Advanced News

You might also like

Download as doc, pdf, or txt
Download as doc, pdf, or txt
You are on page 1of 3

አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ.

የዜናው ቆይታ:- 7 ደቂቃ

08/09/2016. የመስመር ብዛት:- 38

በ ሶስና አለሙ

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስድስት ኪሎ ካምፓስ ውስጥ ያሉት መፀዳጃ ቤቶች በአብዛኛው የንፅህና ጉድለትና የአጠቃቀም
ችግር እንዳለባቸው ታወቀ።

መፀዳጃ ቤቶቹ ለተማሪዎች ተገቢውን አገልግሎት መስጠት የማይችሉና የተበላሹ መሆናቸውንም ለመገንዘብ
ተችሏል።ዝርዝሩን ሶስና አለሙ አዘጋጅታዋለች።

በአዲስአበባ ዩኒቨርስቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ ተዘዋውረን ባደረግነው ምልከታ በዩኒቨርስቲው ግቢ ውስጥ ካሉት መፀዳጃ
ቤቶች መካከል ለተማሪዎች ግልጋሎት የሚሰጡት አነስተኛ መሆናቸውን እንዲሁም ንፅህናቸው በአግባቡ እየተጠበቀ
እንዳልሆነ ተመልክተናል።

በተማሪዎች የመኝታ አገልግሎትና ቤተመፅሀፍት አካባቢ ያሉትን መፀዳጃ ቤቶች ሄደን የተመለከትናቸው ሲሆን
ለተማሪዎች ግልጋሎት የሚሰጡት መጸዳጃ ቤቶች ላይ ከፍተኛ የሆነ የንፅህና ጉድለትና የአጠቃቀም ችግር
አስተውለናል።

ከተጠቃሚዎች ባገኘነው መረጃ መሰረትም ተማሪዎች በሚኖሩበት ስፍራ ያሉት መፀዳጃ ቤቶች ከፍተኛ የሆነ
የአጠቃቀም ጉድለትና የውሀ እጥረት እንደዳለባቸው ለማስተዋል ተችሏል።

በመማሪያ ህንፃዎች ላይ ያሉት መፀዳጃ ቤቶችም እቃዎቻቸው ያልታደሱና የተሰበሩ፤ ቧንቧዎቹም አገልግሎት
የማይሰጡ እንዲሁም መጥፎ ጠረን ጭምር ያላቸው መሆኑ ተማሪዎች የሚቸገሩበት ጉዳይ ነው።

በማንዴላና በቢሄቪሪያል ኮሌጆች ላይ የሚታየው የመፀዳጃ ቤት ዕጥረትና ንፅህና ጉድለት ደግሞ ከሁሉም ጎልቶ በይበልጥ
ይታያል።ይህም ለተማሪዎች ከፍተኛ ችግር እንደሆነባቸውና ከማንዴላ ህንፃ ወደ ማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ድረስ ሄደው
ለመጠቀም እንደተገደዱ ገልፀውልናል።

ድምፅ 1 መግቢያ (ትንሽ ይቀረዋል...)

መዝጊያ(... ብንሰራ ጥሩ ነው ብዬ አስባለሁ)

ድምፅ 2 መግቢያ (በቃ ሽንት ቤት አይደሉም...)


መዝጊያ (... ሚገባ ሁሉ አይመስለኝም)

ይህ ለምን ሆነ ስንል የአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ ፋሲሊቲ አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ዘላለም መላኩን አነጋግረናቸዋል።

ድምፅ 3 መግቢያ (የኮሪደርና መፀዳጃ ቤቶችን...)

መዝጊያ(... እዛ እንዲጠቀሙ ነው የሚደረገው)

በማንዴላ ህንፃ ውስጥ ስለተቆለፈባቸው መፀዳጃ ቤቶች አቶ ዘላለምን ባነሳንላቸው ጥያቄ ላይ በቂ ምላሽ ሳይሰጡ
አልፈዋል።

ከዚህም በተጨማሪ በተማሪዎች የቤተመፅሀፍት አገልገሎት ህንፃ ላይ መፀዳጃ ቤት አለመኖሩ እንደትልቅ ችግር
ይነሳል።በግቢው ካሉት ሁለት ቤተመፅሀፍት መካከል በአንዱ መፀዳጃ ቤት ቢኖርም ለመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች
አገልግሎት እንደማይሰጥ ታውቋል።

ሁለተኛውና ስመጥሩ ጆን ኤፍ ኬኔዲ ቤተ መጽሐፍትም ለተማሪዎች መፀዳጃ ቤት እንዳላዘጋጀ ተመልክተናል ፡፡ በዚህም


ምክንያት ተማሪዎች በለሊት በሚያነቡበት ጊዜ መፀዳጃ ቤት ለመጠቀም በጨለማ ብዙ ርቀትን ተጉዘው እንደሆነና
ለስርቆትና ለተለያዩ ተያያዥ ችግሮችም እንደሚጋለጡ ለማወቅ ተችሏል ፡፡

ድምጽ 4 መግቢያ ( ያው ዶርሙ በጣም ሩቅ ስለሆነ...)

መዝጊያ (...ከሱ አንፃር በጣም ያስፈራል)

ለአቶ ዘላለም በድጋሚ ባነሳንላቸው ጥያቄ ስለ ቤተ መጽሐፍቶቹ መፀዳጃ ቤቶች ይህን ብለውናል፡፡

ድምፅ 5 መግቢያ ( ዲጂታል ላይብረሪ ላይ አለ...)

መዝጊያ (...ካለ ቼክ የምናደርገው ነው የሚሆነው)

በዲጂታል ቤተ መጽሐፍት ውስጥ ያሉት መፀዳጃ ቤቶች ለተማሪዎች ክፍት እንዲሆን ታዞ ሳለ ለምን አገልግሎት
አልሰጡም ብለን በዲጂታል ቤተ መጽሐፍት የህግ ክፍል ሀላፊ የሆኑትን አቶ ወልደኪዳን ለማን ጠይቀናቸዋል ፡፡

ድምፅ 6 መግቢያ (እርግጥ ነው በፍሎሮች ላይ...)

መዝጊያ (...በጣም ትልቅ ፕሮብሌም ነው የፈጠረብን)

የፅዳት ሠራተኞችም አብዛኛዎቹ በትጋት ስራቸውን ቢያከናውኑም ልክ እንዲሁ ደግሞ ስራቸውን በቸልተኝነት
የሚያልፉ መኖራቸውን ካነጋገርናቸው ሰዎች መካከል ለመረዳት ችለናል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ተማሪዎች ላይ በራሱ የአጠቃቀም ችግር በሰፊው እንደሚስተዋል እኛም በቦታው ተገኝተን
ለመመልከት ችለናል፡፡

በአጠቃላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሚገኙ መፀዳጃ ቤቶች የንፅህናቸው ችግር እንዲቀረፍና ለሁሉም ተደራሽ የሆነ
አገልግሎት እንዲሰጥ መንግስት ተገቢውን በጀት በተገቢው ቦታ እንዲያከፋፍልና የአስተዳደር ሠራተኞችም ጉድለቱን
በየጊዜው በመፈተሽ ቸልተኛ የፅዳት ሠራተኞችንም እንዲሁ በመቆጣጠር ተገቢውን ክትትል ማድረግ እንደሚገባቸው
ከወዲሁ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን፡፡

ለዛሬ የያዝነው የዜና ትንታኔ ያደመጣቹትን ይመስል ነበር፡፡ በሌላ የዜና ትንታኔ እስከምንገናኝ ቸር ሰንብቱ፡፡

###

You might also like