Professional Documents
Culture Documents
አራት መሰረቶች ለሙስሊም ነጋዴዎች
አራት መሰረቶች ለሙስሊም ነጋዴዎች
"الرجل يطيل السفر أشعث أغبر يمد يديه إلى السماء: وذكر عليه الصالة والسالم
ومطعمه حرام ومشربه حرام وملبسه حرام وغذي بالحرام فأنى، يا رب يا رب
"يستجاب لذلك
የአላህ መልክተኛ ﷺየሚከተለውን ተናግረዋል፡-
“ግለሰቡ ጸጉሩ የተንጨፈረረ ፤ አካለ ቡላ ሆኖ ጉዞን ያበዛል ፤ ጌታየ ሆይ! ጌታየ ሆይ!
በማለት እጆቹን ወደሰማይ ዘርግቶ ጌታውን ይማጸናል ፤ ምግቡ ሀራም መጠጡ ሀራም
ልብሱ ሀራም በአጠቃላይ በሀራም ነው የተገነባው እንዴት ይህን ሰው ዱዓውን ሊቀበለው
ይችላል?!” ሙስሊም፡
እንደዚህ አይነት ባህሪ ያለውን ሰው አላህ እንዴት መልስ ሊሰጠው ይችላል?!
በዚህ ምክንያት ከቀደምቶች አንዱ የሚከተለውን ተናግሯል፡-
5/6
" فليطب طعمته، "من سره أن يستجيب هللا دعوته
“ዱዓውን አላህ እንዲቀበለው የፈለገ ሰው አላህ የፈቀደውን ይመገብ፡፡” ጃሚዕ አል ዑሉም
ወል ሂከም፡
ይህ ክፍል ከሙስሊም ነጋዴዎች ዘንድ መሰረታዊ ነገር ነው፡፡ ይህን ጉዳይ መገንዘብና
ማወቅ ላይ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል፡፡ ሳይገነዘብ ወይም አላህ የፈቀደው መሆኑን ሳያውቅ
ወደምግብና መጠጥ ዘሎ መግባት የለበትም፡፡ ሀራም ወይም ብዥታ የሚፈጥር ከሆነ
ደግሞ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊያደርግና ፈጥኖ ሊርቅ ይገባል፡፡ አላህ የፈቀደውን ምግብ
መብላት የሚደራደሩበት ጉዳይ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ረሡል ﷺለነጋዴዎች
ከጠቀሷቸው መሰረታዊ ነገሮች አንዱ እርሱ ነውና፡፡ ይልቁንም ከእርሱ ዘንድ ጥልቅ
እና የተረጋገጠ ጉዳይ ሊሆን ይገባል፡፡
አንተ ነጋዴ የሆንክ ሙስሊም ወንድሜ ሆይ! እነዚህን አራት መሰረታዊ መርሆዎች
በደንብ ጠብቀህ ያዛቸው፤ አታጥፋቸው፤ ከመጥፎ አዛዥ፣ ከነፍስያ ተንኮልና ከሰይጣን
በአላህ ተጠበቅ ፡፡ በገቢያ ውስጥ አብዛኛው ሰው በሐሰት የሚነግድ በመሆኑ
“እውነትን ይዥ እንዴት ያዋጣኛል ፤ ሰዎች ሁሉ በውሸት እየማሉ ነው የሚነግዱት ፤
በዚህ ምክንያት ኪሳራ ውስጥ መግባቴ አይቀርም” አትበል ፤ አንተ ብቻ በሐቅ ላይ
ሁን ፤ በሐቅ ላይ ከሆንክ አላህ በጥበቃውና በድጋፉ ከአንተ ጋር ነው፡፡
የተንጣለለው ሰፊ የንግድ ሜዳ የሰው ልጅ ስነምግባር የሚለካበት መድረክ ነው፡፡
ከዱንያ የሚያመልጥህ ትርፍ ቢኖርም እንኳ ነብዩ ﷺየመከሩህን አራት መሰረታዊ
መርሆዎች የህይዎትህ መመሪያ አድርጋቸው ፤ በሱና ላይ ትዕግስት ካደረክ የነብዩን
ﷺአደራ ከጠበክ በዱንያም በአኼራም ያማረ ፍጻሜ ለአንተ ነው የሚሆነው፡፡
ስለዚህ በዚህ ላይ ተስፋ ልትቆርጥ አይገባም፡፡
የተከበርክ ወንድሜ ሆይ! ከመጥፎ ስነምግባር አላህ ይጠብቅህ! ሀላል የሆነ ገንዘብና
መልካም የሆነ ኑሮ አላህ ይለግስህ ! እነሆ እርሱ ሰሚና ዱዓን ተቀባይ የሆነ ጌታ
ነውና፡፡
6/6
:إعداد
الشيخ عبدالرزاق بن عبدالمحسن البدر
ትርጉም፡ ዩሱፍ አሕመድ