Download as doc, pdf, or txt
Download as doc, pdf, or txt
You are on page 1of 21

የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

መግቢያ

የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋም ሥራ አጥነትን ከማስወገድ አንጻር ያለዉ ሚና እጅግ ጉልህ ከመሆኑ በተጨማሪ
የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ድጋፍ የሚሰጠውም ሆነ ለመካከለኛና ከፍተኛ ተቋሞች የሚያስፈልገው ብቃት ያለው
የሰለጠነ የሰው ኃይል የሚመነጨውም ከዚሁ ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ሥርዓቱ እንደሆነ የተቀረጹ የልማት
ስትራተጂዎቻችን ያስቀምጣሉ። የስትራቴጂው ግቦችም በሃገሪቷ ብቁ የሰለጠነ የሰው ሀይል በማፍራት እና በኢንዱስትሪ
ኤክስቴንሽን አገልግሎት የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ተወዳዳሪነት በማሳደግ ድህነትን ከሀገራችን ማስወገድና
ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋጽኦ ማድረግ ናቸው። ከዚህ ጋር በተያያዘ በከተማም ሆነ በገጠር ለሚገኙ ሥራ አጥ
ዜጎች የሥራ ገበያ ፍላጎትን መሰረት ያደረገ አጫጭር ሥልጠና በመስጠት ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር ከሚተኮርባቸው ዋነኛ
ግቦች አንዱ ነው።

የትኛዉም የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ማሠልጠኛ ተቋማት ከተወዳዳሪዎቹ ልቆ እንዲገኝ ከሚያደርጉት ነገሮች ዋነኞቹ በቂ
ቴክኒካል ክህሎትና የኢንተርፕሪነርሽፕ ባህሪይ የተላበሰ የሰው ሐይል እንዲሁም ምርጥ ቴክኖሎጂና የጥራትና ምርታማነት
ማሻሻያ አሰራር ሲኖር ነው፡፡ ይህ አሰራር ከሌለ በስተቀር ማንኛውም አይነት ግብአት፣ መሰረተ ልማትና ዘመናዊ አደረጃጀት
ቢኖርም ለትርፋማነትና ለተወዳዳሪነት ሊያበቁ እንደማይችሉ የተለያዩ የጥናት ውጤቶች ያመለክታሉ።

በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ስትራቴጂ ላይ በግልጽ እንደሚታየው ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን
ለማልማት ከተቀመጡት የድጋፍ ማእቀፎች ውስጥ አንዱ ለኢንተርፕራይዞቹ ብቃት ያለው የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን
አገልግሎት መስጠት ነው። ይህ አገልግሎት የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ችግር በፍላጎት ላይ ተመስርቶ ክፍተትን
የለየና የተሟላ መረጃ የማደራጀትና ስልጠናና ምክር፣ የቴክኖሎጂ ልማት፣ ምርጥ ተሞክሮ ቅመራና ማስተላለፍን የሚያካትት
ድጋፍ ነው፡፡

1. የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት ትግበራ መነሻ

በቴ/ሙ/ት/ስ/ ዘርፍ ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚሰጠው የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን


አገልግሎትም የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት የድጋፍ ፓኬጁ ሲሆን ፓኬጁ አራቱን ድጋፎች (የቴክኒካል ክህሎት
አቅም ልማት፣ የቴክኖሎጂ አቅም ልማት፣ የስራ ፈጣሪነት አቅም ልማት እና የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ
አሰራር) ባካተተ መልኩ ተግባራዊ በማድረግ በገበያ ላይ ተወዳዳሪነታቸውን ማሳደግ ይገባል፡፡

በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ትግበራው ሂደት የተገኙ ምርጥ ተሞክሮዎችን ቀምሮ በማስፋት የአገልግሎቱን
ተደራሽነት በማረጋገጥ ኢንተርፕራይዞቹን ወደሚቀጥለው የዕድገት ደረጃ ለማሸጋገር እንዲቻል

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-1


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

የኤክስቴንሽን አገልግሎቱን አሰጣጥ በማጠናከር ነባር አንቀሳቃሾች እንዲመዘኑ ከተመዘኑት ውስጥ መሪ


መዛኞችን በማፍራት እንዲሁም ኢንተርፕራይዞችን የምዘና ማዕከል እንዲሆኑ ለማድረግ በጋራ ተቀናጅቶ
መስራት ያስፈልጋል፡፡

በመሆኑም የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ተወዳዳሪነታቸውንና ምርታማነታቸውን አሁን ካለበት ደረጃ በተሻለ ሁኔታ
ለማሳደግ እንዲቻል ይህ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር አገልግሎት ድጋፍ ማስተግበሪያ ማንዋል
ተዘጋጅቷል፡፡

1.1 የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አስፈላጊነት

አገራችን እየተከተለች ያለችው ከግብርና መር የኢኮኖሚ ስርአት ወደ ኢንዱስትሪው ክፍለ ኢኮኖሚ ለሚደረገው ሽግግር
የመሪነቱን ሚና እንደሚይዝ ታሳቢ ተደርጎ እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ ይገኛል፡፡

የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር አገልግሎት ድጋፍ የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን


ችግር የለየና በፍላጎት ላይ የተመሠረተ የተሟላ መረጃ የማደራጀትና የመስጠት፣ ሥልጠናና ምክር፣
የቴክኖሎጂ ልማት፣ ግብይት፣ ምርጥ ተሞክሮ ቅመራና ማስተላለፍን የሚያካትት ድጋፍ ነው፡፡ የኢንዱስትሪ
ኤክስቴንሽን አገልግሎት በኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂው በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት
የኢንተርፕራይዞችን ችግሮች በጥናት ላይ ተመስርቶ በቅድሚያ በመለየት ችግር ፈቺ የሆነ መፍትሄ በሚሰጥ
መልኩ በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት እየተከናወነ ይገኛል፡፡

ይህም አገልግሎት በአራት ማዕቀፎች እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን እነዚህም፡-

1. የካይዘን /የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ/ ድጋፍ፣

2. የቴክኒካል ክህሎት ድጋፍ፣

3. የቴክኖሎጂ ድጋፍና

4. የኢንተርፕርነርሽፕ ድጋፍ ናቸው፡፡

1. የካይዘን /የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ/ ድጋፍ፡- ይህ ድጋፍ የሚሰጠው ጥቃቅንና አነስተኛ


ኢንተርፕራይዞች ብክነትን በማስወገድ፣ ወጪን በመቀነስና የስራ ቦታን አመቺ በማድረግ ቀጣይነት ያለው
የምርታማነትና የጥራት መሻሻል እንዲያመጡ ለማስቻል ነው፡፡

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-2


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

2. የቴክኒካል ክህሎት ድጋፍ፡- ይህ ድጋፍ የሚደረገው የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች


በፍጥነትና በየጊዜው ከሚፈጠሩ የቴክኖሎጂና የገበያ መለዋወጥ ምክንያት የሚያጋጥሟቸውን የቴክኒካል
ክህሎት ክፍተቶች ለመሙላት ነው፡፡

3. የቴክኖሎጂ ድጋፍ፡- ይህ ድጋፍ የሚደረገው ደግሞ ለአገራችን ነባራዊ ሁኔታ የሚስማማውንና ተመርጦ
መቶ ፐርሰንት የተቀዳውን ቴክኖሎጂ በመውሰድ ውጤታማ የቴክኖሎጂ አብዢዎች እንዲሆኑና በቴክኖሎጂ
ሽግግር ስራ ብቁ ተዋናኝ እንዲሆኑ ለማስቻል ነው፡፡

4. የአንተርፕሩነርሺፕ አገልግሎት ድጋፍ፡- ይህ ድጋፍ የሚሰጠው ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች


የዘመናዊ ንግድ አሰራርን እንዲተገብሩና ተወዳዳሪ ሆነው እንዲቆዩ ለማድረግ ሲሆን በተጨማሪም ዘርፉ
በከተሞች በዋነኝነት የስራ እድልን በመፍጠር እነዚህ ኢንተርፕራይዞች ለኢንዱስትሪ ልማት መሰረት መጣል
እንዲችሉ ነው፡፡

1.2 የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ዓላማ


1.2.1 አጠቃላይ ዓላማ

ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት በመስጠት በገበያ ውስጥ


በአገልግሎት/ በምርት ጥራት፣ በቴክኖሎጂ፣ በምርታማነት፣ በአሰራርና በዋጋ ተወዳዳሪና ትርፋማ እንዲሆኑ፤ ቀጣይነት
ባለው ሁኔታ የላቀ ለውጥ እንዲያመጡ፣ ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል እንዲፈጥሩና ገቢያቸው እንዲሻሻል ማድረግ፡፡

1.2.2 ዝርዝር ዓላማዎች

 የጥ/አ/ኢንተርፕራይዞች የመስሪያ ቦታቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ማስቻል፣


 የኢንተርፕራይዞችን የምርት ጊዜ ማሻሻልና ምርታማነታቸውን ማሳደግ፣
 የማያቋርጥ የምርትንና አገልግሎት የአመራረት ኡደትን ማሻሻል፣
 የጥ/አ/ኢንተርፕራይዞችን የምርት ወጪን በመቀነስና ጥራትን በመጨመር ትርፋማነታቸውን
ማሳደግና የደንበኛን ፍላጎት ሙሉ ለሙሉ ማርካት፣
 ምርጥ ተሞክሮዎችን በመቀመር የጥ/አ/ኢንተርፕራይዞችን ክፍተት ከብቃት አሃድ ጋር በማዛመድ
ተግባር ላይ እንዲያውሉ በማድረግ የምርታማነታቸውንና የተወዳዳሪነታቸውን አቅም ማሳደግ፣
 ከአገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ ጋር የተጣጣመ የቴክኖሎጂ መረጣና መቶ ፐርሰንት የቴክኖሎጂ መቅዳት ስራ
በመስራት ለጥ/አ/ኢንተርፕራይዞች ማሸጋገር፣
 የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች አንቀሳቃሾች የኢንተርፕሪነሪያል አመለካከታቸውን፣ እውቀታቸውንና
ክህሎታቸውን መገንባት፣

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-3


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

 የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ዘመናዊ የሂሳብ አያያዝ ስርዓትን እንዲተገብሩ በማድረግ ትርፋማነታቸውን
እንዲጨምሩ ማስቻል፣
 ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የገበያ ልማት እውቀትና ክህሎት እንዲያዳብሩ በማገዝ በገበያ ላይ በምርት
ጥራት፣ ዋጋና አቅርቦት ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ማስቻል፣

1.3 የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት መርሆዎች


1. በገበያ ፍላጎት የሚመራ፣ የተቀናጀና የተዋሃደ የኢንዱስትሪ ና ቴክኖሎጂ ሽግግር አገልግሎት
መስጠት፤

2. የቴክኖሎጂ አቅምን መገንባት ለኢኮኖሚ እድገት ቁልፍ መሳሪያ መሆኑን አምኖ መተግበር፤

3. የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርኘራይዞች እድገትና ጥቅም የእኔም ጥቅም ነው ብሎ በማመን


መንቀሳቀስ፤

4. የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርኘራይዞች መፈልፈያና


የቴክኖሎጂ ሽግግር ማእከላት እንዲሆኑ ማድረግ፤

5. ለነባርና ሞዴል ኢንተርኘራይዞች ቅድሚያ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር


አገልግሎት መስጠት እንዳለበት አምኖ መንቀሳቀስ፤

6. ግልጽነት፣ ተጠያቂነትና ታማኝነት የተላበሰ አገልግሎት መስጠት፣

1.4 የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ትርጓሜና ድጋፍ የማስተግበሪያ ሥልቶች


1.4.1 የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ትርጓሜ

“ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ ማለት የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ችግር በፍላጎት ላይ ተመስርቶ
የለየና የተሟላ መረጃ የማደራጀትና የመስጠት፣ ስልጠናና ምክር፣ የቴክኖሎጂ ልማት፣ ግብይት፣ ምርጥ ተሞክሮ ቅመራና
ማስተላለፍን የሚያካትት ድጋፍ ነው፡፡”

1.4.2 የማስተግበሪያ ሥልቶች

 የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ/ KAIZEN/ አቅም ግንባታ


 የቴክኒካል ክህሎት አቅም ግንባታ
 የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታና
 የኢንተርፕርነርሽፕ አቅም ግንባታ ሲሆኑ ሁሉም ድጋፎች መሰረት የሚያደርጉት
በአገር አቀፉ የሙያ ደረጃ ላይ የተቀመጡትን የብቃት አሀዶች ነው።

1.4.2.1 የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ /KAIZEN/ አቅም ግንባታ


የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ /KAIZEN/ አቅም ግንባታ ማለት ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በዕለት
ተዕለት የስራ እንቅስቃሴዎቻቸው የማያቋርጥ የምርታማነትና የጥራት ለውጦች እንዲያመጡ የሚያስችላቸው የአቅም
ግንባታ ስራ ማለት ነው፡፡

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-4


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

የካይዘን (KAIZEN) አስተሳሰብ የተጀመረውም ሆነ በስፋት ስራ ላይ የዋለው በጃፓን ሲሆን የተገነባውም ከሁለት የጃፓን
ቃላት ነው፡፡ እነርሱም ካይ (KAI) እና ዘን (ZEN) ናቸው፡፡ ካይ ማለት ለውጥ ማለት ሲሆን ዘን ማለት ደግሞ መልካም
(ጥሩ) ማለት ነው፡፡ አጠቃላይ የቃሉ ፍቺም የማያቋርጥ መልካም ለውጥ በሚለው የአማርኛው ቃል ሊመነዘር ይችላል፡፡ ይህ
የማያቋርጥ መልካም ለውጥ በአንድ ድርጅት/ተቋም ውስጥ በሚከናወነው የእለት ተእለት የስራ እንቅስቃሴ በምርቱና
በአገልግሎቱ የሚታይ ይሆናል፡፡

የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ ድጋፍ አገልግሎት መነሻ የሚያደርገው በአገሪቱ የሙያ ደረጃዎች ላይ
በተቀመጡት የካይዘን /የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ/ የብቃት አሀዶችና በነዚህ ስር ባሉ ዝርዝር ስራዎች ላይ
ነው፡፡

ደረጃ 1 (Level I): የአምስቱን “ማ” ዎችን የአሰራር ስርአቶች መተግበር (Apply 5s

Procedures)

 የጥራት ስርአት ግንዛቤን ማጎልበት (Develop understanding of quality system)


 የሚፈለጉትን እቃዎች ከማይፈለጉት ማጣራት (Sort needed items from unneeded items)
 የተለዩትን እቃዎች በአግባቡ ማስቀመጥ (Set workplace in order)
 የስራ ቦታን ማፅዳት (Shine work area)
 ከላይ የተከናወኑትን ተግባራት ማስቀጠል (Standardize activities)
 አምስቱ “ማ” ዎችን ስርአት አድርጎ ማዝለቅ (Sustain 5S system)
ደረጃ 2 (Level II) ፡ ቀጣይነት ያለውን የማሻሻያ ሂደቶችን መተግበር (Apply
Continuous improvement processes (KAIZEN)
 በእለታዊ የስራ ተግባራት የጥራት ስርአት ተፈላጊውን እርካታ ማምጣት (Satisfy quality system
requirements in daily work)
 ለውጤታማ ተግባር መልካም አጋጣሚዎችን መተንተን (Analyze opportunities for corrective
and/or optimization action)
 ለውጤታማ ተግባር መልካም አጋጣሚዎች ስራ ላይ እንዲውሉ ሀሳብ ማቅረብ (Recommend
corrective and/or optimization actions)
 መልካም አጋጣሚዎች ስራ ላይ በሚውሉበት እንቅስቃሴ ላይ ተሳትፎ ማድረግ (Participate in the
implementation of recommended actions)
 ቀጣይነት ያለውን የማሻሻያ ስትራቴጂዎችን የማጎልበት ስራ ላይ ተሳትፎ ማድረግ (Participate in
the development of continuous improvement strategies)
ደረጃ 3 (Level III) ፡ የጥራት ስርአትና ቀጣይነት ያለውን የማሻሻያ ሂደቶችን ማስጠበቅ

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-5


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

(Maintain quality system and continuous improvement processes)


 በስራ ቦታ ላይ የጥራት ስርአት መዋቅር መዘርጋትና ማጎልበት (Develop and maintain quality
framework within work area)
 የጥራት ሰነድን በአግባቡ መጠበቅ (Maintain quality documentation)
 ደረጃቸውን የጠበቁ የአሰራር ደንቦችን ተግባራዊ የሚደረጉበትን ሁኔታ ማመቻቸት (Facilitate the
application of standardized procedures)
 በጥራት የአሰራር ስርአቶችና የስራ ማሻሻያ ሂደቶችን ላይ ስልጠና መስጠት (Provide training in
quality systems and improvement processes)
 የስራ አፈፃፀምን መከታተልና መገምገም (Monitor and review performance)
 ቀጣይነት ያለው የስራ ማሻሻያ ሂደትን መገንባት (Build continuous improvement process)
 የስራ ማሻሻያ መልካም እድሎችን ማመቻቸትና መለየት (Facilitate the identification of
improvement opportunities)
 አግባብነት ያላቸውን የጥራት ስርአት ክፍሎቸ መገምገም (Evaluate relevant components of
quality system)
ደረጃ 4 (Level IV) ፡ ቀጣይነት ያለው የስራ ማሻሻያ ስርአትን መምራት (Manage
Continuous improvement system)
 ፕሮግራሞችን፤ስርአትችንና ሂደቶችን መገምገም (Review programs, systems and processes)
 ቀጣይነት ላለው የስራ ማሻሻያ ስርአት አማራጮችን ማጎልበት (Develop options for continuous
improvement)
 አዳዲስና ውጤታማ የስራ ሂደቶችን መተግበር (Implement innovative processes)
ደረጃ 5 (Level V) ፡ ቀጣይነት ያለው የስራ ማሻሻያ ስርአትን መተግበር (Implement
Continuous improvement system)
 ወቅታዊ የሆነ የውሰጥ አሰራር ማሻሻያ ስርአት መለኪያ መዘርጋት (Establish parameters of
current internal improvement system)
 የላቀ ለውጥ የሚያመጣ አሰራር ማሻሻያ ስርአት መለየት (Distinguish breakthrough
improvement processes)
 ቀጣይነት ያለው የስራ ማሻሻያ ተግባርን ማጎልበት (Develop continuous improvement practice)
 ወቅታዊ የሆነ የውጭ አሰራር ማሻሻያ ስርአት መለኪያ መዘርጋት (Establish parameters of
current external improvement system)

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-6


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

 ቀጣይነት ያለው የእሴት ማሻሻያ ሂደቶችን ለማጎልበት መልካም አጋጣሚዎችን ማሰስ (Explore
opportunities for further development of value stream improvement processes)
 ከማሻሻያ ስትራቴጂ ጋር የሚጣጣሙ የአሰራር ስርአቶችን መገምገም (Review systems for
compatibility with improvement strategy)
 የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ/ ድጋፍ ተግባራዊ ስናደርግ መከተል ያለብን የአተገባበር ሂደት፡-

ውጤታማ የሆነ የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ ስርዓትን በኢንተርፕራይዞች ስንተገብር ከዚህ በታች
የተዘረዘሩትን የአተገባበር ሂደቶችን መከተል አለብን፡፡

 ካይዘን ከመተግበሩ በፊት የኢንተርፕራይዙን ነባራዊ ሁኔታ የሚገልፁ መረጃዎችን በፅሁፍ፣ በቁጥር፣
በፎቶ፣በቪዲዮና ነባራዊ የስራ ፍሰትን የሚገልፅ ንድፍ በሚገባ ማዘጋጀትና መያዝ
 ከመረጃው በመነሳት ዋና ዋና ችግሮችን ከላይ ከተገለፁት ነጥቦች አንጻር መለየትና የችግሩን መንስኤ
መተንተንና ማደራጀት፣
 የተለዩትን ችግሮች በምን ያህል አሁን ካለው በጥራትና ምርታማነት ፍልስፍናና መሳሪያዎች
በመጠቀም ማሻሻል እንደሚቻል ግብ ማስቀመጥ፣
 ለተለዩት ችግሮች መፍቻ/መፍትሄ ሊሆኑ የሚችሉትን መሳሪያዎችና አሰራሮች መምረጥና ለድርጅቱ
በሚሆን መልኩ ማዘጋጀት፣
 የተዘጋጁትን የመፍትሄ እርምጃዎች/መሳሪያዎች ተግባራዊ ለማድረግ ዝርዝር የትግበራ እቅድ
ማዘጋጀት
 የተመረጠውን የመፍትሄ እርምጃ መተግበር፣
 የትግበራውን አፈጻጸም ከተቀመጠው ግብ አንጻር ማወዳደር፤ ይህ ማለት ምን ያህል ሰዓት እንደ
ተሻሻለ፣ በቀን የሚመረተውን ምርት ከበፊቱ ምን ያህል እንደጨመረ፣ ምን ያህል የማምረቻ ወጪን
እንደቀነሰ፣ በምርት ጥራት የጨመረ የደንበኛ ብዛት፣ የተገኘን የቦታ ስፋትና አጠቃቀም፣ጠፍቶ የተገኘ
ንብረት፣ የጨመረ የሽያጭና የገቢ መጠን ከበፊቱ አፈጻጸም አንጻር፣ ሰራተኞቹ ምን ያህሉን ሰዓት
እሴት በሚጨምር ስራ ላይ እንደሚያሳልፉ፣ የስራ ቦታ ደህንነት በመጠበቁ የቀነሰ ወጪና ወዘተ…
 ከላይ ከተገለጹት ነጥቦች በመነሳት የተገኘውን ለውጥ/ልዩነት ከበፊቱ አንጻር በማስላት ወደ ገንዘብ
መለወጥ፣

 ቀጣይነት ያለው የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ ሰሌዳ /KAIZEN BOARD/ ዝግጅት፡

የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ/ማትግያ ስርአት ሰሌዳ/KAIZEN BOARD/ የካይዘን ቀጣይነት ማረጋገጫ


ሰሌዳ ሲሆን እያንዳንዱ የኢንተርፕራይዙ ሰራተኛ ብቃቱ እየተገመገመ ያሉበትን የክህሎት ክፍተት እየታየ

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-7


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

የሚሞላበት፣ ምርታማነትን ለማሳደግም ሆነ የአገልግሎት ጥራትን ለማስጠበቅ የማሻሻያ ሀሳቦች


የሚንፀባረቁበት እንዲሁም የተለያዩ ችግሮች ለመፍትሄ የሚቀርቡበትና በተግባር የሚፈተሽበት የካይዘን
ማሻሻያ/ማትጊያ ስርአት ነው፡፡

የጥራትና ምርታማነት ማሻሻያ ሰሌዳ /KAIZEN BOARD/

የሰራተኞች የክህሎት መገምገሚያና ማብቂያ ስኬት


ተ. ዝርዝር ክፍተት ምርመ
ቁ ስራዎ አለ ክፍተት ራ ጥሩ አፈፃፀም ያሳየ የሰራተኛ ምስል
ች የለም
1
2

ዝርዝር ስራዎች 1 2 3 4 5

ሰራተኛው ስም

ችግር/ሀሳብ የመፍትሄ ሀሳብ


ሀሳብ ሀሳብ መፍትሄ
1 2 1
አንድ ሳምንት>>> አንድ ሳምንት>>>

ችግር 1 ችግር 2 መፍትሄ 2

1.4.2.2 የቴክኒካል ክህሎት አቅም ግንባታ

የቴክኒካል ክህሎት አቅም ግንባታ ማለት ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በገበያ ላይ ተወዳዳሪ እንዳይሆኑ
የሚያደርጓቸውን የክህሎት ክፍተቶችን ነቅሶ በመለየት እነዚህን ክፍተቶች ሊያስወግድላቸው የሚያስችል የአቅም
ግንባታ ስራ ነው። የተለየ የቴክኒክ ክህሎት ክፍተት ሳይኖር የክህሎት አቅም ግንባታ ፕሮግራሞችን ማቀድና
ማከናወን እንደ ብክነት ሊቆጠር ይገባል። ሰራተኛው ከፕሮግራሙ ባገኘው ክህሎት የሚያስመዘግበው
ምርታማነት ለአቅም ግንባታው ከዋለው ሀብትና በክህሎት አቅም ግንባታ ፕሮግራሞች ላይ ለመሳተፍ ከስራ

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-8


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

ገበታው በተለየበት ጊዜ ባለማምረቱ ምክንያት ከሚከሰቱት ወጪዎች /opportunity costs/ እና ሌሎችም


ግብአቶች በላይ መሆን ይኖርበታል።

ሀ. የቴክኒካል ክህሎት አቅም ግንባታ ድጋፍ ከብቃት አሀዶችና ዝርዝር የስራ ተግባራት

ጋር የማስተሳሰር ሂደት

የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን የቴክኒካል ክህሎት ድጋፍ አሰጣጥ በአገልግሎት ተቀባዩ ምርጫ መሰረት
በአገልግሎት ሰጪ ክፍተቶቹ ከተለዩ በኋላ ከደረጃ አንድ እስከ ደረጃ አምስት በተለያዩ ሙያዎች ካሉት የሙያ
ደረጃ የብቃት አሀዶች እና ዝርዝር ስራዎች ጋር በማዛመድ ክፍተቶቹ የሚሞሉና ብቃታቸው በምዘና
የሚረጋገጥ ሲሆን ዝርዝር አተገባበሩ በሚከተለው ቅደም ተከተል ይሆናል፡

1. የአንቀሳቀሹን የቴክኒካል ክህሎት ክፍተት መለየት


2. የተለዩ ክፍተቶችን መሙላት የሚያስችል የብቃት አሃድ መምረጥ
3. የተመረጠውን የብቃት አሃድ ሊያስጨብጥ የሚችል የስልጠና መርሀ ግብር ማዘጋጀት፣
4. የስልጠና መርሀ ግብሩን ለመተግበር የሚያስችል ዝግጅት ብቃታቸው በተረጋገጠ አሠልጣኝ ወይም
ባለሙያ ማድረግ
5. መርሀ ግብሩን ብቃቱ በተረጋገጠ አሠልጣኝ ወይም ባለሙያ የቴክኒካል ክህሎት ክፍተት ለታዩባቸው
አንቀሻቃሾች መስጠት፣
6. የቴክኒካል ክህሎት ክፍተቱን መሙላት የሚያስችል አቅም መፈጠሩን በምዘና ማረጋገጥ፣
7. የቴክኒካል ክህሎት አቅም ግንባታውን ውጤት መገምገም፡ የቴክኒካል ክህሎት አቅም ግንባታ ዋና
የማስፈጸሚያ ስልት የስልጠና ፕሮግራሞችን በማዘጋጀትና በመስጠት ነው። የስልጠናን ፋይዳ ደግሞ
ከታለመለት ግብ ስኬታማነት አንጻር መገምገም ያስፈልጋል፡፡

ለ. የቴክኒካል ክህሎት አቅም ግንባታ አተገባበር ስልት

ያለንን ሀብት በአግባቡ ስራ ላይ ለማዋልና የአቅም ውስንነትን ትኩረት ውስጥ በማስገባት የክህሎት አቅም
ግንባታ ድጋፎችን በምናካሄድበት ወቅት በአካባቢያችን የትኩረት ኢንዱስትሪዎች መሰረትና
በኢንተርፕራይዞች ውስጥ ባሉ ለተወዳዳሪነት ወሳኝ በሆኑ የስራ ሂደቶች ላይ በሚያጋጥሙ የክህሎት
ክፍተቶች ላይ ማተኮር ይኖርብናል።በተጨማሪም በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የእድገት ደረጃ
መሰረት ትኩረት በማድረግ የአቅም ግንባታውን ማካሄድ ስልታዊ ጠቀሜታ እንዳለው ይታመናል።

የቴክኒካል ክህሎት አቅም ግንባታን ቅድሚያ አሰጣጥ ከኢንተርፕራይዞች ፍላጎትና ካለው የክህሎት ደረጃና
ከትኩረት ዘርፉ ወሳኝነትና አስፈላጊነት አንጻር ለመገምገም ይቻል ዘንድ እያንዳንዱን ስራ ከአስቸጋሪነት
/difficulty፣ ከአስፈላጊነት /importance፣ ከድግግሞሽ /frequency (DIF) አንጻር መተንተንና ቅድሚያ
የሚሰጣቸውን መወሰን ያስፈልጋል። ይህም ውስን ሀብትን በማያስፈልጉ የስልጠና ፕሮግሮሞች ላይ
እንዳናባክንና በተወሰኑ ችግሮች ላይ ብቻ በማተኮር ውጤታማ እንድንሆን ይረዳናል።

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-9


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

ሐ. የቴክኒካል ክህሎት አቅም ግንባታ ሂደቶች

 የምርጥ ተሞክሮ መለየት

.ተወዳዳሪ የሚያያደርጉ ቁልፍ አሰራሮችን፣ ስርዓቶችን፣ የስራ ሂደቶችን፣ ወዘተ… መለየት

.በተለዩ አሰራሮች፣ ስርዓቶች፣ የስራ ሂደቶች፣ ወዘተ… ላይ ያለውን የተወዳደሪነት ክህሎት

ደረጃና ከተቀመጠው የሙያ ደረጃ/የብቃት አሃድ አንጻር መቀመር

1.4.2.3 የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ

የቴክኖሎጂ አቅም ግንባታ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከቴክኖሎጂ ለውጥ ጋር ተስማምተው እንዲሄዱ
የሚያስችል የማያሻማና የተቀናጀ ችሎታ/አቅም እንዲፈጥሩና እንዲያጎለብቱ የሚያድረግ የአቅም ግንባታ
ሂደት ነው፡፡ በዚህ መሰረት የኢንተርፕራይዞችን ተወዳዳሪነት ለማረጋገጥ ተፈላጊውን ቴክኖሎጂ በመለየት፣
በማግኘትና በመኮረጅ በማመሳሰልና አቅምን አዳብሮ ለማሻሻል አዋጪ የሆነ የአሰራር ስርዓት ሂደት ሞዴል
መከተል ያስፈልጋል፡፡

i. የእሴት ሰንሰለት ትንተና

የእሴት ሰንሰለት ማለት የአንድን ለገበያ የሚቀርብ ምርት ከግብዓቱ ጀምሮ እስከ ፍጆታ (ጥቅም ላይ
እስክዋለበት ጊዜ) ድረስ ያሉና ለምርት አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ነገሮች የሚቀነባበሩበት ዓላማ መር ቅደም
ተከተል ነው፡፡ የእያንዳንዱን ኢንዱስትሪ ሥራ ከግብዓት እስከ ውጤት ድረስ መዘርዘር የሚያስፈልግበት ዓላማ
በመጨረሻ ላይ የምርቱን ጥራት የሚወስኑ ነገሮች ከግብዓቱ ወይም ከአሰራሩ ወይም ሌላ ከምን እንደሆነ
ለመወሰን እንዲቻል ነው፡፡

ii. የቴክኖሎጂን ክፍተት መለየት

ከላይ የቴክኖሎጂን ትርጓሜና ክፍሎቹ ላይ በመንተራስ የእሴት ሰንሰለቱ ሲተነተን የቴክኖሎጂ ክፍተቶችን
(ቁሳዊ፣ ዕውቀታዊ፣ ሰነዳዊ፣ ድርጊታዊ) ብሎ በመለየት በምርት ጥራት ላይ ችግር/ ክፍተት ያመጣውንና
ቢሻሻል ሊያመጣ ይችል የነበረውን ክፍተት መለየት አንድ ትልቁ ሥራ ነው፣ ምክንያቱም ችግርን ማወቅ
የመፍትሄው ግማሽ አካል ነውና፡፡

iii. ክፍተቱን ለመሙላት የሚወሰዱ አካሄዶች

ለገበያ በሚቀርቡ ምርቶች ከግብዓት ጀምሮ ምርቱ ጥቅም ላይ እስከሚውልበት ድረስ ያለውን ሰንሰለት
በማጥናትና በምርት ጥራት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ሊያመጡ ያስቻሉትን ችግሮች/ክፍተቶች ከተለዩ ቦኋላ
የሚወሰዱ የቴክኖሎጂ አማራጮችን በዝርዝር ማየት ነው፡፡

በመሆኑም የተለያዩ አማራጮችን በመዘርዘር (ለእያንዳንዱ ዝርዝር አሰራር በመፃፍ) የመጨረሻና አማራጭ
የሆነውን ምርጥ ቴክኖሎጂ በግልጽ ማስቀመጥና የተመረጠበትን የአሠራር ዝርዝር ከሌሎቹ ጋር በአዋጭነት
መስፈርት መሰረት ማነፃፀር ያስፈልጋል፡፡

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-10


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

iv. አዋጭነት

የቴክኖሎጂ ክፍተቶች ያለበትን አንድ የምርት ሰንሰለት ክፍተት ከላይ በተጠቀሰው መሠረት ክፍተቱን
የሚሞሉ አማራጭ ቴክኖሎጂዎች ከተመረጡለት በኋላ የሚቀጥለው ሥራ ለተመረጠት የቴክኖሎጂ
አዋጭነት ግምገማ ማካሄድ ነው፡፡ አዋጭነት ከብዙ መንገድ የሚታይ ሲሆን ዋና ዋናዎቹ ምርታማነት፣ ጥራት፣
ጉልበትን በስፋት መጠቀምና ዋጋ ናቸው፡፡

v. ምርጡን ቴክኖሎጂ መለየት

የአንድን ምርት የዕሴት ሰንሰለት በማየትና ያለበትን ክፍተት ለመሙላት ሊጠቅሙ የሚችሉ ቴክኖሎጂዎች
ከተዘረዘሩ በኋላ የሚቀጥለው ሥራ የእያንዳንዱን አዋጭነት በመተንተን አንድ ቴክኖሎጂ መምረጥ ነው፡፡
ምርጡን ቴክኖሎጂ በመምረጥ ሂደት ውስጥ ከአዋጭነት በተጨማሪ ሌሎች መታየት ያለባቸው ነገሮት
የአሠራር ደህንነትንና የጤና ጉዳዮች ናቸው፡፡

vi. ቴክኖሎጂን ማቀብ (ማከማቸት)

በኢኮኖሚ ቀጠና ውስጥ ያለ የትኩረት ኢንዱስትሪን የዕሴት ሰንሰለት ትንተና ያገናዘበ ምርጥ ቴክኖሎጂን
ለማስተላለፍና ሌሎች ደረጃውን ጠብቀው እንዲሰሩት ለማድረግ ቴክኖሎጂውን ማቀብ (ማከማቸት)
ያስፈልጋል፡፡

ቴክኖሎጂ በማቀብ ሂደት ውስጥ የተመረጠውን ቴክኖሎጂ ንድፍ (Blue Print) ማዘጋጀትና ናሙና ሰርቶ
ተከታታይ ፍተሻ ማካሄድ ዋና ዋና ሥራዎቹ ናቸው፡፡ የቴክኖሎጂ ተቋማት ቴክኖሎጂ ማቀብ ዋና ስራቸው
በመሆኑ በሳይንሳዊ ትንተናና መረጃ ተመስርተው የቴክኖሎጂ ንድፍ ማዘጋጀት ይጠበቅባቸዋል፡፡ በተዘጋጀው
ንድፍ መሠረት ብቃት ያለው ናሙና ማዘጋጀት፣ የተዘጋጀውን ናሙና በተገቢው ቦታና የሥራ ምህዳር
ደረጃውን ጠብቆ ለመሠራቱ ተከታታይ የፍተሻ ሥራ ማካሄድ፣ በፍተሻ በተገኙ መረጃዎች ላይ በመመርኮዝ
ማስተካከያ/ማሻሻያ አድርጎ ማጠናቀቅ ይጠበቅባቸዋል፡፡

vii. ቴክኖሎጂ ማሸጋገር

አንድ ቴክኖሎጂ ከተለየ፣ ንድፍ ተዘጋጅቶለት የናሙና ስራ ከተከናወነ እንዲሁም በተሠራው ናሙና ላይ የፍተሻ
ስራ ተካሄዶበት ፍተሻውን ካለፈ በኋላ ወደ ማሸጋገር ስራ ይገባል፡ ከናሙናነት አንስቶ አባዝቶ ወደ ገበያ
ለማሸጋገር በመጀመሪያ አብዢዎችን የመለየትና እነሱን የማብቃት ስራ ሊሠራና ከዛም አልፎ ቴክኖሎጂውን
ከገበያ ጋር ማስተሳሰር ይገባል፡፡

viii. የአብዢዎችን አቅም ክፍተት መለየት

አንድ ቴክኖሎጂ የፍተሻ ስራ ከተሠራበትና ፍተሻው ካለፈ በኋላ የማብዛት ስራ ይሰራል፡፡ ቴክኖሎጂውን
ለማብዛት መጀመሪያ አብዢን መለየት ያስፈልጋል፡፡ አብዢዎችን ስንለይ ልንመለከታቸው ከሚገቡን ነገሮች
መካከል ዋንኛው የአብዢዎቹን አቅም ማወቅ ነው፡፡ የአብዢዎችን አቅም ስንል የሰው ሀይል፣ የማምረቻ
ቴክኖሎጂ፣ የገንዘብ አቅምን ከግምት ያካተተ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ሽግግር ሂደት ውስጥ የማብዛቱን

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-11


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

ስራ ሊሠሩ የሚችሉት የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ናቸው፡፡ ከጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት መካከል
የተፈተሸውን ቴክኖሎጂ ለማብዛት አቅሙ ያላቸውን መርጦ የማባዛት ስራው እንዲሰራ ማድረግ ይገባል፡፡

ix. አብዢዎችን ማብቃት

አብዢዎችን የማብቃት ስራ ሊሠራ የሚችለው በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ሲሆን


የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ቴክኖሎጂን የማብዛት ስራ እንዲሰሩ ይደርጋል::

x. ድጋፍ በመስጠት የብቃቱን ውጤት መገምገም

የማብዛት ስራ በሚሰራበት ጊዜ የማብዛቱን ስራ የሚሰራው ተቋም የተለያዩ ድጋፎች ሊያስፈልጉት ይችላሉ፡፡


ይህ ድጋፍ በገንዘብ፣በሰው ሀይል ወይም ሙያዊ አስተያየትና ልምዶችን ለማካፈል ሊሆን ይችላል፡፡ ስለሆነም
በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ፓኬጅ በተቀመጠው መሰረት አንድ የማብዛት ስራን የሚሠራ ተቋም
ስራውን በትክክል ያከናውን ዘንድ ሊያገኝ የሚገባውን ድጋፍ በሙሉ ማግኘቱን ሊረጋግጥ ይገባል፡፡

xi. ገበያ ማፈላለግ

በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ፓኬጅ እንደተቀመጠው፣ ቴክኖሎጂ የማብዛት ስራ ከተሠራ በኋላ


የሚቀጥለው ገበያን ወደ ማፈላለግ ስራ መሄድ ይሆናል፡፡ ቴክኖሎጂን ከገበያ ጋር ለማስተሳሰር የማስተዋወቅ
ስራዎች ሊሰሩ ይገባል፡፡ የቴክኖሎጂውን ውጤታማነት ያለውን ተፈላጊነት ገበያው እንዲረዳው የተለያዩ
የገበያ ጥናቶችና የማስተዋወቂያ ስራዎች ሊሰሩ ይገባል፡፡ በዚህ ላይ የመንግስት፣ የግል እንዲሁም ሌሎች በገበያ
ነክ ጉዳይ ላይ የተሰማሩ ተቋማት ሊሳተፉ ይችላሉ፡፡

1.4.2.4 የኢንተርፕሪነርሽፕ ዕውቀትና ክህሎት አቅም ግንባታ

የኢንተርፕርነርሽፕ ክህሎትና ዕውቀት አቅም ግንባታ ማለት የጥቃቅንና አነስተኛ አንተርፕራይዝ


ሰራተኞች/አንቀሳቃሾች ከተቀመጠው የሙያ ብቃት አሃድ አንጻር በምርት ዋጋ፣ በምርት ጥራት፣
በትርፋማነት፣ በደንበኞች አያያዝ፣ በሂሳብ መዝገብ አያያዝ፣ በስራ ፈጠራና ተነሳሽነት እንዲሁም በመሳሰሉት
ጉዳዮች ላይ ተወዳዳሪ መሆን ያላስቻላቸውን ክፍተቶች በመለየት ክፍተቶቹን ለመሙላት የሚከናወን
የአቅም ግንባታ ስራ ነው፡፡ ስለዚህ ጥ/አ/ኢንተርፕራይዞች ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡና ተወዳዳሪ
እንዲሆኑ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ድጋፎችና የንግድ ልማት ክህሎት (Business development Skills)
ያስፈልጋቸዋል፡፡

2. ሥራ ፈጠራ (ኢንተርፕሪነርሽኘ)

2.1 ሥራ ፈጠራ (ኢንተርፕሪነርሽኘ) ትርጉም


ሥራ ፈጠራ ወይም ኢንተርፕሪነርሽፕ፡ ማለት በህይወታችን የተለያዩ ምቹ አጋጣሚዎችን በመጠቀም አዲስ ነገር ፈጥሮ
በመስራትና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በማለፍ በኑሮ ላይ ለውጥ/ዕድገት የማምጣት ሂደት ነው፡፡

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-12


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

2.2 የሥራ ፈጠራ (ኢንተርፕርነሽኘ) ጠቀሜታዎች


 የስራ እድል ፈጠራ
 በአካባቢ የሚገኙ ግብአቶችን መጠቀምና ዋጋቸው እንዲጨምር ማድረግ
 በተለያዩ ቦታዎች የተለያዩ የንግድ ዘርፎችን እንዲስፋፋ ማድረግ
 ቴክኖሎጂን ማስተዋወቅና ማላመድ
 ሀብት ማፍራትና ማስፋፋት
 የስራ ፈጠራ ባህልን ማዳበር

2.3 የኢንተርፕሪነርሽፕ (ሥራ ፈጠራ ) ሂደት


 አካባቢን መቃኘት
 ምቹ የስራ ዕድሎችን (አጋጣሚዎችን )መለየትና መምረጥ
 ለስራው አስፈላጊ ግብአቶችን ማስባሰብ
 ወደ ትግበራ መግባት
 በስራ የተገኘውን ውጤት ማግኘት
2.4 የኢንተርፕሪነር (ሥራ ፈጣሪ) ትርጉም
ኢንተርፕሪነር/ሥራ ፈጣሪ ማለት በራሱ ተነሳሽነት ያሉትን የንግድ (የስራ) አጋጣሚዎችን ማየትና መለየት የሚያስችል ባሉት
ሀብቶች በአግባቡ የሚጠቀም በውጤት ላይ ያተኮረ ስራ ላይ የሚሰማራ፣ ሊመጡ የሚችሉ ችግሮችን ከወዲሁ በመገመት
አስፈላጊውን ጥንቃቄ የሚያደርግና የተመጣጠነ ሃላፊነት ( ሪስክ) መውሰድ የሚችል የንግድ ሰው ነው፡፡

2.5 የኢንተርፕሪነር (ሥራ ፈጣሪ) ባህርያት

ኢንተርፕሪነር(ሥራ ፈጣሪ) ብቃትን ለመመዘን የሚያስችሉ የብቃት መመዘኛ ባህርያት አሉ፡፡ እነዚህ ባህርያት ሥራን
የማከናወን ብቃትዎን፣ የማቀድ ብቃትዎን እንዲሁም በራስ መተማመንና ሰዎችን የማግባባት ብቃትዎን በሚፈትሹ አጠቃላይ
ባህርያት ሥር ተሰባስበዋል፡፡

2.5.1 የዕቅድ ጉድኝት (PLANNING CLUSTER)


ከ 3 ቱ ዓለም አቀፍ የስራ አመራር ጥበቦች አንዱና የመጀመሪያው የእቅድ ጉድኝት (Planning Culster) ይባላል፡፡ ይህ የማቀድ
ጉድኝት በውስጡ እንደ ጓደኛሞች የማይነጣጠሉ ሦስት ክፍሎች አሉት፡፡ እነሱም፡-
i. የመረጃ አሰባሰብና ማጠናቀር (Information Seeking)
ii. ግብን መተለም (Goal Setting) እና
iii. የማቀድና የመቆጣጠር ዘዴ (Systematic planning & Monitoring) “ቸው፡፡

ሀ.የመረጃ አሰባሰብና ማጠናቀር (Information Seeking)

ሥራ ፈጣሪው ማለትም አንተርፕሪነሩ ለስራ ከመነሳቱ በፊት ማድረግ ያለበት መረጃ ማሰባሰብና ማጠናቀር ነው፡፡ መረጃ የሚገኘው
ተፈጥሮ ካደለችን የስሜት ህዋሳት ማለትም በማየት፣ በመስማት፣ በማሽተት፣ በመቅመስና በመዳሰስ በመጠቀም ነው፡፡

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-13


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

ለ. ግብን መተለም /Goal Setting/

ግብ መጠኑ ሰፋ ያለ ጊዜን መሰረት ያደረገ እንቅስቃሴን የሚያመለክት ፅንስ-ሀሳብ ሲሆን መሪ ዕቅድ የሚለው ቃል በትክክል ይገልፀዋል፡፡
ግብና ዓላማ ትርጉማቸው እንዳይምታታና አንዱ ያንዱን ቦታ እንዳይወሰድ መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ ግብ ከፍ ላለ የጊዜ መጠን
የሚቀመጥ ሲሆን ዓላማ በጊዜ መጠኑ አነስ ይላል፡፡ ሁለቱም በ 3 ንዑሳን ክፍሎች ይከፈላሉ፡፡

i. የረዥም ጊዜ ግብ የ 10 ዓመት ዕቅድ መድረሻ ነጥብ


ii. የመካከለኛ ጊዜ ግብ የ 5 ዓመት ዕቅድ መድረሻ ነጥብ
iii. የአጭር ጊዜ ግብ የ 1 ዓመት ዕቅድ መድረሻ ነጥብ
 ግብ ሲቀረፅ የሚከተሉትን ነጥቦች ያገናዘበ (SMART) መሆን አለበት:: እነዚህም፡-

አጭርና ግልፅ Specific

የሚለካ Measurable

ግ ግብ ተጨባጭ Achievable

ምክንያታዊ Reasonable

ጊዜን መሰረት ያደረገ Time-bound

ሐ. የማቀድና የመቆጣጠር ዘዴ/Systematic Planning & Monitoring/

ከዕቅድ ጓደኞች ውስጥ ሦስተኛው የማቀድና የመቆጣጠር ዘዴ የተባለው ነው፡፡ በውስጡ ደግሞ ማቀድ /Planning/እና መቆጣጠር
/Monitoring/አሉት፡፡

i. ማቀድ/ Planning/

ማቀድ/ Planning / እጅግ ቁልፍ የሆኑ ስድስት ጥያቄዎችን በማቅረብ ፕሮጀክታችን ማለትም ልንሰራው ያሰብነው ምርት ወይም
አገልግሎት በመጀመሪያ ሊመልሳቸው የሚገባቸውን መልሶች በስርዓትና በተደራጀ መልክ የምንመልስበት መሳሪያ ነው፡፡ እነርሱም፡-

1. Why- ለምን? (የፕሮጀክቱ አስፈላጊነት ፣ ዓላማና መስፈርቱ)


2. What- ምን? (የፕሮጀክቱ ጠቀሜታ ማለትም ልናበረክት የፈለግነው ምርት ወይም አገልግሎት
ወሰን(Scope of the project)
3. How- እንዴት? (ምርቱን ወይም አገልግሎቱን ለማዘጋጀትና ለማቅረብ የምናደርገው
የእንቅስቃሴ ሂደትና ዘዴ (Methodlogy)
4. Who- ማን? (የፕሮጀክቱ ድርጅታዊ መዋቅር ማለትም የሚፈለገው የሰለጠነ የሰው ሀይል
ብዛትና ጥራት የሚለካበት)
5. How much- ምን ያህል? (የፕሪጀክቱን በጀት፣ የምርት አቅርቦት መጠን)
6. When- መቼ? (የፕሮጀክቱ የድርጊት መርሃ ግብር ይመለከታል፡፡)

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-14


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

2.5.2 የተግባር ጉድኝት (Power Cluster)

የተግባር ጉድኝት ስሙ እንደሚመለከተውና በምዕራፍ አንድ እንደተጠቀሰው ያቀድነው ቢዝነስ እንዴት ወደ ገበያ እንደምናቀርበው
የምንማርበት ዘዴ ነው፡፡ በተግባር ጉድኝት (Power Cluster) ውስጥ ሁለት ጓደኛሞችን እናገኛለን፡፡ እነርሱም፡-

1. ሰዎችን የማሳመንና የግንኙነት መረብ (Persuation & Networking)


2. ግላዊ ነፃነትና በራስ መተማመን (Independence & Self Confidence) ሲሆኑ እያንዳንዱ እንደሚከተለዉ
ቀርበዋል፡፡

i. ሰዎችን የማሳመንና የግንኙነት መረብ (Persuation & Networking)


በንግግር ሰዎችን ለማሳመንና የግንኙነት መረብ ስለመዘርጋት ሶስት መርሆዎችን መጠቀም አለብን፡፡ እነርሱም፡-

1 ኛ. የጀመርነውን የቢዝነስ /የንግድ ዓላማ ውጤታማ ለማድረግ ቁልፍ ሰዎችን እና የድርጅት ወኪሎችን በግንባር በማነጋገር በጓደኝነት
መንፈስ ቀርበን ልናሳምናቸው ይገባል፡፡
2 ኛ. ተከታታይነትና ዘላቂነት ያለው ታክቲክና ስትራቴጂ በመቀየስ የምርታችንን እና አገልግሎታችንን ጠቃሚነት ልንገልፅላቸው
ይገባል፡፡
3 ኛ. የንግዳችን ጤንነትና ጭድገት የተጠበቀ እንዲሆን ተደጋጋሚ ጥረት ያስፈልጋል፡፡በተለይ ንግግርን ለማድረግ ተፈጥሮ ለሁላችንም
ሁለት ነገሮችን አድላናለች፡፡እነርሱም አይናችንና እጃችንን ነዉ፡፡ ሌላው ልንጠነቀቅ የምንገባው ጤንነታችን ፣ ንፅህናችን እና አለባበሳችን
ሰዎችን የሚማርክ መሆን አለበት፡፡

ii. ግላዊ ነፃነትና በራስ መተማመን(Independence & Self Confidence)


ግላዊ ነፃነትና በራስ መተማመንን ለማዳበር የሚከተሉትን ሦስት መርሆዎች እንመልከት፡፡
1 ኛ. በቀዳሚ ህይወታችን የነበረ የስኬት መጥመምን ረስተን ስለወደፊቱ በማስብ በዓላማችንና በውሳኔያችን መፅናት፡፡
2 ኛ. ከሌሎች ሰዎች ቁጥጥርና ተገዥነት የራሳችንን ዕድል ለመወሰን መጣር
3 ኛ. በተገኘው አጋጣሚ ባነጋገርም ሆነ በአኗኗር በራስ መተማመናችንን ማሳየት ይኖርብናል፡፡

2.5.3 የስኬታማነት ጉድኝት (ACHIEVEMENT CLUSTER)

i. አማራጭ መፈለግና ተነሰሽነት (Opportunity Seeking & Initiative)


• ሰዎች በኃላፊነት ሳይጠይቁን ስራችንን መወጣት፣
• ንግዳችንን (በአዲስ አካባቢ፣ ምርትና አቅርቦት) ማሳደግ ፣
• ለየት ያሉ የገንዘብ ማግኛ ዘዴዎችን መቃኘት አለብን፡፡
ii. ኃላፊነት መሸከም/Risk Taking/
• ትንሽ አቅማችንን የሚፈትኑ ኃላፊነቶችን መፍራት የለብንም፣
• በኃላፊነት ላይ አደጋ አምጭ ነገሮችን መቀነስ፣
• አደጋ የሚያመጡ ነገሮችን ለመቃኘት መፍትሄ መሰብ አለብን፡፡

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-15


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

iii. የስራ ብቃትና ጥራት /Demand for Efficientcy & Quality/


• የተኮናተርነውን ስራ በጥራትና በተባለው ሰዓት ማጠናቀቅ፣
• መልካም ዝና ለማምጣት መሞከር፣
• ስራዎችን ከተፎካካሪዎቻችን ጋር ሲነፃፀር በጥራት ፣በፍጥነትና በርካሽ ዋጋ መስራት ይጠበቅብናል፡፡
iv. የዓላማ ፅናት /Persistance/
• መሰናክል ሲያጋጥመን እርምጃ መውስድ፣
• መሰናክሉን ለመዝለል ተደጋጋሚ ጥረትና ስትራቴጂ መቀየስ፣
• ግብና ዓላማችንን ሳንዘነጋ እስከ መጨረሻ ውጤት መስራት አለብን፡፡
v. በቃላችን መገኘትና ውልን መፈፀም /Commitment to the work Contract/
• ሥራችንን ለመጨረስ ግላዊ መስዋዕትነትና ብርቱ ጥረት ማድረግ፣
• የኮንትራት ስራው እንዲጠናቀቅ ከሰራተኞቻችን ጋር አብረን መስራት፣
• የደንበኞቻችንን እርካታ ለመጠበቅና በአጭር ጊዜ ግንኙነት የረዥም ጊዜ መልካም ስምና ዝና ለመገንባት ጥረት
ማድረግ አለብን፡፡

3. ¾Ówà (ÑuÁ) ›S^`“ Y`¯ƒ


3.1 ¾Ówà U”’ƒ
ÓwÃ:- TKƒ ¾Å”u™‹” õLÔƒ KTTELƒ U`ƒ“ ›ÑMÓKAƒ” ƒ`õ” K=Ácј uT>‹M SMŸ< ¾SeÖƒ H>Ń
’¬ :: ገዢና ሻጭ ፍላጎታቸዉን ለማሟላት ምርትና አገልግሎትታቸዉን የሚለዋወጡበት ሂደት ነዉ፡፡ Ÿƒ`Ñ<S< S[ǃ
¾U”‹K¬ ¾Å”u™‹” õLÔƒ T¨p ÃÑv“M TKƒ ’¬:: ÑuÁ Là ¾U”ðMѨ<” G<K< ›U`}” SgØ ›”‹MU::

eK²=I ¾›”É ›=”}`ý^ô ›”kdni ¾T>Ÿ}K<ƒ” H>Å„‹ T¨p ›Kuƒ::


 ደንበኞች እነማን እንደሆኑ መረዳት ፣
 ¾Å”u—” õLÔƒ SK¾ƒ ፣
 የቢዝነሱ ባለቤት በገበያ ጥናት በተደገፈ መረጃ በትክክል ደንበኞች የሚፈልጉትን ምርት ማወቅ፣
 የገበያ ባለሙያዉ ደንበኞች ለወደፊት ምን እንደሚፈልጉ መገመትና አዳዲስ ምርቶችን ማቅረብ አለበት፡፡
3.2 የገበያ ጥናት ምንነት
የገበያ ጥናት፡- ማለት በማያቋርጥ ሁኔታ ከገበያ ላይ መረጃን መሰብሰብ÷መተንተንና ለዉሳኔ እንዲያመች አድርጎ
የማዋቀር ሂደት ነዉ፡፡
3.2.1 የገበያ ጥናት አስፈላጊነት
የገበያ ጥናት አስፈላገነት የምንላቸዉ፡-
 የትኩረት ገበያን ለይቶ ለማወቅ
 በትኩረት ገበያ ተጠቃሚዎችን የገቢ ሁኔታና የመግዛት አቅም ለመረዳት
 እርግጠኛ ለመሆን
 አፋጣኝ ዉሳኔ ለመስጠት
 የገበያ ተፎካካሪዎችን አቅም ዋጋ ትራትና አጠቃላይ እንቅስቃሴ ለማወቅ
 አስቸጋሪ የገበያ አሠራሮችን ለመለወጥ
 የደንበኞችን ፍላጎት በመለየት የተሸለ የገበያ አመራርና ስልት ለመተግበር

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-16


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

 መልካም አጋጣሚዎችንና ሥጋቶችን ለመለየት


 ትክክለኛ ትንበያ ለማድረግ
 በጀት በአግባቡ ለመጠቀም…ወዘተ ናቸዉ፡፡
3.2.2 ከገበያ የሚሰበሰቡ ዋና ዋና መረጃዎች
ከገበያ መረጃ መሰብሰብ ጉልህ ጠቀሜታ አለዉ፡፡ ከገበያ የሚሰበሰቡ ዋና ዋና መረጃዎች የምንላቸዉ፡-
 ስለ ደንበኛ÷ስለተፎካካሪ÷ ስለአቅራቢዎችና ስለምርት
 ስለዋጋ÷ ስለማስተዋወቂያ÷ ስለሥርጭትና የመሳሰሉት ናቸዉ፡፡
3.2.3 መረጃ የማግኛ ዘዴዎች
ከገበያ መረጃን በተለያዩ ሥልቶች/ዘዴዎች ማግኘት ይቻላል፡፡ እነዚህም፡-
 የጽሑፍ ጥያቄዎችን በማዘጋጀት
 በቃለ-መጠይቅ/በቃለ-ምልልስ
 በምልከታ
 በሙከራ/ experiment/ በማድረግና ወዘተ ናቸዉ፡፡
3.3 የገበያ ዉህዶች /Marketing Mix/
ድርጅቶች ዓላማቸዉን ለማሳካት የሚከተሉትን የገበያ ዉህዶች ወይም የተለያዩ ሥልቶችን በመጠቀም ተግባራዊ
ማድረግ አለባቸዉ፡፡የገበያ ዉህዶች የምንላቸዉ ምርት÷ ዋጋ÷ ማስተዋወቅና ማከፋፈል ናቸዉ፡፡
ሀ.ምርት (Product): ለገበያ የሚቀርብ ሆኖ ድርጅቶች፡-
 የተለያዩ ምርቶችን እንደየደንበኛዉ ፍላጎት ማቅረብ/ማምረት/
 ጥራቱን መጠበቅ
 ለምርቱ ተጨማሪ እሴት መፍጠር /ከለር ዲዛይን… /ወዘተ
 የንግድ ምልክት የንግድ ስም መጠቀም
 ማሸጊያዎችን ማዘጋጀት
 ተጨማሪ አገልግሎት መስጠት
 ዋስትና መስጠትና …ወዘተ ይጠበቅባቸዋል፡፡
ለ. ዋጋ (price)፡- ምርት የሚሸጥበት ተመን ሲሆን፡-
 ተመጣጣኝ ዋጋ መተመን
 ቅናሽ ማድረግ
 የክፍያ ጊዜን ማራዘምና
 ዱቤ መስጠት ነዉ፡፡

የዋጋ አወጣጥ ሥልቶች፡- የተለያዩ ዓይነቶች የዋጋ አወጣጥ ሥልቶች አሉ፡፡ እነዚህም፡-
1. ወጪ ላይ ተመስርቶ ዋጋ መወሰን

2. የተፎካካሪዉ ዋጋ ላይ ተመስርቶ መወሰንና

3. የደንበኛ ፍላጉት ላይ ተመስርቶ መወሰን ናቸዉ፡፡

ሐ. ማስተዋወቅ (promotion): ምርት የተሻለ ግብይት እንዲያገኝ ማድረግ ሆኖ ስልቶቹም፡-

 የሽያጭ ሠራተኞች ክህሎት መጠቀም

 ሚዲያዎችን መጠቀም /TV, Radio, News Paper /

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-17


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

 ደንበኛን በመጠቀም (Word of Mouth)

 ተጨማሪ ግልጋሎቶችን መስጠት (ነፃ ትራንስፖርት÷ ዋስትና መስጠት)እና

 የጥገና አገልግሎት መስጠት ናቸዉ፡፡


መ. ማከፋፈል (place):ምርት ለተጠቃሚዉ ህብረተሰብ/ደንበኛ እንዲደርስ ማድረግ ሆኖ፡
 የማስፋፊያ ቦታዎች መምረጥ
 የተለያዩ የትራንስፖርት ዓይነቶችን መጠቀም
 ወኪሎችን/ደላሎችን መጠቀም
 ማከማቻ ማዘጋጀት ዋና ዋናዎቹ ዘዴዎች ናቸዉ፡፡

3.4 የሽያጭ ሂደት እና ሥልት

ቅድመ ጥናት በማድረግ ለወደፊት ሊገዙ የሚችሉ ወይም የምርታችን ተጠቃሚ ሊሆኑ ይችላሉ የምንላቸዉን ደንበኞች መለየት አስፈላጊ
ነዉ፡፡በተጨማሪም፡

 ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉ ደንበኞትን መረጃ መሰብሰብ

 እራስንንና ድርጅትን ማስተዋወቅና የሄድንበትን አላማ ማሳወቅ

 ስለምናመርተዉ ምርትና አገልግሎት ገለጻ ማድረግ

 ምርቱን እንዴት እንደሚጠቀሙበት ማሳየት

 ቅድመ ግዢ ቅሬታን ወይም የሚነሱ ጥያቄዎችን መመለስ

 ሽያጭ መፈፀም

 ድህረ ሽያጭና ክትትል ማድረግ ያስፈልግል፡፡


3.5 የደንበኛ አገልግሎት (Customer Service)

ደንበኛ ማለት ማንኛዉም ግለሰብ ድርጅት ወይም ተቋም የሌላዉን ምርት ወይም አገልግሎት የሚፈልግ / የሚገዛ
ማለት ነዉ፡፡

ደንበኛ ንጉስ/ንግስት መሆኑ/ን ÷ደንበኛ ከሌለ እኛም የለንም÷ምርት የመግዛት ወይም ያለመግዛት ዉሳኔ በደንበኛ እጅ
ነዉና አምራች/አከፋፋይ ድርጅት በደንበኛዉ ላይ ጥገኛ ናቸዉ የሚሉትን አባባሎች ታሳቢ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

3.5.1 መሠረታዊ የደንበኛ ፍላጎትና ባህሪያት

ሀ. መሠረታዊ የደንበኛ ፍላጎቶች

ሁለት መሠረታዊ የደንበኛ ፍላጎቶች አሉ፡፡ እነርሱም፡-

1. ትክክለኛ ግልጋሎት በትክክለኛዉ ሠዓት በትክክለኛዉ ሰዉ እንዲሰጣቸዉ ይፈልጋሉ

2. አቅምን ያገናዘበ ዋጋ ጥራት ያለዉ ምርት አፋጣኝ መፍትሔ እና ሙገሳን ይፈልጋሉ፡፡

ለ. የደንበኛ ባህሪያት

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-18


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

ደንበኞች የተለያዩ ዓይነቶች ባህሪያት አሏቸዉ፡፡ እነዚህም፡-


1. ዝምተኛ/ Silent type/ ወረኛ/ለፍላፊ/Talkative type/ ክርክር የሚወዱ/Argumentative type/
ጭምት/ዓይናፋር/Shy type/
2. የሚታለሉ የሚመስላቸዉ /Suspicious type/ ጓደኝነት /Friendly type/
3. ትዕግስት የሌላቸዉ/ Impatient type/ ለራሳቸዉ ትልቅ ክብር የሚሰጡ/ Pompous/
3.5.1.1 ደንበኛ ማጣት የሚያስከትለዉ ዉጤት
ደንበኛ የተዘጋጀን ምርት በወቅቱ ለማንሳትና የድርጅትን/ግለሰብን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ያለዉ ሚና ጉልህ መሆኑ
ይታወቃል፡፡ በተቃራኒዉ ደንበኛ ማጣት ደግሞ በተዘጋጀ ምርት ላይ አሉታዊ አስተዋጽኦ ያሳድራል፡፡ በዋናነት ደንበኛ
ማጣት የሚያስከትሉ ዉጤቶች የሚከተሉ ናቸዉ፡፡
1. የድርጅት ሽያጭ አቅም መቀነስ
2. የትርፍ ማሽቆልቆልና ድርጅትን መዝጋት
3. የሥራ አጥ ቁጥር መበራከት

3.6 የደንበኛ አያያዝ ሥልቶች

የደንበኛ አያያዝ ሥልቶች ከታች የተመለከቱት ዋና ዋናዎቹ ናቸዉ፡፡ እነዚህም፡-

 ቀልጣፋና ተገቢ አገልግሎት መስጠት፣

 በተጠቃሚው ፍላጎት ላይ ተመስርቶ መምራት /አገልግሎት መስጠት

 ዋጋ የደንበኛን የመግዛት አቅም ያገናዘበ ማድረግ

 የደንበኛን የእርካታ መጠን መለካት

 በአገልግሎትም ሆነ በምርት ጥራት ከተፎካካሪዎች ልቆ መገኘት

 ከደንበኛ ጋር ቤተሰባዊ ግንኙነት መፍጠር

 ተፈላጊ ያልሆነ ግብዓት አለመጠቀም

 የስራ ቦታንና ሰዓትን ለደንበኛ ማመቻቸት

 በምርቱ/ በአገልግሎቱ ላይ ቀጣይነት ያለው እሴት መፍጠር

 የተጠቃሚውን ጤና የሚያውኩ ምርቶችን ማስወገድ

 በቃል መገኘት

 ሁል ጊዜ በአዳዲስ ፈጠራዎች ላይ መሳተፍ

 ለደንበኛዉ በሚያመጣዉ ገንዘብ ልክ እርካታ መስጠት

 የደንበኛን ቅሬታ በአግባቡ ማስተናገድ

3.7 የአገልግሎት አሠጣጥ እሴቶች/ values/


 ዉጤታማነት(Achievement)

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-19


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

 ደንበኛን ማስቀደም( Customer first) በእኩልነት ማየት (equality) እና ማክበር (Respect)

 ታማኝነት (Honesty) ግልፅነት(Transparency) እና ሚስጢር ጠባቂነት (Confidentiality)

 ቁርጠኝንት(Commitment)

 የአገልግሎት ጥራትን መጠበቅ(Maintain quality)

 ሃይልን አሟጦ መጠቀም (Maximum utilization of capacities)

 ለመማር ሁል ጊዜ ዝግጁ መሆን(Ready to learn)

 በቁጠባ መሥራት(More with less cost)… ወዘተ

4. የንግድ ዕቅድ (Business Plan)


4.1 የንግድ ዕቅድ ምንነት

የንድ ዕቅድ (Business Plan) ማለት አንድ ድርጅት በየጊዜዉ ምን እንደሚሠራ የት እንደሚሰራ እንዴት እንደሚሰራ
ለምን እንደሚሰራ እና ምን ዓይነት ሥልቶች ወደ ግብ እንደሚያደርሱ የሚያመለክት በወረቀት ላይ የተጻፈ መንገድ
ወይም ካርታ ነዉ፡፡

4.2 የንግድ ዕቅድ የሚዘጋጅባቸው ዋና ዋና ምክንያቶች

የንግድ ዕቅድ ለማዘጋጀት ስድስት ዋና ዋና ምክንያቶች አሉ፡፡ እነርሱም፡-

1. ገንዘብ ለማግኘት
2. ግቦችን አስቀምጦ ለመንቀሳቀስ ቢዝነስ ፕላን እንደ ካርታ ሆኖ ያገለግላል
3. የየዕለቱን ተግባራት ለመተግበር እንደ መመሪያ ሆኖ ያገለግላል
4. ችግሮችን ቀድሞ ለማየትና የፕሮጀክቱን አዋጪነት ለመገምገም በዚህም ጊዜንና ገንዘብን ይቆጥባል
5. ስለ ደንበኞችና ስለገበያው የጠለቀ ዕውቀት እንዲኖረን ያስችላል
6. ቢዝነሱን እንዴት መልቀቅ እንደሚገባን የሚያሳይ ስትራቴጂም ሊያካትት ይችላል
4.3 የንድ ዕቅድ (Business Plan) ዝግጅት

ማንኛዉም ኢንተርፕራይዝ ወይም ኢንዱስትሪ የቢዝነስ ዕቅድ ማዘጋጀቱ በይበልጥ ሥራዉን ዉጤታማ ያደርግለታል፡፡
የንግድ ዕቅድ በዉስጡ የሚይዛቸዉ ነገሮች፡-

ሀ. የድርጅቱ/ኢንተርፕራይዙ/ ታሪክ (Executive Summary)

ይህ ሥም አመሠራረት የባለቤት/ቶች ስም አድራሻ የባለቤቱ/የመሥራቹ የግል መረጃ ዕድሜ የት/ት ደረጃ ልምድ
የመነሻ ካፒታል እና አሁን ያለዉ ካፒታል የሚያመርታቸዉ የምርት ዓይነቶች የኢንተርፕራይዙ ዓይት አምራች/አከፋፋይ
የሚሉትን ያካትታል፡፡

ለ. የድርጅቱ ራዕይ ተልዕኮ እሴቶች ግብና ዓላማ

ሐ. የድርጅቱ የሥራ መዋቅር (የሥራ ክፍፍል ኃላፊነትና ተጠያቂነት)

መ. የሚጠቀማቸዉ የገበያ ሥልቶች( የማምርት ዋጋ የመተመን የማስተዋወቅና የማከፋፈል ሥልት

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-20


የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሺን አገልግሎት አተገባበር ማንዋል

ሠ. ድርጅቱ ላይ ተፅዕኖ ያሳድራሉ ተብለዉ የሚገመቱ

 ዉስጣዊ ተፅዕኖዎች ጥንካሬና ድክመት

 ዉጫዊ ተፅዕኖዎች መልካም አጋጣሚዎችና ሥጋቶች

ረ. ወርሃዊ/ ዓመታዊ የሽያጭ እና ግዢ ትንበያዎች

ሰ. ወርሃዊ/ዓመታዊ የሂሳብ መግለጫ ናቸዉ፡፡

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ቴ/ሙ/ትም/ሥ/ቢሮ የታርጫ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የተዘጋጀ ጥር 2011 /-21

You might also like