Professional Documents
Culture Documents
Gädlä Bestawros ( )
Gädlä Bestawros ( )
፳፻፲፭ ዓ.ም፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፤ ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ፡፡
Gädlä Bestawros (ገድለ ብስጣውሮስ)
መክሥተ አርእስት
መክሥተ አርእስት...................................................................................................................................... 1
፩) መግቢያ (Introduction) ..................................................................................................................... 2
፩.፩) የመጣጥፉ አጠቃላይ ዳራ (Overview) .......................................................................................... 2
፩.፩.፩) የመጣጥፉ አዘጋጅ ማንነት (የመጣጥፉ ጸሓፊ ማን ነው?) .......................................................... 2
፩.፩.፪) መጣጥፉ መቼና የት ተዘጋጀ? (ጊዜውና ቦታው) ፡- ................................................................ 3
፩.፩.፬) መጣጥፉ የተጻፈበት ምክንያት፡- .............................................................................................. 3
፩.፩.፭) የመጣጥፉ ዓላማ፡- ................................................................................................................. 3
፪) ዋና ሐሳብ (Main Body) ................................................................................................................ 5
፪.፩) የመጣጥፉ ይዘት: - .................................................................................................................... 5
፪.፩.፩) አጠቃላይ ይዘት፤ ................................................................................................................... 5
፪.፪) የመጣጥፉ ጠቀሜታ: - ............................................................................................................. 10
፫ ማጠቃለያ፡-..................................................................................................................................... 10
ስምዐት (ዋቢ መጻሕፍት) ..................................................................................................................... 10
ገጽ| 1
Gädlä Bestawros (ገድለ ብስጣውሮስ)
፩) መግቢያ (Introduction)
በዐዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጥንታውያን ጽሑፋት ጥናት (ፊሎሎጂ) ረዳት ፕሮፌሰር ኹነው በማስተማርና
በምርምር ላይ የሚገኙት ቀሲስ አምሳሉ ተፈራ የቤ/ክን ልጅ ናቸው፤ በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ
ምሩቅና መምህር ኹነውም አገልግለዋል፤፣ በትምህርት በቆዩባቸው በጣልያንና በጀርመን፣ እንዲኹም
መጽሐፋቸው ነው፤
1 ይኽን Article የሚዳስሰው ተማሪ ‹መጣጥፍ› ሲል ‹Article› የሚለውን አቻ ቃል ተጠቅሞ እንደኾነ ልብ ይሏል፡፡
ስለዚኽ ‹Article Review - የመጣጥፍ ዳሰሳ› ተብሎ ሊወሰድ ይችላል፡፡
ገጽ| 2
Gädlä Bestawros (ገድለ ብስጣውሮስ)
የመጣጥፉ ዋና ዓላማ በተገኘው የግእዝ ገድል ብራና መጽሐፍ ቅጂ Philological and textual
analysis መሥራት ነው፤ አክሎም በተጨማሪ ማብራሪያ (Annotation) በማጠንከር በእንግሊዝኛ
ቋንቋ ተርጕሞ ማሳየት ነው፤ አዘገጃጀቱም የተማረውንና ተመራማሪውን ማኅበረሰብእ ታሳቢ ያደረገ
ይመስላል፡፡
2 The article is excerpted from my MA thesis, Philological and textual analysis of Gadla Bostawros
Abbot of Dabra Hayq, submitted to the School of Graduate Studies, Addis Ababa University 2006.
The researcher would like to thank Prof. Paolo Marrassini, who spent much time and effort
offering constructive comments, invaluable insights and suggestions while I was writing the thesis.
Moreover, he facilitated the publishing of this paper and dedicated many hours to editing not
only the content but also the language. Thanks also to Dr. Gideon P.E. Cohen and Dr. Alessandro
Gori for their careful editing of this paper.
ገጽ| 3
Gädlä Bestawros (ገድለ ብስጣውሮስ)
በተለይ ዶ/ር አምሳሉ የተጠቀሙት ብራናዎች ተአማኒነት ያላቸውና ቅቡልነታቸው የሰፉትን ነው፡፡
በካልኣይ ምንጭነት ደግሞ አስፈላጊ ግብአት እንዲኾን በዛ ያሉ የተለያዩ ከቅዱስ ብስጣውሮስ ታሪክ
ጋራ ተያያዥነት ያላቸውን ከአርባ ዐምስት በላይ መጻሕፍትና ጥናታዊ የምርምር ሥራዎችን እንዲኹም
ጆርናሎችን በመመልከት ለጥናታዊ ሥራቸውና ለመጣጥፉ በግብአትነት አገልግለዋል፡፡
መጣጥፉ ጠብሰቅ ባለ በ103 የግርጌ ማስታወሻ ተጨማሪ ማብራሪያ ሐሳቦችና ትንተናዎች የበለጸገ
የጥናትና ምርምር ዘዴን የተከተለ ሥራ ነው፡፡
እንደመግቢያ እነዚኽን አርእስተ ሐሳቦች በመጣጥፉ ላይ ከተነሣ ቀጣይ ደግሞ የመጣጥፉን ዋና ይዘትና
እንዲኹም ጠቀሜታውን በዐጭሩ ለመቃኘት ይሞከራል፡፡
ገጽ| 4
Gädlä Bestawros (ገድለ ብስጣውሮስ)
አቡነ ብስጣውሮስ ዘሐይቅ ሙሉ ስማቸው ዐቃቤ ሰዓት አቡነ ብስጣውሮስ ተብለው የሚጠሩ ሲኾን
የትውልድ አገራቸው መቅደላ ነው፡፡ አባታቸው ፍተ ድንግል እናታቸው ጽዮን ሞገሳ የሚባሉ ደጋግ
ቅዱሳን ናቸው፡፡ አቡነ ብስጣውሮስ በ17ኛው መ/ክ/ዘ የነበሩ ታላቅ ጻድቅ ሲኾኑ የታላቁና የጥንታዊው
ትምህርት ቤትና የሥርዐተ ገዳም ተቋም የደብረ ሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ አቡነ ኢየሱስ ሞአ ገዳም
አበምኔት ነበሩ፡፡ በልጅነታቸው ትምህርት ቤት ገብተው የሐዋርያትን ሥርዐትና የቅዱሳት መጻሕፍትን
ትርጓሜ በሚገባ ተምረዋል፡፡
አንድ ቀን አንዱ የደብረ ሐይቅ መነኲሴ የገዳሙን ምርት ገበያ ለመሸጥ ይዘው እንደኼዱ አንድ ቀማኛ
ወንበዴ አግኝቶ ሊቀማቸው ሲል አቡነ ብስጣውሮስ ደርሰው አዳኑት፡፡ መነኵሴውንም ወደ ቤታቸው
ወስደው በመልካም መስተንግዶ አሳደሯቸው፡፡ መነኵሴውም በዚያች ሌሊት ስለ አቡነ ብስጣውሮስ
ብዙ ነገር ከተመለከቱ በኋላ አቡነ ብስጣውሮስን ስለ ምንኵስና አስተማሯቸው፡፡ መነኵሴው በማግስቱ
ሲኼዱ ወደ ሐይቅ አቡነ ኢየሱስ ሞአ ገዳም መጥተው እንዲጎበኟቸውና እንዲባረኩ ነግረዋቸው ኼዱ፡፡
አቡነ ብስጣውሮስም እግዚአብሔር መንገዳቸውን ይመራቸው ዘንድ ብዙ ከጸለዩ በኋላ ወደ ሐይቅ ገዳም
ገቡ፡፡
ገጽ| 5
Gädlä Bestawros (ገድለ ብስጣውሮስ)
በገበያ ያገኘውና በቤቱ ያሳደረውም መነኵሴ ሲያያቸው ደስ ተሰኝቶ የገዳሙ አበምኔት ዐቃቤ ሰዓት አባ
ዘወልደ ክርስቶስ ዘንድ ወሰዳቸው፡፡ አበምኔቱም አቡነ ብስጣውሮስን ገና እንዳዩአቸው ጸጋ
እግዚአብሔር እንዳደረባቸው ተመልክተው በጣም ደስ ተሰኙ፡፡ አቡነ ብስጣውሮስም መመንኰስ
እንደሚፈልጉ ለአበምኔቱ ሲነግሯቸው አበምኔቱ "የምንኵስና ሥራ ቀላል አይምሰልህ፤ ብዙዎች ወደ
እኛ መጡ ነገር ግን መታገስ ተስኗቸዋል፡፡" በማለት የምንኵስና ሕይወት ከባድ ፈተና እንዳለበት
ነገሯቸው፡፡ የእግዚአብሔር ሰው ብስጣውሮስም "በልዩ ልዩ ዐይነት ፈተናዎች ፈትኑኝና ሥራዬን ካዩ
በኋላ ያመነኵሱኛል" አሏቸው፡፡ ከዚኽም በኋላ አቡነ ብስጣውሮስ በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት
እየተጋደሉ ገዳሙን በጉልበት ሥራ ብዙ ካገለገሉ በኋላ ከገዳሙ አበምኔት ከዐቃቤ ሰዓት አባ ዘወልደ
ክርስቶስ እጅ ምንኵስናን ተቀበሉ፡፡ ተጋድሎአቸውንም ከበፊቱ ይበልጥ በማብዛት መኖር ጀመሩ፡፡
ገጽ| 6
Gädlä Bestawros (ገድለ ብስጣውሮስ)
አቡነ ብስጣውሮስ በእንዲኽ ዐይነት ተጋድሎ ገዳሙንና አገራችንን እየጠበቁ ሲኖሩ በመኻል የቅብዐት
እምነት ነገር በገዳሙ ተነሣ፡፡ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችንን አምላካችንን ኢየሱስ ክርስቶስን
"ከትስብእት ጋራ ከተዋሐደ በኋላ መንፈስ ቅዱስ ተቀባ፣ በዚኽም ቅብዐት በጸጋ ልጅ፣ ንጉሥም፣
ነቢይም፣ ሊቀ ካህናትም ተባለ" የሚሉ ከሓድያን ተነሡና የእግዚአብሔር ሰው ብፁዕ አባታችን
ብስጣውሮስ ይኽንን የክሕደት ትምህርት ሰምተው እጅግ እያዘኑና እያለቀሱ የካዱትን ሰዎች በብዙ
ምሳሌ እያደረጉ ማስተማር ዠመሩ፡፡ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈስ ቅዱስ ቅብዐት በጸጋ ልጅ
እንዳልኾነ፣ ነገር ግን በባሕርይው የአብ ልጅ እንደኾነ፣ እርሱ ራሱ ቅብ፣ እርሱም ራሱ ቀቢ፣ እርሱ
ራሱ ተቀቢ እንደኾነ በብዙ ምሳሌ እያደረጉ የቀደሙ የአባቶቻችንንም ትምህርት ኹሉ እየጠቀሱ
አስተማሯቸው፡፡ ነገር ግን ሰይጣን አንድጊዜ አስክዷቸዋልና አንዳንዶቹ እምቢ አሏቸው፡፡ በዚኽም
ጊዜ ሐዋርያት ከመሠረቷት አንዲት ቤተ ክርስቲያን አውግዘው ለዩአቸው፤ ቤተ ክርስቲያንም ሰላም
ኾነች፡፡ በዚኽም አባታችን ከሓድያንን የሚዘልፉ ዳግማዊ ቄርሎስ ተባሉ፡፡ ይኽም ክሕደት መዠመሪያ
ሰይጣን ለጳውሎስ ሳምሳጢን ያስተማረው ነው፡፡ ጳውሎስ ሳምሳጢን በገዳም ቅጠል እየበላ የሚኖር
ተሐራሚ መናኝ ነበር፡፡ በጾም በጸሎት ሲኖር ሰይጣን ራሱን ሰውሮ መጥቶ ተገለጠለትና "ጸሎትኽ
በእግዚአብሔር ዘንድ ተሰምቶልሃል፤ ነገር ግን አምላክ ያለሩካቤ በድንግልና የተወለደ አይምሰልኽ
በሩካቤ ተወለደ እንጂ፤ ይኽም ልጅ ደግ ሰው ኾነ፣ በ30 ዘመኑ በዮሐንስ እጅ በዮርዳኖስ ተጠመቀ፣
ገጽ| 7
Gädlä Bestawros (ገድለ ብስጣውሮስ)
መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል በራሱ ላይ ተቀመጠ፣ ያን ጊዜም ይኽ ሰው በጸጋ የሥላሴ ልጅ ኾነ"
ብሎ አስተማረው፡፡ ጳውሎስ ሳምሰጢንም ሰይጣን የነገረውን ነገር በልቡ አምኖ ለደቀ መዝሙሩ
ለተያስሮስ አስተማረው፡፡ ተያስሮስም ለድያድርስ አስተማረው፡፡ ድያድርስም ለንስጥሮስ
አስተማረው፡፡ ንስጥሮስም ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችንን አምላካችንን "መንፈስ
ቅዱስ ያደረበት ዕሩቅ ብእሲ ነው" ብሎ ለልዮንና ለመርቅያን አስተማራቸው፡፡
ንስጥሮስ ይኽን ዐዲስ የክሕደት ትምህርት እንዳመጣ በሰሙ ጊዜ 200 ኤጲስ ቆጶሳት በቅዱስ ቄርሎስ
ዘእስክንድርያ መሪነት በኤፌሶን ተሰብስበው ሲያስተማሩት እምቢ ቢላቸው አውግዘው ለዩት፡፡
ንስጥሮስም ሰውነቱ መግሎ ክፉ አሟሟት ሞተ፡፡ በኋላም መርቅያን ሲነግሥና ልዮንም የሮም ሊቀ
ጳጳስ ሲኾን ኹለቱም አባታቸው ንስጥሮስ ያስተማራቸውን ሃይማኖት ማስፋፋት ቻሉ፡፡ እነ ልዮንም
ንስጥሮስ በተወገዘበት ጉባኤ ላይ የነበሩትና አኹን ለሥጋቸው የፈሩ አባቶችን ይዘው ከንስጥሮስ ክሕደትና
ከቅዱስ ቄርሎስ ትምህርት አወጣጥተው የራሳቸውን የረከሰ ሃይማኖታዊ ድንጋጌ አወጡ፡፡ "ክርስቶስ
ኹለት አካል ነው፣ አንዱ የማርያም ልጅ አንዱ የእግዚአብሔር ልጅ በመቀራረብ አንድ ኾኑ ያለውን
አውጥተው ከቅዱስ ቄርሎስም ቃልና ከንስጥሮስ ክሕደት ቀላቅለው መለኮት የመለኮትን ሥራ ይሠራል፣
ትስብእትም የትስብእትን ሥራ ይሠራል፤ በኹለት መንገድ አንዱ ተኣምራትን ያደርጋል ኹለተኛው
መከራን ይቀበላል፤ ስለዚኽም ትስብእት ከመለኮት ያንሳል" ብለው ጻፉ፡፡ ይኽንንም የክሕደት
ጽሕፈታቸውን ለቅዱስ ዲዮስቆሮስ ላኩለት፡፡ እርሱም ኺዶ ከክሕደታቸው እንዲመለሱ
አስተማራቸው፡፡ "በአንዱ ክርስቶስ ላይ ለምን የኹለትነት ነገር ትናገራላችኹ? ወደ ሰርግ ቤት ተጠርቶ
የኼደው ውሃውንም የወይን ጠጅ ያደረገው እርሱ አንዱ ክርስቶስ ነው…" እያለ በብዙ ምሳሌ
ካስተማራቸው በኋላ ልዮንንና መርቅያን የጻፉትን የክሕደት ጽሕፈት በፊታቸው ቀደደው፡፡ እነርሱ ግን
አንድ ጊዜ ክደዋልና የቅዱስ ዲዮስቆሮስን ፂሙን ነጭተው ጥርሱን አውልቀው ብዙ አሰቃዩት፡፡
እርሱም የነጩትን ፂሙንና ያወለቁትን ጥርሱን ሰብስቦ "እነሆ የሃይማኖቴን ፍሬ ተቀበሉ" ብሎ
ለእስክንድርያ ክርስቲያኖች ላከላቸው፡፡ ከሓድያኑም ወደ ጋግራ ደሴት አጋዙትና በዚያው ዐረፈ፡፡
ሰይጣን ለመዠመሪያ ጊዜ ለጳውሎስ ሳምሳጢን ያስተማራትን ያችን ክሕደት በእንደዚኽ ዐይነት ኹኔታ
ሰይጣን የሚያድርባቸው ሰዎች እየተቀባበሏት እስከ ንስጥሮስንና እስከ ልዮን ድረስ ከደረሰች በኋላ
የልዮን ልጅ በኾነው በአውፍንስ አማካኝነት በዐፄ ሱስንዮስ ዘመን ለመዠመሪያ ጊዜ ወደ አገራችን
ኢትዮጵያ ገባች፡፡ አውፍንስም ክሕደቱን ለኹለት የአገራችን መነኰሳት አስተማራቸው፡፡ ለአንደኛው
"ወልድ ሦስት ልደት አለው፣ በመዠመሪያ ከአብ ተወለደ፤ ዳግመኛም በመንፈስ ቅዱስ ሥጋ ከድንግል
ተወለደ፤ ሦስተኛም በቤተልሔም ተወለደ" ብሎ ካስተማረውና ካስካደው በኋላ ስሙን "ተክለ ሃይማኖት"
ገጽ| 8
Gädlä Bestawros (ገድለ ብስጣውሮስ)
አቡነ ብስጣውሮስም እነዚያን ከሓዲዎች አውግዘው ለዩአቸው፡፡ ከዚኽም በኋላ ከሓድያኑ አባታችንን
ከሰሷቸውና ከጐንደሩ ንጉሥ ጋራ አጣሏቸው፡፡ ንጉሡም የእነዚያን ከሓዲዎች እምነት አምኖ ተቀብሎ
ነበርና አባታችንን ወደ ጐንደር እንዲያመጧቸው ጭፍሮቹን ላከ፡፡ አቡነ ብስጣውሮስም ነገሩን ዐውቀው
ስለ ቀናች ሃይማኖት ይመሰክሩ ዘንድ አንደበት እንዲኾናቸው ጌታችንን በጸሎት ሲጠይቁ ጌታችንም
"ልጄ ብስጣውሮስ ሆይ አይዞኽ እኔ ከአንተ ጋራ ነኝ፣ እኔ ስለመሠረትኳት አንዲት ሃይማኖት ጽና"
አላቸው፡፡ አባታችንም ወደ ንጉሡ ዘንድ ኼዱና ንጉሡ ሰዎቹን ስለማውገዙ ጠየቃቸው፡፡ አባታችንም
ንጉሡን ስለ ቀናች ሃይማኖት እየመሰከሩለት አስተማሩት፡፡ ንጉሡም በብዙ ስጦታና ሽንገላ
ሊያታልላቸው ሞከረ ነገር ግን አባታችን አጥብቀው ተቃወሙት፡፡ ንጉሡም ዕውቀታቸውንና
ጽናታቸውን ባየ ጊዜ አባታችንን በእግር ብረት አሳስሮ እስር ቤት ውስጥ ጣላቸው፡፡ በዚኽም ጊዜ
የእግር ብረቱ እንደሰም ቀልጠ፡፡ ወታደሮቹም ይኽንን ተኣምር ዐይተው ፈርተው ኼደው ለንጉሡ
ነገሩት፡፡ ንጉሡም ሰምቶ ደነገጠ፤ እየፈራና እየተንቀጠቀጠ ወደ አባታችን መጥቶ ሰገደና "አባቴ ሆይ
ይቅር በሉኝ የሃይማኖትንም ነገር እንደገና አስተምሩኝ" አላቸው፡፡ እሳቸውም አስተምረው ባረኩት፡፡
በመከራቸውም ታግሰው ለልጆቻቸውና ለእኛም የሐዋርያትን ሃይማኖት አጸኑልን፡፡ እድሜአቸውም 90
ዓመት በኾነው ጊዜ ዕረፍታቸው እንደደረሰ ዐውቀው የቀናች ሃይማኖት በአገራችን ለዘለዓለም ጸንታ
ትኖር ዘንድ ጌታችንን አጥብቀው ለመኑት፡፡ ጌታችንም በደሙ የመሠረታት የቀናች ሃይማኖት
በአገራችን ጸንታ እንደምትኖርና ሌላም የምሕረት ቃል ኪዳን ከገባላቸው በኋላ ግንቦት 19 ቀን ዐረፉ፡፡
ይኽ የታሪካቸው መተታሰቢያም በስንክሳር ላይ ታስቧል፡፡
በዚያች ዕለትም ሐይቅ አለቀሰች፤ የሐይቅም ባሕር ሦስት ዓመት በኀይል ስትታወክ አቡነ አላኒቆስ ይኽ
ኹሉ የኾነው ስለ አባታችን ስለ ብስጣውሮስ ማረፍ መኾኑን ዐውቀው ወደ ንጉሡ ኼደው የአባታችንን
ዐፅም እንዲሰጣቸው ጠየቁት፡፡ ንጉሡ ግን "በረድኤታቸው ይጠብቁኛልና አልሰጥም" አላቸው፡፡
ንጉሡ ስለከለከላቸው አቡነ አላኒቆስም ቊስቋም ወደምትባል በወርቅና በከበረ ዕንቁ ወደተሸለመች ወደ
እመቤታችን ቤተ ክርስቲያን ኼደው በእመቤታችን ሥዕል ሥር ወድቀው አለቀሱ፡፡
ገጽ| 9
Gädlä Bestawros (ገድለ ብስጣውሮስ)
ሥዕሏም በሰው አንደበት አናግራ ካጽናናቻቸው በኋላ የአባታችን ዐፅም ከመሠዊያው በስተቀኝ በኩል
እንደሚገኝ ነገረቻቸው፡፡ አቡነ አላኒቆስም ዐፅማቸውን አፍልሰው ወደ ሐይቅ በተመለሱ ጊዜ የመዓዛው
ሽታ የንጉሡን አገር ኹሉ መላው፤ መቃብሩ በነበረበት ቦታም የብርሀን ዐምድ ተተክሎ ታየ፡፡ ንጉሡም
መነኵሴው የአባታችንን ዐፅም እንደወሰዱ ባወቀ ጊዜ መነኵሴውን ይዘው ከአባታችን ዐፅም ጋራ
ያመጡለት ዘንድ ብዙ ፈረሰኛ ወታደሮቹን ላካቸው፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር በጥበቡ ሰውሯቸዋልና
አቡነ አላኒቆስን ሊያገኟቸው አልቻሉም፡፡ አቡነ አላኒቆስም የቅዱስ አባታችንን ዐፅም ወስደው በሐይቅ
በመሠዊያው በስተቀኝ በኩል በቀበሩት ጊዜ በፊት ያስቸግር የነበረው የባሕሩ ኀይለኛ ንውጽውጽታ
በአንድ ጊዜ ጸጥ አለ፡፡ ሌላም ብዙ ተኣምራት ተደርገው ታዩ፡፡ ይኸውም ፍልሰተ ዐፅማቸው የካቲት
8 ቀን የተፈጸመ ነው፡፡
እንግዲኽ ከመጣጥፉ አንደምናነበው የገድላቸው ታሪክ ከብዙው በጥቂቱ ይኽን ይመስላል ይዘቱ፡፡
፫ ማጠቃለያ፡-
ገጽ| 10