All Document Reader 1710961360104

You might also like

Download as pdf or txt
Download as pdf or txt
You are on page 1of 6

አዲስ አበባ እንዲህ እንደ ዛሬው አልነበረችም። ዘመናዊ ፎቆች ለምልክት እንኳ አልነበሩም :: ምንአልባት

ፎቅ ከተባሉ አራዳ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ፊት ለፊት እንዳለው የእንጨት ደረባ ቤት ዓይነት ካልሆነ በስተቀር
እንደ ዛሬው ተመልካችን በውበታቸው የሚያነሆልሉ ሰማይ ጠቀስ ቤቶችን አዲስ አበባ ገና አልተዋወቀችም
ነበር።

የዚያኔዋ አዲስ አበባ ፎቅ ብቻ ሳይሆን ዘመናዊ የአስፋልት መንገዶችም ገና አልተስፋፉባትም ::


ከከተማ
ወጣ ስንል የምናያቸው ከእንጨትና ከጭቃ የተሠሩ ችምችም ያሉ የገጠር መንደሮች የዚያኔዋን አዲስ አበባን
በሚገባ ሊያስታውሱን የሚችሉ ይመስለኛል፡፡

ከእኒያ ጕስቁል የአዲስ አበባ ሰፈሮች መካከልም ጠመንጃ ያዥ በመባል የምትታወቀው አንዷ ሠፈር

ነበረች:: ጠመንጃ ያዥ እንደ ሌሎቹ የሀገራችን ቦታዎች በተወላጆቿ የምትለማ፣ ሕጻናት እንደ ልብ
የሚቦርቁባት፣ ኮረዶች ፍቅርን በነፃነት የሚሸምቱባት፣ ወጣቶች እንዳሻቸው የሚፈነጩባት አልነበረችም፡፡
በአንጻሩም ጣሊያኖችና ባንዳዎች በአስነዋሪ ድርጊታቸው የሚጠየቁባት ሰዓት መቅረቧን አውቀው እንደ ባሕር

ቄጠማ መራድ የጀመሩባት ወቅት ናት - መስከረም 1933 . :: ዓ ም

ምንም እንኳ ዘመኑ እንደ_ ወትሮው በነፃነት መቦረቅ የተከለከለበት ቢሆንም፣ መስከረም የጸደይ ወራት
መግቢያ በመሆኑ ጋራው ሸንተረሩ፣ በተፈጥሮ ጌጥ መንቈጥቈጥ ጀምሯል፡፡

ዕለቱ የመስቀል በዓል የሚከበርበት ነው - መስከረም 17 1933 .


ቀን ዓ ም። በዚህ ዕለት
የመስቀል ገጸ በረከት የሚሆን አንድ ስጦታ ለወላጆቼ ከአምላክ ተበረከተ፡ ቤታችንም በደስታ ተሞላ፡፡

በአጭር አነጋገር እኔ ተወለድሁና ወላጆቼ በደስታ ወይን ስከሩ፡፡ ይሁን እንጂ በማላውቀው ምክንያት የወላጆቼን

ፍቅር ከስድስት ወር በላይ ለማጣጣም አልታደልሁም :: /


የእናቴ የወ ሮ ጌጤነሽ ጉርሙ እናት ( )
አኮይ

/
እያልሁ የምጠራቸው አያቴ ወ ሮ ነገኤ ዲንሳ ወሊሶ ይኖሩ
ነበርና በስድስተኛ ወሬ ወደዚያው ወሰዱኝ፡ አባቴ አቶ ገሠሠ ወልደ ኪዳን አገሩ ቡልጋ ሲሆን፤ የአባቴ እናት

( ) /
አያቴ ወ ሮ ሐበሻ ሁሴን አሊ ሰዲቅ ደግሞ የወሎ ተወላጅ ናቸው ::
እናቴ ወ ሮ ጌጤነሽ ጉርሙ /
ግን ከወሊሶ አለፍ ብሎ ከሚገኘውና ‹‹ጐሮ›› እየተባለ በሚጠራው ወረዳ ውስጥ ነው የተወለደችው፡፡ እናቴ

ለእናቷ ብቸኛ ልጅ ነበረች :: እኔም ለእናቴ አንድ ነኝ :: /


የአባቴ እናት ወ ሮ ሐበሻ ሁሴን ዓሊ ሰዲቅ

ሙስሊም ነበሩ :: /
የአባቴ አባት አያቴ አቶ ወልደ ኪዳን የኋላዬ ወ ሮ ሐበሻን ያገቡት በስገሌ ዘመቻ

ላይ ተገናኝተው ነው ::
ከጋብቻቸው በኋላም ክርስትና አስነሥተዋቸው ወ ሮ ሐበሻ ግዛው ተብለው /
ተጠሩ። እኔም አልተጠመቅሁም ነበር፡፡ እናቴንና ሴት አያቴን ክርስትና ያስነሥዋቸው አያቴ አቶ ወልደ ኪዳን

ናቸው፡፡ እኔም ክርስትና የተነሣሁት በ 12 ዓመቴ እዚሁ አዲስ አበባ

ኮልፌ አካባቢ ነው :: ኮልፌ የሄድኩበት ምክንያት ከተወሰነ ጊዜ በኋላ አባቴ ከጠመንጃ ያዥ ሠፈር ወደ
ኮልፌ በመዛወሩ ምክንያት ነው፡፡

አባቴና ዘመዶቼ ሲናፍቁኝ ከወሊሶ እመጣና ለተወሰነ ጊዜ እርሱ ዘንድ እቆይ ነበር፡፡

የወሊሶው ሠፈራችን በተለምዶ ‹‹አረብ ተራ›› ተብሎ ይጠራ ነበር፡፡ ዛሬ ቀበሌ ዜሮ ሦስት በሚል ስያሜ

ይታወቃል :: ሠፈሩ እንደ ሌሎች

የገጠር መንደሮች አቧራ የሞላበት ቢሆንም የልጅነት ዓለሜን ያየሁበት

በመሆኑ ዛሬም ይናፍቀኛል፡፡

የጨርቅ ኳስ ሰፍተን የምንዝናናበት፣ ቡሄ የምንጨፍርበት፣ ጥና ሲልም በቡድን የምንደባደብበት ወዲያውም

የምንታረቅበት በመሆኑ በእርግጥም ወሊሶ ሊረሳ የሚችል አይደለም ::


/
ወሊሶ እያለሁ “ጌታቸው ንጋቱ፣ ግርማ ወ ጊዮርጊስ፤ ጌታቸው አባ ሙዳ፣ በኃይሉ ጌታሁን፤ ዘሪሁን ጆቴ :
ከበደ ተክሉ " የሚባሉ ጓደኞች ነበሩኝ፡፡ በጣም እንዋደድ
ነበር፡፡ ከእነዚህ ልጆች ጋር ደግሞ በሠፈር ብቻ ሳይሆን የምንማረውም በአንድ ትምህርት ቤት ውስጥ ነበር።

የትምህርት ቤታችን ስም ግዮን›› ይባል ነበር። በኋላ ስሙ ተለውጦ ‹ራስ ጐበና አባ ዳጨው፡ ተብሏል ::
በአሁኑ ወቅት የትምህርት ቤቱ ስም ወሊሶ ሊበን , ተብሎ ተሠይሟል :: ትምህርት ቤት ከገባሁ በኋላ

( ጥበቡ በቀለ፣ ከበደ ዓለማየሁ፤ ሰናይ፣ ሽፈራው ጥላሁን፤ ..." የሚባሉ ጓደኞችንም ማግኘት

ችያለሁ :: ግና ምን ያደርጋል ትምህርት ላይ እስከዚህም ነበርሁ ::


በእንግሊዝኛ በሳይንስና በሒሳብ
አፈር ስበላ በመዝሙር አንበሳ ነበርሁ፡፡ ትምህርቱ ሁሉ በመዝሙር ቢሆንልኝ ደስታውን አልችለውም ነበር።

የእኔ ጥንካሬ፤ የእኔ ጉብዝና መዝሙር ላይ ብቻ ነው፡፡ የመዝሙር አስተማሪዎቻችን እነ ጽጌ፣ እነ ወ ሮ /


በቀለች ነበሩ :: የሒሳብ አስተማሪያችን ደግሞ ኮሞዶር ጣስው ይባሉ ነበር። ጋሼ ሐጐስም አማርኛ

/
ያስተምሩን እንደ ነበር አስታውሳለሁ፡፡ የት ቤቱ ዲሬክተር

<< ሚስተር እዝሚን >> ይባሉ ነበር።

መምህሮቼ ምንም ያህል ቢወዱኝ እኔ ከትምህርት


/
ይልቅ ጨዋታ ነፍሴ ነበር። አንዴ ከበደ ተክሉ፤ ዘሪሁን ጆቴ፣ በኃይሉ ጌታሁን፣ ግርማ ወ ጊዮርጊስና ጌታቸው
ንጋቱ፣ እኔ ሆነን በአማርኛ ‹‹እሼ›› በኦሮምኛ ቆላዲ›› የሚባል የዛፍ ፍሬ ለመልቀም ‹‹ቂሎ” ወደ ተባለ ቦታ
ሄድን፡፡ ሁላችንም ዛፍ ላይ ለመውጣት ከጦጣ ያላነሰ ችሎታ ስለ ነበረን የዛፍ ፍሬ ለመልቀም ችግር
አልነበረብንም።

ዛፍ ላይ ወጥተን ያንን ቆላዲ እየተሻማን ስንለቅም የዛፉ ቅርንጫፍ ይገነጠልና ከሥር ካለው ባሕር ውስጥ
እንገባለን፡፡ ከሁላችንም ለአደጋ የተጋለጠው ዘሪሁን ጆቴ ነበር፡፡ እሱን ለማውጣት ስንረባረብ ለካስ አካባቢው

የሽፍቶች መናኸሪያ ኖሯል፤ ድንገት ጥይት ይተኵላል። በዚህ ጊዜ የት እንግባ ?አትምህርት ቤት ጠፍተን
ነው የመጣነው፡ ወላጆቻችን የት እንዳለን አያውቁም። የሚገርመው ነገር የጥይት ድምፅ ለመጀመሪያ ጊዜ

የሰማሁት ያን ዕለት ነበር ::

You might also like