4

You might also like

Download as pdf or txt
Download as pdf or txt
You are on page 1of 7

የይቅርታን ኀይል መለማመድ

መግቢያ

 ዛሬ በጣም አስቸጋሪ ከሆኑት ርእሰ-ነገሮች መካከል፣ ነገር ግን በሕይወት ውስጥ ደግሞ እጅጉን
አስፈላጊ ከሆኑት ነገሮች አንዱ ስለሆነው ስለ ይቅርታ እንነጋገራለን፡፡
 ለምንድን ነው ይቅርታ አስቸጋሪ የሚኾነው? አስቸጋሪ የሚሆንበት ምክንያት ሰብኣዊ ባሕርያችን
ከይቅርታ ይልቅ በቀልን ፈላጊ በመኾኑ ነው፡፡ አንድ ሰው ሲጎዳን በተፈጥሮኣችን እኛም በጎዳን ሰው
ላይ በአጸፋው እንደዚያው እንድናደርግበት ይነግረናል፤ ማለትም ዋጋውን ወይም ዋጋዋን ማግኘት
አለበት/አለባት ብሎ በውስጥ ሹክ ይለናል፡፡
 ኢየሱስ ያደረገው ግን እንደዚህ አልነበረም፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም እንዲህ እንድናደርግ አያዘንም፡፡
 ይቅርታ ለምን በጣም አስፈላጊ ሆነ? አስፈላጊ የሆነበት ዋናው ምክንያት ነፃ ስለሚያወጣን ነው፡፡
እኛን ብቻ አይደለም የጎዱንንም ሰዎች ጭምር ነፃ ስለሚያደርጋቸው ነው እንጂ፡፡
 የይቅርታን ኀይልን ስናገኝ፣ ሕይወታችንን፣ ቤተሰቦቻችንንና፣ ማኅበረሰባችንን ይለውጣል!

ኢየሱስን የገደለው ማን ነው?

 ኢየሱስ ክርስቶስን ማን እንደገደለው አስባችሁ ታውቃላችሁ?


 አይሁዶች ነበሩን? አይደሉም፤ እነሱ ርሱን ጥፋተኛ እንደሆነ አድርገው ብቻ ነበር ያወገዙት፡፡
 ሮማውያን ነበሩን? አይደሉም፣ እነሱ ይዘው የነበሩት አለንጋ/ጅራፍ/ና መዶሻ ብቻ ነበር፡፡
 ታዲያ ማን ነበር? እኔና እናንተ ነበርን!
 ኢየሱስን ለሞት ያበቃው ኀጢአታችን ነበር፡፡ መስቀል ላይ እንዲቸነከርና ተጠርቆ እንዲውል
ያደረገው በራሱ ላይ የተሸከመው ኀጢአታችን ነበር፡፡
 ኀጢአትን ባንፈጽም ኖር፣ ኢየሱስ ባልሞተ ነበር፡፡
 የእግዚአብሔር ፍቅር ምን ያህል ታላቅ እንደሆነ ታስተውላላችሁን? እግዚአብሔር አንድያ ልጁን
በሞት እንዲሰዋ እንዳደረገው ሁሉ፣ ሕዝብን ለማዳን ሲል ራሱን መስዋእት ለማድረግ የሚቻለው
ማንም ሰው በየትኛውም ሃይማኖት ውስጥ ቢኾን አይገኝም፡፡
ይቅርታ ያስፈልገናል

 ሮሜ 3:23 "ሁሉ ኀጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጐድሎአቸዋል" ይላል፡፡


 ኀጢአታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ደም ይደመሰስልን ዘንድ፣ ያለ ምንም ልዩነት ሁላችንም ቢኾን
የኀጢአት ይቅርታ ያስፈልገናል፡፡ ከዚያ በኋላ ነው የዘላለምን ሕይወት የምንቀበለውና ከሰማያዊው
አባታችንም ጋር ያለን ኅብረት የሚታደሰው፡፡
 ይሁን እንጅ፣ ይቅር ከተባልንም በኋላ እንኳ ፍጹማን አይደለንም፤ ትክክል ያልሆኑ ነገሮችን
ከማሰብ፣ መናገርና ማድረግ አናቆምም፡፡ ስለዚህ በቀጣይነት የኀጢአትን ይቅርታ መቀበል
ይኖርብናል፡፡
 እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ መኖር እንድንችልና የሚያጋጥሙንን ፈተናዎች ሁሉ ለመጋፈጥም ዕለት
በዕለት የእግዚአብሔርን ኀይል መቀበል ያስልገናል፡፡

የእግዚአብሔር ጸጋ

 የእግዚአብሔር ጸጋ በእኛ ላይ እንዲህ ይሠራል፡-

1) የዘላለምን ሕይወት ተስፋን ይሰጠናል፣

2) ከሰማያዊው አባታችን ጋር ያለንን ግንኙነት/ኅብረት/ ያድሰዋል፣

3) በዚህ ምድር ስንኖር ንጹሕ፣ ቅዱስና፣ ፍሬ የሚያፈራን ሕይወት እንዲኖረን ኀይልን ያስታጥቀናል፡፡

 የእግዚአብሔር ጸጋ አስደናቂ አይደለምን? የማይገባንንና ልንከፍለው የማንችለውን፣ እግዚአብሔር


በነፃ ይሰጠናል፡፡
 እኔና እናንተ ማድረግ ያለብን ነገር ቢኖር፣ ይህንን ስጦታ በትሑት መንፈስና በምስጋና መቀበል ብቻ
ነው፡፡

ይቅር ይለናል ሳይኾን፣ አስቀድሞ ብሎናል

 እግዚአብሔር ይቅር ያላችሁ ስለሚገባችሁ እንዳልሆነ ሁሌም አትዘንጉ፡፡ ነገር ግን ስለሚወዳችሁና


ለነፍሳችሁም ቤዛ ይሆን ዘንድ ዋጋን ስለከፈለ ነው፡፡
 እውነታው እግዚአብሔር ከ 2,000 ዓመታት በፊት ይቅር ብሎናል! በጎልጎታ/በቀራንዮ/ መስቀል
ላይ ኢየሱስ ያለፈውንና የወደፊቱን ኀጢአታችሁን ሁሉ ተሸክሞታል፣ እንዲሁም በገዛ ደሙ
አጥቦታል፡፡
 እናም፣ "በርግጥ እግዚአብሔር ይቅር ሊለኝ ይችላልን?" ብላችሁ ታስቡ ይኾናል? መልሱ፡-
የምሥራች እርሱ ቀድሞውኑ ይቅር ብሎናል!
 ነገር ግን እርሱ ለእናንተ ያደረገውን እስክትቀበሉ ድረስ፣ የተባለው ነገር ሁሉ ለእናንተ ረብ
አይኖረውም፡፡
 አሁን ጥያቄው ይቅርታውን ተቀብላችሁ ነጻ መሆን ትሻላችሁን? የሚለው ይሆናል፡፡

ሌሎችን ይቅር የማለት ኀይል

 የእግዚአብሔርን ጸጋ ስትቀበሉ፣ በደል ያደረሱባችሁን ሰዎች ይቅር ማለት የሚያስችል ኀይልን


ታገኛላችሁ፡፡ በርግጥ ነገሩ እንደመናገር ቀላል ላይሆን ይችላል፣ ነገር ግን በመንፈስ ቅዱስ ኀይል
የሚቻል ይሆናል፡፡
 ይቅርታ የምርጫ ጒዳይ ነው፤ ይቅር ማለትንም መርጠናል፣ ይህም ሰዎች ሰለሚገባቸው ሳይኾን
እግዚብሔር በነጻና ያለ ቅደመ ሁኔታ ይቅር ስላለን፣— እኛም በተመሳሳይ መንገድ ሌሎችን ይቅር
እንድንል ስላዘዘን ነው፡፡
 ደቀ መዝሙሩ ጴጥሮስ አንድ ጊዜ ኢየሱስን እንዲህ ሲል ጠየቀው፡-"…ጌታ ሆይ፥ ወንድሜ
ቢበድለኝ ስንት ጊዜ ልተውለት? እስከ ሰባት ጊዜን? አለው። ኢየሱስ እንዲህ አለው፦ እስከ ሰባ ጊዜ
ሰባት እንጂ እስከ ሰባት ጊዜ አልልህም።" (ማቴዎስ 18: 21-22)

ይቅርታ እና እርቅ

 ይሁን እንጂ አንድ ሰው ይቅርታ እንዲደረግለት የማይፈልግ ከሆነስ? እሱ ወይም እሷ ይቅር ለማለት
ፈቃደኛ ካልሆኑስ?
 በይቅርታ እና እርቅ መካከል ልዩነት አለ? እርቅ— ማለት በሁለት ወገኖች መካከል " ግንኑነትን
ማደስ" ሲሆን፣ ይቅርታ ግን ከአንድ ወገን የሚመጣ ነው፡፡
 በሌላ አባባል ይቅር መባል የማይፈልጉትን እንኳ ይቅር ማለት ትችላላችሁ ማለት ነው፡፡. ይቅር
ማለት የእናንተ ምርጫ ሲሆን ፣ መቀበል ደግሞ የእነርሱ ምርጫ ነው፡፡
 ኢየሱስ ይቅር እንዲላቸሁ እስክትጠይቁት ድረስ ዝም ብሎ ይቅር ሳይላችሁ ቢቆይ ኖሮ፣ ከዛሬ
2,000 ዓመታት በፊት ስለ ኀጢአታችሁ ባልሞተም ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ሳትጠይቁትም ቢሆን
አድርጎታል፡፡
የኢየሱስን አብነት ተከተሉ

 ኢየሱስ ያፌዙበትን፣ ያሰቃዩትንና መስቀላይ ሰቅለው የቸነከሩትን ወታደሮችንም እንኳ ሳይቀር


ይቅር አለ፡፡ እንዲህም አለ፡- "አባት ሆይ፥ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው አለ።"(ሉቃስ
23:34)
 እነዚህ ወታደሮች ይቅር መባል የሚያስፈልጋቸው ይመስላችኋል? ይቅርታስ ይገባቸው ነበር
ብላችሁስ ታስባላችሁን?
 ኢየሱስ ይቅር ብሎአል፣ ለእኔና ለእናንተ የሚሆን አብነትንም አኑሮልናል፡፡
 ኢየሱስ የሰጠንን አርአያነት ስንከተል ፣ የቱንም ያህል ከባድ ቢመስልም፣- ልክ እንደ ኢየሱስ የሰማይ
አባታችንን እናከብራለን ደስም እናሰኘዋለን፡፡

የእዳ ስረዛ

 ይቅርታ ማለት እዳን መሰረዝ ማለት ነው፤ ጌታ ለደቀ መዛሙርቱ ባስተማራቸው ጸሎት ውስጥ
ስላለው አንድ ሐረግ አስባችሁ ታውቃላችሁን? እንዲህ ይላል፡- "እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር
እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን፤" (ማቴ 6፡12)፡፡
 ለምድን ነው ኀጢአታችንን ይቅርበል ማለትን ትቶ በደላችንን ይቅር በል ያለው?
 አንድን ሰው ስንበድል፣ ከዛ ሰው ላይ አንድን ነገር እየሰረቅንበት ሊሆን ይችላል፤ ምናልባት
ደስታውን፣ መልካም ስሙን፣ ቅንነቱን፣ ወይም የወደፊት እድል ፈንታ ጽዋ ተርታውን፡፡
 ይቅር ትሏቸው ዘንድ ሰዎች በድለው የሰረቁባችሁ ምን ነገሮች አሉ? ሰዎችስ ምን ይዳዳሉ?
 ሰዎች ነጻ እንዲሆኑ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መሰረዝ የምትፈልጉት የበደል'ዳ ምን አለ?

ይቅር ማለት ነጻ ያወጣችኋል

 የይቅርታ አስገራሚው ነገር— ሌሎችን ይቅር ስትሉ፣ እንዲሁም የመበቀል መብታችሁን ትታችሁ
ዕዳ-በደላቸውን በመሰረዛችሁ ምክንያት ራሳችሁን ነጻ ማውጣታችሁ ነው!
 ይቅር ያለማለት የልብ ባርነት ይፈጥርብናል፣ ይልቁንም ደግሞ መራርነትና ጮካነት-ጥርጥር
በውስጣችሁ እንዲወለድ ያደርጋል፡፡
 ይቅር ስትሉ ግን አንቀው የያዟችሁ ምሬትና ጮካነት (ክፉ አሳቢነት፣ ጥርጥር) ይለቋችሁና ልባችሁ
ነጻ ይወጣል፡፡
 ይህ ሲባል ግን ሁሉም ጠባሳዎች ይወገዳሉ፣ እንዲሁም ሕመሙ በሙሉ ይጠፋል ማለት
አይደለም፡፡ ይቅር ማለት መርሳት አይደለምና፡፡
 ይሁን እንጂ ለመኖር፣ ለመተንፈስ፣ በንጹሕ ልቡናና ኅሊና ሌላውን ለመውደድ ነጻ ናችሁ ማለት
ነው፡፡
አጋዥ ዘዴ

 የበደሏችሁንና የጎዷችሁን ሰዎች ይቅር ማለት ውስጣችሁ የሚታገላችሁ ከሆነ ሊያግዛችሁ የሚችል
ዘዴ እንሆ፡-
 አንድ ወረቀት አውጡና ይቅር ማለት ያቃታችሁን ሰው የሰረቀባችሁን ነገሮችን በሙሉ ጻፉ፤
ደስታችሁን፣ ክብራችሁን፣ በራስ መተማመናችሁን፣ ጓደኞቻችሁ፣ ቤተሰቦቻችሁ፣ ... በተቻለ
መጠን ለይታችሁ ለመናገር/ለመጻፍ ሞክሩ፡፡
 ከዚያም ወረቀቱን እየተመለከታችሁ፡- "አዎን በደል ተፈጽሞብኛል፣ አዎን ይህ ሰው ብዙ ነገር
አድርጎኛል፡፡ የመናደዱ መብትም አለኝ፤ ነገር ግን ሰይጣን ልቤን በሰንሰለት ጠፍሮ እንዲይዘው
አልፈቅድለትም፡፡ ይቅር ማለትን መርጫለሁ፤ የዚህን ሰው በደል ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ሰርዤ
ይህን ሰው ነጻ ለማውጣት መርጫለሁ!" ትላላችሁ፡፡
 ከዚያም ወረቀቱን ጨባብጡትና በእሳት አቃጥሉት— እጅግ ነጻ የመውጣት ተመክሮ(ልምምድ)
ይሆንላችኋዋል!

የተሰረዙ እዳዎች ከእንግዲህ በኋላ ሊኖሩ አይችሉም

 አንዴ እዳ-በደሎችን ከሰረዛችሁ በኋላ ከእንግዲህ ሊኖሩ አይችሉም፡፡ ሰውየው የበደለኝነት ስሜት
እንዲሰማው መልሳችሁ መላልሳችሁ ነገሮቹን እየጎተታችሁ አታመጧቸውም ማለት ነው፤ ያን
የምታደርጉ ከሆነ ግን ይቅርታ ያለማድረጋችሁ ማሳያ ነው ማለት ነው፡፡
 ሰውዬው ይቅርታችሁን ተቀበለ አልተቀበለ፣ ምንም የሚለወጥ ነገር የለም፣ ምክንያቱ ከዚያ በኋላ
ነገሩ በእርሱና በእግዚአብሔር ዘንድ የተያዘ ይሆናል፡፡
 አንድ ቀን እግዚአብሔር ፍጹም የሆነ ፍትህን ያመጣል፡፡ እያንዳንዱ ሰው በጻድቁና በእውነተኛው
ዳኛ ፊት መቆሙ ብሎም ለድርጊታቸው እና ለሐሳባቸው በሙሉ ተጠያቂዎች መሆናቸው አይቀሬ
ነው፡፡
 ይቅርታ ማድረግ ማለት በቀልን መተውና የሰው ልጆችን ሁሉ በጽድቅና በርትእ ሊፈርድ ባለው
በእግዚአብሔር እጅ ሁሉንም ነገር ማኖር ማለት ነው፡፡
የይቅርታ የሕይወት ዘይቤ

 በነፃነት መኖር የምትፈልጉ ከሆነ፣ የጸጋን እና የይቅርታን የሕይወት ዘይቤ(አኗኗር) ማዳበር


ይኖርባችኋል!
 ይቅርታን ለመጠየቅ የፈጠናችሁ ሁኑ፤

1) በሐሳብ፣ በንግግርና በተግባር ያደጋችኋቸው ነገሮች ስህተት እንደሆኑ ሲገባችሁ፣

2) አንድን ትክክል የሆነን ነገር ከማሰብ፣ ከመናገርና ከማድረግ ችላ እንዳለችሁ ሲሰማችሁ፣


 ክርስቶስ እናንተን ይቅር እንዳላችሁ ሁሉ፣ ሌሎችን ይቅር ለማለት የፈጠናችሁ ሁኑ!
 የጸጋን መነጽር አድርጉና ባልንጀራችሁን (ሰውን ሁሉ) ችግራቸውን እንደራስ በመቊጠርና
በይቅርታ ሌንስ(መስታወት) ሁል ጊዜ ለመመልከት ወስኑ፡፡
 ሰዎች ሲበድሏችሁ፣ እነርሱ ይቅር በሉን ብለው እስኪጠይቋችሁ ድረስ አትዘግዩ፤ ወዲያውኑ ይቅር
በሉ!

ይቅር ባይነት ያልሆነው . . .

 ይቅር ባይነት ማለት አስከፊ ባሕሪዎቻቸውን ፊት ለፊት መጋፈጥ የለባችሁም ማለት አይደለም፡፡
 ይህም ሲባል ደግሞ ዘለፋዊ ግንኙነት ውስጥ መቆየት ወይም ትክክለኛ ያልሆኑ ተግባሮች
እንዲቀጥሉ መፍቀድ አለባችሁ ማለትም አይደለም፡፡
 የበዳያችሁን የበደል እዳ መሰረዝና የእሱን/የሷን መጻኢ እድል ፈንታም ደግሞ ሁሉን ለሚችልና
ለሚያውቅ አምላክ እጆች አሳልፎ መስጠት ብቻ ነው ማለት ነው፡፡

እኔና እናንተስ?

 ነጻነት ማለት ልብን የማንጻት ጒዳይ ነው፡፡


 "ይቅርታን-መለማመድን" የኑሮ'ዜያችን አድርገን እናዳብር— ለሚያጋጥመን ለማንኛውም
የሚያናድድ ቃልና ድርጊት ሁሉ ደግሞ ይቅርታን አጸፋዊ ምላሻችን እናድርግ፡፡
 ከዚያም ማንኛውንም የምሬትና የጥርጥር ዘር በልባችን ውስጥ ሥር እንዲሰድና ጠላትም ነፍሳችንን
አንቆ እንዲይዝ ፈጽመን መፍቀድ የለብንም፡፡
 በእውነት ነጻ እንሆናለን፣ የሰማያዊ አባታችንም ባሕርይንም እናንጸባርቃለን፡፡( መዝመር 103፡ 8-
12 አንብብ)፡፡
 እንጸልይ፡፡ (በጸሎት ይዘጋ)

ለቡድን ውይይት የቀረቡ ጥያቄዎች

 ከክፍለ ትምህርቱ ምን ገንቢና ጠቃሚ ሐሳቦችን አገኛችሁ?


 ኢየሱስ ይቅር ያላችሁ ምንድን ነው?
 እባካችሁን እናንተ ይቅርታን ስትቀበሉ ወይም ሌላውም ሰው ይቅርታን ያደረጋችሁበትን
ምስክርነታችሁን አካፍሉ፡፡
 መናዘዝ የምትፈልጉት አሊያም ደግሞ ይቅርታን ለመጠየቅ የምትፈልጓቸው ነገሮች አሉን?
 ሌሎችን ይቅር ማለት የምትፈለጉት አንዳች ነገር አለን? በደል-እዳቸውስ ምንድን ነው?
 ዛሬ እነሱን ይቅር ለማለት ዝግጁዎች ናችሁን? ወይም ፈቃደኞች ሆናችሁ በደል -ዕዳዎቻቸውን
ለመሰረዝስ ምን ማድረግ ይኖርባችኋል?
 የይቅርታን ኀይል በቤተሰባችሁ ውስጥ፣ በሥራ ገበታችሁ፣ እና በማኅበረሰባችሁ ውስጥ እንዴት
ተግባራዊ ታደርጉታላችሁ ወይም ትለማመዱታላችሁ?

ጸሎት (በትንንሽ ቡድኖች ውስጥ)

 ወሰንየለሹን የእግዚአብሔርን ጸጋና ይቅርታ ተቀበሉ፣


 የገዛ-ራሳችሁን ይቅር በሉ፣
 የበደሏችሁን ሌሎችን ይቅር የማለትን ኀይልን እንድታገኙ ጸልዩ፣
 በቤተሰቦቻችሁ፣ በሥራ ቦታችሁ፣ እና በማኅበረሰባችሁ ውስጥ የክርስቶስን ያልተገደበ ጸጋ እና
ይቅርታ ማስተላለፊያ መሥመር/አሸንዳ/ ለመሆን እንዲያስችላችሁ ኀይልንና ጥበብን እንድታገኙ
ጸልዩ፡፡

You might also like