Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 9

በኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት

የብሔራዊ ዓሣና የውኃ ውስጥ ህይወት ምርምር ማዕከል

ስለተቀናጀ የዓሣ ግብርና፤ የዓሣ ምግብ፤ ጫጩት አረባብ እና የወንድ ቆረሶ ዓሣን ለይቶ
ስለማሳደግ

የስልጠናና ሠርቶ ማሣያ ትግበራ ንድፈ ሐሳብ እቅድ

የግብርና ኤክስቴንሽንና ኮሚኒኬሽን የሥራ ሂደት


አዘጋጅ፡ አቶ ያሬድ መስፍን

የካቲት 24 ቀን‚ 2013 ዓ.ም


የብሔራዊ ዓሣ እና የውኃ ውስጥ ህይወት ምርምር ማዕከል
ሰበታ

ርዕስ፡- የተቀናጀ ዓሣ ግብርና፤ የወንድ ቆረሶ ዓሣን ለይቶ የማሳደግ እና ስለ ዓሣ ምግብ ዓይነቶች ግንዛቤ
ማስጨበጫ ስልጠናና ሠርቶ ማሳያ
የስልጠናና ሠርቶ ማሳያው ቦታ፡ በብሔራዊ ዓሣ እና የውኃ ውስጥ ህይወት ምርምር ማዕከል፤ ሰበታ

ተሳታፊ ሰልጣኞች የሚመረጡባቸው ወረዳዎች፡-

ከምስራቅ ሸዋ (ቢሾፍቱ)፤ ከምዕራብ ሸዋ (ኤጀርሳ፤ ቶኬ፤ ጅባት፤ ቀርጫ ቡሌሆራ) እንዲሁም ከደቡብ
ምዕራብ ሸዋ ወንጪ ወረዳ

የሰልጣኞች አይነት፡ ዓሣ የሚያረቡ አርሶ አደሮች፤ እንዲሁም የወረዳ ባለሙያዎች እና የቀበሌ ልማት ጣቢያ
ሠራተኞች

ከውጭ የተጋበዙ አጠቃላይ ተሳታፊዎች ብዛት፡ 73

ዓሣ አርቢ አርሶ አደሮች፡- 52

የወረዳ ባለሙያዎች እና የቀበሌ ልማት ጣቢያ ሠራተኞች፡- 14

ከየወረዳው የመጡ ሾፌሮች፡- 7

በስልጠናው ላይ የሚሳተፉ የማዕከሉ ሰራተኞች

ከሰልጣኞች ውጪ ያሉ ተሳታፊ የማዕከሉ ሠራተኞች ብዛት፡- 12

የምርምር ሥራው ባለቤት ተሳታፊዎች ፡- 2 (2 አስተባባሪዎች)

ከሒሳብ ክፍል ፡- 2 የሒሳብ ሠራተኛ

አሠልጣኞች፡- 2

የጽዳት ሠራተኞች፡- 2

አስተናጋጅ፡- 1

ሾፌር፡- 1

ማዕከል ዳይሬክተር፡- 1

አይሲቲ፡- 1

የስልጠናና ሠርቶ ማሣያው አስፈላጊነት፤ ይዘት፤ አካሔድ እና ዓላማ

እንደሚታወቀው ማዕከላችን በዓሣ ግብርና ዙርያ አብረውን ለሚሠሩ እና እየሠሩም ላሉ የተለያዩ አካላት

ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታ ሥራ እየሠጠ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ከዚህ በፊት በማሕበራዊ የምርምር ዘርፍ
በተደረገው የዳሠሣ ጥናት ውጤት መሠረት እና በተከታታይነት ባገኘናቸው የአቅም ግንባታ ፍላጎቶች

መሠረት አሁን እየተገበሩ ላሉት የዓሣ ግብርና ሥራም ሆነ በቀጥይነት ላሰብናቸው በራስ (በአምራቹ) አቅም

ለሚከወኑ የማስፋፋት ሥራዎች ይረዳ ዘንድ ለዓሣ ግብርና እንደ ዋና ተግዳሮት ከሆኑት መካከል ከኩሬ አያያዝ

በተጨማሪ እንደ ዓሣ ምግብ፤ እና ጫጩት የመሣሠሉት ዋነኞቹ ሲሆኑ እነዚህን እና ሌሎቹንም በዘላቂነት

ለመፍታት ቅድሚያ የአቅም ግንባታ አስፈላጊ ስለሆነ ይህንንም በመረዳት እስከዛሬ ስንሰራባቸው ከነበሩ ዞኖች

እና በተጨማሪነት በእቅድ ከተያዙ ወረዳዎች መካከል ከዞን ምስራቅ፤ ምዕራብን እና ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞንን

እንዲሁም በወረዳ ደረጃ ከምዕራብ ሸዋ ኤጀርሳ፤ ቶኬ፤ ጅባት፤ ቀርጫና ቡሌሆራ፤ ከደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን

ደግሞ ወንጪ ወረዳን የሚያሳትፍ የሥልጠናና ሠርቶ ማሳያ መርሐ ግብር ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

የሥልጠናና የሠርቶ ማሳያው መርኃ ግብር በአጠቃላይ የታቀደው ለ 6 ቀናት ሲሆን አጠቃላይ ተሳታፊውም ለ

2 ተከፍሎ ለመጀመሪያው ዙር ለ 3 ቀናት በሚካሔደው አጠቃላይ ተሳታፊዎች 33 ማለትም 30 ሰልጣኞች

እና 3 ሾፌሮች ከምዕራብ ሸዋ ዞን ካሉ ወረዳዎች፡ ኤጀርሳ፤ቡሌሆራና፤ቶኬ ወረዳዎች ሰልጣኞች ተጋብዘው

ሲመጡ በሁለተኛው ዙር ደግሞ 37 አጠቃላይ ተሳታፊዎች ማለትም 33 ሰልጣኞች እና 4 ሾፌሮች ከምዕራብ

ሸዋ ዞን ጅባት እና ቀርጫ ወረዳዎች እንዲሁም ከምስራቅ ሸዋ ዞን ቢሾፍቱና ከደቡብ ምዕራብ ዞን ወንጪ

ወረዳ ይጋበዛሉ፡፡ በአጠቃላይ ሁለቱም ዙሮች እያንዳናዳቸው አጠቃላይ የጉዞ ቀናትን ጨምሮ 3 ቀናትን

ይወስዳሉ፡፡ የስልጠና በመርኃ ግብሩም የመጀመሪያው ቀን ከላይ በተለዩት አርዕስት ሥልጠና በመስጠት

በተከታዮቹም ሁለት ቀናት በአሠልጣኝ የተደገፈ እና በሠልጣኞችም የሚብራራ የሠርቶ ማሣያ ተግባራት

እንዲሁም የግብረ መልስ መሠብሠቢያ ውይይቶች ይከናወናሉ፡፡

በአጠቃላይ የዚህ ሥልጠናና ሠርቶ ማሣያ ዓላማም በመስክ ዳሰሳ ጥናት እና የግምገማ ጉብኝት ወቅት በዓሣ

አምራቹ ዘንድ ከዚህ በፊት በተለዩ የአቅም ውስንነቶች ላይ ተመርኩዘን ለምሳሌ በተቀናጀ የዓሣ ግብርና ዘዴ

እንደ አካባቢው የግብርና ሥራ ዓይነት እንዲስፋፉ የምንፈልጋቸውን የአሠራር ዘዴዎችን ለማሰልጠን፤ እና

ሠርተን ለማሳየት እንዲሁም ከሠልጣኞች የሚመጠትን እና ምርምሩን አቅጣጫ ለማስያዝ የሚረዱ ግብረ

መልሶችን ለመሰብሰብ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ከተሳታፊ ባለድርሻ አካላት ጋር ዘላቂ ትስስርን ለመፍጠርም

የሚረዳ መድረክ ነው፡፡


ከስልጠናውና ሠርቶ ማሳያው ይገኛል ተብሎ የሚታሰበው እውቀትና ክህሎት

 የተሳታፊ አርሶ አደሮችን የሥራ ተነሳሽነት መጨመር

 በዓሣ ግብርና ላይ ተሳታፊ የሆኑ አርሶ አደሮች በራሳቸው የዓሣ ጫጩትን እንዲባዙ
የሚስችላቸውን እውቀት እና ክህሎት ማስጨበጥ

 አማራጭ የዓሣ ምግቦችን በአካባቢያቸው ከምን ሊያገኙ እንደሚችሉ ማሳወቅ እንዲሁም


የወንድ ቆረሶ አሶችን ብቻ መርጦ በማሳደግ ሁለቱንም ጾታዎች አንድ ኩሬ ውስጥ ከማሳደግ
ይልቅ የተሻለ እድገትን እንደሚያሳይ እና የዓሣ ግብርናን ከሌሎች የግብርና ሥራዎች (ሰብልና

እንስሳት) ጋር በማቀናጀት የተሸለ አጠቃላይ ምርት እንዲሁም ወጪ ቀናሽ አማራጮችን


ማሳወቅ ናቸው፡፡

ለስልጠናውና ሠርቶ ማሳያው የሚያስፈልጉ ግብዓቶችና ፋሲሊቲዎች

 ለዓሣ ምግብነት ሊውሉ የሚችሉ የኢንዱስትሪ ተረፈ ምርቶች (የኑግ ኬክ ወይም ፋጉሎ፤

የስንዴ ብጣሪ ወይም ፉሩሽካና የቢራ እህል ጭማቂ) ቢያንስ ከእያንዳንዱ አንድ አንድ ኪሎ

በጎድጓዳ ሳህን)
 ሁለት ወላድ አሶች እና አንድ ለማሳያነት የሚውል ኩሬ
 አንድ ጫጩት ዓሶችን የያዘ ኩሬ (ቢያንስ ለማሳያነት የሚሆኑ ሁለት ጫጮቶችን ማግኘት

የሚቻልበት)
 በሙከራ ላይ ያለ የተቀናጀ ዓሣ ግብርና ሰርቶ ማሣያ ቦታ (ለምሳሌ የተቀናጀ የዓሣ ግብርናው
ቦታ ወይም መንደር ዶሮን፤ የተፈጥሮ ማዳበሪያ መስሪያ ቦታን፤ ደክ ዊድ እና አዞላ የውኃ
ውስጥ የዓሣ ምግቦችን፤ የአትክልት እና አልፋልፋ ሰብል ማሳን ሊያካትት ይችላል፡፡

ከውጭ የሚጋበዙ ተሳታፊዎች ዝርዝር

በብሔራዊ ዓሣና የውኃ ውስ ሕይወት ምርምር ማዕከል ቅጽር ግቢ ውስጥ ለሚካሔደው የሠርቶ ማሳያ መርኃ
ግብር የሚሳተፉ ተሳታፊዎች ብዛት እና የሚመረጡባቸው ወረዳዎች

ተ.ቁ የወረዳው ስም ተሳታፊ ብዛት ወንድ ሴት

1. ኤጀርሳ አርሶ አደሮች 7 5 2


የግብርና ባለሙያ 1 1 -
የልማት ጣቢያ ሠራተኛ 1 1 -
2 ቡሌሆራ አርሶ አደሮች 7 5 2
የግብርና ባለሙያ 1 - 1
የልማት ጣቢያ ሠራተኛ 1 - 1
3 ቶኬ አርሶ አደሮች 7 5 2
የግብርና ባለሙያ 1 1 -
የልማት ጣቢያ ሠራተኛ 1 1 -
4 ጅባት አርሶ አደሮች 7 5 2
የግብርና ባለሙያ 1 - 1
የልማት ጣቢያ ሠራተኛ 1 - 1
5 ቀርጫ አርሶ አደሮች 7 5 2
የግብርና ባለሙያ - - -
የልማት ጣቢያ ሠራተኛ 1 1 -
ጠቅላላ የተሳታፊ ብዛት 44 30 14

ከእያንዳንዱ ወረዳ አንድ አንድ ሾፌር ቢመጣ ተብሎ ታስቦ አጠቃላይ ከ 5 ሾፌር ጋር 49 ተሳታፊዎች
ይጋበዛሉ፡፡

በብሔራዊ ዓሣና የውኃ ውስ ሕይወት ምርምር ማዕከል ቅጽር ግቢ ውስጥ ለሚካሔደው የሠርቶ ማሳያ መርኃ
ግብር የሚሳተፉ ተሳታፊዎች ብዛት

ተ.ቁ የወረዳው ስም ተሳታፊ ብዛት ወንድ ሴት

1. ቢሾፍቱ አርሶ አደሮች 7 5 2


የግብርና ባለሙያ 2 1 1
የልማት ጣቢያ ሠራተኛ 2 1 1
2 ወንጪ አርሶ አደሮች 10 7 3
የግብርና ባለሙያ 1 1 -
የልማት ጣቢያ ሠራተኛ - - -
ጠቅላላ የተሳታፊ ብዛት 22 15 7

በአጠቃላይ ከ 2 ሾፌር ጋር 24 ተሳታፊዎች ከእነዚህ 2 ወረዳዎች ይጋበዛሉ፡፡

በ 2ቱ ዙር ስልጠናዎች የሚኖረው የበጀት አመዳደብ

1. በመጀመሪያው ዙር ስልጠና አጠቃላይ የተሳታፊዎች ብዛት እና የሚያስፈልገው በጀት

1.1. የስልጠና ውሎ አበል


ተ.ቁ ተሳታፊ የተሳታፊ የቀን አበል የሥልጠናው ቀን አጠቃላይ
ብዛት ብዛት ክፍያ
1. አርሶ አደሮች 21 250 3 15,750
የግብርና ባለሙያዎች 4 450 3 5400
የልማት ጣቢያ 4 300 3 3,600
ሠራተኞች
የወረዳ ሾፌሮች 4 200 3 2,400
የማዕከሉ አሠልጣኝ 1 1 300 6 1,800
የማዕከሉ አሠልጣኝ 2 1 300 6 1,800
የሥራው አስተባባሪዎች 2 300 5 3,000
ሒሳብ ክፍል (ሒሳብ 1 301 3 903
ሠራተኛ)
ሒሳብ ክፍል (ገንዘብ 1 259 3 777
ጽዳት
ከፋይ) ሠራተኞች 2 259 3 1,554
አስተናጋጅ 1 259 3 777
የማዕከል ዳይሬክተር 1 400 3 1,200
የማዕከል ሾፌርና 2 301 3 1,806
ስምሪት
አይሲቲ 1 301 3 903
ድምር 42 - - 41,670

1.2 የመስተንግዶ ወጪ
ተ.ቁ የተሳታፊ ብዛት የመስተንግዶ ወጪ በአንድ ሰው የሥልጠናው ቀን ብዛት አጠቃላይ ክፍያ
1 42 280 3 35,280

1.4 የመጓጓዣ ወጪ
ተ.ቁ የተሳታፊ ብዛት ደርሶ መልስ የመጓጓዣ ወጪ በአንድ ሰው የጉዞ ብዛት አጠቃላይ ክፍያ
1 27 200 ደርሶ መልስ 5,400

ለመጀመሪያ ዙር ስልጠናና ሠርቶ ማሳያ አጠቃላይ ወጪ 82,350 ብር

2. በሁለተኛው ዙር ስልጠና አጠቃላይ የተሳታፊዎች ብዛት እና የሚያስፈልገው በጀት

2.1. የስልጠናና ሠርቶ ማሳያ ውሎ አበል


ተ.ቁ ተሳታፊ የተሳታፊ የቀን አበል የሥልጠናው ቀን አጠቃላይ
ብዛት ብዛት ክፍያ
1. አርሶ አደሮች 31 250 3 23,250
የግብርና ባለሙያዎች 3 450 3 4,050
የልማት ጣቢያ 3 300 3 2,700
ሠራተኞች
የወረዳ ሾፌሮች 3 200 3 1,800
የማዕከሉ አሠልጣኝ 1 1 300 6 1,800
የማዕከሉ አሠልጣኝ 2 1 300 6 1,800
የሥራው አስተባባሪዎች 2 300 5 3,000
ሒሳብ ክፍል (ሒሳብ 1 301 3 903
ሒሳብ
ሠራተኛ) ክፍል (ገንዘብ 1 259 3 777
ከፋይ)
ጽዳት ሠራተኞች 2 259 3 1,554
አስተናጋጅ 1 259 3 777
የማዕከል ዳይሬክተር 1 400 3 1,200
የማዕከል ሾፌርና 2 301 3 1,806
ስምሪት
አይሲቲ 1 301 3 903
ድምር 53 - - 46,320

2.2 የመስተንግዶ ወጪ
ተ.ቁ የተሳታፊ ብዛት የመስተንግዶ ወጪ በአንድ ሰው የሥልጠናው ቀን ብዛት አጠቃላይ ክፍያ
1 53 280 3 44,520

2.4 የመጓጓዣ ወጪ
ተ.ቁ የተሳታፊ ብዛት ደርሶ መልስ የመጓጓዣ ወጪ በአንድ ሰው የጉዞ ብዛት አጠቃላይ ክፍያ
1 37 200 ደርሶ መልስ 7,400

የመጀመሪያ ዙር ስልጠናና ሠርቶ ማሳያ አጠቃላይ ወጪ 98,240 ብር

የስልጠናው አጠቃላይ ወጪ (በሁለቱም ዙሮች)

ለ 95 የስልጠናው ተሳታፊዎች የአበል ክፍያ = 87,990

አጠቃላይ የመስተንግዶ ወጪ= 79,800

አጠቃላይ የመጓጓዣ ወጪ= 12,800


ድምር--------------------- 180,590 ብር

የስልጠናው ቀን፡- መጋቢት 15፣ 2013 ዓ.ም

You might also like