Download as pdf or txt
Download as pdf or txt
You are on page 1of 8

የመንፈሳዊ አመራር መመሪያ መስከረም / 2016

የዚህ ስልጠና ዋና ዓላማ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚገኙ ወጣትና ተተኪ መሪዎች ራእይን በማወቅ ውስጥ
ያለውን ራስን መርቶ ሌላውን የመምራት ሂደት እንዲገነዘቡ ማስቻል ነው፡፡
መግቢያ - የመንፈሳዊ አመራር ትርጓሜ
ክፍል አንድ - የመንፈሳዊ አመራር ሁለንተናዊ ገጽታ
ክፍል ሁለት - መልካም ተጽእኖን የሚያመጣ ራእይ
ክፍል ሶስት - ለራእያችን የሚመጥን ዲሲፕሊን
ክፍል አራት - ለራእያችን የሚመጥን ባህሪይ
ክፍል አምስት - ለራእያችን የሚመጥን ክህሎት

ለአዲስ አበባ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን


መካነ ኢየሱስ ለወጣቶች የተዘጋጀ ስልጠና

By Dr. Eyob Mamo


የመንፈሳዊ አመራር መመሪያ

መግቢያ
የመንፈሳዊ አመራር ትርጓሜ
“13ከእናንተ መካከል ጥበበኛና አስተዋይ የሆነ ሰው ማን ነው? ሥራውን ከጥበብ በሆነ በመልካም አኗኗር ያሳይ። 14ነገር ግን መራራ ቅናትና ራስ
ወዳድነት በልባችሁ ቢኖር ኵራት አይሰማችሁ፤ እውነትንም አትካዱ። 15እንዲህ ያለችዋ ጥበብ ከላይ አይደለችም፤ ነገር ግን ከምድር፣ ከሥጋና
ከአጋንንት ናት። 16ቅናትና ራስ ወዳድነት ባሉበት ስፍራ በዚያ ሁከትና ክፉ ሥራ ሁሉ ይገኛሉ። 17ከሰማይ የሆነችው ጥበብ ግን በመጀመሪያ
ንጽሕት ናት፤ በኋላም ሰላም ወዳድ፣ ታጋሽ፣ እሺ ባይ፣ ምሕረትና መልካም ፍሬ የሞላባት፣ አድልዎና ግብዝነት የሌለባት ናት። 18የጽድቅም ፍሬ
ሰላምን ለሚያደርጉ በሰላም ይዘራል” - ያዕ. 3፡13-18

• “መምራት” (በእንግሊዝኛው “to lead”) የሚለው ቃል “ሌድን” (“leden”) ወይም “ሎዳን” (“loadan”) ከሚለው ጥንታዊ የእንግሊዝኛ ቃል
የመጣ እንደሆነ ይታመናል፡፡
• ትርጓሜውም፣ “ወደ ፊት ማስኬድ”፣ “ምሪት መስጠት”፣ “መንገዱን ማሳየት” ነው፡፡
• በአመራር ሂደት ውስጥ እኛ ያልሆንነውን ነገር ሰዎች ወደመሆን እንዲመጡ ማድረግ አንችልም፡፡
• በአመራር አለም ውስጥ እኛ በውስጠ-ሕሊናችንና በተግባር ወዳልሄድንበት
አቅጣጫ ሰዎችን መምራት አንችልም፡፡
• አመራር ማለት ራሳችንን፣ ሰዎችን፣ አገልግሎትን ወይም የስራ ሂደትን
የምንመራበት የስነ-ጥበብ ዘርፍ ነው፡፡
• አመራር “ሳይንስ” አይደለም፣ ምክንያቱም በተለያዩ ሁኔታዎች ውስጥ ለተከሰተ
ተመሳሳይ ክስተት የምንሰጠው ምላሽ ሊለያይ ስለሚችል ማለት ነው፡፡
• አመራር ማለት በራሳችን ላይ፣ በሰዎች ላይና በአንድ የአሰራር ሂደት ላይ
መልካም ተጽእኖ ማምጣት ማለት ነው፡፡
• ይህ የመልካም ተጽእኖ እውነታ መንፈሳዊ ጥበብን የሚጠይቅ ጉዳይ ነው፡፡

ሁለቱ የአመራር ጥበብ ምንጮች

• ከስነ-ጥበብ አንጻር ስንመለከተው የአመራር ስልቶች ሁለት ናቸው፡፡


• አንደኛው ስልት የዚህች ዓለም ጥበብ የሚያስተምረን ስልት ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ቃሉ የሚያስተምረን ስልት ነው፡፡
• በዚህች ዓለም ውስጥ ያለ ማንኛውም ጤናማ የአመራር ስልት ምንጩ የጌታ ቃል ነው፡፡
• በዚህች ዓለም ውስጥ ያለ ማንኛውም ጤና-ቢስ የአመራር ስልት ምንጩ የዚህ ዓለምና አጋንንታዊ ጥበብ ነው፡፡

1. ሰማያዊው የአመራር ጥበብ

• “13ከእናንተ መካከል” ጥበበኛና አስተዋይ የሆነ ሰው ማን ነው? ሥራውን ከጥበብ በሆነ በመልካም አኗኗር ያሳይ . . . 17ከሰማይ
የሆነችው ጥበብ ግን በመጀመሪያ ንጽሕት ናት፤ በኋላም ሰላም ወዳድ፣ ታጋሽ፣ እሺ ባይ፣ ምሕረትና መልካም ፍሬ የሞላባት፣ አድልዎና
ግብዝነት የሌለባት ናት። 18የጽድቅም ፍሬ ሰላምን ለሚያደርጉ በሰላም ይዘራል” ያዕ. 3፡13-18
• ሰማያዊው የአመራር ጥበብ የክርስቶስን ማንነት ከተላበሰ ማንነትና ከመልካም ባህሪይ የሚመነጭ ነው፡፡

2. የዚህች ዓለም ጥበብ

• “14ነገር ግን መራራ ቅናትና ራስ ወዳድነት በልባችሁ ቢኖር ኵራት አይሰማችሁ፤ እውነትንም አትካዱ። 15እንዲህ ያለችዋ ጥበብ ከላይ
አይደለችም፤ ነገር ግን ከምድር፣ ከሥጋና ከአጋንንት ናት። 16ቅናትና ራስ ወዳድነት ባሉበት ስፍራ በዚያ ሁከትና ክፉ ሥራ ሁሉ ይገኛሉ”
ያዕ. 3፡13-18
• የዚህች ዓለም የአመራር ጥበብ ምንጩ ምድራዊ፣ ስጋዊና አጋንንታዊ ነው፡፡

የውይይት ሃሳቦች

• ባለንበት ዘመን የዚህች ዓለም (የምድር፣ የስጋ እና የአጋንንት) ጥበብ ወደ አማኞች ሕይወት የሚገባው በምን መንገድ ይመስላችኋል?
• ከዚህች ዓለም ጥበብ ይልቅ ወደ ሰማያዊው ጥበብ ለማድረላት ምን አይነት ልምምድ ያስፈልገናል ብላችሁ ታስባላችሁ?

1 Prepared for NextGen Leaders / ዶ/ር ኢዮብ ማሞ


የመንፈሳዊ አመራር መመሪያ

ክፍል አንድ
የመንፈሳዊ አመራር ሁለንተናዊ ገጽታ
“ይህን ሕዝብ የምትመራው አንተ ነህና በርታ” - ኢያ. 1፡6

“መሪያቸው ከራሳቸው ወገን ይሆናል፤ ገዣቸውም ከመካከላቸው ይነሣል፤ ወደ እኔ አቀርበዋለሁ፤ እርሱም ይቀርበኛል” - ኤር. 30፡21

• ልጅ ሆኖ የማያውቅ አባት መሆን አይችልም፤ ተማሪ ሆኖ የማያውቅም አስተማሪ መሆን ያስቸግረዋል፤ አገልጋይ ሆኖ የማያውቅ ተገልጋይ
መሆን ያዳግተዋል፡፡
• በተመሳሳይ ሁኔታ ተመሪ እና ተከታይ ሆኖ የማያውቅ መሪ መሆን አይችልም፡፡
• መንፈሳዊውን የአመራር ጥበብ ለመከተልና ስኬታ ለመሆን በቅድሚያ እኛ የምሪትን ሕይወት መለማመድ አስፈላጊ ነው፡፡
• ከዚህ በታች የሚገኙትን ከአመራር፣ ከመሪነትና ከተመሪነት ጋር የሚዛመዱ እይታዎች በሙላት ስንለማመድ ሌሎችን በመልካም ተጽእኖ
የመምራትን ብቃት ይሰጠናል፡፡
• ሌሎችን ለመምራት የሚያበቃ የምሪት ሕይወትና ልምምድ አራት ጽታዎችን ያቀፈ ነው፡፡

1. በቃሉ መመራት

• “ሕግህ ለእግሬ መብራት፣ ለመንገዴም ብርሃን ነው” - መዝ. 119፡105


• “ይህ የሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፤ በውስጡ የተጻፈውን ሁሉ በጥንቃቄ እንድትፈጽመውም ቀንም ሆነ ሌት ከሐሳብህ አትለየው፤
ይህን ካደረግህ ያሰብኸው ይቃናል፤ ይሳካልም” - ኢያ. 1፡8
• በሕይወታችን በማንኛውም አይነት የአመራር ተጽእኖ ውስጥ ከመግባታችን በፊት በቃሉ የመመራትን ልምምድ መለማመድ አለብን፡፡

2. በመንፈስ ቅዱስ መመራት

• “በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና” - ሮሜ 8:14


• “የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል” - ዮሐ. 16:13
• በሕይወታችን ለእግዚአብሔር መንፈስ እውቅና እና ስፍራ ስንሰጠው እንደቃሉ የሆነን የምሪት ሕይወት እንለማመዳለን፡፡

3. ራስን መምራት

• “ራስህን አታስተምርምን?” - ሮሜ 2፡21


• “ራስህን አስለምድ” - 1ጢሞ. 4፡7
• የጌታ ቃልም ሆነ መንፈሱ የሚሰጠንን ምሪት ይዘን ራሳችንን ለመምራት
ፈቃደኛ ካልሆንን ከስህተት መንገድ አናመልጥም፡፡

4. ጌታ በሰጠን መሪዎች መመራት

• “የእግዚአብሔርን ቃል የነገሯችሁን መሪዎቻችሁን አስቡ፤ የኑሯቸውን


ፍሬ ተመልከቱ፤ በእምነታቸውም ምሰሏቸው” - ዕብ. 13:7
• “እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፤ በእናንተ መካከል በትጋት የሚሠሩትን፣ በጌታም የበላዮቻችሁና መካሪዎቻችሁ የሆኑትን እንድታከብሯቸው
እንለምናችኋለን፤ ስለ ሥራቸውም በፍቅር እጅግ አክብሯቸው” – 1ተሰ. 5:12-13
• በቃሉና በመንፈሱ የሚሰጠንን ምሪት በመከተል ራሳችንን ስንመራ፣ በተሾሙልን መሪዎች የመመራትን ልምምድ እናዳብራለን፡፡

የውይይት ሃሳቦች

• አንድ አማኝ ቃሉን አውቃለሁና የመንፈስ ቅዱስ ምሪት አለኝ እያለ ራሱን የማይመራ ከሆን ለምን አይነት ሁኔታ ሊጋለጥ ይችላል?
• አንድ አማኝ ራሱን በራሱ እንደሚመራ እያሰበና እየተናገረ ለቤተ ክርስቲያን አመራር ራሱን ካላስገዛ ለምን አይነት ሁኔታ ሊጋለጥ ይችላል?

2 Prepared for NextGen Leaders / ዶ/ር ኢዮብ ማሞ


የመንፈሳዊ አመራር መመሪያ

ክፍል ሁለት
መልካም ተጽእኖን የሚያመጣ ራእይ
“ባሪያውን ዳዊትን መረጠ፤ ከበጎች ጕረኖ ውስጥ ወሰደው፤ ለሕዝቡ ለያዕቆብ፣ ለርስቱም ለእስራኤል እረኛ ይሆን ዘንድ፣ የሚያጠቡ በጎችን
ከመከተል አመጣው። እርሱም በቅን ልቡ ጠበቃቸው፤ ብልኀት በተሞላ እጁም መራቸው” - መዝ. 78፡70-72

• የመልካም ተጽእኖ መሪዎች ለመሆን አራት ልምምዶች ያስፈልጉናል፡- 1) ራእይ፣ 2) ዲሲፕሊን፣ 3) መልካም ባህሪይ፣ እና 4) ክህሎት፡፡
• “እንደ ልቤ የሆነና እኔ የምሻውን ሁሉ የሚያደርግ የእሴይን ልጅ ዳዊትን አገኘሁ” (የሐዋ. 13፡22) ከተባለለት ከዳዊት ሕይወት
እንመለከታለን፡፡

1. ዳዊት የተጽእኖ መሪ ለመሆን ራእይን የተቀበለ ሰው ነበር፡- “ባሪያውን ዳዊትን መረጠ” - ቁ. 70


2. ዳዊት ለተቀበለው የመሪነት ራእይ የሚመጥን ዲሲፕሊን ያዳበረ ሰው ነበር፡- “ከበጎች ጕረኖ ውስጥ ወሰደው፤ ለሕዝቡ ለያዕቆብ፣ ለርስቱም
ለእስራኤል እረኛ ይሆን ዘንድ፣ የሚያጠቡ በጎችን ከመከተል አመጣው” - ቁ. 70-71
3. ዳዊት ለተቀበለው የመሪነት ራእይ የሚመጥን ባህሪይ ነበረው፡- “እርሱም በቅን ልቡ ጠበቃቸው” - ቁ. 72
4. ዳዊት ለተቀበለው የመሪነት ራእይ የሚመጥን ክህሎት ነበረው፡- “ብልኀት በተሞላ እጁም መራቸው” - ቁ. 72

የራእይ እውነታዎች
አምስቱ የራእይ የመነሻ ሃሳብ፡-

“ከዐሥራ አራት ዓመት በኋላም፣ ዳግመኛ ወደ ኢየሩሳሌም ወጣሁ፤


በዚህ ጊዜ ከበርናባስ ጋር ነበርሁ፤ ቲቶንም ይዤው ሄጄ
ነበር። ካገኘሁትም መገለጥ የተነሣ ወደዚያ ሄድሁ፤ በአሕዛብ መካከል
የምሰብከውን ወንጌል ለእነርሱም ገለጥሁላቸው። ይሁን እንጂ፣
ምናልባት በከንቱ እየሮጥሁ ወይም ሮጬ እንዳይሆን በመሥጋት፣
ዋነኞች ለሚመስሉት ብቻ በግል ይህን አስታወቅኋቸው” - ገላ. 2፡1-2

1. ራእይ የምንሄድበትን አቅጣጫ፣ ርቀትና ስፋት ይወስናል፡-


“ካገኘሁትም መገለጥ የተነሣ ወደዚያ ሄድሁ”
2. ራእይ ከስፍራና ከሕዝብ ጋር ይነካካል፡- “በአሕዛብ መካከል
የምሰብከውን ወንጌል”
3. ራእይ ግልጽ የሆነ ተግባቦትን ይጠይቃል፡- “ለእነርሱም
ገለጥሁላቸው”
4. ራእይ ከፍኛ የሆነን ትኩረት ይሰጣል፣ ይጠይቅማል፡- “ምናልባት በከንቱ እየሮጥሁ ወይም ሮጬ እንዳይሆን በመሥጋት”
5. ራእያችንን ለማን እንደምንነግር ጥንቃቄን ይፈልጋል፡- “ዋነኞች ለሚመስሉት ብቻ በግል ይህን አስታወቅኋቸው”

አምስቱ መሰረታዊ ትርጓሜች፡-

1. ራእይ፡- “የምናደርገውን ነገር የምናደርገው ለምንድን ነው?”


2. ተልእኮ፡- “የምናደርገው ነገር ምንድን ነው?”
3. እሴት፡- “የምናደርገውን ነገር የምናደርገው እንዴት ነው?”
4. ግብ፡- “ወደራእዩ የሚወስዱን በጊዜ ገደብ የተቀመጡ ተግባሮች ምን ምን ናቸው?”
5. ተግባር፡- “በተሰጣቸው የቀን ገደብ መሰረት ቅድመ-ዝግጅት በማድረግ የምትገብራቸው ተግባሮች ምን ምን ናቸው?”

አምስቱ ራእይ ያልሆኑ ነገሮች

1. ጌታን የማክበርና የማስከበር ፍላጎት የመነሻ ሃሳብና የሁሉ ነገር መጨረሻ እንጂ ራእይ አይደለም፡፡
2. አንድን ተግባር የማድረግ ፍላጎት ለራእይ መዋጮ የሚያደርግ ተግባር እንጂ ራእይ አይደለም፡፡
3. የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ራእይን ለማስፈጸም የሚሰጠን ጸጋ ነው እንጂ ራእይ አይደለም፡፡
4. በተፈጥሮ ያገኘነው ወይም በስልጠና ያዳበርነው የሞያ ክህሎት ራእይን በተሻለ መንገድ ለመፈጸም ያግዛል አንጂ ራእይ አይደለም፡፡
5. የትንቢትና የመገለጥ መልእክት ራእይን ለማረጋገጥ ሊመጣ ይችላለ እንጂ ራእይ አይደለም፡፡

3 Prepared for NextGen Leaders / ዶ/ር ኢዮብ ማሞ


የመንፈሳዊ አመራር መመሪያ

የራእይ ጤናማ ሂደትና ባህሪይ


“በቀላሉ እንዲነበብ፣ ራእዩን ጻፈው፤ በሰሌዳም ላይ ቅረጸው። ራእዩ የተወሰነለትን ጊዜ ይጠብቃልና፤ ስለ መጨረሻውም ይናገራል፤ እርሱም
አይዋሽም፤ የሚዘገይ ቢመስልም ጠብቀው፤ በርግጥ ይመጣል፤ ከቶም አይዘገይም” - ዕንባ. 2፡2-3

• የራእይ ምንጩም ሆነ የአሰራሩ ሂደት መለኮታዊ ስለሆነ ሁል ጊዜ ከሰውኛው ምልከታ ጋር እንደተጋጨ ይኖራል፡፡
• መለኮታዊ ምንጭና መንፈሳዊ ባህሪይ ያለውን ራእይን ለመገንዘብና አብሮ ለመፍሰስ መንፈሳዊ ግንዛቤን ይጠይቀናል፡፡
• ራእይን አስመልክቶ በእኛና በጌታ መካከል ያለውን የምልከታ ክፍተት ለመሰተካከል ትርጉሙንና አሰራሩን መገንዘብ የግድ ነው፡፡

1. ራእይ አጭር፣ ግልጽና ቀላል መሆን አለበት


• “በቀላሉ እንዲነበብ ራእዩን ጻፈው” - ቁ. 2
• የራእይ ገለጻ ከተንዛዛና ውስብስብ ከሆነ፣ የራእይ አለመኖርን ወይም ራእይ ኖሮ ነገር ግን ግንዛቤ አለመኖርን ሊጠቁም ይችላል፡፡

2. ራእዩ መጻፍ አለበት


• “ራእዩን ጻፈው፤ በሰሌዳም ላይ ቅረጸው” - ቁ. 2
• ራእይን መጻፍ በአንድ ጎኑ የራእያችንን መነሻ ለማስታወስ
ሲጠቅም፣ በሌላ ጎኑ ደግሞ ሰዎች በቀላሉ እንዲገነዘቡት
ያግዘናል፡፡

3. ራእይ ጊዜ ይፈልጋል
• “ራእዩ የተወሰነለትን ጊዜ ይጠብቃልና” ቁ. 3
• ራእይ “ሂደታዊ” እንጂ “ቅጽፈታዊ” አይደለም፤ ስለዚህ ማድረግ
የሚገባንን በማድረግ ሂደቱን ልንጠብቅለት ይገባል፡፡

4. ራእይ የመጨረሻውን ውጤት ነው የሚያሳየን


• “ስለ መጨረሻውም ይናገራል” - ቁ. 3
• ራእይ በመጀመሪያ በአይነ-ህሊናችን አይተነው የተነሳነውና
ከብዙ ስራ በኋላ በአይነ-ስጋችን የምናየው ነገር ነው፡፡

5. ራእይ እውነትና እውን ነው


• “እርሱም አይዋሽም” - ቁ. 3
• ማንኛውም መልካምና ትክክለኛ ራእይ ምንጩ እግዚአብሔር ስለሆነ ተገቢውን ሂደት ከተከተል መፈጸሙ አይቀርም፡፡

6. ራእይ እስከሚከናወን ይፈትናል


• “የሚዘገይ ቢመስልም ጠብቀው” - ቁ. 3
• ራእይ “የሚዘገየው” እኛ በጠበቅነው ጊዜና ሁኔታ ስለማይከናወን ስለሆነ ከመጠበቅ ውጪ ምርጫ የለንም፡፡

7. ራእይ መሳካቱና መፈጸሙ አይቀርም


• “በርግጥ ይመጣል፤ ከቶም አይዘገይም” - ቁ. 3
• የራእይን ትክክለኛ ሂደት ከተከተልን ራእዩ ጌታ ባሰበው ጊዜና እሱ በፈቀደው መንገድ እንደሚመጣ ቃሉ ያረጋግጥልናል፡፡

የውይይት ሃሳቦች

• አብዛኛው አማኝ የራእይን ትክክለኛ ትርጉም የተገነዘበና የግል ራእዩን ለይቶ የሚያውቅ ይመስላችኋል? መልሳችሁ “አይመስለኝም” ከሆነ
ምክንያቱ ምን ይመስላችኋል?
• “አምስቱ ራእይ ያልሆኑ ነገሮች” በሚለው ርእስ ስር ከጠቀስናቸው አምስት ነጥቦች መካከል ራእይ እንደሆነ አስባችሁት የምታውቁት ነጥብ
የትኛው ነው? አሁን ከትምህርቱ የተነሳ ምን ማስተካከያ የምታደርጉ ይመስላችኋል?
• እጃችሁ ላይ ባለው ወረቀት በአጭሩ ራእያችሁ ምን እንደሆነ ለመጻፍ ሞክሩ፡፡

4 Prepared for NextGen Leaders / ዶ/ር ኢዮብ ማሞ


የመንፈሳዊ አመራር መመሪያ

ክፍል ሶስት
ለራእያችን የሚመጥን ዲሲፕሊን
“ለውድድር የሚዘጋጅ ማንኛውም ሰው በሁሉም ነገር ራሱን ይገዛል” – 1ቆሮ. 9፡25

• ዲሲፕሊን ማለት ዓላማችንን በሚመጥንና ሁለ-ገብ በሆነ መልኩ ራስን መግዛት ወይም መቆጣጠር ማለት ነው፡፡
• ዲሲፕሊን ለራእዩ ሲባል ማድረግ የማይፈልጉትን ማድረግ ወይም ማድረግ የሚፈልጉትን አለማድረግንም ይነካል፡፡
• “በሁሉም ነገር ራሱን ይገዛል” (ቁ. 25) የሚለው ሃሳብ ዲሲፐልን ሁለ-ገብ ወይም ሁለንተናዊ እንደሆነ ጠቋሚ ነው፡፡

ዲሲፕሊን በሶስት መልኩ ይመጣል

1. ራስን በማስለመድና በማስገደድ - “ለእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወት ራስህን አሠልጥን” – 1ጢሞ. 4፡7
2. በትምህርትና በስልጠና - “ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለባቸው ናቸው፤ ለማስተማር፣ ለመገሠጽ፣ ለማቅናት በጽድቅም
መንገድ ለመምከር ይጠቅማሉ” – 2ጢሞ. 3፡16
3. በቅጣትና በቁጥጥር - “ቅጣት ሁሉ በወቅቱ የሚያሳዝን እንጂ ደስ የሚያሰኝ አይመስልም፤ በኋላ ግን ለለመዱት ሰዎች የጽድቅና የሰላም ፍሬ
ያስገኝላቸዋል” - ዕብ. 12፡11

ዲሲፕሊን ጊዜያዊ ነው

ለእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወት ራስህን አሠልጥን። 8የአካል ብቃት ልምምድ ለጥቂት ነገር ይጠቅማልና፤
ለእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወት ራስን ማሠልጠን ግን ለአሁኑም ሆነ ለሚመጣው ሕይወት ተስፋ ስላለው
ለሁለቱም ይጠቅማል” - 1ጢሞ. 4:7-8

• በዲሲፕሊን መኖር ማለት ሁል ጊዜ ራስን በማስገደድ፣ በቅጣትና በቁጥጥር መኖር ማለት ሲሆን
መጨረሻው ግን እሱ አይደለም፡፡
• በዲሲፕሊን፣ ማለትም ራስን በማስለመድና በማስገደድ፣ በትምህርትና በስልጠና፣ እንዲሁም
በቅጣትና በቁጥጥር ማድረግ የጀመርነውን ነገር ወደ ልማድ ደረጃ እስከሚደርስ ድረስ
ልንደጋግመው ይገባል፡፡
• ስለዚህም የዲሲፕሊን ዋነኛ ዓላማ አንድ ተግባር ከመደጋገሙ የተነሳ ልማድ ወደመሆን እንዲመጣ
ማድረግ ነው፡፡

ከዲሲፕሊን እስከ ልማድ

• “እንደ ልማዱም ደግሞ ያስተምራቸው ነበር” - ማር. 10:1


• “ሕዝቡም ወጥተው እንደ ልማዱ ያደርግላቸው ዘንድ እየጮኹ ይለምኑት ጀመር” - ማር. 15:8
• “እንደ ልማዱም በሰንበት ቀን ወደ ምኵራብ ገባ፥ ሊያነብም ተነሣ” - ሉቃ. 4:16
• “ወጥቶም እንደ ልማዱ ወደ ደብረ ዘይት ሄደ፤ ደቀ መዛሙርቱም ደግሞ ተከተሉት” - ሉቃ. 22:39
• “ጳውሎስም እንደ ልማዱ ወደ እነርሱ ገባ” - የሐዋ. 17:2
• “ዳንኤልም ዐዋጁ እንደ ወጣ ባወቀ ጊዜ ወደ ቤቱ ሄደ፤ መስኮቶቹ በኢየሩሳሌም አንጻር ተከፍተው ባሉበት በሰገነቱ ቀድሞ ያደርግ እንደ
ነበረው በቀን ሦስት ጊዜ ተንበርክኮ ጸለየ፤ አምላኩንም አመሰገነ” - ዳን. 6:10

ዲሲፕሊንን እስከ ልማድ ደረጃ የማድረስ ልምምድ

1. ለዲሲፕሊን ልምምድ ያነሳሳኝን ግብ ማወቅ፡፡


2. እዚያ ግብ ላይ ለመድረስ ምን አይነት ዲሲፕሊን እንደሚያስፈልገኝ መለየት፡፡
3. የዲሲፕሊኑን ልምምድ በትንሹ (baby steps) መጀመር፡፡
4. ዲሲፕሊኑ ልማድ እስከሚሆን ድረስ በፍጹም አለማቆም፡፡
5. አልፎ አልፎ ማቆም ሲከሰት ተስፋ ሳይቆርጡ እንደገና መጀመር፡፡
6. የዲፕሊኑን ልምምድ ባቆመው ምን ጉዳት እንደሚያስተክል በግልጽ አስቦ መገንዘብ፡፡
7. በዲፕሊን የጀመርኩት ነገር ልማድ እስከሚሆንና ግቤን እስከምመታ ድረስ ብቀጥለው የሚሰጠኝን ጥቅም በግልጽ አስቦ መገንዘብ፡፡
8. በአንድ ነገር ላይ ዲሲፕሊን ማዳበር ፈጽሞ ሲያቅተኝ አጠገቤ የሚከታተለኝ (የሚቆጣጠረኝ) ሰው ማድረግ፡፡

5 Prepared for NextGen Leaders / ዶ/ር ኢዮብ ማሞ


የመንፈሳዊ አመራር መመሪያ

ሰባቱ የራእይ መሰረቶች


ራእያችንን ከለየንና መከተል ከጀመርን በኋላ ራእዩ ዘላቂና ስኬታማ እንዲሆን የሚሸከሙ ሰባት ገጽታ ያላቸው ጤናማ ልምምዶች አሉ፡፡ እነዚህ
ልምምዶች የሚከተሉት ናቸው፡፡

1. መንፈሳዊ ገጽታ፡- በክርስትና ሕይወታችን እንደቃሉ የሆነንና ጤናማ ሕይወት መኖር፡፡


2. የስሜት ገጽታ፡- የራስንም ሆነ የሌሎችን ሰዎች ስሜት መገንዘብና አያያዙን ማወቅ፡፡
3. አካላዊ ገጽታ፡- ወደ አካላችን የሚገባውንና የሚወጣውን በመቆጣጠር ለእድሜያችን የሚመጥንን አካላዊ ጤንነት ማዳበር፡፡
4. ማሕበራዊ ገጽታ፡- ባለን ማሕበራዊ ሕይወት ጤናማ እና ሚዛናዊ ግንኙነትን መለማመድ፡፡
5. የአእምሮ ገጽታ፡- በአዎንታዊነትና ማወቅ ያለበትን ነገር በማወቅ የተሞላ አእምሮን ማሳደግ፡፡
6. የፍቅር/የትዳር ሕይወት ገጽታ፡- ባለን የፍቅር፣ የትዳር ወይም ለብቻ የመሆን ሕይወት ደስተኛ እና የተደላደልን መሆን፡፡
7. የገንዘብ ገጽታ፡- ለግላችን፣ ለቤተሰባችንና ራእያችንን ለመከታተል የሚያስችል የገንዘብ አቅም መገንባት፡፡

ስለዲሲፕሊን ከተማርነው ሃሳብ በመነሳት ከላይ ከተጠቀሱት ዘርፎች መካከል ዲሲፕሊን የሚጠይቁት የትኞቹ እንደሆኑ ተወያዩ፡፡ ዲሲፕሊን
የሚጠይቁት ዘርፎች ምን ምን አይነት ዲሲፕሊን እንደሚጠይቁ በመወያየት ከዚህ በታች አስፍሩ፡፡

1. መንፈሳዊ ገጽታ፡-

2. የስሜት ገጽታ፡-

3. አካላዊ ገጽታ፡-

4. ማሕበራዊ ገጽታ፡-

5. የአእምሮ ገጽታ፡-

6. የፍቅር/የትዳር ሕይወት ገጽታ፡-

7. የገንዘብ ገጽታ፡-

6 Prepared for NextGen Leaders / ዶ/ር ኢዮብ ማሞ


የመንፈሳዊ አመራር መመሪያ

ክፍል አራት
ለራእያችን የሚመጥን ባህሪይ
“እንግዲህ በጌታ እስረኛ የሆንሁ እኔ፣ ለተቀበላችሁት ጥሪ የሚገባ ኑሮ ትኖሩ ዘንድ እለምናችኋለሁ። ፍጹም ትሑታንና ገሮች ሁኑ፤ እርስ
በርሳችሁም በፍቅር እየተቻቻላችሁ ትዕግሥተኞች ሁኑ። በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ” - ኤፌ. 4፡1-3

• ጌታ ለሰጠን ራእይ ስኬታማነት ወሳኝ ከሆኑ አንጋፋ ነገሮች መካከል ባህሪያችን አንዱ ነው፡፡
• የአዲስ ኪዳን መልእክቶች ስለ ደህንነታችን ከመናገር ባሻገር የሚያወሩት የወንጌል ጥሪያችን ስለሚፈልግብን ባህሪይ ነው፡፡
• ይህ እውነታ የጌታን ስራ ከመስራታችን በፊት እኛ የመሰረታችንን ጉዳይ አስፈላጊነት ያጎላዋል፡፡
• ለተቀበልነው ጥሪና ራእይ የሚገባ ባህሪይና የኑሮ ዘይቤ የሚከተሉትን ያጠቃልላል፡፡

1. ትህትናና ገርነት፡- “ለተቀበላችሁት ጥሪ የሚገባ ኑሮ ትኖሩ ዘንድ . . . ፍጹም ትሑታንና ገሮች


ሁኑ”
• መብተኝነትን የመጣል ትህትና፡- “ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን ሊለቀው እንደማይገባ
አድርጎ አልቈጠረውም” - ፊል 2፡6
• ወደሌሎቹ አቅም ወረድ የማለት ትህትና፡- “በሰውም አምሳል ተገኝቶ፣ ራሱን ባዶ አደረገ፤
ሰው ሆኖ ተገልጦም፣ ራሱን ዝቅ አደረገ” ፊል 2፡7-8
• እስከ ጥግ የመታዘዝ ትህትና፡- “እስከ ሞት፣ ያውም በመስቀል ላይ እስከ መሞት ድረስ ታዛዥ
ሆነ” - ፊል 2፡5-8

2. መቻቻልና ትእግስት፡- “ለተቀበላችሁት ጥሪ የሚገባ ኑሮ ትኖሩ ዘንድ . . . እርስ በርሳችሁም


በፍቅር እየተቻቻላችሁ ትዕግሥተኞች ሁኑ”
• በትእግስት መስማማት፡- “እርስ በርሳችሁም ተስማሙ” - ማር. 9፡50
• በትእግስት መቀባበል - “እርስ በርሳችሁ ተቀባበሉ” - ሮሜ 15፡7
• በትእግስት መሸካከም - “እርስ በርሳችሁ ሸክም ተሸካከሙ” - ገላ. 6፡2

3. ሰላምና አንድነት፡- “ለተቀበላችሁት ጥሪ የሚገባ ኑሮ ትኖሩ ዘንድ . . . በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ” - ኤፌ. 4፡1-3
• አንድ ልብ (እምነት)፡- “ያመኑትም ሁሉ በአንድ ልብና . . . ተስማምተው ነበር” - የሐዋ. 4፡32
• አንድ ሃሳብ (ስሜትና ፈቃድ)፡- “ያመኑትም ሁሉ በአንድ . . . ሐሳብ ተስማምተው ነበር” - የሐዋ. 4፡32
• አንድ አቅርቦት (ሀብት)፡- “ያመኑትም ሁሉ . . . ያላቸውም ሁሉ የጋራ ነበር እንጂ የራሱ የሆነውን ሀብት እንኳ እንደ ግሉ የሚቈጥር
ማንም አልነበረም” - የሐዋ. 4፡32

ማጠቃለያ፡- ራእያችንን ስኬታማ በመሆኑ ሂደት ላይ የባህሪይ ጉዳይ ወሳኝና አስፈላጊ ስለሆነ ሐዋርያው በብዙ መልኩ ይገልጸዋል፡፡

1. ያበረታታል
• “ወደ መንግሥቱና ወደ ክብሩ ለጠራችሁ ለእግዚአብሔር እንደሚገባ ትኖሩ ዘንድ አበረታታናችሁ” – 1ተሰ. 2፡12
• አንዳንድ ጊዜ ለራእያችን ከሚመጥን ባህሪይ ወጣ የምንለው በአንዳንድ የሕይወት ሂደቶች ተስፋ ስንቆርጥ ነው፡፡

2. ያጽናናል
• “ወደ መንግሥቱና ወደ ክብሩ ለጠራችሁ ለእግዚአብሔር እንደሚገባ ትኖሩ ዘንድ … አጽናናችሁ”– 1ተሰ. 2፡12
• አንዳንድ ጊዜ ለራእያችን ከሚመጥን ባህሪይ ወጣ የምንለው በኃዘን ውስጥ ስንሆን ነው፡፡

3. ይለምናል
• “ወደ መንግሥቱና ወደ ክብሩ ለጠራችሁ ለእግዚአብሔር እንደሚገባ ትኖሩ ዘንድ … አጥብቀንም ለመንናችሁ” – 1ተሰ. 2፡12
• አንዳንድ ጊዜ ለራእያችን ከሚመጥን ባህሪይ ወጣ የምንለው በፍላጎት ማጣትና በግድ-የለሽነት ነው፡፡

የውይይት ሃሳቦች

ባለፈው ስልጠና ከጠቀስናቸው ሰባት የራእይ መሰረቶች መካከል የመልካም ባሪይ ጉዳይ በከፍተኛ ደረጃ የሚመለከታቸው የትኞቹ እንደሆኑ፣ ምን
አይነት መልካም ባህሪይን እንደሚጠይቁ እና የእነዚህ ባህሪያት መጉደል ምን መዘዝ ሊኖረው እንደሚችል ተወያየዩ፡፡

7 Prepared for NextGen Leaders / ዶ/ር ኢዮብ ማሞ

You might also like