Professional Documents
Culture Documents
መክሥተ አርእስት ቅኔ
መክሥተ አርእስት ቅኔ
ሠኔ ፳፻፲ወ፭ ዓ.ም
i
መክሥተ አርእስት
ii
፯. ርእይ...................................................................................................................................................... 4
፩.፬ ዋይዜማ ቅኔ ዘአለቃ ለማ ........................................................................................................................... 5
፩. የቅኔው ትርጕም፤ ................................................................................................................................... 5
፪. የቅኔው መፈጠሪያ፤ ................................................................................................................................. 5
፫. የቅኔው ዐውድ (መቸት)፤ ........................................................................................................................ 5
፬. ቅኔው የቀረበበት መንገድ፤....................................................................................................................... 5
፭. የቅኔው ዐቢይ መልእክት፤....................................................................................................................... 5
፮. ተጨማሪ................................................................................................................................................. 6
፯. ርእይ...................................................................................................................................................... 6
፩.፭. ሣህልከ ቅኔ ............................................................................................................................................. 6
፩. የቅኔው ትርጕም፤ ................................................................................................................................... 6
፪. የቅኔው መፈጠሪያ፤ ................................................................................................................................. 6
፫. የቅኔው ዐውድ /መቼት/፤ ....................................................................................................................... 6
፫. የቅኔው ዐቢይ መልእክት፤ ....................................................................................................................... 7
፮ ተጨማሪ .................................................................................................................................................. 7
፯. ርእይ...................................................................................................................................................... 7
፩. የቅኔው ትርጕም፤ ................................................................................................................................... 8
፪. የቅኔው መፈጠሪያ፤ ................................................................................................................................. 8
፫. የቅኔው ዐውድ መቼት፤ ........................................................................................................................... 8
፬. ቅኔው የቀረበበት መንገድ፤....................................................................................................................... 8
፭. የቅኔው ዐቢይ መልእክት፤....................................................................................................................... 8
፮. ተጨማሪ................................................................................................................................................. 8
፯. ርእይ...................................................................................................................................................... 9
፪.፪. መወድስ ዘአለቃ ለማ ኃይሉ - ወጽአ ይዝራዕ ........................................................................................ 9
፩. የቅኔው ትርጕም፤ ................................................................................................................................... 9
፪. ቅኔው መፈጠሪያ (ምንጭ)፤................................................................................................................... 10
፫. የቅኔው ዐውድ (መቼት)፤ ...................................................................................................................... 10
፬. ቅኔው የቀረበበት መንገድ፤..................................................................................................................... 10
፭. የቅኔው ዐቢይ መልእክት፤..................................................................................................................... 10
፮. ርእይ .................................................................................................................................................... 10
iii
፪.፫ መወድስ ቅኔ ዘአለቃ ለማ ኃይሉ- ትዕግሥተ ንባቡ ................................................................................... 11
፩. የቅኔው ትርጕም፤ ................................................................................................................................. 11
፪. የቅኔው መፈጠሪያ /ምንጭ/፤ ................................................................................................................ 11
፫. የቅኔው ዐውድ (መቼት)፤ ...................................................................................................................... 11
፬. የቅኔው መንገድ፤................................................................................................................................... 12
፭. የቅኔው ዐቢይ መልእክት፤..................................................................................................................... 12
፮. ርእይ .................................................................................................................................................... 12
፪.፬. መወድስ ቅኔ ዘአለቃ ለማ -ጻድቅ ይምሕር............................................................................................... 12
፩. የቅኔው ትርጕም፤ ................................................................................................................................. 13
፪. የቅኔው መፈጠሪያ፤ ............................................................................................................................... 13
፫. የቅኔው ዐውድ (መቼት)፤ ...................................................................................................................... 13
፬. ቅኔው የቀረበበት መንገድ፤..................................................................................................................... 13
፭. የቅኔው ዐቢይ መልእክት፤..................................................................................................................... 13
፮. ርእይ .................................................................................................................................................... 13
፪.፭. አሠረ ንጉሥ ዘአለቃ ለማ - ምኒልክ ግበር .............................................................................................. 14
፩. የቅኔው ትርጕም፤ ................................................................................................................................. 14
፪. የቅኔው መፈጠሪያ (ምንጭ)፤ ................................................................................................................. 14
፫. የቅኔው ዐውድ (መቼት)፤ ...................................................................................................................... 14
፬. ቅኔው የቀረበበት መንገድ፤..................................................................................................................... 14
፭. የቅኔው ዐቢይ መልእክት፤..................................................................................................................... 14
፮. ተጨማሪ............................................................................................................................................... 15
፯. ርእይ.................................................................................................................................................... 15
ማጠቃለያ ...................................................................................................................................................... 16
ስምዐት/ወሃቢ/ዋቢ/ ....................................................................................................................................... 17
iv
መግቢያ
ቅኔ ማለት እንደመልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬና እንደ ቅኔ ምሁራን ‹‹ቀነየ›› ገዛ ከሚለው ኀላፊ ግስ
የተገኘ ሲኾን ቃላዊና ምስጢራዊ ትርጉሙ ደግሞ በዋናነት ለፈጣሪ መገዛት፤ ለፈጣሪ የሚቀርብ አምኃ
ስብሐት፤መሥዋዕተ ስብሐት፤ የነገር ስልት (ጥበብ)፤ ግጥም ብቻ ያይደለ ምጣኔ፤ስያሜ ያለው፤ አንድ
ሰው በተረዳው መጠን ከሰው የማይበደረው (የማይኮርጀው)፤ ዐስቦና ቈጥሮ የሚነግረው፤ የሚዘረፍና
ከባለቅኔ የሚነጠቅ፤ የራስ የኅሊና ሀብት ብቻ የኾነ፤ ያልተማሩት የሚጠሉትና የሚመኙት፤ የተማሩት
ደግሞ ልሙትልህ ብለው የሚያፋቅሩት፤ ሐሳባቸውንና ቁጭታቸውን የሚገልጹበት እውነተኛ ትምህርተ
እግዚአብሔር ነው፡፡
ቅኔ ከሊቃውንቱ አንደበት ላይ ሊነጠቅ ይችላል፤ ነገር ግን አይመረመርም፤ የሰዎች ቅኔም ለፈተና ቀርቦ
ማንም ሊቅ (ሰው) በፈተናው እስካኹን ድረስ አልፎ አልተገኘም፤ ምክንያቱም ከእግዚአብሔር ቅኔ
(ሐሳብ) ይልቅ የግለሰብእ ሐሳብ (ቅኔ) ስለሚከብድ ነው፡፡
እንደማሳያም ይኽ መጽሐፍና የቅኔው ደራሲ ታላቁ ሊቅ አለቃ ለማ ኀይሉ ከረቂቁ ቅኔያቸው ጋራ
ተጠቃሽ ናቸው፡፡
ii
ክፍል ፩ዱ
፩. ቅኔያት ፩
= መጽሐፋዊ ነው፤
ጥቅስ =
‹‹ወይሤርየነ ወያሐይወነ በሰኑይ መዋዕል፤›› (ሆሴዕ. ፮÷፫)
‹‹ወምንት/ተ/ ይበቊዖ ለሰብእ ለእመ ኩሎ ዓለመ ረብሐ ወነፍሶ ኀጉለ፡፡›› (ማቴ. ፲፮÷፳፮፤ ሉቃ. ፱÷፳፭)
1
፩.፪ ዋይዜማ ቅኔ
ኢይበቁዕ ክብረ አዝማድ
እስመ ወልደ ባዕል ወድቀ ውስተ እደረኀብ ኃያል፤
አግብርት እንዘጽጉባን ወይተርፍ እክል፤
ምሳሌዝኒ ነገር አጠየቀተነ ጎል፤
አምጣነ ወልዳ ኢድኅነ እምለቢሰቈጽል፤
እንዘወርቀ ትፈትል ድንግል፡፡ (መንግሥቱ ለማ፤ 2003፤228/229)
2
፭. ዐቢይ የቅኔው መልእክት
ሀ. በሠም ሲገለጽ = አባባል፤ ዘመድ አይጠቅምም
ለ. የወርቅ ዐቢይ መልእክት እግዚአብሔር ወልድ ለድኅነተ ዓለም ከድንግል ማርያም በጎለ እንሰሳ
ተወልዶ ‹ከደነቶ እሙ ቈጽለ በለሶን› የሚለውን የሚሳይና በሥጋ መራቡን የሚያስተምር ነው፡፡
፮. ተጨማሪ
ሀ. የቅኔው የዜማ ስልት - ዓራራይ
ለ. የቤቱ ግጥም (መምቻው) ‹‹ል›› ቤት
ሐ. ደምፀት = ረኀብ ፡ ችግር (መቸገር)፤
፯. ርእይ
ሀ. ቅኔው የቀረበበት የዐ.ነገር ስልት በሁለት ማሠሪያና በሁለት አሥረጅ በመኾኑ መልካም ነው፡፡
ለ. ከሙያ አንጻር = ባለቤት ቀድሞ ሳይነገር ዝርዝር መቅደሙ ከባል ቀድሞ ልጅ ይሰጥሽ የሚለውን
የቅኔ መምህራን የስሕተት አባባልን እውን ያደርገ ነው፤ ምሳሌ ወልዳ የሚለው ነው፡፡
3
፫. የቅኔው ዐውድ (መቼት)፤
የጻድቁ አቡነ አሮን ዘመቄት የበዓል ዋይዜማ ይመስላል፡፡
፮. ተጨማሪ
ሐ. ድምፀት = ጥላቻ/ጠብ
፯. ርእይ
ሀ. እጅግ የቅኔው አሰካክ/አወቃቀር/ ይበል ነው፡፡
ለ. ምን አልባት ‹‹እምበዊአ ቤቱ›› እም "በ" ከሚለው በስተቀር
4
፩.፬ ዋይዜማ ቅኔ ዘአለቃ ለማ
ዘካርያስ አበአሐዱ ወአበብዙኀን አብርሃም
እምወሊደ ውሉድ አቀብ ዘኖፃ በረስዓኖሙ ኢስእኑ፤
አብ እምነውሉድ ይቀድም አኮኑ፤
ለኢትዮጵያሰ እም ዕበያ ዘአይትርከብ መጠኑ፤
እስከጽንፈ ዓለም ከመንዜኑ፤
እምነኵሉ ትውልድ በበዘመኑ፤
አበዊሁ ዘወለደ መኑ፡፡ (መንግሥቱ ለማ፤ 2003፤234)፡፡
፩. የቅኔው ትርጕም፤
ያንድ ልጅ አባት ዘካርያስ፤ የብዙዎች አባት አበርሃም
ልጆቹን ከመውለድ/የአሸዋ ዓቀበት በእርግናቸው ጊዜ አልተሣናቸውም (አልደከሙም) አባት ከልጁ
ይቀድማል፡፡ ልኩ መጠኑ የማይታወቅ የኢትዮጵያን ገናናነት ግን እስከ ዓለም ዳርቻ እንናገር ዘንድ፤
በየዘመኑ ከትውልድ ኹሉ አባቱን የወለደ ማን ነው?
፪. የቅኔው መፈጠሪያ፤
አባባል፤ ‹ልጅ ካባት አይበልጥም›
5
፮. ተጨማሪ
ሀ. የቅኔው የዜማ ስልት = ዕዝል /ሕዙል/
ለ. የቅኔው ግጥም /ቤት = "ኑ"
ሐ. ድምፀት = የአባትና የልጅ መቅደምና መከተል ነው፡፡
መ. ቅኔው የቀረበበት የዐረፍተ ነገር ስልት ባንድ የግስ ማሠሪያና አስረጅ፤ በአንድ የመኾን ግስ ነው፡፡
፯. ርእይ
የቅኔው ምስጢር ለባለቅኔው ብቻ የቀረ ነው፡፡
፩.፭. ሣህልከ ቅኔ
ማእዜ ለመደት ገዳመ ዕዝራ
አስካለ ማርያም ዘወጽአት እምድካመ አንስት ብሔራ፤
ለዘይሬእያ ኀይለጸላዒ
እስመ ብእሲተ ኢኮነት በግብራ፡፡ (መንግሥቱ ለማ፤ 2003፤234/35) ፡፡
፩. የቅኔው ትርጕም፤
የዕዝራን ገዳም መቼ ለመደችው?
ከሴቶች ድካም/አገሯ የወጣች አስካለ ማርያም
ለሚያያት የጠላት ኃይል በሥራዋ ሴት አልኾነችምና፡፡
፪. የቅኔው መፈጠሪያ፤
መጽሐፋዊ ነው፤ የአስካለ ማርያም የሥራ ኹኔታ
‹‹ዕዝራኒ ርእያ በርእየተ ብእሲት ወሶበ ርእያ ኢኮነ ብእሲተ አላ ሀገር ቅድስት››
(ዝማሬ ገጽ ፵፫፤ ዚቅ ገጽ ፸፪-፸፫፤ ጾመ ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ 353 ዕዝራ፲)፡፡
6
፫. የቅኔው ዐቢይ መልእክት፤
ሀ. ሠም = ወሶበ ርእያ ዕዝራ ኢኮነት ብእሲተ
ለ. ወርቅ = የአስካለ ማርያም ሴት ስትኾን ሀገር ናት ማለት ሀገር ኹሉን ቻይ መኾኑን ያሳያል፡፡
፮ ተጨማሪ
ሀ. የቅኔው የዜማ ስልት ግእዝ
ለ. የቅኔው ግጥም /ቤት/= ራ
ሐ. ድምፀት = ሙገሳ
መ. የቅኔው ግጥም ብዛት ሁለትና ማንደርደሪያ ያለው መደብ በሰረገላ ነው፡፡
፯. ርእይ
ለሰሙ የተጠቀሰው ጥቅስ ግልጽ ሲኾን
በወርቁ በኩል ግን የቅኔው ምስጢር ለባለቅኔው ብቻ ነው ግልጽነቱ፤
ምክንያቱም አስካለ ማርያም ማናት? የትኛዪቱስ ንግሥት?
ክፍል ሁለት
፪. ቅኔያት ፪
፪.፩ መወድስ ዘአለቃ ለማ ኃይሉ - ሰይፈ ምኒልክ
ሰይፈ ምኒልክ ክርስቶስ ዘኢይሠአር
ላእከ ኮነ ለግዝረተ ክሳድ በየዋሃቱ፤
ወእንተ ኢዘርዑ ሰብአ እምኢትዮጵያ ገራህቱ፤
የአርሩ እንበለ ጊዜሁ አስይፍት መገብቱ፤
ወኢተዘከረ ምኒልክ፤
ለመሥዋዕት በግዐ አምጣነ ሮማዊ መሥዋዕቱ፤
ለዓለም
አሕጸረሂ ኑኀ ምልክና በመጠነ ፀሓይ መስፈርቱ፤
አምጣነ ረሰየ አድማስ ወሰነ ለመንግሥቱ፤
ወእንዘ ይእኅዝ ምድረ ለባሕቲቱ፤
ሰማየ ለሥላሴ ኀደገ በኂሩቱ፡፡ (መንግሥቱ ለማ፤ 2003፤150/219)፡፡
7
፩. የቅኔው ትርጕም፤
የማይሻር ክርስቶስ/የምኒልክ ሰይፍ፤
አንገትን ለመግዘር መልእክተኛ አገልጋይ ኾነ፤
ያልዘሩትን ሰው ከርሻው/ኢትዮጵያ ያለ ጊዜው ያጭዳሉ ሹማምንቱ/አስይፍት፡፡
ምኒልክ ለመሥዋዕት በግ አላሰበም፤ መሥዋዕቱ ሮማዊ ነውና (ኢጣሊያ)፤
ያገዛዙን ቁመት ወርድ በመስፈሪያው/ፀሓይ ልክ አሳጠረ፤
ለመንግሥቱ ዳርቻ አድማስን አድርጓልና፡፡
ምድርን ለብቻው ይዞ፤ በቸርነቱ ሰማይን ለሥላሴ ተወላቸው፡፡
፪. የቅኔው መፈጠሪያ፤
መጽሐፋዊ ነው፤ ‹እብል እንከ ክርስቶስ ላእክ ኮነ ለግዝረት› (ሮሜ. ፲፭ ÷፰)
‹‹ማእረሩሰ ኅልቀተ ዓለም እሙንቱ ወዐጸዱኒ እሙንቱ መላእክት›› (ጾመ ድጓ ዘደብረ ዘይት ገጽ ፻፬)
፮. ተጨማሪ
8
፯. ርእይ
- ገጸ ንባቡ እጅግ ይበል የሚያሰኝ ነው፤ ቅኔው ንባብም ምስጢርም አለው፤ ነገር ግን በውስጠ ተሳቢ
በቅኔ ሞያ ሲታይ የሳቢና የተሳቢ ቅደም ተከተልን የሳተ ይመስላል፡፡
ምሳሌ፡- ‹ወእንተ ኢዘርኡ ሰብአ እምኢትዮጵያ ገራህቱ፤
የአርሩ እንበለ ጊዜሁ አስይፍት መገብቱ፤›ን የመሰለ ነው፡፡
፩. የቅኔው ትርጕም፤
ገበሬ/እግርሽ በዝናብ/በቀል (ቂም ጠብ) መውረድ
የጣቶችን ደም ሊዘራ ወጣ
ለግብፅ እሾኾችም መጠጊያ እግርሽ አላቸው፤ ረኃብና ድካም በኾድሽ በረሀ መመለስ/በዓልን አድርገዋልና፡፡
ከሚጮኹት ደንጋዮች ድምፅ የተነሣ የደጃፍ/እግር መድረክ ከፍ ከፍ ማለት ዠመረ፤
በፊትሽ ምስሓል (የመቅደሱ መለመኛ) ዐይናቸው ብዙ የኾነ የመልክእ መለዋወጥ/ ኪሩቤል በመፈራራቅ
ይገርዳሉ፤ የመብል/ባርያ ብዛትን ያላስከተልሽ ድንግል፤
እግዚአብሔር ካንቺ ጋራ እያለ የፊት እንባን አያርቅምና፡፡
9
፪. ቅኔው መፈጠሪያ (ምንጭ)፤
መጽሐፋዊና ተሰዶተ ድንግል ነው ፡፡
‹‹ናሁ ወጽአ ዘራዒ ከመይዝራዕ ወእንዘ ይዘርዕ ቦ ዘወድቀ ውስተ ፍኖት … ወቦ ዘወድቀ ውስተ ሦክ››
(ማቴ. ፲፫÷፫-፰) ፡፡
‹‹ወኮኑ ኪሩቤል ይረብቡ ክነፊሆሙ እመልዕልት እንዘ ይጼልሉ ክነፊሆሙ መልዕልተ ተድባብ ወገጾሙ
ይትናጸር በበይናቲሆሙ በዲበ ተድባብ›› (ዘፀ. ፴፯÷፰)፡፡
‹‹እግዚአብሔር አምላከ እስራኤል ዘትነብር ዲበ ኪሩቤል›› (ኢሳ. ፴፯÷፲፯) ፡፡
፮. ርእይ
10
፪.፫ መወድስ ቅኔ ዘአለቃ ለማ ኃይሉ- ትዕግሥተ ንባቡ
ትዕግሥተ ንባቡ ለኢዮብ እምኀበ ኢሰምዐ
ባሕታዌ ልደት ኤልያስ ለሀገረ ልማድ ዘየኀይሣ፤
ዕራቆ ኢወጽአ ለወላዲቱ እምከርሣ፤
ወለእንተ ዝናም ይውኅዛ
ጠፈረ ሰማይ በቃሉ ፈወሳ፤
አምጣነ አልቦ እንተያርኁ
ወዘየዐፁ ሰማየ ዘእንበሌሁ ጊዜኀሠሣ፤
ለዓለም
አንስትሂ ዘሰማርያ ለእምረኀበ ፀንሣ፥
ለልደተ ቅብዕ ኢያስተብቊዓ ዘፈረ ከመይግሥሣ፤
ወለሠገራት ዘወጽኡ ለኀሢሠ በቀል አንበሳ፤
ኀበ ማዕዱ ነደ እሳት አርፈቆሙ በበኀምሳ፤ (መንግሥቱ ለማ፤ 2003፤229/30)፡፡
፩. የቅኔው ትርጕም፤
የኢዮብን ትዕግሥት ነገር ካልሰማ ዘንድ
ልማድ አገርን የሚነቅፍ የልደት ብቸኛ (በልደቱ ልዩ የኾነ) ኤልያስ
ከናቱ ኾድ ራቁቱን አልወጣም፤ ዝናም የሚፈሳት ሰማይንም በቃሉ አዳናት፤
ያለሱ በቀር በፈለገ ጊዜ ሰማይን የሚዘጋና የሚከፍት የለምና፤
የሰማርያ ሴቶች ረኃብ ቢፀንሱ ቅቤ ዘይትን ለመውለድ የልብሱን ዘርፍ ሲዳስሱ አልለመኑትም፤
ቂም በቀል አንበሳን ለመፈለግ የመጡ ወታደሮችን ኸማዕዱ ነደ እሳት ዐምሳ ዐምሳ አድርጎ አስቀመጣቸው፡፡
11
፬. የቅኔው መንገድ፤
ሀ. አንጻር፤ ነቃፊ ጥቅስ፡- ትዕግሥተ ንባቡ ለኢዮብ
ለ. ሠምና ወርቅ፡- ባሕታዊ ኤልያስ
ሐ. ወርቅ ረገፍ፡- ሠም ረገፍ፤
፮. ርእይ
ሀ. ከዚኽ ቅኔ አንዱን ካንዱ አሰናስሎ መቀኘት የሊቅነት ሞያ እንደኾነ መረዳት ችለናል፡፡
ለ. ከሞያ አንጻር = ለወላዲቱ እምከርሳ = ለ ና እም ወለሠገራት
ሐ. ከዜማ ልክ አንጻር = ዘፈረ ከመ ይግሥሣ
መ. ከግጥም (ከስንኝ) አንጻር = አንበሳ ፈወሳ እምከርሣ፤ ኀሠሣ፤ ቤቱ መፋለሱን ያሳያል፡፡
12
፩. የቅኔው ትርጕም፤
ለከብቱ አካል ያዝናል ይራራል ደግ ሰው፡፡
ይኽንን ሕግ ግን ያዕቆብ ቸል አለው፡፡
የበግ ደም በግፍ የዮሴፍን ልብስ በለወጠው (ቀለም ባገባው) ጊዜ
የተበደለ በግን ትቶ ያዕቆብ ለልጁ አልቅሷልና
ንጹሕ አርዌን ያለበደል ያማዋል ክፋቱን እየነገረ፡፡
አብ ግን የበግን መበደል የያዕቆብን መበደል ዐይቶ፤
የበግ ቤዛ (ዋጋ ለውጥ) ሲያደርገው ለልጁ አላዘነም አልራራም፡፡
ጠላት ‹እንደ ያዕቆብ እንጂ ልጁን ባያየው ነው! › እንዳይል፤
ቅድመ ዓለም ድኅረ ዓለም አልተለየውም፡፡
፪. የቅኔው መፈጠሪያ፤
መጽሐፋዊ አባባል ነው፤
‹‹ወነሥኡ ክዳኖ ዘዐስቅ ወሐረዱ ላዕሌሁ ማሕስዐ ጠሊ ወመልእዎ ደመ ለክዳኑ›› (ዘፍ. ፴፯÷፴፩)፡፡
‹‹ይሜጡ ነፍሶ ቤዛ አባግዒሁ›› (ዮሐ. ፲÷፲፩-፲፮)
‹‹ወልዶ ጥቀ ኢምህከ እምኔነ አላ መጠወ በእንተ ኵልነ›› (ሮሜ. ፲÷፴፪)፡፡
፮. ርእይ
13
፪.፭. አሠረ ንጉሥ ዘአለቃ ለማ - ምኒልክ ግበር
ምኒልክ ግበር ላዕለሮምያ መጠነ እዴከ ትክል፤
አምጣነ ለአጺድ በጽሐ ማእረራ ወመዋዕሊሃ ለኀጉል፤
ዓዲ ተዘከር ወስተ ወንጌል፤
ላዕለሮምያ በለስ ኢሀሎ አስካል፤
ከመይቤ ወልደ ያሬድ ቃል፡፡ (መንግሥቱ ለማ፤ 2003፤141/215/16)፡፡
፩. የቅኔው ትርጕም፤
ምኒልክ በሮምያ ላይ እጅኽ እንደ ቻለ መጠን አድርግ፤
መከሯ ለመታጨድ፡ ቀኗም ለጥፋት ቀርቧልና፡፡
ዳግመኛ በወንጌል ያለውን ዐስብ፤ በሮምያ/በለስ ላይ ፍሬ የለም እንዳለ ወልደ ያሬድ/ቃል (ወልድ)፡፡
- ‹‹ኅድግዎ ይልሀቁ ኅቡረ እስከ ጊዜ ማእረር ወሶበ ፈጸመ ፈርዮተ ሶቤሃ ይፌኑ ማዕጸደ›› (ማቴ.
፲፫÷፴ ፤ማር. ፬÷፳፱ ፤ ዮሐ. ፬÷፳፭)፡፡
14
፮. ተጨማሪ
ሀ. የቅኔው የዜማ ስልት ዕዝል
ስሙ የዕዝል ዕጣነ ሞገር አሠረ ንጉሥ/ ነጋሢ
ለ. የቤት መምቻው ፤ ል፤ የቤቱ ቊጥር = ፭ ቤት ነው፤
ሐ. ድምፀት = ምጽአተ ጣሊያን ወኅልቀታ/ ይኽም የባለ ቅኔውን መንፈሳዊነት ያሳያል፡፡
፯. ርእይ
15
ማጠቃለያ
በመጽሐፈ ትዝታ ዘአለቃ ለማ ወልደ ታሪክ በሚለው ጽሑፍ ውስጥ በቊጥር ዐሥር ከኾኑ ቅኔዎች
በመነሣት የእያንዳንዱን ቅኔ መነገሪያ (መፈጠሪያ)፤ ዐውድ (መቼት)፤ ቅኔው የቀረበበት መንገድና ዐቢይ
መልእክት ምን እንደኾነ መመርመርና መረዳት እንድንችል አድርጎናል፤ በዚያ ዘመን የአለቃ ለማ የቅኔ
ብስለትንም ካኹኑ ዘመን ቅኔና የቅኔ መምህራን ጋራ ሲነጻጸር የሰማይና የምድር ርቀት ያኽል እንደኾነ
ተመልክተናል፤ ዐቅማችንንም ዐውቀንበታል፡፡
ይኽም ማለት ምንም እንኳን የሊቃውንቱን ቅኔ ሙሉ በሙሉ መተርጐምና ማመስጠር፤ ሞያዊ
ኺደቱንም ጭምር እንደዚኽ ነው፤ ይኽንንም ይመስላል፤ ባይባልም መገመት ግን እንደሚቻል
ተረድተንበታል ለማለት ነው፡፡ ምክንያቱም ቅኔ በኹኔታው /በጠባይዑ ያለ ደራሲው/ ያለ ባለቤቱ/
በደንብ አይተረጐምም፤ አመስጥሮም የለውም፡፡
ለዚኽም ነው ‹‹እሳት ያለ ባለቤቱ አይነድም›› እንደሚባለው በየጊዜው የተነሡ የቅኔ መምህራን ኹሉ
የቅኔያቸውን አመስጥሮ ቀርቶ ተራ የቅኔያቸውን ትርጕም ‹ይኽን ብትፈታ አንገቴን ለስለት እሰጣለኹ! ›
የሚሉት፡፡
ስለኾነም በመምህራችን ዶ/ር ዘለዓለም መሠረት ትምህርታዊ ትእዛዝ ምክንያት የተሰጠንን የቤት ሥራ
በመጽሐፈ ትዝታ ውስጥ ከቅኔው ትርጕምና የምስጢር ፍንጭ በመነሣት /በመታገዝ/ መሥራት ስላስቻለን
ቸሩ መድኀኔዓለም የተመሰገነ ይኹን፡፡
16
ስምዐት/ወሃቢ/ዋቢ/
፩. መምህር ሔኖክ ወልደሚካኤል፤ ንግድ ማተሚያ ድርጅት፤፲፱፻፺፩ ዓ.ም ፡፡
፪. መጽሐፈ ዚቅ ወመዝሙር፤ ትንሣኤ ማሳተሚያ ድርጅት፤፲፱፻፹፮ ዓ.ም ፡፡
፫. መንግሥቱ ለማ፤ መጽሐፈ ትዝታ ዘአለቃ ለማ ኃይሉ ወልደ ታሪክ፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬስ፤
፪ሺሕ፫ ዓ.ም፡፡
፬. መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ፤መጽሐፈ ቅኔ /ዝክረ ሊቃውንት/፤ ትንሣኤ ማሳተሚያ ድርጅት
፳፻፲ወ፪ ዓ.ም፡፡
፭. ምዕራፍ ዘቅዱስ ያሬድ፤ ትንሣኤ ማሳተሚያ ድርጅት፤፲፱፻፹፯ ዓ.ም፡፡
፮. ቡሩክ ጌታቸው (መጋቤ ምስጢር)፤ ጾመድጓ ዘቅዱስ ያሬድ ፳፻፲፭ ዓ.ም፡፡
፯. ብሉይ ኪዳን ስምንቱ ብሔረ ኦሪት፤ ትንሣኤ ማሳተሚያ ድርጅት ፲፱፻፺፬ ዓ.ም ፡፡
፰. ትንቢተ ኢሳያስ ፤ ትንሣኤ ማሳተሚያ ድርጅት ፳፻ወ፩ ዓ.ም ፡፡
፱. አርባዕቱ መጻሕፍተ ብሉያት፤ ትንሣኤ ማሳተሚያ ድርጅት ፲፱፻፺፰ ዓ.ም ፡፡
፲. ወንጌል ቅዱስ ዘእግዚእነ ወመድኀኒነ ኢየሱስ ካርስቶስ፤ተስፋ ገብረ ሥላሴ ፲፱፻፹፰ ዓ.ም፡፡
፲፩. ዝማሬ መዋሥዕት፤ ትንሣኤ ማሳተሚያ ድርጅት ፲፱፻፹ ዓ.ም፡፡
፲፪. የቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት ንባቡና ትርጓሜው ትንሣኤ ዘጉባኤ ማሳተሚያ ፲፱፻፹፰ ዓ.ም፡፡
17