Aderejajet

You might also like

Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 9

በምዕራብ ኦሞ ህዝቦች ልማት ማህበር

የዞን፣ የወረዳ፣ የከተማ አስተዳደር፣ የቀበሌና የተቋማት

የአባላት የአደረጃጀት መመሪያ

2024 እ.እ.አ
ጀሙ

አደረጃጀት፣ ተግባርና ሀላፊነት


1. መግቢያ
የምዕራብ ኦሞ ህዝቦች ልማት ማህበር (ምኦህልማ) በዞኑ ውስጥ ያሉ የልማት ክፍተቶች ለመሙላት በህዝቡ

ይሁንታ የሚመሰረት ሀገር በቀል የልማት ተቋም ነው፡፡ ማህበሩ የሚቋቋምበትን ዓላማ መሰረት በማድረግ

በትምህርት፣ በጤና፣ በውሃ፣ በመንገድና በማህበረሰብ አቅም ግንባታ ላይ በርካታ ስራዎችን በመስራት ህዝብን

ተጠቃሚ ማድረግ የሚችል ተቋም ነዉ፡፡ በዚህ ሂደት በተለይም በአባላት ማፍራት ረገድ ያለውን ሥራ

ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመምራትና ወቅቱን ታሳቢ ያደረገ የአባላት ክፍያ ትኩረት አድርገው መስራት

ለማህበሩ ቀጣይነት ስራ ወሳኝ በመሆኑ በየእርከኑ ባሉ የአባላት ክፍያ ላይ የተለየ ትኩረት በማድረግ ይህ

መመሪያ ተዘጋጅተዋል፡፡

2. የማህበሩ አመሠራረት ራዕይና ተልዕኮ


ማህበሩ አዲስ ሆኖ የምዕራብ ኦሞ ህዝቦች ልማት ማህበር በሚል ስያሜ የሚደራጅበት 2016 ዓ.ም (2024
እ.እ.አ) ሆኖ በሰረታዊነት የማህበሩ የትኩረት አቅጣጫዎች ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ ሥራዎች በትምህርት፣
በጤና፣ በውሃ፣ በመንገድና በማህበረሰብ አቅም ግንባታ ያከናዉናል፡፡

2.1. የማህበሩ ራዕይ

በመንግስት ተደራሽ ያልሆኑ የአካባቢው ህዝቦች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች ተቀርፈው መሰረተ ልማት
ተስፋፍተውና ህዝቡ የዘላቂ ልማት ተጠቃሚ ሆኖ ማየት፡፡

2.2. የማህበሩ ተልዕኮ

የምዕራብ ኦሞ ህዝቦች ልማት ማህበር (ምኦህልማ) ህብተሰቡን በማስተባብር ከአባላት በሚሰበሰብ ገቢና
ፕሮጀክት ቀርፆ ከአጋር ድርጅቶች ጋር ተባብሮ በመስራት በሚገኘዉ ገቢ የአከባቢውን የልማት ክፍተት
በመሙላት የህዝብን ተጠቃሚነት የማረጋገጥ ተልዕኮ አለው፡፡

2.3 ዓላማ
የማህበሩን ገቢ አሁን ካለበት ከምንም ተነስተን ከፍ በማድረግ በርካታ ስራዎችን በመስራት የማህበረሰቦቻችንን
የልማት ፍላጎት በአፋጣኝና በተሳለጠ መልኩ ምላሽ መስጠት ነው፡፡
2.4. አስፈላጊነት
የውጭ ድጋፍ ሰጭና ረጂ ድርጅቶችን ብቻ ጠብቆ በልማት ጥማት ውስጥ ከመኖር ይልቅ የማህበረሰብ
አቅማችንን በማቀናጀትና ያሉንን ፀጋዎች ወደ ሀብት በመቀየር በርካታ ልማቶችን በማልማት አሁን የታዩ
የእድገት ደረጃዎቻችን ከፍ ለማድረግ ገቢያችን ወሳኝ ሚና ስላለው ይህ መመሪያ ተዘጋጅቷል፡፡
3. የማህበሩ ገቢ ምንጭ
ከማህበሩ ገቢ ምንጮች አንዱ በአባላት ማፍራት ዘርፍ አማካኝነት የሚሰበሰብ የአባላት መዋጮ ክፊያ ገቢ
ሲሆን ማህበሩ ይህን ሀብት በመሰብሰብ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ሁሉም በሚባል ደረጃ በወረዳዎችና
በከተማ አስተዳደር ያከናዉኗል፡፡
4. የተቋምና የአባላት የአባልነት ክፊያ እርከንን ቀመር

4.1. የተቋም አባላት ክፊያ እርከን


o ፕላቲኒየም ደረጃ 50,000 ብርና ከዚያ በላይ
o ወርቅ ደረጃ 30,000 ብርና ከዚያ በላይ
o ብር ደረጃ 20,000 ብርና ከዚያ በላይ
o ነሐስ ደረጃ 10,000 ብርና ከዚያ በላይ
o መደበኛ አባል 5,000 ብርና ከዚያ በላይ

4.2. የአባላት ክፊያ እርከን


 የወረዳ አመራር መዋጮ በወር 50 በዓመት 600 ብር
 የመንግስት ሠራተኛ
 የወር ደመወዝ ከ 1000-1500 በወር 5 ብር በዓመት 60 ብር
 የወር ደመወዝ ከ 1501-3500 በወር 6 ብር በዓመት 72 ብር
 የወር ደመወዝ ከ 3501-6500 ብር በላይ በወር 10 ብር በዓመት 120 ብር
 የወር ደመወዝ ከ 6501-9000 ብር በላይ በወር 12 ብር በዓመት 144 ብር
 የወር ደመወዝ ከ 9001 በላይ በወር 15 ብር በዓመት 180 ብር
 አርብቶና አርሶ አደር እንዲሁም የከተማ ነዋሪ በወር 4 ብር በዓመት 48 ብር
 የንግድ ማህበረሰብ
 ደረጃ ሐ ግብር ከፋይ በወር 10 በዓመት 120 ብር
 ደረጃ ለ ግብር ከፋይ በወር 30 በዓመት 360 ብር
 ደረጃ ሀ ግብር ከፋይ በወር 125 በዓመት 1500 ብር ይከፍላሉ፡፡
 የተማሪ አባል በወር 5 ብር በዓመት 60 ብር እንዲከፍሉ ይደረጋል፡፡

5. የካርኒ ማሰራጨትና እንዲሰበሰቡ ማድረግ


በወቅቱ የአባላት መዋጮ ደረኝ/ካርኒ/ አሰራር ስርዓቱ ማውረድና በወረዱ ካርኒዎች የተሰበሰበው ገቢ በወቅቱ
እንዲመለስ በማደረግ ቀጣይነት ያለው ስራ መስራትና ክትትል ማድረግ

6. የተጨማሪ ገቢ አማራጮችን ማፈላለግ


በማህበሩ ተጨማሪ ገቢዎችን ለማግኘት ከመንግስት ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በዞን፣ በወረዳና በክ/ከተማ ላይ
የሚሰሩ ሌሎች የገቢ ማስገኛ ኢቨስትመንቶችና ባዛሮች ላይ የማስተባበር ሥራ ይሰራል፡፡
7. የወረዳ ፅ/ቤት ተወካይ ጥቅማ ጥቅም
በወረዳው በግለሰቦቹ ጥረትና ስኬት ጋር የሚመጥን የማትጋት ስርዓት ሊኖረን እንደሚገባ ታሳቢ በማድረግ
ተወካዩ በዞን ደረጃ በወር 3500 ብር (ሦስት ሺ አምስት መቶ ብር) ቶፕ አፕ፣ የ 1000 ብር (አንድ ሺህ ብር)
የቤት ኪራይ የ 600 ብር (ስድስት መቶ ብር) ለሥራ የሞባይል ካርድ እንዲቀርብላቸው በማድረግ ስራውን
ማስቀጠል ይኖርበታል፡፡
8. የዘርፍ አደረጃጀት

8.1. በዞን መምሪያዎች ደረጃ የሚቋቋም የአባላት ማፍራት ኮሚቴ

 መምሪያ ኃላፊዎች በሚመሩት መድረክ 3(ሦስት) አባላት ያሉት ልማትና አባላት ማፍራት ኮሚቴ
በሠራተኛው ሙሉ ድምጽና ተሳትፎ እንዲመረጡና ወደ ስራ እንዲገቡ ይደረጋል፡፡
 የማህበሩን አባላት በማስተባበር የፋይናንስ ማቴሪያልና የእውቀት ድጋፍ የማሰባሰብ ሥራን ጨምሮ
ፕሮጀክት እስከ ማዘጋጀት የሚደርስ እንቅስቃሴ ማድረግ፡፡
 ተጠሪነትን በተመለከተ ኮሚቴው ለመ/ቤታቸው ኃላፊና ለልማት ማህበሩ ጽ/ቤት ተጠሪነት
ይኖራቸዋል፡፡

8.2. በወረዳ ደረጃ የሚቋቋም የአባላት ማፍራት ኮሚቴ

1. የወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ሰብሳቢ


2. የወረዳ ዋና ም/አስተዳዳሪ ም/ሰብሳቢ
3. የማህበሩ ፅ/ቤት ተወካይ ፀሀፊ
4. የወረዳ ት/ጽ/ቤት ኃላፊ አባል
5. የወረዳ ጤና/ጽ/ቤት ኃላፊ አባል
6. የወረዳ መንገድና ትራንስፖርት/ጽ/ቤት ኃላፊ አባል
7. የወረዳ ውሃ/ጽ/ቤት ኃላፊ አባል
8. የወረዳ ሴቶች፣ ህፃናት ወጣቶች/ጽ/ቤት ኃላፊ አባል የሆኑበት ኮምቴ ተደራጅቶ አጠቃላይ የአባላት
ማፍራትና የልማት ስራዎችን ይከታተላሉ ይገመግማሉ አቅጣጫም እየሰጡ ይመራሉ፡፡

8.3. በቀበሌ ደረጃ የሚቋቋም የአባላት ማፍራት ኮሚቴ

1. የቀበሌ ዋና አስተዳዳሪ ሰብሳቢ


2. የቀበሌ ም/አስተዳዳሪ ም/ሰብሳቢ
3. የቀበሌ ሥ/አስኪያጅ ፀሐፊና ፎካል ፐርሰን
4. የቀበሌ ግ/ጽ/ኃላፊ አባል
5. የት/ቤት ር/መ/ር አባል
6. የቀበሌ ጤና ኤክስተንሽን አባል
7. የቀበሌ ኦሞ ኤጀንት አባል በመሆን የቀበሌውን የልማትና የአባላት ማፍራት ተግባራትን በጠንካራ
አደረጃጀት የመምራትና የማስተባበር ስራ በጋራና በግል ደረጃ ይሰራሉ፡፡

9. የግንኑነት ስርዓት
9.1 ወረዳ ልማትና አባላት ማፍራት ኮሚቴ ተግባርና ኃላፊነት
የወረዳ ልማትና አባላት ማፍራት ኮሚቴ ተጠርነቱ ለዞን ልማት ማህበር ሥራ አመራር ኃላፊ ሆኖ የሚከተሉት
ተግባርና ኃላፊነቶች ይኖሩታል፡፡

o የወረዳው አመታዊ የልማት ዕቅድ መዘጋጀቱን መከታተል ገምግሞ ወደ ስራ ማስገባት


o ተወካዩን በመደገፍና በማብቃት በየሩብ አመቱ መገምገምና ግብረ መልስ መስጠት
o ከዞን ልማት ማህበር ጋር ግንኙነት በማድረግ የወረዳው ሪፖርት በየጊዜው መላኩን ማረጋገጥ
o ተወካዩን በአፈጻጸሙ ገምግሞ አርሞ ማብቃትና የማይታረምና ተግባርን የማይፈጽም ከሆነ በቦታው
ሌላ ሰው እንዲተካ ለማህበሩ በማሳወቅ ስራ እንደጀምር ማድረግ፡፡

9.2 የመንግስት መ/ቤት ስራ ኃላፊዎች ተግባርና ኃላፊነት

 ሥራውን በባለቤትነት መምራትና ማስተባበር፡


 በተቋማቸው ሠራተኛውን አባል ማድረግና የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ማስተባበር፡
 ተቋማቸውን አባል ማድረግና የአባልነት ግዴታ እንዲወጣ ማድረግ፡፡
 በተቋምና በሰራተኞች የሚሰበሰበው ገንዘብ በአሰራር ስርዓቱ ወደ ፋይናንስ እና ወደ ልማት
ማህበሩ አካውንት መግባቱን ይከታተላል፡፡
 የተቋም ፎካል መምረጥና አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ

9.3 የቀበሌ ልማትና አባላት ማፍራት ኮሚቴ ተግባርና ኃላፊነት

የቀበሌ ልማትና አባላት ማፍራት ኮሚቴ ተጠሪነቱ ለወረዳ ልማትና አባላት ማፍራት ኮሚቴ ሆኖ የሚከተሉት
ተግባርና ኃላፊነት ይኖረዋል፡፡
o የቀበሌው አመታዊ የልማት ዕቅድ መዘጋጀቱን መከታተል ገምግሞ ወደ ስራ ማስገባት
o ፎካል በመደገፍና በማብቃት በየወሩን ስራ አፈጻጸም መገምገምና ግብረ መልስ መስጠት
o ከወረዳ ልማት ማህበር ጋር ግንኙነት በማድረግ የቀበሌውን ሪፖርት በየጊዜው መላኩን ማረጋገጥ
o ፎካሉ በአፈጻጸሙ ልክ ማትጋትና በጉድለቱ ልክ የማረም ስራ በመስራት በእጁ ያለውን የቀበሌዋ
የልማት እድገትና ኃላፊነት በጫንቃቸው ላይ የተጣለባቸው መሆኑን በማወቅ መረባረብ
ይኖርባቸዋል፡፡
9.4 የወረዳ ተወካይ ተግባርና ኃላፊነት

 የወረዳ ተወካይ ጣምራ ተጠርነቱ ማለትም በአስተዳደራዊ ጉዳይ ለወረዳ ልማትና አባላት ማፍራት
ኮሚቴና ለዞን ልማት ማህበር ጽ/ቤት ሆኖ የሚከተሉት ተግባርና ኃላፊነት ይኖረዋል፡፡
 የወረዳውን የአባላት ማፍራትና የልማት ዕቅድ አዘጋጅተው የማቅረብ የማስገምገምና ሲፈቀድ ወደ
ተግባር መግባት
 ከማህበሩ አባላትና ከተለያዩ የገቢ ምንጮች ገቢ በማህበሩ ገቢ ደረሰኝ ይሰበስባል ለዞን ምኦህልማ
ጽ/ቤት ቦርድ አካውንት በማስገባት ሪፖርት ያደርጋል፡፡
 አቅሙን በመገንባት በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ አባላትን ለማፍራት ጥረት ማድረግና የልማት ስራዎችን
እንዲተግብሩ መደገፍና ክትትል ያደርጋል፡፡
 በየቀበሌ ያለውን አፈጻጸም በመከታተል ወራዊ ሪፖርት አዘጋጅተው በኮሚቴው ማስገምገም፡፡
 በተገቢው መንገድ ሪፖርቶችን ማዘጋጀት በኮሚቴው ማስገምገምና ለጽ/ቤት ሪፖርት ማድረግ
 በአፈጻጸማቸው የተሻሉ ተቋማት፣ ፎካሎችና አደረጃጀቶችን በመለየት እውቅና እንዲያገኙ
ማድረግን ጨምሮ በኮሚቴው የሚሰጡትን ተግባራት በታማኝነትና በትጋት የሚያከናውን ይሆናል፡፡

9.5 በየተቋማትና በቀበሌ ያሉ ፎካሎች ተግባርና ሀላፊነት

 በየተቋማትና በቀበሌ ያሉ ፎካል ፐርሰኖች በያሉበት አከባቢ የማህበሩን ተልዕኮዎች እንዲሳኩ ርብርብ
ያደርጋሉ ፡፡
 የዞንና የወረዳ ሴክተር ፎካሎች የአባላት ማፍራት ስራው በአግባቡ እንዲመራ በማድረግ አባሉ
የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እየተወጣ ስለመሆኑ ከመ/ቤቱ የበላይ ኃላፊ ጋር በጋራ እየፈተሸና እየገመገመ
ለወረዳ ፎካል ፐርሰን መረጃ ይሰጣሉ
 ከተቋሙ ሰራተኞች የአባልነት መዋጮ በማህበሩ የገቢ ደረሰኝ እንዲሰበስብ የዞን ተወካይ ለዞን የወረዳ
ተወካይ ለወረዳ ፋ/ኢ/ል/መ/ጽ/ቤት የአባል ዝርዘር ያስተላልፋል፡፡
 የቀበለ ፎካል ፐርሰኖችም በቀበሌው አባላት ማፍራትና በልማት ስራ ዙሪያ ያለውን አፈጻጸም
እያስገመገመ ለወረዳ ሪፖርት በወቅቱ የሚልኩ ይሆናል፡፡
 ከአባላትና ከተለያዩ ገቢ ምንጮች ገቢ በማህበሩ የገቢ ደረሰኝ ይሰበስባል ለወረዳው ያስገባል
 በቀበሌው በልማት ቡድኖች መካከል ጤናማ የልማትና አባላት ማፍራቱን ስራ በንቅናቄ መንገድ
በፉክክር መንፈስ እንዲፈጸም ይሰራሉ የተሻሉትን እውቅና እንዲያገኙ ያድርጋሉ
 በጥቅሉ ይች አጠር ያለች የአደርጃጀት አሰራርና በሰው ሀይል ምደባ ዙሪያ ያለብንን ክፍተት
ለመሙላት የተዘጋጀች ሰነድ በመሆኗ ወደ ተግባር እየተገባ በሚገኝ ተጨማሪ ግብዓት እንደምታዳብሩ
ታሳቢ በማድረግ ለተግባራዊነቱ በጋራ እንዲንረብርብ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
10. የሥራ ባለቤቶችና የባለድርሻዎች ሚና

በልማት ማህበሩ ውጤታማ ስራ ለመምራት የባለድርሻዎች ማለትም የማህበሩ አመራርና ሰራተኞች፣


የመንግስት ባለስልጣኖችና አመራሮች፣ ፎካል ፐርሰኖች፣ በየደረጃ ያለው አጠቃላይ የማህበሩ አባላትና አጋር
ድርጅቶች በሙሉ የጋራ ቅንጅትና ጤናማ የሆነ የሥራ ግንኙነት ሊኖራቸው ያስፈልጋል፡፡
ስለዚህ ከማን ምን ይጠበቃል የሚለውን በአግባቡ በመገንዘብ እያንዳንዱ ባለድርሻ አካላት ድርሻቸውን
በአግባቡ ለይተው በማወቅ የበኩላቸውን ድርሻውን መወጣት ይኖርባቸዋል፡፡
10.1 ከዞን ማህበር ጽ/ቤት ተወካይ የሚጠበቅ ድርሻ

 በየደረጃው ግንዛቤ መፍጠር


 የወረዳ አሠራሩ ከተወካዩ ተቀናጅቶ በሚሰሩት ሁኔታ ላይ የጋራ መድረክ የመፍጠር
 ደረሰኞች ማሳተምና ማሰራጨት
 ወደ ወረዳና ቀበሌ ወርዶ ሥራ መደገፍ
 በየሩብ ዓመቱ የተወካዮች ሪፖርት በዞን ማዕከል እንዲገመገም ማድረግ
 ለየወረዳዎች ፊድባክ መስጠት
 ውጤታማ ሥራ የሠሩትን ለይቶ ማበረታታትና እውቅና መስጠት

10.2 ከወረዳና ከተማ አስተዳደር ተወካይ የሚጠበቅ ሚና

o የአባላት ማፍራት /የመንግስት ሠራተኛው የፔሮል አባል እንዲሆን/ ስራውን በባለቤትነት


ማስተባበር
o የግንዛቤ ክፍተት ባለበት ግንዛቤ መፍጠር
o ደረሰኞች መውሰድና ማሰራጨት
o ቀድመው የተሰጡ ደረሰኞች ከሚመለከተው አካል ጋር በመቀናጀት እንዲመለሱ ማድረግ
o ከአ/አደሩ የሚሰበሰብ ገቢ ለብክነት ሳይዳረግ ፈጥኖ ወደ አካዉንት እንዲገባ ማድረግ
o በየሳምንትና 15 ቀኑ የስራ ሪፖርት በስልክ ማስተላለፍ
o በወር 1 ጊዜ የፅሑፍ ሪፖርት ለዞን መላክ
o በሩብ ዓመት የተደራጀ ሪፖርት በመያዝ በዞን ደረጃ ማስገምገም
o የሚሰጡ የማስተካከያ ሃሳቦች ወስዶ መተግበር
o በወረዳ ደረጃ የሚከናወን የገቢ ማስገኛ ባዛር ሲኖር በባለቤትነት መንቀሳቀስና ጽ/ቤቱ
የሚሰራቸውን ተጨማሪ ተግባራት እንዲያከናውን ይጠብቃል፡፡

11.1 የዞን፣ ወረዳና ከተማ አስተዳደር የዋና አስተዳደርና ከንቲባ ሚና

 ሥራውን በባለቤትነት መምራትና ማስተባበር


 ሁሉንም ተቋማት አባል ማድረግ
 የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረኮች እንዲመቻቹ የማድረግ
 አስፈላጊ በጀት ለማህበሩ መመደብ
 ለማህበሩ የተደራጀ ቢሮና የስራ ቦታ በቋሚነት እንዲኖር ማድረግ
 በማዕከል ደረጃ ተወካይ መመደብና ድጋፍ በሚጠይቅ ጊዜ ድጋፍ መስጠት

11.2 የዞን፣ ወረዳና ከተማ አስተዳደር የአጠቃላይ አመራር ሚና

 ሥራውን በባለቤትነት መምራትና ማስተባበር


 በተቋማቸው ሠራተኛውን አባል ማድረግ
 በሚደግፉት ቀበሌ አርሶና አርብቶ አደሩ አባል እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ መፍጠር
 ተቋማቸውን አባል ማድረግና የአባልነት ግዴታ እንዲወጣ ማድረግ
 የተቋም ፎካል መምረጥና አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ
 የማህበሩን የገቢ ማስገኛ ፕሮግራሞ መደገፍ

11.3 የቀበሌ አመራር


በዋናነት በቀበሌ ዋና አስተዳዳሪ የሚመራና በቀበሌ ሥራ አስኪያጅ ተወካይነት የሚንቀሳቀስ
ሆኖ የሚከተሉትን ተግባራት ያከናውናሉ፡፡
o በቀበሌ ደረጀ ለግብር ከፋዩ አባወራ በነቂስ ስለማህበሩ ግንዛቤ እንዲያገኝ ማድረግ
o ከወረዳና ከተማ አስተዳደር ካርኒ ወጪ አድርጎ መውሰድ
o ገቢውን ማስባሰብና ለወረዳ ተወካይ ገቢ ማድረግ
o ቀደም የተሰራጩ ካርኒዎች እንዲሰበሰቡ ማድረግ
o በቀበሌ ደረጃ ያሉ ተቋማት ቀበሌ አስተዳደሩን ጨምሮ የትምህርት፣ የጤና፣ የመንገድ፣ የግብርናና
መሰል ተቋማት የተቋም አባል እንዲሆኑ በማድረግ ግዴታቸውን እንዲሰራ ማድረግ ይሆናል፡፡

11.4 የት/ቤቶች፣ ግብርና እና የጤና ተቋማት ሚና በቀበሌ ደረጃ


 በተቋማቸው ለሠራተኛው ግንዛቤ መፍጠርና አባል ማድረግ
 ለተማሪዎቻቸው ግንዛቤ መፍጠርና አባል ማድረግ
 ተቋማቸውን አባል ማድረግና የአባልነት ግዴታ እንዲወጣ ማድረግ
 ፎካሉ ድጋፍ በሚጠይቅ ጊዜ ድጋፍ መስጠት
12. የአፈፃፀም ስልት
o የአባላት ማፍራት ሥራውን በቀን በሳምት በ 5 ቀንና በወር የሚከናወንበት አክሽን ፕላን አዘጋጅቶ
በዚሁ መሠረት ሥራውን የመምራት ስልት ቀይሶ በመምራት
o ግንዛቤ መፍጠር ላይ ማተኮርና ለመድረክ የሚመጥኑ መረጃዎች አደራጅቶ በማቅረብ
o የአባላት ማፍራት ሥራውን ከግለሰብ እስከ ተቋም አባል የማድረግ ሥራ በትኩረት እንዲፈፀም
በማድረግ
o ከባለድርሻዎች ጋር ያለን ግንኙነት ጤናማና በቀና አስተሳሰብና መተባበር ላይ እንዲመሰረት በማድረግ
o አብረውን የሚሰሩ ወገኖችን የሥራ ጫና ከግምት ያስገባ የጊዜ አጠቃቀም ስልት ተከትሎ በመሥራት
ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ይታሰባል፡፡

13.የመመሪያው ተፈጻምነትን በተመለከተ

ይህ መመሪያ ለቦርድ ቀርበው ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡

--------- 2024 እ.እ.አ

ጀሙ

You might also like