Professional Documents
Culture Documents
1
1
ቀን_______________
ኢዲስ አበባ፤
እንደሚታወቀው የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት በቀን 15/06/2015 ዓ.ም ደብዳቤ ቁጥር
ፅወዳ/1827/15 በፃፉት ደብዳቤ በኦሮሚያ ክልል ባቱ ከተማ ዋና መንገድ ላይ የብስክሌት መንገድ ለማሰራት
የቦታ ልየታ፤የጨረታ ግዥና ከከተማው መስተዳድር ጋር የጋራ ውይይት ማድረጋቸውንና ለግንባታ ስራው
በዋናነት የኛን ተቋም የሚመለከት መሆኑን በመግለፅ ድጋፍና ትብብር እንድናደርግላቸው ጠይቀውናል፡፡
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በናንተ በኩል በተሰጠን አቅጣጫ መሰረት ግንባታው ወደሚከናወንበት ቦታ ባለሙያዎችን
በመላክ የመስክ ምልከታ ያደረግንና ከመንገድ ደህንነትና መንገድ ፈንድ አገልግሎት ተወካዮች ጋር ውይይት
አድርገናል፡፡
በመሆኑም የብስክሌት መንገዱ ቢገነባ ሊኖረው የሚችል ጠቀሜታና በመንገዱ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን
ችግር ከዚህ እንደሚከተለው ይሆናል፡-
- በተለይ በስተግራ በኩል የሚሰራው የብስክሌት መንገድ የእግረኛ መሄጃ መንገድ (Shoulder)
ሙሉ በሙሉ የሚወስድ በመሆኑ ከተማው ላይ ከፍተኛ የሆነ የትራፊክ መጨናነቅ ሊያስከትል
ይችላል፤
- በስተቀኝ የሚገነባው የብስክሌት መንገድ ቦታው ላይ ባለው ኮብል ንጣፍ ድንጋይ ላይ የሚገነባ
በመሆኑ በቀጣይ የመፈራረስ ችግር ሊያጋጥመው ይችላል፡፡
- በብስክሌት መንገዱ ላይ በሚቀመጡት የአበባ ማስቀመጫዎች (Flower Pot) መካከል ክፍተት
ስለሚኖር ህገወጥ ሞተረኞች፤ ባጃጅና መኪኖች እየገቡ አደጋ ሊከሰት ይችላል፡፡
የመፍትሔ ሀሳቦች፡-
በሌላ በኩል የቀረበው የብስክሌት መሄጃ መንገድ ንድፍ (Drawing) በጥልቀት የተመለከትነው ሲሆን
በኛ በኩል ምንም አይነት ጉድለት ያላገኘንበት መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ከሠላምታ ጋር//
ግልባጭ:-
ፋይል፤