Professional Documents
Culture Documents
ለሚ ኩራ ህዋስ ማወያያ ሰነድ.docx
ለሚ ኩራ ህዋስ ማወያያ ሰነድ.docx
ለሚ ኩራ ህዋስ ማወያያ ሰነድ.docx
ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት
ታህሳስ/2016 ዓ.ም
ለሚ ኩራ
1. መግቢያ
እንደሚታወቀው አገራችን የበርካታ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ትውፊቶች ባለቤት ከመሆንዋ ጋር ተያይዞ በአለም
5
አቀፍ ቅርስነት ተመዝግበው አገራችንን በማስተዋወቅ ላይ የሚገኙ ቅርሶቻችን በርካታ ሲሆኑ ከነዚህ
ዉስጥ አንዱ የከተራ/ጥምቀት በአል አንዱ ነዉ፡፡
የከተራ/ጥምቀት በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ሃይማኖታዊ ትውፊቱን ጠብቆ በደማቅ ሥነ-
ስርዓት የሚበር ክብረ በዓል ሲሆን በአለም አቀፍ ደረጃ የተመዘገበ ቅርስ በመሆን ቱሪዝምን በመሳብ
የአገራችን የገጽታ ግንባታ ከፍ የሚያድርግ ከመሆኑ በተጨማሪ ቱሪስቶችን በመሳብ የውጪ ምንዛሪን
እያስገኝ ይገኛል፡፡
የጥምቀት የአደባባይ በዓል በመሆኑ የሀገራችንና የአለም ሕዝብ በቀጥታ የሚከታተለው በዓል ነው፡፡
ስለሆነም በአወንታ የሚመለከቱት ሁሉ በጉጉት የሚጠባበቁትን ያህል የጥፋት ኃይሎች ትውፊቱን
ለመጉዳት እና በገጽታው ላይ ጥላሸት ለመቀባት እንዲሁም የራሳቸውን አጀንዳና ሴራ በዚህ አጋጣሚ
ለማሳካት የሚችሉትን ሁሉ ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማይሉ ይታወቃል፡፡
ይህም በተለያየ አካባቢ (ክልል)የሚንቀሳቀሱ ጽንፈኛ ቡድኖች የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም የበአሉን ኩነት
የማበላሸትና ያልተገቡ መልዕክቶችን የመስተላለፍ ፍላጎት ያለዉ መሆኑን መረጃዎች ያሳዩናል፡፡ ጽንፈኛው
ኃይል ቡድንም ፀጉረ ልውጦችን ወደ ከተማ በማስገባት የተለያዩ ብጥብጦችን እንዲነሱና የተለያዩ
ጥፋቶችን በመፈፀም የሕዝቡን ሰላም በማወክ መንግስት ሕግን ማስከበር አልቻለም የሚል መልዕክት
ለማስተላላፍ እየተዘጋጁ ይገኛል፡
በሌላ በኩል በዚህ ብቻ የሚቆም ሳይሆን ብጥብጡን የብሔርና የሃይማኖት መልክ በማስያዝ በሕዝቦች
መካከል ያለመተማመን እንዲፈጠርና ግጭት እንዲባባስ ለማድረግ ያለውን ኃይል ሁሉ ለመጠቀም ሰፊ
ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡ስለሆነም መላው አመራራችንና አባላችን በዓላቱን እንደምቹ አጋጣሚ
በመጠቀም ጽንፈኛዉንና ጸረ-ሰላም ኃይሉ ተላላኪዎችን የማስረግና የማስማራት እቅድ ማክሸፍ
የሚያስችል ጠንካራ ዝግጅት በማድረግ በአሉን በአብሮነት እና በወንድማማችነት/እህትማማችነት መንፈስ
እንዲከበር አስፈላጊውን ሁሉ ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡
1
በሀገራችን በየዓመቱ ጥር 10 ቀን በከተራ ዕለት ታቦታት ከየአቢያተ ክርስቲያናቱ በዓሉ ወደ ሚከበርበት ቦታ
በምዕመናን ታጅበው እየዘመሩ ይሄዳሉ። እዚያም በየተዘጋጀው ድንኳን እንዲያርፉ ተደርጎ ሌሊቱን እዛው
በተለያዩ ሀይማኖታዊ ስነ ስርዓቶች ያሳልፋሉ።
ጥር 11 ቀን የጥምቀት ዕለት ጎኅ ሲቀድ ምእመናን እዚያው በድንኳኑ ዙሪያ አስቀድሰው ሲጨርሱ በካህናት
መሪነት ሁሉም ወደ ከተራው ያመራና ውሃውም ተባርኮ ሕዝቡ ይረጫል። የክርስትና ስማቸውንም የረሱ ወደ
ካህናቱ ይቀርቡና አዲስ የክርስትና ስም ይቀበላሉ። «ተጠምቀ ሰማያዊ በእደ መሬታዊ፤ ሰማያዊው
በመሬታዊው እጅ ተጠመቀ» የሚለው የዕለቱ ቀለም በሊቃውንቱ አንደበት በያሬዳዊ ዜማ ጎልቶ ይሰማል።
ከዚህ ሥነ ሥርዓት በኋላ በመቋሚያ፣ በከበሮና በጽናፅል በሚታጀብ ኃይማኖታዊ ዝማሬና ወንዱ በሆታ፤
ሴቱ በእልልታ፤ ካህኑ በሃሌታ ታቦተ ሕጉን አጅበው፣ እንደያመጣጣቸው ወደየ ቤተክርሲያናቸው
ይመለሳሉ።ወጣቶች ከመንፈሳዊ ዝማሬው ጎን ለጎን የተለያዩ ባህላዊ ዘፈኖች፣ጭፈራዎችና ትርዒቶች
ጭምር የሚቀርብበት በመሆኑ በዓሉን ሁሉም በጉጉት የሚጠብቀው በዓል ነው፡፡
2
በከተማችን ከ1200 ሄክታር በላይ የቤተ እምነት ቦታ በመስጠት፣በህገወጥ መንገድ የተያዙትን ወደ
ህጋዊነት የመቀየር፣ለጥምቀት ማክበርያ ቦታ ጭምር ካርታ በመስጠትና ምቹ እንዲሆኑ የማድረግ ስራ
ለአብነት በክፍለ ከተማችን በወረዳ 14 በአባዶ ጂ7፣በወረዳ 8 ሰሚት ፔፕሲ ፊት ለፊት፣በወረዳ 13 መሪ
አካባቢ ያሉትን የታቦት ማደርያ ስፍራዎችን ማንሳት ይቻላል፡፡የሀይማኖት አባቶችም ለከተማ አስተዳደሩ
ምስጋናና ዕውቅና መስጠቱ የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው፡፡
3
የጥፋት ሀይሎች መግቢያ በመሆኑ ለጸጉረ ልውጦች የተጋለጠ ስለሚሆን ሰፊ ስራ የሚጠብቅ ይሆናል፡፡
4
6. የአባላት ሚና
በአሉን አሴቱና ሃይማታዊ ስነስርአቱን በጠበቀ አግባብ በሰላም እንዲከበርና ህዝቡ ያለምንም
የጸጥታ ችግር ማጠናቀቅ የሚያስችል ሁኔታ መፍጠር፣
በአሉን በቅድመ በዓል፣ በበዓል ዕለት እና በድህረ በዓል ዕለታት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን
ቀድሞ በመተንበይ በመረጃና በዕውቀት ላይ የተመሰረተ የቅድመ መከላከል ሥራዎችን ለመስራት፣
በዓሉ በዩኔስኮ የማይዳሰሱ ቅርሶች የተመዘገበ በመሆኑ የሀገራችንን መልካም ገጽታ በሚያጎላ
መልኩ ተከብረው በሰላም እንዲጠናቀቁ የሚያስችል ሁኔታ መፍጠር ፡፡
በዓሉን በሰላም ለማክበር በተለይ የሰላም ጉዳይ ባለቤት እንዲሆን ማስጨበጥና ከፀጥታ
መዋቅሩ በተደራጀ መልኩ እንዲሳተፍ ማድረግ፤
በዓላቱ ለየትኛውም የፖለቲካ ኃይሎች እንዳይውልና በኣሉ የሕዝብና የሕዝብ ብቻ እንደሆነ
በመረዳት መንግስት የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነትና ግዴታ እንዳለው ማህበረሰቡ በተደራጀ መልኩ
ከመንግስት ጎን በመሆን የክ/ከተማውን ሰላም መጠበቅ እንዳለበት በቂ ግንዛቤ እንዲያገኝ ማድረግ፤
ከማንኛውም ግጭት ቀስቃሽ ድርጊቶች ተቆጥበው በፍቅርና በጨዋነት መንፈስ እንዲከበር
የማስቻል ስራ መስራት፤
በዓሉ በሰላማዊ መንገድ እንዲከበር የማይፈልጉ ግለሰቦችና ቡድኖች የሚያሰራጩትን
የማደናገርያ ወሬ ተከትሎ ህብረተሰቡ ውዥንብር ውስጥ እንዳይገባ አስፈላጊውን የግንዛቤ ማሰጨበጥ ስራ
መስራት ይጠበቅበታል፡፡
ማጠቃለያ
በክፍለ ከተማችን ከ70ሺ በላይ የብልፅግና አባላት የሚኙ ሲሆን እነዚህ አባላት በልማት፣በፀጥታ፣በበጎ
ፍቃድ፣በተለያዩ የፓርቲና የመንግስት የንቅናቄ ስራዎች ላይ የሚያደርጉት ተሳትፎ እጅግ በጣም ከፍተኛ ነው፡፡በዚህም
ክፍለ ከተማችን በሁሉም ተግባራት ወደ ፊት እንዲወጣ አይነተኛ ሚኛ ተጫውተዋል፡፡በርካታ የጥፋት ድግሶችም
በአባላችን ቆራጥ ተሳትፎና በሰላም ወዳዱ ህዝባችን ተጋልጠዋል፣በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉም ማድረግ
ተችሏል፡፡አሁንም መጪውን የጥምቀት በዓል ከመቼውም ጊዜ በላይ በደመቀ፣ሀይማኖታዊና እሴቱን በጠበቀና
ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲከበር የግንባር ቀደም በመሆን ግዴታችንን መወጣት ከእያንዳንዳችን ይጠበቃል፡፡