Professional Documents
Culture Documents
Road Regulation Handout-A4
Road Regulation Handout-A4
Road Regulation Handout-A4
ምዕራፍ አንድ
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 1
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
የሚያስተላልፉት መልዕክት በጥቁር ሲሆን በስዕል፣ በክብደት፣ በቁጥር፣ በቀስት ትዕዛዝ ያስተላልፋሉ፡፡
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 2
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
10. ከሁለት እግር በላይ ያላቸውን አነስተኛ ተሽከርካሪዎች ምልክቱ ከተተከለበት ስፍራ
ጀምሮ መጨረሻ የሚል ሌላ ምልክት እስክሚታለፍ ድረስ መቅደም ክልክል ነው
11. ከሁለት እግር በላይ ያላቸው ሞተር ተሽከርካሪዎች በዚህ በኩል ማለፍ የተከለከለ ነው
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 3
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
14. ጠቅላላ ክብደቱ በቶን በምልክቱ ላይ ከተመለከተው በላይ ለሆነ ማንኛውም ተሽከርካሪ
ማለፍ ክልክል ነው
16.
20. የአክስሉ ጭነት በምልክቱ ላይ ከተመለከተው ክብደት በላይ ለሆነ ተሽከርካሪ ማለፍ ክልክል
ነው
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 4
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
21. ጠቅላላ ስፋቱ በምልክቱ ላይ ከተመለከተው በላይ ለሆነ ተሽከርካሪ ማለፍ ክልክል ነው
22. ጠቅላላ ከፍታው በምልክቱ ላይ ከተመለከተው በላይ ለሆነ ተሽከርካሪ ማለፍ ክልክል ነው
23. የከተማ ክልል ምልክት ስለሆነ የከተማ ውስጥ ህጎችን ሳያከብሩ ማሽከርከር ክልክል ነው
24. የከተማ ክልል ወሰን መጨረሻ ስለሆነ እንደ መንገዱ ደረጃና ሁኔታ ለመንገዱ በሚፈቅደው
የፍጥነት ወስን አሽከርክር
ለ/ በውስጡ መጨረሻ የሚል ፅሁፍ ያለበት የዚህ ዓይነት ምልክት እስክታልፍ ድረስ
ተሽከርካሪ ማቆም ክልክል ነው
27. ይህ ምልክት ከተተከለበት ስፍራ ጀምሮ፡-
ሀ/ መገናኛ / መስቀለኛ መንገድ እስክታልፍ
ለ/ በውስጡ መጨረሻ የሚል ፅሁፍ ያለበት የዚህ ዓይነት ምልክት እስክታልፍ ድረስ
ለአጭርም ሆነ ለረጅም ጊዜ በፍፁም ማቆም ክልክል ነው
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 5
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
30. ይህ ምልክት ባለበት መንገድ ላይ ከፊት ለፊት ለሚመጣ ተሽከርካሪ ቅድሚያ ሳይሰጡ
ማሽከርከር ክልክል ነው
36. ጠቅላላ ክብደቱ በምልክቱ ላይ ከተገለፀው በላይ የሆነ የጭነት ተሽከርካሪዎች ማለፍ ክልክል
ነው
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 6
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
44. ይህ ምልክት ባለበት ከፊት ለፊት ደሴት ላይ ቅድሚያ በመስጠት ተጠንቅቀህ አሽከርክር
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 7
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
2.3. የሚያስገድዱ የመንገድ ዳር ምልክቶች፡- የሚያስገድዱ የመንገድ ዳር ምልክቶች የሚሰጡት ትዕዛዝ አስገዳጅ
ነው፡፡ አብዛኛው ቅርፃቸው ክብና አራት ማዕዘን፣ መደባቸው ሰማያዊ የሚያስተላልፉት መልዕክት በነጭ
ሲሆን በስዕል፣ በቀስት፣ በቁጥር ይገለፃሉ፡፡
49. በተለያየ ረድፍ ውስጥ ተፈፃሚ እንዲሆን የተቀመጠ አነስተኛ የፍጥነት ወሰን
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 8
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
55. ይህ ምልክት ባለበት አካባቢ ለተሽከርካሪዎች ማቆሚያ የተዘጋጀ ወይም የተወሰነ ስፍራ
አለ
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 9
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 10
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
2) አቅጣጫ አመልካች፦ የመንገዶችን ዘላቂ መሆን ወይም አለመሆን የሚገልፁ የመንገድ ዳር ምልክቶች ናቸው፡፡
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 11
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
82. ጅማ ከተማ
85. ቦሌ አካባቢ
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 12
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
በአጭር ርቀት ውስጥ እግረኞች መንገድ ማቋረጥ እንዲችሉ የሚሰመር መስመር ነው፡፡
አለባቸው፡፡
2) በመንገድ አቅጣጫ የሚሰመሩ መስመሮች፡- አንድን መንገድ ለሁለት የሚከፍል መስመር ሲሆን አሽከርካሪዎች
ይህ መስመር የትራፊክ መጨናነቅ በማይበዛባቸው ወይም ለዕይታ አስቸጋሪ ባልሆኑ መንገዶች ላይ በመሰመር
ማንኛውም አሽከርካሪ ያልተቆራረጠውን መስመር አልፎ ዞሮ መመለስ፣ መቅደምና ታጥፎ መሄድ አይችልም፡፡
ነገር ግን እንደመንገዱና እንደትራፊኩ ሁኔታ መስመሮቹን ሳይረግጥ በራሱ ነጠላ መንገድ ላይ የግራ ረድፉን ይዞ
መቅደም ይችላል፡፡
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 13
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
ቀድሞ በተገለፀው ሁኔታ ደሴቱን ሳይረግጥ በራሱ ነጠላ መንገድ የግራ ረድፉን ይዞ መቅደም ይችላል፡፡
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 14
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 15
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
የመቆሚያ ስፍራ ቅብ፡- አሽከርካሪዎች በምልክቱ ውስጥ ለማቆሚያ በተዘጋጀው ስፍራ ላይ ብቻ መቆም
አለባቸው፡፡
ቅድሚያ ስጥ የሚል ምልክት ቅብ፦ ምልክቱ / ቅቡ ቅድሚያ ለተላላፊ በመስጠት በጥንቃቄ ማሽከርከር
3) ከተተከለበት ውጭ አያገለግልም፣
4) በሌላ አቅጣጫ ተሽከርካሪ ቢኖርም ባይኖርም በኤሌክትሪክና በኤሌክትሮኒክስ እገዛ ኡደቱን ጠብቆ
ያስተላልፋል፣
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 16
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 17
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 18
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 19
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 20
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 21
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
2. በተሽከርካሪ ላይ የሚጫን ጭነት መትረፍ የሚችለው ከፊት 1 ሜትር ሲሆን ከኋላ 2 ሜትር ነው፣
3. ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ከባድ ተሽከርካሪዎችን በከተማ አውራ ጎዳና ላይ ከ 2 ሰዓት በላይ ማቆም የተከለከለ
ነው፣
4. አንድ ተሽከርካሪ በሌላ ተሽከርካሪ ሲጎተት በመሃል ያለው ርቀት ከ 3 ሜትር መብለጥ የለበትም፣
7. ከባቡር ሃዲድ ማቋረጫ በ 6 ሜትር ክልል ውስጥ ማርሽ መለዋወጥ የተከለከለ ነው፣
9. ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ምክንያት በከተማ ክልል ውስጥ ተሽከርካሪ ማቆም የሚፈቀደው ለ 6 ሰዓት ብቻ
ነው፣
10. ማንኛውም ዓለም አቀፍ የመንገድ ዳር ምልክቶች በተተከሉበት ቦታ በ 12 ሜትር ውስጥ ተሽከርካሪ አቁሞ
11. የመንገዱ ስፋት ከ 12 ሜትር ካልበለጠ በስተቀር በቆመ ተሽከርካሪ ትይዩ አንፃር ማቆም የተከለከለ ነው፣
12. "ቁም" የሚል የመንገድ ዳር ምልክት ባለበት ስፍራ በ 12 ሜትር ክልል ውስጥ ማቆም የተከለከለ ነው፣
13. በሆስፒታል የመጀመሪያ ዕርዳታ መስጫና ከእሳት አደጋ መከላከያ መግቢያ በሮች በ 12 ሜትር ባነሰ ርቀት
ውስጥ ተሽከርካሪ ማቆም ክልክል ነው፣
14. በመስቀለኛ መንገድ ውስጥ ወይም ከመስቀለኛ መንገድ በ 12 ሜትር ክልል ውስጥ ተሽከርካሪ ማቆም ክልክል
ነው፣
15. በነዳጅ መቅጃ (ማደያ) መግቢያና መውጫ በ 12 ሜትር ክልል ውስጥ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ክልክል ነው፡፡
16. የአውቶቡስ ማቆሚያ ስፍራ አካባቢ ከፊትና ከኋላ በ 15 ሜትር ባነሰ ክልል ውስጥ ተሽከርካሪ ማቆም ክልክል
ነው፣
17. በባቡር ሃዲድ ማቋረጫ አካባቢ ከ 20 ሜትር ባነሰ ርቀት ውስጥ ተሽከርካሪ ማቆም የተከለከለ ነው፣
18. በመስቀለኛና በባቡር ሃዲድ ማቋረጫ መስመር በ 30 ሜትር ክልል ውስጥ መቅደምና አቅጣጫ መቀየር
የተከለከለ ነው፡፡
19. ተሽከርካሪ መንገድ ዳር በምናቆምበት ወቅት ከመንገድ ዳር ጠርዝ 40 ሳ/ሜ መሆን አለበት፣
20. የተበላሸን ተሽከርካሪ ከከተማ ክልል ውጪ በአውራ ጎዳና ላይ ከ 48 ሰዓት በላይ ማቆም የተከለከለ ነው፣
21. ተሽከርካሪ በብልሽት ምክንያት መንገድ ላይ ቢቆም ባለሶስት ማዕዘን አንፀባራቂ ምልክት ከፊትና ከኋላ በ 50
ሜትር ላይ መቀመጥ አለበት፣
22. ከፊት ለፊትህ የሚመጣን ተሽከርካሪ በ 50 ሜትር ርቀት ማየት የማይቻልበት ማንኛውም መታጠፊያ ቦታ
ላይ መቅደም የተከለከለ ነው፣
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 22
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
23. ረጅሙን የግንባር መብራት በከተማ ውስጥ፣ የትራፊክ ፍሰት በሚበዛባቸው ቦታዎችና ከፊት የሚመጣ
ተሽከርካሪ በ 50 ሜትር ክልል ውስጥ ከሆነ ማብራት ክልክል ነው፣
24. ፍሬቻ መታጠፊያ /መዞሪያ/ ቦታ ከመድረሳችን 50 ሜትር ሲቀር ማብራት አለብን
25. የሚያስጠነቅቁ የመንገድ ዳር ምልክቶች ድርጊት ከሚፈፀምበት 50 ሜትር ላይ ይተከላሉ፣
26. አንድን ከፊት ያለ ተሽከርካሪ ከቀደምን በኋላ ወደ ቀኝ ረድፍ ለመግባት ከቀደምነው ተሽከርካሪ 50 ሜትር
መራቅ አለብን፣
27. የአደጋ አገልግሎት ዕርዳታ መስጫ ተሽከርካሪዎችን ከ 100 ሜትር ባነሰ ርቀት ተከታትሎ ማሽከርከር
የተከለከለ ነው፣
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 23
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
4) የፍጥነትና አቅጣጫ መቆጣጠሪያ መሳሪያዎች፡- እነዚህ መሳሪያዎች የተሽከርካሪን ፍጥነትም ይሁን አቅጣጫ
መቆጣጠር የሚያስችሉ ናቸው፡፡ እነሱም፡- መሪ፣ የእግር ፍሬን፣ የእጅ ፍሬን፣ የነዳጅ መስጫ ፔዳል፣ ማርሽ
መለዋወጫ ዘንግ ናቸው፡፡
5) የትዕይንት መቆጣጠሪያ መሳሪያዎች፡- የግንባር /የፊት መስታወትና መብራቶች፣ የጎንና የኋላ ትዕይንት
መቆጣጠሪያ መስታወቶች፣ የፀሃይ ጨረር መከላከያዎች፣ የበረዶ ወይም ጭጋግ ማቅለጫ ሙቀት ሰጪ
መሳሪያና የውስጥና የውጪ መብራቶች ናቸው፡፡
6) የስርቆሽ መከላከያ መሳሪያዎች፡- ተሽከርካሪያችንን ካቆምንበትና በቂ ጥበቃ ከሌለበት ስፍራ በሌቦች
እንዳይሰረቅ የሚከላከሉ መሳሪያዎች ናቸው እነሱም፡- የማስነሻ ቁልፍ /ደውል/፣ የመሪ ዘንግ ቁልፍና የበር
ቁልፍ ናቸው፡፡
የፍሬቻ አገልግሎት
የግራ ፍሬቻ የቀኝ ፍሬቻ
ከቆምንበት ለመነሳት ለመቆም
ለመቅደም ለማስቀደም
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 24
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
4. ረድፍ ለመያዝና ተከታትሎ ለማሽከርከር ማድረግ ያለብን፡- አሽከርካሪዎች ማሽከርከር በሚፈልጉበት አቅጣጫ
ለማሽከርከር የመንገድ መሃል መስመር ህግና ደንብን በማክበር ረድፋቸውን በመያዝ ማሽከርከር ይጠበቅባቸዋል፡፡
5. ተከታትሎ ለማሽከርከር፡- ማንኛውም አሽከርካሪ ከሌላ ተሽከርካሪ ተከትሎ በሚያሽከረክርበት ወቅት
በማንኛውም ጊዜ ያለአንዳች አደጋ ማቆም እንዲችል ራሱንና ከፊት የሚያሽከረክረውን ተሽከርካሪ ፍጥነት፣
የመንገዱን ግልፅነት፣ የትራፊክ እንቅስቃሴን ብዛትና ሁኔታ በማመዛዘን በሚያሽከረክረው ተሽከርካሪና ከፊቱ
ባለው ተሽከርካሪ መሃል በቂ ርቀት ጠብቆ ማሽከርከር አለበት፡፡
6. ለመቅደም፡- አሽከርካሪዎች ሌሎች ተሽከርካሪዎችን መቅደም በሚፈልጉበት ጊዜ ሊያደርጓቸው የሚገባቸው፡-
መቅደም የሚቻለው በግራ በኩል ብቻ መሆኑን መገንዘብ፣
የተወሰነ ርቀት ከተጓዝን በኋላ አደጋ በማያስከትል ሁኔታ ረድፍ ለመያዝ በቀኝና በመሃል ስፖኪዮ
የቀደምነውን ተሽከርካሪ ፍጥነትና ርቀትን መመልከትና የቀኝ ፍሬቻ በማሳየት የመሪ እርምጃ በመውሰድ
ረድፍ መያዝ፣
የቀደምነው ተሽከርካሪ በኋላ መመልከቻ መስታወት ውስጥ እስኪታይ ድረስ አቅጣጫ ሳይለውጡ ቀጥታ
ማሽከርከር፣
ሶስተኛ ተደራቢ ሆኖ መቅደም ክልክል ነው፣
መቅደም ከመጀመራችን በፊት ከሌላ አቅጣጫ የሚመጣ ተሽከርካሪ ሳይደርስ ከቀደምን በኋላ ወደ ቀኝ ረድፍ
ለመመለስ የሚያስችል በቂ ርቀት እንዳለ መገመት ያስፈልጋል፣
7. ለማስቀደም፡- ምልክት የሰጠን ተሽከርካሪና በፍጥነት በመጓዝ እየመጣ ያለን ተሽከርካሪ በኋላ መመልከቻ ስፖኪዮ
መመልከት፡፡
በቀኝ ጎን መመልከቻ ስፖኪዮ ሌሎች ተሽከርካሪዎች አለመኖራቸውን ማረጋገጥ፣
ፍቃደኛ መሆናችንን የሚገልፅ የቀኝ ፍሬቻ ማሳየት፣
ወደ ቀኝ የመሪ እርምጃ መውሰድና ረድፍ መያዝ፣
የቀደመን ተሽከርካሪ ትክክለኛ ረድፍ እስኪይዝ የተሽከርካሪ ፍጥነት መቀነስ አለብን፣
8. ከፊት ለፊት የሚመጣን ተሽከርካሪ ለመተላለፍ
ከፊት ለፊት የሚመጣውን ተሽከርካሪ ለመተላለፍ ከቀኝ በኩል ካለው የመንገዱ ዳር ተጠግተህ በመንዳት በቂ
የመተላለፊያ ቦታ በግራ በኩል መተው ያስፈልጋል፡፡
ተራራማና ዳገት በሆኑ ቦታዎች ላይ አሽከርካሪዎች መተላለፍ ቢያስፈልግ ቁልቁለት የሚወርደው አሽከርካሪ
ወደ ዳገት ለሚወጣው አሽከርካሪ እንደአስፈላጊነቱ ፍጥነቱን በመቀነስ ወይም በማቆም የማሳለፍ /ቅድሚያ
የመስጠት/ ግዴታ አለበት፡፡
የህዝብ ማመላለሻ የያዘ አሽከርካሪ በሁለቱም አቅጣጫ ቢሆን ቅድሚያ አለው፡፡
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 25
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
ምዕራፍ ሁለት
2. ሥነ-ባህሪ
2.1. የሥነ-ባህሪ ምንነት
ይህ ምዕራፍ ከማሽከርከር ስነ-ባህሪ ጋር የሚገናኙ ጉዳዮችን ያብራራል፣
እንዲሁም የአሽከርካሪ ሙያዊ ስነ-ምግባርን ይተነትናል በመጨረሻም የአሽከርካሪን ሃላፊነትና ተግባር ይገልፃል፣
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 26
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
ባህሪ፡- የሰው አስተሳሰብ፣ አመለካከትና ድርጊት ውጤት ነው፡፡ በቀጥታ ሊቃኝ፣ ሊመዘገብና ሊለካ የሚችል
ወይም በተዘዋዋሪ መንገድ ሊታወቅ የሚችል ሊሆን ይችላል፡፡
የተለያዩ የስነ-ባህሪይ ባለሙያዎች ለስነ-ባህሪይ የተለያየ ትርጓሜ ሰጥተዋል፡፡ ከነዚህ ትርጓሜዎች ውስጥ ሁለቱ
እንደሚከተለው ተገልፀዋል፡፡
ሥነ-ባህሪ፡- የሰዎችንና የእንስሳስትን ባህሪይ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ የሚያጠና ዲስፕሊን ነው፡፡
ሥነ-ባህሪ፡- ባህሪንና የአዕምሮ አስተሳሰብ ሂደትን ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ የሚያጠና ዲስፕሊን ነው፡
የስነ-ባህሪ ግቦች
ባህሪን መግለፅ
የተለያዩ ባህሪያትን መንስኤ ማብራራት
ወቅታዊ የባህሪን ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት የወደፊቱን መተንበይ
ባህሪን ማሻሻል ማለትም የሰው ልጅ መልካምና መጥፎ ባህሪያትን እንዲያዳብር
መልካም ያልሆነውን ባህሪይ በተለያዩ የስነ-ባህሪይ ዘዴዎች መለወጥ ሌላኛው የስነ-ባህሪ ግብ ነው
2.2. የማሽከርከር ስነ-ባህሪ
አሽከርካሪዎች በሚያሽከረክሩበት ወቅት የሚያሳዩትን ባህሪ የሚያጠና የስነ-ባህሪይ ዘርፍ ነው፡፡
የማሽከርከር ስነ-ባህሪ ዓላማ፡- አላስፈላጊ የማሽከርካር ባህሪን በማስተካከል በተሽከርካሪ የሚደርስ አደጋን
መቀነስ ነው፡፡
በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የአለማችን ክፍሎች በአሽከርካሪዎች የሚደርስ አደጋን ለመቀነስ የተለያዩ ጥረቶች
የተደረጉ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡
ይህን አደጋ ለመቀነስ ከሚደረጉት ጥረቶች መካከል የአሽከርካሪዎችን መልካም ባህሪ በማዳበር ወይም
በማጠናከር ነው፡፡
ይህም የሚከናወነው በግንኙነት ክፍሎቶች ላይ የሚከተሉትን ጉዳዮች እንዲያበረታ አደርጎ በማስተማር
ነው፡፡
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 27
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
ሀ/ መገንዘብ (Sensetion)
መረጃን ከአካባቢያችን በስሜት ህዋሳቶቻችን የመቀበል፣ የመለወጥና ወደ አዕምሯችን የመላክ ሂደት ነው፡፡
የመስማት ሂደት ተግባሩን የሚያከናውነው በስሜት ህዋሳቶቻችን አማካኝነት ማለትም በማየት፣ በመስማት፣
በማሽተት፣ በመቅመስና በመዳሰስ ነው፡፡
አይን አካባቢን ለማወቅ ከፍተኛ ሚና የሚጫወት የስሜት ህዋስ ነው፡
በብዙ ጥናቶች እንደተረጋገጠው በአብዛኛው ከ 80% እስከ 90% አካባቢን ለማወቅና ስለአከባቢ መረጃ
ለመሰብሰብ የሚያስችለው በማየት ነው፡፡
ለ/ ትኩረት /Attention/
ትኩረት በስሜት ህዋሳቶቻችን አማካኝነት ከሚደርሱን መረጃዎች መካከል ዋናውንና ተፈላጊውን የመምረጥ
ሂደት ነው፡፡
በመሆኑም አሽከርካሪዎች ለማሽከርከር የሚረዳቸው መረጃ ላይ ትኩረት ማድረግን ሊያዳብሩት የሚገባ ጉዳይ
መሆኑን ማወቅ ይገባል፡፡
ሐ/ ማስተዋል /Perception/
በስሜት ህዋሳቶቻችን አማካኝነት የመጣን መረጃ የመምረጥ፣ የማቀናበርና ትርጉም የመስጠት ሂደት ነው፡
አሽከርካሪዎች በሚያሽከረክሩበት ወቅት አዕምሯቸው በመስራት ላይ እንዳለ ኮምፒዩተር ነው ማለት ይቻላል፡፡
2.3. የባህሪ መለዋወጥ መንስኤዎች
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 28
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
1) ከተፈጥሮ የሚወረስ /ከቤተሰብ የወረስናቸው/ ባህሪያት፡- ያለን አመለካከት፣ አስተሳሰብና ተግባራዊ እንቅስቃሴ
ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ይኖራቸዋል፡፡ በዘር / በውርስ ያገኘኸውን ባህሪ ማወቅ የአኗኗር ስልትህን ከሁኔታዎች ጋር
ለማለማመድና በተወሰኑት ባህሪያት ላይ ትኩረት ለመስጠትና በሌሎች ላይ ጊዜን ላለማጥፋት ይረዳል፡፡
2) የምንኖርበት አካባቢ፡- ከአካባቢያዊ ነገሮችና ሁኔታዎች ጋር በምናደርገው መስተጋብር ባህሪያችን ላይ ተፅዕኖ
የሚኖረው ሲሆን እየተቀረፀና እያደገ ይመጣል፡፡ አንዳንድ አሽከርካሪዎች ድምፅ በሚበዛበት፣ በጣም ሞቃት
በሆነ አካባቢና የትራፊክ መጨናነቅ ባለበት ቦታ በሚያሽከረክሩበት ጊዜ የተለመደውን ዓይነት ባህሪ
እንደሚያንፀባርቁ ይገለፃሉ፡፡ ለምሳሌ፡- በሚደክመንና የህመም ስሜት በሚሰማን ወቅት የባህሪ ለውጥ ልናሳይ
እንችላለን፡፡
3) አካላዊ ሁኔታ፡- የአካላችን ሁኔታ ማለትም የሰውነት ጥናካሬና ክብደት እንዲሁም የዕድሜ ሁኔታ በባህሪ ላይ
ከፍተኛ አስተዋፅኦ አላቸው፡፡
4) ሃይለ-ስሜታዊ /ውጥረት/፡- ውስጣዊ ፍላጎትን፣ ፍቅርን፣ ጥላቻን፣ ሃዘንን፣ ብስጭትን ወዘተ… የመግለፅ ሂደትን
ያመላክታል፡፡
ለሰዎች ወይም ለነገሮች ያሉን ስሜቶች ከሚፈለገው በላይ በሚሆንበት ወቅት ወደ ሃይለ-ስሜት ውጥረት
ውስጥ ይከተናል፡ ይህም ለባህሪ መለዋወጥ ምክንያት ይሆናል ማለት ነው፡፡
አሽከርካሪዎች ለሃይለ-ስሜት ውጥረት መንስኤ የሆኑትን ምክንያቶች ለይቶ በማወቅ ሁኔታዎችን ከግምት
ያስገባ ውሳኔ ላይ ለመድረስ ያስችላቸዋል፡፡
5) ስልጠና፡- የተመረጠ አመራርና ዕቅድ ባለው መንገድ የሚከናወን ድርጊት ሲሆን የሰውን ልጅ በሚፈለገው
አኳኋን ለማስተማር ያስችላል፡፡ ስለሆነም የሰው ልጅ በሰለጠነበት ዘርፍ የባህሪ ለውጥ እንዲያመጣ ያስችለዋል፡፡
በአሽከርካሪዎች ከሚደረገው አደጋ የተወሰነው ከአሽከርካሪዎች ብቃት ማነስ የሚከሰት መሆኑን የዘርፉ
ባለሙያዎች ይገልፃሉ፡፡
ስለሆነም ከአሽከርካሪዎች ብቃት ማነስ ችግር የሚፈጠርን አደጋ ደረጃውን በጠበቀ የአሽከርካሪዎች
ስልጠና ሊወገድ ይችላል፡፡ ምክንያቱም ስልጠና የባህሪ ለውጥ ማምጫ መንገድ በመሆኑ ነው፡፡
2.4. የአሽከርካሪዎች ሙያዊ ሥነ-ምግባር
ሙያ፡- በህብረተሰቡ ውስጥ የተከበረና የተወደደ የስራ መስክ ሆኖ በተወሰነ የዕውቀት መስክ በትምህርትና
ስልጠና የሚገኝ ነው፡፡
ስነ-ምግባር፡- መልካሙንና መጥፎውን ለመለየት የሚያስችልና መጥፎውን በመተው መልካሙን
እንድንከተል የሚያበረታ እሴት ነው፡፡
ስነ-ምግባር ለማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር አብሮ ለመስራትና ለመኖር አስፈላጊ ነው፡፡
የሙያ ስነ-ምግባር፡- ማለት ባለሙያው በተሰማራበት ሙያ የሚሰራውን ስራ ውጤታማ እንዲሆን
እንደተሰማራበት የሙያ ዓይነት አባላቱ በጥብቅ መከተል የሚገባቸውን መርሆዎችና ስነ-ስርዓቶች ያመላክታል፡፡
በተለይም ማሽከርከር የአዕምሮና የአካል እንቅስቃሴን ቅንጅት የሚጠብቅ ሙያ በመሆኑ ትኩረት ሊሰጠው
ይገባል፡፡
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 29
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 30
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
ሞገደኝነት
ከሚፈለገው በላይ ራስ ወዳድነት
ሃይለ-ስሜታዊ አለመረጋጋት
ቸልተኝነት
ትኩረት ለመሳብ መሞከር (ልታይ ልታይ ባይነት)
ሃላፊነት መዘንጋት
ሱሰኝነት ወዘተ…
የሌ 0 ላውን መንገድ የሚዘጉና ካለ እነርሱ በስተቀር ሌላ የመንገዱ ተስተናጋጅ እንደሌለ የሚቆጥሩ፣
ቅጣት ከሌለ በስተቀር ህግን በራሳቸው ተነሳሽነት የማያከብሩ፣
መግጨትና መጋጨትን በቀላሉ የሚመለከቱ፣
ማቆም በማይገባቸው ቦታ ላይ መኪናቸውን የሚያቆሙና ለአጠቃላይ እንቅስቃሴ እንቅፋት የሚሆኑ፣
ካልጠጡ የማይነዱ፣
ከተቃራኒ ፆታ ጋር ተቀምጠው ከነዱ ጠቅላላ ህጉችን በመሻር በማን አለብኝነትና በእብጠት በመወጠር
በከፍተኛ ፍጥነት በማሽከርከር ልታይ ልታይ ባይነት የሚያጠቃቸው፣
ጫት መቃምና ማጨስ በሚያሽከረክሩበት ወቅት የሚያዘወትሩ ናቸው፡፡
2.5. የአልኮል መጠጥና የትራፊክ አደጋ
የትራፊክ አደጋ እንዲፈጠር ምክንያት ከሚሆኑት ነገሮች ውስጥ የአልኮል መጠጥ ጠጥቶ ማሽከርከር አንዱ
ነው፣
የአልኮል መጠጥ የአሽከርካሪውን የማሽከርከር ሁለንተናዊ ብቃት በመቀነስ የትራፊክ አደጋ እንዲፈጠር
ምክንያት በመሆኑ ብዙዎች አካለ ጎደሎ እንዲሆኑ፣ ህይወታቸው እንዲያልፍ፣ቤተሰቦቻቸው እንዲበተኑና
ንብረት እንዲወድም ስለሚዳርጉ በዘርፉ የተደረጉ ጥናቶች አረጋግጠዋል፣
በአንድ ጥናት እንደተመለከተው በአሜሪካ ከአደገኛ የመንገድ የትራፊክ አደጋዎች ውስጥ 44% የሚደርሰው
የአልኮል መጠጥ ጠጥተው በሚያሽከረክሩ አሽከርካሪዎች ነው፣
ስለዚህ "ከጠጡ አይንዱ ከነዱ አይጠጡ" የሚለውን የትራንስፖርት ደንብ ማክበር በዘርፉ ለሚደርሰው አደጋ
መቀነስ አስተዋፅኦ ይኖረዋል፣
በማሽከርከር ችሎታ ላይ የአልኮል መጠጥ ተፅዕኖ
የአልኮል መጠጥ በማዕከላዊው ስርዓተ-ነርቭ ላይ የመደበት /Derpressant/ ተፅዕኖ ያደርሳል፡፡
የአልኮል መጠጥ በደማችን ውስጥ በፍጥነት በመሰራጨት የአዕምሯችንን መደበኛ የሆነ ተግባር የሚቀንስ
ሲሆን ውሳኔ የመስጠት ብቃት፣ ስሜትና ባህሪይ ላይም ተፅዕኖ ያደርሳል፡፡
ተሽከርካሪን ማሽከርከር አብዛኛውን መሰረታዊ ክፍሎች የሚጠብቅ ድርጊት ነው፡፡ ይኸውም መገንዘብን፣
ማተኮርን፣ ውሳኔ መስጠትን፣ አካላዊ ቅልጥፍናንና እነኝህን ክህሎቶች የማቀናጀት ችሎታ የሚጠይቅ
ድርጊት ነው፡፡ በመሆኑም የአልኮል መጠጥ የአሽከርካሪውን የማየት፣ የማተኮር፣ የማገናዘብ፣ ውሳኔ
የመስጠት ችሎታውንና ቅልጥፍናውን በመቀነስ የትራፊክ አደጋ እንዲፈጠር ምክንያት ይሆናል፡፡
የአልኮል መጠጥ ጠጥቶ የሚያሽከረክር አሽከርካሪ ባሪያት
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 31
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 32
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
አልኮል፣ አደንዛዥ ዕፅ፣ ከባድ መድሃኒት ወስዶ በእንቅልፍ፣ በድብርት ወይም በከባድ ህመም ውስጥ
ሆኖ ማሽከርከር ነው፡፡
ተናደው፣ ተቆጥተው ወይም እነኝህን መሰል ስሜት ውስጥ ሆነው ማሽከርከር
በፍርሃት ውስጥ ሆነው ማሽከርከር፣ በጭንቀት ውስጥ ሆነው ማሽከርከር፣
በማሽከርከር ላይ እያሉ አትኩሮትን በሌላ ነገር መውሰድ፣
በፍጥነት ማሽከርከር ሱስ ተይዞ ማሽከርከር፣
የትራፊክ ህጎችን ያለማክበር፣ የተሳሰተ ግምትና ማጠቃለያ መስጠት
የትራፊክ ህጎች ግንዛቤ አለመኖርና የራስን የአነዳድ ስህተቶች አለመቀበል፡፡
የሞገደኛ አነዳድ ፈርጆች
1) ትዕግስት ማጣትና ትኩረት አለመስጠት
የትራፊክ መብራትን አለማክበር (ቀይ መብራት መጣስ)
የትራፊክ ቢጫ መብራት ሲበራ ፍጥነት ያለመቀነስ
ያለአግባቡ ረድፍን መቀየር ወይም መሽሎክሎክ
ከተፈቀደው ፍጥነት በላይ ማሽከርከር
ከፊት ለፊት ያለን ተሽከርካሪ በጣም ተጠግቶ ማሽከርከር
አስፈላጊውን የትራፊክ ምልክት ለሌሎች አሽከርካሪዎች አለማሳየት
ፍጥነት በመጨመርና በመቀነስ መወላወል
የማቋረጫ መንገዶችን መዝጋት
2) ተፅዕኖ የማድረግ ትግል
ተሽከርካሪን ላለማሳለፍ መንገድ መዝጋት
በተሽከርካሪዎች መካከል ሊኖር የሚገባው ክፍተት ሌላ ተሽከርካሪ እንዳይገባ የመኪና ጥሩንባ
በተደጋጋሚ በማስጮህ፣ በምልክትና በመጮህ መሳደብና ማስፈራራት
ለማስፈራራት ወይም ለማስገደድ ሲባል ከፊት ለፊት ያለን መኪና ከኋላ ተጠግቶ ማሽከርከር
ለመበቀል ተሽከርካሪን በድንገት ማቋረጥ
በበቀል ስሜት በድንገት ፍሬን መያዝ
3) ግዴልሽነትና የመንገድ ላይ ፀብ
በአልኮል መጠጥ ተመርዞ ማሽከርከር
መሳሪያ መደቀን ወይም መተኮስ
በጣም ከፍተኛ በሆነ ፍጥነት ማሽከርከር
መንገድ ዳር ተሽከርካሪ በማቆም ማስፈራራት ወይም መደባደብ
ሞገደኛ አሽከርካሪ ላለመሆን መደረግ የሚገባቸው ክንዋኔዎች
ወደሚፈልጉብት ቦታ በሰዓቱ ለመድረስ በቂ ጊዜ መመደብ፣ (የሚያሽከረክሩት በከተማ ውስጥ ከሆነ)
ከተቻለ የጉዞን ፕሮግራም በስራ መግቢያና መውጫ ሰዓቶች ላይ አለማድረግ፣
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 33
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 35
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 36
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 37
ወታ/አሽ/ሥ/ዲ/መንት
መንገድ ሥነ-ሥርዓት ገፅ 38