Professional Documents
Culture Documents
July 15, 2020: Published On
July 15, 2020: Published On
July 15, 2020: Published On
በብሉይ ኪዳን ከሚገኙ ታላላቅ የትንቢት መጻሕፍት አንዱ ትንቢተ ኢሳይያስ ነው። ታላቅ
የተባለባቸው በርካታ ምክንያቶች አሉ፤ በመጀመሪያ፥ ትንቢተ ኢሳይያስ ስለ እግዚኣብሔር
ግርማ፥ ቅድስናና በነገሮች ሁሉ ላይ ስላለው ሉዓላዊ ሥልጣን ግልጽ የሆነ ትምህርት
ይሰጣል። ስለ እግዚአብሔር ባሕርይ የማያሻማ ገለጻ ያቀርባል። አንድ ክርስቲያን
የእግዚአብሔርን ባሕርይ የበለጠ በተረዳ ቍጥር፥ በሕይወቱ በሚገጥሙት አስቸጋሪና
አጠራጣሪ ጉዳዮች ውስጥ በእግዚአብሔር በመተማመን በእርግጠኝነት መጓዙን
ይቀጥላል። ሁለተኛ፥ ትንቢተ ኢሳይያስ ከመዝሙረ ዳዊት በቀር ከማንኛቸውም የብሉይ
ኪዳን መጽሐፍ ይልቅ በአዲስ ኪዳን ተጠቅሶአል፤ ይህም 80 ጊዜ ያህል ነው። በሦስተኛ
ደረጃ፥ ትንቢተ ኢሳይያስን ታላቅ ያሰኘው በርካታ የወንጌል መመሪያዎችን መያዙ ነው።
በመሠረቱ አንዳንዶች ትንቢተ ኢሳይያስን «አምስተኛው ወንጌል» በማለት ይጠሩታል።
ይህም የሆነው፥ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ክርስቶስን የሚያሳዩ ብዙ ተምሳሌቶች ስላሉና ሰው
በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ የሚሆንበት መንገድ በግልጽ ስለቀረበ ነው (ለምሳሌ፡-1፡18፤
44፡22፥ 55፤ 64፡6)።
2 ኛ ጥያቄ፥ በትንቢተ ኢሳይያስ ውስጥ የሚገኙ ከዚህ ቀደም ያበረታቱህ አንዳንድ
ክፍሎችን ጥቀስ።
በምሁራን መካከል ይህ ልዩነት የሚታየው ለምንድን ነው? ቢያንስ ሁለት ጸሐፊዎች ነበሩ
የሚል አቋም ያላቸው ጸሐፊዎች የሚያቀርቡት ምክንያት እንደሚከተለው ነው፡-
ይህ መጽሐፍ የተጻፈው በአንድ ጸሐፊ ብቻ ነበር የሚል አመለካከት ያላቸው ሰዎች ይህን
አመለካከት የሚቀበሉት በሚከተሉት ምክንያቶች ነው፡-
ስለዚህ የትንቢተ ኢሳይያስን መጽሐፍ የጻፉት ሁለት ወይም ከዚያ የሚበልጡ ሰዎች
ናቸው ብለን የምናምንበት አንዳችም ምክንያት የለም። ትንቢተ ኢሳይያስን በሙሉ የጻፈው
ኢሳይያስ እንደሆነና እግዚአብሔር አንዳንድ አስደናቂ የሆኑ ትንቢቶችን እንዲጽፍ
እንዳደረገው ማመን ለእኛ ከሁሉም የተሻለ ነገር ነው።