Professional Documents
Culture Documents
25
25
የአአትሪኮን ማህበር በ 2015 ዓ.ም የተመሰረተ የግል ማህበር ሲሆን የእንጀራ መጋገር ስራ በመጀመር ሲሰራ
የቆና እና ስራውን በማስፋት የዳቦ ጭርቻሮ ስራ በመጀመር በጠንካራ አባሎቹ ብርታትና ጥንካሬ ለአስር ወር
ሲሰራ ቆይቷል፡፡ ሥራው ብዙ ውጣውረድ የሚጠይቅ እና የቅርብ ክትትል የሚፈልግ ከመሆኑ አንፃር የአባሉን
የስራ ጫና ለመቀነስ እና በድርጅቱ ለሚቀጠሩ ባለሙያዎች ቀልጣፋ የአሰራር ስልት እንዲኖር ለማድረግ፤
ማህበሩ ዓላማውን ከግብ ለማድረስ የሚያስችል የሰው ሃይል፣ ገንዘብ እና ንብረትን በስራ ላይ ማዋል
የሚያስችል የአደረጃጃት መዋቅርና የሰው ሃብት አስተዳደር ስርዓት ሊኖራቸው የሚገባ በመሆኑ፤
ማህበሩ ስራን በአግባቡ ለማቀድ፣ ለማደራጀት፣ ለመምራት፣ ለመቆጣጠር እና አስፈላጊ ውሳኔዎችን በወቅቱ
በመስጠት ውጤታማ እንዲሆን ማስቻል በማስፈለጉ፤
ማህበሩ የሰራተኞችን አደረጃጀት በማዘመን እንደየስራው ስፋት እና ክብደት የሰው ሀይል አስተዳደር ስርዓትን
የተከተለ እንዲሆን ማድረግ በማስፈለጉ፤
ማህበሩ የሰራተኞችን ተጠያቂነትንና ግልጸኝነትን ያሰፈነ አሰራር እንዲኖር ለማስቻል ይህን መመሪያ
አውጥቷል፡፡
ክፍል አንድ
1
ሀ. ማንኛውም በአአትሪኮን ማህበር ውስጥ የሚሰራ ሥራ የማህበሩን አሰራር ተከትሎ የተዘጋጀ የሰው ኃይል
ድርጅታዊ መዋቅር ይኖረዋል፡፡
ለ. በዚህ ክፍል የተዘጋጀውን መመሪያ ማህበሩ የሰው ኃይል ድርጅታዊ መዋቅሩን እና ተግባሩን ሲያሰፋ
ወይም ሲያጠብ በጥናት ላይ ተመስርቶ የሰው ኃይል መዋቅሩን ሊያሻሽለው ይችላል፡፡
2. የአአትሪኮን ማህበር የሰው ሃይል አደረጃጀት መዋቅር በሚዘጋጅበት ወይም በሚሻሻልበት ወቅት
የሚከተሉትን ጉዳዮችን ታሳቢ ማድረግ አለበት፣
3. ማህበሩ የሰው ኃይል ድርጅታዊ መዋቅር በሚያዘጋጅበት ወይም በሚያሻሽልበት ወቅት ባለሙያ ወይም
በሙያው የተሻለ ክህሎት ባላቸው ሰዎች የዳሰሳ ጥናት ተደርጎ በስራ አመራር ኮሚቴ ወይም ቦርድ
ተገምግሞ ትክክለኛነቱ መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡
4. በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 3 ተጠንቶ የጸደቀው የማህበሩ የሰው ኃይል ድርጅታዊ መዋቅር ተግባራዊ
የሚሆነው ከዚህ በታች የተገለጹ ነጥቦችን ማሟላት ይኖርበታል፣
ሀ. የማህበሩ የሰው ኃይል ድርጅታዊ መዋቅር የጥናት ውጤት በጠቅላላ ጉባኤ ከጸደቀ በኋላ፤
ለ. የሰው ኃይል ድርጅታዊ መዋቅር የእያንዳንዱን ሠራተኞች የሥራ መደብ ተጠሪነት፣ መብት፣ ግዴታ፣
የሚያከናውኗቸው ተግባራት እና የደመወዝ ክፍያ መጠን በአንድ ላይ ማካተት ይኖርበታል፡፡
2
ሐ. የማህበሩ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ተጠሪነቱ ለማህበሩ የሥራ አመራር ኮሚቴ ወይም ዋና ስራ አስኪያጅ
ይሆናል፡፡
6. ማህበሩ የሰው ኃይል ለማሟላት ዝርዝር መዋቅር እና የሰው ኃይል በማጥናት ተግባራዊ ማድረግ አለበት፡፡
3
ክፍል ሁለት
7. የማህበሩ ሥራ አስኪያጅ ተጠሪነቱ ለሥራ አመራር ኮሚቴ ወይም ለጠቅላላ ጉባኤ ሆኖ የሚከተሉት
ተግባርና ኃላፊነት ይኖሩታል፡፡
መ. ቢዝነስ ፕላን ወይም የሥራ ዕቅድ፣ በጀትና የስራ መመሪያዎችን አዘጋጅቶ ለሥራ አመራር ኮሚቴ
ወይም ዋና ስራ አስኬያጅ ያቀርባል፣ ሲወሰንም ተግባራዊ ያደርጋል፤
4
ሠ. ሠራተኞችን ይቀጥራል፣ በሠራተኞች አደረጃጀትና አስተዳደር መመሪያ መሠረት ያስተዳድራል፣
ያሰናብታል፣ የሥራ አፈጻጸማቸውን ይገመግማል፤
ረ. ከሥራ አመራር ኮሚቴ አባላት ጋር በመሆን የባንክ አካውንት ይከፍታል፣ በተሰጠው ኃላፊነትና ውክልና
መሠረት ክፍያ ይፈጽማል፤
ሰ. የማህበሩን የሂሳብ ሰነዶች በአግባቡ እንዲያዝና ቢያንስ በወር አንድ ጊዜ ኦዲት እንዲደረግ ያደርጋል፤
ሸ. ማህበሩ በተጠናከረና በተስተካከለ ሁኔታ ሥራውን እንዲያከናውን የሥራ አመራር ኮሚቴውን ያማክራል
የተሻሻሉ የአሠራር ስልቶች እንዲቀየሱ ያደርጋል፡፡
ቀ. የማህበሩ ገንዘብ፣ ሀብትና ንብረት ምርታማነትን ለማሳደግ በአግባቡና በተገቢው መንገድ በሥራ ላይ
መዋሉን ይቆጣጠራል፤
በ. ወቅታዊ የሥራ ሪፖርት ለሥራ አመራር ኮሚቴ ወይም ለጠቅላላ ጉባኤ ያቀርባል፤
ተ. ወቅታዊ የሥራ ሪፖርት እንደ አስፈላጊነቱ የሥራ አመራር ኮሚቴ ወይም ቦርድ በማጸደቅ ሪፖርት
ለሚመለከተው አካል ያቀርባል፤
ሠ. በመጠጥ ወይም አእምሮን የሚያደነዝዝ እጽ ተጠቅሞ በስራ ገበታ ያለመገኘት፤ የማህበሩን የስራ ስዓት
የማክበር፣ እንዲሁም በመደበኛ የስራ ስዓት ከማህበሩ ስራ በስተቀር ሌላ የግል ስራ አለመስራት፤
5
ሰ. የሚመለከተው ኃላፊ ሳይፈቅድ ማንኛውንም ንብረት፣ መሳሪያ ወይም ቁሳቁስ መውሰድ ወይም ለሌላ
አሳልፎ መስጠት ወይም ከማህበሩ ስራ ጋር ላልተያያዘ ተግባር አለማዋል እና ሌሎችም
እንዳይፈጽሙ መቆጣጠር፤
ጋር ይዋዋላል፤
ነ. በማናቸውም ፍ/ቤት ማህበሩ ከሳሽ ተከሳሽ ወይም ጣልቃ ገብ በሚሆንበት ጉዳይ ለሚጠራው
የውጭ ስብሰባ ሁሉ ማህበሩን በመወከል አስፈላጊውን ይፈፅማል፤
ኘ. ጠቅላላ ጉባኤውን ስብሰባ ይጠራል በዕለቱ ጸሀፊ ይወክላል፤
ያሠናብታል፤
ያሳውቃል፤
እንዲካሄዱ ያደርጋል፤
6
ሰ. በስሩ ያሉ ሰራተኞችን በመከታተል ግልጸኝነትና ተጠያቂት እንዲሰፍን ያደርጋል፡፡
ሸ. እንዳስፈላጊነቱ የገበያ ጥናት በማድረግ በግዥ ክፍል የሚገዙ ቁሳቁሶችን የገበያ ጥናት
ያደርጋል፤
ቀ. የሚቀርቡ አቤቱታዎችን እና ቅሬታዎችን ተቀብሎ ያስተናግዳል፣ ተገቢውን ምላሽ ይሰጣል፤
በ. የግዥ እና የወጪ ቅፆችን ያዘጋጃል፤
ይቀጣል።
ዘ. ሰራተኞች በማኅበሩ ንብረት ላይ ወይም በሌላ ሠራተኛ ላይ ጥፋት ወይም ጉዳት ሲያደርስ ወይም
ያስቀምጣል፤
አለበት፡፡
7
መ. በአግባቡ ኃላፊነታቸውን ለማይወጡ ሠራተኞች ማስጠንቀቂያ ይሰጣል፣
ያሠናብታል፤
ያሳውቃል፤
እንዲካሄዱ ያደርጋል፤
ሸ. እንዳስፈላጊነቱ የገበያ ጥናት በማድረግ በግዥ ክፍል የሚገዙ ቁሳቁሶችን የገበያ ጥናት
ያደርጋል፤
ቀ. የሚቀርቡ አቤቱታዎችን እና ቅሬታዎችን ተቀብሎ ያስተናግዳል፣ ተገቢውን ምላሽ ይሰጣል፤
በ. የግዥ እና የወጪ ቅፆችን ያዘጋጃል፤
ይቀጣል።
ክፍል ሦስት
11. በሌሎች ህጎች የተሰጡ መብቶች እንደተጠበቁ ሆነው የማህበሩ ዋና ሥራ አስኬያጅ መብት የሚከተሉትን
ያካትታል፡-
ለ. በዚህ መመሪያና ተፈጻሚነት ባላቸው ሕጎችን መሠረት በማድረግ የመቅጠር የመቅጣት፣ ከሥራ
የማገድ፣ ከሥራ የማሰናበትና በሠራተኛው ላይ ሕጋዊ የሆነ የዲሲፕሊን እርምጃ የመውሰድ፤
8
ሐ. የሥራ መደቦችን የመሰረዝ ወይም የማሻሻል፣ በተጠኑ የሥራ መደቦች ላይ ሰራተኞችን የመመደብ እና
የማሰናበት መብቶች አሉት፡፡
መ. ማጭበርበር፤
9
ሠ. ሠራተኛው ራሱንም ሆነ የሥራ ጓደኞቹን አዳጋ ላይ የሚጥል ወይም የማኅበሩን ጥቅም የሚነካ ሁኔታ
ሲያጋጥመው ወዲያውኑ ለአሰሪው የማሳወቅና በሥራ ቦታ በህይወትና በንብረት ላይ አደጋ
ሲደርስ ተገቢውን ትብብር የማድረግ፤
ረ. አንድ ሠራተኛ በመደበኛ የሥራ ስዓት ከሥራ አካባቢው ላይ ተነስቶ ከመሄዱ በፊት ከቅርብ ኃላፊው
ፈቃድ የመጠየቅ፤
ሰ. በስራ ገበታው ላይ ያልተገኘን ሠራተኛ ሥራ ለማሟላት ከክፍል ኃላፊው ወይም ከበላይ ኃላፊው
የሚሰጠውን ተገቢ የጹሁፍም ሆነ የቃል ትዕዛዝ ተቀብሎ የመፈጸም፤
ቀ. በሠራተኛው ቸልተኝነት ወይም ግዴለሽነት በንብረቶች ላይ ለሚደርስ ጉዳት በዕዳ ተጠያቂ የመሆን፤
በ. የሚመለከተው ኃላፊ ሳይፈቅድ ማንኛውንም ንብረት፣ መሳሪያ ወይም ቁሳቁስ መውሰድ ወይም ለሌላ
አሳልፎ መስጠት ወይም ከማኅበሩ ስራ ጋር ላልተያያዘ ተግባር ማዋል እና ሌሎችም እንዳይፈጽሙ
መቆጣጠር፤
ነ. የፈረቃ ሰራተኛ የቅርብ አለቃው እስካልፈቀደ ድረስ የተረከበውን የማምረቻ እና ሌሎች መሳሪያዎች
ለተተኪ ሰራተኛ ሳያስረክብ አለመሄድ፤
ኘ. ሌላው ሠራተኛ በማኅበሩ ንብረት ላይ ወይም በሌላ ሠራተኛ ላይ ጥፋት ወይም ጉዳት ሲያደርስ ወይም
ሲሰርቅ፣ ሲደባደብ በዝምታ ያለማለፍና ለማኅበሩ ኃላፊዎች የማሳወቅ ኃላፊነት፡፡
አ. በቂ ባልሆነ ምክንያት የምርት ውስንነት ከታየና ድርጅቱ ስጋት ውስጥ ከገባ ይጠየቃሉ፡፡
ለ. የዲሲፕሊን እርምጃዎችና በመሳሰሉት ጉዳዮች አፈጻጸም ሂደት ቅሬታ ካለው ስለአፈጻጸሙ የተወሰዱ
እርምጃዎችን ቀርቦ የመረዳትና የማስረዳት፤
10
መ. አድሎ ከተፈጸመበት ለማኅበሩ ቅሬታ የማቅረብ፣ በጹህፍ ወይም በቃል መልስ የማግኘት፡፡
16.የኦዲተር ኃላፊነት
ሀ. የማኅበሩ ገንዘብና ንብረት አስተዳደር በሕግና በማኅበሩ መመሪያ መሠረት መሆኑን ያረጋግጣል፣
ጉድለቶች ሲኖሩ በጊዜው እንዲታረሙ ያደርጋል፤
ለ. የማኅበሩ የሥራ እንቅስቃሴ በማህበሩ ሕግና መተዳደሪያ ደንብ፣ በወጡ ዕቅዶች መሠረት መካሄዱን
ያረጋግጣል፤
ሐ. በማኅበሩ ስብሰባና ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴዎች ስብሰባ ቃለ-ጉባዔዎች በአግባቡ መያዛቸውን
ያረጋግጣል፤
መ. ዕለታዊ፣ ወርሀዊ እና ዓመታዊ የኦዲት ሪፖርት ለጠቅላላ ጉባዔው ያቀርባል፤ ማነኛውንም የድርጅት
እንቅስቃሴ ኦዲት ያደርጋል፤
ሠ. ሰነዶችን፣ የግዥ እና ወጪ ደረሰኞችን ኦዲት ያደርጋል፤
ረ. እንደ አስፈላጊነቱ ከስራ አስኬያጅ የሚሰጠውን ስራ ይፈጽማል፡፡
11
ቀ. የሂሳብ ሰነዶች በመለየት ይመዘግባል፣ በቅደም ተከተል እንዲደራጅ ያደርጋል፣ በአግባቡ ተጠብቀው
መያዛቸውን ይከታተላል፤
በ. የሂሳብ አያያዝ እና የክፍያ አፈጻጸም በደንብና መመሪያ መሠረት መከናወናቸውን ያረጋግጣል፣
ይከታተላል፤
ተ. ያልተወራረዱ ክፍያዎችን ለይቶ ይከታተላል፣ እንዲወራረዱ ያደርጋል፤
ቸ. የተቋሙን የፋይናንስ አፈጻጸም መግለጫዎችና ሪፖርቶች በማዘጋጀት ለሚመለከተው አካል
በወቅቱ ያቀርባል፤
ኀ. በኦዲት ሪፖርት ግኝት መሠረት የማስተካከያ እርምጃ መግለጫዎች ለኃላፊ ያቀርባል፣ አፈፃፀሙን
ይከታተላል፤
ነ. የስራ ክፍሉ ተግባራት የሚመሩበትን መመሪያዎች እንዲዘጋጁ ያደርጋል፣ ሲፀድቁም በአሰራሩ
መሠረት መፈጸማቸውን ያረጋግጣል፣ በየጊዜው እንዲሻሻሉ ሃሳብ ያቀርባል፤
ኘ. በስራ ክፍሉ ሰራተኞች መካከል አለመግባባት ሲፈጠር ጉዳዩን አጣርቶ ተጠያቂነት እንዲሰፍን
ያደርጋል(የዲስፕሊን ቅጣት እንዲኖር) ያደርጋል፤
አ. ተመላሽ የሆነን ብር በወቅቱ ወደ ማህበሩ አካውንት ያስገባል፡፡
12
ለ. ቡኮውን ስራ አስኪያጁ በሚያስቀምጥለት የጊዜ ገደብ(ሰዓት) በደንብ አሽቶ ያቦካል፣ ያሻል ይወቅጣል፤
ረ. ውሐ ይቀዳል ሮቶ ይሞላል፤
ሸ. ችግሮች ሲኖሩ ለስራ አስኪያጅ ያሳውቃል፤
ቀ. በቸልተኝነት ወይም ግዴለሽነት በንብረቶች ላይ ለሚደርስ ጉዳት በዕዳ ተጠያቂ ይሆናል፤
በ. የሚመለከተው ኃላፊ ሳይፈቅድ ማንኛውንም ንብረት፣ መሳሪያ ወይም ቁሳቁስ መውሰድ ወይም ለሌላ
አሳልፎ መስጠት አይችልም፤
ተ. የማኅበሩን ፈቃድ ሳያገኝ ማንኛውንም የውጭ ሰው ይዞ መግባት አይችልም።
18.3. የአመላላሽ ኃላፊነት
ሀ. እንጀራ ሲወጣ ቆጥሮ አረጋግጦ ይወስዳል፤
ለ. የወሠዳቸውን እቃዎች በወቅቱ ይሰበስባል፤
ሐ. የእንጀራ መሸፈኛ ፌስታሎችን በወቅቱ ያጥባል፤
መ. የተቋሙን ንብረቶች በጥንቃቄ መጠቀም እና መጠበቅ አለበት፤
ሠ. ችግሮች ሲኖሩ ለስራ አስኪያጅ ያሳውቃል፤
ረ. በቸልተኝነት ወይም ግዴለሽነት በንብረቶች ላይ ለሚደርስ ጉዳት በዕዳ ተጠያቂ ይሆናል፤
ሰ.የማኅበሩን ፈቃድ ሳያገኝ ማንኛውንም የውጭ ሰው ይዞ መግባት አይችልም።
18.4. የዳቦ ቤት ሽያጭ ሰራተኛ ኃላፊነት
ሀ. በቀን የተሸጡ ነገሮችን በጊዜው መዝግቦ ያስቀምጣል፤
ለ. ፈጠን ብሎ በማግባባት ይሸጣል፤
ሐ. ዱቤ ከኃላፊው ካልተፈቀደለት በስተቀር ለማንም አይሸጥም፤
መ. በተፈቀደለት ጊዜ እና ሰዓት ብቻ ይወጣል ይገባል፤
ሠ. በመደበኛ የሥራ ስዓት ከሥራ አካባቢው ላይ ተነስቶ የሚሄደው ከቅርብ ኃላፊው ፈቃድ ካገኘ ብቻ ነው፤
ረ. የኃላፊውን ፈቃድ ሳያገኝ ማንኛውንም የውጭ ሰው ወይም ዘመድ ይዞ መግባት አይችልም።
13
የአአትሪኮን ማህበር ወርሀዊ የጠቅላላ ጉባዔ ስብሰባ
ቃለ ጉባኤ
የስብሰባ ቦታ፡- ላፍቶ ክ/ከተማ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ማህበረ ቅዱሳን ቅ/ጽ/ቤት
የስብሰባ ቀን፡- 03/05/2016 ዓ/ም
የስብሰባ ሰዓት፡-ከምሽቱ 1፡30-7፡00
አወያይ፡- አቶ ይታያል ንብረቱ የማህበሩ ሰብሳቢ እና ዋና ስራ አስኬያጅ
በስብሰባው የተገኙ ስም ዝርዝር
1. አቶ ይታያል ንብረቱ………………..…..ዋና ስራ አስኬያጅ
2. አቶ ያስችላል እምቢአለ…………………የዳቦ ቤት ዋና ኦዲተር
3. አቶ ሲሳይ መለሰ ……………….….…..የእንጀራ ቤት ግዥና ፋይናንስ ኃላፊ
14
4. አቶ ተመስገን ሙሉ ……………….......የዳቦ ቤት ም/ስራ አስኬያጅ
5. አቶ ዳኛው ይመር ………………………የእንጀራ ቤት ዋና ኦዲተር
6. አቶ ደርብ ዘውዴ ……………………….የእንጀር ቤት ም/ኦዲተር
7. ወ/ሮ አያልነሽ ዋለ………………………..የዳቦ ቤት ም/ኦዲተር
8. ወ/ሪት አገርነሽ ያንበል………….………..የዳቦ ቤት ግዥና ፋይናንስ ኃላፊ
9. ወ/ሮ መቅደስ መኳንት………….………..አባል
የስብሰባው አጀንዳዎች
አጀንዳ 1:- የሥራ መዋቅርን እና መመሪያን ለማጽደቅ ጠቅላላ ጉባዔውን በማወያየት ግብዓቶችን ማካተት
በዚህ አጀንዳ ላይ የተነሱ አስተያየቶች፣ የተደረገ ውይይት እና ውሳኔዎች
ውይይቱን አስጀምረዋል፡፡
ማህበሩ ሥራ ከመጀመሩ በፊት የመመስረቻ ጽሁፍ(ደንብ) በማውጣትና በማጽደቅ ሲተዳደርና
ሲሰራ ቆይቷል፡፡ ይሁን እነጂ ደንቡ እናዳለ ሆኖ የሥራ መመሪያ በማውጣት ማህበሩ ስራን
በአግባቡ ለማቀድ፣ ለማደራጀት፣ ለመምራት፣ ለመቆጣጠር እና አስፈላጊ ውሳኔዎችን በወቅቱ
በመስጠት ድርጅቱን ውጤታማ ለማድረግ መዋቅር እንዲጸድቅ ተደርጓል፤
ከስራ ዝርዝር አንፃር ሥራን መከፋፈልና በትብብር መስራት ቢቻል የሚል ሀሳብ ተነስቷል፡፡
ሁሉም የራሱ የሆነ መክሊት እንዳለው እና በመክሊቱ መሰረት እሄን እሰራለሁ ብሎ ኃላፊነት
ቢወስድ የሚበረታታ መሆኑ ተገልፆ፤ በተዘጋጀው መዋቅር መሰረት በዕለቱ ለተገኙ አባላት
ኃላፊነት ተሰጥቷል፤
ኃላፊነቱን ያልተወጣ ማነኛውም ሰው በጠቅላላ ጉባኤው እንደሚቀጣ ተወስኗል፡፡
15
እንጀራ ቤት ላይ የሚሰሩ ሰራተኞች የተሰጣቸውን ሥራ አውቀው ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ በማድረግ የተሻለ
የሥራ እንቅስቃሴ መኖር እንዳለበት የተነሳ ሲሆን በዚህም ላይ ኃላፊነታቸውን ለማይወጡ ሰራተኞች እርምጃ
መወሰድ እንዳለበትና የተሻለ የስራ እንቅስቃሴ መደረግ እንዳለበት ሥምምነት ላይ ተደርሷል፡፡
16