Download as doc, pdf, or txt
Download as doc, pdf, or txt
You are on page 1of 6

(

በሀብት በገንዘብ ማገልገል የገንዘብ አገልግሎት )


 መፅሐፍ ቅዱስ እግዚአቢሔር የበረከት ሁሉ ባለቤት እና ምንጭ እንደሆነ በግልፅ ይነግረናል፡፡
" ብሩ የእኔ ነው ወርቁም የእኔ ነዉ " U ጌ 1፡8
- ከበረከቱ ለወደደው እንደወደዳ ይሰጣል ለአላማኙ ለፍጥረት ሳይቀር
- በፈለገበት ጊዜ ይሰጣል በፈለገበት ጊዜ ይነሳል
 የዚህ ትምህርት ዓላማ አማኝ ሁሉ በተለይ የቤተክርስቲያናችን አባላት ሁሉ እግዚአቢሔር በኪዳኑ ባፁናው
በረከት ውስጥ እንደገቡ እና በእዚያም እንዲቆዩ መርዳት ማሣየት ነው።
 በኪዳን የፀና በረከት ማለት
- የበረከቱ ምንጭ እና የበረከቱ አስቀጣይ እግዚአብሔር እራሱ ነው
- በረከቱ በግልፅ በልዩነት እየጨመረ የሚሄድ እንጂ የሚፈተን አይደለም
አብርሃም የተባረከበት አይነት....ባለፀጋ ነበር 300 ሰራተኞ አሉት
ያዕቆብ የተባረከበት አይነት........በላባ ቤት በተዓምራት ተባረከ
ይስሃቅ የተባረከበት አይነት........በዚያች አመት መቶ አገኘእጥፍ
እስራኤላውያን በተለያየ ጊዜ የተባረከበት አይነት በረከትናቸው
" ከዚች ቀን ጀምሬ እባርካችዋለው " ሀጌ 2 : 19
 በኪዳን የፀና በረከት ወደ እነዚህ ሰዎች የመጣበት ምክንያት የተለያየ ቢሆንም በሀጌ ዘመን የተገለጠው ግን
እግዚአብሔር በሰጣቸው ሀብት እግዚአቢሔርን ለማገልገል በመወሰናቸው ነው።
 ቀድሞ በነበረ ጊዜ እግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በዘነጋ መልኩ ይመላለሱ ነበር
 እግ/ር በነብዩ በኩል ከተቆጣቸው ቡሃላ ግን ፊታቸውን በገንዘባቸው ወደ ማገልገል ዞር አድርገዋል፡፡
 እግዚአብሔርም ከዚች ቀን ጀምሮ ሊባርባቸው ቃል ገብቶላቸዋል።
 ዛሬም በዚህ አይነት በረከት ቤ/ክ እንድትባረክ ያስፈልጋታል
 መንገዱ እግዚአብሔር የሰጠንን ሀብት/ ገንዘብ በተገቢ ሁኔታ መጠቀም ማስተዳደር እና በእግዚአቢሔር
መንግስት ላይ በተገቢ ሁኔታ ማዋል ናቸው።
 ለዚህ የሚረዳውን በገንዘብ የማገልገል ምንነት እንደሚከተለው እናያለን
1 - ሀብት በገንዘብ እራሱ ምንድን ነዉ?
U) በትክክለኛ አያያዝ ሲሆን
~ ሀብት መገልገያ ነው።
~ መሠረታዊ እና መሰረታዊ ላልሆኑ ፍላጎቶቻችን ማሟያ ነው
~ እለፍ ሲል ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጠ አደራ
ለ) አያያዙ እና እይታው ሲበላሽ
~ መውደድ ሲጨመርበት የሐጥያት ሁሉ ስር/ምንጭ ነው 1 ጢም 6:9-10
~ ልብን መግዛት ሲጀምር የጌታን ስፍራ ሊወስድ የሚችል ሌላኛው ጌታ ነው ማቴ፡2፡6 :24
~ አታላይ ነው ማቴ 13፡22 የባለጠግነት ማታለል እንደያፈራ አንቀዉ
~ ሰዎች ወደ መንግስተ ሰማያት በሚያደርጉት ጉዞ ላይ ያለ መሰናክል ነው ማቴ 19፡23-24
~ በመጨረሻው ዘመን የብዙዎችን ትኩረት የሚይዝ ጉዳይ ነው 1 ጢም 3:1-2
2- በገንዘብ ማገልገል ማለት ምን ማለት ነው?
~ እግዚአብሔር በሰጠን ሀብት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለወንጌል አገልግሎት አቅም መሆን ማለት ነው
ፍሊ 4:16-19
~ በእጃችን ያለዉን ሀብት እንደ ባለ አደራ ክርስቲያናዊ ስነ ምግባርን በጠበቀ እና ተገቢ በሆነ መንገድ
መጠቀም ማለት ነው
~ ከትርፉ ብቻ ሣይሆን ከጉድለትም ቢሆን ለ ወንጌል አገልግሎት መቆረስ ማለት ነው። ማር 12፡44
~ የራስን ፍላጎት ከማርካት አልፎ ወይም ቆርሶ ለሌሎ መትረፍ መቻል ማለት ነው። ኤፌ 4፡28
~ ለእግዚአብሔር ቀጣይ በረከት እንራስን ማዘጋጀት ማለት ነው ማቴ 25 ሚል 3
~ በጌታ ምፅዓት ቀን ዋጋ ባለዉ ለአክሊል በሚያበቃ መልኩ ስራ ላይ ማዋል ማለት ነው። ሉቃ 12 ሰነፉ
ገበሬ በምድር ሚያከማች በእግዚአቢሔር ዘንድ ባለጠጋ ያልሆነ
3- በገንዘብ ማገልገል ማለት ምን ማለት አይደለም?
~ የገንዘብ አገልግሎት ማለት በገንዘብም ማገልገል ማለት ነዉ እንጂ በገንዘብ ብቻ ማገልገል ማለት
አደለም። በልዩ ሁኔታ ለጥቂቶች ብቻ ካልሆነ በስተቀር።
~ እራስን እና ጊዜን ከመስጠት በፊት የሚመጣ አገልግሎት አይደለም
~ ጥሩ ላልሆነ ህይወት ቢዝነስ እና ምስክርነት ማካካሻ የሚሆን አገልግሎት አይደለም።
4 - ለአገልግሎት የማይውሉ ገንዘቦች አሉ ወይ?
~ በግፍ እና በማጭበርበር ከተገኘ ሀብት የሚደረግን አገልግሎት ቤ/ክ ልትቀበልትችል ይሆናል።
በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ተቀባይነት የለውም።
~ አራጣ በማበደር የተገኘ ትርፍ የተጨነቀን በማስጨነቅ የተገኘ በመሆኑ
~ ሐጥያት በሆኑ የስራ መስኮች በመሳተፍ የሚገኝ ገንዘብ
~ ለተይታ ለሰው ሙገሳ የሚደረግ አገልግሎት ከልብ ስላልሆነ ዋጋ የለውም
 በገንዘብ የምናገለግልባቸው 6 ቱ መንገዶች
1. በመባ ስጦታ
 የመባ ስጦታ ሰዉ በእግዚአቢሔር ፊት ለመታየት በሚመጣበት ጊዜ ባዶ እጁን እንዳይመጣ
እግዚአብሔር የሰጠው ትዕዛዝ ነው።
 ሰዉ ከእግዚአብሔር የሚፈልገውን ጉዳይ እንደሚጠባበቅ ሁሉ ካለው ነገር ሁሉ ደግሞ ለጌታ ስጦታ
ይዞ የሚመጣበት ስርዓት ነው።
 ሰዉ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት በዶ እጁን እንዳይታይ አዞዋቸው ነበር።
“ስጦታ ያመጡልኝ ዘንድ ለእስራኤል ልጆች ተናገር፤ በገዛ እጁ ሊሰጠኝ በልቡ ከሚያምረው ሰው
ሁሉ መባ ተቀበሉ።” ዘጸአት 25፥2
 ማንም ሰው ባዶ እጁን አይታይ ይላልና ...... ምሳሌ
2. በኩራት/የምስራች ስጦታ
 በኵራትን መስጠት የተጀመረው በአቤል ነው። ከበጎቹ በኵረት አቀረበ
 በሙሴ በኩል በኵር ሁሉ የእግዚአብሔር እንደሆነ ተናግሯል፡፡ ሰውን ጨምሮ።
 የመጀመሪያ ፍሬ ሁሉ እንዲሁ የእግዚአብሔር ነው።
“ለእስራኤል ልጆች እንዲህ ብለህ ንገራቸው፦ ወደምሰጣችሁ ምድር በገባችሁ ጊዜ፥ መከሩንም
ባጨዳችሁ ጊዜ፥ የእናንተን መከር በኵራት ነዶ ወደ ካህኑ አምጡ፤” — ዘሌዋውያን 23፥10
 በኵራት በዚህ ዘመን ጥቂቶች ብቻ የሚሰጡት ነው
 የመጀመርያ የሆነ ሁሉ ለእግዚአቢሔር መሆን አለበት
3. ስጦታ በመስጠት ነው
 ስጦታ መፅሐፍ ቅዱሣዊ በገንዘብ የምናገለግልበት አንዱ መንገድነው።
"ስጦታ ያመጡልኝ ዘንድ ለእስራኤል ልጆች ተናገር፤ በገዛ እጁ ሊሰጠኝ በልቡ ከሚያምረው ሰው ሁሉ
መባ ተቀበሉ።” ዘጸአት 25፥2
 እስራኤላውያን በተለያየ ጊዜ ስጦታ ሰጥተዋል። በተለይ በቤተመቅደስ ስራ ላይ።
 ያላቸውን ሁሉ ወርቃቸውን ብራቸውን ለእግዚአቢሔር ጠት ይስጡ ነበር።
 አህዛብን ጨምሮ እግዚአብሔር ያነሣሣቸው ሁሉ በታሪክ ስጦታን ይስጡ ነበር
 መገናኛ ድንኳን በነበረ ጊዜ በነህምያ የተሃድሶ ጊዜ የሰለሞን ቤተ መቅደስ በተሰራ ጊዜ በሚታስስበት
ጊዜ ስጦታዎች ይመጡ ነበር።
ዘጸአት 35
²¹ከእነርሱም ሰው ሁሉ ልቡ እንዳነሣሣው መንፈሱም እሺ እንዳሰኘው ለመገናኛው ድንኳን ሥራ
ለማገልገያውም ሁሉ ለተቀደሰውም ልብስ ለእግዚአብሔር ስጦታ አመጡ።
²² ወንዶችና ሴቶችም ልባቸው እንደ ፈቀደ ማርዳዎችን፥ ሎቲዎችንም፥ ቀለበቶችንም፥
ድሪዎችንም፥ የወርቅ ጌጦችንም ሁሉ አመጡ፤ ሰዎችም ሁሉ የወርቅ ስጦታ ወደ እግዚአብሔር
አቀረቡ።
 በሐዋርያት ዘመን ለወንጌል አገልግሎት እንዲውል ስጦታን አሰባስበው የስረከቡ ነበር።
 ፊልጵስዩስ 4
¹⁸ ነገር ግን ሁሉ አለኝ ይበዛልኝማል፤ የመዓዛ ሽታና የተወደደ መሥዋዕት የሚሆነውን
ለእግዚአብሔርም ደስ የሚያሰኘውን ስጦታችሁን ከአፍሮዲጡ ተቀብዬ ተሞልቼአለሁ።
¹⁹አምላኬም እንደ ባለ ጠግነቱ መጠን በክብር በክርስቶስ ኢየሱስ የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ
ይሞላባችኋል።

በገንዘብ ማገልገል
በገንዘብ ማገልገል
ክለሣ
 ገንዘብ መገልገያ ነው ብለናል
 የተሣሣተ እይታ እና አያያዝ ካለ ግን ከጌታ ጋር ያለንን ግንኙነት የሚያበላሽ አደገኛ ሁኔታ ውስጥ
የሚያስገባን ነገር ነው
~ ከወደድነው የሐጥያት ሁሉ ምንጭ ነው
~ የእግዚአብሔርን ቦታ የሚተካ ጌታ
~ አታላይ ነው
~ በመንግስተ ሰማየት መንገድ ላይ ያለ ወጥመድ ነው
 በገንዘብ ማገልገል ማለት
~ ከአጠቃቀሞ ጠናማነት ጀሞ ለሌሎች መቆረስን የሚያካትት ነው
~ በወንጌል አገልግሎ ላይ በቀጥታም በሌላም አስዋጽዖ ማድረግ ማለት ነው
~ ከትርፍ / ሲተርፉ መስጠት ሳይሆን ከልብ ትዳርን አስከ መጣል በሚመስል መስጠት መስጠት ማለት
ነው።
 በገንዘብ የምናገለግልባቸው 6 መንገዶች አሉ ብለን 3 አይተን ነበር
~ መባ
~ በኵራት
~ ስጦታ
ዛሬ የተቀሩትን 3 ቱን እናያለን
4. በበጎ አድራጎት ስራ ላይ በማዋል ነው
 በጎ ማድረግ ለተቸገሩት እና እርዳታችንን ለሚፈልጉ መዘርጋት በፍላጎት የሚደረግ ጉዳይ ሳይሆን
የክርስቲያናዊ ግዳታ ነዉ
 በጎ ማድረግ እግዚአቢሔር ደስ ከሚሰኝበት አገልግሎታችን መካከል አንዱ ነው
 ሐዋርያት የአገልግሎትቸው አንድ አካል እንዲያደርጉ አደራ የተባሉበት ጉዳይ ነው
 የክርስቶስ ፍቅር እና ርህራሄ ያለን መሆኑ የሚያሳይ ጉዳይ ነዉ
“ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት አምልኮ በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ይህ ነው፤ ወላጆች የሌላቸውን
ልጆች ባልቴቶችንም በመከራቸው መጠየቅ፥ ....።” — ያዕቆብ 1፥27
“ነገር ግን መልካም ማድረግን ለሌሎችም ማካፈልን አትርሱ፤ እንዲህ ያለው መሥዋዕት
እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋልና።”— ዕብ 13፥16
ገላትያ 2
⁹ ደግሞ የተሰጠኝን ጸጋ አውቀው፥ አዕማድ መስለው የሚታዩ ያዕቆብና ኬፋ ዮሐንስም እኛ ወደ
አሕዛብ እነርሱም ወደ ተገረዙት ይሄዱ ዘንድ ለእኔና ለበርናባስ ቀኝ እጃቸውን ሰጡን፤
¹⁰ ድሆችን እናስብ ዘንድ ብቻ ለመኑን፥ ይህንም ደግሞ ላደርግ ተጋሁ።
“ነገር ግን የዚህ ዓለም ገንዘብ ያለው፥ ወንድሙም የሚያስፈልገው ሲያጣ አይቶ ያልራራለት
ማንም ቢሆን፥ የእግዚአብሔር ፍቅር በእርሱ እንዴት ይኖራል?” — 1 ኛ ዮሐንስ 3፥17
“አምላክህ እግዚአብሔር በሰጠህ በአገርህ ደጅ ውስጥ ከሚኖሩ ከወንድሞችህ አንዱ ቢደኸይ፥
ልብህን አታጽና፥ በድሀው ወንድምህ ላይ እጅህን አትጨብጥ።” — ዘዳግም 15፥7
5. አስራትን በመክፈል
 አስራትን በተመለከተ እንደዚች ቤ/ክ ሰፊ ክፍተት አለ
 ይህ ትምህርት እንዲዘጋጅ የተፈለገውም ከዚህ በመነሳት ነው
 ያለው ችግር ምንድን ነዉ?
 1 ኛ ሰዉ አስራት አይከፍልም የመድረክ አገልጋዮችም ጭምር
 2 ኛ የሚከፈለውም በትክክለኛ ጊዜ ኣይከፍልም አብዛኛው ሰው ደስ ባለው ጊዜ ነው የሚከፍልው
 3 ኛ በዚህም ጊዜ ቢሆን ትክክለኛ መጠን አይከፍልም ጥቁት ሰው ብቻ በዚህ ልክ ተጠንቅቆ ይከፍላል

 ለምን? ያለማወቅ ነው? አደለም ታደያስ? በአመት አንድ ጊዜ ት/ት ይሰጣል
 1 ኛ: እግዚአብሔርን ያለማመን ጉዳይ ነዉ
 ሰዉ አስራት በመክፈሉ የሚጎድልበት ይመስለዋል
 እግዚአብሔር ሰጪ ነዉ ብሎ ያለማመን ጉዳይ ነዉ
 እግዚአብሔር ግን ስጡኝ እና ፍትኑኝ የሚጎድልባችሁ ስትሰጡ ሳይሆን ሳትሰጡ ስትቀሩ ነዉ
 “በቤቴ ውስጥ መብል እንዲሆን አሥራቱን ሁሉ ወደ ጎተራ አግቡ የሰማይንም መስኮት
ባልከፍትላችሁ፥ በረከትንም አትረፍርፌ ባላፈስስላችሁ በዚህ ፈትኑኝ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ
እግዚአብሔር።”
 — ሚልክያስ 3፥10
 በአዲስ ኪዳን አገልግሎቱን መደገፉን ስቶ መቀበል ዘርቶ ማጨድ ይለዋል ፍሊ 4:15 -17
 2 ኛ፡ የእራስ ወዳድነት ጉዳይ ነዉ
 ገንዘቡ ለቤ/ክ ይልቅ እኔን ያስፈልገኛል ብሎ ማሰብ ነው
 መክፈል እንዳለበት እያወቀ ብሰራበት ብጠቀምበት በሚል ሀሳብ በመያዝ ሌላ ጊዜ ለመስጠት
ያቆየዋል
 ሌላ ጊዜ ሌላ ፈተና መጥቶ ሀሳብ ይቀየራል ወይም ገንዘቡ ያሣሣው እና መከፈሉ ይቀራል
ኣሚል 3 ሁል ጊዜ መብል እንዲኖር
በጊዜው መስጠት ይኖርበታል በሣምነት በወር እና ለጥቂቶች በ 3 ወር
 3 ኛ፡ በታማኝነት አለመክፈል
 በአዲስ ኪዳን አስራት 1/10 ኛ አይደለም ሁለንተናን /እራስን እስከ መስጠት ነው
 ቢያንስ ግን ሰዉ 10 ኛውን መስጠት ይኖርበታል። ነገር ግን 10 ኛውን እራሱ ሰዉ አይከፍልም
2 ኛ ቆሮ 9
⁶ ይህንም እላለሁ፦ በጥቂት የሚዘራ በጥቂት ደግሞ ያጭዳል፥ በበረከትም የሚዘራ በበረከት ደግሞ
ያጭዳል።
⁷ እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፥ በኀዘን ወይም በግድ
አይደለም።
 ስለ አስራት አንዳንድ ነገሮችን እናንሣ
 አስራትን ማን ነው መክፈል ያለበት
 ለዚህ ጥያቄ መልስ ለማግኘት ለመጀመሪያ ጊዜ በመሃላ ሊስጥ ቃል የገባው ያዕቆብን ሊስጥ
የተነሣበትን ሀሳብ ማየት ጥሩ ነው።
 ያዕቆብ በራሱ ጊዜ ተነሣስቶ አስራቱን ሊሰጥ ቃል የገባ ሰው ነው
 ምክንያቱ ደግሞ እግዚአብሔር የሚባለውን የሚጠጣውን እና የሚለብሰውን እግዚአብሔር
ስላላሣጣው ነው
ዘፍጥረት 28
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁰ ያዕቆብም እንዲህ ብሎ ስእለት ተሳለ፦ እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ቢሆን፥ በምሄድባትም በዚች
መንገድ ቢጠብቀኝ፥ የምበላውንም እንጀራ የምለብሰውንም ልብስ ቢሰጠኝ፥
²¹ ወደ አባቴ ቤትም በጤና ብመለስ፥ እግዚአብሔር አምላኬ ይሆንልኛል፤
²² ለሐውልት የተከልሁት ይህም ድንጋይ የእግዚአብሔር ቤት ይሆናል፤ ከሰጠኸኝም ሁሉ ለአንተ
ከአሥር እጅ አንዱን እሰጥሃለሁ።
 ስለዚህ አስራትን መክፈል የሚገባው እግዚአቢሔር የሚያስፈልገውን የሰጠው ሰዉ ነዉ
 የበረከቱ ምንጭ እራሱ እግዚአብሔር መሆኑን የሚያምን ሁሉ ነው
 የተረፈው ብዙ ያለው አገልጋዮች የፈለጋ አይደለም
 የሚያስፈለገውን እግዚአብሔር የሰጠው ሰዉ ሁሉ ነው
 ለምንድን ነው መክፈል ያለበት?
 ለቤ/ክ አገልግሎት እና ለአገልጋዮች አስፈላጊውን ነገር ለማድርግ ነው
 የተቸገሩትን ደካሞችን ለመርዳት ነው
 ዘዳግም 14
 ²² ከእርሻህ በየዓመቱ ከምታገኘው ከዘርህ ፍሬ ሁሉ አሥራት ታወጣለህ።

²⁷ ድርሻና ርስት ከአንተ ጋር ስለሌለው በአገርህ ደጅ ውስጥ ያለውን ሌዋዊ ቸል አትበል።
²⁸ በየሦስተኛው ዓመት መጨረሻ በዚያ ዓመት የፍሬህን አሥራት ሁሉ አምጥተህ በአገርህ ደጅ ውስጥ ታኖረዋለህ፤
²⁹ ሌዋዊውም፥ ከአንተ ጋር ክፍልና ርስት የለውምና፥ በአገርህም ደጅ ያለ መጻተኛ ድሀ አደግም መበለትም
መጥተው ይበላሉ ይጠግባሉም፤ ይኸውም አምላክህ እግዚአብሔር በምታደርገው በእጅህ ሥራ ሁሉ ይባርክህ ዘንድ
ነው።
እንዴት ነው የሚሰጠው
 ገብቶን እና ደስ እያለን እንጂ ግድ ሆኖብን መስጠት የለብንም
 የሚሰጥ በልግስና እንጂ ብድራት ፍለጋ መሆን የለበትም
 እኛ እራሱ የጌታ መሆናችን ተረድተን የእኛ የሆነው ሁሉ የእርሱ መሆኑን በማመን ልንሰጥ ይገባል። አስራት
የቸርነት ጉዳይ ሳይሆን የመታመን ጉዳይ ነው። ስራቃችሁኛል!
6. ገንዘባችን ከክፉ ዓላማ በመጠበቅ
 ገንዘብ አቅም ነው። ገንዘብ ያለዉ ብዙ ነገር የማድረግ አቅም አለው።
 ገንዘባችን ከእግዚአብሔር መንግስት ሀሳብ ጋር ተቃራኒ ለቆመ ነገር ሀይል መሆን የለበትም።
“ኢየሱስ ግን አሳባቸውን አውቆ እንዲህ አላቸው፦ እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግሥት ሁላ
ትጠፋለች፥ እርስ በርሱ የሚለያይ ከተማም ሁሉ ወይም ቤት አይቆምም።” — ማቴዎስ 12፥25
 ልናፈርሰው የተሰማራንበትን የሰይጣንን መንግስት የሚገነባ ነገር ልናደርግ አይገባንም
 በፀሎታችን በትምህርቶችን በህይወታችን አንድ አይነት አቌም ከሌለን ለጠላት ምቹ እድል ነው
የሚፈጥረው
 ልጆቻችን በሱስ እንዳይያዙ እየፀለይን እየመከረን በገንዘባችን በዚህ ተቃራኒ ብንቶም አይሆንም
 እዚህ ጋር የሰሞኑን የቤ/ክ መመሪያ ላንሣ

You might also like