Professional Documents
Culture Documents
መጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ለአብርሐም ሀ (1)
መጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ለአብርሐም ሀ (1)
ቅዱስ
ጥናት
( አምስተኛ ክፍል)
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
1
የሚሰጠው የትምህርት ርዕስ፦ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙ ከተሞችና ሀገሮች
ምዕራፍ ስድስት
1.1 ባሕሮች
በሀገረ እስራኤል ሁለት ታላላቅ ባሕሮች ይገኛሉ። አንደኛው የገሊላ ባሕር ሲሆን ሁለተኛው
ደግሞ ሙት ባሕር ነው።
የገሊላ ባሕር
ጌታችን ከደቀ መዛሙርቱ ጋር በዚህ ባሕር በታንኳ ሲጓዝ ተነሥቶ የነበረውን የማዕበል
ንውጽውጽታ ጸጥ አድርጎታል። ማቴ 8፥23 ለአምላክነቱ አልገዛም የሚል ፍጥረት የለምና።
ጌታችን በባሕሩ ላይ በእግሩ ተራምዷል። ማቴ 14፥22-23 ቅዱስ ጴጥሮስ ከጌታችን ታዝዞ
ለተጠየቁት ግብር የሚከፍሉትን ሁለት እስታቴር ያገኘበትን ዓሣ አጥምዶ ያወጣው በዚህ
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
2
ባሕር ነው። ማቴ 17፥24-27 በዚህ ባሕር አጠገብ ጌታችን ከትንሣኤ በኋላ ለሦስተኛ ጊዜ
ተገልጧል። ያጡትንም ዓሣ ሰጥቷቸዋል። አብሯቸውም ተመግቧል። ዮሐ 21፥1-14 ቅዱስ
ጴጥሮስ “ግልገሎቼን አሠማራ፣ ጠቦቶቼን ጠብቅ፣ በጎቼን አሠማራ” የተባለው በገሊላ ባሕር
አጠገብ ነው። ዮሐ 21፥15-17
ሙት ባሕር
ባሕረ ኤርትራ
እስያና አፍሪካን የሚለያይ ባሕር ነው። ርዝመቱ 2175 ኪ.ሜ ሲሆን ስፋቱ ደግሞ
370 ኪ.ሜ ነው። በአንዳንድ ቦታዎች የ1830 ሜትር ጥልቀት አለው። ወደ ባሕሩ የሚገባ
ምንም ዓይነት ወንዝ የለም። እስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት ነጻ ሲወጡ በዚህ ባህር ውኃው
እንደ ግንብ ቆሞ መሀሉ ደረቅ መሬት ሆኖ ተሻግረው ሀገራቸው ገብተዋል። ዘጸ 14፥15-31
1.2 ወንዞች
የዮርዳኖስ ወንዝ
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
3
ከአርሞንኤም ተራራ ግርጌ ተነሥቶ በገሊላ ባሕር በማለፍ ወደ ጨው ባሕር ይፈሳል።
የወንዙ ስፋትና ጥልቀት እንደ ዝናቡ መጠን ይለዋወጣል። ይኸውም ከአንድ ሜትር እስከ
ሦ ስት ሜትር ጥልቀትና እስከ ሠላሳ ሜትር ስፋት የሚደርስበት ወቅት ይኖራል። በዮርዳኖስ
ወንዝ በተለያዩ ጊዜያት ገቢረ ተአምራት ተፈጽመውበታል።
ግዮን
በኢትዮጲያ የሚገኝ ወንዝ ነው። የጣናን ሐይቅ ከሁለት ከፍሎ ይጓዛል። በተለያዩ የመጽሐፍ
ቅዱስ ክፍሎች የዓባይ ወንዝ ተብሎ ተጠቅሷል። ኢሳ 19፥7-8 ፣ 23፥3 በበረሃማው የግብጽ
ምድር የዓባይ ወንዝ የሚያልፍበት ቦታ ሁሉ ለምለም ነው። ሱዳንና ግብጽን አጠጥቶ ወደ
ሜዲትራንያን ባሕር ይገባል። ከመነሻው እስከ መድረሻው ያለው ርቀት 6470 ኪሎ ሜትር
ያህል ነው። የሙሴ ወላጆች ከፈርዖን ትእዛዝ የተነሣ ሙሴ እንዳይሞትባቸው ከዓባይ ወንዝ
ዳር ሸሽገውታል። ዘጸ 2፥1-10 ፈርዖን እስራኤልን አልለቅም ብሎ ልቡን ባጸናበት ወቅት
ከእግዚአብሔር በታዘዘው መሠረት በግብጽ ምድር ብቻ የዓባይ ውኃ ወደ ደምነት ተቀየረ።
ዘጸ 7፥20-21
ተግባር
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
4
የሚሰጠው የትምህርት ርዕስ፦ ተራሮች፣ ሜዳዎች፣ ምንጮች፣ ዋሻዎች
1.3 ተራሮች
1. ደብረ ሲና
ደብር ማለት ተራራ ማለት ነው። ደብረ ሲና ማለት የሲና ተራራ ማለት ነው። ኮሬብ
እየተባለም ይጠራል። ዘጸ 3፥1 ፣ ዘዳ 4፥9-10 የእግዚአብሔር ተራራም ይባላል። ዘጸ
3፥1 ፣ 1ኛ ነገ 19፥8 ከግብጽ በስተምሥራቅ ከእስራኤል ደግሞ በስተደቡብ ይገኛል።
እግዚአብሔር ለሊቀ ነቢያት ሙሴ ለመጀመሪያ ጊዜ የተገለጠለት በዚህ ተራራ ነው።
ዘጸ 3፥2-12 እግዚአብሔር በሙሴ በትር አማካኝነት ከዓለት ውኃ አፍልቆ ለሕዝበ
እስራኤል ያጠጣው በኮሬብ ተራራ አጠገብ ነው። ዘጸ 17፥5-7 እግዚአብሔር በዚህ
ተራራ ለሙሴ በደመና በነጎድጓድና በመብረቅ ተገልጦለታል። ዘጸ 19፥16-25
በሁለት የድንጋይ ጽላት የተጻፉት ዐሠርቱ ትእዛዛት ለሙሴ የተሰጡት በዚህ ተራራ
ነው። ዘጸ 34፥28 ለሁለተኛ ጊዜ ጽላቱን ለመቀበል ወደ ተራራው ወጥቶ አርባ ቀንና
አርባ ሌሊት በጾም ቆይቷል። ዘጸ 34፥28 በዚህ ሥፍራ ግሪኮች “ቤተ ክርስቲያን”
ሠርተዋል።
2. ሞሪያ
ከኢየሩሳሌም ከተማ በስተምሥራቅ ይገኛል። አብርሃም በስተርጅና ያገኘውን ልጁን
ሊሠዋበት የሄደበት ተራራ ነው። ዘፍ 22፥2 ጠቢቡ ሰሎሞንም በዚህ ተራራ
ቤተመውደሱን እንደሠራ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። 2ኛ ዜና 3፥1
3. ደብረ ታቦር
ከገሊላ ባሕር በስተደቡብ ምዕራብ አቅጣጫ 10 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከናዝሬት
ደግሞ በስተ ምሥራቅ ከዮርዳኖስ ወንዝ በስተምዕራብ የሚገኝ ተራራ ነው። ከባሕር
ጠለል በላይ 572 ሜትር ከፍታ አለው። የዛብሎንን፣ የይሳኮርንና የንፍታሌምን ርስት
ያዋስናል። እንግልጣሮች (እንግሊዘኛ ተናጋሪዎች) Transfiguration Mount
ይሉታል። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን እንደገለጠበት
ሲያጠይቁ ነው። ዐረቦች ደግሞ ጀበል ቶር (Djebol Tor=Mountain of the bull)
ይሉታል። በዚህ ተራራ ባርቅና ዲቦራ የእስራኤል ጠላት ሆኖ የተነሣውን ሲሣራን
ድል አድርገውበታል። መሳ 4፥4-24 በልምላሜ የተሞላ ተራራ መሆኑ ይነገርለታል።
በሐዲስ ኪዳን ስሙ አይጠቀስ እንጂ ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ረጅም
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
5
ተራራ የተባለው እርሱ ነው። ማቴ 17፥1-9 ፣ መዝ 88፥12 በዚህ ምክንያት ሊቀ
ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ “ቅዱስ ተራራ” ብሎታል። 2ኛ ጴጥ 1፥18 በደብረ ታቦር
ግሪኮችና ላቲኖች (ሮማውያን) በ1923 ዓ.ም እ.ኤ.ዕ “ቤተ ክርስቲያን” ሠርተዋል።
4. ደብረ ዘይት
የዘይት ታራራ ማለት ሲሆን በወይራ ዛፍ የተሸፈነ በመሆኑ የተሰጠው ስያሜ ነው።
800 ሜትር ያህል ከባሕር ጠለል በላይ ከፍታ አለው። ከኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ
በቅርብ የሚገኝ ቦታ ነው። ጌታችን ቀን ቀን ኢየሩሳሌም ከተማ ሲያስተምር ውሎ
ወደ ማታ በደብረ ዘይት ተራራ በኩል ወደ አልዓዛር ቤት ቢታንያ ለማደር ይሄድ
ነበር። ማር 11፥19 ፣ ማቴ 21፥17 ከተራራው ግርጌም ቤተ ፋጌና ቢታንያ የሚባሉ
መንደሮች ይገኛሉ። ከፍታ ያለው ተራራ በመሆኑ ከጫፉ ላይ ሆኖ ኢየሩሳሌምን፣
ኤዶምያስን፣ ሞዓብንና አሞንን ማየት ይቻላል። ጌታችን ማታ ማታ ያድርበት የነበረ
ሲሆን ጥንት መቃብረ ነቢያት እንደነበር ይነገራል። ጌታችን ስለነገረ ምጽአት
ያስተማረው በዚህ ተራራ ነው። ማቴ 24፥3 ፣ 25፥31-46 ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም
ጌታችን በደብረ ዘይት ዓለምን ሊያሳልፍ እንደሚመጣ ተስፋ ታደርጋለች። ዘካ 14፥
4 ጌታችን በሆሳዕና ዕለት በአህያ ሆኖ ወደ ኢየሩሳሌም የገባው ከዚህ ተራራ ተዳፋት
ተነሥቶ ነው። ማር 11፥1 ጌታችን የተያዘውም ከተራራው ግርጌ በምትገኘው
ጌቴሴማኒ ነው። ማቴ 26፥30-36 ጌታችን ወደዚህ ዓለም የመጣበትን የቤዛነት ሥራ
ከፈጸመ በኋላ ያረገው በዚህ ተራራ ነው። ሉቃ 24፥51-52 ፣ ሐዋ 1፥12 ዛሬ ግን
ቦታው በመሐመዳውያን እጅ ይገኛል። ጌታችን አቡነ ዘበሰማያትን (አባታችን ሆይ
የሚለውን ጸሎት) ያስተማረው በዚህ ሲሆን ዛሬ ግን በ35 ቋንቋዎች ጸሎቱ ተጽፎ
ይገኛል። ከእነዚህም ቋንቋዎች አንዱ ግእዝ ነው።
5. ደብረ ጽዮን
ጽዮን ማለት አምባ ማለት ነው። 770 ሜትር ከፍታ አለው። ከኢየሩሳሌም በስተደቡብ
ምሥራቅ ከቄድሮስ ወንዝ በስተምዕራብ ይገኛል። ቅዱስ ዳዊት በዚህ ተራራ ላይ
ከተማ መሥርቶ ነበር። ታቦተ እግዚአብሔርንም አምጥቶ በዚህ ስላስቀመጣት ጽዮን
እየተባለች መጠራት እንደጀመረች እንጠራለን። 2ኛ ሳሙ 5፥6-9 ፣ 6፥10-12 ጽዮን
የሚለው ቃል መላውን ኢየሩሳሌምን የሚያመለክትበት ጊዜ አለ። 2ኛ ነገ 19፥21 ፣
መዝ 47፥2 ፣ 68፥35
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
6
1.4 ምንጮች
የአጋር ምንጭ
የያዕቆብ ምንጭ
የቤተልሔም ምንጭ
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
7
ለጦር ሰጥተው ተዋግተው ያመጡለትን ውኃ አልጠጣም። ነፍሳቸውን ለሞት እንኳ ሰጥተው
ያመጡት በመሆኑ “ደማቸውን መጠጣት ይሆንብኛል” ሲል ያን የወደደውን ውኃ አፈሰሰው።
1ኛ ዜና 11፥15-19
1.5 ሜዳዎች
የአርማጌዶን ሜዳ
የሰናዖር ሜዳ
1.6 ሸለቆዎች
የሄኖም ሸለቆ
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
8
ጊዜ እንደ አባቱ እንደ ዳዊት በእግዚአብሔር መንገድ በመሔዱ በሄኖም የነበሩ የማምለኪያ
ዐጸዶችንና መሠዊያዎችን አጠፋቸው። 2ኛ ነገ 23፥10-14
የኢዮሳፍጥ ሸለቆ
ኢዮሳፍጥ ከ870 እስከ 845 ከክርስቶስ ልደት በፊት በይሁዳ የነገሠ አራተኛው ንጉሥ
ነው። እግዚአብሔር ጠላቶቹን ያሸንፍ ዘንድ ኃይል ስለሰጠውና ጠላቶቹንም ድል
ስላደረጋቸው፣ ምርኮአቸውንም ከወሰደ በኋላ በዚህ ሸለቆ ፈጣሪውንም ስላመሰገነበት
የኢዮሳፍጥ ሸለቆ ተባለ። የኢዮሳፍጥ ሸለቆ በኢየሩሌምና በደብረዘይት መከከል የቄድሮን
ወንዝ ይፈስበታል። በአሁኑ ጊዜ ብዙ የአይሁድና የእስላም መቃብር ይገኝበታል። ነቢዩ
ኢዩኤል በኢዮሳፍጥ ሸለቆ በሕዝብና በአሕዛብ ላይ እግዚአብሔር የሚፈርድባቸው መሆኑን
ተናግሯል። ኢዩ 3፥2-12 በኢየሩሳሌም ነግሠው የነበሩ ነገሥታት ሥጋ በዚሁ ሸለቆ የተቀበረ
መሆኑም በተለያዩ መጽሐፍት ተገልጧል።
የራፋይም ሸለቆ
1.7 ዋሻዎች
ዋሻ ማለት በተፈጥሮም ሆነ በሰው ኃይል የተቦረቦረ፣ የተፈለፈለ መሬት ቋጥኝ ነው። ብዙውን
ጊዜ ዋሻ መናንያን ገብተው ይጸልዩበታል። ስደተኞች ይጠጉበታል። አራዊትም
ይኖሩበታል። በመጽሐፍ ቅዱስም የተለያዩ ዋሻዎች ተመዝግበዋል።
የኤልያስ ዋሻ
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
9
የሴዴቅያስ ዋሻ
ተግባር
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
10
የሚሰጠው የትምህርት ርዕስ፦ የሕብረተሰብ ክፍሎች በመጽሐፍ ቅዱስ
ምዕራፍ ሰባት
2.1 በነገዳቸው
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
11
አሞናውያን፦ ሎጥ ከወለዳቸው ልጆች መካከል አንዱ ከታናሺቱ ልጁ የወለደው አሞን
ይባላል። በአሞንም ልጆቹ አሞናውያን ተብለው ተጠሩ። ዘፍ 19፥38 ይኽኛው አሞን የይሁዳ
ንጉሥ ከነበረው ከምናሴ ልጅ ከንጉሡ አሞን ይለያል።
ከዮርዳኖስ ወንዝ ሸለቆ በስተምሥራቅ በያቦቅና አርኖን ወንዞች መካከል የሚገኝ ቦታ አሞን
ተብሎ ይጠራል። ይህም የዛሬው የዮርዳኖስ ዋና ከተማ አማን ያለችበት ዙሪያ ነው። አማን
የሚለው ስምም አሞን ከሚለው የተወሰደ ይመስላል። እደሞዓባውያን ሁሉ እስራኤልን
አናሳልፍም በማለታቸው እስከ ዐሥር ትውልድ ድረስ እግዚአብሔር ረግሟቸዋል። መሳ 11፥
12-28 መስፍኑ ዮፍታሔም በእርሱ ዘመን አናሳልፍም በማለታቸው ተዋግቶ ድል
ነሥቷቸዋል። መሳ 11፥29-33 “ሞሎክ” ወይም “ሚልካ” እየተባለ የሚጠራ ጣዖት ያመልኩ
ነበር። 1ኛ ነገ 11፥7-33 ንጉሥ ሰሎሞን እንደ ካሞሽ ሁሉ ለዚህኛውም ጣዖት ሰግዷል።
እግዚአብሔር ግን ቀጥቶታል። ለዚህ ጣዖታቸው መስዋዕት እያሉ የሰው ልጆችን ያቃጥሉ
ነበር። ዘሌ 18፥21
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
12
ኤዶም ከሙት ባሕር በስተደቡብ ምሥራቅ፣ በምዕራብ በኩል ደግሞ ዓረብን አዋሳኙ ያደረገ
ቦታ ነው። ይህ አካባቢ የዛሬዋ ደቡባዊ የዮርዳኖስ ግዛትን ያመለክታል። ኤዶማውያን
እስራኤል ከግብጽ በወጡ ጊዜ በእነርሱ በኩል እንዲያልፉ አልፈቀዱላቸውም። ዘኁ 2፥14-
21 ቅዱስ ዳዊት ኤዶማውያንን አስገብሯቸዋል። 2ኛ ሳሙ8፥13-14 ሰሎሞን ከጣዖት
አምላኪዎች ከፈርዖን ልጅ፣ ከሞዓባውያን፣ ከአሞናውያን፣ ከኤዶማውያንና ከኬጤያውያን
ሴቶች ጋር በዝሙት በወደቀ ጊዜ የአባቱን ድል በኤዶምያስ ንጉሥ በሃዳድ ተነጠቀ። 1ኛ
ነገ 11፥1-2
2.2 በሥራቸው
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
13
ቀራጮች፦ የቄሣር መንግሥት በሀገረ እስራኤል ግብር እንዲሰበስቡ ዘንድ የሾማቸው ሰዎች
ቀራጮች ይባላሉ። እንደ ባንዳ በእስራኤላውያን ዘንድ በጣም የተጠሉ ነበሩ። በዚህም እንደ
ኃጢያተኛ ይቆጠሩ ነበር። ሉቃ 18፥17 ጌታችን ግን ምንም እንኳ በኅብረተሰቡ ዘንድ
የተጠሉ በሆኑም አብሯቸው ተመግቧል። ማቴ 9፥11 ከእነዚህ ወገን የሆነውን ወንጌላዊው
ማቴዎስንም ይከተለው ዘንድ ጠርቶታል።
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
14
በጌታችን መዋዕለ ስብከት 6000 የሚያህሉ ፈሪሳውያን እንደነበሩ ይነገራል። እነርሱም
በየሙክራቦቹ መሪዎች የነበሩ ሲሆኑ ሀብታሞችም ናቸው። ፈሪሳውያን ባዕለ ጸጋ እስከ መሆን
የደረሱት ሕዝቡን በመበዝበዝ ሲሆን ጌታችን ማቴ 23፥23-24 ጌታችን መድኃኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲሰቀል ምክንያት እየፈለጉ ይከሱት ነበር። በመጨረሻም ጲላጦስ “ምን
ላድርግላችሁ?” ብሎ ሲጠይቅ “ስቀለው ስቀለው” እያሉ ጮኸዋል።
በዘመነ ብሉይ እንደ ካህኑ ዕዝራ ያለ ንጹሕ ሰው ከእነርሱ መካከል ተገኝቷል። ዕዝ 7፥6
በመጀመሪያ ከካህናት መካከል ነበሩ በኋላ ግን ለብቻቸው በመሆን ቡድን መሠረቱ።
በደንባቸው መሠረት ለዕለት ኑሯቸው የእጅ ሥራ በመሥራት ሕግን ደግሞ በነፃ ያስተምሩ
ነበር። በጌታችን ዘመን ግን ከፈሪሳውያን ጋር ሕዝቡን ወደ መበዝበዝ አምርተዋል።
የጸሐፊዎች ሥራ በሦስት ዓይነት ነው።
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
15
የሚሉ ናቸውና ፈሪሳውያን ግን ሁለቱንም ያምናሉ። ሐዋ 23፥8 በዚህም የተነሣ ሁለቱም
ይከራከሩ ነበር። ሐዋ 23፥7-9
ተግባር
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
16
የሚሰጠው የትምህርት ርዕስ፦ የሥራ መስክ እና መገበያያ በመጽሐፍ ቅዱስ
ምዕራፍ ስምንት
ግብርና፦ እርሻን፣ ከብት እርባታንና አደንን የሚያጠቃልል የሥራ መስክ ነው። ገብሬ
የሚለው በአብዛኛው የእርሻ ሥራን ሲያመለክት ይገኛል።
እርሻ፦ በሀገረ እስራኤል እንደ ወይን፣ ስንዴ፣ የወይን ዛፍ፣ ተምር እና በለስ
የመሳሰሉት ይመረታሉ። የእርሻ ሥራ ከአዳም ጀምሮ ተያይዞ የመጣ ነው። ዘፍ 4፥2 ኖኅም
በእርሻ ሥራ ይተዳደር ነበር። ዘፍ 9፥20 አበ ብዙሀን አብርሃምም ገበሬ ነበር። “አብርሃም
በቤርሳቤህ የተምር ዛፍን ተከል” ዘፍ 21፥33 ነቢየ እግዚአብሔር ኤልሳዕም ከመጠራቱ በፊት
በዐሥራ ሁለት ጥማድ በሬ የሚያርስ የሚያጎርስ ገበሬ ነበር። 1ኛ ነገ 19፥19 ኤልዛቤል
በቅናት ያስገደለችው ኢይዝራኤላዊው ናቡቴም የወይን እርሻ የነበረው ገበሬ ነበር። 1ኛ ነገ
20፥1
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
17
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የሰውን ልብ በእርሻ መስሎ አስተምሯል።
ማቴ 13፥1-49
ከብት እርባታ፦ በእስራኤል ጥንታውያን ከሆኑት የሥራ መስኮች ዋነኛው ነው። አቤል
በግ ጠባቂ ነበር። ዘፍ 4፥2 እስራኤላውያን በከፍተኛ ደረጃ የበግ እርባታን ያከናውናሉ።
እስከዛሬም ድረስ ይታወቁበታል። አብርሃምና ሎጥም ከብት አርቢዎች እንደነበሩ ተጽፏል።
ዘፍ 12፥5 ፣ ዘፍ 13፥5-8 ታላቁ ያዕቆብም ለረጅም ዓመታት ከብት ጠባቂ ሆኖ ቆይቷል።
ዘፍ 30፥29 በግብጻውያን ዘንድ በግ ጠባቂ እንደ ርኩስ ይቆጠር ነበርና ዮሴፍ ቤተሰቦችን
ፈርዖን ቢጠይቃችሁ ከብት አርቢዎች ነን በሉት አላቸው። ዘፍ 46፥34 ቅዱስ ዳዊትም ወደ
መንበረ ሥልጣን ከመውጣቱ በፊት በግ ጠባቂ ነበር። 1ኛ ሳሙ 16፥11 ነቢዩ አሞጽም
ለነቢይነት ከመጠራቱ በፊት በከብት አርቢነት ሥራ ተሰማርቶ ይኖር ነበር። አሞ 1፥1
አደን፦ በዱር ውስጥ የሚኖሩ እንሰሳትን አስድዶ መያዝ ወይም መግደል አደን
ይባላል። “ዔሳውም አደን የሚያውቅ የበረሀ ሰው ሆነ” ሲል አደን እንደ አንድ የሥራ መስክ
ይወሰድ እንደ ነበር ያሳያል። ዘፍ 25፥27
ንግድ፦ በጥንት ጊዜ ንግድ ታላቅ የሥራ መስክ ነበር። ታላቁ አባት አብርሃም ከእርሻና
ከከብት እርባታ በተጨማሪ የንግድ ሥራንም ያከናውን ነበር። “አብራምም በከብት፣ በብርና
በወርቅ በለጠገ” ዘፍ 13፥3 ይኖርባት የነበረችው በከለዳውያን ምድር የምትገኘው ዑር
በንግድ የገነነች ሀገር ነበረች።
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
18
ሀገረ እስራኤልም ታላቅ የንግድ መናኽሪያ ከመሆኗ የተነሣ ጠቢቡ ሰሎሞን በጊዜው
ከተለያዩ ሀገራት ይመላለሱ ከነበሩት በርካታ ነጋዴዎች ግብር ይቀበል እንደነበር መጽሐፍ
ቅዱስ ያስረዳል። 1ኛ ነገ 10፥11 ነቢዩ ዮናስ ወደ ተርሴስ ለመጓዝ የተነሣው በነጋዴዎች
መርከብ ተሳፍሮ ነበር። ይህም የባህር ንግድ ተስፋፍቶ እንደ ነበር ያመለክታል። በተለይ
ጢሮስ ከፍተኛ ከፍተኛ የንግድ ሀገር ነበረች። “በእንጨት፣ በሸራ፣ በሐር፣ በቆርቆሮ፣ በእርሳስ፣
በብርና በብረታ ብረት፣ በዝሆን ጥርስ፣ በወርቀ ዘቦ፣ በዞጲ፣ በቅመማ ቅመም. . . ንግድ እጅግ
የከበረች ነበረች” ሕዝ 27፥1-25
ንግድ በተስፋፋት ወቅት የዕቃ በዕቃ ለውጥ (Bartering) አንዱ የመገበያያ መንገድ
እንደሆነ ተጽፏል። “ይለውጡ ዘንድ የዝሆን ጥርስና ዞጲ አመጡልሽ” ሕዝ 27፥15 አብርሃም
እና ያዕቆብ በከብት ቦታ ገዝተዋል። ዘፍ 21፥28 ፣ 33፥18-20
ሕክምና፦ መጽሐፍ “ወይስ በዚያ ሐኪም የለም?” ሲል ሕክምና ጥበብ የነበረ መሆኑን
ያመለክታል። ኤር 8፥22 “ዮሴፍም ባለመድኃኒቶች አገልጋዮቹ አባቱን በሽቱ ያሹት ዘንድ
አዘዘ።” ተብሎ እንደ ተነገረ የሕክምና ሥራ ከጥንት ጀምሮ አለ። ዘፍ 50፥2 እንዲሁም
ንጉሡ አሳ እግሩን በታመመ ጊዜ “ባለ መድኃኒቶች እንጂ እግዚአብሔርን አልፈለገም።” 2ኛ
ዜና 16፥12 ባለመድኃኒቶች የተባሉ ሐኪሞች ናቸው። አባታችን ጻዲቁ ኖኅ ከእግዚአብሔር
በተገለጠለት ጥበብ የመጀመሪያው ሐኪም ነው። እግዚአብሔር ከተለያዩ ዕፆች ወይም ዕፅዋት
ብዙ ዓይነት መድኃኒት ሊሠራ እንደሚችል አሳይቶታል።
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
19
ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊው “ባለ መድኃኒቱ” ተብሎ የተጠራው ሐኪም በመሆኑ ነው። ቆላ 4፥
14 ፣ ዐሥራ ሁለት ዓመት ደም ሲፈሳት የነበረችው ሴትም ከክርስቶስ አስቀድሞ ከብዙ ባለ
መድኃኒቶች ጋር ተገናኝታ ነበር። ማር 5፥26
ግንበኝነት፦ የሰናዖርን ግንብ ከተሰሡት ሰዎች ጀምሮ በመጽሐፍ ቅዱስ በሰፊው ተጠቅሶ
የሚገኝ የሥራ መስክ ነው። ዘፍ 11፥1-9 እስራኤላውያን በዚህ ሥራ የታወቁ ነበሩ።
በተለይም ወደ ግብጽ በተሰደዱበት ጊዜ ዓለም የሚያደንቃቸውን ፒራሚዶች እንደሠሩ
ይነገራል። ምክንያቱም በኦሪት የተጻፉት ታሪኮች ከዚህ ጋር የተያያዙ ናቸው። ጡብ
በመሥራት ለፈርዖን ፊቶምና ራምሴ የተባሉ ጽኑ ከተማዎችን እንደከተሙ ተጽፏል። ዘፍ
1፥8-14
በተግባረ ዕድ /በእጅ ሥራ/ የተሰማሩ ሰዎች ጥንት በባልጩት /ስለታም ድንጋይ/ እና በናስ
ሥራዎቻቸውን ማከናወን ጀመሩ። ዘፍ 4፥22 ከዚያም ብረትን ማቅለጥ እና መቀጥቀጥ
ሰቻል የተለያዩ መሳሪያዎች ተገኙ። ከእነዚህም መሳሪያዎች የሚከተሉት ይገኛሉ። መራጃ፣
መጥረቢያ፣ መቅረጫ፣ መዶሻ፣ መጋዝ፣ ምሳር፣ ቢላዋ፣ ካራ፣ ማጭድ፣ ማረሻ፣ ወስፌ፣ መርፌ
. . . ወዘተ። 1ኛ ነገ 6፥7 ፣ ኢሳ 44፥13 ፣ መሳ 5፥26 ፣ 2ኛ ሳሙ 12፥31 ፣ ዘዳ 19፥5 ፣
2ኛ ነገ 6፥5 ፣ ዘፍ 22፥6 ፣ ምሳ 30፥14 ኢሳ 2፥4 ፣ ዘጸ 21፥6 ፣ ማቴ 19፥24
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
20
ተግባር
3.2.1 መስፈሪያ
የፈሳሽ ነገር መስፈሪያ፦ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሦስት ዓይነት የፈሳሽ መለኪያዎች
ይገኛሉ። አብዛኛውን ጊዜ ውኃ፣ ወይን እና ዘይት ይገኛሉ።
ባዶስ፦ ባዶስና ኢፍ እኩል ይዘት አላቸው። የቆሮስ አንድ ዐሥረኛ ክፍል ነው። ሕዝ
45፥11 ፣ 14 አንድ ባዶስ የ40 ሊትር ይዘት አለው።
ኢን፦ የባዶስ አንድ ስድስተኛ ክፍል ነው። 6 ሊትር ተኩል አካባቢ ነው። ሕዝ 4፥
1 ፣ ዘጸ 29፥40 ፣ ዘሌ 23፥13
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
21
ሎግ፦ የባዶስ አንድ ዐሥራ ሁለተኛ ወይም የኢን አንድ ሁለተኛ ክፍል ነው። 3
ሊትር አካባቢ ነው። ዘሌ 14፥10
ምናን፦ አንድ ምናን ከ500 እስከ 700 ግራም ክብደት እንዳለው ይነገራል። ዕዝ 2፥
69 ፣ 1ኛ ነገ 10፥17
ዳሪክ፦ ለቤተ እግዚአብሔር መስሪያ የተበረከተው ወርቅ የተለካው በዳሪክ ነው።
“ስድሳ አንድ ሺህ የወርቅ ዳሪክ” እንዲል። ዕዝ 2፥69
ሰቅል፦ ከ12 – 14 ግራም ያህል ክብደት አለው። ጎልያድ የለበሰው የነሐስ ጥሩር
5000 ሰቅል ያኽል ነበር። 1ኛ ሳሙ 17፥5 ይህም ወደ 65 ኪሎ ግራም አካባቢ
ይመዝን ነበር። “አብርሃም በ400 ሰቅል ለሣራ መቃብር በኬብሮን ገዛ” ዘፍ 23፥1-
16 ፣ 1ኛ ነገ 10፥16
የንጉሥ፣ የመቅደስና የሕዝብ የሚባል ሰቅል እንደ ነበር በመጽሐፍ ተገልጧል። 2ኛ
ሳሙ 14፥26 ዘጸ 30፥12-14
አቦሊ፦ አንድ አቦሊ የሰቅል አንድ ሃያኛ ነው። ዘጸ 30፥14
መክሊት፦ አንድ መኤክሊት ሠላሳ ኪሎ ግራም ነው። 2ኛ ነገ 18፥14 ፣ 1ኛ ነገ 10፥
14 እና 15
ንጥር፦ አንድ ንጥር 327.45 ግራም አካባቢ ይመዝናል። ዮሐ 19፥39
ታላንት፦ አንድ ታላንት 3 ፈረሱላ አካባቢ ወይም 50 ኪ.ግ ያህል ይመዝናል።
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
22
የሰንበት መንገድ፦ 6 ምዕራፍ ወይም 1200 ሜ /1.2 ኪ.ሜ ያህል ነው። በብሉይ
በሰንበት ቀን ከዚህ ርቀት በላይ መጓዝ አይፈቀድም ነበር። ዘጸ 16፥29 ፣ ሐዋ 1፥
12
የሰው ቁመት፦ አራትክንድ ወይም ስድስት ጫማ ያህላል። ለባሕር ጥልቀት
መለኪያም ይውል ነበር። ሐዋ 27፥28
3.2.2 ገንዘብ
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ገንዘብ የሚለው ቃል ሁለት ዓይነት አገባብ አለው። አንደኛው
ለመገበያያ ይሆን ዘንድ ከተለያዩ ዓይነት ማዕድናት /ከወርቅ፣ ከብር፣ ከመዳብ እና ከነሐስ/
በተለያየ መጠን የሚሠራውን ሲያመለክት፣ ሁለተኛው ደግሞ በአ ጠቃላይ ሀብትን ወይም
ንብረትን ያመለክታል። ሆኖም የመጀመሪያውን የገንዘብ ዓይነት በተመለከተ መጽሐፍ ምን
እንደሚል እንመለከታለን።
ከክርስቶስ ልደት በፊት እስከ 700 ዓመት ድረስ ምንዛሬ ያለው ገንዘብ እንዳልነበር ብዙዎች
ይስማማሉ። ሆኖም ግን ከወርቅ፣ ከብር፣ ከመዳብ እና ከነሐስ የተሠሩ ልዩ ልዩ የግሪክና
የሮማውያን ገንዘቦች በመካከለኛው ምሥራቅ አካባቢ የታወቁ መገበያያዎች እየሆኑ መጡ።
ጌታችን “ወርቅ ወይም ብር ወይም ናስ በመቀነታችሁ . . . አታግኙ ያለው ከእነዚህ
መዓድናት የተሠሩ ገንዘቦች እንደነበሩ ያመለክታል። ማቴ 10፥9 አይሁድም በግሪኮችና
ሮማውያን ቅኝ ግዛት ሥር ሆነው ስለነበር የእነዚህን መንግሥታት ገንዘቦች ጥቅም ላይ
አውለዋል። እነዚህም ገንዘቦች
የግሪክ ገንዘቦች
1. መክሊት፦ የወርቅ መሐለቅ ነው። በእስራኤል ዘንድ የታወቀ የመገበያያ ገንዘብ ነው።
ጌታችንም እየመሰለ በተናገረባቸው አንዳንድ ቦታዎች ላይ ተጠቅሞበታል። ማቴ
18፥24 ፣ ማቴ 25፥14-15 አንድ መክሊት 2100 የኢትዮጲያ ብር ያህል ይመነዘራል።
2. ምናን፦ 35 የኢትዮጲያ ብር ያህል ይመነዘራል። ጌታችን በማቴዎስ ወንጌል ላይ
በመክሊት መስሎ ያስተማረው በሉቃስ ወንጌል ደግሞ በምናን ተተክቶ መነገሩ
ሁለቱም የገንዘብ መጠን መናገሪያዎች በመሆቸው ነው። ሉቃ 19፥13-27
3. ድራክማ፦ ድሪም እየተባለ በአማርኛው መጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሰው ገንዘብ ነው።
ዲናር ተብሎ የሚጠራው የሮማውያንን ገንዘብ ያህል ዋጋ አለው። ዕድሜው ከሃያ
ዓመት በላይ የሆነው አይሁዳዊ ሁሉ በየዓመቱ ለቤተ መቅደስ ሁለት ሁለት ድሪም
/ድራክማ/ ግብር ይከፍል ነበር። ሉቃ 15፥8
የሮም ገንዘቦች
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
23
1. ዲናር፦ የብር መሐለቅ ነው። አንድ ዲናር የአንድ ቀን ሠራተኛ ዋጋ ነበር። ማቴ
20፥9-10 በጌታችን መዋዕለ ስብከት በዲናሩም ላይ የሮማ ነገሥታቶች /ቄሣሮች/
ምስል ይታተምበት ነበር። ማር 12፥15-17 ፣ ሉቃ 10፥35
2. እስታቴር፦ አንድ እስታቴር ዐራት ዲናር ያህል ነው። ማቴ 17፥27
3. አሣርዮን፦ የቄሣር መልክ ያለበት የመዳብ ገንዘብ ነው። በአማርኛው መጽሐፍ ቅዱስ
ውስጥ አምስት ሳንቲም የተባለው አንድ አሣርዮን ነው። “ሁለት ድንቢጦች በአምስት
ሳንቲም ይሸጡ የለምን?” ማቴ 10፥29
4. ካድራንስ፦ የአሣርዮን ሩብ ነው።ይህም በአማርኛው መጽሐፍ ቅዱስ አንድ ሳንቲም
የተባለው ነው። ማር 12፥42
5. ሌፕቶን፦ እስካሁን ከተጠቀሱት ሁሉ የሚያንስ ሲሆን የኳድራንስ ግማሽ ነው።
በአማርኛው መጽሐፍ ቅዱስ ግማሽ ሳንቲም ተብሎ የተጠቀሰው ነው። ሉቃ 12፥59
፣ ማቴ 5፥26 ፣ ማር 12፥42
ሰይፍ፦ በሁለት በኩል የተሳለ ከብረት የሚሠራ የጦር መሣሪያ ዓይነት ነው። ከጎራዴ
የሚለየው በሁለት በኩል የተሳለ እና አጠር ያለ በመሆኑ ነው። በአንድ በኩል ብቻ የተሳሉ
አንዳንድ ሰይፎችም ይኖራሉ። 1ኛ ሳሙ 13፥19-22 ፣ ሉቃ 22፥53 ጌታችን በተያዘ ጊዜም
ቅዱስ ጴጥሮስ የሊቀ ካህናቱን የቀያፋን ባሪያ /የማልኮስን/ ቀኝ ጆሮ በሰይፍ መትቶ
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
24
ቆርጧል። ዮሐ 18፥10 ቃለ እግዚአብሔር በሰይፍ ይመሰላል። “የመንፈስን ሰይፍ ያዙ
እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው።” ኤፌ 6፥17 ፣ ዕብ 4፥12 ፣ መዝ 149፥6
ጥሩር፦ ከአንገት እስከ ጉልበት የሚጠለቅ ከቆዳ ወይም ከተለያዩ ብረታ ብረት የሚሠራ
መከላከያ ነው። 1ኛ ሳሙ 17፥38-39 ፣ 1ኛ ነገ 22፥34 ፣ ነህ 4፥16 ጥሩር የጽድቅ ምሳሌ
ነው። “የጽድቅ ጥሩር ለብሳችሁ” ኤፌ 6፥13-15
ጋሻ፦ ከብረት፣ ከናስ ወይም ከቆዳ የሚሠራ በእጅ የሚያዝ ለሚወረወርም ሆነ ለሚሰነዘር
የጦር መሳሪያ መከላከያ ወይም መመከቻ የሚውል ነው። ነህ 4፥16 ጋሻ በእምነት
ይመሰላል። “እናንተ መሳፍንት ሆይ ተነሡ፣ ጋሻውን አዘጋጁ” ኢሳ 21፥5 “የእምነት ጋሻ
አንሱ” ኤፌ 6፥16 ፣ መዝ 34፥2 ፣ ዘፍ 15፥1
ቁር፦ በራስ ላይ የሚጠለቅ ከናስ፣ ከብረትና ከሌላም ቁሳቁስ ሊሠራ የሚችል የጦር መከላከያ
ነው። “በራሱም ላይ የጦር ቁር ደፋለት። 1ኛ ሳሙ 17፥38 ፣ ቁር የመዳኛ ምሳሌ ነው።
“የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ” ኤፌ 6፥17
ቀስትና ፍላፃ፦ ቀስት ከእንጨት ወይም ከሌሎች ብረታ ብረት የሚሠራ እንደ ደጋን ያለ
ቅርጽ ያለው ሲሆን ከአንዱ ጫፍ እስከ ሌላው ጫፍ ከጅማት ወይም ከጭራ የተገመደና
የተወጠረ ክር ያለው መሣሪያ ነው። ፍላፃ ደግሞ በቀስቱ አማካኝነት እንዲፈናጠር ሆኖ ዘንጉ
ብረት ወይም እንጨት የሆነ ጫፉ ግን ሹል ብረት ያለው መሣሪያ ነው። ዘፍ 21፥20 ፣ 1ኛ
ዜና 5፥18 ፣ 1ኛ ዜና 12፥2
ተግባር
22. ተማሪዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሰላጢን፣ ቀጭኔና ካራ፣ ጎመድ እና ጎራዴ
ስለተሰኙት የጦር መሳሪያዎች የተገለጸውን ጽፋችሁ በመምጣት ለተማሪዎችና
ለመምህሩ ያንብቡላቸው።
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
25
የሚሰጠው የትምህርት ርዕስ፦ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙ እንስሳት እና እጽዋት
የዕለቱ ጥቅስ፦ “እንደ እባብ ብልሆች እንደ ርግብ የዋሆች ሁኑ” ማቴ 10፥16
ምዕራፍ ዘጠኝ
ከትናንሽ እንሰሳት እስከ ታላላቅ ፍጥረታት ድረስ በተለያየ ሁኔታና ምሳሌ የተጠቀሱ
እንስሳት በመጽሐፍ ቅዱስ ይገኛሉ።
ርግብ
መጽሐፍ ቅዱስ በተደጋጋሚ የሚያነሳት ከአዕዋፍ ዝርያ የሆነች እንስሳ ናት። የመንጻት
ወራት ሲፈጸም ለመስዋዕት ትቀርብ ነበር። ዘሌ 12፥6-8 ፣ ሉቃ 2፥22-24
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
26
የኖኅ ርግብ የጥፋት ውኃ ጎደለ ስትል የለመለመ የወይራ ቅጠል እንዳመጣች
ድንግል ማርያምም በእግረ አጋንንት ይቀጠቀጥ ለነበረው ዓለም የሰላም አለቃ፣
የብዙዎች ደስታ የሆነውን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወልዳዋለች። ሉቃ 2፥
14
የኖኅ ርግብ በተላከች ጊዜ በጎ ምላሽ ይዛ እንደመጣች ሁሉ ድንግል ማርያምም
በአማላጅነቷ ለሚተማመኑ ሁሉ ምሕረትን ከእግዚአብሔር ታመጣለች።
3. የየዋሕት ምሳሌ፦ “እንደ እባብ ብልሆች እንደ ርግብ የዋሆች ሁኑ” ማቴ 10፥16
ርግብ ከየዋሕነቷ የተነሣ በጥፋት ውኃ ጊዜ በእባብ አፍ ውስጥ እንቁላል ጥላለች።
ነገር ግን በፍጹም የዋሕነት በእግዚአብሔር ቸርነት ተጠብቃለችና። እናንተም
በየዋሕነት ተጠበቁ ሲል ነው።
በግ
አራት እግር ያለው፣ ቆዳው በጠጉር የተሸፈነ፣ ሥጋቸው ለምግብነት ከሚውሉ የቤት
እንስሳት መካከል አንዱ ነው። ከምግብነት ባሻገርም ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ይቀርቡ
ከነበሩት እንስሳትም የመጀመሪያው ነው። ዘፍ 4፥4 ፣ ዘሌ 22፥19
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
27
በእስራኤል በግ ጠባቂ ከበጎቹ ፊት ፊት ይሄዳል። እነርሱም መሪያቸው፣
ጠባቂያቸው መሆኑን ለይተው እርሱ በሄደበት ሁሉ ይከተሉታል። መልካም
ማሰማሪያ ላይ ሲደርስም በትሩን ይተክላል። እነርሱም ይሰማራሉ። ድምጹንም
ሲያሰማቸው ወደ እርሱ ይሰባሰባሉ። ወደ ሌላ ቦታ መሔድ ሲያስፈልጋቸውም
እረኛው እየመራቸው እነርሱ ይከተሉታል። ምዕመናንም በእረኛ የተመሰለ
ኢየሱስ ክርስቶስን ፈጣሪያቸው ጠባቂያቸው መሆኑን ያውቃሉ። ቃሉንም
ይሰማሉ። የእርሱን ፈለግ ተከትለው ርስት መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳሉ።
እረኛ የሚጠብቃቸውን በጎች እየመራ ሔዶ ለምለም መስክ ሲያገኝ በትሩን
ይተክላል እነርሱም ይህን ዐውቀው ይሰማራሉ፣ በትሩን ሲነቅልም ወደ እርሱ
ይሰበሰባሉ። ጌታችንም የማዳን ጉዞውን በቀራንዮ በተተከለው መስቀል በፈጸመ
ጊዜ የአዳም ተስፋው ሞላለት ወደ ቀደመ ክብሩም መለሰው። ምዕመናንም
በመስቀሉ ሰላምን ወደ ሰጠው ወደ ጌታቸው ይሰበሰባሉ። ዮሐ 21፥15-17
3. የጻድቃን ምሳሌ፦ ክርስቶስ በዳግም ምጽአቱ ጊዜ “በጎችን በቀኙ . . . ያቆማቸዋል”
ተብሏል። ማቴ 25፥33
በግ ወደ ምድር እያየ ይሔዳል፤ ጻድቃንም ዕለተ ሞታቸውን ግብአተ
መሬታቸውን እያሰቡ ንስሐ ገብተው ለሞት ተዘጋጅተው ይኖራሉ።
በግ በላቷ ኃፍረቷን ትሸፍናለች (ትሰውራለች) ጻድቃንም የራሳቸውን ኃጢአት
በንስሐ የሌላውን ኃጢአት በትዕግሥት ይሠውራሉና።
በግ ጭቃ አይጸየፍም ጻድቃንም በሃይማኖት የሚመጣባቸውን መከራ
አይሰቀቁም። በግ ኑሮው በደጋ ነው። ጻድቃንም ኑሯቸው በደጋ መንግሥተ
ሰማያት ነውና።
ንሥር
በሰማይ ከሚበርሩት እና ታላላቅ ከሚበሉት አእዋፍ አንዱ ነው። የባሮክን ደብዳቤ
ከኢየሩሳሌምን ወደ ባቢሎን በምርኮ ወደ ነበረው ነቢዩ ኤርምያስ ያደረሰው ንሥር ነው።
ተረ.ኤር 10፥12 ፣ 11፥8 በመጽሐፍ ቅዱስ ከሚታወቅባቸው ጠባያት አንዱ ፈጣንነት ነው።
“ከንሥር ይልቅ ፈጣኖች ነበሩ” እንዲል 2ኛ ሳሙ 1፥23 ፣ ንሥር በሰማይ ሲበርር ከመንገዱ
የሚያስታጉለው እንቅፋት የለበትም። እግዚአብሔርም እግዚአብሔርን ከግብጽ ሲያወጣ
የቀትር ሐሩር እንዳያቃጥላቸው ደመና ጋርዶ፣ የሌሊቱ ግርማ እንዳያስደነግጣቸው ብርሃን
አብርቶ፣ ባሕረ ኤርትራ እንዳያሰጥማቸው በሕሩን ከፍሎ፣ ከእ ንቅፋት ሁሉ ጠብቆ በቸርነቱ
እንዲወጡ አድርጓቸዋል። ዘጸ 19፥4
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
28
ንሥር የኃይለ እግዚአብሔር ምሳሌ ነው። “እግዚአብሔርን በመተማመን የሚጠባበቁ ግን
ኃይላቸውን ያድሳሉ። እንደ ንሥር በክንፍ ይወጣሉ፤ ይሮጣሉ፣ አይታክቱም፣ ይሔዳሉ፣
አይደክሙም” ኢሳ 40፥31
ከ4ቱ ወንጌላውያን አንዱ የሆነው ነባቤ መለኮት /ታኦጎሎስ/ ቅዱስ ዮሐንስ በሚከተሉት
ምክንያቶች በንሥር ይመሰላል።
ላም
ከለማዳ የቤት እንስሳት መካከል አንዷ ስትሆን ግዙፍና ታዛዥ ለምግብነት የምትውል እንስሳ
ናት። የላምና የበሬ ሥጋቸው እንዲሁም ጉልበታቸው፣ ቆዳቸውና ቀንዳቸው ለሰው ልጆች
የተለያየ ጥቅም ይዘጣል። የላም ወተትም በአብዛኛው ክፍለ ዓለም በምግብነት ያገለግላል።
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
29
የጠፋው ልጅ ታሪክም እንደሚያስረዳን የጠፋው ልጅ አባት የእግዚአብሔር አብ፣
የጠፋው ልጅ የአዳም፣ ፍሪዳው የጌታችን ሥጋና ደም ምሳሌዎች ናቸው።
2. የምዕመናን ምሳሌ፦ የላም መንጋ በአንድ መሪ ይጓዛል፤ ምዕመናንም በአንዱ
በኢየሱስ ክርስቶስ መሪነት በሥርዓት ይጓዛሉና። ላሞች ጉልበት እያላቸው ለጌታቸው
ይታዘዛሉ፤ ምዕመናንም እንደ ሰብእ ዓለም ኃጢአት መሥራት ሲችሉ ስለጌታቸው
ፍቅር ብለው ኃጢአትን ከመሥራት ይቆጠባሉና።
ከ4ቱ ወንጌላውያን አንዱ የሆነው ቅድስ ሉቃስ በላም ይመሰላል። ይኸውም ቅዱስ
ሉቃስ ጌታችን በከብቶች በረት ስለመወለዱ እና ጌታችን በፍሪዳ መስሎ ያስተማረውን
ጽፏልና።
ዋላ
ረጅም ቀንድ ያለውና የፍየል ዝርያ ያለው በተራራማ ቦታ የሚኖር የዱር እንስሳ ነው።
በዘልማድ ዋልያ እየተባለ የሚጠራ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከሀገራችን ከኢትዮጲያ በስተቀር
በየትኛውም የዓለማችን ክፍል አይገኝም። በተራራ አካባቢ ይኑር እንጂ ውኃ ካለበት አካባቢ
ርቆ መኖር አይችልም። ስለዚህ ከግርጌው ውኃ በሚመነጭ ተራራ አካባቢ ይኖራል። ውኃ
ሲጠማው ለመጠጣት ከታራራው ይወርዳል። ከጠጣ በኋላ ተመልሶ ተራራውን ሲወጣ ቆዳው
ስስ ነውና አብዛኛው የጠጣው ውኃ በላብ ይወጣል። እንደገናም ውኃ ለመጠጣት ይናፍቃል።
መዝ 41፥1 ዋላ ከውኃ ምንጭ ርቆ መኖር እንደማይችል ምዕመናንም የሕይወት ውኃ (ስቴ
ሕይወት) ከሆነው ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ርቀው መኖር አይችሉም። ሁል ጊዜ የእርሱን
የሕይወት መጠጥ ደመ መለኮትን ለመጠጣት ይናፍቃሉ።
ፍየል
በቆላማ አካባቢ የምትኖር ቆዳዋ ስስ በሆነ ጠጉር የተሸፈነ ለማዳ የቤት እንስሳ ስትሆን
ሥጋዋ ልምግብ ቆዳዋ ደግሞ ለተለያዩ አገልግሎቶች ይውላል። በተለይም ቆዳዋ ለብራና
በጣም ተፈላጊ ነው። ለልብስነትም ያገለግላል። ዕብ 11፥37
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
30
ፍየል ሁል ጊዜ ቀና ብላ ትሔዳለች እንጂ በአትኅቶ ርእስ /ራስን ዝቅ በማድረግ/
መጓዝ አትችልም፤ ኃጥኣንም ከእኛ ይልቅ ወንድማችን ይሻላል እኛ ዝቅ ብለን
እናገልግለው አይሉም። በትዕቢት ከማን እንሳለን ሲሉ ይኖራሉና።
ፍየል ኃፍረቷን በጅራቷ አትሸፍንም ኃጥኣንም በደላቸውን ጥፋታቸውን በንስሐ
አጥበው ለመንጻት በእግዚአብሔር ቸርነት ለመከለል አይሹምና።
ፍየል ዝናቡን ጭቃውን ትመረራለች /ትጸየፋለች/ ኃጥአንም አምነው መከራን
መቀበል ይመረራሉና።
ፍየል ለጠባቂ አስቸጋሪ ናት፤ ኃጥኣንም የመምህራንን ቃላቸውን ሰምተው ትእዛዘ
እግዚአብሔርን ለመፈጸም አስቸጋሪዎች ናቸው።
ፍየል በሆነው ባልሆነው መጮህ ታበዛለች፣ ኃጥኣንም የምሬት ድምጽ በማሰማት፣
ሰዎችን ለማንቋሸሽ በሆነው ባልሆነው ንግግር /ጽርፈት/ ያበዛሉና።
አህያ
ከማይበሉት የእንስሳት ወገን ስትሆን የጋማ ከብት እየተባሉ ከሚጠሩት ውስጥ ትመደባለች።
እንደ ፈረስና በቅሎ በቤት እንስሳነት የጭነት አገልግሎት በመስጠት ከፍተኛውን ደረጃ
ይዛለች። “እነርሱም እህሉን በአህያዎቻቸው ላይ ጫኑ” ሲል ከጥንት ጀምሮ አህያ የሸክም
ሥራ ትሠራ እንደነበር ያሳያል። ዘፍ 42፥26 ለሰው መቀመጫነትም ታገለግላለች። 2ኛ ነገ
4፥22 ፣ 1ነገ 13፥11-25
1. አድገ በለዓም /የበለዓም አህያ/፦ ሀብተ መርገም የተሰጠው በለዓም ባላቅ ከተባለው
የሞዓብ ንጉሥ ጋር በመስማማት በመስማማት እስራኤልን ለመርገም በአህያ ላይ
ተቀምጦ ጉዞ በጀመረ ሰዓት ከፊቷ የተመዘዘ ሰይፍ የያዘ መልአክን አህያዋ
በመመልከቷ በመሬት ላይ በመደፋት ለመልአኩ በመስገድ ሰግዳለች። ይህንንም
ያልተረዳው በለዓም አብዝቶ ቢደበድባት አንድበት አውጥታ “ሦስት ጊዜ የመታኸኝ
ምን አድርጌብህ ነው? . . . እስከ ዛሬ ድረስ የምትጠቀምብኝ አህያህ አይደለሁምን?
በውኑ እንዲህ አደርግ ዘንድ ልማዴ ነበርን?” ብላዋለች። ዘኁ 22፥21-35
ከዚህም የምንረዳው የእግዚአብሔርን ምስጢር ሰዎች ተረድተው መናገር
ባይችሉ ግዕዛን የሌላቸው ፍጥረታትን አስነሥቶ ሊያናግር እንደሚችል ነው። በዕለተ
ሆሳዕናም የቢታንያ ድንጋዮች አመስግነዋልና።
ኋላ ግን እግዚአብሔር የበልዓምን ዐይኖች ከፈተ፣ መልአኩንም ለማየት በቃ፣
በግንባሩም ተደፍቶ ሰገደለት። በለዓም ዐይኖቹ የተከፈቱለት ዐይነ ሥውር ስለነበር
አይደለም። የተከፈተለት ዐይነ ልቡናው ነው።ያኔ ነው መልአኩን ያየው፣ የሚገባውንም
የጸጋ ስግደት በግንባሩ ተደፍቶ ለጥ ብሎ የሰገደለት። ከዚህም የቅዱሳን መላእክትን
ክብር ዐውቆ መስገድ የሚቻለው እግዚአብሔር ዐይነ ልቡናን ሲያበራ ብቻ ነው።
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
31
2. የቤተልሔም አህዮች፦ “በሬ የገዥውን አህያም የጌታውን ጋጣ ዐወቀ” ኢሳ 1፥3
ተብሎ እንደተነገረ ጌታችን በተወለደ ጊዜ በበረት ከነበሩት እንስሳት መካከል አንዷ
አህያ ትንፋሿን ለአምላኳ ገብራለች።
3. የሆሳዕና አህዮች፦ በዕለተ ሆሳዕና ጌታችን በቤተ ፋጌ ታሥረው የነበሩትን እናትና
ልጅ አህዮች አስፈትቶ ወደ ኢየሩሳሌም እየተዘመረለት ገብቷል። ጌታችንም በአህያ
ላይ ተቀምጦ መጓዙ እና የታሰሩትን ማስፈታቱ ምስጢር አለው። ይኸውም፦
የምዕመናን ምሳሌ፦ ፈትታችሁ አምጡልኝ ማለቱ ሰው ሁሉ ከማዕሠረ
ኃጢኣት የሚፈታበት ጊዜ ደርሷል ሲል ነው። እነዚህ አህዮች ተሰርቀው
የታሠሩ ነበሩ ቢሉ ዲያቢሎስ ሰርቆ በሲኦል አሥሯቸው የነበሩት ነፍሳት ነፃ
ይወጣሉና። ጌታችንም ገና ማንም ባልተቀመጠባት ውርንጫዋ
እንደተቀመጠባት ሁሉ በንጹሐን መሃይምናን (አማንያን) አድሮባቸው
ይኖራልና። በአካባቢውም የነበሩ ሰዎች ልብሳቸውን ጎዘጎዙለት ይኸውም፦
ኮርቻ ሲቀመጡበት ይቆረቁራል ልብስ ግን አይቆረቁርም፤ አንተም
የማትቆረቁር መልካሟን ሕገ ወንጌልን ሰጠኸን ሲሉ ነው። አንድም ልብስ
የሰውነትን ነውር ይሸፍናል፤ አንተም ከባቴ አባሳ (በደልን የማትቆጥር) ነህ
ሲሉ ነው። ጌታችን በአህዮቹ ላይ በመቀመጡ አህዮቹ በተነጠፈ ልብስ ላይ
ለመጓዝ በቁ። ሰዎችም እግዚአብሔር ካደረባቸው እንዲህ ይከብራሉ።
የሰላም ምሳሌ፦ በዘመነ ብሉይ ነቢያት የጠብ ዘመን የመጣ እንደሆነ በፈረስ
ተቀምጠው ዘገር ነጥቀው ይታያሉ። ዘመነ ሰላም የመጣ እንደሆነ ደግሞ በአህያ
ተቀምጠው መነሳንስ ይዘው ይታያሉ። ጌታችንም በአህያ ተቀምጦ ወደ
ኢየሩሳሌም የመጣው ሰላምሽ እኔ ነኝ ሲል ነው። ሉቃ 19፥42 አንድም ለሰው
ልጅ ሁሉ ሰላምና ደስታ የሚሆንበት ጊዜ ደርሷልና ሲል ነው። ለዚህም ነው
ከትንሣኤ በኋላ ደቀ መዛሙርቱን “ሰላም ለእናንተ ይሁን” ያለው። ዮሐ 20፥
19 ፣ ቆላ 1፥20
ፍጥነቷ ደካማ ከመሆኗ የተነሣ በአህያ የተቀመጠ ሸሽቶ አያመልጥም
አሳድዶም አይዝም፤ ጌታችንም ካልፈለጉኝ አልገኝም ከፈለጉኝ አልታጣም
ሲል በአህያ ተቀምጧል።
የእስራኤልና የአህዛብ ምሳሌ፦ እናቲቱ አህያ (ዕድገት) የእስራኤል ምሳሌ
ናት። እናት አህያ የሠረገላ ቀንበር መሸከም የለመደች እንደሆነች ሁሉ
እስራኤልም ሕግን (ኦሪትን) መጠበቅ ለምደዋልና ነው። ውርንጫዋ (ዕዋል)
የአሕዛብ ምሳሌ ናት። ውርንጫዋ ቀንበር መሸከም ገና ያልለመደች እንደሆነች
ሁሉ አሕዛብም ሕግመጠበቅ ያልለመዱ ናቸውና። ቢሆኑም ግን በአምላክነቱ
ካመኑ ልቡናቸውን ለእርሱ ማደሪያነት ከቀደሱ በእስራኤልም በአሕዛብም ላይ
አድራለሁ ሲል ነው።
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
32
ዓሣ
በባሕር ውስጥ የሚኖር እና በምግብነቱ እጅግ ተወዳጅ የሆነ እንስሳ ነው።
የሚተነፍሰው በጊል (በስንጥብ) ነው። ከባሕር ውስጥ ከወጣ ከጥቂት ሰኮንድ በኋላ ይሞታል።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የምዕመናን ምሳሌ ሆኖ ተጠቅሷል። ጌታችን ጴጥሮስንና ወንድሙ
እንድርያስን ዓሣ ሲያጠምዱ አገኛቸው። ከዚያም “በኋላዬ ኑና ሰዎችን አጥማጆች እንድትሆኑ
አደርጋችኋለሁ።” አላቸው። ማቴ 4፥19 ሰውን እንደ ዓሣ፣ ወንጌልን እንደ መረብ፣ ዓለምን
እንደ መረብ አድርጋችሁ እንድታስተምሩ አደርጋችኋላሁ ሲላቸው ነው።
ተግባር
23. ተማሪዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ዋኖስ፣ አንበሳ፣ ሰጎን፣ የሜዳ አህያ፣
ገብረ ጉንዳን፣ ሽኰኰ፣ አንበጣ፣ እንሽላሊት፣ ውሻ፣ እርያ፣ ቁራ፣ ቀበሮ፣
ተኩላ፣ እባብ፣ እፉኝት ስለተሰኙት እንስሳት የተገለጸውን እንዲሁም
ምሳሌነታቸውን ጽፋችሁ በመምጣት ለተማሪዎችና ለመምህሩ
ያንብቡላቸው።
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
33
. . ወዘተ ሥራ ላይ በመዋላቸው የተነሣ የተጠቀሱ አሉ። ከእነዚህም መካከል የተወሰኑትን
ቀጥሎ እንመለከታለን።
ዕጣን
የዕጣን ዛፍየሚገኘው በበረሃ ነው። የቤተ መቅደስ አገልግሎት ከተጀመረበት ጊዜ
አንሥቶ ዕጣን የጸሎት ማሳረጊያ መሥዋዕት ሆኖ በካህናት ይቀርባል። ዘጸ 30፥1 ፣ 7፥27
፣ ዘሌ 16፥12-13 “የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት
ወጣ” ራእ 8፥3-4 ፣ ራእ 5፥8
ዕጣን የጌታችን ምሳሌ ነው። ሰብአ ሰገል ዕጣን አምኃ አድርገው የሰጡትም እንደ
ዕጣን ትሰዋልናለህ ሲሉ ነው። ማቴ 2፥11 ዕጣን ስለ ሌሎች ጸሎት እንደሚሠዋ
ጌታችንም ስለ ሰው ልጆች ሁሉ ራሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቷል። ለዚህም ነው
ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ምዑዘ ባሕርይ የምትለው። የዕጣኑ መዓዛ የጌታችን
ርኅራኄና ፍቅር ምሳሌ ነው። ዕጣኑን ያሸተተ ሁሉ ደስ እንዲሰኝ የጌታችን
ርኅራኄና ፍቅር የተሞላበት ጉዞ ያስተዋለ ሁሉ ደስ ይሰኛልና።
ዕጣን የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ነው። “መዓዛዋም እንደ ከርቤና ዕጣን የሆነችው፣
ከልዩ ከነጋዴ ቅመም ሁሉ የሆነችው ይግች ከምድረ በዳ እንደጢስ ምሰሶ
የወጣችው ማን ናት?” ሲል በምድረ በዳ ከተመሰለችው ዓለም ተለይታ ወደ ሰማይ
ንጉሥ ወደ እግዚአብሔር የምትዘረጋ ጸሎቷም የሚሠማላት ቤተ ክርስቲያንን
በዕጣን መስሏታል። መኃ 3፥6 ደግሞም የእመቤታችን ምሳሌ ነው። ጠቢቡ
ሰሎሞን እንዲህ ሲል የተናገረው ከሰው ልጆች ሁሉ (ከምድረ በዳ) ተለይታ ሰማያዊ
ምግባርን ንጽሐ ሥጋ፣ ንጽሐ ልቡናን፣ ንጽሐ ነፍስን ገንዘብ ያደረገች እመቤታችን
ናት ሲል ነው።
ዕጣን የምዕመናን ምሳሌ ነው። ቅዱስ ጳውሎስ “በሚድኑትና በሚጠፉት ዘንድ
ለእግዚአብሔር የክርስቶስ መዓዛ ነንና ለእነዚህ ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ
ለእነዚህም ለሕይወት የሚሆን የሕይወት ሽታ ነን” እንዳለ 2ኛ ቆሮ 2፥15-16።
ዕጣን በተሠዋ ቁጥር ወደ ላይ እንደሚወጣ የክርስቲያኖችም ሕይወት ከክብር ወደ
ክብር ወደ ሰማያዊ ማዕረግ ትሄዳለችና። የዕጣን ሽታ አካባቢን እንደሚለውጥ
ክርስቲያኖችም ሥጋዊ ሥራ የነገሠበትን ዓለም በምግባራቸው አሸናፊነት
ይለውጣሉና።
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
34
ወይን
በመጽሐፍ ቅዱስ ከፍተኛ ሥፍራ ከተሰጣቸው ዕፅዋት አንዱና ዋነኛው ነው። በሀገረ
እስራኤል ከጥንት ጀምሮ በከፍተኛ ደረጃ ይመረታል። “ኖኅም ገበሬ መሆን ጀመረ ወይንም
ተከለ” ዘፍ 9፥20 ያለው እና “መለኬጼዲቅም እንጀራንና የወይን ጠጅን አወጣ” ዘፍ 14፥15
ያለው ከጥንት ጀምሮ የወይን እርሻ እንደ ነበር ያመለክታል።
የወይን ተክል ቶሎ ያድጋል። ክንዱ እየተቆረጠ ሰባት ሰባት ክንድ ያህል እየተራራቀ
ይተከላል። ቅርንጫፉ እየተከረከመ ተኮትኩቶና ተጠብቆ ሁለት ዓመት ያህል ይቆያል።
በሦስተኛው ዓመት ፍሬ እንዲያፈራ ይተዋል።
የወይን ተክል የምዕመናን ምሳሌ ነው። “ስለ ወዳጄና ስለ ወይን ቦታው ለወዳጄ
ውኔ እቀኛለሁ። ለወዳጄ በፍሬያማ ኮረብታው ላይ የወይን ቦታ ነበረው። በዙሪያው
ቆፈረ፣ ድንጋዮችንም ለቅሞ አወጣ፣ ምርጥ የሆነውን አረግ ተከለበት፣ በመካከሉም
ግንብ ሠራ ደግሞም የመጥመቂያ ጒድጓድ ማሰለት፣ ወይንንም ያፈራ ዘንድ
ተማመነ፣ ዳሩ ግን ሆምጣጣ ፍሬ አፈራ” ኢሳ 5፥1-2
የወይን ተክል የተባሉ እስራኤል ናቸው። ወዳጄ የተባለ እግዚአብሔር ነው።
ድንጋዮችንም ለቅሞ አወጣ አለ፤ አሕዛብንና እንግዶች አማላእክትን አጠፋ ሲል
ነው። ግንብ ሠራ አለ፤ ከመከራ ከወረራ ጠበቃቸው ሲል ነው። የመጥምቂያ
ጒድጓድ ማሰለት አለ፤ ገነት መንግስተ ሰማያትን አዘጋጀላቸው ሲል ነው። ይህ
ሁሉ ቢደረግም ሆምጣጣ ፍሬ አፈራ አለ፤ ተመልሰውም በጣኦ አምልኮ በኃጢኣት
ሥራ ተጠመዱ፣ ጌታቸውን ሰቀሉ። ውኃ ቢጠማው ኃሞትና ከርቤ ሆምጣጤም
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
35
አቀረቡለት ሲል ነው። ወይን በየዓመቱ ይገረዛል፤ ምዕመናንም በየጊዜው በንስሐ
ይታደሳሉ።
ወይን የፍሬ ሃይማኖት ምሳሌ ነው። “አንድ ሰው የወይን አትክልት ተከለ
ለገበሬዎችም አከራይቶ ለብዙ ዘመን ወደ ሌላ ሀገር ሄደ በጊዜውም የወይኑ
አትክልት ጌታ ገበሬዎች ካፈሩት ፍሬ እንዲሰጡት አንድ ባሪያ ወደ ገበሬዎቹ
ላከ። ገበሬዎቹ ግን ደበደቡት ባዶውንም ሰደዱት። ጨምሮም ሌላውን ባሪያ ላከ።
እነርሱም ያን ደግሞ ደበደቡት። አዋርደውም ባዶውን ሰደዱት። ጨምሮም
ሦስተኛውን ላከ። እነርሱም ይህን ደግሞ አቁስለው አወጡት። የወይኑም አትክልት
ጌታ ምን ላድርግ? የምወደውን ልጄን እልካለሁ፤ ምናልባት እርሱን አይተው
ያፍሩታል አለ። ገበሬዎቹ ግን አይተው እርስ በእርሳቸው ሲነጋገሩ፦ ወራሹ ይህ
ነው፤ ርስቱ ለእኛ እንዲሆን እንግደለው አሉ። ከወይኑም አትክልት ወደ ውጭ
አውጥተው ገደሉት። እንግዲህ የወይኑ አትክልት ጌታ ምን ያደርጋቸዋል?
ይመጣል፤ እነዚህንም ገበሬዎች ያጠፋል፤ የወይኑንም አትክልት ለሌሎች
ይሰጣል።” የሚል ምሳሌ ጌታችን ተናግሯል። ሉቃ 20፥9-16
በዚህ ምሳሌ የወይኑ ጌታ የተባለ አብ ነው፣ ገበሬዎች የእስራኤል ዘሥጋ፣ የወይኑ
ፍሬ የምግባረ ሃይማኖት፣ ወራሹ ልጅ የአብ የባሕርይ ልጅ የክርስቶስ፣ ሦስቱ
ባሮች የካህናት፣ የመሳፍንት /የነገሥታት/ እና የነቢያት ምሳሌዎች ናቸው።
እስራኤል በዘመነ ካህናት፣ በዘመነ መሳፍንት /ዘመነ ነገሥታት/ እና በዘመነ
ነቢያት ፍሬ ሊያፈሩ ቀርቶ የእግዚአብሔር መልእክተኞችን አሰቃይተዋልና። ኋላ
ግን አንድ ልጁን ላከላቸው እርሱንም ሰቀሉት።
ወይን የጌታችን ምሳሌ ነው። ራሱ “እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ” እንዳለ።
ዮሐ 15፥1 እመቤታችንም ሐረገ ወይን /የወይን ሐረግ/ ትባላለች። ልጇ ኢየሱስ
ክርስቶስ ደግሞ በወይኑ ፍሬ ይመሰላል። ከወይን ሐረግ የወይን ፍሬ እንደሚገኝ
ድንግል ማርያም ኢየሱስ ክርስቶስን አስገኝታለችና።
የወይን ጠጅ ለቁስለ ሥጋ መድኃኒት እንደሆነ /ሉቃ 10፥34 ፣ 1ኛ ጢሞ 5፥
23/ ጌታችን ከቁስለ ሥጋና ከቁስለ ነፍስ የሚያድን እውነተኛ መድኃኒት ነውና።
ወይን በብሉይ ኪዳን ለመሥዋዕት ይቀርብ ነበር። ዘጸ 29፥40 በሐዲስ ኪዳን ግን
በወይን መልክ የምንቀበለው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አማናዊው ደሙን ነው።
“ጽዋውንም አንሥቶ . . . የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው” ብሎ ራሱ ጌታችን
እንደተናገረ። ማቴ 26፥27-29 ጌታችንም ደሜ አለ አንጂ የደሜ ምሳሌ አላለም።
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
36
ወይራ
በአብዛኛው በእስራኤልና በኢትዮጲያ ይገኛል። በብሉይም ሆነ በሐዲስ የወይራ ዘፍ
በቤተ እግዚአብሔር ውስጥ ከፍተኛ አገልግሎት አለው። ከወይራ ተክል ዘይት ይገኛል።
ሮሜ 11፥17 የወይራ ዛፍ ፍሬ የሚያፈራው በተተከለ በሰባት ዓመት ሲሆን ከዚያ በኋላ ግን
አንድ አንድ ዓመት እያሰለሰ በሁለት በሁለት ዓመት ፍሬ ይሰጣል። አንድ የወይራ ዛፍ ጥሩ
ሆኖ ከተጠበቀ እና ሥፍራውም ከተመቸው በአንድ ጊዜ ከሃምሳ እስከ መቶ ሊትር ሊገኝበት
ይችላል።
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
37
ዘንባባ
ዘንባባ የሰሌን ተክል ነው። በብሉይ ኪዳን የዳስ በዓል ሲከበር እስራኤል ለዳስ
መሥሪያ ከሚጠቀሙባቸው ዛፎች መካከል አንዱ ነው። ነህ 8፥14-15
በለስ
በለስ ቅጠሉ ሰፋፊ፣ ነጭ ደም ያለው፣ ፍሬው የሚበላ አጭር ዛፍ ወይም ቁጥቋጦ
ነው። እንደ ወይን ሁሉ በተለይ በሀገረ እስራኤል የበለስ ፍሬ ለምግብነት ይውላል። ዘዳ 8፥
8 ፣ ዕን 3፥17 ፣ ሚክ 4፥4
ተግባር
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
38
መርጃ መሳሪያ እና ማመሳከሪያ
ይህንን ትምህርት መምህሩ
1. መጽሐፍ ቅዱስ
2. ከኦሪት ዘፍጥረት ጀምሮ እስከ ራዕይ ድረስ ያሉ የትርጓሜ መጻህፍት
3. የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በማህበረ ቅዱሳን
4. የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በዲ. አባይነህ ካሴ ቁጥር 1 እና 2
5. መጽሐፍ ቅዱስን የማንበብ እና የማጥናት ዘዴ በመ.ቸሬ አበበ
6. በመጽሐፍ ቅዱስ የሚገኙ ከተሞች እና ሀገራት ዲ.ዳንኤል ክብረት
7. የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ለሰንበት ትምህርት ቤቶች
ማስተማሪያ ያዘጋጀው መጽሐፍ
8. መርሐ ህይወት መጽሐፍ እና ሌሎች መጻህፍት
በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ትምህርት
ክፍል የተዘጋጀ
39