Download as doc, pdf, or txt
Download as doc, pdf, or txt
You are on page 1of 57

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት

የአካባቢ፣ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን

የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ መመሪያ

ቁጥር 001/2010

ሚያዚያ 2012 ዓ.ም


ባህር ዳር
ማውጫ ገጽ

1 መግቢያ...............................................................................................................................................3
2 ዓላማዎች.............................................................................................................................................4
3 አጭር ርዕስ...........................................................................................................................................4
4 ትርጉም................................................................................................................................................4
5 የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሂደት ወሰን ልየታ ስለማካሄድ....................................................................................8
6 የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርት አዘገጃጀት................................................................................................11
6.1 የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ የቋንቋ አጠቃቀም.........................................................................................11
6.2 የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት ይዘት..............................................................................................11
6.2.1 ማጠቃለያ........................................................................................................................12

6.2.2 መግቢያ............................................................................................................................12

6.2.3 የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማው ዓላማ.....................................................................................12

6.2.4 የጥናቱ ወሰን.....................................................................................................................13

6.2.5 የጥናቱ ስልት ወይም ዘዴ....................................................................................................13

6.2.6 በጥናቱ ወቅት የተወሰዱ ታሳቢዎችና ያጋጠሙ ክፍተቶች......................................................13

6.2.7 የፖሊሲ፣ የህግና የአስተዳደር ማዕቀፎች...............................................................................14

6.2.8 የፕሮጀክቱ መግለጫ..........................................................................................................14

6.2.9 ፕሮጀክቱ የሚተገበርበት ቦታ መግለጫ................................................................................14

6.2.10 የአካባቢ ተጽዕኖ ትንተና ስለማካሄድ....................................................................................16

6.2.11 የተፅዕኖ ማቅለያ እርምጃዎች.............................................................................................16

6.2.12 የአካባቢ አያያዝ ዕቅድ........................................................................................................17

6.2.13 የአካባቢ ክትትል ዕቅድ........................................................................................................17

6.2.14 በፕሮጀክቱ ተፅዕኖ የሚደርስባቸውንና የሚመለከታቸውን አካላት ስለማወያየት.......................17

6.2.15 ማጠቃለያና ምክረ-ሃሳብ....................................................................................................18

6.2.16 ዋቢ መፃህፍት/ማጣቀሻዎች...............................................................................................19

6.2.17 እዝሎች...........................................................................................................................19

6.2.18 የነባር ፕሮጀክት የአካባቢ አያያዝ ሰነድ ዝግጅት.....................................................................20

7 የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርትን ስለመገምገምና ውሳኔ ስለመስጠት................................................................20


8 የአካባቢ የይሁንታ ፈቃድ ስለመከልከል......................................................................................................23
9 የተሰጠ የአካባቢ ይሁንታ ፈቃድ ስለመሰረዝ................................................................................................23
10 የአካባቢ ይሁንታ ፈቃድ የአገልግሎት ክፍያ ታሪፍ.....................................................................................24
11 የአካባቢ ህግ ማስከበር ግብረ-ሀይል ስለማቋቋም.......................................................................................25
12 የአካባቢ አማካሪነት የሙያ ፈቃድ ስለመስጠት..........................................................................................26
12.1 የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርት የማዘጋጀት ስልጣን............................................................................26
12.2 ለአካባቢ አማካሪነት መሟላት የሚገባቸዉ መስፈርቶችና የሰርተፊኬት አሰጣጥ..............................................26
12.3 የማማከር ፈቃድ ለማውጣትና ለማሳደስ የአገልግሎት ክፍያ.....................................................................29
12.4 የአማካሪዎች ኃላፊነትና ኃላፊነትን ባለመወጣት ስለሚወሰዱ እርምጃዎች.....................................................30
13 ግዴታዎች......................................................................................................................................31
14 ቅጣት............................................................................................................................................32
15 ተፈፃሚነት ስለማይኖራቸው ህጎች.........................................................................................................33
16 መመሪያ ስለማሻሻል..........................................................................................................................34
17 መመሪያዉ የሚጸናበት ጊዜ..................................................................................................................34
18 ዕዝሎች..........................................................................................................................................35
18.1 የአካባቢ አያያዝ ዕቅድ ሰንጠረዥ.......................................................................................................35
18.2 የአካባቢ ክትትል ዕቅድ ሰንጠረዥ.....................................................................................................36
18.3 የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ሪፖርት መገምገሚ ማጠቃለያ ቅፅ....................................................................37
18.3.1 የአካባቢ ተጽእኖ ጥናት ዘገባ መገምገሚያ ዝርዝር መመዘኛ ቅፅ..........................................................38

18.3.2 የተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርቱን ለመገምገም የሚጠቅሙ ማብራሪያዎች.............................................50

18.4 የአካባቢ አያያዝ ሪፖርት ማድረጊያ ቅጽ...............................................................................................51


18.5 የአማካሪ ባለሙያዎችና ድርጅቶች መመዘኛ መስፈርት.............................................................................52
18.6 ለአካባቢ ተፅዕኖ ጥናትና ኦዲት አገልግሎት የአማካሪ ባለሙያዎች መስፈርቶች...............................................55
18.7 ለአካባቢ ተፅዕኖ ጥናትና ኦዲት አገልግሎት የአማካሪ ድርጅቶች መስፈርቶች..................................................56
18.8 ማመልከቻ ቅጾች..........................................................................................................................57
18.8.1 ባለሙያዎች አዲስ የአማካሪነት ፍቃድ ለማዉጣት የሚያመለክቱበት ቅጽ.............................................57

18.8.2 አማካሪ ባለሙያዎች የእድሳት አገልግሎት ለማግኘት የሚያመለክቱበት ቅጽ..........................................59

18.8.3 የጠፋ ምስክር ወረቀት እንዲተካለቸው የአማካሪ ባለሙያዎች ማመልከቻ ቅጽ.......................................61

18.8.4 አማካሪ ድርጅቶች የአማካሪነት ፍቃድ ለማግኘት ማመልከቻ ቅጽ.......................................................61

18.8.5 አማካሪ ድርጅቶች ደረጃቸውን ለማሳደግ ማመለከቻ ቅጽ.................................................................63

18.8.6 አማካሪ ድርጅት የብቃት ማረጋገጫቸውን ለማሳደስ ማመለከቻ ቅጽ...................................................64

18.8.7 አማካሪ ድርጅቶች የጠፋ የምስክር ወረቀት እንዲተካላቸው ማመልከቻ ቅጽ..........................................65

18.9 የፕሮጀክት ባለቤቱ የውል ስምምነት..................................................................................................66

2
1 መግቢያ

ቀጣይነትና ዘለቄታ ያለው ልማት ለማምጣት የአካባቢ ደህንነትን ማረጋገጥ አንዱና ዋነኛው ተግባር ሲሆን ይህንን
ለማረጋገጥ ደግሞ ወደ ትግበራ የሚገቡ የልማትና የአገልግሎት ሰጪ ፕሮጀክቶች ከመተግበራቸው በፊት በአካባቢ
ተፅዕኖ ግምገማ ሂደት እንዲያልፉ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤

በሌላ መልኩ የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት ሳያቀርቡና የይሁንታ ፈቃድ ሳይዙ ወደ ትግበራ የገቡ በርካታ
የልማትና የአገልግሎት ሰጪ ፕሮጀክቶች በመኖራቸው በአካባቢውና በማህበረሰቡ ላይ የሚደርሰውን ተፅዕኖ
የሚያስተካክል ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ በመሆኑ፤

የሚዘጋጀው የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርትም ደረጃዉን የጠበቀ እንዲሆን የማማከር ፍቃድ ባላቸዉ
ባለሙያዎች እንዲዘጋጅ ማድረግና ይህንንም ስርዓት ባለው መንገድ መምራት አስፈላጊ በመሆኑ፤

በአካባቢና በማህበረሰቡ ላይ የሚያደርሱትን የተጽዕኖ ደረጃዎች በመለየት የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት
እንዲያቀርቡ የሚገደዱና የማይገደዱ ፕሮጀክቶችን ምድብ መለየት አስፈላጊ በመሆኑ፤

የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርት ወጥነት ያለውና ውሳኔ ለመስጠት የሚያስችል በቂ መረጃ እንዲይዝ ለማድረግ
ሪፖርቱ የሚያካትታቸውን ይዘቶች ለመወሰንና የቀረበውን ሪፖርት ለመገምገም የሚያስችሉ ወጥነት ያላቸው ዝርዝር
መስፈርቶችን ማዘጋጀት በማስፈለጉ፤

በክልሉ የአካባቢ፣ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 232/2008 ዓ.ም አንቀጽ 6
ንዑስ አንቀጽ 14 እና አንቀጽ 18 ንዑስ አንቀጽ 2 መሰረት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ያወጣውን
የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ አዋጅ ቁጥር 181/2003 ዓ.ም ማስፈፀሚያ መመሪያ ማዘጋጀት በማስፈለጉ ይህ
መመሪያ ተዘጋጅቷል፡፡

2 ዓላማዎች

1) ወደ ትግበራ የሚገቡና እየተተገበሩ ያሉ የልማትና የአገልግሎት ሰጪ ፕሮጀክቶች በአካባቢ ተፅዕኖ


ግምገማ ስርዓት እንዲያልፉ ለማድረግ፣

2) የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት የሚያስፈልጋቸውንና የማያስፈልጋቸውን ፕሮጀክቶች ምድብ ለመለየት፣

3) የአካባቢ አማካሪዎችን የአሰራር ስርዓት ለመወሰን፣

3
3 አጭር ርዕስ

ይህ መመሪያ “የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ መመሪያ ቁጥር 001/2010 ዓ.ም” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡

4 ትርጉም

የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ መመሪያ ውስጥ፣

1) “ባለስልጣን” ማለት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የአካባቢ፣ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት
ባለስልጣን ማለት ነው፡፡
2) “አካባቢ” ማለት በመሬት፣ በከባቢ አየር፣ በአየር ሁኔታ እና በአየር ንብረት፣ በውኃ፣ በሕያዋን፣
በድምፅ፣ በሽታ፣ በጣዕም፣ በማሕበራዊ ጉዳዮች እና በሥነ ውበት ሳይወሰን በተፈጥሯዊ ሁኔታቸው
ወይም በሰው አማካኝነት ተሻሽለው ወይም ተለውጠው የሚገኙ ነገሮች በሙሉ ያሉበት ቦታ፣
እንዲሁም መጠናቸውን ወይም ሁኔታቸውን ወይም ደግሞ የሰው ወይም የሌሎች ሕያዋን በጎ ሁኔታን
የሚነኩ መስተጋብሮቻቸው ድምር ነው፡፡
3) “የአካባቢ ጥበቃ” ማለት የሰው ልጅን ጨምሮ የማንኛውም ህይወታዊ አካልና እድገት የሚወስኑ
የመሬት፣ የውኃና የአየር እንዲሁም ሌሎች ተመሳሳይ የአካባቢ ሀብቶች፣ ክስተቶችና ሁኔታዎች
እንዳይጠፉ፣ እንዳይቀንሱ ወይም ባህሪያቸዉ እንዳይለወጥ የመንከባከብ ተግባር ነው፡፡
4) “የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ” ማለት ኘሮጀክቶች ተግባራዊ ሲሆኑ ሲስፋፉና ሲቋረጡ በአካባቢ ላይ
የሚደርሱ ጠቃሚም ሆነ ጎጅ ተፅዕኖዎችን ለይቶ የማወቂያና ለችግሮችም ማቃለያ ወይም ማስወገጃ
እርምጃዎችን የመተንተን ሂደት ነው፡፡
5) “ተፅዕኖ” ማለት በፕሮጀክቶች ትግበራ ወቅት በአካባቢ ወይም በንዑሳን ክፍሎች ላይ በሚፈጠር
ለውጥ ምክንያት ማንኛውም በሰው ጤና ወይም ደህንነት፣ በዕፅዋት፣ በእንስሳት፣ በአፈር፣ በአየር፣
በውኃ፣ በአየር ንብረት፣ በተፈጥሯዊ ወይም በባሕላዊ ቅርስ፣ በሌላ ቁሳዊ አካል ወይም በአጠቃላይ
ሲታይ በአካባቢያዊ፣ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ ወይም በባሕላዊ ገጽታዎች ላይ የሚከሰት ተከታይ
ለውጥ ነው፡፡
6) “ብክለት” ማለት በህግ የተደነገገን ማንኛውንም ማዕቀብ፣ ግዴታ ወይም ገደብ ጥሶ በአካባቢ በሚገኙ
ህይወታዊ፣ ቁስ አካላዊና ኬሚካላዊ ሃብቶች ላይ የሚደርስ በሰዉ ጤና ወይም በጎነት ወይም ደግሞ
በሌሎች ህያዋን ላይ አደገኛ የሆነ ወይም አደገኛ ሊሆን የሚችል ገፅታ ያለው የመለወጥ ሂደት ነው፡፡
7) “በካይ” ማለት ፈሳሽ፣ ጠጣር ወይም ጋዝ የሆነ በቀጥታም ሆነ ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ ያረፈበትን
አካባቢ በመለወጥ ጠቀሜታ የመስጠት አቅሙን የሚያጓድል ወይም በሰው ጤና ወይም በሌሎች
ሕያዋን ላይ ጉዳት የሚያደርስ ወይም ሊያደርስ የሚችል መርዝን፣ በሽታን፣ መጥፎ ሽታን፣ ጨረርን፣
ድምፅን፣ ንዝረትን፣ ሙቀትን ወይም ሌላ ክስተትን የሚያመነጭ ማንኛውም ነገር ነው፡፡
8) “ፕሮጀክት” ማለት ማንኛውም በአዲስ መልክ የሚተገበር ወይም እየተተገበረ ያለ የልማት ወይም
የአገልግሎት ሰጪ የስራ እንቅስቃሴ ነው፡፡
4
9) “አዲስ ፕሮጀክቶች” ማለት የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ አስጠንተው ወደ ትግበራ የሚገቡ ፕሮጀክቶች
ማለት ነዉ፡፡
10) “ነባር ፕሮጀክቶች” ማለት የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ አዋጅ ወደ ስራ ከመግባቱ በፊትና ከዚያም በኋላ
የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ሳያካሂዱ ወደ ትግበራ የገቡ ፕሮጀክቶች ማለት ነዉ፡፡
11) “የፕሮጀክት ባለቤት” ማለት የሚመለከተው የመንግሥት አካል ወይም የግለሰብ ወይም የሁለቱንም
ጥምረት ባለቤትነት የሚያመላክት ነው፡፡
12) “ሌሎች ፈቃድ ሰጭ መስሪያ ቤት” ማለት እንደሁኔታዉ የኢንቨስትመንት ወይም የንግድ ወይም
የተለያዩ የስራ ፈቃዶች ለመስጠት በህግ ስልጣን የተሰጠዉ ማንኛዉም የመንግስት አካል ነዉ፡፡
13) “ተሻጋሪ” ማለት ከአንድ ቀበሌ ወደ ሌላ ቀበሌ ወይም ከአንድ ወረዳ ወደ ሌላ ወረዳ ወይም ከአንድ ዞን
ወደ ሌላ ዞን ኘሮጀክቱ የሚያስከትለው ወይም ሊያስከትል የሚችለው ተፅዕኖ መተላለፍ ወይም
መዛመት ማለት ነው፡፡
14) “የአካባቢ ይሁንታ ፈቃድ” ማለት ማንኛውም የግል ወይም የመንግስት አካል ወደ ፕሮጀክት ትግበራ
ከመግባቱ በፊት ወይም ከገባ በኋላ ለባለስልጣኑ ወይም በተዋረድ ለሚገኝ የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት
በሚያቀርበው የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት መሰረት ተቀባይነት ሲያገኝ የሚሰጥ ፈቃድ ነው፡፡
15) “ክልል” ማለት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሰተ ነዉ፡፡
16) “በተዋረድ ያለ የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት” ማለት የዞን፣ የወረዳ ወይም የቀበሌ አካባቢ ጥበቃ
አደረጃጀት ማለት ነዉ፡፡
17) “የአካባቢ ተቆጣጣሪዎች” ማለት ለክትትል፣ ለምርመራና ለቁጥጥር ስራ በባለስልጣኑ ወይም
በተዋረድ በባለስልጣኑ ስር ባለ መስሪያ ቤት የሚሰየሙ ባለሙያዎች ማለት ነዉ፡፡
18) “ምድብ 1 ፕሮጀክት” ማለት የፕሮጅከቱ ትግበራ በአካባቢና ማህበረሰብ ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽእኖ
የሚያደርስና ተጽዕኖውን ለመቀነስ (ለማስቀረት) ጥልቅ የአካባቢ ተጽእኖ ጥናት ዘገባ እንዲቀርብባቸው ከሚገደዱ
ፕሮጀክቶች ምድብ ውስጥ የሚካተትና ሙሉ የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት የሚያስፈልገው ፕሮጀክት ነው፡፡
19) “ምድብ 2 ፕሮጀክት” ማለት በፕሮጀክቱ ትግበራ የሚከሰቱ የአካባቢና ማህበራዊ ተጽእኖዎች ስፋት መለስተኛ የሆነ
(ዉስብስብ ያልሆነ) እና ተጽዕኖው በመለስተኛ የማቃለያ እርምጃዎች የሚቀረፍ ከፊል የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት
የሚያስፈልገው ፕሮጀክት ነው፡፡
20) “ምድብ 3 ፕሮጀክቶች” ማለት በፕሮጀክቶች ትግበራ ምክንያት በተናጠልም ሆነ በተደማሪነት በአካባቢ ላይ የጎላ
ተጽዕኖ የሌላቸው ወይም በአካባቢ ላይ አወንታዊ ተጽእኖ የሚኖራቸው ፕሮጀክቶች ምድብ ሲሆን በዚህ ምድብ
ውስጥ የሚካተቱ ፕሮጀክቶች የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት እንዲያካሂዱ የማይገደዱ ናቸው፡፡
21) “የመጀመሪያ ደረጃ የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት” ማለት ፕሮጀክቶች በሚያከናዉኗቸዉ ተግባራት የተነሳ የሚከሰቱ
የአካባቢ ተጽእኖዎችን ደረጃና የጥናት አይነት ለመለየት አስቸጋሪ ሲሆን የተጽዕኖዎችን ደረጃና የሚያስፈልገውን
የጥናት አይነት ለመለየት የሚካሄድ የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት አይነት ነው፡፡
22) “በቀላሉ ለጉዳት ተጋላጭ የሆኑ ወይም ልዩ ጥንቃቄ የሚሹ አካባቢዎች” ማለት በተፈጥሮ አደጋ ወይም ሰዎች
በሚያካሂዱት የዕለት ተዕለት የልማት እንቅስቃሴ ምክንያት የጎላ አሉታዊ ተጽዕኖ ሊደርስባቸው እና በቀላሉ ሊጠፉ

5
የሚችሉ ወይም አንዴ ከጠፉ መልሰው ሊተኩ የማይችሉ ነገር ግን ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ፣ ባህላዊ፣
ታሪካዊና አካባቢያዊ ጠቀሜታ ያላቸው የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ሀብቶች ናቸው፡፡
23) “ተዳማሪ ተፅዕኖ” ማለት ሁለትና ከዚያ በላይ ፕሮጀክቶች በአንድ አካባቢ ሲተገበሩ የሚያስከትሉት የአሉታዊ
ተፅዕኖዎች ድምር ወይም የሁለትና ከዚያ በላይ ፕሮጀክቶች መስተጋብር ውጤት በአካባቢው ካሉ ፕሮጀክቶች
ድምር ተጽዕኖ በላይ የሆነ አሉታዊ ተጽዕኖ ሲፈጠር ነው፡፡
24) “የአካባቢ ክትትል” ማለት በአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት ሪፖርት ውስጥ በአካባቢ አያያዝ ዕቅድ ላይ የታቀዱ የማቅለያ
ተግባራት ስለመፈፃመቸው፣ ከተተነበዩ ተጽዕኖዎች በተጨማሪ ሌሎች አዳዲስ ተፅዕኖዎች ስለመከሰታቸው፣
በመሰረታዊ የአካባቢ መረጃ ላይ የተለዩ የአካባቢ ጉዳዮች በትግበራ ጊዜ ምን ያህል እንደተለወጡ፣ የፕሮጀክት
ትግበራ ከወጡ የአካባቢ ህጎች ጋር ምን ያህል ተጣጥሞ እየተተገበረ እንደሆነና የማቅለያ ተግበራት አፈጻጸም
ውጤታማነትን ለመገምገምና ወቅቱን የጠበቀ የማስተካከያ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል ስልታዊና ተከታታይነት
ያለው መረጃን የመሰብሰብ፣ የመለካት፣ የመተንተንና የማስተካከያ እርምጃ የመውሰድ እና የመደገፍ ሂደት ነው፡፡
25) “የአካባቢ ምርመራ” ማለት አጠቃላይ የፕሮጀክቱን አፈፃፀም ከወጡ የአካባቢ ህጎችና ደረጃዎች ጋር ምን ያህል
ተጣጥሞ እየሄደ እንደሆነ ለመገምገም፣ በአካባቢ ተጽዕኖ ጥናቱ የተለዩ ተጽዕኖዎችን ለመቀነስ (ለማቃለል)፣ የታቀዱ
ተግባራትን አፈፃፃምና ውጤታማነት ለማረጋገጥ፣ እየተተገበረ ያለው የአካባቢ አያያዝ እቅድ ያመጣውን ለውጥ
ለመገምገም ወይም ፕሮጀክቱ ከአንዱ አካል ወደሌላ አካል ከመዛወሩ በፊት ያለውን አጠቃላይ የአካባቢ አያያዝ
ሁኔታ ለማወቅ እንዲሁም ሊደርሱ የሚችሉ የአካባቢ ተጽዕኖዎችና አደጋዎችን ለመለየትና ለችግሮቹ መፍትሄ
ለመስጠት የሚያስችል የአካባቢ መረጃን በተወሰነ የጊዜ ክፍተት የመሰብሰብ፣ የመለካት፣ ያሉ ሰነዶችንና ሪፖርቶችን
የመመርመርና የመተንተን ሂደት ነው፡፡
26) “የአካባቢ ቁጥጥር” ማለት ጥርጣሬ ሲኖር ወይም ጥቆማ ሲደርስ የሚካሄድ ድንገተኛ የአካባቢ ፍተሻ ወይም ቀደም
ሲል በተካሄደ የአካባቢ ክትትልና ምርመራ ላይ የተሰጠ ግብረመልስን የአፈፃፀም ደረጃ ለማረጋገጥ ወቅቱን
ባልጠበቀ ምልከታ የሚረጋገጥበትና በቁጥጥሩም መሰረት የተለያዩ ህጋዊና አስተዳደራዊ የእርምት እርምጃዎች
የሚወሰድበት ሂደት ነው፡፡
27) “የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት ወሰን ልየታ” ማለት የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት በሚካሄድበት ወቅት በትኩረት (በጥልቀት)
መታየት ያለባቸው ዋና ዋና ጉዳዮችና ተፅዕኖዎች የሚለዩበትና ጥናቱን ለማካሄድ የሚያገለግል የጥናት እቅድ ወይም
ቢጋር የሚዘጋጅበት የጥናት ሂደት ነው፡፡
28) “የተፅዕኖ ማቅለያ እርምጃዎች” ማለት በፕሮጀክት ትግበራ ወቅት በአካባቢና በማህበረሰብ ላይ የሚደርሱ አሉታዊ
ተፅዕኖዎችን ለመቀነስ ወይም በተወሰነ ደረጃ ለማስቀረት ካልሆነም ደግሞ ለማካካስ የሚከናወኑ ተግባራት ናቸው፡፡
29) “የአካባቢ ህግ አስከባሪ ግብረሀይል” ማለት በፕሮጀክቶች ትግበራ ሂደት የሚፈጠሩ የአካባቢ ብክለትና
ብክነት ሁኔታዎችን ከአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት የሚቀርብለትን ጥቆማና ማስረጃ በመገምገም
የእርምት እርምጃ የሚወስድ አደረጃጀት ነው፡፡
30) “ኃላፊ” ማለት በየደረጃው ያለ የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤቶች ዋና ዳይሬክተር፣ ምክትል ዋና
ዳይሬክተር፣ ዳይሬክተር፣ መምሪያ ኃላፊ፣ ጽ/ቤት ኃላፊና ቡድን መሪዎችን ያጠቃልላል፡፡

6
31) “የአካባቢ አያያዝ ሰነድ” ማለት ነባር ፕሮጀክቶች በአካባቢና በማህበረሰቡ ላይ የሚያደርሱትን
አሉታዊ ተፅዕኖዎች በመለየት ችግሮቹን ለማቃለል የሚዘጋጅ የተፅዕኖ ማቃለያ ሰነድ ነው፡፡

32) “የአካባቢ አያያዝ እቅድ” ማለት በአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት እና በአካባቢ አያያዝ ሰነድ ውስጥ የሚገኝ
አንዱ የጥናት ክፍል ሲሆን የሚከሰቱ የአካባቢ ተጽዕኖዎችን ለማስቀረት፣ ለመቀነስ ወይም ለማካካስ
የሚከናወኑ ዝርዝር ተግባራት የድርጊት፣ የፈጻሚ አካላት፣ የበጀትና የጊዜ መርሀ ግብር ነው፡፡
33) “ሰው” ማለት የተፈጥሮ ሰው ወይም በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው አካል ነው፡፡

5 የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሂደት ወሰን ልየታ ስለማካሄድ

የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት ወሰን ልየታ አላማ ዋና ዋና የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖዎችንና ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን
ለመለየትና የተጽዕኖ ጥናት ስራውን በእቅድ ለመምራት ሲሆን የሚከተሉት ዝርዝር ተግባራት መፈጸም
ይኖርባቸዋል፡፡

1. የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት ወሰን ልየታ ሪፖርት ለአካባቢ ጥበቃ ተቋም ቀርቦ ካልጸደቀ በስተቀር ዋናውን
የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ መጀመር አይቻልም፡፡

2. የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት ወሰን ልየታ ሪፖርት ለሚመለከተው የአካባቢ ጥበቃ መስሪያቤት ከመቅረቡ በፊት
ፕሮጀክቱ ስለሚያስከትላቸው አካባቢያዊና ማህበራዊ ተጽዕኖዎች ከሚመለከታቸው አካላትና
የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ግልጽ ውይይት ሊካሄድ ይገባዋል፡፡ የማህበረሰብ ውይይት ቃለጉባኤ
የሚከተሉትን ነጥቦች ያካተተ መሆን አለበት፡-
1) ለህብረተሰቡ የቀረቡ የፕሮጀክቱ ዋና ዋና አካባቢያዊና ማህበራዊ አሉታዊና
አዎንታዊ ተጽዕኖዎች፣
2) ህብረተሰቡ ስለፕሮጀክቱ ተጽኖዎች ያለው አመለካከት፣
3) በፕሮጀክቱ አካባቢ ያለ የቀበሌና ወረዳ የመንግስት አስተዳደር አካላት ስለፕሮጀክቱ
አካባቢያዊና ማህበራዊ አሉታዊ ተፅዕኖዎች የሰጡት አስተያየት፣
4) በህብረተሰቡ የተነሱ ስጋቶች፣
5) በተነሱ አሉታዊ ተፅዕኖዎችና ስጋቶች ላይ የተቀመጡ የመፍትሄ ሃሳቦች፤
6) በፕሮጀክቱ ትግበራ ተጠቃሚ፣ ተጎጂ፣ ፍላጎቱ ያላቸውና የሚመለከታቸውን አካላት
ተለይተው ከፕሮጀክት ባለቤትና ከአማካሪ ድርጅቱ ጋር የተወያዩበትና
የተፈራረሙበት ቃለ ጉባኤና ምስል፡፡
3. አንድ የፕሮጀከት በለቤት የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት ወሰን ልየታ ሪፖርት እንዲያቀርብ የሚፈቀድለት አጠቃላይ
የፕሮጀክቱ ዝርዝር መግለጫ ለአካባቢ ጥበቃ ተቋም ቀርቦና ተገምግሞ ከአካባቢና ማህበራዊ ደህንነት አኳያ
ተቀባይነት ሲያገኝ ብቻ ይሆናል፡፡

7
4. የአካባቢ ወሰን ልየታ ሪፖርት የውጭ ሽፋን የፕሮጀክቱ ስም፤ የፕሮጀክቱ ባለቤት ስምና ሙሉ
አድራሻ፤ የአማካሪ ድርጅቱ ሙሉ ስምና አድራሻ፤ ሰነዱ የተዘጋጀበት ጊዜ ወርና ዓም እንዲሁም
ሰነዱ የተዘጋጀበት ቦታ ስም ሊይዝ ይገባዋል፡፡

5. የአካባቢ ወሰን ልየታ ሪፖርቱ የመጨረሻ ውጤቱ የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት ወሰን (ToR) ማዘጋጀት
ስለሆነ ወሰኑ የሚከተሉትን ነጥቦች ያካተተ መሆን አለበት፡-

1) የፕሮጀክቱ ዝርዝር መግለጫ ማለትም ፕሮጀክቱ የሚጠቀመው የግብዓት አይነትና


መጠን፣ የምርት አይነትና መጠን ፣ የቆሻሻ አይነትና መጠን፣ የአመራረቱ ዘዴ፣
በእያንዳንዱ የፕሮጀክቱ ደረጃዎች (ግንባታ፣ ትግበራ እና መዝጊያ ጊዜ) የሚከናወኑ ዋና
ዋና ተግባራት ፕሮጀክቱ የሚጠቀመው ቴክኖሎጂ፣ የፕሮጀክቱ የትግበራ ጊዜን መሰረት
በማድረግ ለእያንዳንዳቸው ቢያንስ ሁለት ሁለት አማራጮችን በማወዳደር ከአካባቢያዊ፣
ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አዋጭነት አኳያ የተሻለውን አማራጭ ለመምረጥ የሚያስችል
የጥናት ስራ እንደሚሰራ እንዲሁም ፕሮጀክቱ ቢተገበርና ባይተገበር ያለውን ጠቀሜታና
ጉዳት ለማመዛዘን የሚያስችል ትንተናዎችን የሚያካትት መሆን ይኖርበታል፤

2) በካርታ የተደገፈ የፕሮጀክት ቦታው መገኛና አዋሳኞች፣


3) የአካባቢ ተጽዕኖ የጥናት ዘዴ (ስልት) ማለትም ከመረጃ ስብሰባ እስከ ትንተና ጥቅም ላይ
የሚውሉ ዝርዝር የጥናት ዘዴዎች፣
4) የጥናት ቡድኑ የሙያ ስብጥር፣ ኃላፊነትና ግዴታዎች፣
5) በቀጣይ በስፋት መተንተን ያለባቸው አማራጮች፣
6) በተጽዕኖ ግምገማ ሂደት የማህበረሰቡና የተቋማት የተሳትፎ ሁኔታ፣
7) ጥናቱ የሚያካትታቸው ዋና ዋና አካባቢዊና ማህበራዊ ተፅዕኖዎች እና ሌሎች ቁልፍ
ጉዳዮች፣ እንዲሁም የተጽዕኖዎች ትንተና፤
8) የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት ሰነድ ይዘት (table of contents)፤
9) የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ጥናት ስራ የሚካሄድበት የጊዜ ሰሌዳ ናቸው፡፡
6. ከላይ በተ.ቁ 5 ከተዘረዘሩት በተጨማሪ ሪፖርቱ ፕሮጀክቱ የሚተገበርበትን ልዩ ቦታና ተጽዕኖ
የሚያደርስበትን አካባቢ አጭርና ግልፅ የሆነ ባዮፊዚካል፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መረጃ መያዝ
አለበት፡፡ መረጃውም የውሃ አካላትን፣ የአፈርን፣ የእንስሳትንና እፅዋትን፣ የጥበቅ ቦታዎችንና
ተያያዥነት ያላቸውን የስርዓተ-ምህዳሮች ጠቀሜታን፣ የማህበራዊና ባህላዊ እሴቶችን፣ ታሪካዊ
ቅርሶችን፣ የህብረተሰብ ጤናና የመሰረተ ልማት ሁኔታዎችን መረጃ ያካተተ መሆን አለበት፡፡
7. አሳማኝ ምክንያት ካልተፈጠረ በስተቀር የአንድ ፕሮጀክት የተጽዕኖ ግምገማ የጥናት የጊዜ ሰሌዳ
የወሰን ልየታው ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በአንድ አመት ውስጥ መጠናቀቅ አለበት፡፡ በመዘግየቱ
ምክንያት የሁኔታ ለውጥ አለ ተብሎ ከታሰበ በድጋሜ መስክ ምልከታ ሊካሄድ ይችላል፤

8
8. የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት ስራው በጸደቀው የጊዜ ሰሌዳ ለማጠናቀቅ የማያስችል አሳማኝ ምክንያት
ሲያጋጥም ለአካባቢ ጥበቃ ተቋም የበላይ ኃላፊ በማቅረብ እስከ ስድስት ወር ድርስ ማራዘም
ይችላል፤
9. የሚከተሉት መረጃዎች በዕዝል ውስጥ መያያዝ አለባቸው፤
1) የጥናት ቡድኑ አባላት የትምርት ዝግጅትና የሥራ ልምድ መረጃ ወይም ግለ-ታሪክ፣
2) የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የታደሰ የአካባቢ አማካሪ ድርጅት እና የሙያ ብቃት ፈቃድ፣
3) የህብረተሰብ ተሳትፎ ቃለ ጉባኤ፣
4) የፕሮጀክቱ ቦታ ካርታና ኮኦርዲኔትስ፣
5) አካባቢውን የሚያሳዩ ፎቶግራዎች፣
6) በአካባቢ ጥበቃ ተቋም የተሰጠው የአማካሪ ድርጅቱ ባለሙያዎች ዝርዝር መረጃ ፎቶ
ኮፒ
7) የማህበረሰብ ውይይት ተሳታፊዎችን የሚያሳዮ ፎቶግራፎች፣
8) ከሚመለከታቸው አካላት የድጋፍ ደብዳቤና ሌሎችም መረጃዎች (ካሉ)፤
9) መጀመሪያ በቀረበው ሰነድ ላይ ከአካባቢ ጥበቃ ባለሙያዎች እንዲካተትና
እንዲስተካከል የተሠጠ አስተያየት ቅጅ
10. የተለየ ሁኔታ ካልተፈጠረ በስተቀር የአካባቢ ጥበቃ ባለሙያዎች የፕሮጀክት የመስክ ምልከታ
የሚያካሂዱት አንድ ጊዜ ብቻ ይሆናል፡፡ ሆኖም ግን የፕሮጀክቱ ባህሪ ውስብስብ ከሆነ በአካባቢ
ጥበቃ መስሪያ ቤቶች የበላይ ኃላፊዎች ውሳኔ ሁለተኛ መስክ ምልከታ እንዲደረግ ሊታዘዝ
ይችላል፡፡ የአካባቢ ጥበቃ ባለሙያዎች ፕሮጀክቱን የሚመለከት ቸክሊስት በማዘጋጀት የመስክ ምልከታ
ያደርጋሉ፡፡
11. የመስክ ምልከታ ቸክሊስቱ ከፕሮጀክቱ ዝርዝር መግለጫ፣ በሪፖርቱ እዝል ላይ ከተያያዙ መረጃዎችና በክልሉ
የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በሚዘጋጀው የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ የአሰራር መመሪያ (Guideline) ላይ
ከተዘረዘሩት የፕሮጀክት ተጽዕኖ መጠይቆች መካከል የፕሮጀክቱን አይነት መሰረት በማድረግ ይዘጋጃል፡፡
12. የመስክ ምልከታ ያደረገ የአካባቢ ጥበቃ ባለሙያ በአዘጋጀው ቸክሊስት መሰረት የሰበሰበውን መረጃ
በመተንተን፣ በምስል በማስደገፍና የውሳኔ ሀሳብ በማካተት የመስክና የዴስክ ግምገማውን ያካተተ የወሰን
ልየታ ሪፖርት ግብረመልስ በማዘጋጀት ዘገባውን ላቀረበ አማካሪ ድርጅት በ 5 የስራ ቀናት ውስጥ እንዲደርስ
ያደርጋል፡፡ የግብረ-መልሱ ግልባጭ ለክትትል ይረዳ ዘንድ ለቅርብ ሀላፊው እንዲደርስ መደረግ አለበት፡፡
13. የግምገማ ሂደቱን ያጠናቀቀ የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት ወሰን ልየታ ሪፖርት የጥናት የውል ስምምነት ሆኖ
ስለሚያገለግል ለአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤቶች ሲቀርብ በባለሀብቱና በአማካሪ ድርጅቱ ተረጋግጦና ማህተም
አርፎበት ሊሆን ይገባል፡፡

9
6 የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርት አዘገጃጀት
6.1 የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ የቋንቋ አጠቃቀም

የፕሮጀክቱ ባህሪ የሚያስገድድ ካልሆነ በቀር ሪፖርት የሚቀርበው በክልሉ የስራ ቋንቋ በአማርኛ ይሆናል፡፡ የፕሮጄክቱ
ባለቤት የውጭ አገር ዜግነት ያለው ከሆነ በእንግሊዝኛ ሪፖርቱ ሊቀርብ የሚችል ሲሆን ከሚቀርበው ሪፖርት ውስጥ
ግን የአካባቢ አያያዝና የክትትል ዕቅዱ ክፍል በአማርኛ ተተርጉሞ የሪፖርቱ አካል ሆኖ ይቀርባል፡፡

6.2 የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት ይዘት

የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት ሲዘጋጅ መካተት የሚገባቸዉ ዝርዝር ጉዳዮች የሚከተሉት ይሆናሉ፡፡

6.2.1 ማጠቃለያ
1) ማጠቃለያው ከሁለት ገጽ ያላነሰ ከአምስት ገጽ ያልበለጠ ሆኖ የፕሮጀክቱ ገምጋሚዎችና ውሳኔ ሰጭ አካላት
የፕሮጀክቱን ምንነት፣ ተጽዕኖዎችንና የተጽእኖ ማቃለያ መንገዶችን በቀላሉ እንዲረዱት ሆኖ መዘጋጀት አለበት፡፡
2) ማጠቃለያው ስለፕሮጀክቱ ግልፅ፣ ትክክለኛና የማይጣረስ መረጃ ሊይዝ ይገባል፡፡
3) በዚህ ክፍል ሊካተቱ የሚገባቸው ዋና ዋና ጉዳዮች፡- የፕሮጀክቱ ስምና አድራሻ (መገኛ ቦታ)፤ የፕሮጀክቱ ባለቤት
ስም፤ ጥናቱን ያጠናው አማካሪ ድርጅቱ ስም፤ የፕሮጀክቱ ምንነት አጭርና ግልጽ ማብራሪያ፤ የፕሮጀክቱ ቦታ
አጭርና ግልጽ የመነሻ መረጃ፤ የጥናት ስልት፣ የፕሮጀክቱ አማራጮች፤ በፕሮጀክቱ ምክንያት ይከሰታሉ ተብሎ
የሚገመቱ ዋና ዋና የአካባቢ ተፅእኖዎች፤ የተለዩ የተጽእኖ ማቅለያ ዘዴዎች (የገንዘብ ወይም በአይነት ካሳን
ጨምሮ)፣ የአካባቢ ክትትል ስራዎችና የማስተግበሪያ ስልቶች ይሆናሉ፡፡
6.2.2 መግቢያ

ይህ ክፍል የፕሮጀክቱ አጠቃላይ የመነሻ ሀሳብ የሚገለጽበትና የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናቱ አደረጃጀት የሚመላከትበት ክፍል
ሲሆን ጽሁፉ ከሶስት ገጽ መብለጥ የለበትም፡፡ የጥናቱም መግቢያ የሚከተሉትን ነጥቦች በግልፅ ማሳየት ይኖርበታል፡፡
1) የፕሮጀክቱ የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት መነሻ ሀሳቦች፤
2) ፕሮጀክቱን ባጭሩ ማስተዋወቅ
3) የአካባቢ ተጽእኖ ጥናት ዘገባው አደረጃጀት፤
4) የጥናት ዘገባው አላማ፣ የባለሀብቱን ግዴታ፣ የህግ ተጠያቂነትንና በቀጣይ የሚከናዎኑ ተግባራትን የሚያገልጽ መሆን
አለበት፡፡

6.2.3 የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማው ዓላማ

1) ከፕሮጀክቱ ትግበራ በፊት የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት ማካሄድ ያስፈለገበት ጥቅል አላማና የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናቱ
የሚያረጋግጣቸው ዝርዝር አላማዎች በዚህ ክፍል በአግባቡ ሊገለጹ ይገባቸዋል፡፡
2) የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናቱ በዚህ ክፍል ለተለዩት ዝርዝር አላማዎች ምላሽ የሚሰጥ መሆን አለበት፡፡

10
6.2.4 የጥናቱ ወሰን

1) የፕሮጀክቱ የአካባቢ ተጽእኖ የጥናቱ ጥልቀትና ስፋት በግልጽ መጠቀስ ይኖርበታል፡፡


2) የፕሮጀክቱ የአካባቢ ተጽእኖ የጥናት ወሰን እንደ ፕሮጀክቱ ዓይነትና ፕሮጀክቱ እንደሚተገበርበት አካባቢያዊ፣
ማህበራዊ፣ ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ተለይቶ መቀመጥ ይኖርበታል፡፡
3) ጥናቱ የሚካሄድባቸው አካባቢዎች ስም ዝርዝር መካተት አለበት፡፡
4) የጥናት ወሰኑ የፕሮጀክቱን የጥናት ክልል የሚያሳይ ካርታ ሊያካትት ይገባዋል፡፡

6.2.5 የጥናቱ ስልት ወይም ዘዴ

በዚህ ክፍል አወንታዊና አሉታዊ የአካባቢ ተፅእኖዎችን ለመለየት፣ ለመተንበይና ለመተንተን፣ እንዲሁም ያሉ
አማራጮችንና የማቃለያ እርምጃዎችን ለመለየትና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለማሳተፍ ጥቅም ላይ የሚውሉ
ዘዴዎች የሚገለጽበት የዘገባ ክፍል ነው፡፡ በመሆኑም በዚህ ክፍል የሚከተሉትን ነጥቦች በግልፅ ማስቀመጥ ይገባል፡-
1) ጥናቱን ለማካሄድ ጥቅም ላይ የሚውል የጥናት ስልት፣ የሚያስፈልግ ግብዓት፣ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎችና
የትንተና ዘዴዎች (ለምሳሌ የባለሙያዎች ሙያዊ አስተያየት፣ የአዋጭነት ትንተና፣ የመገምገሚያ ቅፆች፣ ከአሁን
በፊት ያሉ ልምዶች፣ የቦታ ሽፋን፣ ወዘተ)
2) የሚመለከታቸውን አካላት ለማሳተፍ ጥቅም ላይ የሚውል የማሳተፊያ ዘዴ ወይም ስልትና የተሳትፏቸው ደረጃ
3) በጥናቱ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ብዛት፣ የሙያ ስብጥር፣ ኃላፊነትና ሙሉ አድራሻ

6.2.6 በጥናቱ ወቅት የተወሰዱ ታሳቢዎችና ያጋጠሙ ክፍተቶች

በቂ የመረጃ ምንጭ ባለመገኘቱ የተነሳ ሊተገበር በታሰበው ፕሮጀክት ዙሪያ የሚሰበሰቡ መረጃዎች ከአጠራጣሪ ምንጮች
ሊሰበሰቡ ይችላሉ፡፡ በዚህ ምክንያት አንዳንድ የጥናት ዳሰሳዎች በግምት ወይም በመላምት ላይ ተመርኩዘው ሊሰሩ
ስለሚችሉ ተፅእኖዎችን ለመተንበይና ለመተንተን ክፍተት ሊገጥም ይችላል፡፡ ስለዚህ ጥናቱን የሚያዘጋጀው አካል
የሚከተሉትን ነጥቦች በማካተት የዳሰሳ ጥናቱን የእርግጠኛነት ደረጃ በግልፅ ማመላከት ይኖርበታል፡፡ በዚህ ክፍል፡-
1) በጥናት ሂደት ያጋጠሙ የእውቀት ክፍተቶችን፣ በይሆናል የተወሰዱ መረጃዎችንና የመረጃ ምንጭ ያልተገኘላቸውን
ጉዳዮች ይለያሉ፣
2) መላምቶች ያልተሟሉ የሆኑበትን ምክንያት ይዘረዘራል፣
3) የተለዩት የእውቀት ክፍተቶችና መላምቶች በውሳኔ አሰጣጥ ላይ የሚኖራቸው እንድምታ መብራራት ይኖርበታል፣
4) ሌሎች በጥናቱ ሂደት ያጋጠሙ ውስንነቶች ካሉ ከነምክንያታቸው መገለጽ ይኖርባቸዋል፣
5) ያጋጠሙ እጥረቶችንና ውስንነቶችን ለማስወገድ የተወሰዱ መፍትሄዎች መገለጽ ይኖርባቸዋል፡፡

6.2.7 የፖሊሲ፣ የህግና የአስተዳደር ማዕቀፎች

ይህ ክፍል ፕሮጀክቱ ሲተገበር ሊፈጽማቸውና ሊመራባቸው የሚገቡ የፖሊሲ፣ የህግና የአስተዳደር ማዕቀፎች
የሚዘረዘርበት የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርት ክፍል ሲሆን ፕሮጄክቱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ የፖሊሲ፣

11
የህግና የአካባቢ ደረጃ ማዕቀፎች በጥናቱ ይዳሰሳሉ፡፡ ከቦታውና ከፕሮጀክቱ ጋር ተገቢነትና ተያያዥነት ያላቸው
ተጨማሪ የህግ ክፍሎች በዕዝል ሊያያዙ ይችላሉ፡፡

6.2.8 የፕሮጀክቱ መግለጫ

በዚህ ክፍል የሚከተሉት ነጥቦች መካተትና መገለፅ አለባቸው፡-


1) የፕሮጀክቱ ስፋትና ባህሪ፣
2) ለፕሮጀክቱ የተለያዩ አማራጮች ግልፅ ማብራሪያ፣
3) የጥሬ እቃዎች ምንጭ፣ ዓይነት፣ ባህሪና መጠን፣
4) በምዕራፎች የተከፋፈለ የፕሮጀክቱ የትግበራ የጊዜ ሰሌዳ፣
5) የቴክኖሎጂ አይነትና የቴክኖሎጅ አጠቃቀም ገለጻ፣
6) የአመራረት ሂደት፣ የተረፈ-ምርቶችና ዋና ምርቶች ዓይነትና መጠን
7) የደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ስርዓት፣
8) የሰው ኃይልና የግብዓት ፍጆታ ወጪዎች፣ ወዘተ፣

6.2.9 ፕሮጀክቱ የሚተገበርበት ቦታ መግለጫ

በዚህ ክፍል የፕሮጀክቱን አካባቢዊ ሁኔታ የሚገልፅ መሰረታዊ መረጃ በመሰብሰብ አካባቢውን በትክክል የሚያሳይ ዘገባ
ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡ ይህ ክፍል በፕሮጀክቱ ምክንያት ጉዳት ወይም ተጽዕኖ ስለሚደርስባቸው አካባቢዎች ትኩረት
በመስጠት ግልፅ ማብራሪያ ማካተት/መስጠት ይጠበቅበታል፡፡ በመሆኑም መካተት የሚገባቸው መረጃዎች፡-

6.2.9.1 . የባዮፊዚካላዊ መሰረታዊ መረጃዎች፣


1) ፕሮጀክቱ የሚተገበርበትን ልዩ ቦታ የሚመለከት መረጃ (ለምሳሌ የአካባቢውን የመሬት ስሪት ወይም የይዞታ ሁኔታ፣
በዙሪያው ስለሚገኝ የመሬት ሁኔታ፣ በአካባቢው ላይ ያሉና በግልፅ የሚታዩ ተግዳሮቶች፣ በፕሮጀክቱ ውስጥና
በአካባቢዉ ያለው የመሰረተ-ልማት አገልግሎት ሁኔታ ወዘተ)፣
2) አሃዛዊና አሃዛዊ ያልሆኑ ፊዚካላዊና ስነ-ህይወታዊ የአካባቢ መረጃዎች (ለምሳሌ፡- የአየር ንብረት፣ የአፈር፣ የውሃ
ሀብት፣ የስርዓተ ምህዳር፣ የመሬት አቀማመጥ፣ የዕፅዋትና የእንስሳት አይነት ስርጭትና ብዛት ወዘተ…….)፣
3) ልዩ ጥበቃ የሚያስልጋቸው ቦታዎች ገለጻ (ለምሳሌ ብሄራዊ ፓርኮች፣ የዱር እንስሳት መጠለያ ቦታዎች፣ ወዘተ…..)፣
4) ተጽዕኖ የሚደርስበትን ቦታ የሚያመለክቱ ኮኦርድኔቶች፣ ከለር ፎቶግራፎች፣ ሰንጠረዥና ሌሎች ገላጭ መረጃዎች፣
5) የፕሮጀክቱ የትግበራ ቦታ ካርታና የፕሮጀክት ሳይት ፕላን፣
6) ፕሮጀክቱ ድንበር ተሻጋሪ ተፅዕኖ የሚያደርስ ከሆነ ተጽእኖ የሚደርስበት አካባቢ የፊዚካላዊ፣ ስነ-ህይወታዊና
ሌሎች መሰረታዊ መረጃዎች መያዝ አለበት፡፡

12
6.2.9.2 የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መሰረታዊ መረጃዎች፣

1) አሃዛዊና አሃዛዊ ያልሆኑ የማህበራዊና ምጣኔ ሃብታዊ መረጃዎች (ለምሳሌ የህዝብ ቁጥርና ስርጭት፣ የዕድሜ
ስብጥር፣ የኢኮኖሚ እድገት ሁኔታ፣ የውልደትና የጤና ሁኔታ፣ የቤተሰብ የገቢ ሁኔታ መረጃ፣ የኑሮ ሁኔታ፣
የመሰረተ-ልማት አገልግሎት፣ የቤቶች ሁኔታ፣ የሃይል ፍጆታ፣ የውሃ አቅርቦት ወዘተ…..)
2) የባህላዊና ታሪካዊ ቦታዎች ገለጻ (ለምሳሌ፣ የመስህብ ቦታዎችና ቅርሶች፣ በሰውና በእንስሳት ምስል የተሰሩ
ሀውልቶች፣ ትኩረት የሚሰጣቸው ሃይማኖታዊ ቦታዎች ወዘተ…..)፣
3) ተጽዕኖ የሚደርስበትን ቦታ የሚያመለክቱ ኮኦርድኔቶች፣ ከለር ፎቶግራፎች፣ ሰንጠረዥና ሌሎች ገላጭ መረጃዎች፣
4) የፕሮጀክቱ የትግበራ ቦታ ካርታና የፕሮጀክት ሳይት ፕላን፣
5) ፕሮጀክቱ ድንበር ተሻጋሪ ተፅዕኖ የሚያደርስ ከሆነ ተጽእኖ የሚደርስበት አካባቢ የማህበራዊ፣ ምጣኔ ሃብታዊና
ሌሎች መሰረታዊ መረጃዎች መያዝ አለበት፡፡

6.2.10 የአካባቢ ተጽዕኖ ትንተና ስለማካሄድ


1) በዚህ ክፍል አዎንታዊና አሉታዊ የአካባቢና ማህበራዊ ተፅእኖዎች መለየት፣ መተንበይና የተፅዕኖ ደረጃቸው መወሰን
አለበት፡፡
2) የእያንዳንዱ ተፅእኖ ትንተና የተጽዕኖውን ግልጽ ማብራሪያና ትንታኔ (ምሳሌ የተፅዕኖው መጠን፣ የቦታ ስፋት፣
የሚቆይበት ጊዜ፣ ድግግሞሽ፣ ደረጃ፣ ተጽእኖ የደረሰበት አካባቢ ወደ ነበረበት መመለስ የሚቻል መሆኑና አለመሆኑ፣
ስጋትና ያልተጠበቁ ሁኔታዎች ክስተት፣ ተጽዕኖ የሚደርስባቸው ክፍሎች መጠን ወዘተ) ማካተት አለበት፣
3) በፕሮጀክቱ በሚተገበርበት ክልል ውስጥና አካባቢ የሚገኙ ተጽዕኖ የሚደርስባቸው አካላት ትንተና ሊኖረው
ይገባል፣
4) ፕሮጀክቱን ለመተግበር የተለዩ የተጽዕኖ ማቃለያ አማራጮች ንጽጽር ትንተና (ስፋት/መጠን፣ መገኛ ቦታ፣
ቴክኖሎጂ፣ ፕላን፣ የኃይል ምንጭ፣ የጥሬ እቃዎች ምንጭ፣ ቴክኒካዊ ተፈጻሚነት፣ የአካባቢዊና ማህበራዊ
ችግሮች/እጥረቶች) ሊያካትት ይገባል፣
5) አዲሱ ፕሮጀክት ሲተገበር በአካባቢው ካሉ ሌሎች ነባር ፕሮጀክቶችና ወደፊት ሊሰሩ ከታቀዱ ፕሮጀክቶች ጋር
ሲዳመር ሊደርስ የሚችለውን ተዳማሪ የአካባቢና ማህበራዊ ተጽዕኖ ትንተና ሊያካትት ይገባል፣
6) የተጽዕኖ ክስተት ትንበያ የእርግጠኛነት ደረጃ መያዝ አለበት፣
7) ከተዘረዘሩ አማራጮች መካከል የተሻሉ አማራጮችን ለመምረጥ ጥቅም ላይ የዋሉ መረጃዎችን ማካተት አለበት፡፡
8) የፕሮጀክት ማስፋፊያ የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት ሲዘጋጅ የአካባቢ ምርመራ በማካሄድና የምርመራ ሪፖርቱን
በግብዓትነት በመጠቀም ይሆናል፡፡

6.2.11 የተፅዕኖ ማቅለያ እርምጃዎች


1) በፕሮጀክት ትግበራ ወቅት ጉዳት የሚያስከትሉ የፕሮጀክቱን ተግባራት ሙሉ በሙሉ ማስወገድ ቀዳሚ አማራጭ
ተደርጎ መወሰድ አለበት፡፡
2) ከላይ በተራ ቁጥር አንድ ላይ የተጠቀሰውን ማድረግ ካልተቻለ ግን ለእያንዳንዱ ጉልህ ተፅእኖ የሚተገበሩ የተጽዕኖ
ማቅለያ እርምጃዎች በአግባቡ ሊዘረዘሩ ይገባል፡፡

13
3) የተለያዩ የማቃለያ እርምጃዎችን በመለየትና በማደራጀት ከተዘረዘሩት አማራጮች ውስጥ ምክንያታዊ በመሆን
የተሻሉ የማቅለያ እርምጃዎችን በመምረጥ ማሳየት ያስፈልጋል፡፡
4) አዎንታዊ ተፅእኖዎችንም እንዴት የበለጠ ማሳደግ ወይም ማሻሻል እንደሚቻል በዚህ ክፍል መገለጽ አለበት፡፡

6.2.12 የአካባቢ አያያዝ ዕቅድ


1) የተፅዕኖ ማቃለያ መፍትሄዎች በአግባቡ የተመላከቱበት የአካባቢ አያያዝ ዕቅድ ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡ የአካባቢ
አያያዝ ዕቅዱም ሊይዛቸው የሚገባ ነጥቦች የተጽእኖዎች ዝርዝር፣ ለእያንዳንዱ ተጽእኖ የታቀዱ የተጽእኖ ማቅለያ
ተግባራት ዝርዝር፣ የታቀዱ የተጽእኖ ማቅለያ ተግባራት መለኪያ፣ የታቀዱ የተጽእኖ ማቅለያ ተግባራት መጠን፣
ለእያንዳንዱ ተጽእኖ ማቅለያ ተግባራት የተመደበ ገንዘብ መጠን፣ የታቀዱ የተጽእኖ ማቅለያ ተግባራት
የሚተገበሩበት የጊዜ ሰሌዳ፣ የታቀዱ የተጽእኖ ማቅለያ ተግባራትን የሚፈፅሙ አካላት ዝርዝር መሆን አለበት፡፡
2) የአካባቢ አያያዝ እቅድ ፎርማት በእዝል 15.1 የተያያዘ ሲሆን የሚዘጋጀው የአያያዝ እቅድ ከላይ በቀተራ ቁጥር አንድ
የተጠቀሱትን ዝርዝር መረጃዎች መያዝ ይኖርበታል፡
3) የፕሮጀክቱ መተግበርን ተከትሎ በአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርቱ ላይ የተመላከቱ የአካባቢ ተፅዕኖ ማቃለያ
ተግባራት ከፕሮጀክቱ ስራ ጎን ለጎኖን በአካባቢ አያያዝ ዕቅዱ መሰረት መተግበር አለባቸው፡፡
4) የአካባቢ አያያዝ ዕቅዱ ሲዘጋጅ የፕሮጀክቱን ቅድመ ግንባታ፤ ግንባታ፤ ትግበራና መዝጊያ ወቅት ታሳቢ ያደረገ መሆን
ይገባዋል፡፡
6.2.13 የአካባቢ ክትትል ዕቅድ
1) ይህ ክፍል የተጽእኖ ማቃለያ ተግባራት በአግባቡ መከናወናቸውን ለማረጋገጥ የሚዘጋጅ የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገም
ሰነድ አካል ነው፡፡ የአካባቢ ክትትል እቅዱ ፎርማት በእዝል 15.2 ቀርቧል፡፡
2) ይህ እቅድ ክትትል የሚደረግባቸው የማቃለያ ተግባራት ዝርዝር፣ ክትትሉን የሚያደርገው ተቋም፣ ተቋሙ የክትትል
ስራውን ለማከናወን የሚጠቀምባቸው ዘዴዎች፣ የተግባራት አመላካቾችና ጥቅም ላይ የሚዉሉ ደረጃዎች
(ስታንዳርድ) ወይም የአሰራር መመሪያዎች እና የድርጊት መርሃ ግብር መያዝ አለበት፡፡
3) ይህ ዕቅድ በተመሳሳይ ለአካባቢ ምርመራና ቁጥጥር ዕቅድ ሆኖ ሊያገለግል ይችላል፡፡
6.2.14 በፕሮጀክቱ ተፅዕኖ የሚደርስባቸውንና የሚመለከታቸውን አካላት ስለማወያየት

የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ሪፖርት ለማዘጋጀት መካሄድ ካለባቸው ተግባራት መካከል በፕሮጀክቱ ትግበራ ተጽእኖ
የሚደርስባቸውና የሚመለከታቸው አካላት በጥናት ሂደቱ ውስጥ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ማወያየት ሲሆን በተለይም
በወሰን ልየታና በረቂቅ የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት ሪፖርቱ ላይ የሚካሄዱ ውይይቶች ወሳኝ ናቸው፡፡
1) በረቂቅ ሰነዱ ላይ ውይይት ሲደረግ በፕሮጀክቱ ተጎጂ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ወይም የሚመለከታቸው አካላት፣
በየደረጃው ያሉ የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤቶችና አጋር አካላት መገኘት ይኖርባቸዋል፡፡
2) ፕሮጀክቱ በሚተገበርበት ቀበሌ/ወረዳ ውስጥ ያሉ አመራሮች፣ ፕሮጀክቱ የሚተገበርበት ጎጥ መሪዎች፣
የሴቶች/የወጣቶች ተወካዮች፣ በፕሮጀክቱ ምክንያት በቀጥታ ጉዳት የሚደርስባቸዉ የህብረተሰብ ክፍሎች መሳተፍ
አለባቸዉ፡፡

14
3) የውይይት ተሳታፊዎች በአበይት ተጽዕኖዎች፣ በማቃለያ እርምጃዎችና በአካባቢ አያያዝ ዕቅዱ ትግበራ ላይ በዝርዝር
መወያየትና ስምምነት ላይ መድረስ አለባቸዉ፡፡ ውሳኔ ላይ የማይደረስ ከሆነ የሚመለከተው የመንግስት አካል/ተቋም
የውሳኔ ሃሳብ የያዘ ሰነድ መቅረብ አለበት፡፡
4) ሀሰተኛ የማህበረሰብ ውይይት ማስረጃ አያያዞ የሚያቀርብ አማካሪ ድርጅት (የፕሮጀክት ባለቤት) ሰነዱ ሀሰተኛ
መሆኑ ከተረጋገጠ በማንኛውም ጊዜ አግባብ ባለው ህግ መሰረት ተጠያቂ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የተሰጠው
የአካባቢ ይሁንታ ፍቃድ ወዲያውኑ የሚሰረዝ ይሆናል፡፡
5) የተካሄደው ውይይት ሪፖርትም ውይይቱ የተካሄደበት ጊዜ፣ በውይይቱ የተገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ከለር
ፎቶግራፎች፣ እንዳስፈላጊነቱ የድምጽና የተንቀሳቃሽ ምስል፣ ውይይቱ የተካሄደበት መንገድ ወይም ዘዴ፣ በውይይቱ
የተነሱ ስጋቶች/ጥያቄዎች እና የተሰጡ ምላሾች እንዲሁም የማህበረሰቡ የስምምነት ሁኔታ፣ የሚመለከታቸው
ተሳታፊዎች ስም ዝርዝርና ፊርማ የያዘና ፕሮጀክቱ በሚተገበርበት ወረዳ የአካባቢ ጥበቃ ተቋም ኃላፊ የተፈረመና
በማህተም የተረጋገጠ የውይይቱ ቃለ ጉባኤ የያዘ መሆን አለበት፡፡
6) ለማህበረሰብ ውይይት የሚያስፈልገው ወጭ በባለሀብቱ/በአማካሪ ድርጅቱ የሚሸፈን ይሆናል፡፡
6.2.15 ማጠቃለያና ምክረ-ሃሳብ
1) ይህ ክፍል ውሳኔ ለመስጠት የሚያስችሉ ዋና ዋና ጉዳዮችን በአጭሩ ለማስገንዘብ የሚረዳ ሆኖ መዘጋጀት አለበት፡፡
2) በዚህ ክፍል እንዲተገበሩ የተመረጡ አማራጮችና የተመረጡበት ምክንያት በዝርዝር መገለፅ ይኖርበታል፡፡
3) ሊወገዱ የማይችሉ አሉታዊ ተፅኖዎችን ለማካካስ ወይም ተያያዥ የሆኑ ስጋቶችን ለመቀነስ የምንጠቀማቸውን
ስልቶች በዝርዝር ማሳየት ይጠበቅበታል፡፡
4) በዚህ ክፍል የቁልፍ ጉዳዮች ግልጽ ማብራሪያ፣ ጉልህ የሆኑ አሉታዊ ተፅእኖዎችን ለመቀነስ ወይም ለማካካስ
የሚወሰዱ እርምጃዎች፣ አዎንታዊና አሉታዊ ተፅእኖዎችን በማመዛዘን የፕሮጀክቱን አዋጭነት፣ ሊተኩ የማይችሉ
የአካባቢ ሃብቶችን የሚጠቀም/ የሚያጠፋ መሆኑና አለመሆኑ፣ ለክትትልና ቁጥጥር ስራዎች የሚያስፈልጉ የህግ
ማዕቀፎችና ሌሎች ወሳኝ የሆኑ ሃሳቦች መረጃዎች ማካተት አለበት፡፡
6.2.16 ዋቢ መፃህፍት/ማጣቀሻዎች

ይህ ክፍል በሪፖርቱ ውስጥ የተጠቀምንባቸውን መጻህፍቶች፣ የጥናት ሪፖርቶች፣ ድረ-ገፆች ወዘተ.. የሚገለጽበት ክፍል
ነው፡፡ ለመረጃነት ጥቅም ላይ የዋሉ የማጣቀሻ ምንጮች ዓለም አቀፍ የአፃፃፍ ስልቶችን በመጠቀም በፅሁፎች ውስጥና
በመጨረሻም ራሱን ችሎ በዚህ ክፍል መቀመጥ ይኖርበታል፡፡

6.2.17 እዝሎች

በዚህ ክፍል የሚያያዙት መረጃዎች ለገምጋሚው አካል እንደማጣቀሻነት የሚያገለግሉ ስለሆኑ ተለይተው በዋናው የጥናት
ዘገባ ሰነድ መጨረሻ ላይ ይያያዛሉ፡፡ እነዚህ ሰነዶች ገምጋሚው አካል ትክክለኛ ውሳኔ ላይ እንዲደርስ የሚያስችሉ
ናቸው፡፡ በእዝል ላይ መያያዝ የሚገባቸው መረጃዎች፤
1) ከሚመለከታቸው የአካባቢ ጥበቃ መ/ቤቶች ወይም ከአካባቢው አስተዳደሮች የተሰጡ የድጋፍ ደብዳቤዎች፣
2) ፕሮጀክቱ የሚተገበርበትን ቦታ የይዞታ ማረጋጫ ሰነድና የቦታው ካርታ፣
3) የደህንነት ወይም የምርት ጥራት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት፣ የጤና እና የምርት ጥራት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት
(ካስፈለገ)፣
15
4) ጥልቀት ያላቸው ቴክኒካል ሪፖርቶች፣ አመላካች ቻርቶች፣
5) የተካሄዱ የማህበረሰብ ውይይቶችን የሚገልጹና የፀደቁ ቃለ-ጉባኤዎች፣ በውይይት የተሳተፉ ሰዎች ከለር
ፎቶግራፎች፣
6) የጥናት ቡድኑ አባላት ዝርዝር መረጃ (ስም፣ ግለ-ታሪክ፣ ወዘተ)፣
7) ጥናቱን ያካሄደው አማካሪ ድርጅት የታደሱ የሙያና ንግድ ፈቃዶች፣
8) የፕሮጀክቱ ባለቤት ስለ ጥናት ሰነዱ ትክክለኛነት የሰጠው ማረጋገጫ፣
9) በቀረበው የመጀመሪያ ረቂቅ የተጽዕኖ ጥናት ዘገባ ላይ በገምጋሚ ባለሙያዎች የተሰጡ አስተያየቶች ቅጅ እና
ሌሎችም ካሉ ሊያያዙ ይገባል፡፡
6.2.18 የነባር ፕሮጀክት የአካባቢ አያያዝ ሰነድ ዝግጅት
1) በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 6.1 እስከ 6.17 የተዘረዘሩት የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርት ዝግጅት ቅደም
ተከተሎች በሙሉ ለአካባቢ አያያዝ ሰነድ ዝግጅት የሚያገለግሉ ይሆናሉ፡፡
2) የአካባቢ አያያዝ ሰነድ የሚዘጋጀው ወደፊት የሚፈጠሩ ችግሮችን (ተጽዕኖዎችን) በመተንበይ ብቻ ሳይሆን በአካባቢ
ተጽዕኖ ግምገማ ትንተና ወቅት በተጨባጭ እየተከሰቱ ያሉትን ችግሮችና የችግሮችን የተጽዕኖ ደረጃ በመለየትና
የማቃለያ እርምጃ በማዘጋጀት ይሆናል፡፡
3) የአካባቢ አያያዝ ሰነዱ ሲዘጋጅ ከሌሎች መረጃዎች በተጨማሪ የአካባቢ ምርመራ በማካሄድና የምርመራ ሪፖርቱን
በግብዓትነት በመጠቀም ይሆናል፡፡
7 የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርትን ስለመገምገምና ውሳኔ ስለመስጠት
1) የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርት ግምገማ ዓላማ በጸደቀው የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት ወሰን ልየታ መሰረት
መካሄዱን፣ የማህበረሰቡ አስተያየት መካተቱን፣ ውሳኔ ለመስጠት የሚያስችል በቂና የተሟላ መረጃ የያዘ መሆኑን
ለማረጋገጥ እና በሰነዱ ውስጥ ያሉ ክፍተቶችን (ጉድለቶችን) ለመለየት ይሆናል፡፡
2) በግምገማው ወቅት በሪፖርቱ ዋና ዋና ክፍሎች፣ ትክክለኛና ተቀባይነት ያላቸው መረጃዎች፣ የአወንታዊና አሉታዊ
ተጽእኖዎች ልየታና ትንተና፣ ለአሉታዊ ተጽእኖዎች የማቃለያ እርምጃዎች መካተታቸውንና መረጃው ለውሳኔ ሰጭ
አካላትና ለሚመለከታቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ግልጽና በቀላሉ የሚረዱት መሆኑን ማረጋገጥ ይገባል፣
3) ፕሮጀክቱ ተግባራዊ ባይሆን የሚለዉን ጨምሮ ያሉ የተለያዩ የትግበራ አማራጮች በአግባቡ መዳሰሳቸውን ና
አማራጮችን በንጽጽር ለማየት የተጠቀሙባቸው መመዘኛዎች ለሁሉም አማራጮች በእኩል ክብደት የተሰጣቸው
መሆኑን፣ በአንጻራዊነት ተስማሚ የሆነዉ አማራጭ መመረጡንና የተመረጠበትም ምክንያት በአግባቡ መገለጹን
ማረጋገጥ ይገባል፣
4) ጉዳት ሊደርስባቸዉ ይችላል ተብሎ የሚገመቱና በፕሮጀክቱ ላይ አስተያየት ለመስጠት ፍላጎቱ ያላቸዉ አካላት
በአግባቡ መሳተፋቸዉን የሚገልጽ ማስረጃ መካተቱን፣
5) የአካባቢ አያያዝና ክትትል እቅዶች ሊለኩ የሚችሉ፣ የሚያስፈልጋቸው ወጪ፣ ጊዜና ስራዎችን የሚያከናውን ተቋም
(አካል) በሪፖርቱ ዉስጥ መካተቱን፣
6) የሚቀርበው የጥናት ሪፖርት የታደሰ የንግድ እና የአማካሪነት ፈቃድ፤ የጥናት ቡድኑ የባለሙያዎች ስብጥር፣ የሙያ
ዘርፍና ግለ-ታሪክ፣ በጥናቱ ስለመሳተፋቸው የማረጋገጫ ሰነድ፣ በፎቶግራፍ የተደገፈ የማህበረሰብ ውይይት
ቃለጉባኤ፣ የአካባቢው የመንግስት አካል ስለፕሮጀክቱ ትግበራ የተስማማበት የድጋፍ ደብዳቤ፣ የፕሮጀክት ባለቤትና

16
የአማካሪ ድርጅቱ ማህተም በእያንዳንዱ ገፅ ላይ ያረፈበት መሆኑን፣ የይሁንታ ፈቃድ ይሰጠኝ ከሚለው ማመልከቻ
ላይ የፕሮጀክት ባለቤቱ ወይም የተወካዩ ፊርማና ማህተም ያለበት መሆኑን ማረጋገጥ ይገባል፣
7) የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርቱን ለመገምገም በአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት ባሉ ባለሙያዎች ብቻ መገምገሙ በቂ
ነው ብሎ ካልታመነበት የተቋሙ የበላይ ሀላፊ ሰነዱ በዩኒቨርሲቲዎች፣ በምርምር ተቋማትና በሌሎች
የሚመለከታቸው ተቋማት እንዲገመገም ሊያዝዝ ይችላል፡፡
8) የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ባለሙያዉ (የባለሙያዎች ቡድኑ) በእዝል 15.3 በሰንጠረዥ ስር በተዘረዘሩት
የመገምገሚያ ነጥቦች መሰረት ሪፖርቱን በመገምገም የፕሮጀክቱን ትግበራ የውሳኔ አስተያየት ለሚመለከተው ኃላፊ
ያቀርባል፡፡
9) በዕዝል 15.3 የቀረበውን የመገምገሚያ መስፈርት በመጠቀም የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርቱ ተገምግሞ ነጥብ
ይሰጠዋል፡፡ የነጥቡ ክብደት አጠቃላይ 100 ፐርሰንት ሲሆን በሰነዱ ውስጥ አስፈላጊ መረጃዎች ስለመኖራቸው
ከ 56% እና ሰነዱ ለያዛቸው መረጃዎች በቂነት ከ 44% ነጥብ ይሰጣል፡፡
10) በሰነድ ግምገማው የተገኘው ነጥብ አጠቃላይ ውጤቱ 70 ፐርሰንት ወይም በላይ ከሆነ የአካባቢ ይሁንታ
ሰርተፊኬት ተዘጋጅቶ ይሰጠዋል፡፡ ሆኖም ግን የሰነዱ ጥራት 70 ፐርሰንት ወይም በላይ ሆኖ ሰነዱ ወሳኝ የሆኑ
ጉዳዮች ከጎደሉት ይሁንታ ፈቃድ አይሰጠውም፡፡ በመሆኑም ጉድለቱን እንዲያስተካክል አስተያየት ይሰጠዋል፡፡
ለባለሃብቱ የሚሰጠው የይሁንታ ፈቃድ በኋላ ገጽ ላይ በዕዝል 15.9 የተዘረዘሩትን የውል ስምምነቶችን ያካተተ
ይሆናል፡፡
11) አንድ ሰነድ ተገምግሞ የተሰጠው ነጥብ በ 50 እና በ 70 ፐርሰንት መካከል ከሆነ ሰነዱ እንደገና ተስተካክሎ
እንዲቀርብ ነጥብ የተሰጠበትን መገምገሚያ ቅፅ አባሪ በማድረግ በገምጋሚ ባለሙያዎች ለፕሮጀክት ባለቤቱና
ለአማካሪ ድርጅቱ በደብዳቤ ይገለጽላቸወል፡፡
12) የግምገማ ነጥቡ ከ 50 ፐርሰንት በታች ከሆነ የቀረበው ዘገባ ተቀባይነት የሌለው ወይም ጥራት የጎደለው በመሆኑ
በሌላ አማካሪ ድርጅት ተዘጋጅቶ እንደገና እንዲቀርብ በመግለፅ ነጥብ የተሞላበትን የመገምገሚያ ቅፅ አባሪ
በማድረግ በደብዳቤ ለፕሮጀክት ባለቤቱ ይገለጽለታል፡፡
13) በየደረጃዉ ያሉ የአካባቢ ጥበቃ ባለሙያዎች የቀረበላቸውን የአካባቢ ተፅእኖ ግምገማ ሪፖርት በተራ ቁጥር ሶስት
መሰረት በአንድ ሳምንት ውስጥ መርምረው ለውሳኔ ሰጭ አካል የውሳኔ አስተያየት ማቅረብ አለባቸው፡፡ ነገር ግን
ፕሮጀክቱ በጣም ጉልህ የሆኑ ችግሮችን የሚያስከትል ከሆነ ምላሽ የሚሰጥበት ቀን ከ 10 ቀን መብለጥ የለበትም፡፡
14) የባለሙያው የቅርብ ኃላፊ በቀረበለት የውሳኔ አስተያየት መሰረት በሁለት ቀን ውስጥ ለፕሮጀክት ባለቤቱ ውሳኔውን
ማሳወቅ አለበት፡፡ ውሳኔዎቹም ፕሮጀክቱን በማጽደቅ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ሰርተፊኬት መስጠት፣ ከቅድመ
ሁኔታ ጋር ሰርተፊኬት መስጠት፣ ድጋሜ ተስካክሎ እንዲቀርብ እና ፕሮጀክቱን የመሰረዝ ይሆናሉ፡፡
15) በተሰጠው ውሳኔ ያልረካ የፕሮጀክት ባለቤት ቅሬታውን በክልልና በዞን ደረጃ ለሚገኙ ፕሮጀክቶች ለባለስልጣኑ
የበላይ ኃላፊ፤ በወረዳ ደረጃ ለሚገኙ ፕሮጀከቶች ቅሬታውን ለዞን መምሪያ ኃላፊው ማቅረብ ይችላል፡፡
16) ከወረዳዎች ቅሬታ የቀረበለት የዞን አካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት ኃላፊ በዞን ደረጃ ባሉ ባለሙያዎች ፕሮጀክቱ
በድጋሜ እንዲገምና የውሳኔ ሃሳብ እንዲቀርብለት ያደርጋል፡፡ በቀረበለት ውሳኔ ተመስርቶ ኃላፊው ውሳኔ መስጠት
አለበት፡፡

17
17) ከዞኖች ቅሬታ የቀረበለት የክልል የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ኃላፊ በክልል ደረጃ ባሉ ባለሙያዎች ፕሮጀክቱ
በድጋሜ እንዲገምና የውሳኔ ሃሳብ እንዲቀርብለት ያደርጋል፡፡ በቀረበለት ውሳኔ ተመስርቶ ኃላፊው ውሳኔ መስጠት
አለበት፡፡
18) በክልል ደረጃ ለባለስልጣኑ ለአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ዳይሬክቶሬት ቀርቦ በተሰጠው ውሳኔ ላይ ቅሬታ
ያለው የፕሮጀክት ባለቤት ቅሬታውን ለባለስልጣኑ የበላይ ኃላፊ ማቅረብ አለበት፡፡ ቅሬታ የቀረበለት የባለስልጣኑ
የበላይ ኃላፊ ከዩኒቨርስቲዎች፣ ከምርምር ተቋማትና ከሙያው ጋር ቀረቤታ ካላቸው አካላት የተውጣጣ
የባለሙያዎች ቡድን በማቋቋም ሰነዱን በማስመርመር በሚቀርበው ምክረ ሃሳብ መሰረት የመጨረሻ ውሳኔ
ይሰጣል፡፡
19) የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርት የያዘው መረጃ በቂና ትክክለኛ መሆኑን ሳያረጋገጥ የይሁንታ ፈቃድ እንዲሰጠው
የውሳኔ ሀሳብ ያቀረበ ባለሙያ ወይም በመስክ መረጋገጥ ያለባቸውን መረጃዎች በአግባቡ ሳያረጋግጥ መተግበር
በሌለበት ቦታ ላይ እንዲተገበር የውሳኔ አስተያየት ያቀረበ ባለሙያ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድበት ወይም
በዲሲፕሊን መመሪያ እንዲጠየቅ ይደረጋል፡፡
20) አግባብ ባልሆነ መንገድ የይሁንታ ፈቃድ የሰጠ ወይም የከለከለ ኃላፊ በዲሲፕሊን መመሪያ ይጠየቃል፡፡
8 የአካባቢ የይሁንታ ፈቃድ ስለመከልከል
1) አንድ ፕሮጀክት ቢተገበር የሚያስከትለው አሉታዊ ተጽዕኖ ከፍተኛ ከሆነና ተጽዕኖውን በአጥጋቢ ሆኔታ ማስቀረት
የማይቻል ከሆነ ወይም ተጽዕኖውን ለማስቀረት እንደማይቻል ከታመነ፣
2) የማይጣጣሙ ፕሮጀክቶች ጎን ለጎን ተግባራዊ እንዲሆኑ የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርት የቀረበ ከሆነና በኋላ
የቀረበዉ ፕሮጀክት ቀድሞ ከቀረቡት ፕሮጀክቶች ጋር የማይጣጣም ከሆነ የማይጣጣምበትን አሉታዊ ተጽዕኖዎች
በመግለፅ ለፕሮጀክት ባለቤቱ ሌላ አማራጭ ቦታ እንዲፈልግ (የፕሮጀክቱን አይነት እንዲለውጥ) በደብዳቤ
የሚገለፅለት ሲሆን ፕሮጀክቱ በማይጣጣምበት ቦታ እንዳይተገበር ይከለከላል፣
3) አዲስ በቀረበው ፕሮጀክት ምክንያት ተዳማሪ ተጽዕኖ በጣም ከፍተኛ ከሆነና አካባቢው ተጽዕኖውን መሸከም
የማይችል ከሆነ፣
4) ፕሮጀክቱ ሊተገበር በታቀደበት ቦታ ወይም አካባቢ ላይ በማህበረሰቡ ዘንድ ፕሮጀክቱ እንዳይተገበር ከፍተኛ
ተቃውሞ ከገጠመና የተቃውሞው ትክክለኛት ከታመነበት አለመግባባቱ የተፈጠረበት ጉዳይ እልባት እስኪያገኝ
ድረስ፣
5) ፕሮጀክቱ ሊተገበር የታሰበበት ቦታ በተለያዩ አካላት የይገባኛል ጥያቄ ውዝግብ ያለበት ከሆነና ውዝግቡ እስከሚፈታ
ድረስ፣
6) ክልላዊና ሀገራዊ ቅርሶችን፣ ጥብቅ ቦታዎችን፣ ሃይማኖታዊና ባህላዊ ቦታዎችን፣ ታሪካዊ ሃብቶችን፣ እንዲሁም ሌሎች
በቀላሉ ለጉዳት ተጋላጭ የሆኑ ቦታዎችን ፕሮጀክቱ በቀጥታ ጉዳት የሚያደርስ ከሆነና አማራጭ የማይገኝለት ከሆነ፣
7) ፕሮጀክቱ የሚጠቀምባቸው ቴክኖሎጂዎች በአካባቢ ጥበቃ ህጎች የተቀመጡትን የልቀት ደረጃዎች ሊያሟሉ
የማይችሉ ከሆኑና ፕሮጀክቱ ከፍተኛ ልቀት የሚያስከትል ሆኖ ሲገኝ እንዲሁም የተከለከሉ ግብዓቶችን የሚጠቀም
ከሆነ፣
8) ማንኛውም የልማት ትብብር ፕሮጀክት (ለምሳሌ በአለም ባንክ በጀት ድጋፍ የሚደገፍ ፕሮጀክት) ከለጋሽ ድርጅቶች
ፖሊሲ ወይም የህግ ማዕቀፎች ጋር የሚቃረን ወይም በለጋሽ ድርጅቶች እንዲተገበር የማይፈቀድ ከሆነ፣

18
9 የተሰጠ የአካባቢ ይሁንታ ፈቃድ ስለመሰረዝ
1. የፕሮጀክቱ ባለቤት ፕሮጀክቱን የሚተገብረው በተቀመጠዉ የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርት ወይም
የአካባቢ አያያዝ ሰነድ መሰረት መሆኑን ለማረጋገጥ በየደረጃው ያለ የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት በኩል
ክትትል፣ ምርመራና ቁጥጥር ማድረግ አለበት፡፡

2. የፕሮጀክቱ ባለቤት ፕሮጀክቱን በፀደቀው የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርት ወይም የአካባቢ አያያዝ
ሰነድ መሰረት ካልተገበረ በየደረጃው ያለ የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት ማስተካከል ያለበትን ማስተካከያ
እንዲፈፀም የጊዜ ገደብ በመግለጽ ማስጠንቀቂያ መስጠት አለበት፡፡ የጊዜ ገደቡ ግን ከ 6 ወራት
መብለጥ የለበትም፡፡

3. የኘሮጀክቱ ባለቤት በተሰጠው የጊዜ ገደብ መሠረት ችግሮቹን የማያስተካክል ከሆነ በየደረጃው ያሉ
የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት የሰጡትን ይሁንታ ፈቃድ የማገድ ወይም የመሠረዝ ስልጣን አላቸው፡፡

4. ከላይ በተራ ቁጥር ሶስት የተመለከተውን ውሳኔ ተከትሎ ሌሎችም ፈቃድ ሰጭ መስሪያ ቤቶች
ለኘሮጀክቱ ትግበራ የሰጡትን የስራ ፈቃድ ይህን ውሣኔ ተከትሎ ማገድ ወይም መሠረዝ አለባቸው፡፡

5. የፕሮጀክት ባለቤቱ ባቀረበው ጥናት መሰረት የአካባቢ አያያዝ ዕቅዱን ስለመተግበሩ በዓመት አንድ ጊዜ
በየደረጃው ላለ የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት ሪፖርት ማቅረብ አለበት (የሪፖርት ማድረጊያ ቅፁ
በዕዝል 15.4 ተያይዟል)፡፡

6. ከላይ በተራ ቁጥር አምስት በተገለጸው መሰረት የአካባቢ አያያዝ ዕቅድ ትግበራውን በወቅቱ ሪፖርት
የማያደርግ ከሆነ ደረጃውን የጠበቀ ማስጠንቀቂያ ይሰጠዋል፡፡

7. ያለበቂ ምክንያት በተከታታይ ለሁለት ዓመታት ለሚመለከተው የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት


የአፈጻጸም ሪፖርት ካላቀረበ በየደረጃው ያለ የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት የሰጠውን የይሁንታ
ሰርተፊኬት ያግዳል ወይም ይሰርዛል፡፡

10 የአካባቢ ይሁንታ ፈቃድ የአገልግሎት ክፍያ ታሪፍ

በአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ አዋጆች ቁጥር 181/2003 አንቀጽ 9/4 መሰረት የፕሮጀክት ባለቤቶች ሙሉ የአካባቢ ተጽዕኖ
ወጭዎችን የመሸፈን ግደታ ያለባቸው ቢሆንም ለጊዜው በተወሰነ ደረጃ የይሁንታ ፈቃድ ለማግኘት የአገልግሎት ወጭ
እንዲሸፍኑ በዚህ መመሪያ ተደንግጓል፡፡
1. የፕሮጀክቶች የይሁንታ ፈቃድ ለመስጠት የአገልግሎት ክፍያው የፕሮጀክቶችን የተፅዕኖ ምድብ መሰረት ያደረገ
መሆን አለበት፡፡
2. ክፍያ የሚከፈልባቸው የአገልግሎት አይነቶችና የክፍያ መጠን ቀጥሎ በቀረበው ሰንጠረዥ መሰረት የሚፈጸም
ይሆናል፡፡
3. የይሁንታ ፈቃድ ከመሰጠቱ በፊት የአገልግሎት ክፍያ የተፈጸመበት ደረሰኝ ፎቶ ኮፒ ከውሳኔ አስተያየት ሪፖርቱ ጋር
ተያይዞ መቅረብ ይኖርበታል፡፡

19
ሰንጠረዥ 1: የአካባቢ ይሁንታ ፈቃድ ለመስጠት፣ ለማደስ ወይም ለመተካት የሚከፈል የአገልግሎት ክፍያ
ተ/ቁ የአገልግሎት አይነት መለኪያ የአገልግሎት ክፍያ በፕሮጀክት
ምድብ
የክልል የዞን የወረዳ
1 አዲስ ይሁንታ ፈቃድ መስጠት ብር 1000 500 250
2 በወቅቱ ለቀረበ የእድሳት ጥያቄ ብር 500 250 150
3 በልዩ ልዩ ሁኔታ የጠፋና የተበላሸ የይሁንታ ፈቃድ ለመተካት (በወቅቱ ለቀረበ) ብር 600 400 200

4 በወቅቱ ላልቀረበ የእድሳት ጥያቄ (የእድሳት ጊዜው ከ 6 ወራት በላይ ካላለፈ) ብር 600 400 200

5 በወቅቱ ላልቀረበ የእድሳት ጥያቄ (የእድሳት ጊዜው ከ 1 አመት በላይ ካላለፈ) ብር 1000 500 300

6 በወቅቱ ላልቀረበ የእድሳት ጥያቄ (የእድሳት ጊዜው ከ 2 አመት በላይ ካላለፈ) ብር 1200 700 400

7 የጠፋና የተበላሸ የፕሮጀክት የይሁንት ፈቃድ መተካት (የእድሳት ጊዜው ከ 6 ወራት ብር 1000 500 300
በላይ ካላለፈ)
8 የጠፋና የተበላሸ የፕሮጀክት የይሁንታ ፈቃድ መተካት (የእድሳት ጊዜው ከ 1 ዓመት ብር 1200 700 500
በላይ ካላለፈ)
9 የጠፋና የተበላሸ የፕሮጀክት የይሁንታ ፈቃድ መተካት (የእድሳት ጊዜው ከ 2 ዓመት ብር 1400 900 700
በላይ ካላለፈ)
10 በወቅቱ ላልቀረበ የይተካልኝና የእድሳት ጥያቄ (የእድሳት ጊዜው ከ 2 እስከ 3 አመት ቀድሞ ያስጠናውን የተጽዕኖ ግምገማ
ጊዜ ውስጥ ከቀረበ ሪፖርት እንደገና በአማካሪ ድርጅት ተከልሶ
ሲቀርብ በተራ ቁጥር 9 የተጠቀሰውን ከፍለው

4. የክልሉ መንግስት ከሌሎች ለጋሽ ድርጅቶች ጋር በተደረገ ስምምነት የሚተገበሩ የልማት ፕሮጀክቶች የአካባቢ
ይሁንታ ፈቃድ ለማግኘት የአገልግሎት ክፍያ የመክል ግዴታ የለበቸውም፡፡ ሆኖም ግን አስፈፃሚ ተቋማት በለጋሽ
ድርጅቶች ስምምነት መሰረት ለፕሮጀክቶች ድጋፍና ክትትል ለማድረግ የሚያስልገውን በጀት መመደብ አለባቸው፡፡
5. በሠንጠረዡ ላይ የተመላከተው የአገልግሎት ክፍያ እንደ ወቅቱ ሁኔታ ሊሻሻል ይችላል፡፡
11 የአካባቢ ህግ ማስከበር ግብረ-ሀይል ስለማቋቋም
1) አብዛኞች የልማት ፕሮጀክቶች አደገኛ ቆሻሻቸውን በቀጥታ ወደ አካባቢ በመልቀቃቸው የተነሳ በምግብ ስራዓተ
ሰንሰለት፣ በስርዓተ-ምህዳርና በሰዎች ላይ የማይቀለበስ ውስብስብ ችግር እያስከተለ ስለሆነ በአንቀጽ 8 ላይ
በተገለጸው አግባብ ተጽዕኖውን ማስወገድ ካልተቻለ በአካባቢ ህግ ማስከበር ግብረ ኃይል አማካይነት የአካባቢ ህግ
የማስከበር ስራ ይሰራል፡፡
2) ፋብሪካዎችና የአገልግሎት ሰጭ ተቋማት ደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻቸውን አክመውና የሀገሪቱን የቆሻሻ የልቀት ደረጃዎች
ጠብቀው ማስወገድ አለባቸው፡፡ ፕሮጀክቶች አካባቢን ከመበከል እንዲታቀቡ ተደጋጋሚ ድጋፍ ተደርጎላቸው
የአካባቢ ህግን ለማክበር ፈቃደኞች ካልሆኑ በየደረጃው ከተቋቋመው የአካባቢ ጥበቃ ግብረ ኃይል የአካባቢ ጥበቃ
መስሪያ ቤትን ውሳኔ ተግባራዊ እንዲሆን ድጋፍ ያደርጋል፡፡
3) ይህን አስተዳደራዊ እርምጃ (ውሳኔ) ተግባራዊ ለማድረግ በክልል፣ በዞንና በወረዳ ከሚመለከታቸው ተቋማት
የተዋቀረ የአካባቢ ህግ አስከባሪ ግብረ ኃይል በዚህ መመሪያ ተቋቁሟል፡፡ ግብረ-ኃይሉ በየደረጃው የሚከተሉትን
ተቋማት በአባልነት በመያዝ መቋቋም ይኖርበታል፡፡

የግብረ-ኃይሉ አባል የሚሆኑ መስሪያ ቤቶች አባልነት

20
የጠቅላይ አቃቤ ህግ መስሪያ ቤት ሰብሳቢ
ከፖሊስ ተቋም አባል
የጤና ጥበቃ መስሪያ ቤት አባል
የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መስሪያ ቤት አባል
የማዕድን ሀብት ልማት ማስፋፊያ መስሪያ ቤት አባል
የንግድና ገበያ ልማት መስሪያ ቤት አባል
የከተማ ልማት፣ ቤቶችና ኮንስትራክሽን መስሪያ ቤት አባል
የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት ጸሐፊና አባል ይሆናሉ
4) ግብረ ኃይሉ ከአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት በሚያቀርብለት የአካባቢ ብክለትና ብክነት የምርመራና ክትትል
ማስረጃዎች መሰረት በማድረግ ፕሮጀክቶችን እስከ መዝጋት ድረስ እርምጃ ይወስዳል፡፡

12 የአካባቢ አማካሪነት የሙያ ፈቃድ ስለመስጠት


12.1 የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርት የማዘጋጀት ስልጣን

1) በልዩ ሁኔታ ከመንግስት መስሪያ ቤት በተውጣጡ የባለሙያዎች ቡድን እንዲዘጋጁ ከሚፈቀድላቸው በለጋሽ
ድርጅቶች ድጋፍ ከሚተገበሩ አነስተኛ ፕሮጀክቶች ውጭ ማንኛውም ፕሮጀክት የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት
የሚዘጋጀዉ በዚህ መመሪያ ዉስጥ በዕዝል 15.5-15.7 የተዘረዘሩ መስፈርቶችን በሚያሟሉ ህጋዊ ፈቃድ ባላቸው
አማካሪ ድርጅቶች ብቻ ይሆናል፡፡
2) በዚህ መመሪያ በዕዝል 15.5-15.7 የተዘረዘሩ መስፈርቶችን የሚያሟሉ ዩኒቨርሲቲዎችና የምርምር ተቋማት
በማማከር አገልግሎት ሊሳተፉ ይችላሉ፡፡

12.2 ለአካባቢ አማካሪነት መሟላት የሚገባቸዉ መስፈርቶችና የሰርተፊኬት አሰጣጥ

1) ለአማካሪ ባለሙያዎችና ለአማካሪ ድርጅቶች የሙያ ፈቃድ የሚሰጠው ባለስልጣኑ ነው፡፡


2) አማካሪ ድርጅቶች የማማከር ፈቃድ የሚያገኙት ከባለስልጣኑ ይሆናል፤
3) አንድ አማካሪ ድርጅት የማማከር ፈቃድ ለማውጣት ሰባት የተለያዩ የሙያ ዘርፎችን ያካተቱ አማካሪ ባለሙያዎችን
መያዝ አለበት፣
4) አማካሪ ድርጅቱ የታደሰ የማማከርና የንግድ ስራ ፈቃድ ሊኖረው ይገባል፣ እድሳቱ በየሁለት አመቱ መካሄድ
ይኖርበታል፣
5) ባለሙያዎች ከባለስልጣኑ የተሰጠና የታደሰ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ማስረጃ ሊኖራቸው ይገባል፣
6) በአንድ የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርት ዝግጅት ላይ የሚሳተፉ ባለሙያዎች ቁጥር ቢያንስ አራት ባለሙያዎች
ሆኖ የአካባቢና ማህበራዊ ተንታኝ ባለሙያዎች የግድ ሊካቱ ይገባል፣
7) አንድ አማካሪ ድርጅት የራሱ የሆነ የተሟላ ቋሚ ጽ/ቤት፣ ስራ አስኪያጅ፤ ፀሐፊ ባለሙያ እንዲሁም የተሟላ
የመስክና የቢሮ መገልገያ ቁሳቁሶች ሊኖሩት ይገባል፤
8) ሁለት የተለያ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ማስረጃ የተሰጠው አንድ አማካሪ ባለሙያ በአንድ ድርጅት ውስጥ መደራጀት
የሚችለው በአንድ የሙያ ዘርፍ ብቻ ይሆናል፤
9) አንድ ባለሙያ ከሁለት አማካሪ ድርጅቶች በላይ አማካሪ ሆኖ እንዲሰራ ወይም እንዲደራጅ አይፈቀድም፡፡

21
10) አንድ በመንግስት ድርጅት ወይም በግል ተቋም ተቀጥሮ የሚሰራ ባለሙያ የማማከር ፍቃድ ለመግኘት ወይም
ለማሳደስ ከሚሰራበት ተቋም ጋር የጥቅም ግጭት የማይፈጥር መሆኑን ማረጋገጥ አለበት፡፡
11) በሁለቱም ደረጃዎች (ከፍተኛና ጀማሪ) የአካባቢ አማካሪ ድርጅት ስራ አስኪያጅ ለመሆን የከፍተኛ የብቃት
ማረጋገጫ ባለሙያነት ደረጃ ያስፈልጋል፣
12) ማንኛዉም የሙያ ብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ለማዉጣት የሚቀርብ አመልካች በቅድሚያ ባለስልጣኑ
ያዘጋጀዉን የምዝገባ ፎርም ሞልቶ ማቅረብ አለበት፡፡
13) የሙያ ብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ለሚያወጡ ባለሙያዎች ሁለት የቅርብ ጊዜ 3x4 መጠን ያለዉ ጉርድ
ፎቶ ግራፍ ማቅረብ አለባቸው፡፡
14) አዲስ የአካባቢ አማካሪነት ድርጅት ፈቃድ የምስክር ወረቀት እንዲሰጠው ጥያቄ ያቀረበ ድርጅት በባለስልጣኑ
መስሪያቤት የተሰጠና የታደሰ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት እንዲሁም የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ ከአንድ
ፎቶ ኮፒ ጋር ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
15) የምስክር ወረቀት እንዲሰጣቸው ጥያቄ ያቀረቡ የድርጅት ባለቤቶች ከአንድ ግለሰብ በላይ ከሆኑ ስልጣን ባለው
አካል የፀደቀ የድርጅት መመስረቻ ሰነድ፣ መተዳደሪያ ደንብ እና ማመልከቻውን ይዞ የቀረበው ሰው የውክልና
ማስረጃ ከአንድ ፎቶ ኮፒ ጋር ማቅረብ አለበት፡፡
16) ደረጃው እንዲሻሻል የጠየቀ አማካሪ ድርጅት በዚህ መመሪያ መሠረት ማሟላት ያለበት የባለሙያ ዓይነትና ብዛት
በዕዝል 15.7 የተገለጸ ሲሆን፤ የታደሰ የባለሙያዎች የቀበሌ መታወቂያ ከአንድ ፎቶ ኮፒ ጋር፣ የታደሰ የብቃት
ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ከአንድ ፎቶ ኮፒ ጋር እንዲሁም ከተቀጣሪ ባለሙያዎች ጋር የተደረገ የስራ ውል
ስምምነት ከአንድ ፎቶ ኮፒ ጋር ማቅረብ አለበት፤
17) አዲስ የአካባቢ አማካሪ ድርጅት ፈቃድ የምስክር ወረቀት እንዲሰጠው ጥያቄ ያቀረበ ድርጅት የመስሪያ ቢሮ ያለው
መሆኑን ማረጋገጫ ሰነድ ወይም ውል የማዋዋል ስልጣን ባለው አካል የተረጋገጠ ሕጋዊ የቤት ኪራይ ውል ከአንድ
ፎቶ ኮፒ ጋር እና የድርጅቱ ባለቤት ወይም የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ 3x4 የሆነ ሁለት ፎቶ ግራፍ ማቅረብ አለበት፡፡
የመስሪያ ቢሮው የድርጅት ባለቤቱ ከሆነ የድርጅት መስሪያ ቦታ የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ ማቅረብ አለበት፣
18) አዲስ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ለማውጣት የሚቀርብ ማመልከቻ የአመልካቹን ዋና የትምህርት
ማስረጃና የሥራ ልምድ ከአንድ ፎቶ ኮፒ ጋር አያይዞ ማቅረብ አለበት፣
19) በባለስልጣኑና በተዋረድ በሚገኝ የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት እየሰሩ ያሉ ባለሙያዎች የአሰራር ግጭት የሚፈጥር
በመሆኑ በአማካሪነት እንዲሰሩ አይፈቀድም፡፡ በአማካሪነት ለመስራት ተቋሙን መልቀቅ ግዴታ ነው፤
20) የአማካሪ ድርጅት ወይም የባለሙያ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ይሰጠኝ ማመልከቻ ለባለስልጣኑ ቀርቦ
ለባለሙያዎች በተመራ በ 4 ቀናት ውስጥ የማስረጃ ሰነዱ ተግምግሞ ለውሳኔ ይቀርባል፡፡ የሚቀርበው ማመልከቻ
በእዝል 15.8 ላይ በተያያዘው ቅጽ መሰረት የሚቀርብ ይሆናል፤
21) የቀረበው የማመለክቻ ሰነድ ከተመረመረ በኋላ ውጤቱ ላይ ኃላፊው ወይም ዳይሬክተሩ የፈረበት ውሳኔ
ማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ ለ 5 ቀናት ተለጥፎ እንዲቆይ ይደረጋል፤
22) የአማካሪ ድርጅቱ ወይም አመልካቹ ባለሙያ ያላሟላቸው ሰነዶች ካሉ በአምስት ቀናት እንዲያሟላ በውስጥ
ማስታወቂያ ይገለጻል፤ መስፈርቱን ላሟላ አመልካች ውሳኔ በተሰጠ በአምስት ቀናት ውስጥ የሙያ ፈቃድ (የብቃት
ማረጋገጫ ሰርተፊኬት) ይሰጠዋል፤
22
23) አንድ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ይሰጠኝ ብሎ የሚጠይቅ ጀማሪ ባለሙያ የአማካሪነት የምስክር ወረቀት
የሚሰጠው 50% እና በላይ ሲያገኝ ሆኖ 70% እና ከዚያ በላይ ውጤት ካገኘ የከፍተኛ ደረጃ ይሰጠዋል
(መስፈርቱን በዕዝል 15.5 ይመልከቱ)፤
24) አንድ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ይሰጠኝ ብሎ የሚጠይቅ ባለሙያ በአቀረበው ማስረጃ ማለፍ ካልቻለ
በድጋሜ ማመልከት የሚችልው ከስድስት ወር የቆይታ ጊዜ በኋላ ይሆናል፡፡ የተጭበረበረ ማስረጃ አያይዞ
የሚያቀርብ ባለሙያ ካለ የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት እንዳይሰጠው እገዳ ይደረግበታል፤
25) ለከፍተኛ እና ለጀማሪ የአካባቢ አማካሪ ድርጅት ፈቃድ ለማውጣት የሚያመለክቱ አካላት የአማካሪነት ፈቃድ
ለማግኘት በዚህ መመሪያ ዕዝል 15.7 ላይ የተገለጸውን ዝቅተኛ መስፈርት ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፤
26) አንድ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት የተሰጠው ባለሙያ ወይም ፍቃድ የተሰጠው አማካሪ ድርጅት የደረጃ
ይሻሻልልኝ ጥያቄ ማቅረብ የሚችለው ከአንድ ዓመት የቆይታ ጊዜ በኋላ ይሆናል፤
27) በባለስልጣን የሚሰጠው የማማከር የምስክር ወረቀት፡- የባለሙያውን (የድርጅቱን ሙሉ ስም)፣ የስራ አድራሻ፣
የማማከር አገልግሎት ዘርፍ፤ ደረጃ፣ የምስክር ወረቀቱ የተሰጠበት ቀን፣ የምስክር ወረቀቱ ፀንቶ የሚቆይበት የጊዜ
ገደብ፣ የስራ አስኪያጅ ፎቶ ግራፍ፣ መለያ ቁጥር፣ የፈቃድ ሰጪ መስሪያ ቤት ማኅተም መያዝ ይኖርበታል፤
28) የማማከር ፈቃድ ያመለከተ ድርጅትም ሆነ ባለሙያ በተሰጠው ውሳኔ ቅር ከተሰኘ ውሳኔው በተገለፀ በ 10 ቀናት
ውስጥ ቅሬታውን በጽሁፍ ለባለስልጣኑ ዋና ዳሬክተር ማቅረብ ይችላል፡፡ አመልካቹ በ 10 ቀናት ውስጥ ቅሬታውን
ካላቀረበ ውሳኔውን እንደተቀበለ ይቆጠራል፡፡ ቅሬታ የቀረበለት ኃላፊ በ 10 ቀናት ውስጥ ቅሬታውን መርምሮ ምላሽ
ይሰጣል፡፡ ኃላፊው ቅሬታውን መርምሮ በሰጠው ውሳኔ ላይ ቅር የተሰኘ አመልካች ቅሬታውን ለሚመለከተው አካል
የማቅረብ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

12.3 የማማከር ፈቃድ ለማውጣትና ለማሳደስ የአገልግሎት ክፍያ

1) የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ስርቲፊኬት ወይም የአማካሪ ድርጅት ፈቃድ የሚታደሰው በዚህ መመሪያና በአካባቢ ህጎች
የተካተቱ ህጎችና የሙያ ስነ ምግባሮች አፈጻጸም በምርመራ ከተረጋገጠ በኋላ ይሆናል፣
2) ባለሙያዎች አዲስ የሙያ ፈቃድ ለማዉጣት፣ ደረጃቸውን ለማሳደግና የጠፋባቸውን ሰርቲፊኬት በድጋሜ
ለማዉጣት ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) መክፈል አለባቸዉ፣
3) አዲስ የአማካሪ ድርጅት ፈቃድ ለማውጣት፣ የአማካሪ ድርጅት ደረጃ ለማሳደግና የጠፋን የድርጅት ፈቃድ በድጋሜ
ለማውጣት ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) መከፈል አለበት፤
4) የአማካሪ ድርጅት ፈቃድ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር)፤ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ደግሞ ብር 200.00 (ሁለት
መቶ ብር) በመክፈል በየሁለት ዓመቱ ይታደሳል፣
5) ሁለት የብቃት ማረጋገጫ ማስረጃ የሚጠይቁ ባለሙያዎችን ጥያቄያቸውን በአንድ ማመልከቻ ካቀረቡና በአንድ
ወቅት የብቃት ማረጋገጫ ከተሰጣቸው ተጨማሪ የአገልግሎት ክፍያ አይጠይቅም፡፡ በተለያየ ጊዜ የሚቀርብ
የተለያየ የብቃት ማረጋገጫ ይሰጠኝ ጥያቄ ከቀረበ ተጨማሪ የአገልግሎት ክፍያ እንዲከፍል ይደረጋል፤
6) የአማካሪ ድርጅት ፈቃድ ወይም የሙያ ብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ
ካልታደሰ በቀጣይ ሶስት ወራት ውስጥ ከአገልግሎት ክፍያ በተጨማሪ የቅጣት ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር)
እንዲከፍል በማድረግ እንዲታደስ ይደረጋል፡፡ በዚህ የጊዜ ገደብ ውሰጥ ሳይታደስ ከቀረ ለሚቀጥሉት ተጨማሪ
23
ሶስት ወራት 800.00 (ስምንት መቶ ብር) ቅጣት እንዲከፍል በማድረግ እንዲታደስ ይደረጋል፡፡ በዚህ የጊዜ ገደብ
ውስጥ ካልታደሰ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀቱ ወይም የአማካሪ ድርጅቱ ፈቃድ ለአንድ አመት
ይታገዳል፡፡

12.4 የአማካሪዎች ኃላፊነትና ኃላፊነትን ባለመወጣት ስለሚወሰዱ እርምጃዎች

1) አንድ የአካባቢ አማካሪ ድርጅት ባማካሪነት የቀጠራቸውን ባለሙያዎች ሙሉ ማስረጃ፣ በድርጅቱ ውስጥ ያላቸውን
ኃላፊነት መያዝ የሚኖርበት ሲሆን የባለሙያ ለውጥ ሲኖር ደግሞ ለዉጡን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለሚመለከተው
የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት ማሳወቅ ይኖርበታል፤
2) አንድ አማካሪ ድርጅት የሚያዘጋጃቸውን ከአስር አመት ያነሰ የቆይታ ጊዜ ያላቸውን የተጽዕኖ ጥናት ዘገባዎች በሙሉ
በመረጃ ቋት የማስቀመጥና በበጀት ዓመቱ ውስጥ ያዘጋጃቸውን የጥናት ሪፖርቶች ዝርዝር ለባለስልጣኑ የማድረግ
ግዴታ አለበት፡፡
3) የአማካሪ ድርጅት ፈቃድ ወይም የሙያ ብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት የያዘ ማንኛዉም ሰዉ የምስክር ወረቀቱን
በአግባቡ መጠቀም ይኖርበታል፡፡ ይህን ተላልፎ ሲገኝ የሚመለከተዉ የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት ፈቃዱን
እንዲሰረዝና በህግ እንዲጠየቅ ያደርጋል፤
4) የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ወይም የአማካሪ ድርጅት ፍቃድ የተሰጠው አካል ሆነ ብሎ ወይም በቸለልተኝነት ሙያው
የሚጠይቀውን ሥነ-ምግባር በመጣስ ስራውን ያከናወነ ስለመሆኑ በህግ የተረጋገጠ ማስረጃ ሲቀርብ፤ የሌላ ሰውን
ስራ የራሱ አስመስሎ የቀዳ ወይም የገለበጠ መሆኑ ሲረጋገጥ እንደ ጥፋቱ ደረጃ ከአንድ አመት እገዳ እስከ ምስክር
ወረቀት ስረዛ የሚደርስ እርምጃ ይወሰዳል፤
5) አንድ የአካባቢ አማካሪ ድርጅት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት አግኝቶ የአማካሪነት ስራ ሲሰራ
የሚያቀርባቸው የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርቶች ተደጋጋሚ የጥራት ችግር የሚያጋጥማቸው ከሆነ በመጀመሪያ
የቃል ማስጠንቀቂያ ይሰጠዋል፤ ቀጥሎም ይህን ችግር የማያስተካክል ከሆነ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ይጠዋል፡፡
በእነዚህ ሁለት ርምጃዎች የማይሻሻል ሆኖ ሲገኝ የተሰጠውን የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት በመሰረዝ
የአካባቢ አማካሪነት ስራውን እንዲያቋርጥ ያደርጋል፤
6) የትምህርት ዝግጅቱ ፈቅዶለት ከአንድ በላይ የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ያገኘ ባለሙያ አንድ ሰነድ ዝግጅት
ላይ ከአንድ መስክ በላይ ከተሠማራ ለአንድ አመት እገዳ ይጣልበታል፡፡
7) አንድ አማካሪ ድርጅት የራሱን የልማት ፕሮጀክት በአማካሪነት ሊሰራ አይፈቀድለትም፡፡ በመሆኑም ገለልተኛ በሆነ
የአካባቢ አማካሪ ድርጅት አሰርቶ ማቅረብ አለበት፡፡ አንድ አማካሪ ድርጅት የራሱን የልማት ፕሮጀክት ሲሰራ ከተገኘ
ለአንድ አመት እገዳ ይጣልበታል፡፡
8) ከላይ የተገለጹት ተግባርና ኃላፊነቶች እንደተጠበቁ ሆኖ የምስክር ወረቀት የሚሰረዘው፡- የምስክር ወረቀት
የተሰጠው ባለሙያ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለይ፣ ወይም በራሱ ጥያቄ ወይም በሌላ ምክንያት ስራውን

ሲተው፣ አመልካቹ የምስክር ወረቀቱን ያገኘው በማጭበርበር መሆኑ ከተረጋገጠ፣ የምስክር ወረቀት
የተሰጠው ድርጅት መክሰሩ ወይም መፍረሱ አግባብነት ባለው ፍ/ቤት ሲረጋገጥ ወይም በራሱ

ምክንያት ስራውን አቁሞ የምስክር ወረቀቱን ሲመልስ፣ አመልካቹ ከብቃት ማረጋገጫ ምስክር

24
ወረቀቱ ዓላማዎች ጋር የሚቃረኑ ተግባራትን ሲያከናውን ከተገኘ፣የአማካሪ ድርጅቱ ለሰራው የአካባቢ
ተፅዕኖ ዘገባ መልሶ የአካባቢ ኦዲት ሰርቶ ከተገኘና ፈቃድ ባላገኘበት የማማከር ደረጃና ዘርፍ

ተሰማርቶ ከተገኘ ይሆናል፡፡

13 ግዴታዎች
1) የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት ወይም የአካባቢ አያያዝ ሰነድ የቆይታ ጊዜ ጣሪያ 10 ዓመት ሆኖ በጸደቀ በሁለት
አመት ጊዜ ውስጥ የፕሮጀክቱ ትግበራ መጀመር አለበት፡፡
2) ከአስር አመት የጊዜ ቆይታ በኋላ የፕሮጀክቱ የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት ወይም የአካባቢ አያያዝ ሰነድ ተከልሶ
ወይም በአዲስ ተዘጋጅቶ ከአካባቢ ጥበቃ መ/ቤት የይሁንታ ሰርፊኬት ማግኘት አለበት፡፡
3) የአካባቢ ይሁንታ ፈቃድ የተሰጠው ፕሮጀክት በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ የማይተገበር ከሆነ ጥናቱ አዳዲስ ነባራዊ
ሁኔታዎችን አካቶና እንደገና ተከልሶ መቅረብና እንደገና የይሁንታ ሰርተፊኬት ማግኘት አለበት፡፡
4) በምድብ አንድ ስር ለተካተቱ ትልልቅ ፕሮጀክቶች የፕሮጀክቱ ባለቤት ቋሚ የውስጥ የአካባበቢ ክትትል ባለሙያ
የመቅጠር ግዴታ አለበት፡፡
5) የፕሮጀክት ባለቤቶች የአካባቢ አያያዝ እቅድ አተገባበራቸውን በዓመት አንድ ጊዜ በየደረጃው ላለ የአካባቢ ጥበቃ
መስሪያ ቤት ሪፖርት ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡
6) የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርት ተገምግሞ ከጸደቀ በኋላ የፕሮጀክት የዲዛይን ለዉጥ ከተከሰተና የተወሰኑ ዝርዝር
ተግባራት ከተቀየሩ፤ የዲዛይን ለውጡ ከመተግበሩ በፊት እነዚህ ለውጦች ለሚመለከተው የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ
ቤት ማሳወቅና ማፀደቅ ይኖርባቸዋል፡፡
7) የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮና ሌሎች የሚመለከታቸው የስራና የግንባታ ፈቃድ ሰጭ አካላት የአካባቢ
ይሁንታ ፈቃድ ካልተሰጣቸው በስተቀር ለፕሮጀክቶች የግንባታ/ የስራ ፈቃድ መስጠት የለባቸውም፡፡
8) የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮና ሌሎች የሚመለከታቸው ፈቃድ ሰጭ አካላት የአካባቢ ይሁንታ ፈቃድ
ለተሰጣቸው ፕሮጀክቶች የግንባታ ወይም የስራ ፈቃድ በሚሰጡበት ጊዜ በአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርቱ ውስጥ
የተካተቱ የተጽዕኖ ማቃለያ ተግባራት በቀረበው ዲዛይን ወይም የትግበራ ሂደት ውስጥ መካተቱን የማረጋገጥ ግዴታ
አለባቸው፡፡

14 ቅጣት
1. የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፖብሊክ መንግስት የወንጀል እና የፍትሃ ብሄር ሕግ ድንጋጌዎች እንደተጠበቀ
ሆኖ ይህ መመሪያ ወይም ሌላ አግባብ ያለውን ሕግ የሚተላለፍ ማንኛውም ሰው በፈፀመው ጥፋት ቅጣት
ይጣልበታል፡፡
2. ማንኛውም የኘሮጀክት ባለቤት የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ እንዲካሄድበት የተደነገገበትን ማንኛውም ኘሮጀክት
በየደረጃው ካለ የአካባቢ ጥበቃ መስሪያ ቤት ይሁንታ ሳያገኝ ተግባራዊ ያደረገ እንደሆነ ወይም በአካባቢ ተፅዕኖ
የጥናት ዘገባው ውስጥ ሀሰተኛ መግለጫ ያቀረበ እንደሆነ ከሃምሳ ሺህ ብር በማያንስና ከአንድ መቶ ሺህ ብር
በማይበልጥ የገንዘብ መቀጫ ይቀጣል፡፡

25
3. በዚህ አንቀፅ ንኡስ አንቀፅ 2 የተደነገገዉ እንደተጠበቀ ሆኖ ፕሮጀክቱ በአካባቢ ላይ ያደረሰዉ ጉዳት ከፍተኛ ከሆነ
ፕሮጀክቱ እንዲቋረጥ ይደረጋል፡፡
4. ማንኛውም ሰው በዚህ መመሪያ መሠረት ፈቃድ ሲሰጠው የተጣለበትን ግዴታ ካልተወጣ ወይም ተፈላጊ
ዝርዝሮችን በመዝገብ ሳያሰፍር ከቀረ በፈፀመው ጥፋት ከአስር ሺህ ብር በማያንስና ከሃያ ሺህ ብር በማይበልጥ
የገንዘብ መቀጫ ይቀጣል፡፡
5. በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው ድርጅት ጥፋት ሲፈፅም ድርጅቱ እንዲከፍለው ከተፈረደበት መቀጮ በተጨማሪ
የህጉን መከበር ለማረጋገጥ መፈፀም የሚገባውን ተግባር በትጋት ያልተወጣ በመሆኑ የሥራ መሪው ከአምስት ሺህ
ብር በማያንስና ከአስር ሺህ ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል፡፡
6. ይህን መመሪያ በመጣስ ጥፋተኛነቱ የተረጋገጠበትን ሰው ከሚወሰንበት ከማንኛውም ቅጣት በተጨማሪ የደረሰውን
ጉዳት በሙሉ በራሱ ወጪ እንዲያስተካክል ወይም እንዲተካ እና ካሳ እንዲከፍል ስልጣን ያለው ፍርድ ቤት ማዘዝ
ይችላል፡፡
7. ማንኛውም አስፈጻሚ መስሪያ ቤት የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ እንዲካሄድበት የተደነገጉት ፕሮጀክቶችን ከባለስልጣኑ
የይሁንታ ፈቃድ ሳያገኝ ተግባራዊ ያደረገ እንደሆነ ከሃምሳ ሺህ ብር በማያንስና ከመቶ ሺህ ብር በማይበልጥ የገንዘብ
መቀጫ ይቀጣል፡፡
8. የፕሮጀክት ባለቤቱ የአካባቢ ተቆጣጣሪዎችን ክትትል፣ ምርመራና ቁጥጥር እንዳያካሄዱ ወይም ወደ ፕሮጀክቱ ግቢ
እንዳይገቡ የከለከለ እንደሆነ ብር 30‚000.00 (ሰላሳ ሽህ ብር) ተቀጥቶ የመጨረሻ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ
ይሰጠዋል፡፡
9. የተሰጠውን ማስጠንቀቂያ ባለማክበር ለሁለተኛ ጊዜ ክትትል፣ ምርመራና ቁጥጥር እንዳይካሄድ ወይም የአካባቢ
ተቆጣጣሪዎችን ወደ ፕሮጀክቱ ቅጥር ግቢ እንዳይገቡ ከከለከለ ባለሥልጣኑ ወይም በተዋረድ ያሉ የአካባቢ ጥበቃ
መስሪያ ቤቶች የሰጡትን የይሁንታ ፈቃድ ያግዳሉ ወይም ይሰርዛሉ፡፡
10. በየደረጃዉ ካሉ የአካባቢ ጥበቃ መስሪያቤቶች የይሁንታ ፈቃድ ሳይሰጠዉ ወደ ተግባር የገባ ማንኛውም ፕሮጀክት
ብር 15,000.00 (አስራ አምስት ሽህ ብር) ተቀጥቶ ፕሮጀክቱ በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ የአካባቢ አያያዝ እቅድ
አዘጋጅቶ እንዲያቀርብ ይገለጽለታል፤ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ ውስጥ ዘገባውን ማቅረብ ካልቻለ ስራ ፈቃዱ
እንዲሰረዝ ለሚመለከተው የስራ ፈቃድ ሰጭ መስሪያ ቤት ይገለጽታል፡፡
15 ተፈፃሚነት ስለማይኖራቸው ህጎች
1) ከዚህ መመሪያ ጋር ተቃራኒ የሆነ ህግ ወይም አሰራር በዚህ መመሪያ ዉስጥ በተመለከቱት ጉዳዮች ላይ
ተፈፃሚነት አይኖረዉም፡፡
2) በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የአካባቢ ጥበቃ መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ ለአካባቢ አማካሪዎች
ፈቃድ ለመስጠት የወጣ መመሪያ ቁጥር 01/2006 ዓ.ም በዚህ መመሪያ ተሽሯል፡፡
3) በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የአካባቢ፣ ደንና ዱር እንሳት ጥበቃና ባለስልጣን ለአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ
መመሪያ የወጣ መመሪያ ቁጥር 001/2010 ዓ.ም በዚህ መመሪያ ተሽሯል፡፡
16 መመሪያ ስለማሻሻል

ይህን መመሪያ ባለስልጣኑ አስፈላጊ ሆኖ ባገኘዉ ጊዜ ሊያሻሽለዉ ይችላል፡፡

26
17 መመሪያዉ የሚጸናበት ጊዜ

ይህ መመሪያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የፀና ይሆናል፡፡

የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት

የአካባቢ፣ ደንና ዱር እንስሳት ጥበቃና ልማት ባለስልጣን

ባህር ዳር ሚያዝያ 1 ቀን 2012 ዓ.ም

27
18 ዕዝሎች
18.1 የአካባቢ አያያዝ ዕቅድ ሰንጠረዥ
የፕሮጀክቱ አሉታዊ የተግባራት መለኪያና መጠን ፈጻሚ የማቃለያ ተግባራት የሚተገበሩበት ጊዜ የሚያስ
ዝርዝር ተፅኖዎች አካል 1 ኛ ዓመት 2 ኛ ዓመት 3 ኛ ዓመት ፈልግ
ተግባራት በጀት
የፕሮጀክቱ

1 2 3 4 1 2 3 4 1 2 3 4
ምዕራፍ

ዝርዝር መለኪያ መጠን


ምዕራፍ
ግንባታ
ቅድመ
ግንባታ
ምዕራ

(አገልግሎት
በማምረት

) ምዕራፍ
ሲዘጋ( ሲጠና
ፕሮጀክቱ

ቀቅ)

28
18.2 የአካባቢ ክትትል ዕቅድ ሰንጠረዥ

የተጽዕኖ የተፅዕኖ የተግባራት ክትትሉ የአፈጻፀም የክትትል ፈጻሚ ወጪ


ዝርዝር ማቅለያ አመላካቾች የሚደረግበ ማረጋገጫ ድግግሞሽ ተቋም
ተግባራት ት ቦታ ዘዴዎች

ይህ የአካባቢ ክትትል ዕቅድ በአማርኛ ተዘጋጅቶ ለፕሮጀክት ባለቤቱ መሰጠት ያለበት ሲሆን ዕዝል ላይም

አብሮ መያያዝ ይኖርበታል፡፡ የሚዘጋጀው የአካባቢ ምርመራና ክትትል ሪፖርት በተቋሙ በጸደቀው የመስክ

ቢጋር መሰረት የሚቀርብ ሆኖ በዋናነት መግቢያ፣ የተከናወኑ ዋናዋና ተግባራት፣ እቅድ ክንውን
በሰንጠረዥ፣ የምርመራ፣ ክትትልና ቁጥጥር ግኝቶች፣ የታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች፣ ያጋጠሙ ችግሮች፣
የተወሰደ የመፍትሄ እርምጃና ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችን ያካተተ ይሆናል፡፡

18.3 የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ሪፖርት መገምገሚያ ማጠቃለያ ቅፅ

የኘሮጀክቱ ስም…………………….ቀን……… ቁጥር …………… የሰነዱ አይነት……………......


የገምጋሚው (ዎቹ) ባለሙያ (ዎች) ስም …………………………………………….……………

29
የመገምገሚያ መስፈርቶች ክብደት ሌላ ተጨማሪ
ተ/ የገለጻውአስፈላጊነት የገለጻው በቂነት (በበቂ የሚያስፈልግ መረጃ
ቁ (Relevance) ስመመገለጹ) ድምር
Adequately
addressed?
1 ስለ ፕሮጀክቱ የቀረበው ገለጻ 9 6 15%
1.1 የፕሮጀክቱ አላማና አካላዊ (ፊዚካላዊ) ባህርይ በበቂ ሁኔታ ተገልጸዋል? 3.5 1 4.5
1.2 የፕሮጀክቱ ስፋትና መጠን በደንብ ተለክቶ ተገልል ወይ? 0.9 0.8 1.7
1.3 የምርት ሂደቱ እና የሚጠቀማቸው ግብዓቶች በደንብ ተዘርዝሯል ወይ? 1.6 1.5 3.1
1.4 ዝቃጭ/ቅሪትና ወደ አካባቢ የሚለቀቁ ቆሻሻዎች (ፕሮጀክቱን የሚመለከተው 1.3 0.8 2.1
ከሆነ) በአግባቡ ተገልጧል?
1.5 የአደጋና አደገኛ ነገሮች ስጋቶች በትክክል ተገልጸዋል? 1.4 1.2 2.6
1.6 በፕሮጀክቱ አገላለፅ ላይ ሌሎች አስፈላጊ ጥያቄዎች ካሉ? 0.3 0.7 1.0
2 የፕሮጀክቱ አማራጮች ገለፃ 5 5.6 10.6
3 የፕሮጀክቱ አካባቢ መሰረታዊ መረጃ ገለፃ 12.6 8 20.6
3.1 የፕሮጀክቱ አካባቢ ሁኔታ/ጉዳዮች ገለፃ 5.6 3.4 9.0
3.2 የመረጃ አሰባሰብ ስልትና የአሰባሰብ ዘዴ ትክክለኛነት 4.8 2.6 7.4
3.3 በአካባቢ ሁኔታዎች አገላለፅ ላይ ሌሎች አስፈላጊ ጥያቄዎች ካሉ 2.2 2 4.4
4 የፕሮጀክቱ ጉልህ አካባቢዊና ማህበራዊ ተፅዕኖዎች ገለፃ 13.3 10 23.3
4.1 የተፅዕኖ ወሰን ልየታ ሁኔታ 3.6 1.2 4.8
4.2 ቀጥተኛ የአካባቢ ተፅዕኖዎች ትንበያ 1.4 1.3 2.7
4.3 ቀጥተኛ ያልሆነ፣ ጊዜያዊ፣ የአጭር ጊዜ፣ ቋሚ፣ የረዥም ጊዜ፣ ድንገተኛ፣ 1.8 1.3 3.1
ተዳማሪና አንዱ በሌላው ላይ የሚያደርሰው መስተጋብራዊ ተፅዕኖዎች ትንበያ
4.4 በሰዎች ጤናና ዘላቂ ልማት ጉዳዮች ላይ ሊደርሱ የሚችሉ 2.4 1.7 4.1
ተጽዕኖዎች/ለውጦች ትንበያ
4.5 የተፅዕኖዎችን ክብደት ደረጃ መገምገም ሂደት 1.8 1.8 3.6
4.6 የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ዘዴ 1.4 0.9 2.3
4.7 በተፅዕኖ ገለፃ ላይ ሌሎች አስፈላጊ ጥያቄዎች ካሉ 0.5 0.5 1.0
4.8 በማህበረሰብ ዉይይቱ ወቅት ማህበረሰቡ ያነሳቸዉ አስተያየቶች፣ 1.3 1.3 2.6
አመለካከቶችና ስጋቶች በአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ዘገባው ዉስጥ መካተቱንና
ቃለጉባኤ መያያዙን
5 የተፅዕኖ ማስተሰረያ (ማቅለያ ትንታኔ) 11.1 9 20.1
6 የማጠቃለያ ፅሁፍ አገላለፅ 2.8 3.2 6
7 የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ጥናት አቀራረብ/አገላለፅ/አፃፃፍ ጥራት 2.2 2.2 4.4
ጠቅላላ የተሰጠ ክብደት 56 44 100

18.3.1 የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ሪፖርት መገምገሚያ ዝርዝር መመዘኛ ቅፅ


1. የአካ/ተ/ግ/ሰነድ ርዕስ፣ ቀንና ቁጥር ……………………….
2. የኘሮጀክቱ ስም ………………………………………......
3. የገምጋሚው/ዎቹ/ ስም …………………………………
…………………………………
………………………………...
ተ.ቁ የመገምገሚያ ነጥቦች ሌላ ተጨማሪ የሚያስፈልግ መረጃ
የመረጃው

አለ
አስፈላነት
የመረጃ

በቂነት

ክፍል 1. ፕሮጀክቱ ስለሚያከናውናቸው


ተግባራት ሙሉ መግለጫ
የፕሮጀክቱ አላማና አካላዊ (ፊዚካላዊ) ባህርይ
1.1 የፕሮጀክቱ አስፈላጊነትና አላማዉ በበቂ ሁኔታ ተገልጸዋል? 0.5

30
ተ.ቁ የመገምገሚያ ነጥቦች ሌላ ተጨማሪ የሚያስፈልግ መረጃ

የመረጃው
አለ

አስፈላነት
የመረጃ

በቂነት
1.2 ፕሮጀክቱ የሚተገበርበት ፕሮግራም በበቂ ሁኔታ ተገልጧል?
ፕሮጀክቱ ግንባታ በሚጀምርበትና በሚጨርስበት ጊዜ፣ አገልግሎት
በሚሰጥበት ወይም ምርት በሚያመርትበት ጊዜ እና ስራ
በሚያቆምበት ጊዜ የሚከናወኑ ተግባራት በዝርዝር ተገልጸዋልን?

1.3 ሁሉም የፕሮጀክቱ ዋና ዋና ክፍሎች ተጠቅሰዋል?


1.4 እያንዳንዱ የፕሮጀክቱ ክፍሎች የሚገኙበት ቦታ በካርታ፣
በፕላን እንዲሁም በስዕላዊ መግለጫ በአግባቡ ተመልክቷል?
1.5 በፕሮጀክቱ የግንባታ ቦታዎች የአቀማመጥ እቅድ በአግባቡ
ተመልክቷል? (የቦታዉን አቀማመጥ የማደላደል ስራ፣
ህንጻዎችን፣ ከመሬት በታች የሚሰሩ ስራዎችን፣ መጋዝኖችን፣
የዉሃ መስመሮችን፣ የእጽዋት ቦታዎችን፣ የመተላለፊያ
መንገዶችን፣ የፕሮጀክቱን ወሰን እና ሌሎች ፊዚካላዊ
ግንባታዎች ይጨምራል)
1.6 የመስመር ዝርጋታ ፕሮጀክቶች ማለትም የሀይል ማስተላለፊያ
መስመሮች፣ የቧንቧ መስመሮች፣ መንገዶች፣ የውስጥ ለውስጥ
መተላላፊያ መንገዶች፣ የአግዳሚና ቋሚ መተላላፊያዎች
አቀማመጥ፣ ከመሬት በታች ያሉ መተላለፊያ መስመሮች ስራ
በአግባቡ ተገለጸዋል?
1.7 ሁሉም የፕሮጀክቱ ግንባታ ስራዎች ተጠቅሰዋል?
1.8 ፕሮጀክቱ አገልግሎት በሚሰጥበት ጊዜ ወይም ምርት
በሚያመርትብት ጊዜ የሚከናወኑ ተግባራት በሙሉ በአግባቡ
ተገልጸዋል?
1.9 ፕሮጀክቱ ስራ በሚያቆምበት ወቅት የሚሰሩ ስራዎች በሙሉ
ተገልጸዋል? (ማሽን ነቀላ፣ ህንጻ ማፍረስ፣ ማጽዳት፣ ቦታዉን
ወደ ነበረበት መመለስ ወዘተ)
1.10 ሌሎች ለፕሮክቱ የሚያስፈልጉ ተጨማሪ አገልግሎቶች
በሙሉ ተገልጸዋል? (የማጓጓዣ መንገዶች፣ ዉሃ፣ የፍሳሽ
ማስወገጃ መስመሮች፣ የቆሻሻ ማስወገጃ፣ የሚያስፈልገዉ
ሀይል ወይም ተጨማሪ የሚሰሩ የመንገድ፣ የሀይል መስመር
እንዲሁም የዉሃ ቧንቧ መስመሮች ወዘተ)
1.11 በፕሮጀክቱ ልማት የተነሳ ሊተገበሩ የሚችሉ ሌሎች ልማቶች
ተልይተዋል? (አዲስ የቤቶችና መንገዶች ግንባታ፣ የዉሃ
ወይም የፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃዎች፣ የግንባታ ማቴሪያሎች
መቆፈሪያ ቦታዎች ወዘተ)
1.12 በፕሮጀክቱ ምክንያት የሚቀየር ወይም የሚያቆሙ ነባር
ስራዎች ተለይተዋል?
1.13 ከዚህ ፕሮጀክት ጋር ተደማሪ ተጽእኖ ሊያደርሱ የሚችሉ ነባር
ወይም የታቀዱ ልማቶች ተለይተዉ በአግባቡ ተገልጸዋል?
የፕሮጀክቱ ስፋት/መጠን
1.14 በፕሮጀክቱ ቋሚ የግንባታ ክፍሎች እንዲዉል የታቀደዉ
የቦታ ስፋት መጠኑ ተገልፆ በካርታ ላይ ተመልክቷል?
1.15 በፕሮጀክቱ ግንባታ ወቅት በጊዚአዊነት የሚያገለግል ቦታ
(መጋዝን፣ ካምፕ ወዘተ) መጠን ታዉቆ በካርታ ላይ
ተመልክቷል?
1.16 በፕሮጅከቱ ትግበራ ወቅት በጊዜአዊነት ሲያገለግሉ የነበሩትን
ቦታዎች መልሶ የማልማት እቅድ ተካቷል? (የካባ ቦታዎች፣
የመወጣጫ ግንባታዎች፣ የአፈርና አሸዋ ማውጫ ቦታዎች
1.17 ወዘተ )
የፕሮጀክቱ አካል የሆኑት የህንጻ ግንባታዎች ወይም ሌሎች
የግንባታ ስራዎች መጠንና ቦታ ተለይተዋል? (የወለል ስፋትና

31
ተ.ቁ የመገምገሚያ ነጥቦች ሌላ ተጨማሪ የሚያስፈልግ መረጃ

የመረጃው
አለ

አስፈላነት
የመረጃ

በቂነት
የህንጻዉ ርዝመት፣ የአፈር ማዉጫ ጉድጓዶች ስፋት፣
የአፈርና የዉሃ መከላከያ የባዮ ፊዚካል ስራዎች፣ ድልድዮች፣
የዉሃ ፍሰት ወይም ጥልቀት ወዘተ)
1.18 የህንጻ መዋቅሮችና ገፅታዎች ወይም ሌሎች ስራዎች
አይነትና ይዘት ተጠቅሰዋል? (ጥቅም ላይ የሚዉሉት
ግባቶችና አይነታቸዉ፣ የህንጻዉ ቅርጽ፣ የእጽዋት ዝርያዎች
አይነት ወዘተ)
1.19 በከተማ ልማትና በተመሳሳይ የልማት ፕሮጀክቶች
በሚከናወኑበት ጊዜ ልማቱን ተከትለው ሊሰፍሩ የሚችሉ
ማህበረሰቦች ወይንም ሊፈጠር የሚችል የንግድ ማህበረሰብ
በአግባቡ ተገልጿል?
1.20 ፕሮጀክቱ ማህበረሰብንና የስራ እንቅስቃሲዎችን የሚያፈናቅል
ከሆነ በፕሮጀክቱ ምክንያት የሚፈናቀል ህብረተሰብ ብዛትና
ሌሎች ጉዳዮች ተገልጸዋል?
1.21 አዲስ የመንገድ መሰረተ ልማት ወይም ጉልህ የሆነ የትራፊክ
ፍሰት ለዉጥ ሊያስከትል የሚችሉ ፕሮጀክቶች ከሆነ የአዲሱ
ትራፊክ አይነት፣ መጠኑ፣ ጊዜአዊ መተላላፊያ መስመሮች እና
የቦታ ስርጭቱ ተገልጿል?
የአመራረት ሂደቶችና ግብአቶች
1.22 ፕሮጀክቱ በሚተገበርበት ጊዜ የሚከናወኑ አጠቃላይ ሂደቶች
ተጠቅሰዋል? (የማመምረት ወይም የምህንድስና ሂደቶች፣
ለግብአት የሚሆኑ ጥሬ እቃዎችን የማምረት፣ የግብርና ወይም
የደን ዉጤቶችን የማምረት ዘዴዎች፣የማዉጣት ሂደቶች
ወይም ተፈላጊውን ምርት ከጥሬ ዕቃው የመለየትወዘተ)
1.23 በፕሮጀክቱ የሚመረቱ የምርት አይነቶችና መጠን ተገልጸዋል?
1.24 በግንባታ ወቅትና ፕሮጀክቱ ስራውን በሚጀምረበት ወቅት
የሚያስፈልጉ ግብአቶችና የሀይል ፍላጎት መጠንና አይነት
ተገልጧል?
1.25 ግብአቶችን መጠቀም ከአካባቢ አንጻር ያለዉ አድምታ
1.26 ተብራርቷል
የሀይልና ?
የግብአት አጠቃቀም ዉጤታማነት ተገጸዋል?
1.27 ፕሮጀክቱ በግንባታ፣ በማምረት/አገልግሎት በመስጠት ሂደት
እና ፕሮጀክቱ ስራ በሚያቆምበት/ማጠናቀቂያ ወቅት
የሚጠቀምባቸዉ፣ የሚከዝናቸዉ፣ ወይም የሚያመርታቸዉ
ዋና ዋና አደገኛ ቁሶች አይነትና በመጠን ተለይተዋል?
1.28 የግብአት እቃዎችን ወደ ፕሮጀክቱ ስለማጓጓዙና ስለ ትራፊክ
ፍሰቱ ቁጥር ተጠቅሷል?
በግንባታ፣
በትግበራ እንዲሁም
ስራ በሚያቆምበት/ የፕሮጀክቱ ማጠናቀቂያ ወቅት
1.29 በፕሮጀክቱ ምክንያት የስራ አድል መፈጠሩን ወይም ከስራ
መፈናቀል ካለ ተጠቅሷል?
በግንባታ፣
በትግበራ እንዲሁም
ስራ በሚያቆምበት/ የፕሮጀክቱ ማጠናቀቂያ ወቅት
1.30 ፕሮጀክቱ በግንባታ፣ በማምረት/አገልግሎት በመስጠት ሂደት
እና ፕሮጀክቱ ስራ በሚያቆምበት/ማጠናቀቂያ ወቅት
ለሰራተኞችና ደንበኞች አገልግሎት ስለሚሰማሩ
የትራንስፖርት ተደራሽነትና የትራፊክ እንቅስቃሴ ቁጥር
ተጠቅሷል
1.32 ለቋሚና ጊዜአዊ ሰራተኞች የቤትና ሌሎች አገልግሎቶች
አቅርቦት በተመለከተ ተገልጧል?

32
ተ.ቁ የመገምገሚያ ነጥቦች ሌላ ተጨማሪ የሚያስፈልግ መረጃ

የመረጃው
አለ

አስፈላነት
የመረጃ

በቂነት
ዝቃጭ/ቅሪትና ወደ አካባቢ የሚለቀቁ ቆሻሻዎች (ከፕሮጀክቱ የሚመነጩ ካሉ)
1.33 ፕሮጀክቱ በግንባታ፣ በማምረት/አገልግሎት በመስጠት ሂደት
እና ፕሮጀክቱ ስራ በሚያቆምበት/ማጠናቀቂያ ወቅት
በፕሮጀክቱ የሚመነጭ የደረቅ ቆሻሻ መጠንና አይነት
ተለይተዋል? (የግንባታና የህንጻ ፍርስራሽ ቆሻሻ፣ የተበላሸ
ግብዓት/ምርት፣ የምርት ሂደት ቆሻሻ፣ ተረፈ ምርት፣ አደገኛ
ቆሻሻ፣ ከቤት ወይም ከንግድ ድርጅቶች የሚመነጭ ቆሻሻ፣
የግብርና ወይም የደን ውጤቶች ቆሻሻ፣ ከፕሮጀክት ቦታ
ማፅዳትየሚሰበሰብ ቆሻሻ፣ የማእድን ማዉጣት ቆሻሻ፣
ፕሮጀክቱ ሲዘጋ/ሲጠናቀቅ የሚመነጭ ቆሻሻ ወዘተ)
1.34 በፕሮጀክቱ ምክንያት የሚመነጨዉ ሁሉም የደረቅ ቆሻሻ
ዉህዶችና የመርዛማነት ደረጃ ወይም አደገኝነት ተገልጧል?
1.35 ደረቅ ቆሻሻን የመሰብሰብ፣ የማከማቸት፣ የማከም፣ የማጓጓዝና
በመጨረሻም የመስወገዱ ስራ ተገለጧል?
1.36 የደረቅ ቆሻሻ መጨረሻ ላይ የሚወገድበት ቦታዉ ተለይቷል?
1.37 ፕሮጀክቱ በግንባታ፣ በማምረት/አገልግሎት በመስጠት ሂደት
እና ፕሮጀክቱ ስራ በሚያቆምበት/ ማጠናቀቂያ ወቅት
ከፕሮጀክቱ የሚመነጨዉ ፍሳሽ ቆሻሻ በአይነትና በመጠን
ተለይቷል? (ከፕሮጀክት ግቢ የሚመነጭ ጎርፍ፣ በምርት
ሂደት የሚፈጠሩ ፍሳሽ ቆሻሻዎች፣ የማቀዝቀዣ ውሃ/ቆሻሻ፣
ከግቢ የሚወጣ ፍሳሽ ቆሻሻ፣ ከማጣሪያ የሚወጣ የተጣራ
ፍሳሽ ቆሻሻ ወዘተ)
1.38 በፕሮጀክቱ ምክንያት የሚመነጨዉ ሁሉም የፍሳሽ ቆሻሻ
ዉህዶችና የመርዛማነት ደረጃ ወይም አደገኝነት ተገልጧል?
1.39 የፍሳሽ ቆሻሻ አሰባበሰብ፣ አቀማመጥ፣ ማከም፣ መጓጓዝና
በመጨረሻም ማስወገደጃ ዘዴዎች ተገልጧል?
1.40 የሁሉም ፍሳሽ ቆሻሻ የመጨረሻ ማስወገጃ ቦታዉ ተለይቶ
ታዉቋል?
1.41 ፕሮጀክቱ በግንባታ፣ በማምረት/አገልግሎት በመስጠት ሂደት
እና ፕሮጀክቱ ስራ በሚያቆምበት/ ማጠናቀቂያ ወቅት
በፕሮጀክቱ የሚመነጩ የጋዝና የብናኝ ልቀቶች አይነትና
መጠን ተለይተዋል? (የምርት ሂደት ልቀት፣ የጭስ ልቀት፣
ነዳጅን ከሚጠቀሙ ከቋሚና ተንቀሳቃሽ የሀይል
ማመንጫዎች የሚወጣ ልቀት፣ ከተሽከርካሪ የሚወጣ ልቀት፣
ከእቃዎች አያያዝ የሚወጣ አቧሯ፣ ሽታ ወዘተ)
1.42 በፕሮጀክቱ ምክንያት ወደ አየር የሚለቀቁትሁሉም ልቀቶች
ዉህዶችና የመርዛማነት ደረጃ ወይም አደገኝነት ተገልጧል?
1.43 ወደአየር የሚለቀቁ ልቀቶች አሰባሰብ፣ ማጣራትና
በመጨረሻም ወደ አየር የሚለቀቁበት ዘዴዎች ተገልጧል?
1.44 ሁሉም የጋዝ ልቀቶች ወደ አየር የሚለቀቁበት ቦታ እንዲሁም
የሚለቀቁት ጋዞች ባህርይ ተለይተዋል? (የጋዝ/የጭስ
መልቀቂያ ቧንቧ ቁመት፣ የጋዙ/የጭሱ የልቀት ፍጥነትና
የሙቀት ደረጃ ወዘተ)
1.45 ፕሮጀክቱ ቆሻሻ የሚያመነጭ ከሆነ ከነዚህ ቆሻሻዎችና
ዝቃጮች መልሶ የመጠቀም እድሉ ካለ ተብራርቷል? (መልሶ
መጠቀም፣ ለዳግም ዑደት ማዋል ወይም ከፍሳሽና ደረቅ ቆሻሻ
ሀይል ማመንጨት)
1.46 ፕሮጀክቱ ድምጽን፣ ሙቀትን፣ ብርሀን ወይም የኤሌክትሮ
ማግኔቲክ ራዴሽን መጠን የሚጨምር ከሆነምንጫቸዉና
መጠናቸዉ ተለይቶ ታዉቃል?
1.47 ፕሮጀክቱ ዝጋጭና የጋዝ/ጭስ ልቀት የሚያመነጭ ከሆነ

33
ተ.ቁ የመገምገሚያ ነጥቦች ሌላ ተጨማሪ የሚያስፈልግ መረጃ

የመረጃው
አለ

አስፈላነት
የመረጃ

በቂነት
የዉህዶችን አይነትና መጠናቸዉን መለኪያ ዘደዎች
ተቀምጠዋል የጋጠሙ ችግሮችስካሉ ተገልፀዋል?
1.48 ፕሮጀክቱ ዝቃጭና ጋዝ/ጭስ ልቀቶችን የሚያነጭ ከሆነ
የዝቃጩንና የልቀቱን መጠን ለማወቅ ስለተጠቀመው ዘዴ
እርግጠኛነት አብሮ ተብራርቷል?
የአደጋና አደገኛ ነገሮች ስጋቶች
1.49 በፕሮጀክቱ ምክንያት ሊከሰቱ የሚችሉ ስጋቶች/አደጋዎች
ተገልጸዋል?
ከአደገኛ ነገሮች አያያዝ ችግር ሊደርስ የሚችል ስጋት
ከሚፈሱ ነገሮች እሳትና ፍንዳታዎች የሚከሰት አደጋ
የተሸከርካሪ አዳጋ/ስጋት
ከማምረቻ መሳሪዎች መሰበር ወይም አለመስራት ጋር
የሚመጡ አደጋዎች/ስጋቶች
ፕሮጀክቱ በተፈጥሮ አደጋዎች መጋለጥ ምክንያት ሊመጡ
የሚችሉ ስጋቶች (የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ጎርፍ፣ የመሬት
መንሸራተት ወዘተ)
1.50 አደጋና ያልተለመዱ ሁኔታዎችን ለመከላከል ስለሚወሰዱ
እርምጃዎች ተብራርቷል? (የመከለከያ ዘዴዎች፣ ስልጠናዎች፣
የመጠባበቂያ እቅዶች፣ የአደጋጊዜ እቅድ ወዘተ)
ስለፕሮጀክቱ ማብራሪያ ሌሎች ተጨማሪ ጥያቄዎች
የፕሮጀክት አማራጮችን በተመለከተ
2.1 ፕሪጀክቱንየበለጠ ውጤታማ የተደረገበት ሂደት ተብራርቷል?
2.2 ፕሮጅከቱን የበለጠ ውጤታማ በማድረግ ሂደት የተሻሉ
አመራጮች ካሉ ግምት ዉስጥ ገብተዋል?
2.3 ፕሮጅቱ ከመተግበሩ በፊት ያለዉ የአካባቢዉ/ቦታዉ
አጠቃላይወይም ነባራዊሁኔታ ተብራርቷል?
2.4 የተጠቀሱት አማራጮች ተዓማኝነትና ለፕሮጀክቱ ትክክለኛ
አማራጮች ናቸዉ?
2.5 አካባቢያዊ ምክንያቶችን ጨምሮ ፕሮጀክቱ የተመረጠበት ዋና
ምክንያቶች ተብራርተዋል?
2.6 በፕሮጅክት አማራጮች የሚደርሰዉ አካባቢያዊ ተጽእኖ
ከፕሮጀክቱ ተጽእኖ ጋር በተነፃፃሪነት ተገለጧል?
የዋና ዋና አካባቢያዊ ተፅዕኖዎች ማቅለያ አማራጮች ሊተገበር
ከታሰበው ፕሮጀክት ጋር ጠቀሜታው በተነፃፃሪነት ተቀምጧል
ውይ?
የፕሮጀክቱን አማራጮች በተመለከተ ሌሎች ጥያቄዎች
2.7 በጥናት ሰነዱ የተዘረዘሩ አማራጮች ከቦታ፣ ከጊዜ፣ ከቴክኖሎጂ፣ ከጥሬ
ዕቃ፣ ከዲዛይ፣ ከሂደት፣ የማቅለያ ዘዴዎች እና ፕሮጀክቱ ቢተገብርና
ባይተገበር አማራጮችን የዳሰሰ ነው ወይ?
2.8 በእያንዳንዱ አማራጭ ቢንያስ ሁለት ማወዳደሪያ አማራጮች ቀርበው
የከአካባቢና ማህበራዊ ጉዳዮች ግምት ውስጥ ገብተው የተሻለውን
አማራጭ በመምረጥ የተከናወነ ነው ወይ?
ክፍል 3 በፕሮጀክቱ ምክንያት ተጽእኖ ሊደርስባቸዉ ስለሚችሉ አካባቢዎች ገለጻ
የአካባቢዉነባራዊ ሁኔታ
3.1 ለፕሮጀክቱ አገልግሎት ሚውለው ቦታና አካባቢው የመሬት
አጠቃቀሙ ሁኔታ፣ በፕሮጀክቱ የሚወሰደው ቦታ፣
በፕሮጀክቱ ቦታ የሚኖሩ ወይም ቦታውን እየተጠቀሙ ያሉ
ሁሉም ሰዎች ተለይተዋል ወይ? (የመኖሪያ፣ የንግድ፣
የኢንዱስትሪ፣ የግብርና፣ የመዝናኛ ወዘተ)
3.2 የፕሮጀክቱ ቦታና አካባቢዉ መልከዓ-ምድር፣ ስነ-ምድር
እንዲሁም አፈር ሁኔታተብራርቷል?

34
ተ.ቁ የመገምገሚያ ነጥቦች ሌላ ተጨማሪ የሚያስፈልግ መረጃ

የመረጃው
አለ

አስፈላነት
የመረጃ

በቂነት
3.3 የአካባቢዉ መልከአምድር ወይም የአካባቢዉ ስነምድር
ጉልህ መለያ ባህርያት ወይም ገፅታዎች እንዲሁም የአፈሩ
ሁኔታናእየሰጠ ያለዉ ጥቅም ተብራርቷል? (የአፈሩ ለምነት፣
አፈሩ ለክለት ያለዉ ጥንካሬ፣ ለግብርና ያለዉ ጠቀሜታና
ለግብርና የሚዉለዉ የመሬት ጥራትን ጨምሮ)
3.4 ፕሮጀክቱ የሚተገበርበት ቦታና አካባቢዉ ስላሉ እጽዋትና
እነስሳት እንዲሁም የተፈጥሮ መኖሪያ ቦታዎች (ሚችጌ)
በተመለከተ የተብራራና በካርታ ላይ የተመላከተ ነዉ?
3.5 በፕሮጀክቱ ጉዳት ሊደርስባቸዉ የሚችሉ የስነህይዎት መኖሪ
ቦታዎች ባህርያትና በዉስጣቸዉ የያዟቸዉ የዝርያ ብዛት
የሚገልጽ ማብራሪያ አለ እንደዚሁም ተለይተው የታወቁልዩ
ጥበቃ የሚደረግላቸዉ ዝርያዎች ወይም ቦታዎች ተለይተዉ
ተቀምጠዋል(በፕሮጀክቱ አካባባቢ ካለ)?
3.6 ፕሮጀክቱ በዉሃ አካላት ላይ ተጽእኖ የሚያደርስ ከሆነ
የዉሃዉ ሁኔታና አካባቢዉ በአግባቡተገልጧል? (ወራጅና
የቆመ የዉሃ አካላትን ጨምሮ የከርሰምድር ዉሃ፣ ሀይቆች፣
ዉሃ አዘል መሬት፣ ጎርፍና ማንጣፈፊያን ይጨምራል)
3.7 በፕሮጀክቱ ተጽእኖ ሊደርስበትየሚችልየውሃ ሃብት፣ የውሃ
ባህሪና ስርጭት፣ ፍሰት፣ የዉሃ ጥራት እንዲሁም የዉሀ
አጠቃም ተገልጸዋል? (ለመጠጥ ዉሃ አቅርቦት፣ አሳ ማስገርና
እርባታ፣ ለገላ መጣጠቢያና መዋኛ፣ ለመጓጓዣ፣
ለተጣራፍሳሽ ማስወገጃ ያለዉ ጠቀሜታ፣ ስነውበት፣ ወዘተ
ጭምር)
3.8 የአካባቢዉ ከባቢ አየር በፕሮጀክቱ ተጽእኖ የሚደርስበት
ከሆነ የአየር ንብረትና የእለታዊ የአየር ሁኔታ እንዲሁም
በወቅቱ ያለዉ የአየር ጥራት ሁኔታ ተገልጧል?
3.9 ፕሮጀክቱ በአካባቢዉ ድምጽ ላይ ተጽእኖ የሚያስከትል ከሆነ
የወቅቱ የድምጽ ደረጃ ተመልክቷል?

3.10 የአካባቢዉ ብርሀን፣ ሙቀትና ኤሊክትሮማግኔቲክ ጨረራ


ሁኔታ በፕሮጀክቱ ተጽእኖ የሚደርስባቸዉ ከሆነ የወቅቱ
ነባራዊ ሁኔታ ተገልጸዋል?

3.11 በፕሮጀክቱ ጉዳት ሊደርስባቸዉ የሚችሉ ቁሳዊ ሀብቶች


ተብራርተዋል? (ህናጻዎችና ሌሎች አዉታሮች፣ የማእድን
ሀብቶች፣ የዉሃ ሀብቶችን ወዘተ ይጨምራል)
3.12 የፕሮጀክቱ የስራ እንቅስቃሴ የሚነካቸዉ/የሚያቋርጣቸው
የከርሰምድር ቅሬተ አካልና ቦታዎች፣ የታሪካዊ፣ ስነ-ህንፃዎች
ወይም ሌሎች የማህበራዊና ባህላዊ ጠቀሜታ ያለቸዉ
ቦታዎች እንዲሁም ተከልለው የሚጠበቁ/ጥብቅ ቦታዎችን
ጨምሮ ተብራርተዋል?
3.13 በፕሮጀክቱ ሊጎዳምክክንያት ጉዳት ሊደርስበት የሚችል
መልክዓ-መድር፣ተከልሎ የሚጠበቅ/ጥብቅ መልክዓ-ምድር
ቦታን ጨምሮ ተገልጧ?
3.14 የአካባቢዉ የህብረተሰቡ አሰፋፈር፣ አኗኗ፣ ስርጭት፣ የህዝብ
ብዛት፣ የህዝብ እድገት፣ ትፍፍግ፣ ስነተዋልዶ፣ ጋብቻ፣የጤና
ሁኔታ እና ሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች
(ለምሳሌ የስራ እድል ሁኔታ) ተገልጧል?
3.15 ከላይ ከተዘረዘሩት ዉስጥ ፕሮጀክቱ ተግባራዊ ባይሆንም
ወደፊት ሊለወጡ የሚችሉ የአካባቢ ሁኔታዎች ካሉ
ተብራርተዋል ወይ?

35
ተ.ቁ የመገምገሚያ ነጥቦች ሌላ ተጨማሪ የሚያስፈልግ መረጃ

የመረጃው
አለ

አስፈላነት
የመረጃ

በቂነት
የመረጃ አሰባሰብና የመረጃ አወሳሰድ ዘዴ
3.16 የጥናቱ ወሰን ስፋት በፕሮጀክቱ ጉልህ ተጽእኖ ሊድርስባቸዉ
ይችላል ተበሎ የሚታሰቡትን ሁሉንም ቦታዎች የሚያካትት
ነዉ?
3.17 መሰረታዊ መረጃጃዎችን በማሰብሰቡ ሂደት ሁሉምንም
የሚመለከታቸዉ ሀገር አቀፍና ክልላዊ ድርጅቶችና ተቋማት
ጋር ግንኙነት ተደርጓል?
3.18 የመሰረታዊ መረጃ ምንጮችናየተሰበሰበው መረጃ በበቂ
3.19 የአካባቢዉን ነባራዊ ሁኔታ መሰረታዊ መረጃ ለመሰብሰብ
በሚካሄደዉ የአካባቢ ዳሰሳዊ ጥናት ወቅት ተግባር ላይ
የዋሉት ዘዴዎች፣ ያጋጠሙ ማንኛዉም ተግዳሮቶች
እንዲሁም ያልተጠበቁ ሁኔዎች መረጃ ተጠቅሷል?
3.20 የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማን ለማጥናት ጥቅም ላይ የዋሉ
ዘዴዎች አግባብነት ያላቸዉ ነበሩ?
3.21 በአካባቢ መሰረታዊ መረጃው ላይ ያሉ ጠቃሚ የመረጃ
ክፍተቶች ተለይተዋል? ይህንን ክፍተት ለማስወገድ የተወሰዱ
3.22 ዘዴዎችስ
የአካባቢዉንተገልጸዋል
ነባራዊ? መሰረታዊ መረጃ በበቂ ሁኔታ
ለመግለጽ የዳሰሳ ጥናት ቢያስፈልግ ነገር ግን በተለያዩ
ምክንያቶች ይህን ማድረግ ሳይችል ቢቀር ምክንያቶች
ተዘርዝረዋል ወደፊትስ እንዴት መጠናት እንዳለበት
ተመላክቷል?
የአካባቢዉን መሰረታዊ መረጃበተመለከተ ሌሎች ጥያቄዎች ካሉ

ክፍል 4 በፕሮጀክቱ ምክንያት ሊከሰቱ የሚችሉ ጉልህ የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖዎችን ገለፃ
የተጽእኖዎች ወሰን ልየታ
4.1 ለአካባቢ ተጽዕኖጥናትየወሰን ልየታ የአሰራርሂደቱ ተለይቶ
4.2 የታወቀ
ለአካባቢነበር ወይ?
ተጽዕኖጥናት ወሰን ልየታ የተጠቀሙበት ስልታዊ
ዘዴ ግልጽ ነበር?
4.3 ለአካባቢ ተጽዕኖጥናት የወሰን ልየታ ወቅት በቂ የሆነ
ማህበረሰቡ ዉይይት መካሄዱን የሚገልጹ መረጃዎች
ቀርበዋል?
4.4 በማህበረሰብዉይይቱ ወቅት ማህበረሰቡ ያነሳቸዉ
አስተያየቶች፣ አመለካካቶችና ስጋቶች በአካባቢ ተጽእኖ
ግምገማ ዘገባው ዉስጥ ተካቷል?
ቀጥተኛና ዋና (የመጀመሪያ ደረጃ)የሆኑየአካባቢ ተጽእኖዎች ትንበያ
4.5 ፕሮጀክቱ በመሬት አጠቃቀም ላይ፣ በህብረተሰቡ ላይ እና
በሀብት ላይ የሚያደርሰዉ ቀጥተኛ እና ዋና (የመጀመሪያ
ደረጃ) ተጽእኖዎች ተገልጸዋል (ከተቻለ በመጠን ጭምር)?
4.6 ፕሮጀክቱ በመሬት ገጽታና በአፈር ባህርይ ላይ የሚያደርሰዉ
ቀጥተኛ እና ዋና (የመጀመሪያ ደረጃ) ተጽእኖዎች ተገልጸዋል
(በመጠን ጭምር)?
4.7 ፕሮጀክቱ በእጽዋት፣ በእንስሳትና በተፈጥሮ መኖሪያዎች
(ሙቹጌ)ላይ የሚያደርሳቸዉ ቀጥተኛ እና ዋና (የመጀመሪያ
ደረጃ) ተጽእኖዎች ተገልጸዋል (ከተቻለ በመጠን ጭምር)?
4.8 ፕሮጀክቱ በዉሃ ሃብት ስርጭት፣ ፍሰት፣ ባህሪ እና በዉሃ
ጥራት ላይ የሚያደርሳቸዉ ቀጥተኛ እና ዋና (የመጀመሪያ
ደረጃ)ተጽእኖዎች ተገልጸዋል (ከተቻለ በመጠን ጭምር)?
4.9 ፕሮጀክቱ በዉሃ አጠቃቀም ላይ የሚያደርሰዉ ቀጥተኛ እና
ዋና (የመጀመሪያ ደረጃ)ተጽእኖ ተገልጸዋል (ከተቻለ
በመጠን ጭምር)?

36
ተ.ቁ የመገምገሚያ ነጥቦች ሌላ ተጨማሪ የሚያስፈልግ መረጃ

የመረጃው
አለ

አስፈላነት
የመረጃ

በቂነት
4.10 ፕሮጀክቱ በአየር ጥራትና በአየር ንብረት ሁኔታ ላይ
የሚያደርሰዉ ቀጥተኛ እና ዋና (የመጀመሪያ ደረጃ)ተጽእኖ
ተገልጧል (ከተቻለ በመጠን ጭምር)?
4.11 ፕሮጀክቱ በአካባቢው ላይየሚያደርሰዉ ቀጥተኛና ዋና
(የመጀመሪያ ደረጃ)የሆነ የድምጽ (ጫጫታና ንዝረት) ተጽእኖ
ተገልጧል (ከተቻለ በመጠን ጭምር)?
4.12 ፕሮጀክቱ በሙቀት፣ ብርሃን ወይም ኤሌክትሮመግኒጢሳዊ
ጨረራ ላይ የሚያደርሰዉ ቀጥተኛ እና ዋና (የመጀመሪያ
ደረጃ) ተጽዕኖ ተገልጧል (ከተቻለ በመጠን ጭምር)?
4.13 ፕሮጀክቱ በቁሳዊ እሴቶችና ታዳሽ ባልሆኑ የተፈጥሮ ሀብቶች
ላይ የሚያደርሰዉ ቀጥተኛ እና ዋና (የመጀመሪያ
ደረጃ)ተጽእኖ ተገልጧል?
4.14 ፕሮጀክቱ ባህላዊ ጠቀሜታ ባላቸዉ ቦታዎች ላይ
የሚያደርሰዉ ቀጥተኛ እና ዋና (የመጀመሪያ ደረጃ)ተጽእኖ
ተገልጧል?
4.15 ፕሮጀክቱ በመልከዓምድር ገጽታና ዉበት ላይ የሚያደርሰዉ
ቀጥተኛ እና ዋና (የመጀመሪያ ደረጃ) ተጽእኖ በአግባቡ
ተገልጧል?
4.16 በፕሮጀክቱበህብረተሰቡ አሰፋፈር፣ አኗኗ፣ ስርጭት፣ የህዝብ
ብዛት፣ የህዝብ እድገት፣ ትፍፍግ፣ ስነተዋልዶ፣ ጋብቻ፣የጤና
ሁኔታ እና ሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ላይ
የሚያደርሰዉ ቀጥተኛ እና ዋና (የመጀመሪያ ደረጃ) ተጽእኖ
ተገልጧል? (ከተቻለ በመጠን ጭምር)

ሁለተኛ ደረጃ ተጽእኖ፣ ቀጥተኛ ያልሆነ፣ ጊዜአዊ፣ ለአጭር ጊዜ፣ ቋሚ፣ የረጅም ጊዜ፣ በድንገተኛ፣ ተደማሪና አንዱ ተጽእኖ በሌላዉ ላይ
የሚያደርሰዉ (መስተጋብራዊ) ተጽእኖዎች ትንበያ
4.17 ከላይ በተዘረዘሩት አካባቢያዊ ጉዳዮች ተመስርቶ በዋና
(የመጀመሪያ ደረጃ) ተጽዕኖዎች ምክንያት የሚከሰቱ ሌሎች
ሁለተኛ ደረጃ ተጽዕኖዎች ተገልፀዋል ከተቻለ በቁጥር
(በአሃዝ)? (በአፈር አየርና ዉሃ ብክለቶች ምክንያት በእጽዋት፣
እንስሳት ወይም የተፈጥሮ መኖሪያዎች (ምቹጌ) ላይ የሚደርስ
ተጽእኖ፣ በዉሃ ሃብት ለዉጥና በዉሃ ጥራት ለዉጥ
ምክንያቶች በዉሃ አጠቃቀም ላይ የሚደርስ ተጽእኖ፣ በአፈር
መድረቅና መሰነጣጠቅ ምክንያት በመሬት ዉስጥ ባለቅሬተ-
አካል ላይ የሚደርሱ ተጽእኖዎች)
4.18 ፕሮጀክቱ በሚዘጋበት ወይም የተወሰነ ጊዜ ዋናውን ስራ
በሚሰራበት ወይም በግንባታ ወቅት የሚደርሱ
ጊዜያዊ/ለአጭር ጊዜ የሚቆዩ ተጽእኖዎች ተገልጸዋል?
4.19 ፕሮጀክቱ በግንባታ፣ ዋናውን ስራ በሚሰራበት (በማምረት
ሂደት) ወይም በሚዘጋበት ወቅት የሚደርሱ ቋሚ፣ ዘላቂ
ወይም የረዥም ጊዜ ተጽእኖዎች ተገልጸዋል?
4.20 ፕሮጀክቱ በእድሜ ዘመኑ በየጊዜዉ ወደ አካባቢ በሚለቀዉ
የበካይ ነገሮች ጥርቅም ምክንያት ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ
ተጽእኖዎች ተጠቅሰዋል?
4.21 ከአደጋዎች፣ ከአልተለመዱ ሁኔታዎች ወይም ፕሮጀክቱ
በተፈጥሮ ወይም በሰዉ ሰራሽ አደጋዎች በመጋለጡ ምክንያት
የሚፈጠሩ ተጽእኖዎች ተብራርተዋል?ከተቻለ በአሃዝ
4.22 በፕሮጀክቱ ተዛማጅ/ተጓዳኝ ስራዎች ምክንያት በአካባቢ ላይ
የሚደርሱ ተጽእኖዎች ተጠቅሰዋል? (ተዛማጅ ወይም ተጓዳኝ
ስራዎች ለፕሮጀክቱ መጋቢ መንገድ ስራና መሰረተ ልማቶች፣
ለግንባታ የሚሆኑ ቁሳቁሶችን ምሳሌ የድንጋይ፣ የጠጠር፣
የአሸዋናየአፈር ማዉጫ ቦታዎች፣ የሀይል አቅርቦትና

37
ተ.ቁ የመገምገሚያ ነጥቦች ሌላ ተጨማሪ የሚያስፈልግ መረጃ

የመረጃው
አለ

አስፈላነት
የመረጃ

በቂነት
ማምረት፣ ቆሻሻ ማስወገድ ወዘተ)
4.23 በፕሮጀክቱ ተጓዳኝ ስራዎች ምክንያት በአካባቢ ላይ
የሚደርሱ ቀጥተኛ ያልሆኑ ተጽእኖዎች ተገልጸዋል? (ተጓዳኝ
ስራዎች ማለት የፕሮጅከቱ አካል ሳይሆኑ ነገር ግን ፕሮጀክቱን
የሚያጠናክሩ ናቸዉ፡፡ ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልጉ አዳዲስ
እቃዎችንና አገልግሎቶችን ማቅረብ፣ ፕሮጀክቱን ለመደገፍ
የቤት አገልግሎቶችንና ሌሎች ንግዶችን ማቅረብ ወዘተ)
4.24 የፕሮጀክቱ ተደማሪ ተጽእኖዎችና መስተጋብራዊ ወይም
አንዱ በሌላዉ ላይ የሚያደሱት ተጽእኖዎችን ጨምሮ
ከሌሎች ነባርና አዳዲስ ፕሮጀክቶች ጋር በመሆን በአካባቢ
ላይ የሚያደርሱት ተጽእኖዎች ተገልጸዋል
4.25 የእያንዳንዱ ተጽእኖ ከመልከአ-ምድራዊ ስፋት፣ ከቆይታ ጊዜ፣
ከመከሰትድግግሞሽ፣ ወደ ነበረበት ከመመለስ እና ተጽእኖዉ
ከመከሰት እድል አንጻር ተለይተዋል?
በሰዉ ጤናና ዘላቂ ልማት ጉዳዮች ላይ ሊደርሱ የሚችሉ ተጽእኖዎችን መተንበይ
4.26 በፕሮጀክቱ በሰዉ ጤናና ደህንነት ላይ ሊደርሱ የሚችሉ
የመጀመሪያና (ዋና) ሁለተኛ ደረጃ ተጽእኖዎች ተገልጸዋል?
(ወደ አካባቢ መርዛማ ነገሮችን በመልቀቅ፣ ከፕሮጀክቱ ጋር
በተያያዙ አደጋዎች ምክንያት የሚደርሱ የጤናስጋቶች፣
ከፕሮጀክቱ ጋር በተያያዙ በበሽታ አምጭ ነፍሳቶች መለወጥ
ምክንያት የሚመጡተጽእኖዎች፣ ለጉዳት ተጋላጭ በሆኑ
ክፍሎች ላይ የሚደርሱ፣ የአኗኗር ዘየ ለዉጦች ወዘተ
የሚደርሱ ተጽእኖዎች)
4.27 በብዝሀ ህይዎት፣ በአለም የአየር ጸባይ ለዉጥና በዘላቂ ልማት
ላይ የሚደርሱ ተጽእኖዎች ተብራርተዋል?
የተጽእኖዎችን ክብደት/ደረጃ መገምገም
4.28 የተተነበዩትን ተጽእኖዎች ደረጃ/ክብደት ማሟላት
ከሚገባቸዉ የህግ ግዴታዎች አንጻር ተቃኝተዋል?
4.29 በአካባቢ ላይ ሊደርሱ የሚችሉ ተጽእኖዎችን ለመገምገም
አግባብነት ያላቸዉ የክልል፣ የፌደራል ወይም የአለም አቀፍ
የአካባቢ ደረጃዎችና የአሰራር መመሪያዎች በጥቅም ላይ
ዉለዋል?
4.30 ከአሉታዊ ተጽኖዎች በተጨማሪ አወንታዊ ተጽዕኖዎችም
ተገልጸዋል?
4.31 የእያንዳንዱ ተጽእኖ ክብደት/ደረጃ ተብራርቷል?
የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ዘዴ
4.32 ተጽእኖዎችን ለመተንበይ ጥቅም ላይ የዋሉ ዘዴዎችና ለምን
እነዚህ ዘዴዎች እንደተመረጡ እንዲሁም ያጋጠሙ ችግሮችና
4.33 የፕሮጀጅቱን ትክክለኛ ዝርዝር ሁኔታና በአካባቢ ላይ
የሚያደርሰዉን ተጽእኖ እርግጠኛ አለመሆን ለትንበያ
አስቸጋሪ ጉዳዮች መሆናቸዉ ተገልጸዋል?
4.34 የካባቢ ተጽእኖዎችን ለመተንበይ የሚያገልግሉ መረጃዎች
በሚሰበሰቡበት/በሚደራጁበት ወቅት ያጋጠሙ ችግሮች
ተለይተው ታወቀዋል ወይ፣ በጥናቱ ውጤት ላይ
የሚያስከትሉት እንድምታስ ተገልጧል?
4.35 የተጽእኖዎች ደረጃ/ክብደት መገምገሚያ መነሻዎች
ወይምመስፈርቶቹተብራርተዋል?
4.36 የአካባቢ ተጽእኖዎች የተገለጹት ሊተገበሩ የሚችሉ
የማስተሰርያ ዘዴዎችን መሰረት አድርገዉ ነዉ?ቀሪታዊ
ተጽእኖዎችስ ተገልጸዋል?
4.37 የእያንዳንዱ ተጽእኖ ግምገማ ደረጃ ለፕሮጀክቱ የይሁንታ

38
ተ.ቁ የመገምገሚያ ነጥቦች ሌላ ተጨማሪ የሚያስፈልግ መረጃ

የመረጃው
አለ

አስፈላነት
የመረጃ

በቂነት
ዉሳኔ ለማሰጠት በሚያስችል ሁኔታ ነዉ የተካሄደው? በዋና
ዋና ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ እና ጠቃሚ ያልሆኑ ወይም
የማያስፈልጉ ጉዳዮችን ያስወገደ ነዉ?
4.38 ግምገማዉ ለጉልህ ተጽእኖዎች የበለጠ ትኩረት የሰጠና
ለዝቅተኛ ተጽእኖዎች ደግሞ ዝቅተኛ ትኩረት የሰጠ ነዉ?
ሌሎች ሊከሰቱ የሚችሉ ተጽዕኖዎች ጥያቄዎች ካሉ

ክፍል 5 የተጽእኖ ማስተሰረያ/ማቅለያ መግለጫ


5.1 በየትኛዉም አካባቢ ላይ ጉልህ አሉታዊ ተጽእኖዎች
በሚኖሩበት ጊዜ ለማስተሰረያ/ለማቅለያ የሚሆኑ አማራጮች
ተብራርተዋል?
5.2 ተጽእኖዎችን ለማስተሰረይ/ለማቅለል የፕሮጀክት ባለቤቱ
ሊተገብራቸዉ ስላቀዳቸዉ ዘዴዎች በግልጽ ተብራርተዋል?
የተፅዕኖውን ጉልህነትና ክብደት ለመቀነስ የሚያመጣዉ
ለዉጥስ ተገልጧል?
5.3 ለከባድና ጉልህ ተጽዕኖችየተቀመጡየማስተሰርያ ዘዴዎች
የተዋጣላቸዉ/ዉጤታማ የመሆኑ ጉዳይ አጠራጣሪ ከሆነ
ጉዳዩ ተብራርቷል?
5.4 የፕሮጀክት ባለቤቱ የማስተሰርያ/ማቅለያ ዘዴዎችን ተግባራዊ
ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት ግልጽ ነው ወይስ የተቀመጡ
የማቅለያ ዘዴዎች የማይፈፀሙ ለይስሙላ የተቀመጡ ናቸው?
5.5 የፕሮጀክት ባለቤቱ ያቀረባቸዉን የማስተሰርያ/ማቅለያ
ዘዴዎች ለምን እንደመረጣቸዉ ምክንያቱ ተገልጧል?
5.6 የማስተሰርያ/ማቅለያ ዘዴዎችን ለመተግበር የሚመለከታቸዉ
አካላት ወጪዉን ጨምሮ በግልጽ ተቀምጧል?
5.7 አሉታዊ ተጽእኖዎችን የማስተሰረያ/የማቅለል ስራ ተግባራዊ
ማድረግ የማይቻል ከሆነ ውይም የፕሮጀክት ባለቤቱ ምንም
አይነት የማስተሰረያ/ማቅለያ ዘዴዎችን ተግባራዊ ላለማድረግ
ከመረጠ ምክንያቱ በግልጽ ተብራርቷል?
5.8 የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ አጥኝ ቡድኑ እና የፕሮጀክቱ
ባለቤት በአማራጭ ስልት ማለትም የቦታ ለዉጥ፣ የዲዛይንና
አቀማመጥ ለዉጥ፣ የአሰራር ዘዴዎችንና ሂደቶች ለዉጥ፣
የትግበራ እቅድና የአመራር ትግራ ለዉጥ እንዲሁም
ተጽእኖዎችን የማስተሰረያ ምፍትሄና በማካካስ እርምጃዎችን
በመዉሰድ አማራጮችን በሰፊዉ መዳሰሳቸዉ ወይም ግምት
ወስጥ ማስገባታቸው ግልጽ ነዉ?
5.9 ቅሪት ተጽእኖዎችን ለመከታተልና ለመቆጣጠር ቅድመ
ዝግጅቶች ተደርገዋል?
5.10 የተጽኖ ማስተሰርያ ዘዴዉ የሚያደርሰዉ ሌላ አሉታዊ
ተጽእኖ ተጠቅሷል?
ሌሎች የተጽዕኖ ማስተሰረያ/ማቅለያ ጥያቄች
ክፍል 6 አጭር ማጠቃለያ ጽሁፍ
6.1 የአካባቢ ዘገባ ሪፖርቱ አጭር የማጠቃለያ ጽሁፍ አካቷል?
6.2 አጭር የማጠቃለያ ጽሁፉ ስለፕሮጀክቱ አጭርና ግልጽ የሆነ
መግለጫ፣ የፕሮጀክቱን አካባቢ፣ ፕሮጀክቱ በአካባቢ ላይ
ያለዉን ተጽእኖ እና ለተጽእኖዎች የማቅለያ ዘዴዎችን ያካተተ
6.3 የማጠቃለያ አጭር ጽሁፉ ጉልህ አጠራጣሪ የሆኑ ጉዳዮች ስለ
ፕሮጀክቱና ስለሚያስከትላቸው አካባቢዉ ተጽእኖዎች
ያብራራል?
6.4 የማጠቃለያ አጭር ጽሁፉ የፕሮጀክቱን የመጽደቅ ሂደትና

39
ተ.ቁ የመገምገሚያ ነጥቦች ሌላ ተጨማሪ የሚያስፈልግ መረጃ

የመረጃው
አለ

አስፈላነት
የመረጃ

በቂነት
የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ጥናት ያለዉን ሚናያብራራል?
6.5 የማጠቃለያ አጭር ጽሁፉ የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ጥናት
ስልቱን በተመለከተ አጭር ማብራራያ አለዉ?
6.6 የማጠቃለያ አጭር ጽሁፉ የተጻፈዉ በርካታ ጊዜ
ወይምበድግግሞሽ ሙያዊ ቃላትን፣ ዝርዝር መረጃዎችን እና
ሳይንሳዊ ትንታኔዎችንመጠቀምን ባስወገደ መልኩ ነዉ?
6.7 የማጠቃለያ ጽሁፉ በፕሮጀክቱ ለሚጎዱና ፍላጎቱ ላላቸዉ
አባላት በቀላሉ ሊረዱት በሚችሉት ሁኔታ ተፃፈ ወይም
ተደራሽ ነዉ ወይ?
በማጠቃለያ አጭር ጽሁፍ ሌሎች ጥያቄዎች

7 ክፍል 7 የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ጥናቱ


አቀራርብ/አጻጻፍ ጥራት
7.1 በጥናቱ ዉስጥ የተጠቀሱት አካባቢያዊ መረጃዎች በአንድ
ወይም ከዚያ በላይ በሚሆኑ የመረጃ ምንጮች በግልጽ
የሚገኙ ናቸዉ?
7.2 የሰነዱ ይዘት ማዉጫ በሰነዱ መጀመሪያ ገጾች ላይ ነዉ?
7.3 የጥናቱ ሂደት/ቅደም ተከተል በግልጽ ተጽፏል?
7.4 የጥናቱ አቀራረብ አጭርና ግልጽ ሆኖ አላስፈላጊ የሆኑ
መረጃዎችን ያስወገደ ነዉ?
7.5 የጥናቱ ጽሁፍ ጠቃሚ የሆኑ ሰንጠረዥ፣ ምስል፣ ካርታ፣
ፎቶዎች እና ሌሎች ስዕላዊ መግለጫዎችን ተጠቅሟል?
7.6 ሁሉም ትንታኔዎችና ማደማደሚያዎች በመረጃና
በማስረጃበበቂ ሁኔታ የተደገፉ ናቸዉ?
7.7 ሪፖርቱ በዋናዉን የጥናት ጽሁፍ ውስጥ ያሉ ዋና ይዘቶችን
አንብቦ መረዳት ሳያስፈልግ በርካታ መረጃዎችን ለማግኘት
እንዲቻል እዝሎችን አካቷል ወይ?
7.8 አንባቢዉ መረጃዎችን በሰነዱ ዉስጥ በቀላሉ ሊያገኝ
እንዲችል ሰነዱ በአግባቡ የተደራጀና በግልጽ የተዋቀረ ነዉ?
7.9 ለሁሉም የመረጃ ምንጮች ማጣቀሻዎች በአግባቡ
7.10
ተገልጸዋል ?
በአጠቃላይ በሰነዱ ዉስጥ ሙያዊ ቃላቶች አጠቃቀም
ወጥነት ባለው መልኩ ጥቅም ላይ ዉለዋል?
7.11 ሰነዱ ሲነበብ በውስጡ የተገለጹት ርዕሰ
ጉዳዮችንየማይጣረሱና እርስ በርስ የመደጋገፍና እንደ አንድ
ሙሉ ሰነድ ማየት በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ ነው?
7.12 የሰነዱ ጽሁፍ አገላለጹ ሚዛናዊ እንዲሁም አድሎ የሌለበት፣
ያልተዛባናዓላማውን ያልሳተ ነዉ?
የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ጥናቱ አቀራርብ/አጻጻፍ ጥራት ላይ ሌሎች ጥያቄዎች

40
18.3.2 የተፅዕኖ ግምገማ ሪፖርቱን ለመገምገም የሚጠቅሙ ማብራሪያዎች
1) በሰነዱ ዉስጥ አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች መሟላታቸውን ለማረጋገጥ ሪፖርቱን በፍጥነትና በግርድፉ ማንበብ ይገባል፣
2) እያንዳንዱ የመገምገሚያ ጥያቄ ለፕሮጀክቱ አግባብነት ያለው መሆኑን ማረጋገጥና አግባብነት ካለዉ በመገምገሚያ ሰንጠረዡ
ረድፍ ሁለት ላይ አዎ በማለት መጻፍ ይገባል፤
3) ፕሮጀክቱን በተመለከተ በጣም አስፈላጊ የሆኑና በመጠይቁ ያልተካተቱ ጉዳዮች ካሉ በመገምገሚያ ቅጹ መጨረሻ ረድፍ ላይ
ማካተት ይቻላል፣
4) የመገምገሚያ ጥያቄዉ ከፕሮጀክቱ ጋር አግባብነት መኖሩ ከተረጋገጠ ሰነዱን በጥልቀት በመገምገም ከጥያቄዉ ጋር ተያያዥነት
ያለዉ ጉዳይ በአግባቡና በበቂ ሁኔታ የተገለፀ መሆኑን ማረጋገጥ ይገባል፡፡ ሰነዱ ይህን ጥያቄ አሟልቶ ከተገኘ “አዎ” ወይም
አሟልቶ ካልተገኘ ደግሞ “አይደለም” በማለት በመገምገሚያ ሰንጠረዡ 3 ኛ ረድፍ ላይ መሞላት አለበት፣
5) የመረጃውን በቂነት በማረጋገጡ ሂደት ዉስጥ ያልተካተቱ በጣም አስፈላጊ የሆኑ ጉዳዮችና ለውሳኔ አሰጣጥ አስፈላጊ የሆኑ
ነጥቦች ካሉ እንዲካተቱ መደረግ አለበት፣
6) የቀረበው የጥናት ዘገባ በቂ ከሆነ ገምጋሚ ባለሙያው የፕሮጀክት ባለቤቱን ተጨማሪ መረጃ እንዲያቀርብ አይጠይቅም፣
7) የመገምገሚያ ቅፁ በሚዘጋጅበት ጊዜ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ነጥቦች
1) ዉሳኔ ሰጭዉ አካል ፕሮጅክቱን ለማጽደቅ የሚጠቀምባቸው የህግ ማዕቀፎችና ውሳኔ ለመስጠት የሚፈልጋቸው
ነጥቦች መካተታቸውን፣
2) የፕሮጀክቱ ይሁንታ ፈቃድ አሰጣጥ ሂደት የተጽዕኖ ዘገባ ግምገማ መርህን መሰረት ያደረገ ወይም ዝርዝር
የፕሮጀክቱን ዲዛይን መሰረት ያደረገ መሆኑን፣
3) የፕሮጀክቱን ትልቅነትና ዉስብስብነት እንዲሁም የፕሮጀክቱ አካባቢ የተጋላጭነት ሁኔታ ግምት ውስጥ ያስገባ
መሆኑን፣
4) በአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት ዘገባ ውስጥ የተጠቀሱት አካባቢያዊ ጉዳዮች ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልጋቸዉ ከሆነ
በአግባቡ መተንተናቸውና ትኩረት የተሰጣቸው መሆኑን
5) በፕሮጀክቱ ምክንያት ጉዳት የሚደርስባቸዉና የሚያገባቸዉ የማህበረሰብ ክፍሎች አስተያየትና የተነሱ አወዛጋቢ
ጉዳዮች መካተታቸውን፣
6) የመጠይቁ ምላሽ “አይደለም” ከሆነ ወደፊት መታየት የሚገባቸዉን ጉዳዮች ማሰብና በቅጹ ረድፍ አራት ላይ
ማስታዎሻ መጻፉን ማረጋገጥ፤
8) ፕሮጀክቱን የማፅደቅ የውሳኔ አስተያየት የሚሰጠው በመጨረሻ ደረጃ ላይ የተሰጡት ነጥቦች ተደምረው በሚገኘዉ ዉጤት
መሰረት ይሆናል፡፡

18.4 የአካባቢ አያያዝ ሪፖርት ማድረጊያ ቅጽ


የሪፓርት ቁጥር -------------- ሪፓርቱ የተጠናቀረበት ቀን --------------
ሪፖርቱን ያጠናቀረው ባለሙያ/ዎች ስም --------------------------------------------------------
ክፍል-1፣ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ መግለጫ
1. የፕሮጀክቱ ሥም፣ 6. የአካባቢ ይሁንታ የተሰጠበት ቀን፣
2. የፕሮጀክቱ ባለቤት ሥም፣ 7. የአካባቢ ይሁንታ የተሰጠበት ቦታ፤
3. ፕሮጀክቱ ሥራ የጀመረበት ቀን፣ 8. የአካባቢ ይሁንታ ምዝገባ ቁጥር፣
4. የፕሮጀክቱ ቦታ ስፋት፣ 9. የፕሮጀክቱ የአካባቢ ተጽእኖ ሰነድ ቁጥር፣
5.ፕሮጀክቱ የሚገኝበት 10. የፕሮጀክቱ ሰራተኞች ብዛት፡-

41
ዞን፡….. ወረዳ፡…. ቀበሌ/ልዩቦታ፡….. ቋሚ፡…….ጊዜያዊ (አማካይ በወር)፡….. ድምር…..
ክፍል-2፣ በአካባቢ አያያዝ ዕቅድ መሠረት የታቀዱ የማቃለያ እርምጃዎች አፈጻጸም ማጠቃለያ ሪፖርት ማድረጊያ ቅጽ
ተ.ቁ የፕሮጀክቱ የታቀዱ የተጽዕኖ ማቃላያ ማቃላያ እርምጃዎች ክትትል ውጤት ለልዩነት
ምዕራፍ እርምጃዎች አመላካቾች የተደረገበት ቀን ምክንያት
የተገኘ የሚጠበቅ
(መሆን
የነበረት)

ክፍል-3፣ አጠቃላይ አስተያየት

1. በተዘጋጀው የአካባቢ ተጽእኖ ጥናት ዘገባ ውስጥ ያልተለዩ/አዲስ ተጽእኖዎች ተከስተው ከሆነ፡-
1. የተጽእኖው አይነትና የተከሰተበት
ምክንያት-------------------------------------------------------------------------------------------------------
------------------------------------------------------------------ለተከሰተው ተጽእኖ የማቃለያ እርምጃ
ተወስዶ ከሆነ ይገለጽ
-----------------------------------------------------------------------------------------------------------------
-----------------------------------
2. ለተከሰተው ተጽእኖ የማቃለያ እርምጃ ካልተወሰደ ምክንያቱ ይገለጽ
-----------------------------------------------------------------------------------------------------------------
--------------------------
3. ለተከሰተው ተጽእኖ የታቀደዉ የማቃለያ እርምጃ
አይነት----------------------------------------------------------------------------------------------------------
------------------------------------------------
4. የተጽእኖ ማቃለያ እርምጃው የሚከናወንበት ጊዜ፣ ማን እንደሚያከናውነውና መከናወኑን እንዴት ክትትል
እንደሚደረግ ይገለጽ
-----------------------------------------------------------------------------------------------------------------
--------------------------------------------------------------
5. ከላይ በክፍል 2 የተገለጸውን መሰረት በማድረግ በቀጣይ መሻሻል ባለባቸው ወይም መካሄድ ባለባቸው
ጉዳዮች ላይ ምክረ-ሀሳብ (Recommendation) ቀጥሎ ይቅረብ።
-----------------------------------------------------------------------------------------------------------------
------------------
6. ሪፖርቱን በሚመለከተዉ የፕሮጀክት ሃላፊ/ባለቤት በማህተምና በፊርማ ተረጋግጦ መቅረብ ይኖርበታል፡፡

ሪፖርቱን ያጠናቀረው/ቱ ባለሙያዎች ስም---------------------------------------ኃላፊነት---------------


ፊርማ---------------------- ቀን------------------------
ሪፖርቱን ያረጋገጠዉ ኃላፊ ስም ----------------------------ፊርማ--------------------- ቀን------------

ማሳሰቢያ ፡- የቀረበዉን ሪፖርት ትክክለኛነት በባለስልጣኑ የአካባቢ ተቆጣጣሪ ባለሙዎች የሚረጋገጥ ይሆናል፡፡

18.5 የአማካሪ ባለሙያዎችና ድርጅቶች መመዘኛ መስፈርት


የአካባቢ አማካሪ ባለሙያዎችና ድርጅቶች ምልመላና መረጣ መገምገሚያና የነጥብ አሰጣጥ ሂደቱ የሚከተሉትን
መስፈርቶች የያዘ ይሆናል፡-

Table 2 5 ቱ ዋና ዋና የመመዘኛ መስፈርቶች

ተ.ቁ የመመዘኛ መስፈርት የመመዘኛው ምርመራ

42
ክብደት (ከ 100%)
1 የትምህርት ዝግጅት 25
2 የስራ ልምድ 25
3 የማማከር፣ የስልጠናና የአካባቢ ግምገማ/ምርመራ የስራ 25
ልምድ
4 የጥናትና ምርምር የስራ ልምድ 20
5 የህትመቶች 5
ድምር 100

1. የትምህርት ዝግጅት
አመልካቹ/ቿ በዕዝል 15.6 ከተዘረዘሩት የትምህርት መስኮች ቢያንስ በአንዱ የመጀመሪያ ዲግሪ ሊኖረው ይገባል፡፡
የትምህርት ዝግጅቱ በሚከተለው ሁኔታ ነጥብ ይሰጠዋል፡-
 የመጀመሪያ ዲግሪ ያለው/ያላት ………………………………………….. 19 ነጥብ
 ሁለተኛ ዲግሪ ያለው/ያላት ……………………………………………… 21 ነጥብ
 ሶስተኛ ዲግሪ ያለው/ያላት ………………………………………………. 25 ነጥብ
2. የስራ ልምድ ………………………………………………………………………….. 25
አመልካቹ/ቿ በአካባቢ አማካሪነት ሙያ ለመወዳደር ወይም ለመሳተፍ በመረጠው/ችው የአማካሪነት የሙያ ዘርፍ
ለድግሪ ቢያንስ 5 ዓመት፣ ለማስተር ቢያንስ 3 ዓመት እና ለዶክትሬት ድግሪ ቢያንስ 2 ዓመት አግባብነት ያለው
የሥራ ልምድ ሊኖረው/ራት ይገባል፡፡ ለእያንዳንዱ ዓመት ቀጥተኛ የስራ ልምድ 2.5 ነጥብ ይሰጣል፡፡ በመሆኑም 10
ዓመትና ከዚያ በላይ ቀጥተኛ የስራ ልምድ ካለው/ካላት 25 ነጥብ ይሰጣል፡፡ ቀጥተኛ የስራ ልምድ ላልሆኑት
ተጨማሪ ዓመታት የስራ ልምድ ደግሞ ለእያንዳንዱ ዓመት 0.5 ነጥብ ይሰጣል፡፡

“ቀጥተኛ የስራ ልምድ የሚያዘው የአካባቢ አማካሪነት ፈቃድ ከሚያወጣበት የአማካሪነት የሙያ ዘርፍ ጋር ቀጥተኛ
የተግባር ግንኙነት ያለው ሆኖ በዲፕሎማና ከዚያ በላይ ባለ የትህምርት ዝግጅት የተገኘ የሰራ ልምድ ብቻ ይሆናል፡፡
በከፍተኛ አመራር፣ በመካከለኛ አመራርና በባለሙያነት ደረጃ ዘርፉን ከሚመለከቱ ድርጅቶችና ተቋማት የተገኘ
የስራ ልምድና በዲፕሎማና በድግሪ ደረጃ በመምህርነት የተገኘ የስራ ልምድ ቀጥተኛ የሥራ ልምድ ተብሎ ይያዛል፡፡
3. የማማከር፣ የስልጠናና የአካባቢ ግምገማ/ምርመራ የስራ ልምድ………………………. 25
1. በማማከር አገልግሎት የተሳተፈባቸው ልምዶች………………….………………7.5
2. ስልጠና በመሳተፍ/ በመስጠት የተሳተፈባቸው ልምዶች …………………….…7.5
3. በአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማና ምርመራ የተሳተፈባቸው ……………………………10

3.1 በማማከር አገልግሎት የተሳተፈባቸው ልምዶች


የሙያ ፈቃድ ለማውጣት በጠየቀበት የሙያ ዘርፍ በአካባቢ የማማከር አግልግሎት አንድ የፀደቀ የአካባቢ ተፅዕኖ
ግምገማ ሰነድ ካለው/ካላት 1.5 ነጥብ ይሰጣል፤ሁለት የፀደቀ የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሰነድ ካለው/ካላት 3 ነጥብ
ይሰጣል፤ ሶስት የፀደቀ የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሰነድ ካለው/ካላት 4.5 ነጥብ ይሰጣል፤አራት የፀደቀ የአካባቢ ተፅዕኖ

43
ግምገማ ሰነድ ካለው/ካላት 6.0 ነጥብ ይሰጣል፣አምስትና ከዚያ በላይ የፀደቀ የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሰነድ
ካለው/ካላት 7.5 ነጥብ ይሰጣል

3.2. ስልጠና በመሳተፍ/በመስጠት የተሳተፈባቸው ልምዶች


የአማካሪነት የብቃት ማረጋገጫ እንዲሰጠው ከጠየቀበት ዘርፍ ጋር በቀጥታ የሚገናኝ የአንድ ቀን ስልጠና
ከአሰለጠነ/ች ወይንም ከሰለጠነ/ች 2.5 ነጥብ ይሠጣል፣ በድግግሞሽ የሁለት ቀናት ስልጠና ከአሰለጠነ/ች ወይንም
ከተሳተፈ/ች 5 ነጥብ ይሠጣል፣በድግግሞሽ ለሶስት ቀናትና ከዚያ በላይ ስልጠና ከሰጠ/ች ወይንም ከተሳተፈ/ች 7.5
ነጥብ ይሠጣል፡፡ የአማካሪነት ፈቃድ ከተጠየቀበት ዘርፍ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ያለውን ኮርስ ለማስተማሩ መረጃ
የሚያቀርብ የከፍተኛ ተቋማት መምህር ሙሉ ነጥብ ይሰጠዋል፡፡

3.3. የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ/ ምርመራ


የአካባቢ ተጽዕኖ ግምገማ ሪፖርት ግምገማ ወይም የአካባቢ ምርመራ ማካሄድ ለአንድ ፕሮጄክት ለአንድ ሰነድ 2
ነጥብ ይሰጣል፡፡ አምስትና ከዚያ በላይ የሆኑ የአካባቢ ተጽእኖ ግምገማ ሪፖርቶችን የገመገመ ወይም የፕሮጀክቶች
ምርመራ ያካሄደ 10 ነጥብ ብቻ ይሰጣል፡፡

4. የጥናትና ምርምር የስራ ልምድ……………………………………………………..20 ነጥብ


ባለሙያው ካመለከተበት የአማካሪነት የሙያ ፈቃድ ጋር የሚገናኝ አንድ የጥናት/የምርምር ሰነድ ያዘጋጀ/ች
ለመሆኑ/ኗ ህጋዊ ማስረጃ የሚያቀርብ/የምታቀርብ ከሆነ 4.0 የሚሰጥ ሲሆን 5 እና ከዚያ በላይ ለሆኑ
የጥናት/ምርምር ሰነዶች ማስረጃ ከቀረበ 20 ነጥብ ብቻ ይሰጣል፡፡

5. ህትመቶች …………………………………………………………………………. 5 ነጥብ


የአማካሪነት ፈቃድ በተጠየቀበት የሙያ ዘርፍ የታተሙ የጥናት ፅሁፎች በጋዜጣ ወይም በመጋዚንስ/መፅሄት ላይ
የወጡ እያንዳንዳቸው ፅሁፎች አንዳንድ ነጥብ ይሰጣቸዋል፡፡ በአካባቢ ጥበቃ ዙሪያ ስልጠና ለመስጠት የተዘጋጁ
የስልጠና ማንዋሎች ወይም የታተሙ የምርምር ፅሁፎች እያንዳንዳቸው አንዳንድ ነጥብ ይሰጣቸዋል፡፡
ለማንኛውም ሲምፖዚየም፣ ኮንፈረንስና ጥናቶች የቀረቡ የጥናት ፅሁፍ ለእያንዳንዱ ሁለት ሁለት ነጥብ ይሰጣል፡፡
ለማኝኛውም ከአካባቢ ጥበቃ አንፃር አግባብነት ላለው የታተመ መፅሃፍ 5 ነጥብ ይሰጠዋል፡፡ ይሁንና የሚሰጠው
አጠቃላይ ነጥብ ድምር ከ 5 መብለጥ የለበትም፡፡ ከአካባቢ ጥበቃ ጉዳይ ውጭ ህትመቶች ላሉት ለእያንዳንዱ
ህትመት 0.5 ነጥብ ይሰጣል፡፡ ለዚህም የሚሰጠው አጠቃላይ ነጥብ ድምር ከ 5 መብለጥ የለበትም፡፡

44
18.6 ለአካባቢ ተፅዕኖ ጥናትና ኦዲት አገልግሎት የአማካሪ ባለሙያዎች መስፈርቶች
ተ የብቃት ማረጋገጫ የሚሰጠው የትምህርት ደረጃ አግባብነት ያለው
. የሚሰጥባቸው የአካባቢ የብቃት የሥራ ልምድ
ቁ ዘርፍ ጉዳዮች ደረጃ (በአመት)
ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ጀማሪ በኢኮኖሚክስ፣ ኢንቫሮንመንታል ኢኮኖሚክስ፣ ለመጀመሪያ ድግሪ፡ 5
1 ተንታኝ ባለሙያ አማካሪ አግሪካልቸርራል ኢኮኖሚክስ ወይም ተመሳሳይ መስክ ዓመትና በላይ፣
ቢያንስ የመጀመሪያ ድግሪ ያለው ለሁለተኛ ድግሪ፡ 3
ዓመትና በላይ
ከፍተኛ በኢኮኖሚክስ፣ ኢንቫሮንመንታል ኢኮኖሚክስ፣ ለዶክትሬት ድግሪ፡ 1
አማካሪ አግሪካልቸርራል ኢኮኖሚክስ ወይም ተመሳሳይ መስክ ዓመትና በላይ
ቢያንስ የመጀመሪያ ድግሪ ያለው
2 የማህበራዊ ጉዳዮች ጀማሪ በሶሾሎጂ፣ በሶሻል ስተዲስ፣ ሶሻል ዎርክስ፣ ሶሻል ለመጀመሪያ ድግሪ፡ 5
ተንታኝ ባለሙያ አማካሪ አንትሮፖሊጂ ወይም ተመሳሳይ መስክ ቢያንስ የመጀመሪያ ዓመትና በላይ፣
ድግሪ ያለው ለሁለተኛ ድግሪ፡ 3
ዓመትና በላይ
ከፍተኛ በሶሾሎጂ፣ በሶሻል ስተዲስ፣ ሶሻል ዎርክስ፣ ሶሻል
ለዶክትሬት ድግሪ፡ 1
አማካሪ አንትሮፖሊጂ ወይም ተመሳሳይ መስክ ቢያንስ የመጀመሪያ ዓመትና በላይ
ድግሪ ያለው
3 የአካባቢ ጤና ባለሙያ ጀማሪ በአካባቢ ጤና፣ በአካባቢ ሳይንስ፣ የሥራ አካባቢ ጤንነትና ለመጀመሪያ ድግሪ፡ 5
አማካሪ ደህንነት ወይም ተመሳሳይ መስክ ቢያንስ የመጀመሪያ ድግሪ ዓመትና በላይ፣
ያለው ለሁለተኛ ድግሪ፡ 3
ዓመትና በላይ
ከፍተኛ በአካባቢ ጤና፣ በአካባቢ ሳይንስ፣ የሥራ አካባቢ ጤንነትና
ለዶክትሬት ድግሪ፡ 1
አማካሪ ደህንነት ወይም ተመሳሳይ መስክ ቢያንስ የመጀመሪያ ድግሪ ዓመትና በላይ
ያለው
4 የብዝሐ ሕይወት እና ጀማሪ በብዝሃ ሕይወት፣ በደን/ዱር እንስሳት/ እንስሳት እርባታ፣ ለመጀመሪያ ድግሪ፡ 5
የስርዓተ-ምህዳር አማካሪ በሥነ-ሕይወት በእጽዋት /በአግሮኖሚ ወይም ተመሳሳይ ዓመትና በላይ፣
ተንታኝ ባለሙያ መስክ ቢያንስ የመጀመሪያ ድግሪ ያለው ለሁለተኛ ድግሪ፡ 3
ዓመትና በላይ
ከፍተኛ በብዝሃ ሕይወት፣ ስነ-ምህዳር በደን/ዱር እንስሳት/ እንስሳት
ለዶክትሬት ድግሪ፡ 1
አማካሪ እርባታ፣ በሥነሕይወት በእጽዋት ሳይንስ /በአግሮኖሚ ዓመትና በላይ
ወይም ተመሳሳይ መስክ ቢያንስ የመጀመሪያ ድግሪ ያለው
5 የውሃ ሀብት አጠቃቀም ጀማሪ በውሃ ሀብት አጠቃቀም፣ ተፈጥሮ ሃብት አያያዝ፣ የውሃ ለመጀመሪያ ድግሪ፡ 5
አጥኚ ባለሙያ አማካሪ ምህንድስና፣ የከርሰ ምድር ጥናት ወይም ተመሳሳይ መስክ ዓመትና በላይ፣
ቢያንስ የመጀመሪያ ድግሪ ያለው ለሁለተኛ ድግሪ፡ 3
ዓመትና በላይ
ከፍተኛ በውሃ ሀብት አጠቃቀም፣ ተፈጥሮ ሃብት አያያዝ፣ የውሃ
ለዶክትሬት ድግሪ፡ 1
አማካሪ ምህንድስና፣ የከርሰ ምድር ጥናት ወይም ተመሳሳይ መስክ ዓመትና በላይ
ቢያንስ የመጀመሪያ ድግሪ ያለው
6 የአካባቢ ብክለት ተንታኝ ጀማሪ በአካባቢ መሀንዲስ፣ ኬሚካል መሃንዲስ፣ በአካባቢ አያያዝ፣ ለመጀመሪያ ድግሪ፡ 5
ባለሙያ አማካሪ በአካባቢ ሳይንስ፣ ኬሚስትሪ ወይም ተመሳሳይ መስክ ዓመትና በላይ፣
ቢያንስ የመጀመሪያ ድግሪ ያለው ለሁለተኛ ድግሪ፡ 3
ዓመትና በላይ
ከፍተኛ በአካባቢ መሀንዲስ፣ ኬሚካል መሃንዲስ፣ በአካባቢ አያያዝ፣
ለዶክትሬት ድግሪ፡ 1
አማካሪ በአካባቢ ሳይንስ፣ ኬሚስትሪ ወይም ተመሳሳይ መስክ ዓመትና በላይ
ቢያንስ የመጀመሪያ ድግሪ ያለው
7 የሙቀት አማቂ ጋዝ ጀማሪ በአየር ንብረት ለውጥ፣ በኬሚስትሪ፣ በአካባቢ ሳይንስ ለመጀመሪያ ድግሪ፡ 5
ልቀት ተንታኝ ባለሙያ አማካሪ በአካባቢ ጤና ወይም ተመሳሳይ መስክ ቢያንስ የመጀመሪያ ዓመትና በላይ፣
ድግሪ ያለው ለሁለተኛ ድግሪ፡ 3
ዓመትና በላይ
ከፍተኛ በአየር ንብረት ለውጥ፣ በኬሚስትሪ፣ በአካባቢ ሳይንስ
ለዶክትሬት ድግሪ፡ 1
አማካሪ በአካባቢ ጤና ወይም ተመሳሳይ መስክ ቢያንስ የመጀመሪያ ዓመትና በላይ
ድግሪ ያለው
ከላይ ከተዘረዘሩት የትምህርት ዝግጅቶች በተጨማሪ የሙያ ዘርፎችን ትምህርት ዝግጅትን በሚመለከት የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
በአጸደቀው አግባብነት ባለው የትምህርት ዝግጅት መመሪያ መሰረት የሚፈጸም ይሆናል

45
18.7 ለአካባቢ ተፅዕኖ ጥናትና ኦዲት አገልግሎት የአማካሪ ድርጅቶች መስፈርቶች
ለአማካሪው አማካሪው ድርጅት የሚያስፈልጉት የሚሰማራባቸው ሌሎች መስፈርቶች
ድርጅት ባለሙያዎች የአካባቢና
ተ.ቁ
የሚሰጠው የሙያ ማህበረሰብ ተፅዕኖ
ደረጃ ዝርዝር ብዛት ጥናት መስኮች
ደረጃ
1 I የኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ከፍተኛ በክልል ምድብ  ስራ አስኪያጁ ከፍተኛ
ተንታኝ ባለሙያ አማካ 1 የተዘረዘሩትን አማካሪ መሆን አለበት
ሪ ጨምሮ ሌሎች ሙሉ  ስራ አስኪያጁን ጨምሮ
የማህበራዊ ጉዳዮች ከፍተኛ የአካባቢ ተፅዕኖ ቢያንስ ሁለት ቋሚ
ተንታኝ ባለሙያ አማካ 1 ግምገማ ሰራተኞች
ሪ የሚያስፈልጋቸውን  መነሻ ካፒታል ቢያንስ 100
የአካባቢ ጤና ተንታኝ ጀማሪ ፕሮጅክቶች ዝርዝር ሺ ብር
ባለሙያ አማካ 1 የጥናት ዘገባ  የመስሪያ ቦታ/ቢሮ ቢያንሰ
ሪ ያዘጋጃል፤ እንዲሁም
20 ካሬ ሜትር
የብዝሐ ሕይወት እና ከፍተኛ በምድብ ያልተካተቱ
ትልልቅ  የቢሮ የጽህፈት
የስርዓተ-ምህዳር አማካ 1
ፕሮጅክቶችን መሳሪያዎች
ተንታኝ ሪ
ዝርዝር የጥናት ዘገባ /ኮምፒዩተሮች
የውሃ ሀብት አጠቃቀም ጀማሪ
1 ያዘጋጃል፤ ሊኖሩት ይገባል
ተንታኝ ባለሙያ አማካ

የአካባቢ ብክለት ከፍተኛ 1
ተንታኝ ባለሙያ አማካ

የሙቀት አማቂ ጋዝ ልቀት ከፍተኛ 1
ተንታኝ ባለሙያ አማካ

2 II የኢኮኖሚያ ጉዳዮች ጀማሪ በዞን ምድብና ከዚያ  ስራ አስኪያጁ ከፍተኛ


ተንታኝ ባለሙያ አማካ 1 በታች የተመደቡ አማካሪ መሆን አለበት
ሪ ሙሉ የአካባቢ ተፅዕኖ  ስራ አስኪያጁን ጨምሮ
የማህበራዊ ጉዳዮች ጀማሪ ግምገማ ቢያንስ ሁለት ቋሚ
ተንታኝ ባለሙያ አማካ 1 የሚያስፈልጋቸውን ሰራተኞች
ሪ ፕሮጅክቶች ዝርዝር  መነሻ ካፒታል ቢያንስ 50
የአካባቢ ጤና ተንታኝ ጀማሪ የጥናት ዘገባ ሺ ብር
ባለሙያ አማካ 1 ያዘጋጃል፤ እንዲሁም  የመስሪያ ቦታ/ቢሮ ቢያንሰ
ሪ በምድብ ያልተካተቱ
20 ካሬ ሜትር
የብዝሐ ሕይወት እና ጀማሪ መካከለኛና ከዚያ
 የቢሮ የጽህፈት
የስርዓተ-ምህዳር አማካ 1 በታች ያሉ
መሳሪያዎች/ኮምፒዩተ
ተንታኝ ሪ ፕሮጅክቶችን
ዝርዝር የጥናት ዘገባ ሮች
የውሃ ሀብት አጠቃቀም ጀማሪ
ባለሙያ አማካ 1 ያዘጋጃል፤

የአካባቢ ብክለት ጀማሪ 1
ተንታኝ ባለሙያ አማካ

የሙቀት አማቂ ጋዝ ልቀት ጀማሪ 1
ተንታኝ ባለሙያ አማካ

በደረጃ I ፈቃድ ያገኘ አማካሪ ድርጅት ከፍተኛ ድርጅት ሲሆን የማንኛውንም ፕሮጀክት የአካባቢ ተጽዕኖ
ጥናት ዘገባ ማዘጋጀት ይችላል፡፡ በደረጃ II የአማካሪነት ፈቃድ ያገኘ ድርጅት በደረጃ II የተዘረዘሩ
ፕሮጀክቶችን ብቻ የአካባቢ ተጽዕኖ ጥናት ዘገባ ማዘጋጀት ይኖርበታል፡፡

46
18.8 ማመልከቻ ቅጾች

18.8.1 አዲስ የአማካሪነት ፍቃድ የሚያወጡ ባለሙያዎች የሚያመለክቱበት ቅጽ

ሙሉ ስም …………………………………………………………………
አድራሻ
ክልል…………………………ዞን…………………………………
ወረዳ…………………………ከተማ……………………………
ክፍለ ከተማ……………...…..ቀበሌ………………………..የቤ.ቁ……………………….
የቢሮ ስልክ ………………………ሞባይል………………………ፋክስ……………………
ኢ-ሜይል ………………………………………………………
አሁን የሚሰሩበት መስሪያ ቤት……………………………………………
ስም፡ ……………………………………………
አድራሻ፡……………………………………………
1. የትምህርት ደረጃ
ተ.ቁ የተማሩበት ኮሌጅ/ ዩኒቨርስቲ የትምህርት መስክ የዲግሪ ደረጃ
ስም (የመጀመሪያ፣ሁለተኛ፣
ዶክትሬት)

2. የስራ ልምድ
ተ.ቁ የስራ ሃላፊነት የሰሩበት ጊዜ የስሩበት መስሪያ ቤት ስምና አድራሻ
ከ እስከ

3. የአጭር ጊዜ ስልጠናዎች (መሰማራት ከሚፈልጉት ዘርፍ ጋር ግንኙነት ያለው)


………………………………………………………………………………………………
………………………………………………………………………………………………
4. የብቃት ማረጋገጫ ማግኘት የሚጠይቁበት የአካባቢ ዘርፍ ጉዳዮች
1. የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናት/የአካባቢ ኦዲት
2. የአካባቢ ኦዲት
3. የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናት
5. የብቃት ማረጋገጫ ማግኘት የሚጠይቁበት ዝርዝር የአካባቢ ዘርፍ
ጉዳይ………………………………………….

47
6. የጠየቁት የብቃት ደረጃ ------------------------
1) ጀማሪ አማካሪ
2) ከፍተኛ አማካሪ
[

7. የሚከተሉትን መረጃዎች ከቅፁ ጋር አብረው ያያይዙ


1) የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ
2) የትምህርት ማስረጃ ከአንድ ፎቶ ኮፒ ጋር
3) የዘረዘሩትን የሥልጠና ሰርተፊኬት ፎቶ ኮፒ ጋር
4) ሁለት ጉርድ ፎቶግራፍ
5) የተዘጋጁ ዘገባዎችና ዘገባዎቹን ማዘጋጀትዎን የሚስረዳ መረጃ (ጀማሪ አማካሪ-ደረጃ 1
አመልካቾችን አይመለከትም)
6) የሥራ ልምድ ከአንድ ፎቶ ኮፒ ጋር
7) አንድ ፎቶ ግራፍ
የአመልካች ስም………………………………ፊርማ ……………….ቀን …………………...

18.8.2 አማካሪ ባለሙያዎች የእድሳት አገልግሎት ለማግኘት የሚያመለክቱበት ቅጽ

ሙሉ ስም …………………………………………………………………
አድራሻ

48
ክልል…………………………ዞን…………………………………
ወረዳ…………………………ከተማ……………………………
ክፍለ ከተማ……………...…..ቀበሌ………………………..የቤ.ቁ……………………….
ስልክ የቢሮ………………………ሞባይል………………………ፋክስ……………………
ኢ-ሜይል………………………………………………………
አሁን የሚሰሩበት መስሪያ ቤት
ስም፡ --------------------------------------------------
አድራሻ፡
1. የትምህርት ደረጃ
ተ.ቁ የተማሩበት ኮሌጅ/ ዩኒቨርስቲ የትምህርት መስክ የዲግሪ ደረጃ
ስም

2. የስራ ልምድ
ተ.ቁ የስራ ሃላፊነት የሰሩበት ጊዜ የስሩበት መስሪያቤት ስምና አድራሻ
ከ እስከ

3. የአጭር ጊዜ ስልጠናዎች (መሰማራት ከሚፈልጉት ዘርፍ ጋር ግንኙነት ያለው)


…………………………………………………………………………………………
…………………………………………………………………………………………
……
4. የብቃት ማረጋገጫ ማግኘት የሚጠይቁበት የአካባቢ ዘርፍ ጉዳዮች
1) የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናት
2) የአካባቢ ኦዲት
5. የጠየቁት የብቃት ደረጃ
1) አማካሪ
2) ከፍተኛ አማካሪ

6. የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት የተሰጠበት ቀን ……………………………………………..

49
7. የሚከተሉትን መረጃዎች ከቅፁ ጋር አብረው ያያይዙ
8. የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ከአንድ ፎቶኮፒ ጋር
1) የትምህርት ማስረጃ ከአንድ ፎቶ ኮፒ ጋር
2) የተዘረዘሩትን የሥልጠና ሰርተፊኬት ከፎቶ ኮፒ ጋር
3) የተዘጋጁ ዘገባዎችና ዘገባዎቹን ማዘጋጀተዎን የሚያስረዳ መረጃ (ጀማሪ አማካሪ-1
አመልካቾችን አይመለከትም)
4) የሥራ ልምድ ከአንድ ፎቶ ኮፒ ጋር
5) የቀድሞውን የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ከአንድ ፎቶ ኮፒ ጋር
6) አንድ ፎቶ ግራፍ

የአመልካች ስም………………………………….ፊርማ ……………….ቀን …………………...

18.8.3 የአማካሪ ባለሙያዎች የጠፋ ምስክር ወረቀት እንዲተካለቸው የማመልከቻ ቅጽ


ስም …………………………………………………………………
አድራሻ
ክልል …………………………ዞን …………………………………
ወረዳ……………………………ከተማ ……………………………
ክፍለ ከተማ……………...………ቀበሌ………………….የቤ.ቁ ……………………ስልክ……….
የቢሮ………………………ሞባይል………………………ፋክስ……………………
ኢ-ሜይል ………………………………………………………
1) ቀደም ሲል ያገኙት የአካባቢ ዘርፍ ጉዳዮች

50
1) የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናት
2) የአካባቢ ኦዲት
2) አግኝተውት የነበረው ደረጃ
1. አማካሪ (ደረጃ 2)
2. ከፍተኛ አማካሪ
3) የሚከተሉትን መረጃዎች ከቅፁ ጋር አብረው ያያይዙ
1) የአመልካች የቀበሌ መታወቂያ ከአንድ ፎቶ ኮፒ ጋር
2) ሰርተፊኬቱ ስለመጥፋቱ የሚያረጋግጥ የፖሊስ ማስረጃ
3) አንድ ፎቶ ግራፍ
የአመልካች ስም………………………………………….ፊርማ ……………….ቀን ………

18.8.4 አማካሪ ድርጅቶች የአማካሪነት ፍቃድ ለማግኘት ማመልከቻ ቅጽ


የድርጅቱ ስም …………………………………………………………………
አድራሻ
ክልል…………………………ዞን…………………………………
ወረዳ……………………………ከተማ……………………………
ክፍለከተማ……………...………ቀበሌ………………….የቤ.ቁ……………………… ስልክ…………
የቢሮ………………………ሞባይል………………………ፋክስ……………………
ኢ-ሜይል………………………………………………………
1. ለመሰማራት የሚጠይቁት የአካባቢ ዘርፍ ጉዳዮች
1) የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናት
2) የአካባቢ ኦዲት
2. የስራ አስኪያጅ
መሉ ስም …………………………………………………………………
አድራሻ
ክልል…………………………ዞን…………………………………
ወረዳ……………………………ከተማ……………………………
ክፍለከተማ……………...………ቀበሌ………………….የቤ.ቁ………………………
ስልክየቢሮ………………………ሞባይል………………………ፋክስ……………………
ኢ-ሜይል………………………………………………………
የትምህር ደረጃ………………………………………………………

3. የሰው ሃይል
ተ.ቁ. የባለሙያው ስም የምዝገባ ቁጥርና ሰርተፊኬት ያገኘበት የቅጥር ሁኔታ
ቀን መስክ

51
በኮንትራት በቋሚነት

4. የመስክ የላቦራቶሪ መሣሪያዎች


ተ.ቁ የመሣሪያዎቹ ዝርዝረ ብዛት

5. የጠየቁት ደረጃ
1) ደረጃ አንድ
2) ደረጃ ሁለት
6. የሚከተሉትን መረጃዎች ከቅፁ ጋር አብረው ያያይዙ
1) የአመልካች የቀበሌ መታወቂያ ከአንድ ፎቶ ኮፒ ጋር
2) የድርጅቱን ባለቤትነት/ቶችን የሚመለክት ማስረጃ
3) የተጠቀሱትን የባለሙያዎች ሰርተፊኬት ኮፒ
4) ከባለሙያዎች የተደረገው የቅጥር ስምምነት ኮፒ
5) የመስሪያ ቦታ የሚያሳይ መረጃ
6) የመስክ የላቦራቶሪ መሳሪያዎችን የሚያሳይ ዝርዝር
7) የመነሻ ካፕታል የሚያሳይ የባንክ ማስረጃ
8) አንድ ፎቶ ግራፍ
የአመልካች ስም……………………….ፊርማ ……………….ቀን …………………

18.8.5 አማካሪ ድርጅቶች ደረጃቸውን ለማሳደግ ማመለከቻ ቅጽ


የድርጅቱ ስም …………………………………………………………………
አድራሻ
ክልል…………………………ዞን…………………………………
ወረዳ……………………………ከተማ……………………………
ክፍለከተማ……………...………ቀበሌ………………….የቤ.ቁ………………………
ስልክየቢሮ………………………ሞባይል………………………ፋክስ……………………
ኢ-ሜይል………………………………………………………
1. ለመሰማራት የሚጠይቁት የአካባቢ ዘርፍ ጉዳዮች

1) የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናት


2) የአካባቢ ኦዲት
2. የስራ አስኪያጅ
መሉ ስም …………………………………………………………………
አድራሻ

52
ክልል…………………………ዞን…………………………………
ወረዳ……………………………ከተማ……………………………
ክፍለከተማ……………...………ቀበሌ………………….የቤ.ቁ……………………… ስልክ…………………………
የቢሮ………………………ሞባይል………………………ፋክስ……………………
ኢ-ሜይል………………………………………………………
የትምህር ደረጃ………………………………………………………

3. የሰው ሃይል
ተ.ቁ. የባለሙያው ስም የምዝገባ ቁጥርና ቀን ሰርተፊኬት ያገኘበት መስክ የቅጥር ሁኔታ
በኮንትራት በቋሚነት

4. የመስክ የላቡራቶሪ መሣሪያዎች


ተ.ቁ የመሣሪያዎቹ ዝርዝረ ብዛት

5. የጠየቁት ደረጃ
1) ደረጃ አንድ
2) ደረጃ ሁለት
6. የሚከተሉትን መረጃዎች ከቅፁ ጋር አብረው ያያይዙ
1) የአመልካች የቀበሌ መታወቂያ ከአንድ ፎቶ ኮፒ ጋር
2) የድርጅቱን ባለቤትነት /ቶችን የሚመለክት ማስረጃ
3) የተጠቀሱትን የባለሙያዎች ሰርተፊኬት ኮፒ
4) ከባለሙያዎች የተደረገው የቅጥር ስምምነት ኮፒ
5) የመስሪያ ቦታ የሚያሳይ መረጃ
6) የመስክ የላቦራቶሪ መሳሪያዎችን የሚያሳይ ዝርዝር
7) የመነሻ ካፕታል የሚያሳይ የባንክ ማስረጃ
8) አንድ ፎቶ ግራፍ
የአመልካች ስም………………………….ፊርማ ……………….ቀን …………………...

18.8.6 አማካሪ ድርጅት የብቃት ማረጋገጫቸውን ለማሳደስ ማመለከቻ ቅጽ

የድርጅቱ ስም ………………………………………………………………… አድራሻ ………………………………………


ክልል…………………………ዞን…………………………………ወረዳ……………………………ከተማ……………………………

53
ክፍለከተማ……………...………ቀበሌ………………….የቤ.ቁ………………………
ስልክየቢሮ………………………ሞባይል………………………ፋክስ…………………… ኢ-
ሜይል………………………………………………………
1. የተሰማሩበት የአካባቢ ዘርፍ ጉዳዮች
1) የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናት
2) የአካባቢ ኦዲት
2. ብቃት ማረጋገጫ የተሰጠበት ቀን………………………………..
3. የስራ አስካሄጅ
መሉ ስም …………………………………………………………………
አድራሻ
ክልል…………………………ዞን…………………………………
ወረዳ……………………………ከተማ……………………………
ክፍለከተማ……………...………ቀበሌ………………….የቤ.ቁ………………………
ስልክየቢሮ………………………ሞባይል………………………ፋክስ……………………
ኢ-ሜይል………………………………………………………የትምህር ደረጃ………………………………………………………
4. የሰው ሃይል
ተ.ቁ. የባለሙያው ስም የምዝገባ ቁጥርና ቀን ሰርተፊኬት ያገኘበት መስክ የቅጥር ሁኔታ
በኮንትራት በቋሚነት

5. የመስክ የላቡራቶሪ መሣሪያዎች


ተ.ቁ የመሣሪያዎቹ ዝርዝረ ብዛት

6. የጠየቁት ደረጃ
1) ደረጃ አንድ
2) ደረጃ ሁለት
7. የሚከተሉትን መረጃዎች ከቅፁ ጋር አብረው ያያይዙ
1) የአመልካች የቀበሌ መታወቂያ ከአንድ ፎቶ ኮፒ ጋር
2) የድርጅቱን ባለቤትነት /ቶችን የሚመለክት ማስረጃ
3) የታደሰ የባለሙያዎች የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ኮፒ
4) ከባለሙያዎች የተደረገው የቅጥር ስምምነት ኮፒ
5) የመስሪያ ቦታ የሚያሳይ መረጃ
6) የመስክ የላቦራቶሪ መሳሪያዎችን የሚያሳይ ዝርዝር
7) የመነሻ ካፕታል የሚያሳይ የባንክ ማስረጃ
8) አንድ ፎቶ ግራፍ

54
የአመልካች ስም………………………………………….ፊርማ……………….ቀን-------------------

18.8.7 አማካሪ ድርጅቶች የጠፋ የምስክር ወረቀት እንዲተካላቸው ማመልከቻ ቅጽ


የድርጅቱ ስም …………………………………………………………………
አድራሻ
ክልል …………………………ዞን ………………………………ወረዳ……………………………ከተማ ……………………………
ክፍለከተማ……………...………ቀበሌ………………….የቤ.ቁ………………………ስልክ…………………. የቢሮ………………………
ሞባይል………………………ፋክስ……………………ኢ-ሜይል ………………………………………………………
1. ቀደም ሲል ያገኙት የአካባቢ ዘርፍ ጉዳዮች
1) የአካባቢ ተፅዕኖ ጥናት
2) የአካባቢ ኦዲት
2. አግንተውት የነበረው ደረጃ
3) ደረጃ አንድ
4) ደረጃ ሁለት
3. የስራ አስካሄጅ
መሉ ስም …………………………………………………………………
አድራሻ
ክልል …………………………ዞን …………………………………ወረዳ……………………………ከተማ ……………………………
ክፍለከተማ……………...………ቀበሌ………………….የቤ.ቁ………………………ስልክ…………… የቢሮ………………………
ሞባይል………………………ፋክስ……………………ኢ-ማይል ………………………………………………………
4. የሚከተሉትን መረጃዎች ከቅፁ ጋር አብረው ያያይዙ
1) የአመልካች የቀበሌ መታወቂያ ከአንድ ፎቶ ኮፒ ጋር
2) የድርጅቱን ባለቤትነት /ቶችን የሚመለክት ማስረጃ
3) ሰርተፊኬት ስለመጥፋቱ የሚያረጋግጥ የፖሊስ ማስረጃ
4) አንድ ፎቶ ግራፍ
የአመልካች ስም………………………………………….ፊርማ ……………….ቀን ………

18.9 የፕሮጀክት ባለቤቱ የውል ስምምነት

እኔ የ
---------------------------------------------------------------------------------- ------------------------------------------------------------------------ ፕሮጀክት
ባለቤት በፕሮጀክቴ ግብዓት፣ ተግባራትና ውጤት የተነሳ የሚከሰቱ ተጽዕኖዎችን ለመከላከልና ለመቀነስ
የሚከናወኑ ተግባራት ለመፈጸም የተስማማሁ መሆኔን እየገለጽሁ ተጽዕኖውን መከላከልና መቀነስ
ካልተቻልሁ ለተጽዕኖው የካሳ ክፍያ ለመፈጸም በአዋጅ ቁጥር 181/2003 አንቀጽ 9/4 መሰረት ቃል
ገብቻለሁ፡፡ የአካባቢ አያያዝ እቅድ ተግባራትን/ግደታዎችን በተቀመጠላቸው መጠን፣ የአፈጻጸም ጥራትና
የጊዜ መርሀግብር በማከናወን በየስድስት ወሩ የአፈጻጸም ሪፖርት ለሚመለከተው የአካባቢ መስሪያቤት
ለማቅረብ ቃል ገብቻለሁ፡፡

55
ከዚህ በላይ የተዘረዘሩትን ግደታዎች አለመወጣቴ በአካባቢ ምርመራ፣ ክትትልና ቁጥጥር ከተረጋገጠ
በአዋጅ ቁጥር 181/2003 አንቀጽ 25/4 መሰረት ብር 20,000/ሀያ ሽህ ብር/ ቅጣት ለመንግስት ገቢ
አደርጋለሁ፡፡ ፕሮጀክቴ በአካባቢው ስርዓተ ምህዳርና በማህበረሰቡ ላይ ጉዳት ካደረሰ አግባብ ባለው ህግ
መጠየቄ እንደተጠበቀ ሆኖ በአዋጅ ቁጥር 181/2003 አንቀጽ 25/6 መሰረት ለጉዳቱ የካሳ ወጭ ወይንም
የስርዓተ ምህዳሩን ማገገሚያ ወጭ ሙሉ በሙሉ የምሸፍን መሆኑን ተገንዝቢያለሁ፡፡ እንዲሁም በአዋጅ
ቁጥር 181/2003 አንቀጽ 25/3 መሰረት ፕሮጀክቴ ያደረሰው አካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳት ከፍተኛ
መሆኑ በምርመራ፣ ክትትልና ቁጥጥር ከተረጋገጠ የፕሮጀክቴ የስራ እንቅስቃሴ የሚቋረጥ መሆኑን
ተገንዘቢያለሁ፡፡ ከዚህ በላይ የተዘተዘሩትን የህግ ማዕቀፎች የማውቃቸው መሆኔንና ግደታየንም
ለመፈጸም የተስማማሁ መሆኔን በተለመደው ፊርማየ አረጋግጣለሁ፡፡
የፕሮጀክቱ ባለቤት ስም ----------------------------------------------------------------ፊርማ----------------------------------------------
ቀን--------------------------------------ክብ ማህተም

56

You might also like