጤታማነት


እንዲፈጸም ማደረግ፣

70
የሚጠበቅ ውጤት፡ የሕዝብ እርካታ

ስትራቴጂያዊ ግብ 3፡ የፓርቲና የመንግሥት ሚናን በመለያየት ዘላቂ፣ ውጤታማና ዴሞክራሲያዊ

የመንግስት ስርዓትን ማፅናት፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ ነፃነቱ የተረጋገጠ ውጤታማ ሲቪል ሰርቪስና መልካም አስተዳደር

ስትራቴጂያዊ ግብ 4፡ ጠንካራ ሀገረ መንግስት በመገንባት ተጋላጭነቷ የቀነሰና ቀጣይነቷ አስተማማኝ

የሆነች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ፣

የሚጠበቅ ውጤት፡ ነፃ፣ ገለልተኛና ብቃት ያላቸው ተቋማት

5.2. እይታዎች

የፓርቲው ስትራቴጂያዊ የትኩረት መስኮችና ውጤቶችን ለማሳካት ከአሦስት ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች

የተወሰዱ 27 የፓርቲው ስትራቴጂያዊ ግቦች ተለይተዋል፡፡ ስትራቴጂያዊ ግቦችን በተገልጋይ/ባለድርሻ

አካላት፣ በፋይናንስ፣ በውስጥ አደረጃጀት፣ አሠራርና አመራር እና በፖለቲካና ርዕዮተ ዓለም ግንባታ

ዕይታ ተለይተው ተቀርፀዋል፡፡ የግቦቹ ይዘትና ወሰን እንዲሁም የሚጠበቅ ውጤትም ተተንትነዋል፡

71
Table 5 እይታዎና ተቋማዊ ስትራቴጂዎች ግቦች

እይታዎች
ተገልጋይ/ባለድርሻ • የፓርቲና የመንግሥትን ሚና በመለያ
አካላት (20%)
አገልግሎትን በተጠያቂነትና ውጤታማነት

• ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫዎችን በፓርቲ ዲ

• በተደራጀ የሕዝብ ተሳትፎና በውጤታማ

ተገልጋይ እርካታ ማረጋገጥ፣

• በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ታላላቅ

• በኢኮኖሚውና ማሕበራዊ ዘርፉ የግል ባለ

መፈጸም፡፡

ፋይናንስ (10%) • የፓርቲውን ገቢ ማሳደግ፣ የሃብትና ፋይናንስ

• የውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲ በዘላቂነት በመት

በአባሉ መካከል ወንድማማችነትና እህትማማ

• የፓርቲው የአደረጃጀትና የአሰራር መመሪያዎ

የፓርቲው አደረጃጀት፣ • በፓርቲው ህገ ደንብና አሠራር መሰረት የአ


አሠራርና አመራር
• በፓርቲው ህገ ደንብና አሠራር መሰረት የአ
(35%)
አባሉን ጥራትና ብቃት ማረጋገጥ፣

• የፓርቲው ጽ/ቤቶችና አደረጃጀቶች በመርህ

ማድረግ፣
7
ስትራቴጂያዊ ግቦች

ያየትና መንግሥታዊ ተቋማትን አቅም በማሳደግ መሰረታዊ የሕዝብ

ት ማቅረብ፣

ዲሲፕሊን መፈጸም የሚችል የፓርቲ አቅም መገንባት.

የአሰራር ሥርዓት የተገልጋዮችና የባለደርሻ አካላት አመኔታ ማሳደግና የህዝብና

ሕዝባዊ መድረኮች በመፍጠር የብልጽግና ዕሳቤ ልዕልናን ማረጋገጥ፣

ለሃብቱን ድርሻ በማሳደግ የ10 ዓመቱን የመንግሥት እቅድ በውጤታማነት

ስ አጠቃቀም ብቃትና ውጤታማነትን ማሳደግ

ትከል በአመራሩ መካከል፣ በፓርቲው የተለያዩ ትውልዶች መካከል፣ በአመራሩና

ማችነትን ማጎልበት፣

ዎችን በጥናትና ምርምር ላይ ተመስርቶ ማዘመን፣

አባላት ምልመላ በማድረግ የፓርቲውን መሠረት ማስፋት፣

አመራርና አባላት ምደባ፣ ስምሪት፣ ስንብትና ግንባታ በማከናወን የአመራሩንና

ህ ላይ የተመሰረተና ተጠያቂነት ያለበት ውጤታማ ግንኙነት እንዲኖራቸው

72
• የውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊነትን የሚያረጋ

ዲሞክራሲያዊነትና አመራር ማረጋገጥ፣

• ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና በሕዝቡ

• ውጤታማ ድጋፍና ክትትል ሥርዓት መዘ

• ውቅቱን የዋጀ ሐሳብ በማመንጭት፣ በየ

ስኬቶችን በማስቀጠልና በማሳደግ የፓርቲ

• የዲሞክራሲ ተቋማትን በመገንባትና ዲሞ

• ለመንግሥታዊ አገልግሎቶች ውጤታማ

ተጠያቂነትን ማስፈንና የህግ የበላይነትን

• ጠንካራ ሀገረ መንግስት በመገንባት

ማድረግ፣

• የብሔረ መንግሰት (Nation build

ምቹና ተፈቃሪ ሀገር ማድረግ፣

• ከውጭ አገራት ፓርቲዎች ጋር ጠንካራ

• በጠንካራ የዲፕሎማሲ ተቋማት በየሀገራ

• ከተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የፉክክ

• ከሲቪክ ማህበራትና የዴሞክራሲ ተቋማት

ሥርዓቱን ማጠናከር፣

7
ጋገጥ፣ በመላ አባላቱ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ምርጫ በማካሔድ የፓርቲውን

ቡ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ምርጫ በማካሔድ በአብላጫ ድምጽ ማሸነፍ፣

ዘርጋትና ተግባራዊ ማድረግ፣

የጊዜው የሚጋጥሙ ስህተቶችን በማረም፣ በውጤታማ የተግባር አፈጻጸም

ቲውን ቀጣይነት ማረጋገጥ፣

ሞክራሲን በመትከል ለመብቱ የሚታገል የሰለጠነ ማህበረሰብ መገንባት፣

ማ የሥራና የስነምግባር ማዕቅፍ በማዘጋጀትና ተግባራዊ በማድረግ

ን ማረጋገጥ፣

ተጋላጭነቷ የቀነሰና ቀጣይነቷ አስተማማኝ የሆነች ኢትዮጵያን እውን

ding) ግንባታን ስትራቴጂያዊ በሆነ አግባብ እውን በማድረግ ለዜጎቿ

ትስስር መፍጠርና ማጠናከር፤

ራቱ ያሉ ዜጎቻችን ተገቢውን የዜግነት ክብር ማረጋገጥ፤

ክርና ትብብር መርህን የተከተለ ግንኙነት ማጠናከርና ማሳደግ፣

ት ጋር ግልፅና ተከታታይ የግንኙነት ስርዓት በመዘርጋት የመድብለ ፓርቲ

73
• ነፃና ገለልተኛ የዲሞክራሲ ተቋማትን በማ

የፖለቲካና ርዕዮተ- • ቀጣይነት ያለው ችግር ፈቺና የአስተሳስብ


ዓለም ሥራ (35%)
የአመራሩና አባሉን የአመለካከትና የተግባ

• ተከታታይነት ያለው የውይይት ባህል

በመዘርጋት እና የምዘናና እውቅና ስርዓት


• ተከታታይ የአቅም ግንባታ ሥራዎችን በመ

መፈፀም የሚችል አመራር በየደረጃው ማፍ

• ብቃት ያለው የኮሙኒኬሽን ሥርዓት በመ

የጋራ አቋም እንዲይዙ ማድረግ፣

7
ማጠናከር ዲሞክራሲን በዘላቂነት መትከል፣

ብ ልዕልናን የሚያረጋግጡ ተከታታይ የአቅም ግንባታ ሥራዎችን በመተግበር

ባር አንድነትና ቁርጠኝነት ማረጋገጥ፣

በማሳደግ፣ በግልፅ የተልዕኮ ስኬት ላይ የተመሰረተ የምደባ ስርዓት

ት እውን በማድረግ የፓርቲውን አመራርና አባል ጥራት ማረጋገጥ፣


መተግበር የሀገሪቱን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፖሊሲዎችን በብቃት

ፍራትና ማብቃት፣

መዘርጋት አመራሩ፣ አባሉና ባለድርሻዎች የተሟላ መረጃ እንዲደርሳቸውና

74
Table 6 ስትራቴጂያዊ ግቦች ትንተና

የስትራቴጂያዊ ግቦች የግቡ ይዘ


ትኩረቶች
• የህዝብ ጥያቄዎችንና የልማት ፍላጎቶችን

የሚያስችል እቅድ በጋራ መቅረፅና እርካታ

• በተደራጀ የሕዝብ ተሳትፎ ሌብነትንና ብልሹ


የተገልይ/ባለድርሻ አካላትን
• ለሀገራዊ ሰላም ጠንቅ የሆኑ ጉዳዮችንና
አመኔታና እርካታ ለማሳደግ
የአካባቢው ሰላምና ደህንነት ጠባቂና ተጠቃ
የተቀረፁ ግቦች
• በኢኮኖሚውና ማሕበራዊ ዘርፉ የግል ሴክተ

እቅድ በውጤታማነት መፈጸም፣

• ቀጣይነት ያለው የመልዕክት ቀረፃና የተግባ

• የተሟላ የቅድመ ምርጫ፣ የምርጫ ጊዜና

ስምሪት በማካሄድ ጠንካራ እና በህዝብ ዘ

የብልጽግና ዕሳቤ ልዕልናን • በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ታላላቅ ሕ

ማረጋገጥ • ሕዝብና ፓርቲ የመገናኝበት ውጤታማ

• በመረጃ ላይ የተመሰረተ የገቢ ዕቅድ ማዘጋ

• የፓርቲ የገቢ ምንጮችን በጥናት ላይ ተመ

የፓርቲውን የፋይናንስና ቁሳዊ • የአመራርና የአባላት መረጃ በትክክል ዳታ

ሃብት ለማሳደግ የተጣሉ ግቦች ስርዓት ማዘመን፣

• ከአባሉ የሚሰበሰበው የአባላት ወርሃዊ ክፍ

7
ዘትና ወሰን የሚጠበቅ ውጤት

ን ከህዝብ ጋር በመሆን መለየትና ለመመለስ

መፈጠሩን የሚያረጋግጥ ክትትል ማድረግ፣ የተገልጋዮችና የባለደርሻ

ሹ አሰራርን መዋጋት፣ አካላት አመኔታ፣ ያደገ

ና መንስዔያቸውን በጥናት በመለየት ሕዝቡን የፓርቲው ገፅታ፣ የህዝብና

ቃሚ ማድረግ፣ ተገልጋይ እርካታ

ተሩን ድርሻ በማሳደግ የ10 ዓመቱን የመንግሥት

ባቦት ሥራ መሥራት፣

ና የድህረ ምርጫ እቅድ ማዘጋጀትና የፈፃሚዎች

ዘንድ ተቀባይነት ያለው ምርጫ ማካሔድ፣

ሕዝባዊ መድረኮች መፍጠር ሕዝባዊ እውቅና እና


ማ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት ተቀባይነት፣
ጋጀት፣

መስርቶ ማስፋት፣
• ቀልጥፋና ውጤታማ
ታ ቤዝ የማስገባት የፓርቲውን የገቢ አሰባሰብ
አሰራር

• ያደገ የሃብት ምንጭ


ፍያ በወቅቱና በትክክል ገቢ መሆኑን ማረጋገጥ፣

75
• የፓርቲው የውስጥ ኦዲት በማጠናከር የ

መልኩ ስራ ላይ ማዋል፣

• የፓርቲውን ንብረት በአግባቡና በቁጠባ መያ

• ወጭን የመቀለስ ስልት መከተል፣

የአመራሩና አባሉን የአመለካከትና • አመራርና አባላት በፓርቲው ፕሮግራም፣

የተግባር አንድነት ማረጋገጥ መርሆዎች ላይ ተከታታይ ስልጠና እንዲያገ

• የጉባኤ ውሳኔዎች፣ የማዕከላዊና ሥራ አሥ

የሚገኙ አመራሮችና አባላት የጋራ አረዳድ

• በጥናት ላይ የተመሠረተ የአመራር አቅም

ማብቃት፣

• በተለያየ ደረጃ ለሚገኙ አመራር አካላት የ

ልውውጥ ማድረግ፣

• የአቅም ክፍቶች ያለባቸውን አመራሮችና አ

• አመራሮችና አባላት የእርስ በእርስ መማማሪ

• የአጭር፣ መካከለኛና ረጅም ጊዜ የሀገር

እድሎችን ማመቻቸት፣

• በአመራርና አባላት አቅም ግንባታ ሂደት

ሰጪነት፣ ወ.ዘ.ተ ላይ ማተኮር፣

7
የበጀት አጠቃቀም ግልጽነትና ተጠያቂነት ባለው

ያዙንና ጥቅም ላይ መዋሉን በየጊዜው ማረጋገጥ፣

፣ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎች እሳቤዎች፣ ዓላማና

ገኙ ማድረግ ፣

ሥፈጻሚ ኮሚቴ አቅጣጫዎች በሁሉም ደረጃ


የአላማና የተግባር አንድነት
ድ እንዲኖራቸው ማድረግ፣
ያለው የፓርቲ አመራርና
ም ክፍተት የመለየት ሥራ በመሥራት በስልጠና
አባል፣

የልምድ ልውውጥ ሥርዓት በመዘርጋት የተሞክሮ

አባላት በመለየት በሥልጠና ማብቃት፣

ሪያ ፣ትምህርት እና ተሞክሮ ልውውጥ ማካሄድ

ውስጥና የውጪ ሀገር የትምህርትና ስልጠና

ት ሞራል፣ ስነ-ምግባር፣ ችግር ፈቺነት፣ ውሳኔ

76
በአመራሩ መካከል፣ በፓርቲው • የወንድማማችነትና እህትማማችነት ግንኙነት

የተለያዩ ትውልዶች መካከል፣ • በጥናት ላይ የተመሠረተ የትውልዶችን አቅ

በአመራሩና በአባሉ መካከል ማብቃት፣

ወንድማማችነትና እህትማማችነትን • በተለያየ ደረጃ ለሚገኙ አመራርና አባላት የ

ማጎልበት ልውውጥ ማድረግ፣

• አመራሮችና አባላት የእርስ በእርስ መማማሪ

፣ በየደረጃው የውይይትና የክርክር መድረኮ

• በመርህ ላይ የተመሰረተ ግንኙነት፣

• የዲሲፕሊን ጉድለት እርምጃ አወሳሰድ

ዲሲፕሊን ተግባራዊ ማድረግ፣

• የአመራሩንና የአባላትን ስነ-ምግባርና የሥ

ማካሄድ፣ ለዚህም የተዘጋጀውን የአመራሮ

ተግባራዊ ማድረግ፡፡

• የማህበራዊ ግንኙነት ሥርዓት ዘርግቶ ተግባ

• በትውልዶች በካከል ያለው ክፍተት የማይሞ

የማረምና የማሰናበትን አቅጣጫ መከተል፣

የአባላት ምልመላ በማድረግ • የፓርቲው ምልመላ በተቀመጠው አሠራር

የፓርቲውን መሠረት ማስፋት፣ • በተሰማሩባቸው መስኮች በተግባር ግንባር

በማደራጀት በአመራር ፑል እንዲያዙ ማድረ

7
ትን የሚያጎለብቱ ትርክቶችን በጥናት መለየት፣ የዓላማ አንድነት፣

ቅም ክፍተት የመለየት ሥራ በመሥራት በስልጠና የተጠናከረ

ወንድማማችነትና

የልምድ ልውውጥ ሥርዓት በመዘርጋት የተሞክሮ እህትማማችነት

ሪያ ፣ትምህርት እና ተሞክሮ ልውውጥ ማካሄድ

ኮችን በቀጣይነት ማዘጋጀት፣

ረቂቅ መመሪያ መርምሮ ማጽደቅና በጥብቅ

ሥራ አፈፃፀም ውጤታማነት መገምገምና ምዘና

ሮችና የአባላት ግምገማና ምዘና ረቂቅ መመሪያ

ባራዊ ማድረግ፣

ሞላና መስተካከል የማይችል ሆኖ ሲገኝ የማብቃት፣

መሰረት ብቻ እንዲፈጸም ማድረግ፣


መሠረቱ የሰፋ
ቀደም ተሳታፊ የሆኑ አባላትና አመራር መረጃ
አስተማማኝ ፓርቲ
ድረግ፣

77
• ግንባር ቀደምና ለሌሎች አርአያ የሚሆኑ ግ

አባልነት በመመልመል በዕቅድ ዘመኑ 50

• ምልመላው ለፓርቲው እሴት የሚጨምሩ

የአመራርና አባላት ምደባ፣ • የአመራር ምደባ፣ የአመራር ስንብት እና

ስምሪት፣ ስንብትና ግንባታ በአሰራሩ መሠረት መፈጸም፣

በማከናወን የአመራሩንና አባሉን • የፓርቲው የሥራ ቋንቋ እንዲሆኑ የተወሰኑ

ጥራትና ብቃት ማረጋገጥ፣ ቀጥሎ በክልል ደረጃ ተግባራዊ እንዲሆኑ

የሀገራችን የሥራ ቋንቋ እንዲሆኑ መታገል።

• ተለዋዋጭ የሆኑ ሀገራዊ፣ ቀጠናዊና አለም

አመራሩ መረጃ እንዲኖረው ማድረግ፣

• በፓርቲው ንድፈ ሃሳብ መፅሔትና ሌሎች

ግብረ መልሶችን ለቀጣይ ጥናትና ምርምር

• የፓርቲው እሳቤዎች፣ ተግባራዊ እንቅስቃ

ምርምር እንዲታገዙ ማድረግ፣

• የክትትልና ድጋፍ ሥርዓቱ በአሰራሩ መሰረት

• መብቃትና መታረመረ በማይችሉ አባላትና

• የምዘናና እውቅና ስርዓት መዘርጋት፣

• የመውጫ ስትራቴጂ (exit strate

የውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊነትን • የውስጠ ፓርቲ ምርጫ የሚመራበት መ


የሚያረጋገጥ፣ በመላ አባላቱ ዘንድ

7
ግለሰቦችን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በአዲስ

በመቶ ማሳደግ

ምሁራን ላይ እንዲያተኩር ማድረግ፤

የአመራርና የአባል የምዘና ሥርዓት መዘርጋትና


ጥራትና ብቃት

አምስት ቋንቋዎችን መጀመሪያ በማዕከል ደረጃ

ማድረግና ሕገ መንግሥታዊ ዕውቅና አግኝተው

አቀፋዊ ጉዳዮች አስቀድሞ በመተንተን አባላትና

የውይይት ሰነዶች ላይ የሚሰጡ አስተያየቶችና

ር ግብዓትነት ማዋል፣

ቃሴዎችና የክትትልና ድጋፍ ስርዓቶች በጥናትና

ት እንዲፈጸም ማድረግ፣

አመራሮች ላይ የማስናበት እርምጃ መውሰድ፣

egy) ማዘጋጀትና መተግበር፣

መመሪያ ማዘጋጀት

78
ተቀባይነት ያለው ምርጫ • አካታችነትና ተመጣጣኝ ውክልናን እው
በማካሔድ የፓርቲውን • የምርጫ ስትራቴጂ በማዘጋጀት ሰፊ
ዲሞክራሲያዊነትና አመራር ሥራዎችን መስራት፣
ማረጋገጥ፣
• አስፈላጊ የሆኑ የአሠራር መመሪያዎችን

• ጠንካራ የክትትልና ድጋፍ ስርዓት መዘር

• የኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽንን

የፓርቲው ጽ/ቤቶችና አደረጃጀቶች • የተዋረድና የጎንዮሽ ግንኙነቶችን የሚያጠናክ

በመርህ ላይ የተመሰረተና ማዘመን፣

ተጠያቂነት ያለበት ውጤታማ • የኢንፎርሜሽንና ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ

ግንኙነት እንዲኖራቸው ማድረግ፣ በማስፋፋት በዋና ጽ/ቤቱና ቅርንጫፍ ጽ

እንዲሆኑ ማድረግ፣፣

• በፓርቲው ዋና ጽ/ቤትና ቅርንጫፍ ፅ/

ቴክኖሎጂ ማዕከል እንዲጠናከር ማድረግ፣

• የአመራርና የአባላት መረጃ አያያዝ በቴክኖ

• በፓርቲው ዋና ጽ/ቤትና ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶ

• ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነትን በጥብቅ ዲሲ

• የአመራር የጋራ መድረኮች ወቅታቸውን ጠ

• በግኙነት መርሁ የማይሻሻሉ ሁኔታዎች ሲ

ተከትሎ እርምጃ መውሰድ፣

7
ውን ማድረግ፣

የአመራርና አባላት የግንዛቤ ማሰጨበጫ

በማዘጋጀት ማፀደቅና ተግባራዊ ማድረግ፣

ርጋት፣

በየደረጃው ማጠናከር፣
ክሩ አሰራሮች በጥናትና ምርምር ላይ ተመስርቶ
የሚናበብ ተቋማዊ

ግንኙነት፣ ተቋማዊ የሆነ


መሠረተ ልማት በመዘርጋት፣ በማሻሻል እና

ጽ/ቤቶች መካከል ለሚደረጋው ግንኙነት አጋዥ የፖለቲካ፣ የአደረጃጀት፣

የህዘብ ግንኙነት እና

/ቤቶች የተደራጀ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን የጥናትና ምርምር ሥራ፣

ኖሎጂ የተደገፈና ወጥ እንዲሆን ማድረግ፣

ቶች መካከከል ቋሚ የግንኙነት ሥርዓት መዘርጋት፣

ሲፕሊን መፈፀም፣

ጠብቀው እንዲፈጸሙ ማድረግ፣

ሲያጋጠሙ፣ የማይፈቱ ችግሮች ሲፈጠሩ አሰራርን

79
• ሕብረብሔራዊ ማንነትን መንከባከብና
የዴሞክራሲ ተቋማትን
• የቡድን እኩልነትን ማረጋገጥና በቡድን
በመገንባትና ዲሞክራሲን
መጠበቅ፣
በመትከል ለመብቱ የሚታገል
• አካታችነትና ተመጣጣኝ ውክልናን እው
የሰለጠነ ማህበረሰብ መገንባት፣
• ሕብረብሔራዊ ፌዴራሊዝም መገንባት

ማድረግ

• የምርጫ ስትራቴጂ በማዘጋጀት ሰፊ


በጠንካራ ዲሲፕሊን የተመራ
ሥራዎችን መስራት፣
ምርጫ በማካሔድ በአብላጫ
• በ2018 እና በ2023 ለሚካሄደው ሀገራ
ድምጽ ማሸነፍ
• በየደረጃው ምርጫውን የሚያስተባበሩ

• ጠንካራ ሰዎችን በዕጩነት የማዘጋጀት

• በዕጩነት ከሚቀርቡ መካከል የሴቶችን

• በየምርጫ ክልል ከተፎካካሪ ፓርቲዎች

• ለምርጫ ክርክር በቂ ዝግጅት ማድረግ

• ብቃት ያለው የምርጫ ቅስቀሳ ማድረግ

• ብቃት ያለው የኮሙኒኬሽን ሥራ መሥ

• ብቃት ያላቸው አመራሮች መለየትና በ

• ለ2023 ለሚካሄደው ሀገራዊና ክልላዊ

8
ባሕል ማድረግ፣፣
የነቃና የተደራጀ
መብትና በግለሰብ መብት መካከል ሚዛን
ማህበረሰብ፣ እኩልነት፣

ነጻነትና የህግ የበላይነት


ውን ማድረግ፣
እኩልነት፣ ነጻነትና የህግ
የሚያስችሉ ተቋማት መፍጠርና ተግባራዊ
የበላይነት

የአመራርና አባላት የግንዛቤ ማሰጨበጫ

በብልፅግና የሚመራ
ራዊና ክልላዊ ምርጫ በቂ ዝግጅት ማድረግ፣
መንግሥት
ኮሚቴዎችን ማዋቀር፣

ስራ ማከናወን፣

ተሳትፎ ግምት ውስጥ ማስገባት፣

ጋር ኮሚቴ ማዋቀር፣

ግ፣

ግ፣

ሥራት፣

በመንግሥት አመራር ቦታዎች መመደብ

ምርጫ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ፣

80
• ተከታታይ የአቅም መፍጠሪያ መድረኮች
የወጣትና ሴት ሊግ ማጠናከር
• በሀገር ግንባታ ሂደት ውስጥ የበኩላቸ

• በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሃገራት

ተቀራርበው እንዲሰሩ የሚያስችሉ ምቹ

• በተሰማሩበት የሰራ መስክ ግንባር ቀደም

• የሊጉ ሁሉም ተግባራት በሊጉ ህግ ደ

እንዲሆን ማስቻል

• ሊጉ የሚተዳደርበትን የተለያዩ መመርያዎ

በማዘጋጀት በሚያፀድቀው የሊጎች መዋ

• የሊጎች የመረጃ ስርዓት ዘመናዊ እን

ማደራጀት፣

• በውጭም ሆነ በሀገር ውስጥ የልምድ

• የወጣትና ሴቶች ፖለቲካዊ ተሳትፎና ኢ


የወጣቶችና ሴቶች ተሳትፎና ተግባራትን አቅዶ መሥራት፣
ተጠቃሚነት ማሳድ • ወጣቶችና ሴቶች የበጎ ፍቃድ አገልግሎት

• በተሰማሩበት የሰራ መስክ ግንባር ቀደም


• የወጣትም ሆነ የሴት አደረጃጀቶች ለሀገ
ሁኔታ መፍጠር፣
ውጤታማ ድጋፍና ክትትል • በየደረጃው ውጤታማ ዕቅድ እንዲታቀድ

ሥርዓት መዘርጋትና ተግባራዊ • ተከታታይ የሥራ ግምገማና ግብረመልስ

ማድረግ፣ • ተከታታይ የሱፐርቪዥንና ግብረመልስ ሥ

8
ች ማዘጋጅት፣ የተናበበና የተደራጀ
ቸውን ሚና እንዲወጡ ማስቻል፣፣ አመራር
ት የሚገኙ ምሁራን ሊጎች በሀገራቸው ጉዳይ

መፍጠርና መምራት፣

ም እና አርአያ የሆኑ በአባልነት መመልመል፣

ደንብ፣ አሰራርና ውሳኔዎች መሰረት የሚፈፀም

ዎች ከእናት ፓርቲው ትዩዩና በማይቃረን አግባብ

ዋቅር እንዲፀድቅ ማድረግ፣

ንዲሆንና የሊጎች ሰነዶች አመቺ በሆነ መልኩ

ልውውጥ ሥርዓት መዘርጋትና መፈፀም፣

ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ያደገ ተሳትፎና

እርካታ
ት ላይ እንዲሳተፉ ማስቻል፣

ም እና አርአያ እንዲሆኑ መደገፍ፣


ገራዊ ግንባተው ሚናቸውን እንዲወጡ ምቹ

ድና ፈጻሚው እንዲግባባበት ማድረግ፣


አዎንታዊ አፈጻጸም፣
ስ ሥርዓት በመዘርጋት መተግበር፣ የተሸሻለ የአመራር ብቃት

ሥርዓት በመዘርጋት መተግበር፣ የተገልጋይ እርካታ፣ የፓርቲና

81
• ተከታታይና ወቅቱን የጠበቀ ሪፖርት እን

• በየ3ወሩ የአመራሩንና የአባላትን ስነ

መገምገምና ምዘና ማካሄድ፣ ለዚህም የ

ምዘና ረቂቅ መመሪያ በውይይት አዳብ

• መደበኛ ባልሆነ መንገድ መረጃ በ

በማዎቅ(proactive) ሆኖ እንዲመራ

ውቅቱን የዋጀ ሐሳብ • ብቃት ያለው ተቋም በየደረጃው በመገ

በማመንጭት፣ በየጊዜው • በየጊዜው የሚታዩ ስትተቶችን ያለምህ

የሚጋጥሙ ስህተቶችን • አዳዲስ ሐሳቦችን በየጊዜው በማመንጨ

በማረም፣ በውጤታማ የተግባር

አፈጻጸም ስኬቶችን

በማስቀጠልና በማሳደግ

የፓርቲውን ቀጣይነት ማረጋገጥ፣

• በመጀመሪያ አመራሩ ሀሳብ ያመነጫል፣ ሀ


ብቃት ያለው የኮሙኒኬሽን
አምነው በፍላጎት እንዲደግፉት በቂ መግባ
ሥርዓት በመዘርጋት
• የኮሙኒኬሽን አሰራር መዘርጋት
ለተጠቃሚው የተሟላ መረጃ ማድረግ፣

8
ንዲዘጋጅ ማድረግ፣ የመንግስት ሥራ ቅንጅት፣

ነ-ምግባርና የሥራ አፈፃፀም ውጤታማነት በመረጃ ላይ የተመሰረተ

የተዘጋጀውን የአመራሮችና የአባላት ግምገማና ውሳኔ

ብሮ ማፅደቅና ተግባራዊ ማድረግ፡፡

በማሰባሰብ ፓርቲው ነገሮችን አስቀድሞ

ራ የመረጃ ቋት(Archive)

ገንባት ውጤታማ ተግባራትን መከወን፣


የፓርቲው ቀጣይነት፣
ህረት ማረም፣

ጨት ከነባሩ ጋር ማላመድና መተግበር

ሀሳቡን አባሉና በርካታ ሰዎች እንዲገዙት እና

ባባት መፍጠር፣ ያደገ እውቀትና

ት(ስትራቴጂክ ከሙኒኬሽንን ተቋማዊ የጋራ አረዳድ፣


ሕዝባዊ ተቀባይነት

82
እንዲደርስና የጋራ አቋም • መግባባት ከተደረሰበት ጥቅል ሃሳብ ውስጥ

እንዲያዝበት ማድረግ፣ የሚዲያ ሽፋን እንዲያገኙ ማድረግ፣

• አጀንዳ የመትከል፣ አጀንዳ ፕራይሚንግና አ

• አመራሩ ምርጥ አጀንዳ ኮሙኒኬተር መሆኑ

• የፓርቲው የፖለቲካና የድርጅት ሥራዎችና

ሽፋን እንዲያገኙ ማድረግ፣

• በተለያየ ወቅት አመራሩ ለሚዲያዎች መ

መስጠት፣

• በፓርቲያችን ላይ በተለያዩ ሚዲያዎች የ

ለቀጣይ ስራ እንደ ግብዓት መጠቀም፤

• መደበኛ ሚዲያውንና ማህበራዊ ሚዲያውን

• ኮሙኒኬሽናችን እሴት የሚጨምር መሆኑን

• ሁሉንም የኮሙኒኬሽን ሚዲያ አይነት መጠ

ለገፅ ኮሙኒኬሽን፣ የኪነጥበብ ሥራዎች)፣

• የፓርቲ የውስጥ ኮሙኒኬሽንን ማጠናከር፣

• አመራሩና አባሉ በቀውስ ኮሙኒኬሽን ላይ

• በዕቅድ ትግበራው ቅድሚያ የሚሰጣቸውን


የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማህበራዊ
መሰረተ ልማቶችን፣ ተቋማትን፣ ወዘተ መ
ዕቅዶችን መፈፀም የሚችል
መረባረብ፣

• መሰረታዊ የሕዝብ አገልግሎትን በውጤ

8
ጥ መልዕክት በመቅረፅ ሁሉም ውይይቶች በቂ

አጀንዳ ፍሬሚንግ ስልት መከተል፣

ኑን ማረጋገጥ/መለየት/መምረጥ

ና ውሳኔዎች በተለያዩ የብዙሃን መገናኛ ዘዴዎች

መግለጫዎችና ፕረስ ኮንፈረንሶችን ማዘጋጀትና

የተዘገቡ መረጃዎችን በመሰብሰብና በመተንተን

ን ያቀናጀ የተግባቦት ሥራ መሥራት፤

ን ማረጋገጥ፣

ጠቀም(ሕትመት፣ ብሮድ ካስት፣ ኢንተረኔት፣ የገፅ

ግልፅነት መፍጠርና ተልዕኮ መስጠት፣

ን በመለየት፣ በወቅታዊ ችግር ምክንያት የወደሙ

መልሶ በመገንባት፣ ምርት ላይ ትኩረት በማድረግ

ጤታማነት መፈጸም፣

83
አመራር በየደረጃው ማፍራትና • ተጠያቂነትን ማስፈንና የህግ የበላይነትን

ማብቃት፣ • የአስር ዓመቱን የልማት ዕቅድ በተያዘለት ግ

መስጠት፣ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት

ማድረግ፣

• የአስፈጻሚ ተቋማትን አቅም ማሳደግ፣


ጠንካራ ሀገረ መንግስት
• ጠንካራ የህግ አስፈጻሚ ተቋማትን መገንባ
በመገንባት ተጋላጭነቷ የቀነሰና
• የዲሞክራሲ ተቋማትን ማጠናከር፣
ቀጣይነቷ አስተማማኝ የሆነች • ጠንካራ የሀገር መከላከያና ፀጥታ ተቋማት
ኢትዮጵያን እውን ማድረግ፣ • ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ዋሳኝ የሆኑ አጀ

• መንግሥት ተቋማት ከፖለቲካ ወገንተኝነት

• ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ማህበራት ጋ


የብሔረ መንግሰት ግንባታን
የመደገፍና የመቃወም፣ ፅንፈኝነትን ያለመቀ
(Nation building)
• አገር በቀል የእርቅ ሰላም ባህል በመጠቀም
ስትራቴጂያዊ በሆነ አግባብ እውን
በባህላዊ መንገድ እንዲፈቱ ማድረግና የተግ
በማድረግ ለዜጎቿ ምቹና ተፈቃሪ
• ተከታታይ የእርቀ ሰላም ፎረሞችን ማዘጋጀ
ሀገር ማድረግ፣
• ኅብረ ብሔራዊ ቤተሰባዊነትን የሚያጠናክ

አንድነትን በሕግ፣ በአሠራርና በተቋም ደረጃ

ማድረግ።

• የኢኮኖሚና የባህል ልውውጥ የሚዳብሩ

ቤተሰብነት ሚና እንዲኖራቸው ማድረግ፣

8
ን ማስከብር፣ ብቃት ያለው

ግብ መሰረት በብቃት መፈፀም የሚችል አመራር የመንግሥት አመራርና

እንዲተገበር ተቋማዊ ክትትል፣ ድጋፍና ቁጥጥር የሕዝብ እርካታ

ነፃ፣ ገለልተኛና ብቃት

ባት፣ ያላቸው ተቋማት፣

ትን አቅም ማዘመንና ማሳደግ፣

ጀንዳዎችን መቅረጽና ተደራሽ ማድረግ፣

ነፃ እንዲሆኑ አቅዶ መሥራት፣

ጋር ተከታታይ ውይይቶችን በማድረግ በምክንያት


የጠነከረ የጋራ ማንነት፣
ቀበል ሀገራዊ ባህል እንዲዳብር ማድረግ፣
አስተማማኝ የሆነ የጋራ
ም በሁሉም አካባቢ ሚነሱ ግጭቶች ቅድሚያ
አመለካከትና ተሻጋሪና ባህል
ግባቦት ሥራ መሥራት፣
የሆነ የጋራ እሴት፣
ጀት፣ መተግበርና ያመጡትን ውጤት መለካት፣

ክሩ ትርክቶችን በማዳበርና፣ ኅብረ ብሔራዊ

ጃ በማጠናከር ዋነኛ የሀገር አጀንዳ ሆኖ እንዲወጣ

መሠረተ ልማቶች በመገንባት ለኅብረ ብሔራዊ

84
መንግሥታዊ ተቋማትን አቅም • የመንግሥት ተቋማትን የማስፈጸም አቅም
በማሳደግ መሰረታዊ የሕዝብ • ሌብነትንና ብልሹ አሰራርን መታገልና የሕዝ
አገልግሎትን በውጤታማነት • ማነኛውም ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚ
ማቅረብ፣ ጥብቅ አመራር መስጠትና ውጤቱን መገም

• ፍትሃዊ ልማት በማምጣት የተጠቃሚ እር

ለመንግሥታዊ አገልግሎቶች • ለመንግሥታዊ አገልግሎቶች ውጤታማ የሥ


ውጤታማ የሥራና የስነምግባር • የመልካም አስተዳደር መርሆዎችን ተግባራዊ
ማዕቅፍ በማዘጋጀትና ተግባራዊ • ሌብነትንና ብልሹ አሰራርን መታገልና የተ
በማድረግ ተጠያቂነትን በመፈጸም የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ፣
ማስፈንና የህግ የበላይነትን
• ሲቪል ሰርሲሱ ከፖለቲካ ነጻ ሆኖ እንዲሠራ
ማረጋገጥ፣

• ለሀገራዊ ፖለቲካዊ ሁኔታ የተመቸ ምህዳ


ከተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር
አመራርና አባላት ላይ እርምጃ መውሰድ፣
የፉክክርና ትብብር መርህን
• ከተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር
የተከተለ ግንኙነት ማጠናከርና
ማሳደግ(በትብበር መሥራት፣
ማሳደግ፣
• ለፓርቲ ፓርቲ ግንኙነት የሚያጠናክሩ የህግ

• በህዝባዊ ግርግር ስልጣን መያዝ የሚከጅለ

ወደ መሥመር ማስገባት፣

• በምርጫ መወዳደርና ማሸነፍ፣

8
ማሳደግ፣ የተሳለጠ የተግባር

ዝብ ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ፣ አፈጻጸምና የሕዝብ

ሚያዊ እንቅስቃሴ የአካቶነት መርህን እንዲከተል እርካታ

ምገም፣ ማስተካከል፣

ርካታን ማረጋገጥ፣

ሥራና የስነምግባር ማዕቅፍ ማዘጋጀት፣ ነፃና ውጤታማ ሲቪል

ዊ በማድረግ ተጠያቂነትን ማስፈን፣ ሰርቪስና መልካም

ተቀመጡ የህግ ማዕቀፎችን በጥብቅ ዲሲፕሊን አስተዳደር

ራ ምቹ ሁኔታ መፍጠርና ሜሪቶክራሲ ማረጋገጥ፣

ዳር መፍጠር፣ እንቅፋት በሚፈጥሩ የፓርቲያችን ጠንካራ መድብለ-ፓርቲ

ሥርዓት
የተጀመረውን ጤነኛ ግንኙነት ማጠናከርና

ግ ማዕቀፎችን ማዘጋጀትና ተግባራዊ ማድረግ፣

ለውን ተቃዋሚ ኃይል በጠንካራ የፖለቲካ ሥራ

85
• ከሲቪክ ማህበራትና ከዴሞክራሲ ተቋማት
ከሲቪክ ማህበራትና የዴሞክራሲ
• ለሲቪክ ማህበራትና ዴሞክራሲ ተቋማት
ተቋማት ጋር የግንኙነት ስርዓት
ማስተካከል፣
መዘርጋት ፣
• ሲቪክ ማህበራትና ዴሞክራሲ ተቋማት በሀ

መፍጠር

• የዲፕሎማሲ ዐቅም በማሳደግ በውጭ የሚ


በየሀገራቱ ያሉ ዜጎቻችን ተገቢውን
ሆነ መመለስ የሚፈልጉ በሕጋዊ መንቀሳቀስ
የዜግነት ክብር ማረጋገጥ፤
• የዲፕሎማሲ ዐቅም የሚያሳድጉ ተቋማትን

• አፍሪካዊና ቀጣናዊ ትብብርን ማጎልበት:፣

• አካባቢያዊ ሰላምና ደኅንነት ማረጋገጥ፡-

• በሁሉም አካባቢ(ባለብዙ ዋልታ ዓለምን ታ


ከውጭ አገራት ፓርቲዎች ጋር
• ዓለም አቀፍ አጋሮችንና ወዳጅ ፓርቲዎች
ጠንካራ ትስስር መፍጠርና
• ከነባሮቹ ግንኙነት በተጨማሪ አዳዲስ ግንኙ
ማጠናከር፤

8
ጋር በጋራ ማቀድና መስራት፤ ብሔራዊ መግባባት

ሥራ እንቅፋት የሚሁኑ አሠራሮችን በጥናት

ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ነፃ ሆነው እንዲሰሩ ምቹ ሁኔታ

ሚኖሩ ዜጎቻችን በሰላም እንዲኖሩ፣ መሥራትም የዜጎች ክብርና

ቀስ እንዲችሉ መሥራት፣ ሉዓላዊነት

መገንባት፣

ታሳቢ ያደረገ) ኢኮኖሚያዊ ትሥሥር ማጎልበት፣

ጋር የሚደረገውን ግንኙነት ማስፋትና ማሳደግ፣ ብሄራዊ ጥቅማችንን

ኙነቶችን መጀመር፣ የሚያስከብሩ ትብብሮችና

ስምምነቶች

86
ምዕራፍ ስድስት፡ የውጤት አመላካቾችና መለኪያዎች

Table 7 ስትራቴጂያ ግቦች፣ መለኪያዎችና ኢላማዎች

ስትራቴጂያዊ
እይታ ኢላማ ንዑስ ኢላማ
የአፈፃፀም አመላካ

የባለድር ተሳትፎንና የባለ ድርሻ የህብረተሰብ ተሳትፎ ቁጥ


ሻ/ተገልጋ
አመኔታን ተሳትፎን ማሳደግ
ይ እይታ
ማረጋገጥ

የሕዝብ መድረኮችን መፍ

የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ቁጥ
(75%)

ድጋፍና በጎ አገልግሎት ከ
(80%)

8

የትግበራ ጊዜ (ከ1-
መነሻ የመረጃ 3ኛ ጉባኤ)
ካችና መለኪያ
ምንጭ 1 2 3
ጥር ማሳደግ ፅ/ቤት፥ ✓ ✓ ✓

ዘርፎችና

ቅርንጫፍ

ጽ/ቤቶች

ፍጠር(በቋሚነት) ፖለቲካ ዘርፍና ✓ ✓ ✓

ቅርንጫፎች

ጥር ማሳደግ ዋና ፅ/ቤትና ✓ ✓ ✓

ቅርንጫፍ

ጽ/ቤቶች

ከፍ ማድረግ ዋና ፅ/ቤትና ✓ ✓ ✓

ቅርንጫፍ

ጽ/ቤቶች

87
ሌብነትን መቀነስ(75%)

መልካም አስተዳደር ማረ

የመረጃ ጥራትና ተደራሽ

ማሳደግ(90%)

ቅሬታዎችን የፖሊሲዎች፥የህጎች፥ የጋራ


መቀነስ፥ አመኔታ
እርካታ ማሳደግ ተግባራዊነትን ማሳደግ
ማሳደግ

የማህበረሰብ አመኔታ ማ

አስተያየት)

የፓርቲዉን ገቢ የገቢ ምንጭ ማሳደግ (


የፓርቲዉን መጨመር
ከፋይናነ የበጀት አቅም
ስ እይታ ማሳደግ፣

ዓመታዊ ገቢን ማሳደግ(

8
) ዋና ፅ/ቤትና ✓ ✓ ✓

ቅርንጫፍ

ጽ/ቤቶች

ረጋገጥ(80%) ዋና ፅ/ቤትና ✓ ✓ ✓

ቅርንጫፍ

ጽ/ቤቶች

ሽነት አደረጃጀት ✓ ✓ ✓

ዘርፍ

ራ ዉሳኔዎች ዋና ጽ/ቤቱና ✓ ✓ ✓

ቅርንጫፍ

ጽ/ቤቶች

ማሳደግ(በሕዝብ ዋና /ጽቤት፣ ✓ ✓ ✓

ቅ/ጽ/ቤቶች

(85% ) አስተዳደር ✓ ✓ ✓

ዘርፍና

ቅ/ጽ/ቤቶች

(100%) አስተዳደር

ዘርፍና

ቅ/ጽ/ቤቶች

88
ወርሃዊ መዋጮን አሟጦ

መሰብሰብ(100%)

የፓርቲዉን የሀብት ድጋፍ

ከፍ ማድረግ(100%)

የአጠቃቀም ቁጠባንና ብክነትን ማስወገድና ወጪ

ብቃትና ዉጤታመነትን መቀነስ(100%)

ዉጤታማነት ማረጋገጥ

ማሳደግ የወጪ አግባብነትን ማረ

ቀጥጥር (100%)

ብቃትና አሠራርን መሠረት የአባላት ምልመላ (ቁጥር

ተነሳሽነት ያለዉ ያደረገ አባላት

ሃይል ማፍራት ምልመላ፣ ምደባ፣ የአመራር ምልመላ


የፓርቲዉ
አደረጃጀ ሥምሪትና ስንብት
ት፣ የአመራር ምደባና ተልዕኮ
አሠራርና
(100%)
አመራር
የአመራርና አባላት ጥራት

ማረጋገጥ(100%)

8
ጦ አስተዳደር ✓ ✓ ✓

ዘርፍና

ቅ/ጽ/ቤቶች

ፍ ግኝት መጠንን አስተዳደር ✓ ✓ ✓

ዘርፍና

ቅ/ጽ/ቤቶች

ጪን አስተዳደር ✓ ✓ ✓

ዘርፍና

ቅ/ጽ/ቤቶች

ረጋገጥ፥ የሀብት አስተዳደር ✓ ✓ ✓

ዘርፍና

ቅ/ጽ/ቤቶች

ር) 12.25 ሚ አደረጃጀት 14ሚ 16ሚ 18ሚ

ዘርፎች

አደረጃጀት ✓ ✓ ✓

ዘርፎች

ኮ አሰጣጥ አደረጃጀት ✓ ✓ ✓

ዘርፎች

ት አደረጃጀት ✓ ✓ ✓

ዘርፎች

89
የአባላትን መታወቂያ ድ

መድረግ(15 ሚሊ)

ሒስ ግለሂስ(40)

የአመራር ፑል ማዘጋጀት(

የአመራርና አባላት ጥራት

ማረጋገጥ(በቋሚነት

ቅልጥፍናን፥ በፈጠራ፥ የአደረጃጀት ክፍተቶችን መ

ግልፀኝነት፥ በምርምርና እንዲሆን ማድረግ(100%

ተጠያቂነት፥ በልምድ ልዉዉጥ አደረጃጀት በሁሉም ደረጃ


ዲሞክራሲን የሚገኙ አዳዲስ ማድረግ(100%)
በፓርቲዉ አደረጃጀት ለተልዕኮ አፈፃፀም አስቸጋ
ማስፈን አሠራሮችን አሠራሮች መለየት (100
መፍጠር፣

ዘመናዊና ቀልጣፋ አሠራ

መዘርጋት(80%)

ቀልጣፋና የአገልግሎት የብቃት መመዘኛ ሥርዓት

ዉጤታማ ተደራሽነት እና መዘርጋት(100%)

9
ድጂታል አደረጃጀት ✓ ✓ ✓
ዘርፎች

አደረጃጀት ✓ ✓ ✓
ዘርፎች

(100%) አደረጃጀት ✓ ✓ ✓
ዘርፎች

ት አደረጃጀት ✓ ✓ ✓
ዘርፎች

መለየትና የተሟላ አደረጃጀት ✓ ✓ ✓

%) ዘርፎች

ጃ እንዲናበብ አደረጃጀት ✓ ✓ ✓

ዘርፎች

ጋሪ የሆኑትን ጥናትና ✓ ✓ ✓

0%) ምርምርና

አደረጃጀት

ዘርፎች

ራርን አደረጃጀት ✓ ✓ ✓

ዘርፎች

ት ጥናትና ✓ ✓ ✓

ምርምርና

90
አገልግሎት ፈጣን ምላሽ

መስጠት፥ መስጠት

ተልዕኮን በብቃት የሥራ ምዘናን ማዘመን(


መወጣት

የቅሬታ ሰሚ ተቋም በማ

መጠንን መቀነስ(80%)

የእርካታ መጠንን መጨመ

በቴክኖሎጂ የኢንፎርሜሽን የቴክኖሎጂ መሠረ

የዘመነ፥የመረጃና ቴክኖሎጂ መዘርጋት(75%)

ዶክመንቴሽን አጠቃቀም ክህሎት ያላቸዉን ባለሙ


ሥርዓት
የአይቲ ግብዓቶችን ማሟ

የሠራተኛ የሠራተኛ የሥራ አካባቢን ምቹ ማ

ተነሳሽነትና እንዲጎለብት የምዘናና ማበረታቻ


ብቃት ማረጋገጥ፥ ማድረግ ማዘመን(75%)

ቀጣይነት ያለዉ ሥልጠና

9
አደረጃጀት

ዘርፎች

(100%) ጥናትና ✓ ✓ ✓

ምርምርና

አደረጃጀት

ዘርፎች

ማቋቋም የቅሬታ ጽ/ቤቶችና ✓ ✓ ✓

አስተዳደር

ዘርፎች

መር(80%) ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ረተ ልማትን ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ሙያ መመደብ(75%) ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ሟላት(90%) ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ማድረግ(95%) ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ቻ ሥርዓትን ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ና መስጠት(90%) ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

91
ተልዕኮን በብቃት ሀላፊነትንና ተጠያቂነትን

መከወን
የዲስፕልን ችግር መቀነስ

ሊጎችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማ

ውጤታማ
ጉባኤ ማካሔድ(በቁጥር
የማድረግ

የኢንስፔክሽንና ክትትልና ድጋፍ(40 ጊዜ

ስነ-ምግባር ሥራ
አቤቱታዎችን

ማስተካከል(በቋሚነት)

የማህበራዊ እርስ በርእስር መማማር(

ትስስር ትስስር መፍጠር(በቋሚነ

መተማመን መፍጠር(በቋ

ቅቡልነትን ዴሞክራሲያዊ፣ ያደገ ዴሞክራሲያዊ ባህ

ያረጋገጠ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና 75%)፣

በሕዝቡ ዘንድ
በሕዝቡ ዘንድ ያለው ተ
ተቀባይነት ያለው
አስተያየት)፣
ምርጫ ማካሔድ
አብላጫ ድምጽ(65%)

9
ማስፈን(100%) ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ስ(85%) ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ማሳደግ(85%) ✓ ✓ ✓

3) ✓ ✓ ✓

ዜ) ✓ ✓ ✓

መመርመርና ✓ ✓ ✓

(በቋሚነት) ✓ ✓ ✓

ነት) ✓ ✓ ✓

ቋሚነት) ✓ ✓ ✓

ህል(በሕዝብ ተሳትፎ ምርጫ ዘርፍና ✓ ✓ ✓

ጽ/ቤቶች

ተቀባይነት (በሕዝብ ምርጫ ዘርፍና ✓ ✓ ✓


ጽ/ቤቶች

ምርጫ ዘርፍና ✓ ✓ ✓
ጽ/ቤቶች

92
ምርጫውን ማሸነፍ
አሸናፊ መሆን

የምርጫ ወጪ

ወቅቱን የጠበቀ የጉባኤ ዝግጅት በየደረጃው ኮንፈረንስ ማ

ጉባኤ ማካሄድ ማድረግ ጊዜ ).

ሪፖርት ማዘጋጀት(በቁጥ

ዲሞክራሲያዊ የአመራር

ጊዜ)

መደበኛ የማዕከላዊና ሥራ የማዕከላዊ ኮሚቴ መድረ


አሠራሮች የመድረክና
አስፈፃሚ፣
የሪፖርት ዝግጅት ሥራ አስፈፃሚ መድረክ(
አመራር
የፓርቲ አመራር መድረኮ
መድረኮች፣

የድጋፍና ክትትል ሪፖርትና ግብረ-መልስ(ቁ


ዕቅድና ሪፖርትና
ሥርዓት፣
ግምገማ መደበኛ ግምገማ (ቁጥር

ሱፐርቪዥንና ግብረመልስ

የተቋማት ህብረ ወንድማማችነትናእ መልካም ታሪኮቻችንን የ



ብሔራዊነትና ህትማማችነትን ስህተቶችን ሁሉ የማረም

9
ምርጫ ዘርፍና ✓ ✓ ✓
ጽ/ቤቶች

400, ሚሊዮን ምርጫ ዘርፍና 600ሚ ሚ 720


, ሚ
ጽ/ቤቶች

ማካሄድ(በቁጥር 3 ዋና ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ጥር 3 ጊዜ)፣ ዋና ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ር ምርጫ(ቁጥር 3 ዋና ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ረክ(ቁጥር 20)፣ ዋና ጽ/ቤቱ ✓ ✓ ✓

(ቁጥር 40)፣ ዋና ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ኮች(ቁጥር 60)፣ ዋና ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ቁጥር 40)፣ ዋና ጽ/ቤቱ ✓ ✓ ✓

ር 40)፣ ዋና ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ስ(ቁጥር 40)፣ ዋና ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

የማስፋፋትና ዋና ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ም ሥራ(በቋሚነት)

93
አደረጃጀ ሀገራዊ ማረጋገጥ፥ ለብሔራዊ መግባባትና ዕ

አንድነትን የተስተካከለ የታርክ መድረኮችን ማመቻቸትና
ግብኙነት
ማረጋገጥ ዕይታ፥ሀገራዊ መሳተፍ(በቋሚነት)

መረጋጋት፥ ብዝሃ ብዝሃ ቋንቋ በማዕከልና


ቋንቋ ማድረግ(100%)

የፓቲውን አዳዲስ አሠራሮች ማላመ


የፓቲውን ቀጣይነት
ቀጣይነት
ማረጋገጥ
ማረጋገጥ
ነባር አሠራሮችን ማዘመን

መድበለ ግንኙነት ግንኙነት መፍጠር ከተፎካካሪ ፓርቲዎችና ሲ


ፓርቲ
መፍጠር ጋር ቋሚ ግንኙነት መፍ
ሥርዓት
ማጠናከር መተግበር(በቋሚነት)

ከሲቪል ማህበራት ጋር ቋ

መፍጠርና መተግበር(በቋ

9
ዕርቀ ሠላም ዋና ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ና በንቃት

በክልል ተግባራዊ ዋና ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

መድ(በቋሚነት) ዋና ጽ/ቤቶችና ✓ ✓ ✓
አደረጃጀት
ዘርፍ

ን(በቋሚነት) ጽ/ቤቶችና ✓ ✓ ✓

አደረጃጀት

ዘርፍ

ሲቪል ማህበራት የፖለቲካ ✓ ✓ ✓


ፓርቲዎችና
ፍጠርና
ሲቪክ ማህበራ
ዘርፍ

ቋሚ ግንኙነት የፖለቲካ ✓ ✓ ✓
ፓርቲዎችና
ቋሚነት)
ሲቪክ ማህበራ
ዘርፍ

94
ከወዳጅ ግንኙነት መፍጠር ግንኙነት ማሳደግ(በቋሚ
አጋርነትን ፓርቲዎች ጋር
ማጠናከር

ከሌሎች ግንኙነት መፍጠር ግንኙነት መጀመር(በቋሚ


ፓርቲዎች ጋር

የሀገርና ዜጎች የፓርቲዉንናመንግ የሚሲዮን ብቃትን ከፍ

ክብርን ማረጋገጥ ሥትን

ዓለም አቀፋዊ
ዲያስፖራን የማደራጀትና
ተቀባይነት ከፍ
ማከናወን(75%)
ማድረግ

የዉጪ ጉዳይ ተቋም አቅ

መገንባት(በቋሚነት)

የጎረቤት ሀገራት ትሥሥር

ማሳደግ(በቋሚነት)

የዓላማና የአመራርና አባላትን የአቅም ክፍተትን በጥናት

የፖለቲካ የተግባር አንድነት አቅምን ዝግጅት ማድረግ(100%)


ና ያለዉ የፓርቲ መገንባት/ማሳደግ
አይዲዮሎ
አመራርና አባል፣

9
✓ ✓ ✓
ሚነት) የሕዝብና
ዓለም ዓቀፍ
ግንኙነት ዘርፍ
✓ ✓ ✓
ሚነት) የሕዝብና
ዓለም ዓቀፍ
ግንኙነት ዘርፍ

ማድረግ(75%) የህዝብና ✓ ✓ ✓
ውጭ
ግንኙነት

የማንቃት ሥራ የህዝብና ✓ ✓ ✓
ውጭ
ግንኙነት

ቅም በቀጣይነት የህዝብና ✓ ✓ ✓
ውጭ
ግንኙነት

ርን የህዝብና ✓ ✓ ✓
ውጭ
ግንኙነት

ት መለየትና ጥናትና ✓ ✓ ✓

) ምርምር፣

ፖለቲካና

ርዕዮተ-ዓለም፣

95

ተግባራት

ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታን

መቀመር፥መተንተን(85%

ቀጣይነት ያለዉ የመልዕክ

የተግባቦት ሥራ(85%)

የአጭር፥ መካከለኛና ረጅ

መስጠት(95%)

የልምድ ልዉዉጦችን ማ

ወቅቱን የጠበቀ ግምገማ

ማድረግ(80%)

የመንግሥት ሥልጠና(85%)፣
አቅም ግንባታ
አመራር ሥልጠናዊ ግምገማ(85%

ማብቃት፣ ልምድ ልውውጥ(በቋሚነ

ሱፐርቪዥን(በቁጥር 40

የአካባቢን ሠላም ማረጋገ

9
ሥልጠና

ዘርፎች

ን መከታተል፥ ፖለቲካና ✓ ✓ ✓

%) ርዕዮተ-ዓለም

ዘርፍ

ክት ቀረፃና ፖለቲካና ✓ ✓ ✓
ርዕዮተ-
ዓለምና
የሕዝብና
ዓለም ዓቀፍ
ዘርፎች
ጅም ሥልጠና ሥልጠና ዘርፍ ✓ ✓ ✓

ማድረግ(በቋሚነት) ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ማዊ ሥልጠናን ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

%)፣ ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ነት)፣ ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

) ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

ገት(100%) ጽ/ቤቶች ✓ ✓ ✓

96
ምዕራፍ ሰባት፡ ስትራቴጂያዊ እርምጃዎች

ስትራቴጂያዊ እርምጃዎች በተቋሙ የአፈጻጸም መነሻ (Performance Baseline) እና በተቀረጹት

ዒላማዎች መካከል ያለውን ክፍተት ለመሙላት የሚቀረጹ አስቻይ ፕሮግራሞች፣ ፕሮጀክቶችና ዋና

ዋና ተግባራት ናቸው፡፡ በመሆኑም ስትራቴጂያዊ እርምጃዎች ሲባል ከተቋሙ የእለት ከለት ተግባር

የተለዩ እና ለውጥ ለማምጣት የምንተገብራቸው መሳሪያዎች (ዘዴዎች) ማለት ነው፡፡

በሌላ አገላለጽ ስትራቴጂያዊ እርምጃዎች ማለት ስትራቴጂያዊ ግቦችን በማስፈጸም ስኬታማነትን

ለማረጋገጥ የሚረዱ፣ ከስትራቴጂያዊ ግቦች ጋር ትስስር ያላቸው እና ወደ ተግባር የሚቀየሩ እንዲሁም

ትርጉም ያለው ተቋማዊ ለውጥ ለማምጣት ሰፊ ዕድል የሚፈጥሩ የአጭርና የረጅም ጊዜ ተግባራት፣

ፕሮጀክቶች እና ፕሮግራሞች ናቸው፡፡

የፓርቲያችንን ብልፅግና ተልዕኮ በውጤታማነት ለመተግበር በቀጣይ አስር ዓመት በስትራቴጂክ

እቅዱ ሊያገለግሉ የሚችሉ አሁን በስራ ላይ ያሉና አዲስ ዕጩ ስትራቴጂያዊ እርምጃዎችን በመለየት፣

በመምረጥ እና ለተመረጡትም መግለጫና ፕሮጀክት ፕሮፋይል በማዘጋጀት የሚከተሉት 15

ስትራቴጂያዊ እርምጃዎች ተቀርፀዋል፡፡

1. የአመራርና የአባል አቅም ግንባታ ፕሮግራም

2. የብልፅግና ፓርቲ የተግባቦት ትግበራ ፕሮግራም

3. የፓርቲውን የድርጅትና የፖለቲካ ሥራዎች በጥናትና ምርምር የማጠናከር ፕሮጀክት

4. የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂና የመረጃ አያያዝ ፕሮጀክት

5. የብልፅግና ፓርቲ እሳቤዎቹን ማስፋፋትና ማስረፅ ፕሮግራም፣

6. የድርጅት ተግባራትን ማከናወን ፕሮግራም

7. ጉባኤን የማካሄድ ፕሮጀክት

8. የሀገራዊ፣ ክልላዊና አካባቢ ምርጫ ፕሮግራም፣

9. የሰው ሀብት፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ፕሮግራም

10. ከተፎካካሪ ፓርቲዎችና ከዴሞክራሲ ተቋማት ጋር አብሮ የመስራት ፕሮግራም፣

11. ሊጎችን ውጤታማ የማድረግ ፕሮግራም


97
12. የኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ተግባራት ፕሮግራም

13. መልካም አስተዳደርን በማስፈን የተገልጋይ እርካታን ማረጋገጥ ፕሮጀክት

14. የክትትል፣ የድጋፍና ግብረመልስ ትግበራ ፕሮግራም

15. የማህበራዊ ትስስር ማጠናከር ፕሮጀክት፣

16. የወዳጅ ሀገራት ፓርቲዎች ግንኙነት ፕሮግራም፣

17. የፓርቲው የስልጠና ማዕከል ማቋቋም ፕሮጀክት

18. የፓርቲ የውስጥ ምርጫ ፕሮጀክት


19. ፓርቲውን ብራንዲንግ የማድረግ ፕሮጀክት

እርምጃ አንድ. የአባላትና የአመራር አቅም ግንባታ ፕሮግራም

ወሰን፡- ይህ ስትራቴጂያዊ እርምጃ አላማ ያደረገው ተከታታይነት ባለው የዕቅድ ትግበራ፣ ክትትልና

ድጋፍ እንዲሁም ማነቃቂያ በመፍጠር ፈጻሚ ኃይሉና አመራሩ የፓርቲውን ርዕይና ተልዕኮ መፈጸም

በሚችልበት ደረጃ ላይ ማድረስ ነው፡፡ በዚህም የአቅም ክፍቶች በመለየት እና የስልጠና ሰነዶች

በማዘጋጀት ፣የአመራር የልምድ ልውውጥ፣ የእርስ በእርስ መማማሪያ እና የግምገማና የሂስ ግለ

ሂስ ባህል ለሥራ አፈፃፀምና ለፓርቲው አቅም ግንባታ እንዲጠቀሙበት ማድረግ ነው፡፡

ጠቀሜታ፡- አመራሩና አባሉ የተሻለ እውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት ፈጥረውና በፓርቲው ርዕይና

ተልዕኮ ላይ ግልፀኝነትና የጋራ አረዳድ ይዘው የተሰጣቸውን ተልዕኮ በውጤታማነት ለመፈጸም

የሚያስችል ይሆናል፡፡

የሚጠበቁ ውጤቶች፡-

• የአመራርና የአባላት የአመለካከትና የተግባር አንድነት

• ያደገ የአመራርና አባላት የመፈጸም አቅም፣

• የአመራርና አባላት የስራ ባህልና ተነሳሽነት፣

• የተገልጋይ እርካታ፣

የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፡-
98
• የስልጠና ፍላጎት እና የአቅም ክፍቶች መለየት፤

• የስልጠና ሰነዶች በማዘጋጀት ፣

• ሰልጣኞችን መለየት፣

• ስልጠናውን መስጠት፣

• የአመራርና አባላት ብቃት ምዘና ማካሄድ፣

• ስልጠና ያስገኘው ውጤት ጥናት ማድረግ፣

• የድጋፍ፣ ክትትልና ግምገማ ስርዓት መፍጠርና ማጠናከር፣

• የእርስ በርስ መማማሪያ እና ተሞክሮ ልውውጥ ማዳበር፣

• የፓርቲው ግምገማዊ ስልጠና ለሥራ አፈፃፀምና ለፓርቲው አቅም ግንባታ እንዲጠቀሙበት

ማድረግ፣

ለስራው የሚያስፈልግ ገብዓት /በጀት/፡- በግምት 500 ሚሊዮን ብር፣

አስተባባሪ፡- ብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት

የፕሮግራሙ ባለቤት፡- ስልጠና ዘርፍ

ፈጻሚ አካላት፡- አደረጃጀት፣ ፖለቲካ ዘርፍ፣ ስልጠና ዘርፎች፣ ቅ/ጽ/ቤቶች፣

እርምጃ ሁለት፡- የብልፅግና ፓርቲ የተግባቦት ትግበራ ፕሮግራም

ወሰን፤ የፓርቲው ሥራዎች የሚዲያ ሽፋን እንዲያገኙ፣ ለሚዲያዎች መግለጫዎች መስጠት

በማህበራዊ ሚዲያ የፓርቲውን አላማዎች ማስተዋወቅ እና የፓርቲው ዋና ዋና መልዕክቶች

ማስተላለፍ ነው፡፡

ጠቀሜታ፤ የፓርቲውን እሳቤዎችን የበላይነት እንዲያገኝ ያደርጋል፡፡

የሚጠበቅ ውጤት፤

• የፓርቲው ተቀባይነትና ድጋፍ መጨመር፣

99
የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፤
• ብቃት ባለው የሰው ሃይልና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ዘርፉን ማጠናከር፣

• የፓርቲው የፖለቲካና የድርጅት ሥራዎችና ውሳኔዎች በተለያዩ የብዙሃን መገናኛ ዘዴዎች

ሽፋን እንዲያገኙ ማድረግ፣

• የፓርቲው ዋና ዋና መልዕክቶች ቀጣይነት ባለው መልክ የመልዕክት ቀረፃና የተግባቦት ሥራ

በመሥራት ለአመራሩ፣ለአባሉና ለህዝቡ ተደራሽ ማድረግ፣

• ለሚዲያዎች መግለጫዎችና ፕረስ-ኮንፈረንሶችን ማዘጋጀትና የፓርቲውን ዓላማ ማስተዋወቅ

• በማህበራዊ ሚዲያ የፓርቲውን አላማዎች ማስተዋወቅ ፣

ለስራው የሚያስፈልግ በጀት፤ በግምት 20 ሚሊዮን ብር

አስተባባሪ፤ብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት

የፕሮግም ባለቤት፤የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ

ፈጻሚ አካላት፤ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ እና ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች

እርምጃ ሶስት፡ የፓርቲው የድርጅትና የፖለቲካ ሥራዎች በጥናትና ምርምር የማጠናከር


ፕሮጀክት፣

ወሰን፤ ሥልጠናዎችና የፖለቲካ ሥራዎች ያመጡት ውጤት፣ የአደረጃጀትና አሰራር መመሪያዎች

አፈጻጸ ም እና በፓርቲው ንድፈ ሃሳብ መፅሔት ላይ የሚሰጡ ውይይቶች ለቀጣይ ሥራዎች

ጥናትና ምርምር ማካሄድና መሰነድን ያካትታል፡፡

ጠቀሜታ፡- በበቂ እውቀት ላይ የተመሰረተ ውሳኔ መስጠትና ተግባራትን ማከናወን፤

የሚጠበቅ ውጤት፤
• ተልዕኮውን በውጤታማነትና በጥራት መፈፀም የሚችል የፓርቲ መዋቅር ፡

• በመረጃ የተደገፉ ውሳኔዎች፣ ዕቅድና አፈጻጸም፣

100
የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት
• የፓርቲው ፖለቲካና ድርጅት ተግባራት በሚመለከት ጥናትና ምርምር ማድረግ፣

• በፓርቲው ንድፈ ሃሳብ መፅሔት ላይ የሚሰጡ የዉይይት ሪፖርቶች፣ አስተያየቶችና ግብረ

መልሶችን በመጠቀም ለቀጣይ ሥራዎች ጥናትና ምርምር ማካሄድ፣

• ለሀገራዊ ሰላም ጠንቅ የሆኑ ጉዳዮችንና መንስዔያቸውን በጥናት በመለየት ፣

• የመደመር እሳቤና ለሀገራችን ያስገኛቸውን ፋይዳዎች ከሌሎች ፖለቲካዊ አስተሳሰቦች ጋር

በተገኙ ውጤቶች ላይ ጥናት በማድረግ በመረጃ አስደግፎ ማቅረብ ፣

ለስራው የሚያስፈልገው በጀት፤ በግምት 30 ሚሊዮን ብር

አስተባባሪ፤ ብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት

የፕሮጀክቱ ባለቤት፡ የፖለቲካ፣ አደረጃጀትና ጥናትና ምርምር ዘርፍና ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች፣

ፈጻሚ አካላት፤- ዘርፎች እና ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች

እርምጃ አራት፣ የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂና የመረጃ አያያዝ ፕሮጀክት

ወሰን፤ መሠረተ ልማት የመዘርጋት፣ የማሻሻል እና የማስፋፋት ፣ በዋና ጽ/ቤት የተደራጀ

የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ማዕከል ማጠናከር፣ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የቴክኖሎጂ

አጠቃቀም ማጠናከር ፣መላው መዋቅሩን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አቅም መገንባት፣ የአመራርና

የአባላት መረጃ ቋት አያያዝ በማጠናከር ትክክለኛ መረጃ ማግኘት ተግባርን ያካትታል፡፡

ጠቀሜታ፤ የአመራርና የአባላት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ለማሳደግ እና ዘመናዊ አሰራር በመከተል

ውጤታማ ተግባር ለማከናወን፣

• በቴክኖሎጂ የታገዘ የመረጃ እና የዶክመንቴሽን አያያዝ ሥርዓት ለመዘርጋት፣

የሚጠበቁ ውጤቶች፤

• ዘመናዊ መረጃ እና ዶክመንቴሽን ፣


101
• የቴክኖሎጂ አጠቃቀም መጨመር

• ቀልጣፋና ውጤታማ የስራ አፈጻጸም፣

• በመረጃ ላይ የተመሠረተ ውሳኔ፣

የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፤

• በኢንፎርሜሽንና ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ ብቃት ያለው የሰው ሃይል ማፍራት፤

• መሠረተ ልማት የመዘርጋት፣ የማሻሻል እና የማስፋፋት ሥራ ማከናወን፣

• በፓርቲው ዋና ጽ/ቤት የተደራጀ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማዕከል የበለጠ እንዲጠናከር

ማድረግ፣

• ከማዕከል እስከ ወረዳ ያሉ መዋቅሮች የኢንፎርሜሽንና ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ አጠቃቀም

እንዲጠናከር ማድረግ ፣

• የመዋቅሩ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አቅም ማሳደግ፣

• የአመራርና የአባላት መረጃ ቋት አያያዝ እሰከ ወረዳ ድረስ በቴክኖሎጂ እንዲደገፍ ማድረግ፣

• የመረጃና የዶክመንቴሽን አያያዝ ስርዓታችን በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆን

ማድረግ፤

የሚያስፈልግ ግብዓት /በጀት/፤ በግምት 100 ሚሊዮን ብር

አስተባባሪ፤ብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት

የፕሮጀክቱ ባለቤት፡ ጽ/ቤትና አደረጃጀት ዘርፍ

ፈጻሚ አካላት፤ አደረጃጀት ዘርፍ፣ አይሲቲ ክፍል እና ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች

እርምጃ አምስት፡ የብልፅግና ፓርቲ ፖለቲካዊ እሳቤዎችን ማስፋፋትና ማስረጽ ፕሮግራም

102
ወሰን፤ የፓርቲው አመራርና አባል በእሳቤው ላይ እውቀት፣ ክህሎትና የጠራ አመለካከት እንዲይዙ፣

በኅብረተሰቡ ዘንድ ግንዛቤ እንዲያድግ ማድረግ ነው፡፡

ጠቀሜታ፤ የብልጽግና እሳቤዎች አመራሩና አባሉ የጋራ አስተሳስብ እንዲይዝና የህዝቡ ግንዛቤ

እንዲያድግ፡፡

የሚጠበቁ ውጤቶች፤

• የአላማና የተግባር አንድነት ያለው የፓርቲ አመራርና አባል፣

• የፓርቲው እሳቤዎች የበላይነት ማግኘት

የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት

• የብልጽግና ፓርቲ ንድፈ ሃሳብ መጽሔት መጽሔቱን በወቅቱና በጥራት በማዘጋጀት

ማሰራጨት፣

• የፓርቲው እሳቤዎች በኅብረተሰቡ የሚሰርጸባቸውን የተለያዩ ዘዴዎች መለየትና ማደራጀት፣

• ከተለያዩ አካላት መረጃ በመሰብሰብና በመገምገም ለቀጣይ የፖለቲካ ስራ መዘጋጀት፣

• የተለያዩ የፖለቲካ ኮንፈረንሶች/ውይይቶችን/ ማካሄድ፣

• ምሁራንና የፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በተለያዩ ርዕሶች ገለፃ የሚያደርጉበት መድረክ

ማመቻቸት፣

• ሀገራዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ወቅታዊ ፖለቲካዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን መቀመር፣

መተንተን እና ትርጉም በመስጠት ከብልጽግና እሳቤዎች ጋር አጣጥሞ መጠቀም፣

• የተለያዩ የሕዝብ መድረኮችን በመፍጠር ማወያየት፣

• አመራሩና አባሉ በግሉ የመፅሐፍ ክህሎትና የማንበብ ልምድ እንዲያዳብር ማድረግ፣

የሚያስፈልግ ግብዓት፡- በግምት 800 ሚሊዮን ብር

አስተባባሪ፡- ብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት

103
የፕሮግራሙ ባለቤት፤ ፖለቲካና ርዕዮተ ዓለም ዘርፍ

ፈጻሚ አካላት፤ ዘርፉና ቅ/ጽ/ቤቶች

እርምጃ ስድስት፡- የድርጅት ተግባራት ማጠናከርና ማስፋት ፕሮግራም

ወሰን፡- የአባላት ምልመላ፣ ምደባ፣ ስምሪት፣ ስንብትና ግንባታ፣ የመረጃ አያያዝ፣ ሌብነትንና

ብልሹ አሰራርን መታገል፣ ብዝሃ ቋንቋ ተግባራዊ ማድረግ ነው፡፡

ጠቀሜታ፤ ውጤታማ የፓርቲ ተቋም እንዲኖር ያደርጋል፡፡

የሚጠበቀው ውጤቶች፣

• ጠንካራ አደረጃጀት፣

• የአባላት ቁጥር መጨመር፣

• የዘመነ አሰራር፣

• መልካም አስተዳደርና የተገልጋይ እርካታ

የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት

• በየደረጃው ጠንካራ ተቋማዊ አደረጃጀቶች መፍጠርና ማጠናከር፣

• የአባላት ምልመላ፣ ምደባ፣ ስምሪት፣ ስንብትና ግንባታ ተግባራት በአሰራር ብቻ መፈጸም፣


• የአመራርና አባላት ጥራት ለማረጋገጥ በየወቅቱ የማጥራት ስራ መስራት፣

• በቴክኖሎጂ የታገዘ የመረጃና ዶክመንቴሽን አያያዝ ሥርዓት በመዘርጋት ተግባራዊ ማድረግ፣

• የአመራር ፑል ስራችን በየወቅቱ ማዘጋጀትና ለምደባ እንዲጠቀሙ ማድረግ፣

• ሁሉም የፓርቲ አባላት መታወቂያ እንዲኖራቸው ማድረግ፣

• መመሪያዎችን በማዘጋጀት ምክረ ሀሳብ ለሚመለከተው አካል ማቅረብ፣

• በየደረጃው አመራሮችን መልሶ የማደራጀት ስራ በየወቅቱ እንዲከናወኑ ማድረግ፣

• ቤተመጽሐፍት አገልግልሎት ዘመናዊነትን በተላበሰ መልኩ እንዲጀምር ማድረግ፤

• በተደራጀ የሕዝብ ንቅናቄ ሌብነትንና ብልሹ አሰራርን ለማስወገድ መስራት፣

104
• በፓርቲው ህገ-ደንብ የተቀመጠውን ብዝሃ ቋንቋ ተግባራዊ እንዲሆኑ ከሚመለከተው አካላት

ጋር በቀንጅት መስራት፣

• የአመራርና የአባላት ምዘና ወቅቱን ጠብቀው እንዲካሄዱ ማድረግ፣

• የአመራርና የአባላት ሂስና ግለሂስ በወቅቱ እንዲከናወን ማድረግ፣

የሚያስፈልግ ግብዓት፡- አንድ ቢሊዮን ብር

አስተባባሪ፡ ብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

የፕሮግራሙ ባለቤት፡- አደረጃጀት ዘርፍ

ፈጻሚ አካላት፡- አደረጃጀት ዘርፍና ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች

እርምጃ ሰባት፡- የሰው ሀብት፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ፕሮግራም

ወሰን፤ የሰው ሀብት አያያዝን መመሪያ ማሻሻል፣ የማበረታቻ ሥርዓት መዘርጋት፣ የአሠራር

ግልጽነትና የተጠያቂነት ሥርዓት ማስፈን፣ የፓርቲውን ንብረት በአግባቡ መያዝና ጥቅም ላይ

ማዋል፣ ከአባላት የሚሰበሰበው ወርሃዊ መዋጮ በአግባቡ ገቢ መሆኑን መከታተል እና የተመደበ

በጀትን በአግባቡ መጠቀም ነው፡፡

ጠቀሜታ፡- የሰራተኛ የማስፈጸም አቅም ያድጋል፣ አገልገሎት ይሻሻላል፣ የሃብትና ፋይናንስ

አጠቃቅም ብቃትና ውጤታማነት ያድጋል፣

የሚጠበቁ ውጤቶች፤

• ገቢ መጨመር፡፡

• የሰራተኛ የመፈጸም አቅም ማደግ፡፡

• ውጤታማ የንብረትና የበጀት አስተዳደር አጠቃቀም፣

የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፤

105
• የሰው ሀብት አያያዝን መመሪያ ማሻሻል፣

• የጽህፈት ቤት ሰራተኞችን ማስተዳደር፣

• የማበረታቻ ሥርዓት መዘርጋት፣

• የአሠራር ግልጽነትና የተጠያቂነት ሥርዓት ማስፈን፣

• የፓርቲውን ንብረት በአግባቡ መያዝና ጥቅም ላይ ማዋል፣

• ከአባላት እና ከደጋፍ አካላት የሚሰበሰበው ገንዘብ በአግባቡ ገቢ መሆኑን መከታተል፣

• ከቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች የሚሰበሰበውን ገቢ በወቅቱ እንዲያስገቡ ማድረግ፣

• የተመደበ በጀትን በአግባቡ መጠቀም፣

የሚያስፈልግ ግብዓት፡-

አስተባባሪ፡ ብልፅግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

የፕሮግራም ባለቤት፡- አስተዳደር ዘርፍ

ፈጻሚ አካላት፡ አስተዳደር ዘርፍና ቅ/ጽ/ቤቶች

እርምጃ ስምንት፡- የሀገራዊ፣ ክልላዊና አካባቢ ምርጫ ፕሮግራም

ወሰን፡- በሁሉም እርከን ምርጫ ማካሔድ

ጠቀሜታ፡- ዴሞክራሲ ለመገንባት፣ የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ለማጠናከር፣ የሕዝብ ይሁንታና

አመኔታ ያለው መንግሥት ለመመሥረት፣

የሚጠበቁ ውጤቶች፡ በአብላጫ ድምጽ ምርጫን ማሸነፍ፣

የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፤

• በሚካሄደው ሀገራዊና ክልላዊ እንዲሁም የአካባቢ ምርጫዎች ላይ በቂ ዝግጅት ማድረግ፣

• በየደረጃው ምርጫውን የሚያስተባበሩ ኮሚቴዎችን ማዋቀር፣

• የምርጫ ስራዎችን የሚያስፈጽሙ አካላትን ማዘጋጀትና ማሰልጠን፣


106
• ጠንካራ ሰዎችን በዕጩነት የማዘጋጀት ስራ ማከናወን፣

• በዕጩነት ከሚቀርቡ መካከል የሴቶች ቁጥር 50 በመቶ እንዲሆን ከወዲሁ መስራት፣

• የፓርቲ ታዛቢዎችን ማዘጋጀት፣

• ብቃት ያለው የምርጫ ቅስቀሳ ማካሄድና ዕጩዎችን የማስተዋወቅ ስራ መስራት፣

• በየምርጫ ክልል ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ኮሚቴ ማዋቀር

• ለምርጫ ስኬታማነት የገቢ አሰባሰብ ስራ ማከናወን፣

• ለምርጫ ክርክር በቂ ዝግጅት በማድረግ ክርክሩን በብቃት መወጣት፣

• ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ ከሚመለከተው ክፍል ጋር መስራት፣

• ለ2023 ለሚካሄደው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ፣

የሚያስፈልግ ግብዓት፡- በግምት 800 ሚሊዮን ብር

አስተባባሪ፡- ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

የፕሮግራሙ ባለቤት፡- ምርጫ ዘርፍ

ፈጻሚ አካላት፡- ዘርፎችና ቅ/ጽ/ቤቶች

እርምጃ ዘጠኝ፡- ከተፎካካሪ ፓርቲዎችና ከዴሞክራሲ ተቋማት ጋር አብሮ የመስራት


ፕሮግራም፣

ወሰን፡- በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ አብሮ መስራት፣ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የመንግስት ስራን በጋራ

መምራት የሚያስችል አሰራር መፍጠር ነው፡፡

ጠቀሜታ፤ የጋራ ትብብርና አብሮ መሥራት ይኖራል፣ ዴሞክራሲ ይጠናከራል፣

የሚጠበቁ ውጤቶች፤

• የመድብለ ፓርቲ የዴሞክራሲ ሥርዓት መጠንከር፡፡

107
• አብሮ የመስራት ባህል፣

• መቻቻልና የመደማመጥ ባህል፣

የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት

• በሀገራዊ ዋና ዋና ጉዳዮች ጋር ከተፎካካሪ ፓርቲዎችና ከሌሎች አካላት ጋር አብሮ መስራት፣

• አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የመንግስት ስራን ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በጋራ መምራት፣

• ለብሔራዊ መግባባትና ለዕርቀ ሰላም ሥራ መሳካት ከዴሞክራሲ ተቋማትና ከተፎካካሪ

ፓርቲዎች ጋር በጋራ መሥራት፣

• የተፎካካሪ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ለማጠናከር በጋራ መስራት፤

• ከተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከሲቪክ ማህበራትና የዴሞክራሲ ተቋማት ጋር ግልፅና

ተከታታይ የግንኙነት ስርዓት መዘርጋት፣

የሚያስፈልግ ግብዓት፡ 5 ሚሊዮን

አስተባባሪ፡- ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

የፕሮጀክቱ ባለቤት፡- የሲቪክ እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ዘርፍ

ፈጻሚ አካላት፡- የሲቪክ እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ዘርፍና ቅ/ጽ/ቤቶች

እርምጃ አስር፡- የፓርቲ ጉባኤ የማካሄድ ፕሮጀክት

ወሰን፤ ለጉባኤ በቂ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ማካሄድ ነው፡፡

ጠቀሜታ፤ የፓርቲውን ህጋዊነት ለማረጋገጥ፣ ከጉባኤ አስከ ጉባኤ ያለውን ሥራ አፈጻጸም

ለመገምገም፣ አዳዲስ ውሳኔዎች ለመወሰንና የተሻለ አመራር ወደፊት ለማምጣት፣

የሚጠበቅ ውጤት፡- ያደገ የሥራ አፈጻጸም፣ ግልጽ የሆነ አቅጣጫና ብቃት ያለው አመራር

የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት
108
• ለጉባኤ ብቃት ያለው ቅድመ ዝግጅት ማድረግ፣

• የጉባኤ ዕቅድ ማዘጋጀት እና የጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ አባላት ማዋቀር፣

• የጉባኤ ሪፖርት እና የተለያዩ መልዕክቶች ማዘጋጀትና ማሳተም እንዲሁም ማሰራጨት፣

• የጉባኤ ተሳታፊዎች በኮንፈረንስ ማስመረጥ፣

• የጉባኤ ዝግጅት በሚዲያ ማስተዋወቅ፣

• ጉባኤ የሚካሄድበት ቦታ መወሰን፣

• ጉባኤውን ማካሄድ እና ፓርቲውን የሚመሩ አመራሮችን ማስመረጥ፣

• የጉባኤ ሂደት ሙሉ ዶክመንት በመያዝ ለምርጫ ቦርድ ጭምር የሚፈለግ ሰነድ በወቅቱ

መላክ፣

የሚያስፈልግ በጀት፡- በግምት 270 ሚሊዮን ብር

አስተባባሪ፡- ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

የፕሮጀክቱ ባለቤት፡ ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

ፈጻሚ አካላት፡- ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤትና ቅ/ጽ/ቤቶች

እርምጃ አስራ አንድ፣ የሴቶችና ወጣት ሊጎች አደረጃጀቶችን ማጠናከር ፕሮግራም

ወሰን፤ የሴቶችና የወጣቶችን አደረጃጀት ማጠናከር፣ ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ማጎልበት ፣

ጠቀሜታ፤ የሴቶችና የወጣቶች አደረጃጀት ማስፋትና ማጠናከር፣ ተጠቃሚነትንና


ተሳታፊነትን ማረጋገጥ ነው፡፡

የሚጠበቅ ውጤት፡-

• ተሳትፎና ተጠቃሚነት መጨመር፤


• ስራ አጥነት መቀነስ፣
• ጠንካራ አደረጃጀትና ውጤታማ አሰራር፣

109
የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት

• የፖለቲካ ተሳትፎ ሊያሳድጉ የሚችሉ ውይይቶች መደበኛ በሆኑት የመዋቅሩ መወያያ መንገዶች

እና በተለያዬ ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ መፍጠር መቻል፣

• የአመራር አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ የአቅም መገንቢያ ስልጠናዎች መስጠት፣

• አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ መፍጠር ሂደት ውስጥ ሊጎች የበኩላቸውን እንዲወጡ

የሚያስችሉ የተለያዩ ተግባራት ማከናወን፣

• በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሃገራት የሚገኙ ምሁራን ሊጎች በሀገራቸው ጉዳይ ተቀራርበው እንዲሰሩ

የሚያስችሉ ምቹ መፍጠርና መምራት፣

• በተሰማሩበት የሰራ መስክ ግንባር ቀደም እና አርአያ የሆኑ በአባልነት መመልመል፣

• በየደረጃው የሚገኝን የሊጎች አደረጃጀት በየግዜው ለተልዕኮ ብቁ መሆን በሚቻልበት ደረጃ እየፈተሹ

ማደራጀትና ማጠናከር፡፡

• የሊጉ ሁሉም ተግባራት በሊጉ ህግ ደንብ፣ አሰራርና ውሳኔዎች መሰረት የሚፈፀም እንዲሆን ማስቻል

• ሊጉ የሚተዳደርበትን የተለያዩ መመርያዎች ከእናት ፓርቲው ትዩዩና በማይቃረን አግባብ በማዘጋጀት

በሚያፀድቀው የሊጎች መዋቅር እንዲፀድቅ ያደርጋል፡፡

• የሊጎች አባላት፣ አመራሮች አደረጃጀት የመረጃ ስርዓት ዘመናዊ እንዲሆንና የሊጎች ሰነዶች አመቺ

በሆነ መልኩ ማደራጀት፣

• ሊጎች ሀገር ውስጥ ከተደራጁ ማህበራት ጋር የአቻነት እና የመተባበር ግንኙነት መፍጠር፣


• የሊጎች ወቅታዊ አፈጻጸሞችን እና የእናት ፓርቲውን እሳቤዎች ታሳቢ በማድረግ በተለያየ መልኩ ለአባላቱና

ለማህበረሰባችን ማስረፅ፣

• ከሌሎች ሀገር ሊጎች ጋር በሀገሪቱ የውጭ ፖሊስና የፓርቲውን የውጭ ግንኙነት መርህ ላይ

በመመርኮዝ ግንኙነት በማድረግ ወንድማማችነትና እህትማማችነትን የማጠናከር፣የመደጋገፍና ልምድ


የመለዋወጥ ተግባራትን ማከናወን፡፡

• ወጣቶች የበጎ ፍቃድ አገልግሎት አሰጣጥ ባህላቸው በበለጠ ደረጃ እንዲጎለብት በማድረግ

የተለያዩ የማህበረሰብ ችግሮችን በመለየት ጉልበታትና እውቀታቸውን በነፃ በማበርከት

የህብረተሰቡን ችግር እንዲፈቱ ማስቻል፣

የሚያስፈልግ በጀት፡- በግምት 50 ሚሊዮን ብር

አስተባባሪ፡- ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት


110
የፕሮጀክቱ ባለቤት፡ የሴቶችና የወጣቶች ሊግ

ፈጻሚ አካላት፡- የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት ሊጎችና ቅ/ጽ/ቤቶች

እርምጃ አስራ ሁለት፣ የኢንስፔክሽንና ስነ-መግባር ኮሚሽን ተግባራትን ማጠናከር


ፕሮግራም

ወሰን፤የፓርቲውን የፖለቲካ ጥራት እና የስነ -ምግባር ጤንነት፣ ገንዘብ፣ንብረትና ሰነዶች ፣

የአባላት መዋጮ መሰብሰቡን፣ የአባላትና አካላት መብቶችና ጥቅሞች መከበራቸው፣ የስነ ምግባር

ጥሰቶችን እና የሚቀርቡ አቤቱታዎችን በመቀበል መረመርን ያጠቃልላል፣

ጠቀሜታ፤ አሠራርን የተከተለ አፈጻጸም፣ በስነ-ምግባር የዳበረ አመራርና የአባላት፣

የሚጠበቅ ውጤት፡-

• የፖለቲካ ጥራት እና የስነ ምግባር ጤንነት መረጋገጥ፣

• የገንዘብ፣ንብረትና ሰነዶች አያያዝ ስርኣት መሻሻል፣

• የአባላትና አካላት መብቶችና ጥቅሞች መከበር፣

• የስነ ምግባር ጥሰቶችን መስተካከል፣

• የሚቀርቡ አቤቱታዎች የመፍታት አቅሞች መጨመር፣አቤቱታ መቀነስ፣

የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት

• የፓርቲውን የፖለቲካ ጥራት እና የስነ ምግባር ጤንነት ለማረጋገጥ ክትትል ማድረግ፣


• የፓርቲው ገንዘብ፣ንብረትና ሰነዶች በአግባቡ መጠበቃቸውን ክትትል ማድረግ፣
• የአባላት መዋጮ በወቅቱና በትክክል መሰብሰቡን መቆጣጠር፣
• የፓርቲ አባላትና አካላት መብቶችና ጥቅሞች መከበራቸውን መከታተል፣
• በየደረጃው የስነ ምግባር ጥሰቶችን ይመረምራል፣ተገቢውን የእርምት እርምጃ
እንዲወሰድ ማድረግ፣
• ከአባላት የሚቀርቡ አቤቱታዎችን በመቀበል ይመረምራል፣መፍትሄ እንዲገኙ
ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ይሰራል፣
111
የሚያስፈልግ ግብዓት/በጀት/፡- በግምት 15 ሚሊዮን ብር

አስተባባሪ፡- ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

የፕሮጀክቱ ባለቤት፡ ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን

ፈጻሚ አካላት፡- የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽንና ቅ/ጽ/ቤቶች

እርምጃ አስራ ሦስት፣ የክትትል፣ የድጋፍና ግብርመልስ ትግበራ ፕሮጀክት፣

ወሰን፤ ጠንካራ የሪፖርት፣የግምገማና የክትትል፣ ድጋፍ ግብረመልሶች፡፡

ጠቀሜታ፤ መደጋገፍ፣ ተጠያቂነትን በማስፈንና አፈጻጸምን በማሻሻል ያደገ ውጤት


ማስመዝገብ ነው፡፡

የሚጠበቅ ውጤት፡-

• የጨመረ የመፈጸም አቅም፣


• የዳበረ መረዳዳትና መደጋገፍ ሁኔታ ፣
• ወቅታዊ የተገመገመ ሪፖርት፣

የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት

• የክትትልና ድጋፍ ሥርዓቱ የሚመራበትን አሰራር መዘርጋት፣

• የክትትልና ድጋፍ አካላትን ማደራጀት፣

• የክትትልና ድጋፍ ዕቅድና ቼክ ሊስት መዘጋጀት፣

• ክትትልና ድጋፍ የሚካሄድበት አካባቢዎች መለየትና ስምሪት መስጠት፣

• የሱፐርቪዥንና ኢንስፔክሽን ስራ በሚመለከት አካላት ከተገመገመ በኋላ ግብረመልስ

መስጠት ፣

የሚያስፈልግ ግብዓት/በጀት/፡- በግምት 10 ሚሊዮን ብር

112
አስተባባሪ፡- ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

የፕሮጀክቱ ባለቤት፡ ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

ፈጻሚ አካላት፡- የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት እና ዘርፎች ቅ/ጽ/ቤቶች

እርምጃ አስራ አራት፣ መልካም አስተዳደርን በማስፈን የተገልጋይ እርካታን ማረጋገጥ


ፕሮጀክት

ወሰን፤በሁሉም አካባቢ የህብረተሰቡ የቅሬታ ምንጭ የሆኑትን በመለየት ከሚመለከተው


አካል ጋር በመነጋገር መፍታት ነው፣

ጠቀሜታ፤ የህዝቡን ፍላጎት ማርካት፣ የብልፅግና ፓርቲ ገፅታና ተቀባይነት ማሳደግ፣

የሚጠበቅ ውጤት፡-

• የሕዝቡና የፓርቲ መቀራረብ መጨመር፣


• እርካታ መረጋገጥ፣
• ቅሬታ መቀነስ፣

የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት

• በፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የህዝቡን ቅሬታ የሚሰማ እና ከሚመለከታቸው አካላት


ጋር በመነጋገር የሚፈታ አካል መመደብ፣
• ከተለያየ አከባቢ የሚመጣ ቅሬታ መለየትና ማደራጀት፣
• በህግ የሚታዩ ወደ ፍርድ ቤት እንዲሄዱ በግልጽ ለባለጉዮች መንገር እና አስተዳደራዊ
የሆኑ ጉዳዮች ከቅርንጫ ጽ/ቤቶች ጋር በመነጋገር መፍትሄ እንዲያገኙ ማድረግ፣
• በልማትና መልካም አስተዳደር ዙሪያ ከፌዴራል ተቋማትና ከፓርቲ ቅርንጫፍ
ጽ/ቤቶች ጋር በመሆን በተመረጡ አከባቢዎች መድረኮችን ፈጥሮ ማወያየት፣
• የስነ-ምግባር ችግር ያለባቸውን የአመራር አካላት ህዝቡ እንዲያጋልጥ ማድረግ፣

113
• ከውይይቱ የተገኘውን በመገምገምና በማደራጀት ከሚመለከተው አካል ጋር
በመነጋገር በአጭር፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ የሚፈቱትን በመለየት መልሶ ከህዝቡ
ጋር መግባባት መፍጠር፣
• ሕዝቡ ጥቆማ የሚሰጥበትን ስልክ ማዘጋጀትና ማስተዋወቅ፣

የሚያስፈልግ በጀት፡- በግምት 10 ሚሊዮን ብር

አስተባባሪ፡- ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

የፕሮጀክቱ ባለቤት፡ ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

ፈጻሚ አካላት፡- የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት እና ቅ/ጽ/ቤቶች

እርምጃ አስራ አምስት፣ የማኅበራዊ ትሥሥር ፕሮጀክት

ወሰን፤በአመራሩ፣ በአመራሩና በሰራተኛው እና በተቋማት መካከል መልካም ግንኙነት መፍጠር

የፓርቲውን ተልዕኮ መሳካት፣

ጠቀሜታ፤ የጠንካራ ግንኙነት ወንድማማችነት/እህትማማችነት መፍጠር

የሚጠበቅ ውጤት፡-

• ጠንካራ ግንኙነት አሠራር መዘርጋት፣


• የሰራተኛው የመፈጸም አቅም መጨመሩ
• ያደገ እርስ በርስ የመማማር
• የጨመረ የስራ ባህል

የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት

• የጽህፈት ቤት አመራሮችና የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች አመራሮች መካከል ያለውን


ግንኙነት ማጠናከር፣
• በጽ/ቤቱ አመራሮችና ሠራተኞች መካከል ማኅበራዊ ትሥሥርን ማጠናከር፣
• የጋራ ዕሴቶች እና የሥራ ባህል የሚያጠናክር ማኅበራዊ ትሥሥር መፍጠር፣

114
• አዎንታዊ ማኅበራዊ ትሥሥሮች በመፍጠር ለፓርቲው ተልዕኮ እና ርዕይ ስኬት የጎላ
አስተዋፅኦ ማበርከት፣
• የታማኝነት፣ የሕግ ተገዥነት፣ የሙያዊ ሥነምግባር….ልምዶችን ማክበር፣
• በሰራተኛው መካከል የዕውቀት ሽግግር ባህልን ማጎልበት፣
• በሰራተኛው መካከል የመታመን፣ የማመንና በራስ የመተማመን አቅምን ማጎልበት፣
• በፓርቲው ዕሴቶች በመመራት ለጋራ ዓላማ መቆም፣
• በሰራተኛ መካከል ጠንካራ የውሰጠ ፓርቲ ትግል በማጠናክር መተማመንን መፍጠር፣

የሚያስፈልግ በጀት፡-

አስተባባሪ፡- ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

የፕሮጀክቱ ባለቤት፡ ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

ፈጻሚ አካላት፡- የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት እና ቅርናጫፎች

እርምጃ አስራ ስድስት፡ የወዳጅ ፓርቲዎች ግንኙነት የማጠናከር ፕሮግራም፣

ወሰን፡ ከወዳጅ ሀገራት ፓርቲዎች ተቋማት ጋር ጠንካራ ትስስር ማጠናክር እና አዳዲስ ወዳጅ

ፓርቲን መፍጠር፣

ጠቀሜታው፡ ጠንካራ ግንኙነት መፍጠር፣

የሚጠበቅ ውጤት፡

• ያደገ የልምድና የተሞክሮ ልውውጥ


• ጠንካራ የግንኙነት አሠራር መዘርጋት፣
• የመፈጸም አቅም መጨመሩ
• ያደገ የፓርቲ ተቀባይነት
• የበዛ ወዳጅ ፓርቲ

የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት
115
• አሰራር ስርዓት በመፈጠር ግንኙነቱ ህጋዊ እንዲሆን መስራት
• ከአዳዲስ ወዳጅ ሀገራት ፓርቲዎች ጋር ወዳጅነት መፍጠር
• የተለያዩ ወርክ ሾፕ በማዘጋጀት የፓርቲን እሳቤዎች ላይ ግንዛቤ መፍጠር

የሚያስፈልግ በጀት፤50 ሚሊዮን

አስተባባሪ ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

ፕሮጀክት ባለቤት፡ሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ

ፈጻሚ አካላት፡ሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ

እርምጃ አስራ ሰባት፡የፓርቲ የስልጠና ማዕከል መቋቋም ፕሮጀክት

ወሰን፡ የአመራር የመፈጸም አቅም በመገንባት የፓርቲውን ተልዕኮ ማሳካት

ጠቀሜታው፡ተልዕኮውን በውጤታማነት መፈጸም

የሚጠበቅ ውጤት፡

• የጨመረ የአመራር የመፈጸም አቅም


• የአመራር ውጤታማነት
• የጠራ አመለካከት

የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት

• በአስፈላጊነቱ ላይ የተለያዩ አካላትን ማወያየት


• ማሰልጠኛ ማዕከላትን መገንባት/ማዘጋጀት/
• ለስልጠና በቂ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ
• የሚያስፈለገውን የሰው ሃይል ጥናት ማድረግ
• ስልጠናው የሚመራበትን አሰራር መዘርጋት

የሚያስፈልገው በጀት፡ 3 ቢሊዮን ብር

116
አስተባባሪ፤ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

የፕሮጀክቱ ባለቤት፤ ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

ፈጻሚ አካላት፡ ፓርቲ ዋና ጽ/ቤትና ቅርንጫፎች እንዲሁም ዘርፎች

እርምጃ አስራ ስምንት፡- የፓርቲው የውስጥ ምርጫ ፕሮጀክት

ወሰን፡- በሁሉም እርከን ምርጫ ማካሔድ

ጠቀሜታ፡- ዴሞክራሲ ለመገንባት፣ የፓርቲ ፓርቲ አመራር ሥርዓት በየደረጃው ለማጠናከር፣

በመላ አባላት ዘንድ ይሁንታና አመኔታ ያለው መሪ ለማፍራት፣

የሚጠበቁ ውጤቶች፡ በፓርቲው ውስጥ ዲሞክራሲያዊ የምርጫን ሥርዓት መትከል፣

የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፤

• በየደረጃው በሚካሄዱ ምርጫዎች ላይ በቂ ዝግጅት ማድረግ(የሕግ ማቀፍ ማዘጋጀት፣

እቅድ ማውጣት፣ በሕግ ማዕቀፉና ዕቅዱ ላይ መግባባት)፣

• በየደረጃው መሪ መሆን ለሚገባቸው ለሚገባቸው ዝርዝር መስፈርት ማዘጋጀት

• በየደረጃው ምርጫውን የሚያስተባበሩ ኮሚቴዎችን ማዋቀር፣

• ጠንካራ ሰዎችን በዕጩነት የማዘጋጀት ስራ ማከናወን፣

• በዕጩነት ከሚቀርቡ መካከል የሴቶች ቁጥር 50 በመቶ እንዲሆን ከወዲሁ መስራት፣

የሚያስፈልግ ግብዓት፡- በግምት 600 ሺህ ብር ብር

አስተባባሪ፡- ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

የፕሮጀክቱ ባለቤት፡- በየደረጃው ያለ አደረጃጀት ዘርፍ

ፈጻሚ አካላት፡- ብልጽግና ዋና ጽ/ቤትና ቅ/ጽ/ቤቶች

117
እርምጃ አስራ ዘጠኝ፡- ፓርቲውን ብራንዲንግ የማድረግ ፕሮጀክት

ወሰን፡- በሁሉም የፓርቲ መዋቅርና አሰራር

ጠቀሜታ፡- ፓርቲው ወጥ፣ በቀላሉ የሚለይና የሚታወስ ገፅታ እንዲኖረው ማድረግ፤

የሚጠበቁ ውጤቶች፡ ፓርቲው የሚገለፅባቸው ወጥ የሆኑ የቀለም፣ የቅርፅና፣ የንድፍ አቀራረቦች

ይኖሩታል

የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፤

• የፓርቲውን ብራንዲንግ የሚሰራ አካል ማቋቋም፣

• የፓርቲው መገለጫ የሆኑ ቀለሞችን፣ ቅርፅና ንድፎችን መምረጥና ማስተዋወቅ፤

• የፓርቲው ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረቶች፣ ሰነዶች፣ ገለፃዎች በሙሉ የፓርቲውን ብራንዲንግ

የሚጠቀሙበትን መመሪያ ማውጣት፣

የሚያስፈልግ ግብዓት፡- በግምት 50 ሚሊየን ብር

አስተባባሪ፡- ብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት

የፕሮጀክቱ ባለቤት፡- ሕዝብና ውጪ ግንኙነት ዘርፍ

ፈጻሚ አካላት፡- ብልጽግና ዋና ጽ/ቤትና ቅ/ጽ/ቤቶች

118
ምዕራፍ ስምንት፡ ስትራቴጂን ወደፈጻሚ ማውረድ (cascading)

ስትራቴጂን በየደረጃው ላሉ አካላት ማውረድ ሲባል የተቋሙን ስትራቴጂ ሁሉም ፈጻሚ አካላት ተገንዝበውት

የእለት ተእለት ስራቸው እንዲያደርጉት ማስቻል ነው፡፡ በየደረጃው የሚገኙ አካላት ለስትራቴጂው ስኬታማነት

የበኩላቸውን ድርሻ ማበርከት ይችሉ ዘንድ በስትራቴጂው ላይ ሙሉ ግንዛቤ መፍጠርን፣ ሲወስዱትም

ስትራቴጂያዊ ትስስሩን መጠበቃቸውንና ለስኬታማነቱም ከፍተኛ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ መሆናቸውን ማረጋገጥን

ያጠቃልላል፡፡

ስትራቴጂ በየደረጃው ላሉ አካላት የሚወርደው በስትራቴጂያዊ ግቦች አማካይነት ነው፡፡ ስትራቴጂን

የሚያወርደው አካል የተቋሙን ስትራቴጂያዊ ግቦች መሰረት በማድረግ ለሚያዘጋጃቸው ግቦች መለኪያዎችን፣

ዒላማዎችንና እንዳስፈላጊነቱ ስትራቴጂያዊ እርምጃዎችን ማዘጋጀት ይጠበቅበታል፡፡

ስትራቴጂው ለፈጻሚ አካላት ሲወርድ በዋናነት የሚከተሉት ጥቅሞች እንደሚረጋገጡ ይጠበቃል፡፡

• በየደረጃው የሚገኙ ፈጻሚዎች የተቋሙን ራዕይ የጋራ በማድረግ ስትራቴጂውን የዕለት

ተዕለት ተግባራቸው እንዲያደርጉት፣

• እያንዳንዱ ፈፃሚ አካል ስትራቴጂ ተኮር የሆነ የስራ ባህል ለመገንባትና የመጨረሻውን

ተቋማዊ ውጤት እያሰበ እንዲሰራ ለማድረግ፤

• ማበረታቻ ሽልማት ከስትራቴጂያዊ ውጤት ከመያያዙ ጋር በተገናኘ ሠራተኞች “ውጤት

ባመጣ ምን አገኛለሁ?” /What is in it for me?/ በማለት ለሚያነሱት ጥያቄ

ምላሽ እንዲያገኙ እንዲሁም

• የተቋሙ ስትራቴጂ እንዲመነዘርና በየደረጃው ካሉ ግቦችና መለኪያዎች ጋር እንዲተሳሰር

ያስችላል፡፡

ስትራቴጂን ወደ ፈጻሚ አካላት ለማውረድ ስትራቴጂውን ማስረጽ (Spiritual Cascading)፣

ግቦችን ለፈጻሚ አካላት ማውረድ (Physical Cascading) እና ውጤትን ከሽልማት ጋር

ማያያዝ /Reward/ መጠቀም እንደሚገባ ይመከራል፡፡

119
የተቋም ስትራቴጂያዊ ግቦች ወደ ደጋፊ ስራ ሂደት/ቡድን ሲወርዱ የትኛው ዕይታ ላይ መቀመጥ እንዳለባቸው

መወሰን ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ በተቋም ደረጃ የሰው ኃብት ልማትን የሚመለከቱ ግቦች ለሰው ሀብት አስተዳደር

ዘርፍ ወይም ቢሮዎች እንዲወርዱ ይደረጋል፡፡ ከቢሮ በታች ያሉ የሥራ ክፍሎች ልክ እንደ እንደዘርፎች/ቢሮዎች

ከተቋሙ ስትራቴጂያዊ ግቦች በቀጥታ ማውረድ የሚችሉበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል፡፡

የዚህን ስትራቴጂያዊ እቅድ፣ ዓላማና ግቦች መነሻ በማድረግ ቅ/ጽ/ ቤቶች እና ዘርፎች የየራሳቸውን

እቅድ ያዘጋጃሉ፡፡ በዕቅዱ የተለዩት ስትራቴጂያዊ ጉዳዮችና እነሱን ወደፍፃሜ ለማድረስ የተለዩ

ዓላማዎች በዓላማ ፈጻሚ ሴክተሮ/ዘርፎች በዝርዝር የሚታቀዱ ይሆናል። በየዘርፉ መተግበር

የሚገባቸው ፕሮግራሞችና ፕሮጀክቶች በስትራቴጂያዊ ዕቅዱ የተመላከቱ በመሆኑ ለፈጻሚው አካል

አቅጣጫ ሊጠቁሙ ይችላሉ። ስትራቴጂያዊ ዕቅዱን በሚፈለገው ደረጃ ለማውረድ በመጀመሪያ

ደረጃ ዕቅዱ በማኔጅሜንት ማጸደቅና ለቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ኮር አመራሮች ሥልጠና ይሠጣል፡፡

በመሰረተ ሃሳቡ ላይ መግባባት ከተያዘ በኋላ ከማዕከል ሰው በመመደብ ሁሉም ስትራቴጂያዊ

ዕቅድ እንዲያዘጋጁና ዓመታዊ ዕቅዶችም ከዚህ እየተቀዱ እንዲዘጋጁ ይደረጋል፡፡

120
ምዕራፍ ዘጠኝ፡- የክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ ሥርዓት እና ታሳቢዎች

9.1. የክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ ሥርዓት

በዕቅድ ዘመኑ መጨረሻ ሊደረስባቸው የታቀዱ ግቦችን ለማሳካት የሚያስችሉ ዋና ዋና

ስትራቴጂዎችና ተግባራት ተመላክተዋል። ግቦችን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ክትትል፣ ድጋፍና

ግምገማ የማይተካ ሚና አለው፡፡ ዓላማውም ለዕቅዱ መሳካት ሥራ ላይ የሚውሉ ግብዓቶች፣

የሚጠበቁ ውጤቶችና የሚፈጠሩ ተፅዕኖዎች በብቃት እንዲመሩ ማድረግ ሲሆንስልቱም ቅንጅት

ያለው እንዲሆን፣ የተሟላ ግንዛቤና አመለካከት ተፈጥሮ አሠራሩ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘና

ስኬት ተኮር እንዲሆን ይደረጋል፡፡ የክትትልና ድጋፍ ሥርዓቱ ዋና ዋና ተግባራት ሪፖርት ማዘገዘጀትና

መገምገም፣ ተግባራት ያሉበትን ደረጃ በሱፐርቪዥንና ኢንስፔክሽን ማረጋገጥ እና ግብረመልስ

መስጠት ናቸው፡፡

ከላይ ለመጥቀስ እንደተሞከረው የክትትልና ቁጥጥር ተግባሩ በየጊዜውና በተከታታይ የሚደረግ

ሲሆን የግምገማ ሥርዓቱ በተቀመጡት ቁልፍ አመልካቾች መሰረት በየጉባኤው የሚደረግ ይሆናል፡

፡ ክትትልና ግምገማዎች በዕቅዱ የተቀመጡ መሠረታዊ የትኩረት አቅጣጫዎች፣ ዋና ዋና ግቦች

እና የማስፈፀም ኢላማዎች ምን ያህል እየተሳኩ እንደሆነ በዝርዝር ለመፈተሽና ለማረጋገጥ፣ አስፈላጊ

ማስተካከያዎች ካሉም በአስተማማኝ መረጃዎች ላይ የተመሠረቱ የእርምት እርምጃዎችን ለመውሰድ

እንዲሁም በቀሪው የዕቅድ ዘመን የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ እንዲረዳ ነው፡፡ በዕቅድ ዘመኑ

መጨረሻ የሚደረገው ግምገማ ውጤት ተኮር ሆኖ የሚደረስበት ድምዳሜ ለቀጣዩ ስትራቴጂዊ

ዕቅድ መነሻ እንዲሆን ተደርጎ ይሰነዳል፡፡

ግምገማዎች በጥናት ላይ የተመሰረቱ ሆነው አጥኝ አካሉ በየጽ/ቤቱ በተደራጁ የጥናትና ምርምር

ዘርፎች፣ ሱፐርቪዥን ተቋማት ወይም አመራረሩ በሚያደራጀው አካል በጋራ ወይም በተናጠል

121
ሊደረግ ይችላል፡፡ ውጤቱ ግን በተቀናጀ ሁኔታ ውሳኔ በሚሰጠው አካል በዝርዝር ተገምግሞ

የማስተካከያ ዕርምጃ የሚወሰድበት ይሆናል፡፡

9.2. የዕቅዱ ታሳቢዎች

የዕቅዱ ታሳቢዎች ሲባል ስትራቴጂያዊ እርምጃዎችን የሚወስኑ ቁልፍ ጉዳዮች ናቸው፡፡ እነዚህ

ሁኔታዎች ካልተሟሉ ወይም ካልተሳኩ እቅዱን በመሰረታዊነት ሊያደናቅፉ ወይም ሊያስቆሙት

ይችላሉ፡፡ ስለሆነም ይህ የአስር ዓመት ስትራቴጂያዊ እቅድ በሚከተሉት ጉዳዮች ይወሰናል ማለት

ነው፡፡

1. በፓርቲዉ ራዕይ፣ ዓላማና ግቦች ላይ የጋራ አስተሳሰብ የፈጠረ ብቃት ያለዉ አመራርና

አባል በየደረጃዉ ሲፈጠር፣

2. የግልፀኝነትና ተጠያቂነትን ሥርዓትን ታሳቢ ያደረገ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ብቃት ያለዉ

ቀልጣፋ አደረጃጀትና አሠራር ሲፈጠር፣

3. ህገ መንግሥቱን ጨምሮ በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ሲፈጠር፣

4. ዘላቂ ሰላም፣ መረጋጋትና የህግ የበላይነት ሲሰፍን፣

5. የተረጋጋ ማክሮ ኢኮኖሚ ሲኖርና የኑሮ ዉድነት ሲረግብ፣

6. የተፈጥሮ አደጋን ወይም ያልተጠበቀ ክስተትን መቋቋም ሲቻል፣

7. የዉስጥ ተጋላጭነትና የዉጪ ጣልቃ ገብነትን መቋቋም ሲቻል፣

8. በሃያላን ሀገራት መካከል የሚፈጠር ግጭት የሚያመጣዉን አሉታዊ ጫና መቋቋም ሲቻል፣

122
ዋቢዎች

123

You might also like