Professional Documents
Culture Documents
Gospel For...
Gospel For...
Gospel For...
ሙስሊም ወዳጄ ሆይ፣ አብርሃም እግዚአብሔርን ታዝዞ ልጁን ሊሠዋለት በተዘጋጀ ጊዜ፣
ለእግዚአብሔር ፍጹም የሆነ የመሥዋዕትነት ፍቅር እንዳለው በማያሻማ ሁኔታ
እንዳረጋገጠ ከእኔ ጋር የምትስማማ ይመስለኛል። እግዚአብሔርም ላንተ ያለውን
ፍጹም ፍቅር እንዲህ ባለ ተመሣሣይ መንገድ አረጋግጧል፤ ይህንንም ታውቅ ዘንድ
ይፈልጋል። ሮሜ 5፥8 ላይ “ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና
እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል።” ተብሎ ተጽፏል።
አንድ ጥያቄ መጠየቅ እንዲፈቀድልኝ በትህትና ልጠይቃቹ፦ እስልምና ውስጥ ያለው
እግዚአብሔር የአብርሃምን የፍጹም ፍቅር ተምሳሌት የሚስተካከል ፍቅር አሳይቶ
ያውቃል? ቁራን የእግዚአብሔርን ፍጹም መስዋዕታዊ ፍቅር ገልጦልናል?
ሀልቬርሰን የተሰኘ የስነ መለኮት ሊቅ አንድ ሀሳብን የሚያጭር ጥያቄ ይጠይቃል። “ድነት
መልካም ስራ ለሚሰሩት እንደ ሽልማት የሚሰጥ ከሆነ፣ የእግዚአብሔር አላማ ደግሞ
የአብርሃምን ታዛዥነት ለመፈተን ብቻ ከሆነ፣ ለምንድነው ታድያ ‛momentous
መስዋዕትነት’ ያስፈለገው? አብርሃም እግዚአብሔርን ታዝዞ እስከሄደበት ድረስ መሄዱ
በቂ አልነበረምን?”
የልጁ አባት የልጁ ልብስ በደም ተጨማልቆ በተመለከተ ጊዜ ደነገጠ። ልጁም ሰው ገድሎ
እንደመጣ እና የሚጮኹዉ የፖሊስ አምቡላንስ እና የጀት ድምጽ እርሱን የሚያሳድድ
እንደሆነ ተናዘዘ። አባቱም ልጁ በደም የተጨማለቀ ልብሱን በፍጥነት እንዲያወልቅ
ነገረው። አባት በደም የተጨማለቀ የልጁን ልብስ ለራሱ ለብሶ ንጹህ የሆነው የራሱን
ልብስ ለልጁ ሰጠውና እንዲለብስ ነገረው። ፖሊስ ቤታቸውን በሀይል ከደበደበ በኋላ
ሰብሮ ገባ። የአባትየው ልብስ በደም እንደተጨማለቀ በተመለከቱ ጊዜ ይዘው አሰሩት።
አባት ልጁ ለሰራው ወንጀል ዋጋ ከፈለ። እየሱስ ኢንዲህ ብሏል፦ “ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ
ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም።” ዮሐንስ 15፥13።
ንጹሕ የሆነው እንስሳ ከምንም ዓይነት ወንጀል ነጻ እንደሆነ ግልጽ ነው። ነገር ግን
አምላክ ኃጢአት በእርሱ ዓይን ምን ያህል ከባድና አደገኛ እንደሆነ ለሕዝቡ
ሊገልጽላቸው ፈልጎ ይህንን አደረገ። ብሉይ ኪዳን ለወንጌል ትምህርቶች መሠረትን
ጥሏል።
( -
ክርስቶስ ኢየሱስ አል ማሲህ፣ ኢሳ ) የተቀባ የእግዚአብሔር መሲህ
ኢየሱስ በቁርኣን ውስጥ ከአሥር ጊዜ በላይ መሲሕ በሚል ማዕረግ ተጠርቷል። ለምሳሌ
ሱራህ 3፡45 ላይ መልአኩ ገብርኤል ለማርያም ተገልጦ የልጇ ስም “ክርስቶስ ኢየሱስ”
(አል-ማሲህ፣ ኢሳ፤ ማለትም፥ መሲህ፣ ኢየሱስ) እንደሆነ ተናግሯል።
የኢየሱስ የትውልድ ቦታ
ከድንግል መወለዱ
በስቅላት መሞቱ
በወዳጆ ስለመከዳቱ
የዚህ ትንቢት ፍጻሜ በአዲስ ኪዳን በማቴዎስ 26፡47-50 ተመዝግቧል (ይህም ኢየሱስ
በይሁዳ ተከድቶ እና ለእስር ተላልፎ የተሰጠበት ሁኔታ ነው)።
እንዲሁም ኢየሱስ ራሱን "የሰው ልጅ" ብሎም ጠርቷል። ይህንንም ያደረገው መለኮት
እንደሆነው ሁሉ ሰውም መሆኑን ግልጽ ለማድረግ ነው፤ ይህም መሲህ መሆኑን ያሳያል።
ነብዩ ዳንኤል "የሰው ልጅ" የተሰኘውን መሲሓዊ ማዕረግ ተጠቅሞ የሚመጣው መሲሕ
መለኮት ስለመሆኑ ትንቢት ተናግሯል
በዚህ ክፍል ዳንኤል በራዕይ "የሰው ልጅ"ን የሚመስል አካል አይቷል፤ ገጽታውም ሰው
የሚመስል እንደሆነ አመልክቷል። በተጨማሪም ይህ ሰው ሉዓላዊ ስልጣን እንደተሰጠው
እና በሁሉም የሚመለክ እንደሆነ አይቷል። ግዛቱም የማያልፍ የዘላለም ግዛት ነው፥
መንግሥቱም የማይጠፋ ነው። ይህ የሰው ልጅን የሚመስል ሰው ብቻ እንዳልሆነና
ከሰው በላይ እንደሆነ ግልጽ ነው። ነቢያት በቅዱሳን ጽሑፎች የሚመጣው መሲሕ
እንዲሁ ነቢይ ብቻ እንዳልሆነና ከነብይ እጅግ የላቀ እንደሆነ በግልጽ ተናግረዋል።
የብሉይም ሆነ የአዲስ ኪዳን ቅዱሳት መጻሕፍት የመሲሑን (የክርስቶስን) መለኮታዊ-
ሰውነት በሚገባ ያስተምራሉ።
በዚህ ክፍል ኢየሱስ ክርስቶስ የብሉይ ኪዳኑ የእግዚአብሔር መገለጥ እውነተኛ መሆኑን
አረጋግጧል። ደቀ መዛሙርቱን ለወደፊት መከራው እና ስቅለቱ አዘጋጅቷል። ስለ
ትንሣኤው ነግሯቸዋል።
የመልካም ዜና ብስራት
የብሉይ ኪዳን ነቢያት የታላቁን መሲሕ መገለጥ በጉጉት ይጠባበቁ ነበር። ከሰው ልጅ
ታሪክ ሁሉ እንዴት ያለ ታላቅ ጊዜ ነው። መልካሙ ዜና ታወጀ! በመጨረሻም አል-
ማሲህ፣ የሰው ሁሉ አዳኝ መጣ። የመሲሑን መወለድ የእግዚአብሔር ቃል “መልካም
ዜና” ሲል ያውጃል። ይህ ታሪክ በወንጌል ውስጥ ተመዝግቧል። በቤተልሔም ሜዳ ላሉ
እረኞች መልአክ ታይቷል፤ የጌታም ክብር በዙሪያቸው አበራ። መልአኩ ይህን ድንቅ
አዋጅ አወጀ።
(
ኢየሱስ ክርስቶስ፣ “የእርሱ ቃል” ቃሊማቱሁ )
የእግዚአብሔር ቃል ዘለአለማዊነት
ውድ አንባቢዎቼ፥ አንድን ንግግር ስትናገሩ ይህ ንግግር ከእናንተ ውስጥ የወጣ ነው፤ ነገር
ግን ያ ራሱ ንግግር አሁንም እናንተ ውስጥ አለ። የእግዚአብሔር ቃል ኢየሱስ
ከእግዚአብሔር ወጥቶ የመጣ ነው፤ ነገር ግን አሁንም በእግዚአብሔር ውስጥ ይኖራል።
ኢየሱስ ዮሐንስ 14፥10 ላይ “እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ አታምንምን? ”
ይላል። እንዲሁም ዮሐንስ 10: 30 ላይ “እኔና አብ አንድ ነን።” ይላል።
ዘለአለማዊ ቃል ሰው ሆነ