Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 2

ቀን ...................

የመ/ቁ 165381
በፌድራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት
ለን/ስ/ላፍቶ ምድብ 2ኛ የውርስ ችሎት
አዲስ አበባ
አመልካች ፦1. አቶ ልዑል ሰገድ ጉደታ ለማ
ተጠሪ ፦ ወ/ሮ የሺ ጋረደው በላይነህ

በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ 205 እና 154 መሠረት የቀረበ የዕግድ አቤቱታ

አመልካች ወላጅ አባቴ የነበሩት አቶ ጉደታ ለማ ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው ባለቤታቸው የነበሩትን ወ/ሮ የሺ
ጋረደውን ተጠሪ በማድረግ በህይወት ዘመኑ ያፈራው ንብረቶች በውርስ ሀብትነት እንዲጣሩልኝ ማመልከቴ የሚታወቅ
ሲሆን ከእነዚህ ንብረቶች መካከል በባንክ ሊገኝ ይችላል የተባለ ገንዘብ ሲሆን በባንክ በሟች ስም ካለ እንዲታገድልኝ ጠይቄ
ዕግድ መቀበሌ ይታወቃል ። ይሁንና በተጠሪ ወይም ባለቤቱ ስም የሚገኝ ገንዘብ ካለም እንዲጣራልኝ ከጠቀስኩት የባንክ
ገንዘብ የሚካተት ወይም የውርስ ገንዘብ መሆኑ የሚታወቅ ቢሆንም ተጠሪ በስሟ የሚገኝ ገንዘብ ባለመታገዱ በቀላሉ
ልታሸሸው ትችላለች ። ስለሆነም አመልካች የሟች አባቴ የውርስ ሀብት እንዲጣራልኝ ከጠቀስኩት ንብረቶች መካከል
በባንክ ሊገኝ የሚችል ገንዘብ እንዲሁም አክሲዮን በመሆኑ በተጠሪ ስም በባንክ ገንዘብ እንዲሁም አክሲዮን ካለ በቀላሉ
ገንዘቡን ወጪ በማድረግ ተጠሪ ልታሸሸው ስለምትችል በተጠሪ ስም በዳሽን ባንክ ፣ በብርሃን ባንክ ፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
፣ ለንብ ባንክ ፣ ለወጋገን ባንክ ፣ ለዘመን ባንክ ፣ ለአዋሽ ባንክ ፣ ለኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ ፣ ለኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ
፣ ለደቡብ ግሎባል ባንክ ፣ ለአቢሲኒያ ባንክ ፣ ለእናት ባንክ ፣ ለዓባይ ባንክ ፣ ለቡና ባንክ ፣ ለህብረት ባንክ ፣ ለአንበሳ
ባንክ እና ለአዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ የሚገኝ ገንዘብ/የአክሲዮን ገንዘብ የቀረበው የውርስ ይጣራልኝ አቤቱታ ዕልባት
እስኪያገኝ ድረስ ወጪ ሆኖ ክፍያ እንዳይፈፀም የሚያዝ የዕግድ ትዕዛዝ እንዲሰጠኝ በማለት አመለክታለሁ ።

- አቤቱታው በእውነት የቀረበ ለመሆኑ በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ 92 መሠረት አረጋግጣለሁ ።

አመልካች፦
1. አቶ ልዑል ጉደታ ለማ

You might also like