Professional Documents
Culture Documents
Ydb#B B/@Éc B/@Rsïcâ ?zïc KL 58/1999
Ydb#B B/@Éc B/@Rsïcâ ?zïc KL 58/1999
ZïC KLል
hêú ሚያዚያ 3 qN 1999 ዓ/ም›.M Mክር b@T -ÆqEnT ywÈ አዋጅ
ክፍል አንድ
ጠቅላላ
1. አጭር ርዕስ
ይህ ደንብ የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ክልላዊ መንግሥት የከተሞች አደረጃጀትና
የአስተዳደር ስርዓት ደንብ ቁጥር 58/1999 ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡
1
2. ትርጓሜ
በአዋጁ ውስጥ በአንቀጽ ፪ ትርጓሜ የተሰጣቸው ጉዳዮች እንደተጠበቁ ሆነው በዚህ ደንብ
ውስጥ በግልጽ ሌላ ትርጓሜ ካልተሰጣቸው በስተቀር፡-
1. «አዋጅ» ማለት የከተሞች አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 103/99 ማለት ነው፡፡
2. «ቢሮ» ማለት አግባብ ባለው የክልሉ ሕግ መሠረት የተቋቋመ የሥራና ከተማ ልማት
ቢሮና በሥሩ ያሉ የበታች መዋቅር ያካትታል፡፡
3. «ክፍለ ከተማ» ማለት የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል መንግሥት
በከተማች አስተዳደር የከተማው ሁለተኛ የአስተዳደር እርከን ነው፡፡
4. «የቀበሌ አስተዳደር» ማለት የከተማ አስተዳደር ታችኛው የአስተዳደር እርከን ነው፡፡
5. መሪ ከተማ አስተዳደር ማለት በክልሉ ውስጥ የተሻለ እና የመሪነት ሚና የሚጫወት
የሕዝብ ብዛት ከ100 000 በላይ የሆነ ከተማ ነው፡፡
6. ከፍተኛ ከተማ አስተዳደር ማለት በኢኮኖሚና ማህበራዊ እንቅስቃሴ የላቀ ደረጃ የደረሰ፣
የህዝብ ብዛት ከ60000 – 100000 የሆነ ከተማ ነው፡፡
7. መካከለኛ ከተማ አስተዳደር ማለት የተሻለ የኢኮኖሚና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ያለው፣
የህዝብ ብዛቱ ከ30000 እስከ 60000 የሚደርስ ከተማ ነው፡፡
8. ታዳጊ ከተማ አስተዳደር ማለት የነዋሪው ሕዝብ ብዛት ከ10000 እስከ 30000 የሆነ
የተደራጀ የከተማ አስተዳደር ነው፡፡
3. የፆታ አገላለጽ
በዚህ ደንብ ውስጥ ለወንድ ፆታ የተደነገገው የሴቷንም ፆታ ያካትታል፡፡
4. የተፈፃሚነት ወሰን
ይህ ደንብ በአዋጁ መሠረት በተቋቋሙ የክልል የከተማ አስተዳደር ከተሞች እና የማዘጋጃ
ቤት ከተሞች ሁሉ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
ክፍል ሁለት
በከተማነት ስለመቋቋም
5. በከተማነት ለመቋቋም የሚያበቁ ሁኔታዎች
በከተማነት ለመቋቋም በአዋጁ አንቀጽ ፰ ንዑስ አንቀጽ ፪ እና ፫ የተደነገገው አጠቃላይ
ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ የከተማነት እውቅና በቢሮው አነሳሽነት በሚደረግ ጥናት ወይም
በማህበረሰቡ ጥያቄ ሊከናወን ይችላል፡፡
2
1. በቢሮው አነሳሽነት የሚሰጥ የከተማ እውቅና
1.1. ቢሮው በሚያደርገው ጥናት የከተማነት እውቅና መስጠት የሚቻለው መሠረታዊ
መስፈርቶችን የሚቀይር የአዋጅ ወይም ሌሎች ሕጐች በሚያስከትሉት ለውጥ
ብቻ ነው፡፡
1.2. ከላይ በቁጥር 1.1 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ ቢሮው የከተማ እውቅና
እንዲያገኘ የተመረጠው ከተማ በዞኑ አስተዳደር አማካኝነት ጥያቄውን ላቀረበው
ማህበረሰብ ቀርቦ ስምምነት ላይ መደረስ ይኖርበታል፡፡
2. በሕዝቡ ጥያቄ ስለሚሰጥ የከተማነት እውቅና
2.1. አንድ ማህበረሰብ የከተማነት እውቅና እንዲሰጠውና እንዲተዳደር መጠየቅ
ይችላል፡፡
2.2. በማህበረሰቡ የሚቀርብ የከተማነት ጥያቄ በተወካዮቹ የሚቀርብ ሆኖ በዚህ ደንብ
አንቀጽ ፮ እና ፯ በተደነገገው መሠረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
3
2.3. የዳር ድንበሩን ማስረጃ በተመለከተ ማህበረሰቡ ከታቀፈበት የወረዳ/ልዩ ወረዳ
አስተዳደር ምክር ቤት የተሰጠ የድጋፍ ደብዳቤ፡፡
4
9. የከተማነት ዕውቅና ስለማግኘት
1. ከአዋጁ በፊት እውቅና ስላላቸው ከተሞች
1.1. አዋጁ እስከወጣበት ጊዜ ቀደም ሲል በነበረው ህግ መሠረት በክልሉ መስተዳድር
ምክር ቤት የከተማነት እውቀና የተሰጣቸው ከተሞች በዚህ ደንብ የከተማነት
እውቅና ለማግኘት የተመለከቱ ድንጋጌዎች መፈፀም ሳያስፈልጋቸው በአዋጁ
አንቀጽ 5 በተመለከተው መሠረት እንደ ህዝብ ብዛታቸው እየታዩ በየፈርጅ
ይመደባሉ፡፡
1.2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ አንድ መሠረት በየፈርጁ የተመደቡ ከተሞች ዝርዝር
መስተዳድር ምክር ቤቱ በሚያወጣው የህግ ክፍል ማስታወቂያ ይገለፃል፡፡
2. ከአዋጁ በፊት እውቅና ስለሌላቸው ከተሞች
2.1. አዋጁ እስከወጣበት ቀን ድረስ የከተማነት ዕውቅና ካላገኘ ከማንኛውም
ማህበረሰብ የሚቀርብ ጥያቄ በአዋጁና በዚህ ደንብ በከተማነት ለመቋቋም
የሚበቁ ሁኔታዎችና መመዘኛዎች በተመለከተ የተደነገጉ ድንጋጌዎች ተፈፃሚ
ይሆናሉ፡፡
2.2. በአዋጁ አንቀጽ ፰ ንዑስ አንቀጽ 6 መሠረት እያንዳንዱ የከተማነት ደረጃ
የተሰጠው ማህበረሰብ የከተማነት ህጋዊ እውቅና ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት
ይሰጠዋል፡፡
5
01. በነጋሪት ጋዜጣ በይፋ ስለማሳወቅ
አንድ ማህበረሰብ በከተማነት በመቋቋም ህጋዊ ሰውነት ሲያገኝ ወይም ከከተማነት
በመሰረዙ ምክንያት ህጋዊ ሰውነቱን ሲያጣ ይኸው በደቡብ ነጋሪት ጋዜጣ በሚታተም
የህግ ክፍል ማስታወቂያ ይፋ ይደረጋል፡፡
ክፍል ሶስት
የከተማ አስተዳደር ከተሞች አመሠራረት እና አካላት
ምዕራፍ አንድ
አመሠራረት
፲፩ የከተማ አስተዳደር የሚቋቋምባቸው ከተሞች አወሳሰን
1. መመዘኛ መስፈርቶች
1.1. የከተማ ዕውቅና የተሰጣቸውና የከተማ አገልግሎቶችን በመስጠት ላይ
የሚገኝ፣
1.2. የነዋሪው ሕዝብ ብዛት ከ10 ሺህ በላይ የሆነ፣
1.3. በአካባቢው ከሚገኙ ከተሞች በኢኮኖሚ እንቅስቃሴው የተሻለ ደረጃ ላይ
የሚገኝ፣ ከከተሞችና ከገጠሩ ጋር ተሳስሮ በማደግ አካባቢውን ይዞ
ለመልማት ዕድሉ ከፍተኛ የሆነ፣
1.4. በከተማው የመሠረተ ልማት እና ማህበራዊ አገልግሎቶች የተስፋፋበት እና
ገቢ የመሰብሰብ አቅሙ ከፍተኛ የሆነ፣
1.5. የፖለቲካ እና አስተዳደር ማዕከል የሆነ፣
1.6. ሁለት እና ከዚያ በላይ የቀበሌ አስተዳደሮችና ምክር ቤቶች ያሉት፣
2. ውሣኔ ሰጪ አካል
2.1. አንድ ከተማ የከተማ አስተዳደር ሊዋቀርለት የሚችለው ከላይ በንዑስ
አንቀጽ 1 መሠረትና ሌሎች ቴክኒካዊ መስፈርቶችን መሠረት አድርጎ ቢሮው
ለሚያደርገው ጥናት መነሻነት የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት በሚሰጠው
ውሣኔ ነው፡፡
2.2. ከላይ በቁጥር 2.1 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ የከተማ አስተዳደር
እንዲዋቀር በቢሮው የሚደረግ ጥናት ቢያንስ በየ3 ዓመቱ መሆን
ይኖርበታል፡፡
6
03. በሪፎርም ፕሮግራም የታቀፉ ከተሞች
በከተማች አስተዳደር አዋጁ ቁጥር 103/99 በአንቀጽ 6/2 በተደነገገው መሠረት የከተማ
አስተዳደር ከተሞች ሆነው የሚቋቋሙ ከተሞች በሪፎርም ፕሮግራም የታቀፉ ከተሞች
ይሆናሉ፡፡
ምዕራፍ ሁለት
የከተማ አስተዳደር አካላትና አሰያየም
04. የከተማ አስተዳደር አካላት
የከተማ አስተዳደር ከተሞች የሚከተሉት የአስተዳደር አካላት ይኖራቸዋል፡፡
1. የከተማ ምክር ቤትና አፈጉባዔ እንዲሁም እንደአስፈላጊነቱ ምክትል አፈጉባዔ፣
2. ከንቲባ እንደአስፈላጊነቱ ምክትል ከንቲባ
3. የከንቲባ ኮሚቴ
4. የማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች ሥራ አስኪያጅ እንዲሁም እንደአስፈላጊነቱ ምክትል
ሥራ አስኪያጅ
5. የከተማ ነክ ጉዳዮች ፍርድ ቤቶች
6. በዚህ ደንብ አንቀጽ ፲፮ መሠረት የሚቋቋሙ ሌሎች አስፈፃሚ መስሪያ ቤቶች
የሚመሩ ኃላፊዎች፡፡
2. የከንቲባው ተጠሪነት
7
2.1. ከንቲባው በሁሉም ጉዳዮች ለከተማው ምክር ቤት ተጠሪ ይሆናል፡፡
2.2. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 1 የተመለከው እንደተጠበቀ ሆኖ የፌዴራልና የክልል
ህጎች፣ ፖሊሲዎችና ደረጃዎች አፈፃፀም፣ ከመንግሥት ለከተማ የተላለፉትን
ተግባራት ክንውንና የገንዘብ አጠቃቀምን በሚመለከቱ ጉዳዩች፣
ሀ. የመሪ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተጠሪነቱ ለክልሉ ርዕስ መስተዳድር፣
ለ. የከፍተኛና መካከለኛ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ለሚመለከተው ዞን ዋና
አስተዳዳሪ፣
ሐ. የዞን አስተዳደር መቀመጫ የሆነ ታዳጊ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ለዞን
ዋና አስተዳዳሪ፣
መ. በልዩ ወረዳዎች ውስጥ የሚገኝ በማንኛውም ደረጃ የሚገኝ ከተማ ከንቲባ
ለልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ተጠሪ ይሆናሉ፡፡
2. ቃለ መሀላ
የከንቲባው ምርጫ በከተማው ምክር ቤት ከፀደቀ በኋላ ከንቲባው ሥራውን
ከመጀመሩ በፊት በከተማው ምክር ቤት ፊት የሚከተሉትን መሀላ ይፈጽማል፡፡
እኔ በዛሬው ዕለት የ ከተማ ከንቲባ
በመሆን ሥራዬን ስጀምር በሕዝቡና በም/ቤቱ የተጣለብኝን ከፍተኛ ኃላፊነት በብቃት
በመረዳት ለከተማው ልማት መረጋገጥ መልካም አስተዳደር መስፈን ኃላፊነቴን
በትጋት እና በታማኝነት ለመወጣት ቃል እገባለሁ፡፡
ምዕራፍ ሦስት
የከተማ አስተዳደር አስፈፃሚ አካላት ስልጣንና ተግባር
07. አስፈፃሚ አካላት ስለመቋቋም
በአዋጁ አንቀጽ ፳፬ ንዑስ አንቀጽ 3 መሠረት በእያንዳንዱ የክልሉ የከተማ አስተዳደር
ከተሞች ለከንቲባው ተጠሪ የሆኑ የሚከተሉት አስፈፃሚ አካላት ተቋቁመዋል፡፡
1. የመሪ ከተማ አስተዳደር አስፈፃሚ አካላት
1.1. የከንቲባው ጽ/ቤት
1.2. የፋይናንስ ኢኮኖሚ ልማት መምሪያ
1.3. የትምህርትና አቅም ግንባታ መምሪያ
1.4. ጤናና የአካባብ ንጽህና መምሪያ
1.5. የንግድና ኢንዱስትሪ መምሪያ
1.6. ወጣቶች፣ ስፖርትና አካባቢ ልማት መምሪያ
1.7. ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ
1.8. የፍትህ፣ ፀጥታና ደንብ ማስከበር መምሪያ
2. የከፍተኛና መካከለኛ ከተማ አስተዳደር፣ አስፈፃሚ አካላት፣
2.1. የከንቲባው ጽ/ቤት
2.2. የፋይናንስ ኢኮኖሚ ልማት ጽ/በት
2.3. ማህበራዊ አገልግሎትና አቅም ግንባታ ጽ/ቤት
2.4. የንግድና ኢንዲስትሪ ጽ/ቤት
9
2.5. ወጣቶች ስፖርትና አካባቢ ልማት ጽ/ቤት
2.6. ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት
2.7. የፍትህ፣ ፀጥታና፣ ደንብ ማስከበር ዋና ጽ/ቤት
3. የታዳጊ ከተማ አስተዳደር አስፈፃሚ አካላት፣
3.1. የከንቲባው ጽ/ቤት
3.2. የፋይናንስ ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት
3.3. ማህበራዊ አገልግሎትና አቅም ግንባታ ጽ/ቤት
3.4. የሴቶች፣ ወጣቶች እና አከባቢ ልማት ጽ/ቤት
3.5. የንግድና ኢንዲስትሪ ልማት ጽ/ቤት
3.6. የፍትህ፣ ፀጥታና፣ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት
10
11. ስለሥራው አፈፃፀም በየወቅቱ ተጠሪ ለሆነበት አካል በየወቅቱ ሪፖርት ማቅረብ፣
12
1. ህብረተሰቡ እራሱን በልዩ ልዩ ማህበራት እያደራጀ በልማት ሥራው ተሳታፊ
የሚሆንበትን ሁኔታ ያመቻቻል፣ የህብረተሰቡ ተሳትፎ በስርዓት የሚመራበት ስልት
ይቀይሣል፣ ማህበራት የእርስ በእርስ ተሞክሮ ልውውጥና መደጋገፍ እንዲያደርጉ
በቅንጀት እንዲንቀሳቀሱ ተገቢውን ጥረት ያደርጋል፣ ያበረታታል፣
2. የከተማው ወጣቶች በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና ፖለቲካው እንቅስቃሴ ውስጥ የነቃ
ተሳትፎ እንዲያደርጉ ያበረታታል፡፡
3. ወጣቱ ከአጉልና ጎጂ ድርጊቶች እንዲቆጠብና ጥሩ ዜጋ እንዲሆን ከተለያዩ አካላት ጋር
ይንቀሳቀሳል፡፡
4. በከተማው ወጣት ተኮር አካባቢ ልማት እንዲስፋፋ ጥረቶችን ያስተባብራል፣
ፕሮጀክቶችን ይቀርፃል፣ ሲፀድቅም ተግባራዊ ያደርጋል፡፡
5. የክልሉ አጠቃላይ ጨዋታዎች /ውድድሮች/ በከተማው ክልል በሚዘጋጅበት ወቅት
ከክልሉ ስፖርት ኮሚሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጃል፣ በተከማውም የስፖርት ምክር ቤት
እንዲቋቋም ያደርጋል፣
13
፳፭ የፍትህ፣ ፀጥታና ደንብ ማስከበር ዋና ጽ/ቤት ሥልጣንና ተግባራት
1. ቀልጣፋ ፍትህና የነዋሪዎች ሰላምና ደህንነት በከተማች እንዲሰፍን ያደርጋል፣
2. በከተማው አስተዳደር ስር የሚወድቁ የፍትህና ፀጥታ ጉዳዮችን ያስከብራል፣
3. በከተማው የፍትህ ስርዓት ማሻሻያ ፕሮግራም ተግባራዊ ያደርጋል፣
4. የከተማውን ነዋሪ ንቃተ ህግ ለማዳበር ከሚመለከታቸው የክልሉ አካላት ጋር
በመቀናጀት የህግ ትምህርት ይሰጣል፣
5. በህግ ጉዳዮች የከተማው አስተዳዳር ዋና አማካሪ ሆኖ ይሰራል፣ በሌሎች አካልም
ሲጠየቅ የህግ ምክር ይሰጣል፣
6. በህገ ወጥነት ላይ በህጉ መሠረት ተገቢውን እርምጃ ይወስዳል፣
7. የአስተዳደሩንና የነዋሪዎችን መብትና ጥቅም ለማስከበር አስፈላጊ ሆነው ሲያገኛቸው
በፍርድ ቤትና በማንኛውም ዳኝነት ስም ክስ ይመሰርታል፣ ክስ እንዲመሰረት ያደርጋል፣
ወይም ጠበቃ በመግዛት ይከራከራል፣
8. ህጎችና ደንቦች በሥራ ላይ መዋላቸውን ያረጋግጣል፣
9. የውል ማስረጃ ምዝገባዎችን ያከናውናል፣
10.የጽዳት መጓደል፣ ህገ ወጥ ንግድ ፣ ህገ ወጥ ግንባታና ሌሎች ደንብ መተላለፉን
ይቆጣጠራል፣ በህጉ መሠረት ተገብውን እርምጃ ይወስዳል፣ ወይም እንዲወሰድባቸው
ያደርጋል፣
14
፳፰ የገቢዎችና ታክስ አስተዳደር ስለመቋቋም
1. ተጠሪነቱ ለከተማው ከንቲባ የሆነ የገቢዎችና ታክስ አስተዳደር ጽ/ቤት በከተማ
አስተዳደር ከተሞች ተቋቁሟል፡፡
2. የጽ/ቤት ስልጣንና ተግባር የሚከተለው ይሆናል፡፡
2.1. የገቢ አወሳሰንና የሂሣብ አያያዝ በተሳለጠና ብቃት ባለው መልኩ ለማከናወን
የሚያስችሉ የአሠራር ዘዴዎች ይቀይሳል፡፡
2.2. አዲስ የገቢ ምንጮች እያጠና በሥራ ላይ ያውላል፣ ይከታተላል፡፡
2.3. በክልሉ ምክር ቤት በፀደቀው የፋይናንስ ደንብ መሠረት የከተማውን ገቢ
ማስተዳደር፣ ግብር፣ ቀረጥ፣ የአገልግሎት ክፍያና ሌሎች ገቢዎች
ይሰበስባል፣ እንዲሰበሰቡ ያደርጋል፡፡
2.4. ግብር ከፋዮችን ለይቶ ለማወቅና ለመመዝገብ የሚያስችሉ አሠራሮችን
ተግባራዊ ያደርጋል፡፡
2.5. በከተማው የሚሰበሰቡ ገቢዎችን ይወስናል፣ የግብር ውሣኔዎችን ለግብር
ከፋዮች በጽሑፍ ያስታውቃል፣ ይሰበስባል፡፡
2.6. በክፍለ ከተማ የተሰበሰቡ ገቢዎች በወቅቱ ፈሰስ መደረጋቸውን ያረጋግጣል፡፡
2.7. ግብር ከፋዮች ሕጎችን አውቀው መብትና ግዴታቸውን እንዲወጡ
ይቀሰቅሳል፣ ግዴታቸውን መወጣታቸውን ያረጋግጣል፡፡
ክፍል አራት
ስለ ማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች እና የማዘጋጃ ቤት ከተሞች
ምዕራፍ አንድ
የከተማ አስተዳደር በተቋቋመባቸው ከተሞች የማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች
፴፩ የማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች አስፈፃሚ አካላት መቋቋም
የሚከተሉት ለማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች ሥራ አስኪያጅ ተጠሪ የሆኑ አስፈፃሚ አካላት
ተቋቁመዋል፣
1. በመሪ ከተማ አስተዳደር
1.1. የመሠረተ ልማት እና ምህንድስና ኤጀንሲ
16
1.2. የመሬት ዝግጅትና ልማት ኤጀንሲ
1.3. የመሬት አስተዳደር እና አቅርቦት ኤጀንሲ
1.4. የቤቶች ኤጀንሲ
1.5. የገቢዎች ኤጄንሲ
2. በከፍተኛ ደረጃ የከተማ አስተዳደር
2.1. የመሬት ልማትና ምህንድስና ኤጀንሲ
2.2. የመሬት አቅርቦትና አስተዳደር ኤጀንሲ
2.3. የገቢዎች ኤጀንሲ
2.4. የቤቶች ኤጀንሲ
3. በመካከለኛ እና ታዳጊ ከተማ አስተዳደር
3.1. የመሬት ዝግጅት፣ አቅርቦትና ምህንድስና ኤጀንሲ
17
1.6. የከተማው የመሠረተ ልማት ሥራዎች የተቀናጀና ደጃውን የጠበቀ የመሠረተ
ልማት ኔት ወርክ ዲዛይን ጥናት ያካሂዳል፣ በዚህ ዲዛይን መሠረት
የመሠረተ ልማት ገንቢዎች ሥራቸውን አቀናጅተው እንዲሠሩ ያደርጋል፡፡
1.7. የመሠረተ ልማት ግንባታ ሥራዎች የወጣውን ዲዛይንና ስታንደርድ
ጠብቀው መፈፀማቸውን ይከታተላል፡፡
1.8. ማዘጋጃ ቤቱ ለመስራት የሚያቅዳቸውን የመኖሪያ ቤቶችና ሕንፃዎች
በከተማው ማስተር ፕላን የተመለከተው የሕንፃ ዓይነትና ደረጃ ተጠብቆ
ግንባታዎች በተዘጋጀው ዲዛይን ሥራ ዝርዝር መሠረት መሠራታቸውን
ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፡፡
1.9. ማዘጋጃ ቤቱ በኮንትራክተር ለሚያሠራቸው ግንባታዎች አማራጭ የጨረታ
ሠነድ በማዘጋጀት ጨረታው ተገምግሞ ሲፀድቅ ውል እንዲዘጋጅ ያደርጋል
በውሉም መሠረት አፈፃፀሙን እየተከታተለ የግንባታው ሥራ እስከሚጠናቀቅ
ድረስ በውልና በሥራ ዝርዝሩ መሠረት ዲዛይኑን ጠብቄ ለመሠራቱ
ይከታተላል ያረጋግጣል፣ ይቆጣጠራል፡፡
1.10. ከሚመለከታቸው ጋር በመቀናጀት ለከተማው የመንገድ፣ የውሃና ፍሳሽ፣
የስልክና የኤሌክትሪክ እንዲሁም የጎርፍ መስመሮች ውህደት ካርታ
እንዲዘጋጅ ያደርጋል፣ በዚህም ካርታ መሠረት አዳዲስ ሥራዎች
እንዲከናወኑ ያደርጋል፡፡
1.11. የተፈቀዱ የሥራ ፕሮግራሞች በተግባር ለመተርጎም የሠራተኛ፣ የፋይናንስ፣
የማሣሪያዎችና ዕቃ አቅርቦችን ወጪዎች በተመለከተ የድርጊት መርሃ ግብር
እንዲዘጋጅና እንዲቀርብ በማድረግ ተግባራዊነቱን ይከታተላል፡፡
1.12. በከተማው ውስጥ ለተለያዩ ግንባታዎች ፈቃድ ይሰጣል፣ በዚሁ ፈቃድ
መሠረት ብቻ ግንባታ መከናወኑን፣ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ፣ የቀበሌ ቤት
እድሳት፣ የስምና ንብረት ዝውውር እና የመሳሰሉትን የምህንድስና የግምት
ስራዎች ቁጥጥር ያደርጋል፣ በከተማው ውስጥ የሚገነቡ መሠረተ ልማቶች
መረጃ ተመዝግቦ እንዲያዝ ያደርጋል በየጊዜውም ወቅታዊ እንዲሆን
ያደርጋል፡፡
2. የመሬት ልማትና ዝግጅት ኤጀንሲ ስልጣንና ተግባት
2.1. ከተማው ዝርዝር ፕላን በመሪ ፕላኑ መሰረት እንዲዘጋጅ፣ የከተማ ፕላን
ህግጋት እንዲከበሩ፣ የከተማ ፕላን የመረጃ ጥናት ያደርጋል፣ ይከታተላል፣
18
2.2. ከተማ ቦታ በደረጃና በንዑስ ደረጃ በመመደብ የኢንቨስትመንት ፖቴንሻል
ጥናቶችን ያደርጋል፣ የቦታዎቹን ጋይድ ማፕ ያዘጋጃል፣ የቦታዎቹ ምደባ
መሠረት በቦታው ላይ መከናወን ያለበት የኢንቨስትመንት ፕሮጀክት በቅደም
ተከተል በመዘርዘር ለመሬት አስተዳደርና ቅርቦት መምሪያ ያስረክባል፣
2.3. የከተማውን ድርጊት ፕላንና ዝርዝር ፕላን ሥራዎችን በመሪ ፕላኑ
መሰረት ያዘጋጃል፣ ይመራል፣ ይቆጣጠራል፣ አፈጻፀሙን ይከታተላል፣
2.4. የከተማውን የክለሳና የዞኒንግ ጥናት ስራዎች ያጠናል፣ ሲፈቀድም ተግባራዊ
ያደርጋል፣
2.5. የከተማውን እድገት ተከትሎ ለሚመጡ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎች የቦታ
ክለሳ ጥናት ያደርጋል፣ ያዘጋጃል፣ ለቦታ አስተዳደር መምሪያ ያስረክባል፡፡
2.6. የከተማው ውበት የተጠበቀ እንዲሆን የአረንጓዴ ስፍራዎች እንዲለሙ
ጥናቶችን እያደረገ ከሚመለከታቸው ጋር በመወያየት ገቢራዊ ያደርጋል፣
2.7. በከተማው መሬት የመሠረተ ልማት አውታሮች ማለትም የስልክ፣ መብራት
፣የውሃ፣ የመንገድ፣ ወዘተ.. ፊዚካል ፕላኖች ለከተማው እድገት ቀጣይነት
በሚኖረው መልኩ እንዲዘረጉ ለሚመለከታቸው ሁኔታዎችን ያመቻቻል፣
2.8. የከተማው ስትራቴጂክ ፕላን መሰረት የከተማው ድንበር እንዲካለል
ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በሚደረገው ውይይት ይሳተፋል፣ ሲወሰንም
ያስፈጽማል፣
2.9. በከተማው ውስጥ መንግስት ቦታዎችን ለልማት በመፈለጉ ሳቢያ
ለሚፈናቀሉ ባለይዞታዎች በካሣ አዋጅ፣ ደንብና መመሪያ መሠረት
ክፍያዎች ያጠናል፤ የውሳኔ ሃሳብ ለስራ አስኪያጁ ያቀርባል
2.10. በከተማው ውስጥ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚዘጋጁ ቦታዎች የፕላን
ምደባዎች መሠረት አድርገው እንዲዘጋጁ ያደርጋል፣ ይሸነሽናል፣ ተዘጋጅቶ
ለሚመለከተው አካል ያስረክባል፣
3. የመሬት አስተዳደርና አቅርቦት ኤጀንሲ ስልጣንና ተግባር
3.1. የከተማ ቦታ ለተለያዩ የልማት ስራዎች እንዲውሉ የቦታ እደላ መሰረታዊ
የሆነ ጥናት በማድረግ ያከናውናል፣
3.2. ለጥቃቅንና አነስተኛ ንግድ ተቋማት እንዲሰጥ የተዘጋጁ ቦታዎች በተቀላጠፈ
መልኩ እንዲሰጡ የአሠራር ስልቶች ይቀይሳል፣
19
3.3. ሕጋዊ ለሆኑ ባለይዞታዎች የይዞታ ማረጋገጫ ተዘጋጅቶ ስለሚሰጥበት
ሁኔታ ያመቻቻል፣
3.4. የከተማው ቤትና የቦታ ግብር አፈፃፀም ከሌሎች ከሚመለከታቸው
የማዘጋጃ ቤቱ አገልግሎት ጋር በመሆን ማሻሻያ ሃሳብ ለበላይ ኃላፊው
ያቀርባል፣
3.5. የተለያዩ የቤትና የንብረት ይዞታ የማስተላለፍ ውልና የስም ዝውውር
ሥራዎች በህጋዊ መንገድ ተግባራዊ እንዲሆኑ ያደርጋል፣ ያረጋግጣል፣
3.6. በባንክና በግለሰቦች መካል በሚደረገው ብድር ውል ስምምነት ወቅት
ለዋስትና የቀረቡ ቤትና ድርጅት ይዞታ ከማኛውም ዕዳ ነጻ ስለመሆናቸው
ማረጋገጫ ይሰጣል፣
3.7. በሊዝ ደንብ መሠረት ስለሚሰጡት ቦታዎች ያመቻቻል፣ መረጃ ይይዛል፣
ለባለሀብቶች መረጃ ይሰጣል፣
3.8. በሊዝ በተለያዩ ስልቶች ለሚሰጡ ቦታዎች የፕሮሞሽን ሥራዎች
ለሚሠሩበት ሁኔታ ያመቻቻል፣
3.9. የተጠናከረ የካዳስተር ሥርዓት በከተማው እንዲኖር ያደርጋል፣
3.10. የሊዝ ገቢ ያጠናል፣ ስለአጠቃቀሙ የውሳኔ ሃሳብ ያቀርባል፣
3.11. ስለሊዝ ዓመታዊ እቅድ፣ የሊዝ ጨረታ ሰነድ ያዘጋጃል፣ የሊዝ ውል
ያዘጋጃል፣ የክፍያ አሰባሰብና አወሳሰን የውሳኔ ሃሳብ ያቀርባል፣
3.12. ለግንባታ ፈቃድ የሚቀርቡ ዲዛይኖች አርክቴክቸራል፣ ስትራክቸራል፣
ኤሌክትሪካል፣ ሳንቴሪ ፕላኖች ከቦታ ስፋት አንጻር መሆናቸውን
ያረጋግጣል፣ የቦታዎችን አስተዳደር በሚመለከት የማሻሻያ ጥናት
ያደርጋል፣
4. የቤቶች ኤጀንሲ ስልጣንና ተግባር
4.1. ስለ ውርስ የመንግሥት ቤቶች የወጡ ህጎች ተግባራዊነታቸውን ይከታተላል፤
4.2. በከተማው ውስጥ የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ ሊረዱ የሚችሉ ልዩ ልዩ
ጥናቶችን ያደርጋል፣ የግል ባለሀብቶች፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ
ድርጅቶችንና ማህበራት በመስኩ እንዲሳተፉ አስፈላጊውን ድጋፍ ይሰጣል፣
4.3. በከተማ የመኖሪያ ቤት ፍላጎትና አቅርቦት በማጥናት የመፍትሄ አቅጣጫ
ያስቀምጣል፣ የተቀናጀ የቤቶች ልማት ፕሮግራም በማይተገበርበት ከተማ
20
የቤት ችግር ለመቅረፍ በማዘጋጃ ቤቱ ገቢ የቁጠባ ቤቶች እንዲገነቡ
ያደርጋል፣
4.4. በከተማ ውስጥ የተጎሳቆሉና ያረጁ ውርስ የመንግሥት ቤቶችን በማጥናት
ለኢንቨስትመንት እንዲውሉ ያደርጋል፣ የሚታደሱበት ሁኔታ ያመቻቻል፣
4.5. ስለ ቤት ካሣ አከፋፈል፣ ስለ አበል አከፋፈል ስለመካካሻና አዲስ ቤት
አስተዳደር የወጡ መመሪያዎችን በሥራ ላይ እንዲውሉ ያደርጋል፣
አፈፃፀማቸውን ይከታተላል፣
4.6. በክፍለ ከተማ የሚተዳደሩ የውርስ የመንግሥት ቤቶችን አስተዳደር
ይከታተላል፣ ለኢንቨስትመንት እንዲውሉ ሲወሰን ቤቱን የተከራዩ ሰዎች
አስፈላጊ ሁኔታዎችን በማመቻቸት እንዲለቁ ያደርጋል፣
4.7. የከተማ ነዋሪዎችን የቤትን ችግር ለመቅረፍ ለመኖሪያ ቤቶች የህብረት
ሥራ ማህበራት ድጋፍ ያደርጋል፣ ይመዘግባል፣ ለሚመለከተው
ያስተላፋል፣
4.8. አነስተኛ ገቢ ላላቸው ግለሰቦች የመኖሪያ ቤት ግንባታ በቀላሉ ለማስኬድ
የሚያስችላቸው የገንዘብ ምንጭ /ብድር ወይም እርዳታ/ የሚገኝበትን
መንገድ ያጠናል፣
4.9. ውርስ የመንግሥት ቤቶች /የቁጠባ ቤቶች/ የኪራይ ዋጋ በማጥናት
በአካባቢው ገበያ ዋጋ የሚሻሻልበትን ሁኔታ በማጥናት ለበላይ ኃላፊ
ያቀርባል፣ ሲፈቀድም ተግባራዊ ያደርጋል፣
4.10. ከመንግሥት ውርስ ቤቶች የሚሰበሰበውን ኪራይ በወቅቱ ገቢ መደረጉን
ይከታተላል፡፡
5. ገቢዎች ኤጀንሲ
21
5.3. የማዘጋጃ ቤቱ ገቢ አሰባሰብ በዘመናዊ ዕቅድ የሚመራና ከብክነት የፀዳና
ውጤት ተኮር እንዲሆን ስልት ይነድፋል በዋና ሥራ አስኪያጅ ተቀባይነት
ሲያገኝ ተግባራዊ ያደርጋል፡፡
5.4. በተለያየ የገቢ ርዕሶች የሚሰበሰቡ ገቢዎች ወቅታቸውን ጠብቀው
እንዲሰበሰቡ ያደርጋል አፈፃፀሙን በየወቅቱ እየገመገመ እንዲሻሻል
ያደርጋል፡፡
5.5. የተሰበሰቡ ገቢዎች በወቅቱ በተቀመጠው ሥርዓት ገቢ እንዲደረጉ
ያደርጋል፣
5.6. የግብርና ታሪፍ ከፋዮች ዝርዝር በመረጃ እንዲያዝ ይደረጋል፣ ወቅቱን
ጠብቀው ይካተታል፣ ውዝፍ የሚሰበሰብበትን ስልት ይነድፋል፣ ሲፈቀድም
ተግባራዊ ያደርጋል፣
5.7. ኃላፊነታቸውን በማይወጡ ማናቸውም አካላት ላይ አስፈላጊው የማስተካከያ
እርምጃ እንዲወሰድ ለሚመለከተው ክፍል ያስተላልፋል፡፡
ምዕራፍ ሁለት
ስለማዘጋጃ ቤት ከተሞች
22
ሐ. የዳር ድንበሩ ክልል የተወሰነ ስፍራ ያለው እንደሆነ፣
መ. ቢሮ በሚያወጣው መመሪያ በግልጽ የሚደነገጉ ሌሎች መመዘኛዎችን
የሚያሟላ እንደሆነ ነው፡፡
1.2. ዕጩ ማዘጋጃነት የሚሰጠው በቢሮው ሆኖ የሚከተሉትን ተግባር ያስፈጽማል፡፡
ሀ. የእጩ ከተማውን የአስተዳደርና የአደረጃጀት ስርዓት ይወስናል፣
ለ. የእጩ ከተማ ፕላን አዘገጃጀትና የአፈፃፀም እንዲሁም የታሪፍ የግብር
አወሳሰን መመሪያዎችን ያወጣል፣
ሐ. በእጩ ከተማው የሚቀርቡ አገልግሎቶችን ዓይነትና ደረጃ ይወስናል፣
መ. የእጩ ከተማውን የልምድ ሂደት ይገመግማል፣ በውጤቱም መሠረት
ሀ. በከተማነት ለመቋቋም የሚያስችለውን መመዘኛ አሟልቶ ሲገኝ
በከተማነት እንዲቋቋም ለመስተዳደር ምክር ቤት አስተያያት ያቀርባል፣
ለ. በእጩ ከተማነት ለመቆየት የሚያስፈልጉትን መመዘኛዎች አጓድሎ ሲገን
ይሰርዛል፡፡
፴፬ . ቋሚ ያልሆነ የከንቲባ ኮሚቴ
1. አሰያየም
1.1. የከተማ አስተዳደር ባልተቋቋመባቸው ማዘጋጃ ቤት ከተሞች ከቀበሌ ምክር ቤት
አባላት፣ በጎ ፈቃድ ከንቲባና የከንቲባ ኮሚቴ ይሰየማሉ፡፡
1.2. የከንቲባ ኮሚቴ አባልነት የበጎ ፈቃድ ከንቲባው የሚያቀርባቸው ዕጩዎች
ዝርዝር መነሻነት በምክር ቤት ይወሰናል፡፡
1.3. በማዘጋጃ ቤት ከተሞች የሚቋቋመው ቋሚ ያልሆነ የከንቲባ ኮሚቴ ከንቲባውን
እና እሱ የሚመርጣቸውን 5 አባላት የያዘ ይሆናል፡፡
2. የኮሚቴ አባልት የስራ ድርሻ
23
3. የቀበሌ አስተዳደር ጽ/ቤት ተቀጣሪ ሠራተኛ
1. ኮሚቴው በወር አንድ ጊዜ ስብሰባ ያደርጋል፣ ሆኖም በ2/3ኛ የኮሚቴ አባላት ሲጠየቅ
ወይም በከንቲባ አነሳሽነት አስቸኳይ ስብሰባ ሊያደርግ ይችላል፡፡
2. በማንኛውም ስብሰባ ኮሚቴው አባላት ከግማሽ በላይ በስብሰባ ከተገኙ ምልአተ ጉባኤ
ይሆናል፡፡
3. የኮሚቴው ውሳኔ የሚተላለፈው ምልአተ ጉባኤው በሚያቋቁሙት አባላት አብላጫ
ድምጽ ይሆናል፣ ድምጽ እኩል በሆነ ጊዜ ሰብሳቢው የደገፈው ሀሳብ ይጸናል፣
ክፍል አምስት
ስለ ምርጫ
1. በአዋጁና በዚህ ደንብ መሰረት የከተማ ምክር ቤት አባላት ምርጫ በየአምስት ዓመቱ
የሚካድ ሲሆን ምርጫው የሚካሄድበት ጊዜ በክልሉ ምክር ቤት የሚሰጠውን ውሳኔ
ሃሳብ መሰረት በማድረግ በብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ይወሰናል፡፡
24
2. የከተማው ምክር ቤት አባላት ምርጫ አፈፃፀም የከተማውን ቀበሌዎች መሰረት
በማድረግ ይሆናል፡፡
3. የከተማው ምርጫ የሚካሄድበት ቀበሌዎች ዝርዝር የከተማውን ደረጃ መሰረት
በማድረግ ቢሮው አጥንቶ በሚያቀርበው ሀሳብ ላይ በመመስረት የክልሉ መስተዳድር
ምክ/ቤት በሚያወጣው የህግ ክፍል ማስታወቂያ ይገልፃል፡፡
4. ከእያንዳንዱ ቀበሌ ለከተማ ምክ/ቤት መቀመጫዎች የሚመረጡ ተወካዮች ብዛት
የከተማውን ደረጃና የህዝብ ብዛት መሰረት በማድረግ መስተዳድር ምክር ቤት
በሚያወጣው የህግ ክፍል ማስታወቂያ ይወሰናል፡፡
5. ከመሪ ከተማ ውጪ ባሉ ከተሞች ለከተማ ምክር ቤት ምርጫ ከከተማ ዙሪያ
የሚካተቱ የገጠር ቀበሌዎች ብዛትና የተወካዮች ቁጥር የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት
ከተማው ከሚገኝበት ልዩ ወረዳ ወይም ዞን አስተዳደር ጋር በመመካከር ሲወስን
ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
1. በአዋጁ አንቀፅ ፲፯ ንዑስ አንቀጽ 3(1) በተደነገገው መሰረት በእያዳንዱ ከተማ ውስጥ
የሚኖረውን የአካባቢ ብሄረሰቦች ተወላጆች ቁጥር መሰረት በማድረግ ተለይቶ
25
የሚቀመጠው ተጨማሪ የከተማ ምክር ቤት መቀመጫ ብዛት መስተዳድር ምክር ቤት
በሚያወጣው በህግ ክፍል ማስታወቂያ ይገለጻል፡፡
2. ለከተማው የአካባቢ ብሄረሰብ/ቦች የሚቀመጡ ተጨማሪ የከተማ ምክር ቤት
መቀመጫዎች ብሄረሰቡን/ቦቹን ከሚወክለው ከከተማው አካባቢ ገጠር ቀበሌዎች
በሚደረገው ምርጫ በሚወከሉ አባላት የሚያዝ ይሆናል፡፡
3. ከከተማው ምክር ቤት መቀመጫዎች የተወሰነው ቁጥር እንዲመደብላቸው የተወሰነው
የአካባቢ ብሄረሰቦች ቁጥር ከአንድ በላይ የሆነ እንደሆነ ለአካባቢ ብሄረሰቦች ተለይቶ
የሚቀመጠውን መቀመጫ የሚይዙ አባላት ብዛት የብሄረሰቦቹን ተዋፅኦ በማገናዘብ
የሚወሰን ይሆናል፡፡
4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2 ና 3 ሥር የተመለከቱ ድንጋጌዎች የክልሉ መስተዳድር
ምክር ቤት ከተማው ከሚገኝበት ልዩ ወረዳ ወይም ዞን አስተዳደር ምክር ቤት ጋር
በመመካከር በሚወስነው መሰረት የሚፈፀም ይሆናል፡፡
፵፩ . ልዩ መብት
ክፍል ስድስት
የክፍለ ከተሞች አደረጃጀትና አስፈጻሚ አካላት
፵፫. ስለ ክፍለ ከተሞች መቋቋም
26
፵፬. የክፍለ ከተሞች ተጠሪነት
27
9. የክፍለ ከተማ አስፈጻሚና የማዘጋጃ ቤት አገልግሎት ሥራዎችን ይመራል፣
ያስተባብራል፣
10.የአገልግሎት አሰጣጥ ቀልጣፋ፣ ግልጽና ተጠያቂነት ያለበት እንዲሆን ያደርጋል፡፡
የሚሻሻልበትን ሁኔታ ያመቻቻል፣
28
1.3. በክፍለ ከተማው ውስጥ ከመንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር
ግንኙነት በመፍጠር የጥቃቅን አነስተኛ የንግድ ስራ ማህበራት ድጋፍ
እንዲያገኙ ሁኔታዎችን ያመቻቻል፣ በተለይም የማምረቻና መሸጫ ቦታዎች፣
የፋይናንስ የብድር አገልግሎቶች፣ የጥሬ እቃና የማምረቻ መሳሪያዎች
በአንድ ማዕከል የሚያገኙበትን ሁኔታ ያመቻቻል፡፡
1.4. የጥቃቅን አነስተኛ ንግድ ስራዎች ማሰልጠኛ ማእከላት እንዲቋቋሙ
ሁኔታዎችን ያመቻቻል፣ በዘርፉ ለተሰማሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ስልጠናዎች
እንዲዘጋጅ ያደርጋል፣ ያስተባብራል፣
1.5. በክፍለ ከተማ ውስጥ የሚገኙትን ስራ አጥ የሆኑ ወጣቶችና ሴቶች አምራች
ዜጋ ሊያደርጉ የሚችሉ፣ የጥቃቅንና አነስተኛ የንግድ ስራ ፕሮጀክቶች
እንዲጠኑ ያደርጋል፣ ተግባራዊነቱን ይከታተላል፣
1.6. መረጃና ምክር ለተጠቃሚዎች የሚሰጥበትን ስርዓት ይዘረጋል፣
29
3.2. ግብር ከፋዮች ህጎችን አውቀው መብትና ግዴታቸውን እንዲወጡ
ይቀሰቅሳል፣ ግብር የመክፈል ግዴታቸውን በህግ መሰረት እንዲፈጽሙ
ያደርጋል፣
3.3. የክፍለ ከተማው ገቢ የሚያድግበትን ያጠናል፣ የገቢ አሰባሰብ ህጎችና ደንቦች
በስራ ላይ እንዲውሉ ያደርጋል፣
3.4. ግብር ከፋዮች ለይቶ ለማወቅና ለመመዝገብ የሚያስችሉ አሰራሮችን
ተግባራዊ ያደርጋል፣
3.5. የክፍለ ከተማው ሌሎች ገቢዎች በወቅቱ እንዲሰባሰቡ ያደርጋል፣
3.6. የገቢና አወሳሰንና የሂሳብ አያያዝ ብቃት ባለው መልኩ ለማከናወን
የሚያስችሉ የአሰራር ዘዴዎችን ይቀይሳል፣ ተግባራዊነታቸውን ይከታተላል፣
4. ወጣቶች፣ ስፖርትና የአካባቢ ልማት ጽ/ቤት
4.1. የከተማው ወጣቶች በልማትና በዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሊሳተፉ
የሚችሉበትን እንዲሁም ወጣቶች በመልካም ስነ-ምግባር እንዲታነጹና
እውቀት ለመቅሰም የሚያስችላቸውን አገልግሎቶች ማግኘት የሚችሉበት
ሁኔታ ያመቻቻል፣
4.2. ስፖርት የሚሻሻልበትና የሚያድግበት ስልት ይቀይሳል፣ የስፖርት
ማዘውተሪያ ስፍራዎች በአግባቡ እንዲያዙና እንዲጠበቁ ያደርጋል፣ አግባብ
ካላቸው ድርጅቶችና ባለሀብቶች ጋር በመተባበር የስፖርት ትጥቅና
መሳሪያዎች በክፍለ ከተማ ውስጥ እንዲመረቱ ያበረታታል፣ በእርዳታና
በግዥ የሚገኙበትን ሁኔታ ያመቻቻል፣
4.3. ለጎርፉ የተጋለጡ የከተማውን ክፍሎች በተመለከተ ነዋሪዎችንና ሌሎች
ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር የጎርፍ መከላከያ ግንባታ
ያከናውናል ወይም እንዲከናወን ያደርጋል፡፡
4.4. በከተማው የሚገኙ የመዝናኛ ሥፍራዎችና ፓርኮች ያደራጃል፣ ይመራል፣
የሚለሙበት ስልት እየቀየሰ ያስተባብራል፣
4.5. በክፍለ ከተሞች መካከል የሚካሄዱ የአካባቢ ልማት ስራዎች የተጣጣሙና
የተደጋገፉ እንዲሆኑ ያስተባራል፡፡
30
ስልት ይቀይሳል፣ ማህበራት የእርስ በእርስ ተሞክሮ ልውውጥና መደጋገፍ
እንዲያደርጉ በቅንጅት እንዲንቀሳቀሱ ተገቢውን ጥረት ያደርጋል፣
ያበረታታል፣
5.2. በከተማ ውስጥ ማህበራዊ ችግሮችና ጠንቆች ሊወገዱ የሚችሉባቸውን
ህብረተሰቡን የሚያሳትፍ ስልቶች ይቀይሳል፣ ሲፀድቁም ተግባራዊ
መሆናቸውን ያረጋግጣል፣
5.3. መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች በኩል ማህበራዊ ደህንነት በሚመለከት
ለሚካሄዱ ስራዎች ደጋፍ ይሰጣል፣
5.4. ማህበራትን በህብረተሰብ ውስጥ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ተሳትፎ
እንዲያደርጉ ድጋፍ ይሰጣል፡፡
5.5. የሴቶችን አቅም የሚያጎለብቱ ትምህርታዊ፣ ሙያዊ ፣ የተጨማሪ ክህሎት
ስልጠናዎችን ያመቻቻል፣ ሴቶችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶችን
ያፈላልጋል፣
5.6. አግባብ ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር ሴቶችን በማህበራት እንዲደራጁ
የብድርና የቁጠባ አገልግሎቶች እንዲያገኙ ሁኔታዎችን ያመቻቻል፣
5.7. በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ይከላከላል፣
5.8. በኤች አይቪ ኤድስ ላይ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የሚሰጡ ተቋማትን
ያስተባብራል፣ የተጠቁትን አካላት እንክብካቤ የሚያገኙበት ሁኔታ
ያመቻቻል፣
6. የክፍለ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጅ
6.1. መናፈሻዎችን፣ መካነ መቃብርና የጋራ መጸዳጃ ቤቶችን ያስተዳድራል፣
ያስፋፋል፣
6.2. መናፈሻዎች ለተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች እንዲያገለግሉ ያደርጋል፣
መዝናኛዎችን አዘጋጅቶ ያቀርባል፣
6.3. ኅብረተሰቡን በመናፈሻዎች ልማትና እንክብካቤ ያሳትፋል፣
6.4. የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ በተመለከተ የግል ባለሀብቶችና ሌሎች የኅብረተሰብ
ክፍሎች እንዲሳተፉ ያደርጋል፣
6.5. ደረቅ ቆሻሻ እንደገና በስራ ላይ የሚውልበትንና ጠቃሚ ውጤት
የሚያስገኝበትን ስልት በማጥናት ተግባራዊ የሚሆንበትን ሁኔታ
ያመቻቻል፣
31
6.6. በክፍለ ከተማው ባለቤትነት ሥር ያሉ ቤቶችን ይመዘግባል፣ ያስተዳድራል ፣
ቤቶችን በመሻሻል ወደ ግል ባለቤትነት የሚዛወሩበትን ሁኔታ አጥንቶ
ያቀርባል፣
6.7. ቤቶች በሚሰሩበት አካባቢ መሰረተ ልማቶችና ማህበራዊ አገልግሎቶች
የሚሟሉበት ሁኔታ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆኑ ያመቻቻል፣
6.8. በቤት ስራ ማህበራትና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች የመኖሪያ ቤት
ግንባታ እንዲካሄድ ያበረታታል የቴክኒክ ድጋፍ ይሰጣል፣
6.9. እንዲለሙ የሚፈለጉ ቦታዎችን በማጥናት ያዘጋጃል፣
6.10. የመሬት ልማት ሥራ ለማከናወን ፍላጎት ካላቸው አልሚዎች ጋር በጋራ
በመስራት የልማት ስራው የሚካሄድበትን ሁኔታ ያመቻቻል አፈጻጸሙን
ይከታተላል፣
6.11. በካሳ ክፍያ አፈፃፀም መመሪያ መሰረት ተመጣጣኝ ካሳ መከፈሉን
ያረጋግጣል፣
6.12. የግንባታ ህጎች ተግባራዊ መሆናቸውን ያረጋግጣል፣
6.13. የመብራት ሀይል፣ የስልክ፣ የውሃና የመሳሰሉት የመሰረተ ልማት
ግንባታዎች በተቀናጀ ዲዛይን ተጣጥመው እንዲካሄዱ ያስተባብራል፣
6.14. በመሰረተ ልማት ስራዎች ህብረተሰቡ እንዲሳተፍ ሁኔታዎችን ያመቻቻል፣
6.15. ለጎርፍ የተጋለጡ የከተማውን ክፍሎች በተመለከተ የጎርፍ መከላከያ ጥናት
በማድረግ ሲጸድቅም ደረጃ በደረጃ ተግባራዊ መሆኑን ያረጋግጣ፣
6.16. ልደት፣ ሞት፣ ጋብቻ፣ ፍቺ ይመዘግባል፣ የምስክር ወረቀት ይሰጣል፣
6.17. ለነዋሪዎች የነዋሪነት መታወቂያ ወረቀት የሚሰጥበት ሁኔታ ያመቻቻል፣
6.18. በከተማው ተወስኖ ከሚሰጥ የገቢ ምንጮች የማዘጋጃ ቤት ገቢ ያሰበስባል፡፡
ክፍል ሰባት
32
2. በእያንዳንዱ የከተማ አስተዳደር የሚኖሩ የቀበሌ አስተዳደሮች ዝርዝር የክልሉ
መስተዳድር ምክር ቤት በህግ ክፍል ማስታወቂያ ይገለጻል፣
33
4. በቀበሌ ሊቀመንበር አቅራቢነት የቀበሌውን ኮሚቴ አባላትና ማህበራዊ ሸንጎ
ዳኖች ሹመት ያጸድቃል፣
5. የቀበሌ ምክር ቤት ኮሚቴዎችን ያቋቁማል፣
6. በቀበሌው ሊቀ መንበር የሚቀርቡ ዓመታዊና ወቅታዊ ሪፖርት መርምሮ ውሳኔ
ይሰጣል፣
ክፍል ስምንት
ስለ ማህበራዊ ሸንጎና ደንብ አስከባሪ አካል
የቀበሌ ማበራዊ ፍርድ ቤቶችን እንደገና ለማቋቋም በወጣው አዋጅ ቁጥር 65/95
የተደነገገው የማህበራዊ ፍርድ ቤት የዳኝነት ስልጣን እንደተጠበቀ ሆኖ በሚከተሉት
ጉዳዮች ስልጣንና የተሟላ ዳኝነት ይኖረዋል፣
35
2. የማህበራዊ ሸንጎ ፍርድ ቤት ዳኞች በቀበሌው ሊቀመንበር አቅራቢነት በቀበሌው ምክር
ቤት ይሾማሉ፣
ክፍል ዘጠኝ
ስለግንኙነትና የሪፖርት ስርዓት
፷. የከተማና የመንግስት ግንኙነት
36
፷፩. ሕጎችን ደንቦችንና ደረጃዎችን ስለማስፈጸም፣
37
1.6. ለሚቀጥለው ወቅት የታቀዱ ተግባራት
1.7. እቅዶችን ለመፈጸም የሚያስፈልጉ ግብአቶች፣ ከመንግስት የሚያስፈልገው
ትብብርና ድጋፍ፣
2. የገንዘብ አጠቃቀም ሪፖርት በዋነኝነት የሚከተሉትን ማካተት አለበት፣
2.1. የገንዘብ አጠቃቀም እቅድ
2.2. በወቅቱ የተገኘው ገቢ
2.3. በወቅቱ የወጣውን ወጪ
2.4. ለሚቀጥለው ወቅት የተዘጋጀውን የገንዘብ አጠቃቀም እቅድ
2.5. እቅዶችን ለመፈጸም ከመንግስት የሚያስፈልገውን ትብብርና ድጋፍ፣
3. የስራ አፈፃፀም ሪፖርቱም ሆነ የገንዘብ አጠቃቀም ሪፖርቱ አስፈላጊ የሆኑ የድጋፍ
ሰነዶች/መረጃዎች/ ያካተተ ይሆናል፣
38
6. ሁኔታው ከተማው ምክር ቤት መፍረስ የሚያመለክት ከሆነ ውሳኔው በአዋጁ
አንቀጽ 19 በተመለከተው መሰረት በክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት የሚሰጥ
ይሆናል፣
ክፍል አሥር
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
፷፮. የመሸጋገሪያ ድንጋጌ
39