Professional Documents
Culture Documents
የአህመድ አብዱ ጣሂር ትርጉም
የአህመድ አብዱ ጣሂር ትርጉም
ከሚሴ
የፍ/መ/መ/ቁ 3129/2016
ቀን 26/5/2016
ዐ/ህግ/ወ/መዝ/ቁ ፦151/2016
የፖ/ጽ/መዝ/ቁጥር ፦269/2016
ተከሳሽ ፦አህመድ አብዱ ጣሂር እድሜ ፦17 ስራ ፦ አርሶ አደር ስልክ ቁጥር.....አድራሻ ወረዳ ፦አርጡማ ፉርሲ
ቀበሌ፦ጎልቦ አርባ ጎጥ፦ቡርቃ
ወንጀሉ
የወንጀሉ ዝርዝር
ተከሳሽ ሰው ለመግደል በማሰብ በቀን 27/01/2015 ዓ,ም ከቀኑ በግምት 6፡00 ሰአት ሲሆን በአርጡማ ፉርሲ
ወረዳ ጎልቦ ቀበሌ ጎጥ ቡርቃ ተብሎ በሚጠራበት ቦታ ልጅ መታ በሚል ምክንያት ሟች ሁሴን በሺር
የሚባለውን ቁጥሩ 17292 የሆነውን ክላሽ በሚባለው የጦር መሳሪያ በአንድ ጥይት ቀኝ እግሩ ፣ በአንዱ ጥይት
ልቡ ላይ እንዲሁም በአንድ ጥይት ግንባሩ ላይ በአጠቃላይ በሶስት(3) ጥይት በመምታት በጭካኔ ፣ አሰቃቂ ና
አደገኛ በሆነ ሁኔታ ከባድ የሆነ ጉዳት አድርሶበት ስለገደለው በከባድ የሰው ነፍስ ግድያ ወንጀል በመፈፀም
ተከሷል ።
ሀ.የሰው ማስረጃ
1 ኛ አብዱሶመድ ሁሴን በሺር አድራሻ፦ወረዳ አርጡማ ፉርሲ ቀበሌ ፦ ጎልቦ አርባ ስልክ....
2 ኛሀሊማ መሀመድ ጅብሪል አድራሻ፦ወረዳ አርጡማ ፉርሲ ቀበሌ፦ጎልቦ አርባ ስልክ 0960977079
ለ. የሰነድ ማስረጃ
> አልቀረበም
ከሚሴ ቀን፦
አመልካች አህመድ አብዱ በቀረበብኝ ክስ ከፍ/ፍ/ቤቱ በቀን 5/06/2016 በዋለው ችሎት እንድከላከል ብይን
ሰጥቷል።በዚህም መሰረት መከላከያ ምስክሮቼን አንደሚከተለው አቀርባለሁ፦
2. መሀመድ አሊይ ያሲን አድራሻ አርጡማ ፉርሲ ወረዳ ጎልቦ ቀበሌ 3………….አድራሻ
.......4. ......................አድራሻ ...............
ቁጥር ፦529/2016
ለኦሮ/ብሄ/ዞን/ከፍ/ፍ/ቤት ቀን ፦ 29/06/2016
የዐ/ህግ/ወን/መዝ/ቁ ፦151/2016
የፍ/ቤቱ/ወን/መዝ/ቁ ፦0205655
ተከሳሽ በሰው ግድያ ተከሶ ለፍ/ቤቱ ባቀረብነው መሰረት መዝገቡ ተከፍቶ ክርክር ላይ መሆናችን ይታወቃል:
ይሁን እንጂ ከሳሽ ዐ/ህግ ክሱን ሲያቀርብ ወንጀሉ የተፈጸመበትን መሳሪያ ኤግዚቢት ተደርጎ አልተጠቀሰም
።ስለዚህ የተከበረው ፍ/ቤት በወ/ስ/ስ/ህግ አንቀጽ 143/1 እና 2 መሠረት ይህ የተያዘው ኤግዚቢት
• ቁጥሩ 17292 የሆነውን የክላሽ መሳሪያ እና ሶስት ጥይት እንደ ኤግዚቢት እንዲያዝልን እንጠይቃለን ።
የመ/ቁጥር ፦0205655
ቀን ፦26/05/201
ዳኞች
አምዴ ጋቢሳ
ሁሴን ሀሰን
መሀመድ አብደላ
የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን ፍትህ መምሪያ ዐ/ህግ በቁጥር 3129 በቀን 26/05/2015 በተጻፈው ተከሳሽ በከባድ የሰው
ነፍስ ግድያ ወንጀል ተከሷል በማለት የክስ ቻርጅ አቅርቧል ። ስለዚህ መዝገቡ ተከፍቶ ለችሎት ቀርቧል።
ትዕዛዝ
የኬሚሴ ከተማ ማረሚያ ቤት የዐ/ህግን ክስን እና የፍ/ቤቱን መጥሪያ ወረቀት ለተከሳሹ ሰጥቶት ተከሳሹንም
በቀን 05/04/2015 ዓ.ም ቀነ ቀጠሮ እንዲያቀርብ ሆኖ ተከሳሽም የክስ ተቃውሞ ካለው
የመዝ/ቁጥር፦05655
ቀን 04/07/2015
ዳኞች
ፈጠነ
አምዴ ጋቢሳ
ሁሴን ሀሰን
ትዕዛዝ
ዳኞች
1, አሊ መሀመድ
2, ሁሴን ሀሰን
3. አምዴ ጋቢሳ
መዝገቡ ያደረው የተከሳሽ ጠበቃን ለመጠበቅ ነበር : ቀርቧል።ነገር ግን በጸጥታ ችግር ምክንያት
አልተሰራም።
ትዕዛዝ
ክሱን ለመስማት ቀጠሮ ለ 25/08/2015
መዝ/ቀጥር:05655
ቀን : 25/08/2015
ዳኞች
2.አምዴ ጋቢሳ
3.ሁሴን ሀሰን
መዝገቡ ያደረው ተከሳሽ ጠበቃ ቢቀርብ ለመጠበቅ ነበር, አልቀረበም። መንግስት ጠበቃ ያቁምልኝ
በማለት አሳስቧል።
°ተከሳሽ ፦ አህመድ አብዱ ጣሂር የሆነው አድራሻ አርጡማ ፉርሲ ወረዳ ጎልቦ አርባ ቀበሌ የሆነው ቀርቦ
የዐ/ህግ ክስ ተነቦለት ከተገነዘበ ቡሃላ ተከላካይ ጠበቃው የክስ ተቃውሞ የለንም ብሏል። ተከሳሽም ወንጀሉን
አልፈጸምኩም ጥፋተኛ አይደለሁም በማለት ክዶ ተከራክሯል። ዐ/ህግም ምስክሮች ስላሉን አቅርበን
እንድናሰማ ቀጠሮ ይሰጠን በማለት አሳስቧል።
ትዕዛዝ
የዐ/ህግ ምስክሮችን ለመጠበቅ ቀጠሮ 22/09/2015
ቀን 22/09/2015
ዳኛች
1, አሊ መሀመድ
2, ሁሴን ሀሰን
3, አምዴ ጋቢሳ
ትዕዛዝ
ቀን 27/10/2015
ዳኛች
2.ሁሴን አደም
3.አምዴ ጋቢሳ
ትዕዛዝ
መዝ/ቁጥር 05655
ቀን 06/02/2016
ዳኞች
2.ሁሴን ሀሰን
3.አምዴ ጋቢሳ
ቀን 05/03/2016
ዳኞች፦1, አሊ መሀመድ
2, ሁሴን ሀሰን
3, አምዴ ጋቢሳ
መዝገቡ ያደረው የዐ/ሀግ ምስክሮች መቅረብ ለመጠበቅ ነበር በዚህም መሠረት ሁለት ሰዎች ቀርበው
የምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተው ቃላቸው በቴፕ ተቀድቷል ።
ትዕዛዝ
የመዝ/ቁጥር፦0205655
ቀን፦5/03/2016
ዳኞች፦1.አሊ መሃመድ
2.ሁሴን ሀሰን
3.አምዴ ጋቢሳ
መዝገቡ ያደረው የዐ/ህግ ምስክሮችን ከቀረቡ ለመጠበቅ ነበር። ተሟልተው ቀርበዋል ።ዐ/ህግም ጭብጥ
ያስያዘው ምስክሮቻችን ለክሳችን እንዲመሰክሩልን በማለት ጭብጥ አስይዘዋል።
1 ኛ የዐ/ህግ ምስክር
ስም፦አብዱሶመድ ሁሴን እድሜ፦13 ስራ ፦ ተማሪ አድራሻ ወረዳ ፦ አርጡመሠ ፉርሲ ቀበሌ፦ጎልቦ አርባ ዛሬ
ምስክር ሁኜ ነው የመጣሁት ፡ ተከሳሽን አውቀዋለሁ ፡ አህመድ አብዱ ጣሂር ይባላል ፡ ዝምድናም ጠብም
አለን።
ተከሳሹ አባቴን ገድሎ ነው የተከሰሰው። የገደለውም በቀን 27/01/2015 ከቀኑ ከ 6:00 _ 7:00 ባለው ነው።
ቦታውም ጎልቦ አርባ ቀበሌ ጎጥ ቡርቃ ይባላል ። በዚህ ቀን የአባቴ ታላቅ የአምስት ልጆች አባት ጋር ሁነን
ከእርሻ ስንገባ ውሃ ቅዳልኝ ብሎኝ ከዚያም ቡሃላ እኛ ወደ ወንዝ ስንወርድ ተከሳሹ ድንጋይ ወደ ታች
ወረወረብን። እኛም ሸሽተን ገብተን ለአባቴ ተናገርን። አባቴም ይህንን ሰምቶ ከቤት ሲወጣ ሲመታው
አይቻለሁ። አባቴ ተመትቶ የሞተበት ቦታ ቡርቃ ይባላል። ተከሳሹ ከታላቅ ወንድሙ ጋር ነው ። ተከሳሹ
አባቴን በጥይት የመታው ቀኝ እግሩን፣ልቡ ላይ እንዲሁም ግንባሩ ላይ መትቶት ወደ ፊት ወጣ። እሱ ሲመታ
እኛ ወደ ታች ሮጥን ።ከዚያም እናቴ ወደ ታች ሩጣ ደርሳ እሱን አንስተው ወደ ላይ መለሱት። ይህ ተከሳሽ
አባቴን በክላሽ ጥይት መትቶት እኛ ወደ ታች ሄደን እሱጋ ስንደርስ ሞቷል ይህን አይቻለሁ።
አባቴን ተከሳሹ ሲመታው ከበትር ውጪ አንድም ነገር በእጁ አልያዘም ነበር። አባቴ ከቤት ወጥቶ በመንገድ ላይ
ወደ ታች ሲሄድ ነው ተከሳሹ የመታው ፡ ቤታችን እና የተከሳሹ ቤትም አይራራቅም። ተከሳሹ አባቴን
ሲመታውም ከቤቴ ሁኜ ነው ያየሁት፡ እንዲሁም ጥይቱም ሲተኮስ እኔ ከቤት ወጥቼ እናቴ ወደዛ እየሮጠች
ነበር። ከቦታው ስደርስ አባቴ ሞቷል። ተከሳሹን ደግሞ ሰዎች ይዘውት ወደ ቤት እየመለሱት ነበር።
2 ኛ የዐ/ህግ ምስክር
ስም፦ሀሊማ መሀመድ ጅብሪል እድሜ፦40 ስራ፦የቤት እመቤት አድራሻ፦ አርጡማ ፉርሲ ወረዳ ጎልቦ
አርባ ቀበሌ
በቀን 27/01/2015 ከቀኑ 6:30 ነው። በአርጡማ ፉርሲ ወረዳ ጎልቦ አርባ ቀበሌ የሞተበት ጎጥ ቡርቃ ይባላል።
የመታውም ምክንያቱ ከዚህ በፊት ወንድሙ መሀመድ አብዱ ጣሂር የሚባል የአምስት ልጆች አባት ነው
ከባለቤቴ ጋር ያጣላቸው። ባለቤቴ ደግሞ ጤና አጥቶ ነበር: እኔ ነኝ የምንከባከበው ከዘመዶቼ ጋር : የዚህን ጤና
የሌለውን ሰው ልጆች አባረው ውሃ ቅዱልን አላቸው። ትንሹ ልጄ አጥር ስር ቆሞ ነበር: ትልቁ ልጄ ደግሞ እኔ
የትምህርት ስኣት እየረፈደብኝ ኘው እኔ ውሃ አልቀዳም ሲለው ድንጋይ ወርውሮበት ትልቁን ልጅ ወደ ወንዝ
እንዲሄድ አደረገ ትንሹ ልጅ መጥቶ በሺር የት አለ ሲባል መሀመድ አብዱ ወደ ወንዝ አባሮታል አለኝ ለምን
ስለው ውሃ ቅዱልኝ ብሎን ነው።ባለቤቴ ጤና የለውም ተኝቶ ነበር : ተንስቶ ባዶ እጁን ሰይዲ የሚባለው ወደ
መስጂድ ሲሄድ አይቶት እሱን በእጁ ይዞ እነሱን ለቆ ወደኔ ቤት እየተመለሰ ነበር። ሊመለስ ሲል ሰይድ
የሚባለው ለሌላው ደወለለት ይህኛው ወደ ቤት ሲመለስ ተከሳሹ ደግሞ በስተጀርባ መጥቶ በስተጀርባው
በመሳሪያ ተኩሶ መታው። ምንድነው ብዬ ቆርቆሮ ተመታ እንዴ ብዬ በስተጀርባ ዙሬ ሳይ ባለቤቴ ወድቋል። እኔ
ስጮህ ሰዎች ተሰባሰቡ።በስተጀርባው ተመቶ በልቡ ላይ ወጣ ከሜዳ እየገባን ነው ጥፋት ምንም የለም።
ጎረቤትም ሩጠው እሱጋ ሲደርሱ እሱ ሞቷል። ተከሳሹን ይዘውት ወደ ቤቱ መለሱት።
መሳሪያው ሲተኮስ እኔ ቤት ነበርኩ የመንገዱ እርቀትም በመንገዱ መሀል አጥር አለ። ሁለታቸውንም አያለሁ ፣
እሱ ሲተኩስም አይቻለሁ፣ እንዲሁም መሳሪያ ይዞ ወደ ላይ ሲመለስ አይቻለሁ ። እነሱ ከቤት ሶስት አላቸው ፡
መሳሪያው ሲተኮስ የወንድሙንም ሚስት
በዛን ቀን ተከሳሹ እና ባለቤቴ ሊጋደሉ የቻሉት ያኛው ሲደውልለት ይህኛው ጠብቆ በመምታት፡ ጤና
የሌለውን ሰው እና መሳሪያ ከእጁ የሌለውን በልጅ ምክንያት ነው የገደሉት።
ትዕዛዝ
መዝገቡን መርምረን ተከሳሹ ይህንን ወንጀል አልፈጸምኩም ጥፋተኛ አይደለሁም በማለት ክዶ ቢከራከርም
የዐ/ህግ ምስክሮች በክሱ መሠረት ስለመሰከሩበት በወ/ስ/ስ ህግ አንቀጽ 142 መሰረት እንዲከላከል በሙሉ
ድምጽ ብይን ሰጥተናል።
ቀን፦11/04/2016
መዝገቡ ያደረው የተከሳሽን መከላከያ ምስክር ለመጠበቅ ነበር በዚሁ መሠረት ቀርበዋል። ነገር ግን በስራ
ብዛት ምክንያት አልተሰራም።
ትዕዛዝ
ቀን፦05/06/2016
ዳኞች፦አሊ መሀመድ
ሁሴን ሀሰን
መሀመድ አብደላ
መዝገቡ ያደረው የተከሳሽን መከላከያ ምስክር መቅረብን ለመጠበቅ መከላከያ ምስክሮቹ ሁለት ሰዎች
ቀርበው የምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተው ቃላቸው በቴፕ ተቀድቷል።
✍ ተርጓሚ፦ መሀመድ ሀሰን የሱፍ
ትዕዛዝ
መዝገ/ቁጥር/0205655
ቀን፦22/06/2016
መዝገቡ ያደረው መርምረን ውሳኔ ለመስጠት ነበር ፡ ነገር ግን መዝገቡ የተጻፈ የመከላከያ ምስክሮችን
መልስ ስለሌለው አልተመረመረም።
ትዕዛዝ
ቀን፦06/07/2016
ሁሴን ሀሰን
መሀመድ አብደላ
ትዕዛዝ 0205655
ቀን፦ 05/06/2016
ዳኞች፦አሊ መሀመድ
ሁሴን ሀሰን
መሀመድ አብደላ
መዝገቡ ያደረው የተከሳሽ መከላከያ ምስክርን ለመስማት ነበር ፡ ባደረው መሰረት ተሟልተው ቀርበዋል።
የተከሳሽ ጠበቃም ጭብጥ ያስዘው ምስክሮቻችን የሚመሰክሩልን ተከሳሽ በቀን 27/01/2015 ሟች ሁሴን
በሺርን ገድሏል፡ነገር ግን ተከሳሽ የገደለው ሟች እሱን ሊመታው ሲመጣ ራሱን ለመከላከል በመሆኑ፡ሟች
ብረት ይዞ ይህንን ተከሳሽ ሲመታው ብረቱን ለመከላከል ብሎ መሳሪያ ይዞ ነበር ተከሳሹ ላይ መሳሪያውን
ሲይዝ በዚህ ምክንያት እዚህ መሀል ላይ መሳሪያ ተተኩሶ ሟች ህይወቱ ያለፈ መሆኑን በማለት
እንዲመሰክሩልን በማለት የጉዳዩን ጭብጥ አስይዛለችች።
ስም..................መሀመድ አልይ
እድሜ ................45
ስራ......................አርሶ አደር
አድራሻ .......ወረዳ ፦ አርጡማ ፉርሲ ቀበሌ ፦ ጎልቦ አርባ ዛሬ ለምን እንደመጣሁ አውቃለሁ የተከሳሽ
መከላከያ ምስክር ሁኜ ነው የመጣሁት ተከሳሽን አውቀዋለሁ አህመድ አብዱ ይባላል። ከእርሱ ጋር ዝምድናም
ሆነ ጠብ የለንም መታሰሩን አውቃለሁ። መታሰሩን አውቃለሁ ሁሴን በሺርን ገድሏል ተብሎ ነው። ሲገለው
አላየሁም።
በቀን 27/1/2015 ዓ.ም 6፡00 ሰኣት ላይ በአርጡማ ፉርሲ ወረዳ በጎልቦ አርባ ቀበሌ በሚባለው አህመድ አብዱ
ጣሂር እጁን ተመቷል ሁሴን በሺር ደግሞ ሞቷል።እኛ ወደ መስጅድ እየሄድን ነበር መሳሪያ መተኮሱን ሰማን
እንጂ በአይናችን አላየንም። መሳሪያው ሲተኮስ ወደዛ ሮጥን ሰዎችም እየወጡ ነው እነሱ ጋር ስንደርስ።
የተመታው ወንድሙ ሰይድ ይባላል እዛው ነበር ፡ መትቶ አልፏል ይህኛውንጉሥ አልፎታል። ሁሴን በሺር
የሚባለው እብድ ነው የራሱን ቤት አቃጥሏል። ጸብ እንዳላቸው አላውቅም። አብዱሶመድ ሁሴን በሺር ወደዛ
መጥቶ እዛው ነበር። ይህ ሟች ወይም ይህ ሁሴን በሺር በእጁ ገጀራ ይዟል፡ተከሳሽን በገጀራ መታው። ይህ
ሁሴን በሺር የተመታውም ከአህመድ ቤት በር አጠገብ ነው። ወንድሙንም መትቶ አህመድ አብዱንም
ለመምታት ወደ ቤቱ ሄደ እሱ አያቱ ጋር ተቀምጦ ነበር።
በቀን 27/1/2015 6:00 ሰኣት ላይ ነው በአርጡማ ፉርሲ ወረዳ ጎርቦ አርባ ቀበሌ ይባላል ቦታውም ከአያቱ ቤት
ፊት ለፊት ጸብ የላቸውም እሱ እብድ ነው። እብድ መሆኑ የታወቀው ሰውንም ቤቱንም አቃጥሏል። እሪታ
ሲሰማ ሩጠን ለሱ ቤት ሰራንለት። ይህ ሟች ሲሞት እኔ እዛው ሰፈር ነበርኩ ለጁሙኣ ወደ መስጅድ እየሄድኩ
ነበር ሌላ ሰው አልነበረም መሀመድ ጋር ሄድን ፡ ተከሳሹ ግራ እጁን ተመቶ ነበር፡ደም አይቻለሁ ፡ ይህ የሚጎላው
በክላሽ ነው የተመታው። ሁለት ጥይት ሲተኮስ እኔ እና መሀመድ ሩጠን ከቦታው ስደረስን ተከሳሹ ተመትቶ
ቆሟል ሟችም ሞቷል። ሟች ፊቱ ላይ ተመቷልብ ሌላ ቦታ አላስተዋልኩም ፡ አላየሁምም አጠገቡ ቆሜ ነበር
ደንግጫለሁ። እነሱ ሲመታቱ እኔ አላየሁም፡ ሟች ገጀራ ይዟል ጩቤ ወገቡ ላይ አለ አላወጣም ቀደም ብሎ
አውጥቶ መልሶት እንደሆነ አላውቅም እጂ ግን ከወገቡ ላይ ታጥቋል። የተመታበት ቦታው የተከሳሹ ነው ፡
ሟችና ተከሳሹ ጎረቤት አይደሉም ይራራቃል። የተመታቱበትን ምክንያት አላውቅም ድሮውንም እብድ ነው
ይባላል። እኛ እዛው ስንደርስ ሌላ ሰው አላየንም ተከሳሱ የጦር መሳሪያ መሬት ላይ ጥሎ ሸሸ እኛ መሳሪያውን
አነሳን።አስታውሳለሁ ተከሳሹ የለበሰው ነጭ በርበራ ነው ጫማውን አላስታውስም ወደ ታች ሸሸ። እኛ
ከሰዎች ጋር ሟችን ይዘን መስጅድ አደረስን። ስናነሳው ሁለተኛው ምስክር ጋር አብረን ነበርን በዚያው ቀን
11:00 ላይ ተቀበረ።
ሟች ሳንጃ/ጩቤ ወገቡ ላይ ታጥቋል ገጀራው ደግሞ እዛው ተቀምጧል ሚስማር መንቀያውም እዛው ነው
ተከሳሹ እና ሟች ከዚህ በፊት ጸብ እንዳላቸው አላውቅም።
ስም፦መሀመድ አብዱ ጣሂር እድሜ፦35 ስራ፦አርሶአደር አድራሻ፦አርጡማ ፉርሲ ወረዳ ጎርቦ አርባ ቀበሌ
በቀን 27/1/2015 6:00 ሰኣት ላይ በአረርጡማ ፉርሲ ወረዳ ጎርቦ አርባ ቀበሌ ቡርቃ ጎጥ ይባላል እኔ መስጅድ
እየሄድኩ ነበር ያየሁት መጀመሪያ ሁሴን በሺር የአህመድን ወንድም ሰይድ የሚባለውን በብረት መትቶት ሄደ
እኛ ደግሞ ከመስጂድ እየወጣን ነበር ከዛም ሁሴን በሺር ከአህመድ ቤት ሄዶ ከአህመድ ጋር ተያይዘው ሲመታቱ
አይቻለሁ። አህመድ መሳሪያ ይዟል ተያይዘው የኮሰውን አላውቅም መሳሪያው ተተኩሶ ስዞር አህመድ ሄዷል።
ሁሴን በሺር ወድቋል ሁሴን በሺር እብድ ነው ቤቱን አፍርሷል እኛ ደግሞ ሰራንለት አብዶ ታስሮ ይቀመጣል
ሰውን ያሯሩጣል ይህንን አይቻለሁ ሁሴን በሺር አጠገብ ብረት ነበር ይህንን አይቻለሁ ሌላ ነገር አላየሁም።
ተከሳ እና ሟች ከዚህ በፊት ጸብ የላየውም ዝምድና አላቸው። እኔ ወንጀሉ ሲፈጸም እኔ ከመስጅድ እያወጣሁ
ነው እኔና መሀመድ አሊ አብረን ነን ርቀት የለውም ማዶ ናት ማዶ ይተያያል 6:00 ሰኣት ላይ ለሶላት መስጂድ
እየሄድን ነበር ሲያያዙ እና ሲሯሯጡ አይቻለሁ ነገር ግን የተኮሰውን አላውቅም። ሁሴን ከፍ አህመድ ቤት ሄዶ
ተያያዙ ተከሳሹ መሳሪያ ይዟል ግን መመታታቸውን አላየሁም ሟች ረጅም የብረት በትር ይዟል ግን ተከሳሹ
ሲመታ አላየሁም። ሟች እና ተከሳሽ ተያያዙ የተያያዙት ደግሞ በክላሽ ሰደፍ ነው ሁለት ጥይት ተተኮሰ ሟች
እግሩ ላይ ተመትቶ ወደቀ። ተከሳሹ መሳሪያው መሬት ጥሎ ሄደ የት እንደሄደ ግን አላየሁም የለበሰውን ልብስ
አላየሁም ራቅ ብሏል የለበሰውን ልብስ አላየሁም።ተከሳሹ ደግሞ ሽርጥ አሸርጧል። ተከሳሹ ግራ እጁን ነው
የተመታው ፡ እነሱጋ ስንሄድ እኔና ከኔ ጋር የመጣው ምስክር አለ። ይህ ሰው ጋር ደግሞ እነ አህመድ
አደም፣ሰይዱ የሱፍ፣አህመድ ሰይድ፣ እብራሂም ብዙ ሰዎች ነበሩ፣የተቀበረበት ቦታ እኔ ሄጃለሁ ምሽትልቅ
12:00 ሰኣት ነበር አንደኛ ምስክሩም ከኔ ጋር ሄዷል። ሟች መጀመሪያ ሰይዲን ነው የመታው። ከመስጂድ
ሲወጣ እብድ ስለሆነ እንዲሁ መታው። ሀኪም ቤት ሄዷል ግን ምን እንደተሰጠው አላውቅም ።
ወንጀሉ የተፈጸመበት ቦታ ከኛ በፊት ሌላ ሰው የለም፡ እኛ መጀመሪያ በሩጫ ከቦታው ደርሰን ከዚያም ቡሃላ
ሌሎች ሰዎች ተሰባሰቡ። ተከሳሹ ሟችን ገድሎ እኔ ቀብር የሄድኩት እነሱ ዝምድና ስላላቸው እና ሟች ደግሞ
እብድ ስለሆነ ነው። ስለዚህ ካሁን በፊት ጸብ የላቸውም፡ ካሁን በፊት ከቤት ሸሽተን ነበር አሁን ግን
ተመልሰናል። ሟቹ ወንድም የለውም የበሰለ ነገርና የሚያስፈልገውን ነገር እኛው ነን የምናደርግለት ቤተሰብ
ስለሆንን ።
✍ ተርጓሚ ፦ መሀመድ ሀሰን የሱፍ
0205655
እነሱ ሲጋደሉ እለቱ ጁሙኣ ነው እኛ ደግሞ ወደ መስጂድ እየሄድን ነው በዚያው ቀን ተቀበረ በማለት መስክሮ
ተመልሷል።
የቀረቡት ምስክሮች በቂ ስለሆኑ ተከሳሹ ሟችን አስቦበት አልገደለውም ማለት ነው ፡ የቀረበው የዐ/ህግ
ምስክርም በተከሳሹ እና በሟች መካከል ምንም ጸብ እንደሌለ፣ ከዚህ በፊት ሟች የአዕምሮ ህመምተኛ ስለሆነ
ማስረጃ መቅረቡን በተጨማሪ በሰው ምስክር የተጣራ በመሆኑ ፡ እንዲሁም ሟች ከተከሳሹ ቤት ሄዶ
ሊመታው ሲል የተመመታ በመሆኑ ፡ አሁን በተከሰሰበት ወንጀል ጥፋተኛ ሊያስብለው ስለማይችል፡ተከሳሹ
ጥፋተኛ ነው ቢባልም እንኳ ራስን መከላከል በማለፍ ተብሎ በህጉ አንቀጽ 541 መሰረት ጥፋተኛ እንዲባልልን
እና ተከሳሹ ወንጀሉን የፈጸመው ራስን መከላከል በማለፍ፣ እና የ ከዚህ በፊቱ ተከሳሽ ሰይድ አብዱ ጣሂር
የሚባለው የአህመድ አብዱ ጣሂር ወንድምን ባለፈው አመት ሟቹ መትቶት እስካሁን ከመሬት ላይ ያልተነሳ፡
ፓራላይዝ/ሽባ ሁኖ ለምስክርነት መምጣት እንኳ የማይችል መሆኑን አጣርተናል። በዚህ ምክንያት ከዚያ ቀን
ጀምሮ የአህመድ አብዱ ጣሂር ወንድም ከቤት ወጥቶ አያውቅም ሟች አዕምሮው ትክክል ባለመሆኑ ምክንያት
ስለሆነ ጥፋትን የፈጸመው ፡ ፍርድ ቤቱ ይህንን ከግምት ውስጥ በማስገባት የመሰለ ውሳኔ እንዲሰጥልን
ብላለች።
የዓቃቤ ህግ ማሳሰቢያ
ፍርድ ቤቱ የተከሳሽ መከላከያ ምስክሮችን ሰምቷል፡ በተሰሙት ምስክሮች መሰረት አስፈላጊውን ውሳኔ
እንዲሰጥልን በዚሁ መፍትሄ እንዲሰጠን እንጠይቃለን።
ትዕዛዝ
የመ/ቁጥር ፦ 0205655
ቀን፦ 20/07/2016
ሁሴን ሀሰን
መሀመድ አብደላ
መዝገቡ ያደረው ተመርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ነበር ባደረው መሰረት በመከላከያ ምስክሮች የምስክርነት ቃል
ምክንያት ተያይዞ አልተመረመረም
ትዕዛዝ
0205655
ቀን፦11/08/2016
ሁሴን ሀሰን
መሀመድ አብደላ
መዝገቡ ያደረው ለመመርመር ነበር ነገር ግን በስራ ብዛት ምክንያት ምርመራው አልተጠናቀቀም።
ትዕዛዝ
ቀን፦ 24/08/2016
ዳኞች፦
አሊ መሀመድ አደም
ሁሴን ሀሰን
መሀመድ አብደላ
ውሳኔ
መዝገቡ ተከፍቶ ሊቀርብ የቻለው ዓቃቤ ህግ በቁጥር ፍ/መ 3129/2015 በቀን 26/05/2015 ተጽፎ በቀረበ ክስ
ሲሆን የክሱ ዝርዝርም ተከሳሽ የወንጀል ህግ አንቀጽ 539 (1)ሀ ስር የተደነገገውን በመተላለፍ ተከሳሽ ሰው
ለመግደል በማሰብ በቀን 27/01/2015 ዓ,ም ከቀኑ በግምት 6፡00 ሰአት ሲሆን በአርጡማ ፉርሲ ወረዳ ጎልቦ
ቀበሌ ልዩ ቦታው ቡርቃ ተብሎ በሚጠራበት ቦታ ልጅ መታ በሚል ምክንያት ሟች ሁሴን በሺር የሚባለውን
ይዞ በነበረው ቁጥሩ 17292 የሆነውን ክላሽ በሚባለው የጦር መሳሪያ በአንድ ጥይት ቀኝ እግሩ ፣ በአንዱ ጥይት
ልቡ ላይ እንዲሁም በአንድ ጥይት ግንባሩ ላይ መትቶ በማቁሰል ከባድ የሰው ነፍስ ግድያ ወንጀል ፈጽሟል ።
ተከሳሹም ለችሎት ቀርቦ ማንነቱ ከተረጋገጠ ቡሃላ ክሱ ተነቦለት ከተገነዘበ ቡሃላ በተከላካይ ጠበቃው ታግዞ
የተከሳሽ ተከላካይ ጠበቃም የክስ ተቃውሞ የለንም ሲል ተከሳሹ ወንጀሉን አልፈጸምኩም ጥፋት የለኝም
ብሎ ክዶ ተከራክሯል።
ዓቃቤ ህግም ምስክሮች እንዳሉት እና እንደቀረቡ በመግለፅ ይሰሙልን በማለት አሳስቦ ምስክሮቻችንም
ለክሳችን እንዲመሰክሩልን በማለት የጉዳዩን ጭብጥ አስይዟል።
ዓቃቤ ህግም በዚሁ የሰው ምስክር ማሰማቱን እንዳጠናቀቀ በመግለጽ መፍትሔ እንዲሰጠው አሳስቧል።
ፍ/ቤቱም መዝገቡን መርምሮ አይቶ ተከሳሽ የተከሰሰበትን ወንጀል እንደፈጸመ ዓቃቤ ህግ አቅርቦ ባሰማው
የሰው ምስክር እንዳረጋገጠበት ገልጾ እንዲከላከል በማለት ብይን ሰጥቷል።
ተከሳሽም በቀ 0 05/06/2016 ዓ.ም በጻፈው ማመልከቻ የመከላከያ ምስክሮች እንዳሉት በመግለፅ በዝርዝር
አቅርቦ ከመዝገቡ ጋር አያይዟል።
በቀጠሮው ቀንም መከላከያ ምስክሮቹ ቀርበው፡ተከሳሽም መከላከያ ምስክሮቼ የሚመሰክሩልኝ እኔ ሟችን
መትቼ እንደገደልኩት እና ግን የገደልኩት ሟች እኔን ለመምታት ብረት ይዞ ከቤቱ ተነስቶ ከቤቴ ሲመጣ እኔም
ራሴን ለመከላከል ብዬ ሟች መሳሪያዬን ሲይዝብኝ ከመካከላችን ጥይት ተተኩሶ ሟችን መታው በማለት
የጉዳዩን ጭብጥ አስይዟል።
1 ኛ የመከላከያ ምስክር
ተከሳሽንም ሟችንም እንደሚያውቃቸው ገልጾ የተከሰሰውም ሟች ሁሴን በሺርን ገድሏል ተብሎ እንደሆነ፡
ሲገድለውም በአይኑ እንዳላየ ገልጾ ፡ ተከሳሹ ወንጀሉን የፈጸመበት ቦታ፣ቀን እና ሰኣት ክሱ ላይ እንደተገለጸው
መሆኑን በመግለፅ፡ተከሳ ወንጀሉን ፈጸመ የተባለው እሱ ሁለተኛው መከላከያ ምስክር ጋር ለጁሙኣ ሶላት ወደ
መስጂድ ሲሄዱ የመሳሪያ ተኩስ እንደሰሙ፡የመሳሪያ ድምጽ ወደ ሰሙበት ቦታ ተሯሩጠው ሲሄዱ ሟች
በመሳሪያ ተመትቶ ወድቆ እንደሞተ እና ተከሳሽም እጁ ላይ በገጀራ ተመትቶ ገጀራውን ሟች አጠገብ እንዳየ
እና ጩቤ/ሳንጃም ታጥቆ እንዳየ የተከሳሽም መሳሪያ እዛው መሬት ላይ ወድቆ እንዳዩ፣ተከሳሹም ከቦታው ወደ
ታች ሸሽት እንደነበረ፣ሟችንም ከወደቀበት አንስተው ወደ መስጂድ እንዳደረሱት፣ተከሳሹ እና ሟቹ ጉርብትና
እንደሌላቸው እና ቤታቸው እንደሚራራቅ፣ሟችም እብድ/የአዕምሮ ህመምተኛ እንደሆነና ሰፈር ውሰጥ
ሰዎችን በማሯሯጥ እንደሚታወቅ በመግለፅ መስክሯል።
2 ኛ የመከላከያ ምስክር
1 ኛው የመከላከያ ምስክር ገልጾ በመሰከረው መልክ በመመስከር ልዩነቱም ሟች መጀመሪያ ሰይድ የሚባለውን
የተከሳሽ ወንድምን በብረት መትቶ ተመልሶ ወደ ተከሳሽ ቤት ሄዶ ከተከሳሹ ጋር በእጅ እንደተያያዙ በርቀት
እንዳየ ፣ ሟች እና ተከሳሹ የተያያዙበት ቦታ አይቶ ከተከሳሹ በር ላይ እንደሆነ፣የመሳሪያ ድምጽ ሰምተው
ወደ ተጣሉበት ቦታ ሲሄዱ ሟች ተመትቶ ወድቆ እንዳየው ፣ እረጅም የብረት በትር አጠገቡ እንዳለ እና ሌላ
ነገር እንዳልያዘና፣ ተከሳሽም ሟች ከተመታ ቡሃላ የጦር መሳሪያውን ጥሎ እንደሄደ እና ወደየት እንደሄደ
እንዳላየ እና መሳሪያ የተኮሰውን ሰው እንደማያውቅ በመግለፅ መስክሯል።
በ ምርመራችንም 1 ኛ የተከሳሽ የመከላከያ ምስክሮች የዐቃቤ ህግን የምስክርነት ቃልን አስተባብለዋል ወይንስ
አላስተባበሉም? 2 ኛ አላስተባበሉም የሚባል ከሆነ ተከሳሽ የፈጸመው የሰው ግድያ ወንጀል ዓቃቤ ህግ
በከሰሰበት አንቀጽ ስር የሚወድቅ ነው ወይንስ የማይወድቅ? የሚለው ሊጣራ የሚገባ ነጥብ ሁኖ አይተናል።
የመጀመሪያውን ነጥብ አስመልክቶ ተከሳሽ የተጠየቀውን የእምነት እና የክህደት ቃሉን ሲሰጥም ወንጀሉን
አልፈጸምኩም ብሎ ክዶ ተከራክሮ የዐቃቤ ህግ ምስክሮችም ተሰምተው እንዲከላከልም ብይን ተሰጥቶት
የመከላከያ ምስክሮቹን አቅርቦ የመከላከያ ምስክሮቹም ይመስክሩልኝ ብሎ ጭብጥ ያስያዘው ሟች እሱን
ሊመታው ብረት ይዞ ከቤቱ መጥቶ መሳሪያ ሲይዝበት መሀከላቸው ላይ ጥይት ተተኩሶ እንደተመታ በማለት
የጉዳዩን ጭብጥ ያስያዘ መሆኑ የተከሰሰበትን ወንጀል እንደፈጸመ የሚያመለክት ነው። ቀርበው የተሰሙት
የመከላከያ ምስክሮችም ሟች እና ተከሳሽ ተጣልተው በእጅ እንደተያያዙ ተከሳሽ ይዞት የነበረው መሳሪያ
ድንገት መካከላቸው ላይ ተተኩሶ ሟችን መትቶ የገደለው መሆኑን ፣ ቦታው ላይ እንዳልነበሩ እና መሳሪያው
ተተኩሶ ሟችን መትቶ ከገደለው ቡሃላ ተሯሩጠው መሄዳቸውን ያረጋገጡት እንጂ ተከሳሽ እንዴት ይህንን
ግድያ ሊፈጽመው እንደቻለ የጉዳዩን ጭብጥ አስይዘው እንዳላረጋገጡ ተገንዝበናል።ይህም ተከሳሽ
የተከሰሰበትን ወንጀል ሲፈጽም እነዚህ መከላከያ ምስክሮች በቦታው እንደሌሉና በሀሰት ተደራጅተው ቀርበው
የምስክርነት ቃላቸውን የሰጡ የሚያረጋግጥ መሆኑን ማወቅ ችለናል።
0205655
የመከላከያ ምስክሮች የምስክርነት ቃላቸው እርስበርስ በሚጻረር መልኩ መገለጹ ምስክርነታቸው ተከሳሽ
የተከሰሰበትን ወንጀል ሟች ላይ ሲፈጽም በቦታው እንደሌሉ ፣ እንዳላዩ እና በሀሰት ተደራጅተው ቀርበው
የመሰከሩ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው። ስለዚህ ከዚህ በላይ ከገለጽነው ላይ በመነሳት የመከላከያ ምስክሮችን
ቃል ስንመዝን በበቂ መልኩ የዐቃቤ ህግ ምስክሮችን ቃል ስለማያስተባብሉ ውድቅ አድርገናል።
2 ኛውን ነጥብ አስመልክቶ ተከሳሽ ሟችን በአንድ ጥይት መትቶ መግደሉን እንጂ ቂም በመያዝ ወይንም
የወንጀሉን በአሰቃቂ እና ጭካኔ በተሞላበት መንገድ መፈጸሙን የዐቃቤ ህግ ምስክሮች ያረጋገጡት ነገር የለም
ስለዚህ ተከሳሽ የፈጸመው የግድያ ወንጀል በወንጀል ህግ አንቀጽ 539 /1/ሀ ስር የማያስከስሰው ስለሆነ
በወ/ስ/ስ/ህ ቁጥር 113/2/ መሠረት የተከሰሰበትን አንቀጽ ወደ ወንጀል ህግ አንቀጽ 540 በመቀየር ወይንም
በማሻሻል ተከሳሽ በተሻሻለው አንቀፅ ስር ያለውን በመተላለፍ ተከሳሽ ተራ የግድያ ወንጀልን ሟች ሁሴን
በሺር ላይ ፈጽሟል። የፈጸመውም የወንጀል ድርጊት ተሻሽሎ በተቀየረው አንቀጽ መመረት ጥፋት ነው
በማለት በወ/ስ/ስ/ህግ ቁጥር 149/1/ መሰረት በሙሉ ድምፅ የጥፋተኝነት ውሳኔ ወስነናል።
የዐቃቤ ህግ የቅጣት አስተያየት ፦ ተከሳሽ ጥፋተኛ ነው የተባለበት አንቀጽ በቅጣት አወሳሰን መርህ
መሠረት ደረጃ እና እርከን የወጣለት በመሆኑ የወንጀሉ ደረጃ 6 ኛ እንዲሁም የእስራት ቅጣት እርከን 33 ኛ
ላይ ተደርጎልን አስተማሪ የሆነ ቅጣት ይወሰንልን በማለት አሳስቧል።
የተከላካይ ጠበቃዋ የቅጣት አስተያየት ፦ ተከሳሽ የወንጀል ሪከርድ የለበትም፣መሀይም እና ያልተማረ
ነው እንዲሁም በእርሻ ስራ አምስት (5) የቤተሰቦቹን አባል በማገዝ የሚያስተዳድር ስለሆነ ይህ ከግምት ውስጥ
ገብቶ ቅጣቱን በማቅለል እንዲወሰንልን በማለት አሳስባለች።
ቅጣት
ተከሳሽ የሰው ግድያ ወንጀል ፈጽሟል ተብሎ የጥፋተኝነት ውሳኔ የተወሰነበት አንቀጽ የወ/ህ/አንቀጽ 540
ሲሆን፡ይህንን አንቀጽ በመተላለፍ ወንጀልን የፈጸመ ሰው የጥፋተኝነት ውሳኔ ተወስኖበት ከ 5 አመት እስከ 20
አመት በሚደርስ ከባድ የእስር ቅጣት ሊቀጣ እንደሚችል ይደነግጋል።
0205655
ድንጋጌውም በቅጣት አወሳሰን መሰረት ደረጃ እና እርከን የወጣለት በመሆኑ የወንጀሉ ደረጃ 6 ኛ እንዲሁም
የእስራት ቅጣት እርከን 33 ኛ ላይ ይወድቃል። በዐቃቤ ህግ በኩል የቀረበ የቅጣት ማክበጃ ምክንያት የለም
በተከሳሽ በኩል ሶስት(3) የቅጣት ማቅለያ ምክንያቶች ቀርበው ተይዘውለታል ይህም በወ/ህ/አንቀጽ 82/1/ሀ
መሰረት የወንጀል ሪከርድ እንደሌለው እና ያልተማረ መሃይም እንደሆነ ነው እንዲሁም በወ/ህ/አንቀጽ 86
መሠረት በግብርና ስራ 5 ቤተሰቦቹን የሚያስተዳድር መሆኑ ነው ይህም 3 የቅጣት እርከን ይቀንስለታል
የእስራት ቅጣት እርከን 30 ኛ ይሆንለታል ማለት ነው።
እርከኑም ከአስራ አንድ አመት(11) እስከ አስራ ሶስት አመት ከሁለት ወር(13.2) በእስራት ሊያስቀጣ
እንደሚችል ይደነግጋል። ስለዚህ ተከሳሽ ከተያዘበት ቀን 27/01/2015 ዓ.ም ጀምሮ የሚታሰብለት ሁኖ በአስራ
ሁለት አመት ከስድስት ወር /12.6/ ጽኑ እስራት እንዲቀጣ በማለት የቅጣት ውሳኔ ተወስኖበታል።
ትዕዛዝ