Professional Documents
Culture Documents
Nurtata Suit Final Answer
Nurtata Suit Final Answer
ቀን፦____________________
ከሳሽ በተከሳሽ ላይ የቀረበው አቤቱታ በአጭሩ፡- ከሳሽ በቀን 14/09/2016 ዓ/ም ፅፎ ባቀረበው
በዓለም ገበያ ከተማ 01 ቀበሌ ውስጥ የሚገኝ ስፋቱ 4000 ካሬ ሜትር የሆነ እና አዋሰኙን በማጥቀስ በቀን
2/5/2007 ዓ.ም የሆቴል ኢንቨስትመንት አገልግሎት ለመስራት ባልተገደበ ግዜ የመሬት ኪራይ ውል ገብቼ
እና ይዞታ ማረጋገጫ ተሰጥቶኝ G+2 የሆቴል ህንፃ እና 11 ክፍል እንግዳ ማረፊያ ፔንሲዮን ቤቶች ሰርቼ
የያዝኩት 4000 ካሬ ሜትር ይዞታዬ ውስጥ ተከሳሽ ህግን ሳይከትል ከይዞታዬ ውስጥ ቀንሶ 2320 ካሬ
ሜተር እና በላዩ የተገናባ ግምቱ 3,200,000(ሶስት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺህ) ብር የሚሆን ግንባታ
ያለበትን ይዞታዬ እና ንብረት ተነጥቄያለው በሚል የሰጠው ህገ-ወጥ ውሳኔ ህገ-ወጥነቱ ተረጋግጦ ይዞታና
ንብረቱ ሊነጠቅ አይገባም በሚል የቀረበ ክስ ነው፡፡
3 ኛ. ከሳሽ ለሆቴሉ ውበት የሚሆኑ በቁጥር 600(ስድስት መቶ) የሚሆን ግምቱ አንድ መቶ ሺ ብር
የሚሆን የተለያዩ ዛፎች እና ፍራፍሬዎችን በመትከል የለማዋቻውን እና የሻዋር እና ሽንት ቤት እና
የተለያዩ ሰርቪስ ቤቶች ግምታቸው ሶስት ሚሊዮን አንድ መቶ ሺ ብር የሚሆን ያላለቀ
ግንባታ ያለበት ሳያነሱ እያወደሙብኝ ይገኛሉ በማለት ያነሱትን በተማለከ፦ ከሳሽ የክስ አቤቱታ
የተነሳበትን ቦታ በ 2007 ዓ/ም በተደረገ ዉል ለሆቴል ኢንቨስትመንት አገልግሎት በሚል የወሰደ ቢሆንም
ለተባለለት አላማ እና አገልግሎት ከማዋል ይልቅ ቦታዉ ከተማ ማሀል እና አስፓልት ደር እንደመሆኑ
ለቦታዉከከሳሽ በተወሰደው መሬት ላይ ምንም አይነት ያለማ ነገር ዬለበትም፡፡ ከሳሽ ተወሰደብኝ የሚሉት
በውሉ መሰረት ደረጃውን ያልጠበቀ እና ግንባታ ፈቃድ ሳይወስዱ 180 ካ/ሜ ላይ ያረፈ 6 ክፍሎች
የመሰረት ግንባታ ስገነቡ ማዘገጀ ቤቱ ያስቆመው ህገ-ወጥ ግንበታ እንጅ ከሳሽ እንዳሉት ሶስት ሚሊዮን
አንድ መቶ ሺ ብር የሚሆን ግምት ያለዉ አይደለም። ሌላዉ ከሳሽ በተወሰደዉ መሬት ላይ የተለያዩ ግራር
እና ዛፎች የነበሩትን ከሳሽ በራሱ ወጪ ማንሳት እያለበት ተከሳሽ በራሱ ወጪ አንስቶ በቀሪዉ የከሳሽ
ይዞታ ላይ አስቀምጧል። ሊላዉ ከሳሽ እንዳለዉ 600(ስድስት መቶ) ዛፎች እና ፍራፍሬዎች የሌሉ እና
የዋጋ ግመታቸዉም አንድ መቶ ሺ ብር የሚያወጣ አይደለም የወደመም ምንም አይነት ነገር ዬለም።
ባአጠቃላይ በተወሰደዉ መሬት ምንም አይነት የለማ ንብረት ወይም በገንዘብ የሚተመን ንብረት የሌለበት
በመሆኑ የተከበረው ፍ/ቤት ከሳሽ ያቀረቡት አቤቱታ እዉነታዉን ሀቁን የካደ በመሆኑ የከሳሽን አቤቱታ ውድቅ
በማድረግ በነፃ እንዲያሰናብተን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
ቁጥር፦______________________________________
ቀን፦____________________
የተከሣሽ ወኪል፦______________________________________ፊርማ፦______________________________________