Download as pdf or txt
Download as pdf or txt
You are on page 1of 18

የሕማማት ስርአት

በሰሙነ ሕማማት አስር የጸሎት ጊዜያት ያሉ ሲሆን


እነዚህም
1:የቀን 1 ሰአት ጸሎት 6: የማታ 1 ሰአት ጸሎት
2:የቀን 3 ሰአት ጸሎት 7: የማታ 3 ሰአት ጸሎት
3:የቀን 6 ሰአት ጸሎት 8: የማታ 6 ሰአት ጸሎት
4:የቀን 9 ሰአት ጸሎት 9: የማታ 9 ሰአት ጸሎት
5:የቀን 11 ሰአት ጸሎት 10:የማታ 11 ሰአት ጸሎት

በእያንዳንዱ የጸሎት ሰአት ውስጥ ያሉ መርኀ ግብሮችን ለማወቅና ለማጥናት እንዲረዳን ከሞላ ጎደል በሁሉም የጸሎት
ሰአታት ውስጥ የማይቀሩትን የጸሎት ክፍሎች በሰባት ከፍለን እንያቸው።
ክፍል 1:አቡን እና ለከ ኃይል
ክፍል 2:ምንባባት
ክፍል 3:ተአምረ ማርያም እና ተአምረ ኢየሱስ
ክፍል 4:ወንጌል
ክፍል 5:ጸልዩ በእንተ ጽንዐ ዛቲ
ክፍል 6:ኪርያላይሶን
ክፍል 7:ሰላምታ
የእያንዳንዱ የጸሎት ሰአት አጀማመር እንዲህ ነው:- ዲያቆኑ በሴቶች በር በኩል ቃጭል እያጮኅ ቤትክርስትያኑን ሶስት ጊዜ
ይዞራል
ድንግል ማርያምና ዮሐንስ እያነቡ የጌታን መስቀል የመዞራቸው ምሳሌ ነው።
ዞሮ ሲገባ መዝሙረ ዳዊትና ውዳሴ ማርያም
ይደገማል።በመቀጠልም
አንደኛ አቡን በዜማ ይደረስና ለክ ኃይል እየተባለ ይሰገዳል።በመቀጠልም
ሁለተኛ ምንባባት በተከታታይ ይነበባሉ
ሶስተኛ ተአምረማርያምና ተአምረ ኢየሱስ
በተከታታይ ይነበባሉ።
አራተኛ የሰአቱ ወንጌል ይነበባል
አምስተኛ ካህኑ ጸልዩ በእንተ ጽንዐ ዛቲ ሲሉ
እግዚኦ ተሳሃለነ እየተባለ ይሰገዳል
ስድስተኛ ኪርያላይሶን እየተባለ ይሰገዳል
ሰባተኛ የሰአቱ የሰላምታ(መልክአ ሕማማት) በዜማ ይቀርባል
በመጨረሻም ለሰአቱ የሚስማማ መዝሙር በሰንበት ት/ቤት ይዘመርና ካህኑ የሰአቱ
ጸሎት ተጠናቋል በሰላም ሂዱ ለሚቀጥለው የጸሎት ሰአት በሰላም ተመለሱ ይላሉ።
ትንሽ ቆይተው የሚቀጥለውን የጸሎት ሰአት
ያስጀምራሉ።እንዲህ እያለ ይቀጥላል።
ሰባቱን የጸሎት ክፍሎች ከዚህ በታች እናያለን።

/////////////////////////////////////////////////

ክፍል አንድ
ርዕስ:-አቡን እና ለከ ኃይል
ቅዱስ ያሬድ ለተለያዩ በዓላት አቡን የሰራላቸው ሲሆን ለሰሙነ ሕማማት የአቡን ዜማ ሰርቶለታል።

ከሰኞ እስከ ሀሙስ በአንድ ሰአቱም ይሁን በሶስት ሰአቱ በስድስት ሰአቱም ይሁን በሌላው የጸሎት ሰአት የሚነበበው ወንጌል
የሰአቱን አቡን ይወስነዋል። ይሄም ማለት የሚነበበው የማቴዋስ ወንጌል ከሆነ የማቴዎስ አቡን ይባላል።የሚነበበው
የማርቆስ ወንጌል ከሆነም የማርቆስ አቡን ይባላል።ለሉቃስ ወንጌል የሉቃስ አቡን፣ለዮሃንስም ወንጌል የዮሃንስ አቡን ይባላል።

አቡን
1::ከሰኞ እስከ ሀሙስ አቡን
ማስታወሻ:-ከሰኞ እስከ ሀሙስ ለከ ኃይል ከመባሉ በፊት የሚባለው አቡን ከእነዚህ ከአራቱ አንዱ ሲሆን።መሪ እና ተመሪ
ካህናት እየተፈራረቁ ያደርሱታል እንደጨረሱም ለከ ኃይልን ይጀምራሉ))

አቡን ዘማቴዎስ
በ፫ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌሉያ
ስምዕዎኬ ለእግዚእነ ኩልክሙ አብያተ ክርትያናት ከመ ዘአክበሮሙ ለኦሪት ወለነቢያት ፣በወንጌል መንግስት እንዘ ይብል
ክርስቶስ ወልደ ዳዊት አሜን አሜን እብለክሙ እስከ አመ የኅልፍ ሰማይ ወምድር የውጣ እንተ አሐቲ ኅርመታ ወአሐቲ ቅጽረታ
ኢትኅልፍ እምኦሪት ወእምነቢያት እስከ ሶበ ኩሉ ይትገበር ወይከውን ይቤ እግዚእ ዘበእብራይስጢ ልሳን በወንጌለ ማቴዎስ
ብርሃን ዘእምብርሃን።
አቡን ዘማርቆስ
በ፫ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌሉያ
ስምዕዎኬ ለእግዚእነ ኩልክሙ አብያተ ክርስትያናት ከመ ዘእክበሮሙ ለኦሪት ወለነቢያት፣በወንጌለ መንግስት እንዘ ይብል
ክርስቶስ ወልደ ዳዊት ኢይምሰልክሙ ዘመጻእኩ እሥዐሮሙ ለኦሪት ወለነቢያት፣ወኢ ከመ እንሥቶሙ አላ ዳእሙ ዘእንበለ ከመ
እፈጽሞሙ ይቤ እግዚእ በወንጌለ ሰላሙ ዐማኑኤል ስሙ ማርያም እሙ።
አቡን ዘሉቃስ
በ፫ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌሉያ
ይቤ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዘ ይሜህረነ በወንጌለ ሉቃስ ወባሕቱ ይቀልል ሰማይ ወምድር ይኅልፍ እምትደቅ አሐቲ ቃል
እምኦሪት።
አቡን ዘዮሐንስ
በ፫ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌሉያ
ስብሐት ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ በወንጌል ለዘመሀረነ በኦሪት ወበነቢያት ለዘናዘዘነ በከመ መሐረነ እግዚእነ ስብሐት
ለእግዚአብሔር ከመ ናምልኮ ለዘፈጠረነ።
#######################
2:: የእለተ አርብ አቡን
ለእለተ አርብ ግን አቡን የተሰራለት ለየጸሎት ሰአቱ
ነው ይሄም ማለት የነግህ አቡን፣የሶስት ሰአት አቡን የስድስት ሰአት አቡን፣የዘጠኝ ሰአት አቡን ፣የሰርክ አቡን ተብሎ ተዘጋጅቷል።
ማስታወሻ:-በእለተ አርብ በአንድ ሰአት በሶስት ሰአት በስድስት ሰአት በዘጠኝ ሰአት በአስራአንድ ሰአት ለከ ኃይል ከመባሉ በፊት
የሚባለው አቡን ከዚህ በታች ተቀምጧል።መሪ እና ተመሪ ካህናት እየተፈራረቁ ያደርሱታል እንደጨረሱም ለከ ኃይልን
ይጀምራሉ

የአርብ 1 ሰአት አቡን


ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ፣ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ፣ሃሌ ሃሌ ሃሌሉያ
ነአምን ነአምን ነአምን
ሕማሞ ለዘኢየሐምም
ርግዘተ ገቦሁ ነአምን
ወቅንዋተ እደዊሁ ነአምን
ዬ ዬ ዬ ነአምን ሞቶ ወትንሳኤሁ።

የአርብ 3 ሰአት አቡን


ሃሌሃሌ ሃሌሉያ፣ ሃሌሃሌ ሃሌሉያ፣ ሃሌሃሌ ሃሌሉያ
አርዑተ መስቀሉ ፆረ ።አርዑተ መስቀሉ ፃረ
ይስቅልዎ ሖረ ዬ ዬ ዬ ከመ ኪያነ ይቤዙ እግዚኦ
ኮነ ገብረ

የአርብ 6 ሰአት አቡን


ሃሌሃሌ ሃሌሉያ፣ሃሌሃሌ ሃሌሉያ፣ሃሌሃሌ ሃሌሉያ
ተሰቅለ ተሰቅለ ተሰቅለ ወሐመ ቤዛ ኩሉ ኮነ ዬ ዬ ዬ
በመስቀሉ ቤዘወነ እሞት ባልሐነ

የአርብ 9 ሰአት አቡን


ሃሌሃሌ ሃሌሉያ፣ሃሌ ሃሌ ሃሌሉያ፣ሃሌሃሌ ሃሌሉያ
ሶበ ሰቀልዎ ሶበ ሰቀልዎ ሶበ ሰቀልዎ ለእግዚእነ ፀሀይ ጸልመ ወወርኅ ደመ ኮነ ዬ ዬ ዬ አድለቅለቀት ምድር ወተከሥቱ መቃብራት

የአርብ 11 ሰአት አቡን


ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ፣ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ፣ሃሌ ሃሌ ሃሌሉያ
ንዜኑ ንዜኑ ንዜኑ፣ዘአምላክነ ኂሩተ
ትሕትና ወየውሃተ፣ዘእንበለ ዓቅም ዬ ዬ ዬ
እንዘ ይጼዕልዎ ኢጸዐሎሙ
ወእንዘ ያሓምምዎ ኢተቀየሞሙ
------------------------------------------------

ለከ ኃይል
ለከ ኃይል ለሰአቱ የተመረጠው አቡን ከተባለ በኋላ የሚባል የስግደት ስርአት ሲሆን አቡኑ ቢቀያየርም ለከ ኃይል ተመሳሳይ
ነው።ለጥናት እንዲመቸን ለከ ኃይልን በሶስት እንክፈለው

አንደኛ
ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም።
ዐማኑኤል አምላኪየ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም።
ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም።
ኃይልየ ወፀወንየ ውእቱ እግዚእየ።
እስመ ኮንከኒ ረዳእየ እብል በአኮቴት።

አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ።


ትምጻእ መንግስትከ ወይኩን ፈቃድከ ።
በከመ በሰማይ ከማሁ በምድር።
ሲሳየነ ዘለለ ዕለትነ ኀበነ ዮም።
ኅድግ ለነ አበሳነ ወጌጋየነ።
ከመ ንሕነኒ ንሕድግ ለዘአበሰ ለነ።
ኢታብአነ እግዚኦ ውስተ መንሱት።
አላ አድኅነነ ወባልኃነ።
እምኩሉ እኩይ እስመ ዚአከ።
ይእቲ መንግሥት።
ኃይል ወስብሐት ለዓለመ ዓለም።
(አስራ ሁለት ጊዜ )
*.
ሁለተኛ
ለከ ይደሉ ኃይል ወለከ ይደሉ ስብሐት ወለከ ይደሉ አኮቴት ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለመ ዓለም።
(አስራ ሁለት ጊዜ)
*.
ሶስተኛ
ለአምላክ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም።
ለሥሉስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም።
ለማኅየዊ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም።
ለዕበዩ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም።
ለእዘዙ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም።
ለመንግስቱ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም።
ለሕማሙ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም።
ለመስቀሉ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም።
(ለመስቀሉ የሚባለው አርብ ከስድስት ሰዐት በኋላ ብቻ ነው።)

የለከ ኃይል አደራረሱ እንዲህ ነው:-


ህዝቡ ከሁለት ተከፍሎ ከመሪ እና ከተመሪ ካህናት ጋር ሆኖ አየተቀባበሉ ይሰግዳሉ።
ክፍል አንድን መሪና ተመሪ አስራሁለት ጊዜ እየደጋገሙ ይሰግዳሉ በኋላ ወደ ክፍል ሁለት ይሄዳሉ ክፍል ሁለትንም አስራ ሁለት
ጊዜ እየተቀባበሉ በማድረስ ይሰግዳሉ።ሲጨርሱ ክፍል ሶስትን አንድ ጊዜ በማስተካከል እያዜሙ ይሰግዳሉ ሲጨርሱ አንድ ጊዜ
በማስተዛዘል እያዜሙ ይሰግዱና የሰአቱ የለከ ኃይል ፍጻሜ ይሆናል።

ማስተካከል እና ማስተዛዘልን ለማሳየት ያክል


ማስተካከል
መሪ ለአምላክ--ሲል ተመሪ ለአምላክ---ይላል
መሪ ለሥሉስ ሲል ተመሪ ለሥሉስ ይላል
መሪ ለማኅየዊ ሲል ተመሪ ለማኅየዊ ይላል
መሪ ለዕበዩ ሲል ተመሪ ለዕበዩ ይላል
መሪ ለእዘዙ ሲል ተመሪ ለእዘዙ ይላል
መሪ ለመንግስቱ ሲል ተመሪ ለመንግስቱ ይላል
መሪ ለሕማሙ ሲል ተመሪ ለሕማሙ. ይላል
መሪ ለመስቀሉ ሲል ተመሪ ለመስቀሉ ይላል

ማስተዛዘል
መሪ ለአምላክ--ሲል ተመሪ ለሥሉስ---ይላል
መሪ ለማኅየዊ ሲል ተመሪ ለዕበዩ ይላል
መሪ ለእዘዙ ሲል ተመሪ ለመንግስቱ ይላል
መሪ ለሕማሙ ሲል ተመሪ ለመስቀሉ ይላል

//////////////////////////////////////////////

ክፍል ሶስት
ተአምረ ኢየሱስ ወተአምረ ማርያም
በሰሙነ ሕማማት ተአምረ ማርያም እና ተአምረ አየሱስ በአንድ ቀን በትንሹ ሰባት ጊዜ ይነበባሉ።እናንተ በዚህ ሳምንት ወደ
ቤተክርስትያን በምትሄዱበት ጊዜ ተአምረ ማርያም እና ተአምረ ኢየሱስ ሲነበቡ ብትደርሱ በመንፈስ በእምነት ቆማችሁ
የምታዳምጡ ሁኑ።ሙሽራም ያለ አጃቢ ያለ ሚዜ እንደማይወጣ እነዚህ ተአምራት ከመነበባቸው በፊት እና ከተነበቡ በኋላ
የሚደረሱ ዜማወች አሉና እነሱን እናጥና

1:ከተአምረ ማርያም በፊት:-ምንተኑ


2:ከተአምረ ማርያም በኋላ:-ናዛዚትነ እምኅዘን
3:ከተአምረ ኢየሱስ በፊት:-ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ስም
4:ከተአምረ ኢየሱስ በኋላ:-አመ ትመጽእ

እነዚህን አራቱን በጹሁፍ እንዲሁም በድምጽ አስቀምጫለሁ።


@@@@@@@@@@@@@@

ተአምረ ማርያም ከመነበቡ በፊት


ምንተኑ አዐስየኪ ዕሴተ በእንተ ኹሉ ዘገበርኪ ሊተ
ማርያም ሠናይት ዘታፈቅሪ ምህረተ።
ሶበሰ ትትዓቀቢ ዘዚአየ ኃጢአተ ።
እምኢየሐዮኩ አሐተ ሰዓተ።
በሰላመ ቅዱስ ገብርኤል መልአክ ኦ እግዝእትየ ማርያም ሰላምለኪ ድንግል በኅሊናኪ ወድንግል በሥጋኪ እመ እግዚአብሔር
ጸባዖት ሰላምለኪ ቡርክት አንቲ እም አንስት ወቡሩክ ፍሬ ከርስኪ ተፈስሒ ፍሥሕት ኦ ምልእተ ጸጋ እግዚአብሔር ምስሌኪ።

ተአምረ ማርያም ከተነበበ በኋላ


ናዛዚትነ እምሃዘን ወኃይለ ወርዙትነ እምርስዐን።
በማህጸንኪ ተጸወረ ብሉየ መዋእል ህጻን።
ኦ ማርያም ተስፋ ለቅቡጻን።
በጊዜ ጸሎት ወእጣን ወበጊዜ ንጹህ ቁርባን።
ለናዝዞትነ ንኢ ኅበ ዝ መካን።
ሃሌሉያ በብዝሐ ሒሩትኪ ማርያም አድህነኒ በተአምርኪ ።
ወላዲተ አምላክ ማርያም እንበለ ሰብሳብ ወሩካቤ
በይነ ዘአቅረብኩ ለኪ ንስቲተ ቃለ ይባቤ።
ፈትቲ እሙ በረከተ አፉኪ መአዛ ከርቤ
ለነዳይ ብእሲ ወለዘረከቦ ምንዳቤ።
ኅብስተከ ፈትት ኢሳይያስ ይቤ።
ስብሐት ለኪ ማርያም በኁልቆ ኩሉ ስእርትየ
ስብሐት ለኪ ማርያም በኁልቆ ኩሉ አእጽምትየ
ስብሐት ለኪ ማርያም በኁልቆ ኩሉ ዘተርየ
ስብሐት ለኪ ንግስትየ በኁልቆ ኩሉ ዘኢያስተርአየ
ስብሐተ ድንግልናኪ ዘልፈ ይነግር አፉየ።

ተአምረ ኢየሱስ ከመነበቡ በፊት


ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ስም ለዘይጼውዖ።
ኢየሱስ ክርስቶስ ሕብስተ ህይወት ለዘይበልዖ።
ኢየሱስ ክርስቶስ ጽውዐ መድኃኒት ለዘይጸምዖ።
ከመ ይባርኩነ ይፈኑ አርዳኦ
ለጸባኢነ ይጽብኡ ዋልታሁ ነሢኦ
ኢየሱስ ክርስቶስ ዘአጽልልቲሁ ምስሌሁ
ወመስቀለ ሞቱ ቅድሜሁ
አዘቅተ ወይን ገቦሁ ቁርባነ አምልኮ ሥጋሁ
ያብአነ ቤተ መርዓሁ ውስተ ደብተራሁ
አመ ይትጋብዑ ለምሳሕ ሥርግዋን ሐራሁ
ለጥብሐ ሥጋከ ንሴስዮ ወለነቅአ ደምከ ንረውዮ
ኢየሱስ ክርስቶስ በግዕ ዘቀራንዮ
ለላዕከ እትሜነይ ከመ ንርአዮ
ውስተ ሶያሐ ሱራፊ ለሥዕለትየ ደዮ
ወበሕማመ ሞትከ አምላካዊ ለቁስልየ አጥዕዮ
ለጥብሐ ሥጋከ እጸግቦ
ወለነቅዐ ደምከ እሠርቦ
ኢየሱስ ክርስቶስ በግዕ ርጉዘ ገቦ
አይሁዳዊ ከሐዲ አሚነ ሥላሴ ዘአልቦ
ኢተወልደ እማርያም ዘይቤለከ እመቦ
አህጉራተ ዓለም ለይዑድ ከመ ከልብ ርኂቦ

ተአምረ ኢየሱስ ከተነበበ በኋላ


አመ ትመጽእ ለኮንኖ ምስለ ደመገቦ ወአእጋር አማህፀንኩ ነፍስየ ውስተ እዴከ ክቡር ።ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚኣ ሰማያት
ወምድር። ይትዋቀሱ በእንቲአየ ተኮርዖትከ በበትር። ወተሰይጦትከ ከመ ገብር ለኅዳጥ ብሩር።
ሃሌሉያ በብዝሀ ሳህልከ ኢየሱስ አድህነነ እም ተአጉሎ ስጋ ወነፍስ።
ስብሐት ለከ አምላኪየ በኁልቁሰ ወመላእክት
ስብሐት ለከ አምላኪየ በኁልቆ ጽዱላን ከዋክብት
ስብሐት ለከ አምላኪየ በኁልቆ ኩሎን አለማት
ስብሐት ለከ ንጉስየ በኁልቆ እለታት ወአዝማናት
ስብሐት ይደሉ ለመስቀልከ ህይወት እስመ በመስቀልከ ድህነ ኩሉ ፍጥረት።

//////////////////////////////////////////////

ክፍል አራት
ርዕስ:-ወንጌል
ቤተክርስትያናችን አራቱን ወንጌላት ለአመት አካፍላ በአንድ አመት ውስጥ ባሉ በያንዳንዱ ቀናት የሚነበቡ የወንጌል
ክፍሎችን ወስና ያስቀመጠች ሲሆን ለየክብረበዓሉ የሚገባውን ምንባብም በሊቃውንቶቿ አመቻችታ አዘጋጅታለች።
በአመት ውስጥ ላሉ ቀናት ወንጌል እንደተሰጣቸው እንዲሁ ደግሞ ለሁሉም ቀናት ከእያንዳንዱ ወንጌል
በፊት በዜማ የሚባል ምስባክም ሰርታለች።የአመቱን ወንጌልና ምስባክ የያዘው መጽሐፍ መጽሐፈ ግጻዌ ይባላል።
እናንተም በዚህ በሰሙነ ሕማማት በሁሉም የጸሎት ጊዜዎች የሚነበበውን ወንጌል እና ምስባኩን ማወቅ እንድትችሉ
ምእራፍና ቁጥሩን ለብቻ አስቀምጥላችኋለሁ።
ሌላው ወንጌል ከተነበበ በኋላ የምናደርሰው ዜማ ሲሆን ይሄም እንደ ወንጌላዊው ይለያያል።የማቴዎስ፣የማርቆስ፣የሉቃስ እና
የዮሃንስ ወንጌሎች ከተነበቡ በኋላ የሚባለውን እንይ

የማቴዎስ ወንጌል ከተነበበ በኋላ


ካህን፡ ሰማይ ወምድር የኀልፍ። ወቃልየሰ ኢየኀልፍ ይቤ እግዚእ ለአርዳኢሁ።
ሕዝቡ፡ ነአምን አበ ዘበአማን፡ ወነአምን ወልደ ዘበአማን፡ ወነአምን መንፈሰ ሥላሴሆሙ ነአምን። ቅዱሰ
ዘበአማን፡ ህልወ

የማርቆስ ወንጌል ከተነበበ በኋላ


ካህን፡ ዘቦ እዝን ሰሚዐ ለይሰማዕ።
ሕዝብ፡እሉ ኪሩቤል ወሱራፌል ያዐርጉ ሎቱ ስብሕተ እንዘ ይብሉ፡ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ አንተ እግዚአብሔር
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ።

የሉቃስ ወንጌል ከተነበበ በኋላ


ካህን፡ይቀልል ኅልፈተ ሰማይ ወምድር እምትደቅ አሐቲ ቃል እምኦሪት ወእምነቢያት።
ህዝቡ: መኑ ይመስለከ እምነ አማልክት እግዚኦ አንተ ውእቱ ዘትገብር መንክረ አርአይኮሙ ለሕዝብከ
ኃይለከ ወኣድኃንኮሙ ለሕዝብከ በመዝራዕትከ ሖርከ ውስተ ሲኦል ወኣዕረገ ፄዋ እምህየ ወጸጎከነ ምዕረ
ዳግመ ግዕዛነ እስመ መጻእከ ወአድኀንከነ። በእንተ ዝንቱ ንሴብሐከ ወንጸርሕ ኀቤከ እንዘ ንብል፡ ቡሩክ
አንተ እግዚኦ ኢየሱስ ክርስቶስ እስመ መጻእከ ወአድኃንከነ።

የዮሃንስ ወንጌል ከተነበበ በኋላ


ካህን፡ዘየአምን በወልድ ቦ ሕይወት ዘለዓለም።
ህዝብ: ቀዳሚሁ ቃል ውእቱ ቃል ቃለ እግዚአብሔር፡ ውእቱ ቃል ሥጋ ኮነ ወኀደረ ላዕሌነ፡ ወርኢነ
ስብሐቲሁ ከመ ስብሐተ ፡፩ዱ (አሐዱ) ዋሕድ ለአቡሁ፡ ቃለ አብ ሕያው ወቃል ማሕየዊ ቃለ
እግዚአብሔር ተንሥአ ወሥጋሁኒ ኢማሰነ።
ከሰኞ እስከ ሀሙስ ከወንጌል በፊት ያሉ ምስባኮችን መያዝ እና ከወንጌል በኋላ የሚባሉ እነዚህን ዜማወች
ማጥናት በቂ ሲሆን ለእለተ አርብ ግን ከወንጌል በፊት የምናደርሳቻውን ምስባኮች እንዲሁም ከወንጌል
በኋላ የሚባሉ ዜማወች ልዩ ስለሆኑ ለብቻ እናያቸዋለን

//////////////////////////////////////////////

ክፍል አምስት
ርዕስ:-ኪርያላይሶን
ይህ የስግደት ስርአት ሲሆን ህዝቡ በመሪና በተመሪ ሆኖ እየተቀባበለ በማዜም የስግደት ስርአት የሚፈጸምበት የልመና ጸሎት
ስርአት ነው ።በዚህ የጸሎት ስርአት ውስጥ ስላሉ በአማርኛና በግእዝ ስለማናውቃቸው ቃላት ለመግለጽ ያክል:-
በግብረ ሕማማት መጽሐፍ ውስጥ ከዕብራይስጥ፣ ከቅብጥ እና ከግሪክ ቃላት የመጡና ወደ ሀገራችን ቋንቋ ሳይተረጎሙ ፣እንዳሉ
ለአገልግሎት የዋሉ ቃላት ይገኛሉ ፡፡ የእነዚህ ቃላት ትርጉም የሚከተለው ነው፡፡
1:-ኪርያላይሶን ከግሪክ የመጣ «ኪርዬ ኤሌይሶን»
«ኪርያ» ማለት «እግዝእትነ» ማለት ሲሆን «ኪርዬ» ማለት ደግሞ «እግዚኦ» ማለት ነው፡፡ «ኪርያላይሶን» ማለት «አቤቱ
ማረን»ማለት ነው።
2:-ናይናን ከቅብጥ የመጣ
ትርጉሙ «መሐረነ፣ ማረን» ማለት ነው፡፡
3:-እብኖዲ ከቅብጥ የመጣ
ትርጉሙ «አምላክ» ማለት ነው፡፡
«እብኖዲ ናይናን»ማለት «አምላክ ሆይ ማረን»
4:-ታኦስ ከግሪክ የመጣ
ትርጉሙ «ጌታ፣ አምላክ» ማለት ነው፡፡
«ታኦስ ናይናን» ማለት «ጌታ ሆይ ማረን»
5:-ማስያስ ከዕብራይስጥ የመጣ
ትርጉሙ «መሲሕ» ማለት ነው፡፡
«ማስያስ ናይናን»ማለት «መሲሕ ሆይ ማረን»
6:-ትስቡጣ «ዴስፓታ» ከግሪክ የመጣ
ትርጉሙ «ደግ ገዥ» ማለት ነው
ትስቡጣ ናይናን ማለት ደጉ ገዥ ሆይ ማረን።

ወደ ኪርያላይሶን ስናመራ :-መሪው ኦ ክርስቶስ አምላከነ ብሎ ከጀመረ በኋላ ኪርያላይሶን ብሎ ይቀጥላል።


ክርስቶስ አምላክነ፤ ዘመጽአ ወሐመ በእንቲአነ በሕማማቲሁ ቤዝወነ፤ ንሰብሖ ወናልዕል ስሞ ኅቡረ፤ እስመ
ውእቱ ገብረ መድኃኒተ በዕበየ ሣህሉ"
(በዐርብ ዘሐመ ወሞተበእንቲአነ ይባላል፡፡)

ቀጥሎም መሪ እና ተመሪው(ሕዝቡ) በሁለት ክፍል ሆነው የሚከተለውን ጸሎት ሁለት ጊዜ


-አንድ ጊዜ በማስተካከል ከዚያም ሲጨርሱ በማስተዛዘል ይሉታል
1:ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤
2:ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤አብኖዲ ናይን፣ ኪርያላይሶን፣
3:ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ታዖስ ናይን ፣ ኪርያላይሶን፤
4:ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ ማስያስ ናይን፣ ኪርያላይሶን፤
5:ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ ኢየሱስ ናይን፣ ኪርያላይሶን፤
6:ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ ክርስቶስ ናይን፣ ኪርያላይሶን፤
7:ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ አማኑኤል ናይን፣ኪርያላይሶን፤
8:ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ ትስቡጣ ናይን፣ ኪርያላይሶን፤

በማስተካከል ማለት መሪው የሚለውን መድገም ነው ።


መሪው አንደኛውን ሲል ተመሪው አንደኛውን
መሪው ሁለተኛውን ሲል ተመሪው ሁለተኛውን
መሪው ሶስተኛውን ሲል ተመሪው ሶስተኛውን
እንዲህ እያሉ እስከ ተራ ቁጥር ስምንት እየተከታተሉ ይሉታል።እያከታተሉ ካደረሱ በኋላ እንደገና በማስተዛዘል አንድ ጊዜ
ያደርሱታል።

ማስተዛዘል ማለት ደግሞ


መሪው አንደኛውን ሲል ተመሪው ሁለተኛውን
መሪው ሶስተኛውን ሲል ተመሪው አራተኛውን
መሪው አምስተኛውንሲል ተመሪው ስድስተኛውን
መሪው ሰባተኛውን ሲል ተመሪው ስምንተኛውን

ከዚህ በኋላ መሪው20 ጊዜ ተመሪው 21ጊዜ በአጠቃላይ 41 ጊዜ በጋራ ኪርያላይሶን እያልን እንሰግዳለን።

////////////////////////////////////////////// ክፍል ስድስት


ርዕስ:-በእንተ ጽንዐ ዛቲ
ይህ ጸሎት በካህኑና በህዝቡ መካከል የሚደረስ ሲሆን ካህኑ አንዷን ምእራፍ አንብቦ ሲጨርስ ህዝቡ እግዚኦ ተሣሃለነ ወይም
አቤቱ ይቅር በለን እያለ ይሰግዳል።

ይካ. ስለዚች ቦታ መጽናት በቅዱሳን አባቶቻችን ስም ስለሚጠሩም ቦታዎችና ገዳሞች በውስጣቸውም ስለመኖሩ ሽማግሎች
በጠቅላላም ስለዚህ አለም መጠበቅ ጸልዩ። ጌታ ከክፉ ሁሉ ይጠብቃቸው ዘንድ። የኛንም ኀጢአታችንን ያስተሰርይልን።
ይሕ. እግዚኦ ተሣሃለነ።

ይካ. በዚች ቦታና በሌሎች ቦታዎች ስለሚገኙ በነፍስ በስጋ ስለታመሙ አባቶቻችንና ወንድሞቻችን ጸልዩ። ጌታ ለኛም ለነርሱም
ሕይወቱን ጤንነቱን ሰጥቶ በጎ ነገርን ያደርግ ዘንድ ። የኛንም ኃጢአታችንን ያስተሰርይልን።
ይሕ. እግዚኦ ተሣሃለነ።

ይካ. በባሕር በየብስ በወንዝ በቀላይ በሌላውም መንገድ ሁሉ ስለሚጓዙ አባቶቻችንንና ወንድሞቻችን ጸልዩ። ጌታ በቀና
መንገድ መርቶ በሰላም በደስታ ወደ መኖሪያቸው ይመልሳቸው ዘንድ። የኛንም ኃጢአታችንን ያስተሰርይልን።
ይሕ. እግዚኦ ተሣሃለነ።

ይካ. ከእርሻ ስለሚገኝ ፍሬ ስለ ዛፎችና ስለ ወይኖች በአለምም ውስጥ ፍሬወን ስለምታፈራ ዕንጨት ሁሉ ጸልዩ። ጌታ ባርኮ
አብዝቶ ከጥፍትም ጠብቆ ለፍጻሜ ያደርሳቸው ዘንድ። የኛንም ኃጢአታችንን ያስተሰርይልን።
ይሕ. እግዚኦ ተሣሃለነ።

ይካ. የክርስትያን እምነት ላልተፈፀመላቸው ወገኖቻችን ጸልዩ። ጌታ ይባርካቸው ዘንድ እስከ መጨረሻይቱም ሕቅታ በቀናች
ሃይማኖት ያጸናቸው ዘንድ። የኛንም ኃጢአታችንን ያስተሥርይልን።
ይሕ. እግዚኦ ተሣሃለነ።

ይካ. ሐዋርያት ስላጸኗትና ስለሰበሰቧት ስለ አንዲት ቤተ ክርስትያን ሰላም ጸልዩ። ስለ ሕዝቡም ሁሉ መዳንን ስለ ቦታው ሁሉ
መጠበቅ። የኛንም ኃጢአታችንን ያስተሥርይልን።
ይሕ. እግዚኦ ተሣሃለነ።

ይካ. ሊቀ ጳጳሳቱ አባታችን አቡነ ማትያስና ብፁዕ አባታችን አቡነ ሔኖክ በሕይወት በሞት በኑሮም ስለሚደርስባቸው ሁሉ
ጸልዩ። ሕይወታቸውን ጠብቆ ለብዙ ዘመን በመንበረ ስብከታቸው ያፀናቸው ዘንድ። የኛንም ኃጢአታችንን ያስተሥርይልን።
ይሕ. እግዚኦ ተሣሃለነ ።

ይካ. ምዕመናንን በየስፍራቸው ሁሉ በቸርነት ስለሚያስቡና ለበጎ ነገር ስለሚደክሙ የቀና ሃይማኖት ስላላቸው ሰዎች ሁሉ
ጸልዩ። ጌታ ባርኮ ዋጋቸውን እንዲሰጣቸውና ይቅርታን እንዲያደርግላቸው ። የኛንም ኃጢአታችንን ያስተሥርይልን።
ይሕ. እግዚኦ ተሣሃለነ ።

ይካ. ለቁርባን የሚሆን ስንዴውን ዕጣኑን ዘቢቡን የሚነበብባቸው መፃሕፍትን ሌላውንም የቤተ መቅደስ ዕቃ ሁሉ በመስጠት
ስለሚያስቡ ሰዎች ጸልዩ። ጌታ በመንግስተ ሰማያት የበለጠ ዋጋ ይሰጣቸው ዘንድ። የኛንም ኃጢአታችንን ያስተሥርይልን።
ይሕ. እግዚኦ ተሣሃለነ።

ይካ. በደዌ ሥጋ በደዌ ነፍስ ለደከሙና ለተቸገሩ ለባልቴቲቱም አባት እናት ለሌላቸው ለድኆቹ ልጆችና ለተጨነቀችም ሰውነት
በማናቸውም ቦታ ሁሉ ጸልዩ። ጌታ ራርቶ ይቅር እንዲላቸው። የኛንም ኃጢአታችንን ያስተሥርይልን።
ይሕ. እግዚኦ ተሣሃለነ
ይካ. በግዞት በምርኮኝነት ተይዘው ለተጨነቁ አገር ለቀው ለተሰደዱ በአጋንንት አሽክላም ለተያዙ ሰዎች ጸልዩ። ጌታ ከግዞት
ከምርኮኝነት ያወጣቸው ዘንድ፤ ይቅርታውንም ሰጥቶ እነርሱንም እኛንም ያድነን ዘንድ ኃጢአታችንንም ያስተሥርይልን።
ይሕ. እግዚኦ ተሣሃለነ

ይካ.ለነፍሳቸው ይቅርታን እየፈለጉ ክቡር በሆነ በዚህ ስፍራ ስለተሰበሰቡት ሁሉ ጸልዩ። የአምላካችን የጌታችን ይቅርታ ፈጥኖ
ይደረግላቸው ዘንድ ። የኛንም ኃጢአታችንን ያስተሥርይልን።
ይሕ. እግዚኦ ተሣሃለነ ።

ይካ. በዚህ አመት ስለዝናም መዝነም ስለባህርና ስለወንዞችም መምላት ጸልዩ ። እውነተኛ አምላካችን ክርስቶስ በረከቱን ሰጥቶ
እስከ ልካቸው እንዲመላቸው ለምድርም ልምላሜዋን ሰጥቶ ደስ እንዲያሰኛት ሥጋዊን ሁሉ በረድኤት እንዲያፀና ለእንስሳትም
ሁሉ ድኅነትን እንዲሰጥ ጸልዩ። የኛንም ኃጢአታችንን ያስተሥርይልን።
ይሕ. እግዚኦ ተሣሃለነ።

ይካ. በጸሎታችን እናስባቸው ዘንድ አስቡን አትርሱን ስላሉን ሰዎች ጸልዩ። እግዚአብሔር በበጎ ያስባቸው ዘንድ በየጊዜውም
ይቅር ይላቸው ዘንድ። የኛንም ኃጢአታችንን ያስተሥርይልን።
ይሕ. እግዚኦ ተሣሃለነ ።

ይካ. ይህችን ሳምንት ጌታ በበጎ ይፈጽማት ዘንድ ከኛም የጠላትን መፈታተን አርቆ ሰውነታችንን እንዲያድን ይቅር እንዲለን
ጸልዩ። ኃጢአታችንን ያስተሥርይልን።
ይሕ. እግዚኦ ተሣሃለነ።

ይካ. ጌታችን አምላካችን ራርቶ ይቅር እንዲለን ልመናችንንም ተቀብሎ ለዚያ ለፋሲካው እንዲያበቃን የትንሣኤውንም ብርሃን
በፍፁም ደስታ እንዲያሳየን ጸልዩ ኃጢአታችንን ያስተስርይልን።
ይሕ. እግዚኦ ተሣሃለነ ።

////////////////////////////////////////////// ክፍል ሰባት


ርእስ:-ሰላምታ
ሰላምታ ወይም መልክአ ሕማማት የአባታችን
የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ድርሰት ሲሆን እነ ዋልድባን
በመሰሉ ገዳማት ከአመት አመት የሚጸለይ ልዩ ዜማ ሲሆን በስርአተ ቤተክርስትያን ደግሞ በሕማማት ሳምንት በየጸሎት
ሰአቱ የሚደርስ ስለሆነ ለየጸሎት ሰአቱ ከተዘጋጀው ቢያንስ
ሰላምታ ዘነግህ
ሰላምታ ዘሰለስት
ሰላምታ ዘቀትር እና
ሰላምታ ዘሰርክን ከዚህ በታች አስቀምጥላችኋለሁ
====ሰላምታ ዘነግህ==
ክርስቶስ፡ ክርስቶስ፡ ክርስቶስ፡ አንተ፡ወልዱ፡ ለቡሩክ፡ ወልደ እግዚአብሔር፡ተሣሃለነ።
ጋዳ፡ ጋዳ፡ ጋዳ፡ ለአብ፡ ወወልድ፡ወመንፈስ፡ ቅድስ፡ ቅዱስ፡ ቅዱስ፡ ቅዱስ፡አንተ፡ ወልዳ፡ ለማርያም፡ ከሣቴ፡ ብርሃን ፡
ተሣሃለነ።
ቅዱስ፡ አንተ፡ እግዚአብሔር፡ አቡሁ ፡ለእግዚእነ፡ ወመድኃኒነ፡ ኢየሱስ ፡ክርስቶስ፡ ዘዉእቱ፡ ባሕቲቱ።
በአማን፡ ወልድከ፡ ወእቱ፡ ዘበጽድቅ፡አቡሁ፡ አንተ፡ መሐረነ፡ ወተሣሃለነ ፡እግዚኦ፡ ንሕነ፡ ኀቤከ፡ ተማሕፀነ፡ እግዚኦ ፡
መሐረነ፡ ክርስቶስ።
ሰላም ፡ለኪ፡ ማርያም፡ አንቀጸ፡ መድኃኒት፡ ገነተ፡ ትፍሥሕት፡ እመ፡እግዚአብሔር፡ ፀባዖት፡ ዘምስለ፡ ሰጊድ፡ ንኤምኀኪ።
ለባርኮትነ ፡ስፍሒ፡ እዴኪ፡ ጸሎተነ፡
ወስእለተነ፡ ማርያም ። ባርኪ፡ ወኪያነኒ፡ እሞተ ፡ሙስና፡ መሐኪ፡ ፀዳለ፡ ወልድኪ ፡ በዲቤነ፡ ያዋኪ፡ ጸልዪ፡ ወስተ፡
ማኀበርነ ፡ኢይባእ፡ ሐዋኪ።
ሰላም፡ለኪ፡ቤተ፡ ክርስቲያን፡ እምየ፡ ዘትፄንዊ: መጽርየ። ብኪ ጸናእኩ፡ እምከርሠ፡ እምየ። ቤተ፡ክርስቲያን ፡አክሊለ፡ ርእሰየ።
ሰላም ለኪ።
ቤተ፡ ክርስቲያን ፡ብሂል፡ ነፍሰ፡ ክርስቲያን፡ብሂል። እንተ፡ ቀደሰኪ፡ ደመ፡ወልድ፡ጥሉል። ቤተ፡ክርስቲያን፡ ማህደረ፡ ልዑል።
ሰላም ለኪ።መሠረትኪ ፡ሳውል፡ ወመምህርኪ ፡ኬፋ። ወአናቅጽኪ፡ አርድእቱ ለአልፋ። ቤተ፡ክርስቲያን፡ ጸጋዊተ፡ ተሰፋ።
ሰላም ለኪ።
አሕዛብ፡ ወሕዝብ፡ ይሰግዱ፡ ለኪ። ወይትመሐለሉ በቅድመ ገጽኪ። ቤተ ክርስቲያን ማኀደረ መላኪ። ሰላም ለኪ።
በሐኪ በሐኪ ቤተ ክርስቲያን እምነ። ግበሪ ጸሎተነ በእንቲአነ። እምኀይለ ጸላዒ ወፀር ዕቀቢ ኪያነ። ትንባሌኪ የሃሎ
ምስሌነ።
ሰላም ለኪ ማርያም ድንግል ዘመአዛ አፉኪ ኮል። እንተ ትጼንዊ በገዳም ወሐቅል። ወልታ ረዲኦትየ በውስተ ቀትል ። ሰላም
ለኪ።
ተሰፍዎተ ባዕድ አልብየ ዘእንበሌኪ ምክህየ። በኢመንኖ በልኒ ገብርየ ገብርየ። ዘተሣየጥኩከ በንዋይየ። ሰላም ለኪ።
አትሮንሰ ሰሎሞን አንቲ ለሐና ባሕርያ። ንግስታት ፷ ዕቁባት ፹ያ። ወደሳኪ እንዘ ይገንያ ሰላም ለኪ።
አመ ይከውን ድኅረ እለተ በቀል ወፍዳ። ወአመ ኢትድኅን እም ዘወለደት ወልዳ። ባላሒት እሞተ ዕዳ ። ሰላም ለኪ።
በከመ ልማድኪ በሊ ኀበ ወልድኪ ከሀሊ። ኦርኅሩኅ ኢተበቃሊ። ያጥፍኦኑ ለስእሉ ሰአሊ። ኪነተኪ ዘትካት ሐሊ።
ስብሐት ለከ ከመ ንንግር ኩሎ ስብሐቲከ በአናቅጺሃ ለጽዮን ማኅደረ ብዙኅ ሰላም። ዘአንቃ ህከነ እምነ ንዋም። ኢየሱስ
ወልደ ማርያም ስብሐት ለከ ።
ላዕለ ጻድቃን ወኃጥአን ብርሃነ ፀጋ ምውቅ። ዘታሰርቅ ለነ እምነ ምስራቅ። ኢየሱስ ፀሐየ ጽድቅ። ስብሐት ለከ ።
ለዘመጠነዝ ገብርከ ለዕሌሆሙ ፍድፍድና ጸጋ ወሀብት። ፈደዩከ እፎ እኪተ ህየንተ ሠናይት። ኢየሱስ ንጉሠ ስብሐት።
ስብሐት ለከ ። ኢየሱስ ሕሙይ በእንቲአነ ኢየሱስ ሙቁሕ። እንተ አየሙከ ውስተ ዓውደ ፍትሕ። ጊዜ ኮነ ጐሐ ጽባሕ።
ስብሐት ለከ ።
ከመ የዋህ በግዕ ወከመ ላሕም መግዝዕ። መስዋእተ መድሐኒት ትኩን ለቤዝዎ ሰብእ። ዘኀለ ፍከ ዓፀደ ግፍዕ። ስብሐት ለከ

እምልብነ አግህስ እግዚኦ ነገረ ፀላዒ መስሕት ዘአግሐስከ ለነ ጽልመተ ሌሊት። ኢየሱስ ብርሃነ ሕይወት። ስብሐት ለከ ።
አኮቴተ ስብሐት ወትረ ለመንግስትከ ስቡሕ። እምንዋምነ ንነቅህ። ዘናቄርብ ለከ በቃለ ክላህ። ወንፌኑ ስብሐት ዘነግህ።
ግናይ ለክሙ ሥሉስ ቅደስ ማእምራነ ፪ኤ አእምሮ። ለብርሃን በነግህ ዘፈጠሮ። ቃልክሙ በተናግሮ። ግናይ ለክሙ።
እምነ ብርሃን ብርሃነ መጠነ አሐቲ ሥርናይ። እለ አልበስክሙ ነገሥተ ሰማይ። ለወርኅ ወለፀሐይ። ግናይ ለክሙ።
ሰዓት ሌሊት ሥላሴ ዘወሰንክሙ በጐህ። ወዘአክበርክሙ በፀዳል ብሩህ። ፀሐየ እምነ ወርኅ።ግናይ ለክሙ።
ኀበ ርኅራኄክሙ በዝኃ ወኀበ አልቦቱ መሥፈርት። እለ ትሰመዩ በስመ ብእሲት። ሥላሴ ዕደወ ምሕረት። ግናይ ለክሙ።
ከመ ኅብረ ለይ ሥጋየ እመ ኃጢአትየ ቄሐ ። ኀዘን ብየ አምጣነ በዝኃ። ሥላሴ ዘዮም ወዘአሜሃ። በጽባሕ ሀቡኒ ፍሥሓ።
ስብሐት ለእግዚአብሔር በል። ጸሎተ ሃይማኖት። አቡነ ዘበሰማያት በል።

====ሰላምታ ዘሠለስት====
ክርስቶስ ክርስቶስ ክርስቶስ አ ወ ለ ወ እ ተ ጋዳ ጋዳ ጋዳ ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ።
ቅ ቅ ቅ አንተ ወልዳ ለማርያም ከሣቴ ብርሃን ተሣሃለነ።
ሰላም ለኪ ማርያም ርግብ ሰማያዊት ሰላም ለኪ።
ወንስር መንፈሳዊት ሰላም ለኪ።
ሥምረተ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ መላኪ ሰላም ለኪ፡፡
እምትካት ዘኃረየኪ ሰላም ለኪ፡፡
ጊዜ ጸልዮትኪ በጽሐ ከመኢይሙት ገብርኪ።
ቅድሜሁ ስግዲ ወአስተብርኪ። እንዘ ታዘክሪዮ ፃማ ንግደትኪ። ርግብየ የዋሂት ለየዋህ ወልድኪ።
ስብሐት ለከ እዔምኅ አእጋሪከ በጊዜ ሰለስቱ ሰዓት ቅድመ ጲላጦስ ዘቆማ። ኢየሱስ ጠቢብ ወንጉሠ ፌማ። ዘአድክምከ
ኅይለ መስቴማ። ስብሐት ለከ። እንዘ ይሰልቡ ልብሰከ ወክዳነከ ፀዓዳ። እንተ አልበሱከ ከለሜዳ። ኢየሱስ ንጉሠ ይሁዳ።
ስብሐት ለከ።
ተፈፀመ ብከ እግዚኦ ቃለ ዳዊት ንጉሥ። ሶበ ተካፈሉ በእፃ ወፋስ። ልብስከ ልብሰ ሞገስ። ስብሐት ለከ።
ማህበራነ አይሁድ አሜሃ አዕጽምቲከ ኈለቁ። ወዲበ ገጽከ ምራቀ ወረቁ። ላእሌከ እንዘ ይሣለቁ። ስብሐት ለከ ።
እፎ መጦከ ዘባነከ ለጥብጣቤ መቅሠፍት መፅዕቅ። ገጽከኒ ተውክፈ ሐፍረተ ምራቅ። ዘአዕሩግ ወዘደቂቅ። ስብሐት ለከ።
አዕርግ ለነ እግዚኦ በጊዜ ፫ ሰዓት። ዘአቅረብነ ለከ መሥዋዕተ ስብሐት። ከመ ሠርዑ ሐዋርያት። ስብሐት ለከ።
ኀበ ሐዋርያት ኅብሩ በጽርሐ ጽዮን አንግልጋ። ዘፈኖከ ሎሙ መንፈሰ ጸጋ። ፈኑ ለነ እንበለ ንትጋ ያኀድገነ ምግባረ ዘሥጋ።
ሥሉስ ቅዱስ ጠበብት ፫ ሰዓት። አዳምሃ በሳድስ ዕለት። ዘፈጠርክሙ እንበለ ሞት። ግናይ ለክሙ።
ድኅረ ተፈጥሮቱ ለሰብእ በኈልቈ ዕለታት 40ዓ። እለ ታብእሉ ወታነድዩ ሰብአ። መጽሐፍ ከመ አይድዓ ግናይ ለክሙ።
ለሐዋርያት ሥላሴ በጊዜ ሰዓት ፫ቱ በልሳን 72 ሥላሴክሙ ዘትከሥቱ ግናይ ለክሙ።
ለጻላኤ ብርሃን ሰብአ ከመ ዘእኩይ ምግባር እለ ትኔጸሩ ወተአምሩ። ሥላሴ ዘትምሕሩ። ግናይ ለክሙ።
ድኅረ ስብኮ ላህም ዓቀመ በደብረ ኰሬብ መካን። ካህን አሮን ወምእመን። ዘመሐርክምዎ ለአሮን ካህን። መሐሩኒ ሥላሴ
ኄራን ግናይ ለክሙ።
ስብሐት ለእግዚአብሔር በል ወጸሎተ ሃይ በል።

====ሰላምታ ዘቀትር=====
ሰላም ለኪ ማርያም ቡርክት በአፈ ኩሉ ፍጥረት። ታቦት አንቲ ዘሙሴ ጽላት። ዘሕግ ወዘ ሥርዓት። ሰላም ለኪ።
ገይበ ብሩር ጽሪት ወመቅድሐ ጽሩይ ኅሊብ። ማርያም መሶብ ዘመና ልሁብ። እንተ ፆርኪ ሲሳየ ሕዝብ። ሰላም ለኪ።
ትርሢተ ቤቱ ሠናይ ለነቢይ ሐጌ። ወወለት አንቲ ዘሰሎሞን ሐርጌ። ማርያም ዘመነ ጽጌ። ሰላም ለኪ።
እመ ቅድዉ በግዕ ዘቀተልዎ በግፍዕ። ወደብተራ ስምዕ ዘጳውሎስ ረድዕ። ማርያም ዘመነ ፍግዕ። ሰላም ለኪ።
ኦርያሬስ ሰማይ ልብስኪ ወአሳዕንኪ ዕብላ። ጽጌ ደንጐላት ቀይህ ዘምድረ ቈላ። ማርያም ዘመነ ተድላ። ሰላም ለኪ።
በመድበለ ማኅበር ጽፉቅ እዌድሰኪ በጻህቅ። ከመ ትምዓድኒ ነገራተ ጽድቅ። ማርያም ዘመነ እርቅ። ሰላም ለኪ።
ተደንግሎ ሥጋ ወነፍስ ለባሕቲትኪ ኮነ። እመኒ በጐል ወልድኪ ሕፃነ። ኢረስሐ ወኢማሰነ። ሰላም ለኪ።
እሙ በሊዮ በእንቲአየ ለፍሬ ከርሥኪ እምኖዲ። ላዕሌሁ ምሕረተ ኢታጐንዲ። እመ አኅዘንኪ ብእሲ አባዲ። ቤዛ ነፍሱ
ንጽሕየ እፈዲ።
ስብሐት ለከ ኦዘተፈኖከ ኢየሱስ ጻድቅ ማዕከለ ፪ኤ ፈያት። እንዘ ኢትከውን አንተ ገባሬ እኪት። ከመ ትሥዓር ቀኖተ ሞት።
ስብሐት ለከ
እፎ ሰፋሕከ አዕዳዊከ ወተሰቀልከ በዕጸ። ዕፁተ ቀላያት ታርኁ አምሳለ አንቀጽ። ዘሰፋሕከ በብሔረ ግብፅ። ስብሐት ለከ
ፀሐይ ብሩህ አሜሃ ጊዜ ቀትር ፀልመ። ወወርኅኒ ጽዱል ተመሰለ ደመ። ትንቢት ከመ ቀደመ። ስብሐት ለከ
ለአብርሃም አብ ቀዳሚ ዘአስተርአይኮ ክርስቶስ። ቀትረ ታሕተ ዕፀ ድርስ። ተሰቀልከ ከመ ዐቡስ። ስብሐት ለከ
ኀዘነ ማርያም እምከ ነጺረከ ለዘታፈቅሮ ሐዋርያ። ትቤሎ እምከ ነያ። ከመ ትናዝዝ ብዝኃ ብካያ። ስብሐት ለከ
ዘሰአልከ ማየ እምነ ሣምራዊት ብእሲት። ከመ ትፈጽም ኩሎ ነገረ ትስብእት። እንዘ አንተ ማየ ሕይወት። ስብሐት ለከ
ሕጽረነ ወትረ እግዚኦ ለደቂቀ ዛቲ ማኅበር። በመስቀልከ መግረሬ ፀር። እምድድቅ ወእምጋኔነ። ቀትር። ወእምኩሉ ዘይመጽእ
ግብር።
ግናይ ለክሙ ሥሉስ ቅዱስ ዕሩያነ አካል ወገጽ። ዘአስተራአይክሙ እንበለ ሕፀፅ። ጊዜ ቀትር በታህተ ዕፅ ግናይ ለክሙ።
ለንግስክሙ ሰገደ አብርሃም በርእሱ። ቤተ ገብርክሙ እንዘ ትገይሡ። አጋእዝት ዘትሤለሱ። ግናይ ለክሙ።
በላእለ ማርያም ድንግል ሥላሴክሙ ተረክበ። በዮርዳኖስ ቅድመ ወበታቦር ካዕበ። ወንጌል ከመ ነበበ። ግናይ ለክሙ።
ለቤተ ክርስቲያን ሥላሴ አናቅጺሃ አንትሙ። ሱራፌልኒ በቅዳሴሆሙ። ይኤምሩ ግፃዌክሙ። ግናይ ለክሙ።
ፈጣርያነ ፀሐይ ወወርኀ አጋእዝትየ ሥላሴ። ዘነፀሩክሙ ኤልያስ ወሙሴ። በክብር ወበውዳሴ። ግናይ ለክሙ።
ጠፈረ ቤትክሙ ማይ ዘኀብሩ በረድ። የአኮቱክሙ ኀሩያን አንጋድ። በስኢል ወበሰጊድ። ግናይ ለክሙ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እንዘ ፩ዱ ፫ቱ ። ዘተአንገድክሙ ኀበ ሐይመቱ። ለአብርሃም ጊዜ ዕብሬቱ። ግናይ ለክሙ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እምኔክሙ ፩ዱ። እንበለ ሩካቤ ወዘርእ እምድንግል ማኀፈዱ። ዘተወልደ በፈቃዱ። ግናይ
ለክሙ።
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ለዝክርክሙ ሕይወት። ሶበ ከናፍርየ እከሥት። ስመ ዚአክሙ በኩሉ ሰዓት። ይስማዕ
እምአፉየ ወይደንግፅ ሞት።

====ሰላምታ ፱ቱ ሰአት====
ሰላም ለኪ ማርያም እክል መጽንዒት ኃይል ቅቡዓ ብርሃኑ ለገጽ ሰላም ለኪ። ስቴ ወይን ዘነፈርዓዕ ሠርጐ ክብር ወአራዝ
ሰላም ለኪ።
ወመቅደስ ቤተ ትእዛዝ ለአሣዕንኪ ወርኅ ሰላም ለኪ።
ወለአክሊልኪ ጐሐ ጽባህ ሰላም ለኪ።
ደመና ዝናም ንጽሕት ሰላም ለኪ።
ዘይከውን ለቅድሳት ሰላም ለኪ።
ደብረ መድሃኒቱ ለኖህ ሰላም ለኪ።
ዘአድኃንኪዮ እማየ አይኅ ሰላም ለኪ።
ሐይመተ አብርሃም አብ ሰላም ለኪ ።
ዘኮንኪዮ ከመ ተድባብ ሰላም ለኪ።
ቤዛዊተ ኵሉ አለም ሰላም ለኪ።
ሰፋኒት በአርያም ሰላም ለኪ።
ወለተ ኢያቄም ወሐና ሰላም ለኪ።
ሥርጉት በቅድስና ሰላም ለኪ።
ያስምዓኒ ቃለ ፍሥሐ ጊዜ አኃዝን ወአስቈቁ
ሣህልኪ ይምጻእ እምሥራቁ ለእሳት ኃዘን እስከነ ይቈርር ሞቁ ማርያም ለኃጥእ ጽድቁ
ስብሐተ ለከ አምላኪየ አምላኪየ ነጽረኒ ወትረ ወኢትኅድገኒ ዘልፈ እስመ አንተ ትቤ እንዘ ትከስት አፈ ከመ ትፈፅም ሕገ
ዘተጽሕፈ ስብሐት ለከ።
ጊዜ ትወጽእ ነፍስከ እስከ ይሰማዕ ኲለሄ ኦ ዘትቤ ኤሎሄ ኤሎሄ ኢየሱስ አምላከ ርኅራኄ ስብሐት ለከ።
ከመ ታስትየነ ለነ ደመ ገቦከ ነባቤ እንተ አስተዩከ ሐሞተ ወከርቤ ጸማዕኩ በጊዜ ትቤ ስብሐት ለከ።
ድኅረ ሰለጥከ መዊተ በመልዕልተ መስቀል ዐልቦ እንዘ ኃጢአት ላዕሌከ አልቦ ኢየሱስ ርጉዘ ገቦ ስብሐት ለከ።
ስታየ ጽሙጓን ይኩን ወዘያረስዕ ትካዘ ማይ ምስለ ደመ ውኅዘ ገቦከ ጊዜ ተረግዘ ስብሐት ለከ።
ኖላዊነ ኄር ወዐቃቢነ ጽኑዕ እንተ ተሰቀልከ መልዕልተ ምሥዋዕ ኢየሱስ ቤዛ አባግዕ ስብሐት ለከ።
ተወከፍ ሊተ እግዚኦ ከመ ቁርባን ጥሉል በበሱባዔ እንዘ እከፍል ዘአቅረብኩ ለከ ኊልቈ ኢዮቤል ስብሐታተ ከመ አንሰ እክል
ግናይ ለክሙ ሥሉስ ቅዱስ ጠበብተ ፯ቱ አብያት እለ በላዕክሙ ውሣጤ ሐይመት ፩ደ ኅብስተ ትሥልስት ግናይ ለክሙ።
ድኀረ በላዕክሙ ላህመ በእንተ ፍቅረ ሰብእ ፍጹም።ዘበኃይልክሙ ሐይወ ላህም ።ሥላሴ ክቡራነ ስም ግናይ ለክሙ ።
ዘኢትቀሥፉ ወትረ ወኢትትመዓዑ ዘልፈ።እንዘ ሰብእ ይገብር ኃጣውአ እልፈ። በመፅሐፍ ከመ ተጽሕፈ ግናይ ለክሙ።
ከመ ባሕር ስፉሕ ወከመ እሳት ፅዱል ዘሀለ ወክሙ ትስልስተ አካል።ሥላሴ ዕደወ ኃይል ግናይ ለክሙ ።
ድኅረ ልቡናሁ ጼወወ ፍቅረ አሐቲ ብእሲት። ለዘወጽአ ረድዕ እምሃይማኖት።ዘመሐርክምዎ በ፳ዕለት መሐሩኒ ሥላሴ
ነገሥት።
ስብሓት ለእግዚአብሔር ወጸሎተ ሃይማኖት በል።

====ሰላምታ ዘሠርክ =====


ሰላም ለኪ ምልዕተ ጸጋ ምልዕተ ክብር ወብዕል እንበለ ንትጋ።አምላክ ሰማያዌ ዘወለድኪ በሥጋ። ሰላም ለኪ ።
ታቦተ ሕግ አንቀፀ ሥጋኪ ዘበድንግልና ንሡግ። ሀሊበኪ ጠበወ አበ አዕሩግ። ዘየዐውድዎ ዘወንጌል አፍላግ። ሰላም ለኪ።
ኦ እግዝእትየ እሙ ለፀሐይ ዳግሚት ሰማይ። መዝገበ ሥርናይ ወዘወይን ቀላይ። ብኪ ወበወልድኪ ይብዕል ነዳይ። ሰላም
ለኪ።
ሐመረ ብዕል ሙዳየ ዕፍረት ቢረሌ ፅዱል። ምዕራፈ ተድላኪ በብሔር ጥሉል። መልክዓ ገጽኪ በአርያም ሥዑል። ሰላም
ለኪ።
እመ ብርሃን። ዘወለድኪ ለነ ብሉየ መዋዕል አዝማን። ለኪ ወለወልድኪ ይገኒ ልሳን። ሰላም ለኪ።
ሰላማዊት ዘበድንግልና ኅትምት ወበቅድስና ሥርጉት። ነሀብ ዘአሰኒት ዘሲና ዕፀት። ሰላም ለኪ።
ታቦተ ሙሴ እምአመ ንዕስኪ እንተ ኢተኦምሪ ብእሴ። ሐውልተ ስምዕ ዘነቢይ አውሴ። ለኪ ወለወለድኪ ይደሉ ውዳሴ።
ስብሓት ለከ። ሀበነ ሰላመከ መምህረ ትሕትና ክርስቶስ ወልደ አምላክ ወሰብእ። ጊዜ ፍና ሠርክ በዓውደ መብልዕ። ዘረፈቀ
ምስለ አርዳዕ። ስብሐት ለከ ።
ሥጋከ ቅዱስ ለወጢነ ሐዲስ ሥርዓት። አንተ ወኀብኮሙ ለሐዋርያት። ድራር በልዑ ፍሥሓ ኦሪት። ስብሐት ለከ ።
እምሥጢርከ ይንሥኡ ኀበ ሐዋርያት ኀብሩ። አንተ ወሐብክሙ እምድኅረ ተደሩ። ተዝካረከ ከመ ይግበሩ። ስብሐት ለከ።
በእንተ ይሁዳ ዘትቤ ያገብዓኒ ፩ዱ። ተስእሎተ ዝንተ ነገር ለእለ ፈቀዱ። ዘአርአይከ ርደተ እዱ። ስብሐት ለከ ።
ለውእቱ ብእሲ እንተ አፍቀረ እበደ። እምሐየሶ ሶበ ኢተወልደ። እምያግብእከ ጊዜ ፈቀደ። ስብሐት ለከ።
በዛቲ ሰዓት በአዕደወ ፪ኤ ጻድቃን። እንተ ተገነዝከ በአምሣለ በድን። ኢየሱስ መንስኤ ሙታን። ስብሐት ለከ።
ዘንተ ኩሎ በእንተ ፍቅረ ሰብእ ዘኮንከ። ለሕማም ወሞት እስከ በጻሕከ። ይእዜኒ ተወከፍ ነግሀ ወሠርከ። ስብሓታተ
ዘናቄርብ ለከ።
ግናይ ለክሙ ኦ ሥሉስ ቅዱስ መገብተ ፯ቱ ሀብታት ዘትሁቡ አስበ በሠርከ ዕለት። ለቀደምት ወለደኀርት። ግናይ ለክሙ።
ውስተ መዓርጋት ዓሥር ዘአግባዕክሙ ፀሐየ። ሶበ ኃቤክሙ ጊዜ ሠርክ ጸለየ። ሕዝቅያስ እንተ ደወየ። ግናይ ለክሙ።
ጊዜ ጸለዮ ሥላሴ በአእዛነ መንፈስ ዕፁብ። እለ ትሰምዑ ለኆሳሰ ልብ። ወትፀመሙ ብዝኃ። ንባብ። ግናይ ለክሙ።
በይነ ሲሳዩ ሥጋዌ ወመንፈሳዊ ሲሳዩ። ለዘርኅበ ሰብእ በጌጋዩ። ሥለሴ ዘትሔልዩ። ግናይ ለክሙ።
ጊዜ ፍና ሠርክ ዳዊት አመ ውስተ ናኅስ ቆመ። ፫ተ ግብራተ ድኅረ ፈጸመ። ዘመሐርክምዎ ለዳዊት ቅድመ። መሐሩኒ ሥላሴ
ዳግመ።
ስብሓት ለእግዚአብሔር ከአቡነ ዘበሰማያት በል።

You might also like