Professional Documents
Culture Documents
የሐይቅ መ_ዕድር የመቃወሚያ መልስ
የሐይቅ መ_ዕድር የመቃወሚያ መልስ
ቀን ፦ 27/062016.ዓ.ም
ሀዋሳ
የአፈፃፀም ተከሳሽ ለቀረበበት የአፈፃፀም ክስ በቀን 21/06/2016.ዓ.ም ፅፎ ላቀረበው መቃወሚያ ከአፈ/ከሳሽ የተሰጠ
መልስ"፦
1. ከአፈ/ከሳሽ የቀረበውን የአፈፃፀም ክስ " የአፈ/ተከሳሽን እንደማይመለከት ፣ የማህበራዊ ፍርድ ቤቱም ስልጣን
ሳይኖረው የሰጠው ውሳኔ " ነው በማለት የአፈ/ተከሳሽ ይቃወም እንጂ በማህበራዊ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ላይ በግልፅ
እንደተብራራውና በክስ ክርክሩ የቀረቡት የሰገድ ማስአጃዎች እንዳረጋገጡት የአፈ/ከሳሽ እንዲለቀቅለት በጠየቀው ቤት
ላይ ከአከራየኝ የሐይቅ ዳር ክ/ከተማ የቤቶች ልማት ከገባሁት የተከራይነት ሀሰጋዊ ውል መሠረት ከውል የመነጨ መብት
ያለኝ የአሁን የአፈ/ተከሳሽ የማስለቀቅ ክስ ባቀረብኩበት የጥበቃ ቤት ውስጥ የገባው ከስራ ከመሰናበቱ በፊት የመረዳጃ
እድሩ ተቀጣሪ ጥበቃ በመሆኑ በስራ ላይ በነበረ ጊዜ ለማረፊያና ልብስ ለመቀየሪያ ተብሎ የሰጠነው ክፍል ቤት መሆኑ
ክርክር ሊቀርብበት የማይችልና የሚታመን በሆነበት የአፈ/ተከሳሽ የአፈ/ከሳሽን መብትና ጥቅም እንደሌኝ አድርጎ
የፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁጥር 33(2) እና(2)ጠቅሶ ያቀረበው መቃወሚያ ተቀባይነት የሌለውና አስቀድሞ በማህበራዊ ፍ/ቤት
ያልቀረበ መቃወሚያ ውድቅ ሊደረግ የሚገባው ከመሆኑም በላይ ፍርዱን ከመፈፀም የማያድነው ነው ተብሎ ውድቅ
እንዲደረግልኝ፤ የአፈ/ከሳሽ ያቀረበው የሰነድ ማስረጃም የአፈ/ከሳሽ በውል በተከራየነው ቤት ላይ መብት የማይሰጠውና
የክ/ከተማው አስተዳደር ቤት እንዲያፈላልግለት የተሰጠ የትብብር ደብዳቤ በመሆኑ ለዚህ የአፈ/ክስ እንደመከላከያ
ሊቀርብ የማይችል ማስረጃ ነው ተብሎ ውድቅ እኔዲደረግልን።
2. የአፈ/ተከሳሽ የማህበራዊ ፍርድ ቤቱ ስልጣን የለውም ካለ በክስ ክርክሩ ወቅት ይህን መቃወምና በይግባኝ ማሻር እንጂ
አሁን በአፈፃፀም ክስ ጊዜ እንደ ፍርዱ ከመፈፀም ውጭ የማህበራዊ ፍ/ቤቱ ስልጣን አስመልክቶ ተቃውሞ የሚቀርብበት
ፈቃጅ የስነ ስረዓት አካሄድ ባለመኖሩ መቃወሚያው የህግ መሠረት የለውም ተብሎ ውድቅ እንዲደረግልኝ ።
በአጠቃላይ የአፈ/ተከሳሽ የቀረበበትን የአፈፃፀም ክስ እንደ ፍርዱ ላለመፈፀም የሚያቀርበው ያልተገባ መከራከሪያ ስነ
ስረዓታዊ አካሄድን ያልተከተለ በመሆኑ ውድቅ ሆኖ የአፈ/ተከሳሽ ፍርዱን ተገዶ እንዲፈፅምልን ለተከበረው ፍ/ቤት
እናመለክታለን።