የ2014 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ኢፓልኮ

You might also like

Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 74

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን

የ 2014 በጀት ዓመት ዕቅድ


አፈፃፀም ሪፖርት

1
ሰኔ 2014 ዓ.ም
አዲስ አበባ

ማዉጫ
1. ድርሞ/Executive Summary.....................................................................................................................................................3

2. የኢንዱስትሪ ፓርክ ዘርፍ የሚገኝበት አለም አቀፋዊ ፣ ሀገራዊ እና ድርጅቱ የሚገኝበት ሁኔታ...........................................8
3. የዋና ዋና ግቦች ዒላማዎች አፈፃፀም............................................................................................................................................11

4. ኮርፖሬት ገቨርናንስ እና ፋይናንስ.........................................................................................................................................41

4.1. ኮርፖሬት ገቨርናንስ..................................................................................................................................................................41

4.3. የሪፎርምና የሰው ሃይል አቅም ግንባታ ስራዎች......................................................................................................43

5. የበጀት ዓመቱ ሪፖርት በሠንጠረዥ............................................................................................................................................45

6. የፋይናንስ መግለጫዎች (Balance Sheet & Income Statement)....................................................................................605

8. ትኩረት የሚሹና ድጋፍ የሚፈልጉ ጉዳዮች.......................................................................................................................63

2
1. ድርሞ/Executive Summary

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የ 2014 በጀት ዓመት ዕቅድ በዋነኛነት የትኩረት መስክ አድርጎ የኢንዱስትሪ
ፓርኮች ግንባታን በማስፋፋት ፤ የወጪ ንግድን በማሳደግ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ማሳደግ፤ ለወጣቶች የሥራ ዕድል
በመፍጠር የሥራ አጥነትን አገራዊ ተግዳሮት ማቃለል፣ የአካባቢ ጥበቃ ሥራን በማጠናከር ከተሞችን ወደ ላቀ
የዕድገት ደረጃ እንዲሸጋገሩ ማድረግ እና ሌሎች ከኢንዱስትሪያላይዜሽን ጋር የተያያዙ ቁልፍ ተግባራትን በማከናወን
የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ዕድገትን ማስቀጠል ብሎም ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ ክፍለ ኢኮኖሚ የሚደረገውን ሽግግር
ማሳለጥ ላይ አትኩሮት ያደረጉ አገራዊ ግቦችን ከማሳካት ረገድ የበኩሉን አስተዋፅዖ ለማድረግ ያዘጋጀውን የ 2014
በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር እየሰራ ይገኛል፡፡

በ 2014 በጀት ዓመት የሀገራዊ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ስፓሻል ማስተር ፕላንን መሰረት ባደረገ መልኩ የኢንዱስትሪ
ፓርኮች ልማትን ማፋጠን አንዱ ግብ ሲሆን የሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክ የውሃና ፍሳሽ ማጣሪያ ሲቪል ስራዎች
አንዲሁም ሌሎች በፓርኩ ውስጥ መጠናቀቅ የሚገባቸው እና ማስተካከያ የሚያስፈልጋቸው ስራዎች አፈፃፀም
31.6% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙም ማነስ ዋነኛ ምክንያት ከቀረጥ ነፃ ጋር በተያያዘ የእቃ መዘግየት እንዲሁም ከወቅታዊ
ሃገራዊ የፀጥታ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ረዘም ላሉ ወራት ስራ ተቋራጩ በሳይት ላይ ተመልሶ ስራዉን ማከናወን ያልቻለ
በመሆኑ ነው፡፡

በሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የፍሳሽና ውሃ ማጣሪያዎች የእርማትና ማስተካከያ እንዲሁም የአጠቃላይ የፓርኩን
3
ደህንነት በተሟላ ሁኔታ መጠበቅ የሚያስችል የ CCTV እና ተያያዥ ስራዎች ሙሉ ለሙሉ ተጠናቀው የርክክብ
ሂደቱ ተፈጻሚ ሆኗል፡፡ በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርከ ከፍሳሽ ማጣሪያ ፣ Electric Fence & CCTV Camera ገጠማ፣
የጎርፍ መከላከያ እና ተያያዥ ስራዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ መጠናቀቅ የሚገባቸው እንዲሁም የማስተካከያ እና
የእርማት ስራ የሚያስፈልጋቸው ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ የፍሳሽ ማጣሪያ ቀሪ ስራዎችን የማጠናቀቅ እና
የ Test እና Commisioning ስራ ፣ የሎሪ ፓርኪንግ ፤ የጎርፍ ማስተላለፊያ ትቦ( የቦክስ ከልቨርት) ፣ ሁለት ቦታዎች
ላይ አጥር የመዝጋት ስራ፣ የጥበቃ ቤት አንዲሁም የክሊኒክ ቆሻሻ ማቃጠያ ግንባታ ተጠናቋል፡፡

በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ቀደም ሲል የተጀመሩ የግንባታ ሥራዎች በ 2014 በጀት ዓመት የአስራ
ሁለት ወር አማካይ ጠቅላላ የፊዚካል አፈጻጸምን ወደ 100% ለማድረስ የታቀደ ሲሆን የማስተካከያ ስራ እና ርክክብ
መፈጸም ከሚያስፈልጋቸዉ ፕሮጀክቶች ውስጥ የ G+2 Business Incubation ceneter ህንፃ የመጀመሪያ ደረጃ
ርክክብን መፈጸም ተችሏል በዚህም የዕቅዱን 98.3% ማድረስ ተችሏል፡፡

የኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ ፍሳሽ ማጣሪያ ግንባታን በተመለከተ በበጀት ዓመቱ 50% ለማከናወን ታቅዶ የነበረ
ቢሆንም ስራውን በተያዘለት ጊዜ ማከናወን አልተቻለም፡፡ ለዚህም እንደ ዋና ምክንያቶች ከሚጠቀሱት መካከል
የዲዛይን ሥራውን የሚያከናውነው ሥራ ተቋራጭ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ አለመግባቱ እንዲሁም ወቅታዊ ሃገራዊ
የፀጥታ ችግር ናቸው፡፡

በቦሌ ለሚ ምዕራፍ ሁለት እና ቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን በተመለከተ ያልተጠናቀቁ የግንባታና ከመሰረተ
ልማት ጋር የተያያዙ ስራዎች በኮሚቴ በጋራ ተለይተው ክትትል እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡ በዚህም በቦሌ ለሚ 100%
ታቅዶ 67% እንዲሁም በቂሊንጦ 100% ታቅዶ 79.5% ተከናውኗል፡፡ ለሁለቱም ኢንዱስትሪ ፓርኮች ለአፈፃፀሙ
ማነስ ዋነኛ ምክነያት በይዞታ ይገባኛል ጥያቄ ምክነያት የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ገመድ መዘርጋት ባለመቻሉ
ለፓርኮቹ ሀይል ማቅረብ አልተቻለም፡፡ በዚህም ባለሃብቶች በሙሉ አቅማቸው ወደ የምርት ሂደት ስላልገቡ የፍሳሽ
ማጣሪያውን በአቅሙ ማንቀሳቀስ አልተቻለም፡፡

የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የጊዜያዊ ውሃ አቅርቦት በፓርኩ ውስጥ የ 403 ሜ የጥልቅ ውሀ ጉድጓድ ቁፋሮ ተከናውኖ
ውሃ የተገኘ ሲሆን፣ በድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ የዘላቂ ውሃ አቅርቦት ለማረጋገጥ የጥልቅ ውሃ ጉድጓድ ከፓርኩ ከ 8
ኪ.ሜትር ላይ ተቆፍሮ እና መስመር ዘርግቶ የውሃ አቅርቦቱን ተደራሽ ለማድረግ በበጀት ዓመቱ 53.86% ለማከናወን
ታቅዶ 53.86% የተከናወነ ሲሆን፤አፈፃፀሙም 100% ነዉ።

የኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ ጊዜያዊ የኤሌክትሪክ ኃይል በተመለከተ ተጨማሪ 16 ሜጋዋት ለማቅረብ የታቀደ
ሲሆን በ 2014 በጀት ዓመት 60% ክንውን እንዲኖረው ታቅዶ 50.22% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 83.7% ነው፡፡
ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛ ምክንያቶች የኮንክሪት ፖሎች ተከላ ለማከናወን የ ROW(የይዞታ ይገባኛል ጥያቄ) ችግር
፣በሀገሪቱ በነበረው ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ስራውን ለመፈፀም አስቸጋሪ መሆን እንዲሁም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ
አገልግሎት በኩል ስራው በፍጥነት አለመከናወኑ ነው፡፡
4
ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ ማድረግን በተመለከተ ለቦሌ ለሚ ምዕራፍ ሁለት ኢንዱስትሪ ፓርክ ዘላቂ
የኤሌክትሪክ ኃይል እስኪሟላ ድረስ ሻንግቴክስ ለተባለ የግል ባለሀብት 1.2 ሜጋዋት ጊዜያዊ የኤሌክትሪክ ኃይል
ለማቅረብ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 927,749.36 የዋጋ ግምት ቀርቦ ክፍያው ተከናውኗል፡፡ ባለሀብቱ
ያቀረበውን ትራንስፎርመር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የፍተሻ ስራ ተከናውኖ የኤሌክትሪክ መስመሩ
ኢነርጃይዝ ሆኗል፡፡ ለባለሀብቱም የኤሌክትሪክ ኃይል ከታቀደበት ጊዜ አስቀድሞ ቀርቧል፡፡ በበጀት ዓመቱ 100%
ለማጠናቀቅ ታቅዶ 100% ተፈፅሟል፡፡

ለሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክ 10 ሜጋዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የመካከለኛ ቮልቴጅ ማከፋፈያ መስመር
ዝርጋታ፣ ፍተሻና ሙከራ ስራ ተጠናቋል፡፡ በፓርኩ ውስጥ የኤሌክትሪክ ኬብል ዝርጋታ ስራ የተከናወነ ሲሆን
የሰብስቴሽን ወጪ ላይ የዕቃዎች ገጠማ፣ ፍተሻና ሙከራ ተከናውኗል፡፡

የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ 10 ሜጋዋት ጊዜያዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማሟላት በታቀደው
መሰረት በበጀት ዓመቱ 23% ለማድረስ በተያዘው እቅድ መሰረት 14.8% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 64.4% ነው፡፡
ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛ ምክንያቶች የኮንክሪት ፖሎችና ተያያዥ የኤሌክትሪክ ዕቃዎች አቅርቦት መዘግየት፣
በዋነኛነት 11 ኮንክሪት ፖሎች ለመትከል በቦሌ አራብሳ ሰብስቴሽን ውስጥ የሚገኙ ባለይዞታዎች በቅድሚያ የካሳ
ክፍያ ካልተከፈለ ፖሎቹን ማስተከል እንደማይችሉ በመግለፃቸው እንዲሁም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
ክፍያውን በሚፈለገው ፍጥነት አለመፈፀሙ ናቸው፡፡

ለሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክ 10 ሜጋዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የመካከለኛ ቮልቴጅ ማከፋፈያ መስመር
ዝርጋታ ፍተሻና ሙከራ ስራ ተጠናቋል፡፡ ለሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል በ underground Cable
ተደራሽ ለማድረግ በበጀት አመቱ 24% ክንውን እንዲኖረው ታቅዶ 15.6% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 65% ነው፡፡
ለአፈፃፀም ማነስ ምክነያት በኢትዮጲያ ኤሌክትሪክ ኀይል አገልገግሎት በኩል በታቀደው ግዜ ወደ ሥራ
ያለመግባት ነው፡፡

ለቦሌ ለሚ II ኢንዱስትሪ ፓርክ ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ ለማድረግ በበጀት አመቱ 95% ክንውን
እንዲኖረው ታቅዶ 48.8% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 51.36% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛ ምክንያት የሚነሱ
የይገባኛል ጥያቄዎች ከሚመለከተው አካል ምላሽ ባለማግኘታቸው ነው፡፡ የቴሌኮም መሰረት ልማት አቅርቦት ስራ
በበጀት ዓመቱ ለሰመራ 30% እንዲሁም ለባህርዳር 80% ስራ ተጠናቋል፡፡ ለአይሻ ኢንዱስትሪ ፓርክ የቴሌኮም
መሰረተ ልማት እንዲሟላ የቅድመ ዝግጅት ሥራ እንዲከናወን በተያዘው ዕቅድ መሰረት በኢትዮ ቴሌኮም በኩል
የአዋጭነት ጥናት ተከናውኖ ለፓርኩ የሚያስፈልገው የቴሌኮም መሰረተ ልማት ከፓርኩ በ 17.69 ኪ.ሜ ርቀት ላይ
ከሚገኝ የቴሌኮም መሰረተ ልማት ሟሟላት እንደሚቻል ተረጋግጧል፡፡ በ 2014 በጀት ዓመት 20% ክንውን
እንዲኖረው ታቅዶ 20% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 100% ነው፡፡

5
በበጀት ዓመቱ ለኢንዱስትሪ ፓርኮቹ የመዳረሻ መንገድ ግንባታ ለማከናወን ከተያዙት ውስጥ የኮምቦልቻ
ኢንዱስትሪ ፓርክ ተደራሽ ከሚደረገው የ 3.28 ኪ.ሜትር የመዳረሻ መንገድ የቀሪ 2.55 ኪ.ሜትር ግንባታ ዉስጥ ቀሪ
ዉስን የማጠናቀቂያ ስራዎችን ለማጠናቀቅ 11.75% ዕቅድ ተይዞ 11.75% የተከናወነ ሲሆን ይህም አፈፃፀሙም 100%
ነው፡፡

በአጠቃላይ ወደ ኦፕሬሽን በገቡ ኢንዱስትሪ ፓርኮች እስካሁን ለ 67,352 (ወንድ 9,453 እና ሴት 57,899) ዜጎች የስራ
ዕድል የተፈጠረ ሲሆን የሀዋሳ(38.8%)፣ ቦሌ ለሚ(34.6%)፣ እና አዳማ(18%) ኢንዱስትሪ ፓርኮች ከአጠቃላይ የሥራ
ዕድል ፈጠራው ከፍተኛውን ድርሻ ይወስዳሉ፡፡ ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አፈፃፀም (41,208) ጋር
ሲነፃፀር በበጀት ዓመቱ የሥራ እድል ፈጠራ በ 7.58% እድገት ያሳየ ሲሆን በአዳማ ፣ በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ
እና አዲስ ኢንዱስትሪ መንደር ውስጥ ያሉ ባለሀብቶች ከፍተኛ የሆነ የሰው ሀይል በመቅጠራቸው እንዲሁም
የቂሊንጦ አና ባህር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ኦፕሬሽን መግባት በበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈፃፀም መመዝገብ
ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው፡፡ በኢንዱስትሪ ፓርኮች በጀት ዓመቱ ለ 74,200 ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ
በአጠቃላይ ለ 55,266 ስራ ዕድል የተፈጠረ ሲሆን አፈጻጸሙ 74.5% ይሆናል፡፡ በበጀት ዓመቱ ውስጥ 4,373 የሚሆኑ
ሰራተኞች ከአንዱ ድርጅት ወደ ሌላው ድርጅት የተመደቡ (reallocated) የተደረጉ ናቸው፡፡ በበጀት ዓመቱ ውስጥ
በ AGOA በተፈጠረው ተጽዕኖ ምክንያት ኩባንያዎች በመልቀቃቸው (ሀዋሳ) እና በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው
ጦርነት ምክንያት ኩባንያዎች ለተወሰነ ጊዜ ስራ በማቆማቸው፣ ጥቅማ ጥቅም ማነስ፣ ደመወዝ ማነስ እና መኖሪያ
ቤት አቅርቦት ችግር ምክንያት ከኢንዱስትሪ ፓርኮች በአጠቃላይ 51,591 ሰራተኞች የለቀቁ ሲሆን የሰራተኞች
የመልቀቅ ምጣኔን ለመቀነስ እና የስራ ዕድል ፈጠራ እና ምርታማነትን ለማሳደግ ከሰራተኞች መብት እና ጥቅማ
ጥቅም ጋር ተያይዞ የሚታዩ ችግሮች ከባለሀብቶች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል
እየተሰራም ነው፡፡

በኢንዱስትሪ ፓርኮች በበጀት ዓመቱ ምርትና ምርታማነትን በማሻሻል ከወጪ ንግድ የሚገኝ ገቢ እንዲጨምር
የሚያስችሉ ሥራዎች የተሰሩ ሲሆን 212,255,619.00 የአሜሪካን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 179,493,664 የአሜሪካን
ዶላር ማግኘት ተችሏል አፈፃፀሙም 84.56% ነው፡፡ ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፃር በ 28.39 %
እድገት አሳይቷል፡፡ የመብራት መቆራረጥ፣ የሠራተኞች ምርታማነት ውስንነት፣ የኮሮና ቫይረስ መስፋፋትና ወቅታቂ
የሀገሪቱ ጉዳይ በወጪ ንግዱ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ እያሳደረ ሲሆን በነዚህ ጉዳዮች ላይ ዘለቄታዊ መፍትሄን
በማስቀመጥ የወጪ ንግዱን የበለጠ ማሳደግ የሚቻልበት እድል እንዳለ ለመረዳት ተችሏል፡፡ በአጠቃላይ የመቐለ
ኢንዱስትሪ ፓርክ ሳያካትት ወደ ኦፕሬሽን በገቡ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ምርት ከገቡ ጊዜ አንስቶ የኤክስፖርት
አፈጻጸም እስከ ሰኔ ወር 2014 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ የባለፈው 2013 ዓ.ም ተኪ ምርቶች ሽያጭ ጭምር
914,835,812.38 የአሜሪካን ዶላር የሚያወጣ ምርት እንዲመረት ክትትል እና አስፈላጊውን ድጋፍ ተደርጓል፡፡

በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያሉ ድርጅቶች ከሀገር ውስጥ ካሉ አነስተኛ እና መካከለኛ አምራች ድርጅቶች ጋር
የጥሬ እቃ አቅርቦት ትስስርን ለማሳደግና ለማጠናከር በዕቅድ በተያዘው መሰረት በ 5 ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ
6
ያሉ 20 ድርጅቶች ከሀገር ውስጥ ካሉ አምራቾች እና ገበሬዎች ጋር በፈጠሩት የንግድ ለንግድ ትስስር በበጀት ዓመቱ
34,158,862.02 (በብር 1,599,163,464.14) ሚሊዮን ዶላር ግብይት ተፈጥሯል፡፡ ካርቶኖች፣ ማሸጊያዎች፣ ማቅለሚያ፣
ገብስ፣ ጥሬ ቆዳ፣ የእስቴሽነሪ ዕቃዎች የግብይት ዋነኛ የምርት አይነቶች ሲሆኑ በቀጣይም ትስስሩ እንዲጠናከር
ክትትል እና ድጋፍ የሚደረግ ይሆናል፡፡

በኢንዱስትሪ ፓርኮች የሼዶች የመያዝ ምጣኔን በተመለከተ ሼድ በተገነባላቸው 11 ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ
የመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክን ሳይጨምር ካ 162 ሼዶች 716,740 ሜ 2 ስፋት በባለሀብት የተያዙ ሲሆን የመያዝ
ምጣኔውን 84.1% ያደርገዋል፡፡ በድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ ካሉት 15 ሼዶች 7 ብቻ በባለሀብት የተያዙ ሲሆን
የመዳረሻ መንገድ ግንባታ በወሰን ይገባኛል ጥያቄ ምክንያት መጓተቱ ዋነኛ ምክንያት ናቸው፡፡ በበበጀት ዓመቱ
የሼዶችን የማምረት ምጣኔን በሚመለከት ለባለሀብቶች ለምርት ስራ በኪራይ ከተላለፉ 135 ሼዶች ዉስጥ
602,750 ሜ 2 የሚሆኑት ለምርት ስራ የዋሉ ሲሆን ቀሪዎቹ 113,990 ሜ 2 ሼዶች በተሟላ መልኩ ለምርት ስራ
እየዋሉ ባለመሆናቸው የሼዶች የመጠቀም ምጣኔ (Utilization Rate) 84.1% ሆኗል፡፡ የመጠቀም ምጣኔ አፈፃፀም
ከዕቅዱ አንፃር ያነሰበት ምክንያት ሼዶችን ተረክበዉ ወደ ኦፕሬሽን የገቡ ባለሀብቶች በተወሰኑት ሼዶች ላይ ብቻ
በመስራታቸዉና የመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ በወቅታዊ ችግር ምክንያት ፓርኩ ያለበት ሁኔታ አስቸጋሪ በመሆኑ
ነው፡፡ አስፈላጊውን ክትትል እና ድጋፍ በማድረግ የአጠቃቀም ምጣኔውን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡
በተመሳሳይ የለማ መሬት ባላቸው 9 ኢንዱስትሪ ፓርኮች በድምሩ 540.55 ሄክታር የለማ መሬት ውስጥ 61.42
ሄክታር የሚሆነው ለባለሀብቶች በሊዝ የተላለፈ ሲሆን የመያዝ ምጣኔውን 11.36% የሚያደርገው ሲሆን ግንባታ
የተከናወነባቸው እና እየተከናወነባቸው ያሉት 36.4 ሄክታር መሬት (59.26%) ነው፡፡ የሲሚንቶ እጥረት እንዲሁም
በውላቸው መሰረት በወቅቱ ወደ ግንባታ ሥራ አለመግባታቸው አጠቃቀሙ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ፈጥሯል፡፡በአይ ሲ
ቲ ፓርክ ውስጥ መሰረተ ልማት ተሟልቶላቸው ለኪራይ ዝግጁ የሆኑ ቢሮዎች ስፋት 2,565.8 ሜ 2 ሲሆን 2,565.8
ሜ2 የሚሆነው በተከራዮች የተያዘ ሲሆን ይህም የመያዝ ምጣኔው 100% ይሆናል፡፡ ቢሮዎቹን ለምርት እና
አገልግሎት የመጠቀም ምጣኔን በተመለከተ በባለሀብቶች የተያዙ ቢሮዎች ሙሉ በሙሉ በሥራ ላይ ያሉ በመሆኑ
የመጠቀም ምጣኔውን 100% ያደርገዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ ባለሀብቶችን ለመሳብ በእቅድ ተይዞ የነበረ ሲሆን ሀገሪቷ ላይ ባለው አለመረጋጋት ምክንያት
ባለሀብቶችን በታቀደው ልክ ለመሳብ አልተቻለም፡፡ ይሁንና ባለፈው በጀት ዓመት መጨረሻ ላይ በደብረ ብርሀን
ፓርክ የገባው ሻንግቻንግ የተባለው ድርጅት የሼድ ርክክብ የተደረገለት ሲሆን አጠቃላይ የኢንቨስትመንት ካፒታሉ
15.9 ሚሊዮን ዶላር ነው፡፡ ድርጅቱ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ ሲገባ ለ 2 ሺ ሠራተኞችን የሥራ ዕድል የሚፈጥር ሲሆን
20 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ምርት በየአመቱ ለወጪ ንግድ የሚያቀርብ ይሆናል፡፡ በተመሳሳይ በሀዋሳ ኢንዱስትሪ
ፓርክ የሰራተኛ መኖሪያ ቤት ለመገንባት ኮርነር ስቶን የተባለ ሀገር በቀል ኩባንያ 2.08 ሄክታር መሬት በሊዝ የተረከበ
ሲሆን አጠቃላይ ኢንቨስትመንቱ 13.63 ሚሊዮን ዶላር ነው፡፡ ፕሮጀክቱ በ 1 አመት ከ 6 ወር ለማጠናቀቅ በዕቅድ
የተያዘ ሲሆን 6,500 ሠራተኞችን የመኖሪያ ቤት ተጠቃሚ የሚያደርግ ይሆናል፡፡

የኢንዱስትሪ ፓርክ ልማትን ዘለቄታዊ ማድረግ አንዱ ግብ ሲሆን በበጀት ዓመቱ የሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የፍሳሽ
7
ማጣሪያ የማስተካከያና ቀሪ ሥራዎች ማጠናቀቅ 43% ለማከናወን ታቅዶ 21% ተከናውኗል፣ የአዳማ ኢንዱስትሪ
ፓርክ ከፍሳሽ ማጣሪያ ጋር የተያያዙ ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ 28% ለማከናወን በዕቅድ ተይዞ 21% ተከናውኗል፣
አፈፃፀሙም 75% ነው፡፡ የድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ የፍሳሽ ማጣሪያ የማስተካከያና ቀሪ ሥራዎች ማጠናቀቅ 15%
ለማከናወን ታቅዶ 6% የተከናወነ ሲሆን አፈፃፀሙም 40% ነው፡፡ ቦሌ ለሚ ምዕራፍ 2 ፍሳሽ ማጣሪያና ቀሪ
የማስተካከያ ሥራዎች ማጠናቀቅ 85% ለማከናወን ታቅዶ 65% ተከናውኗል፣ አፈፃፀሙም 76.4% ነው፡፡ ቂሊንጦ
ኢንዱስትሪ ፓርክ ፍሳሽ ማጣሪያና ቀሪ የማስተካከያ ሥራዎች ለማጠናቀቅ በበጀት ዓመቱውስጥ 85% ለማከናወን
ታቅዶ 72.5% ተከናውኗል፣ አፈፃፀሙም 85.2%% ነው፡፡

በኢንዱስትሪ ፓርኮች በበጀት ዓመቱ ከሀዋሳ፣ ቦሌ ለሚ እና አዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች 2,018,053 ሜ 3 ፍሳሽ
ለማጣራት የታቀደ ሲሆን 1,636,659.71 ሜ 3 ፍሳሽ ተጣርቷል፡፡ ከሀዋሳ የዜሮ ሊኪውድ ማጣሪያ 1,928,360 ሜ 3
የተጣራ ውሃ ጥቅም ላይ ለማዋል የታቀደ ሲሆን 1,556,284.45 ሜ 3 የተጣራ ውሃ ጥቅም ላይ እንዲውል ተደርጓል፡፡
በበበጀት ዓመቱ 12,949.27 ሜ 3 ደረቅ ቆሻሻ ከሰባት ኢንዱስትሪ ፓርኮች ለማስወገድ እቅድ ተይዞ 15,527.32 ሜ 3
በአግባቡ ተወግዷል፡፡ በአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሩ በበጀት አመቱ 1,000,000 ችግኞችን ለመትከል የታቀደ ሲሆን
በበጀት ዓመቱ አመቱ 785,305 ችግኞች የተተከሉ ሲሆን በቀሪዎች ዝናባማ ወቅቶች ቀሪዎቹ የሚተከሉ ይሆናል፡፡
ቀደም ሲል የተተከሉት ጨምሮ የእንክብካቤ ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡
የበጀት አፈፃፀምን በተመለከተ በበጀት ዓመቱከሼዶች ኪራይ፣ ከለማ መሬት እና ኮርፖሬሽኑ ከሚሰጣቸው
አገልግሎቶች ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብ፤ ከሼዶች ኪራይ፣ ከለማ መሬት ሊዝ፣ ከምክር እና ስልጠና አገልግሎቶች
እና ከሌሎች አገልግሎቶች ብር 998,313,358.30 ሚሊዮን ብር ለማግኘት ታቅዶ ብር 791,417,371.95 ሚሊዮን ገቢ
ተገኝቷል፡፡ ከዚህም በጥሬ ገንዘብ የተሰበሰበ 455,657,916.38 ሚሊዮን ብር ነው፡፡ ይህ አፈፃፀም ከዕቅዱ አንፃር
ያነሰበት ምክንያት በዋነኝነት በኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሉ ተከራዮች የሚጠበቅባቸውን የኪራይና የተለያዩ
አገልግሎቶች ክፍያ በወቅቱ እየከፈሉ ባለመሆኑ፤የደብረ ብርሀን እና አዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች የጋራ መገልገያዎች
አልቀው ወደ ስራ ባለመግባታቸው ነው፡፡ በበጀት ዓመቱ ለሥራ ማስኬጃ 504,462,248.14 ሚሊዮን ብር ወጪ
ለማድረግ ታቅዶ ብር 317,452,632.70 ወጪ በመደረጉ አፈፃፀሙ 62.9% ነው፡፡ በበጀት ዓመቱ ብር 101,137 ሚሊዮን ብር
ትርፍ ለማግኘት የታቀደ ሲሆን በ 9 ወራት ውስጥ ትርፍ 79 ሚሊዮን ብር ማግኘት ተችሏል፡፡

በሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወሠንን ለማስከበር የሚያስችሉ የአጥር ግንባታ ሥራ ለማከናወን፣ የውሃ መስመር
ዝርጋታ ሥራ፣ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ለመዘርጋት ፣ ለባለሀብት ርክክብ የሚፈፀምባቸው ቦታዎች ፣ መዳረሻ
መንገድ ግንባታዎችና በአጠቃላይ ኮርፖሬሽኑ በሕጋዊ አግባብ በተረከባቸው ቦታዎች ከይዞታ ይገባኛል ጥያቄ ጋር
በተያያዘ በርካታ ጥያቄዎች ተነስተዋል፡፡ በዚሁ መሠረት በዕቅድ የተያዙ ሥራዎችን ለማከናወን አሉታዊ የሆነ
ተፅዕኖ አሳድሯል፡፡ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ከዘላቂ የውሀ አቅርቦት ጋር ተያይዞ የድሬዳዋ እና አዳማ ኢንዱስትሪ
ፓርኮች የውሀ አቅርቦት አለመኖር ፣ የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎትን በሚመለከት በሁሉም ፓርኮች በሚባል ደረጃ
የመቆራረጥ ችግር ለሥራዎች አፈጻጸም ተግዳሮት ሆኗል፡፡
8
በጀት ዓመቱን ጥቅል አላማና ግቦችን እንዲሁም ዋና ዋና ተግባራትን መነሻ በማድረግ በኮርፖሬሽኑ የተከናወኑ
ሥራዎች እና ሌሎች ከዕቅድ ውጪ የተከናወኑ ሥራዎችን በማካተት እንዲሁም በክንውን ወቅት ያጋጠሙን
ችግሮችና ለወደፊት መወሰድ ያለባቸውን የማስተካከያ እርምጃዎች በማካተት የ 2014 በጀት ዓመት ዕቅድ
አፈጻጸም ሪፖርት በዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

2. የኢንዱስትሪ ፓርክ ዘርፍ የሚገኝበት አለም አቀፋዊ ፣ ሀገራዊ እና ድርጅቱ የሚገኝበት ሁኔታ
በዓለም የመጀመሪያው የኢንዱስትሪያል ፓርክ ልማት እ.ኤ.አ በ 1896 በማንችስተር ፣ እንግሊዝ ውስጥ
የተጀመረ ሲሆን ፣ በአሜሪካ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በስፋት ልማቱ ሊስፋፋ ችሏል፡፡ የኢንዱስትሪ
ፓርክ ልማት ከምዕራቡ የዓለም ክፍል ወደ እስያ በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን በተለይም በምስራቅ እስያ በፍጥነት
አድጓል። የኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ከምዕራቡ የዓለም ክፍል ወደ እስያ በ 20 ኛው ክፍለ ዘመን በተለይም
በምስራቅ እስያ በፍጥነት አድጓል። በዚህም በቀደምትነት እና በዋነኝነት ቻይና ፣ ሲንጋፖር ፣ ኮርያ እና
ቬትንሀም ፣ ከዘርፉ በመጠቀም በኢኮኖሚያቸው ላይ መዋቅራዊ ዘለቄታዊ ለውጥን ለማሳካት የቻሉ ሀገራት
ናቸው፡፡

የምስራቅ እስያ ሀገራት በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ያስመዘገቡት ስኬት በርካታ የአፍሪካ ሀገራት በዘርፉ
እንዲሳተፉ መሰረት የጣለ ሲሆን ኢትዮጵያም ባለፉት ሰባት አመታት በሀገሪቱ በተለያዩ ክልሎች ከ 20 በላይ
የሚሆኑ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን በመንግስትና በግሉ ዘርፍ በማልማት ወደ ኦፕሬሽን ለማስገባት ችላለች፡፡
በአፍሪካ እንዲሁ ጎረቤታችን ኬንያን ጨምሮ ግብፅ ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ሌሎች ሀገራትም ኢንዱስትሪ
ፓርኮችን የማልማት ሂደት ውስጥ ይገኛሉ፡፡

እ.ኤ.አ. በ 2014 የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ኢትዮጵያ በወቅቱ ተግባረዊ ታደርገው የነበረውን
ሁለተኛውን የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ለማሳካት እንዲሁም አገራዊ የኢንደስትሪላይዜሽን
አጀንዳዎችን ለማፋጠን የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በማልማትና በማስተዳደር ፣የለሙ መሬቶችን ለባለሃበቶች
9
የማስተላለፍ እንዲሁም የመሠረተ ልማት ግንባታ የማሟላት ኃላፊነት ተጥሎበት በመንግስት የልማት
ድርጅትነት ተቋቁሟል። የኢትዮጵያ መንግስት ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ቅድሚያ በሚሰጣቸው ዘርፎች
ለማስተዋወቅ፣ የስራ እድል ለመፍጠር እና የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግርን ለማሳለጥ ሀገር አቀፍ የኢንዱስትሪ
ፖሊሲ በመተግበር ላይ ይገኛል።

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ማቋቋሚያ አዋጅ 886/2015 የኢንዱስትሪ ፓርኮች ዓላማዎችን ፤ ለአገሪቱ የቴክኖሎጂ
እና የኢንዱስትሪ መሠረተ ልማቶች እድገት አስተዋጽኦ ማድረግ፤ በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች እና
ተዛማጅ ኢንቨስትመንቶች ውስጥ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎን ማበረታታት፤ የአገሪቱን የኢኮኖሚ ልማት
ተወዳዳሪነት ማሳደግ እንዲሁም ሰፊ የስራ እድሎችን መፍጠር እና ዘላቂ የኢኮኖሚ ልማት ማስመዝገብ
በማለት በግልፅ ያስቀምጣል፡፡

በአለም አቀፍ ደረጃ ሀገራችን በኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ዘርፉ ገና ከጀማሪ ሀገራት ረድፍ የምትሰለፍ ሲሆን
ከለሙት ኢንዱስትሪ ፓርኮች ከ 80 በመቶ በላይ የሚሆኑት በቀላል ኢንዱስትሪዎች ላይ ያተኮሩ ናቸው፡፡
በፋርማሲዩቲካል እና በአይ ሲ ቲ ኢንዱስትሪ ፓርክ ላይ ያተኮሩ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ከ 10 በመቶ በታች ድርሻ
አላቸው፡፡ ለንፅፅር ቻይና ከበበበጀት ዓመቱ ሺ በላይ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን በመንግስትና በግሉ ዘርፍ ያለማች
ሲሆን ከቀላልና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ቴክኖሎጂ የሚጠቀሙ ኢንዱስትሪዎች ላይ
ያተኮሩ በርካታ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን አልምታ በማስተዳደር ላይ ትገኛለች፡፡ በተመሳሳይ ሲንጋፖር ከፍተኛ
የህዝብ ቁጥር እድገት ላይ የነበረችና ከዚህም ተከትሎ ለመጣው ከፍተኛ የስራ እድል ጥያቄ መፍትሄ ሊሆን
የሚችል እንዲሁም ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ አካባቢን ለመፍጠርና ሀገሪቱ ከነበረችበት ከፍተኛ
‘‘enterport trade’’ ለመውጣት የሚያስችል እቅድ በመቅረፅ በ 1968 ጄቲሲ ኮርፖሬሽንን በማቋቋም
በመጀመሪያው ምዕራፍ ኢንዱስትሪያል እስቴቶችን በጁሮንግ ከተማ የማልማት ስራን ከውናለች፡፡ በሀገሪቱ
በአጠቃላይ በበበጀት ዓመቱ ኢንዱስትሪያል ፓርኮች የሚገኙ ሲሆን በሀይ ቴክ ፣ በሜዲካል እና በኤሮ ስፔስ
ዘርፎች ላይ ያተኮሩ ናቸው፡፡

በኢትዮጲያ 6 የሚሆኑ የግል ኢንዱስትሪ ፓርክ አልሚዎች የሚገኙ ሲሆን ከስራ እድል ፈጠራና የውጪ
ምንዛሬ ግኝት አንፃር የራሳቸውን አስተዋፅኦ እያረጉ የሚገኙ ቢሆንም መንግስት ካለማቸው ኢንዱስትሪ
ፓርከች ጋር ሲወዳደሩ አፈፃፀማቸው አነስ ብሎ ይታያል፡፡ በተጨማሪም በክልል መንግስታት የለሙ 4 አግሮ
ኢንዱስትሪያል ፓርኮች ያሉ ሲሆን ወደ ሙሉ የማምረት አቅም ለማስገባት እየተሰራ ይገኛል፡፡

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ከምስረታው አሁን እስከሚገኝበት ደረጃ በርካታ ተግዳሮቶችን
ሲያልፈ የመጣና እያለፈም የሚገኝ የመንግስት የልማት ድርጅት ነው፡፡ኮርፖሬሽኑ የሚያስገነባቸው ኢንዱስትሪ
ፓርኮች ከውጪ መሰረተ ልማቶች ማለትም ኃይል፣መንገድ፣ቴሌኮሙኒኬሽን፣እንዲሁም የከተማ መሰረተ ልማቶች የውሃ
አቅርቦትና ህክምና፣ቤትና ሌሎች ማህበራዊ መሠረተ ልማቶች የተሳሰሩ በመሆናቸው የሀገር አቀፍ የኢንዱስትሪ ፓርኮች

10
መሪ ፕላን ከአጠቃላይ አገራዊ የመሰረተ ልማት እቅድ ጋር ተቀናጅቶ ለመስራት በርካታ ጥረቶች ተደርገዋል እየተከናወኑም
ይገኛሉ፡፡

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የሚያስገነባቸው ኢንዱስትሪ ፓርኮች በሙሉ አቅማቸው ወደ ሥራ ሲገቡ
በውስጣቸው የደንበኞችን ፍላጎት ለማርካት የሚያስፈልጉ ሁሉም ዓይነት አገልግሎቶች በአንድ ቦታ የተሞሉላቸው ናቸው።
እነዚህም የኢንዱስትሪ ፓርኮቹ የኃይል ማከፋፈያ፣ የቆሻሻ ማከሚያ፣ የንግድና የመኖሪያ ቤቶች፣ የጤና ጣቢያዎች፣ፍቃድ
ሰነድና የታክስ መለያ መስጫ፣የጉምሩክ ክሊራንስ እና የባንክ አገልግሎቶችን፣ የእሳት አደጋ መከላከያ እና የጸጥታ
አገልግሎቶችን ያካትታል።

አምራች ኢንደስትሪዎች በተፈለገዉ ልክ የሀገርን ምጣኔ-ሀብት እንዲደግፋ እና አትራፊ እንዲሆኑ የተመቻቸ የሰላም ሁኔታ
እና ጥሩ የገበያ ትስስር ያስፈልጋል፡፡ ሀገራችን ኢትየጵያም በገጠማት ፈታኝ የምጣኔ ሀብትና አንዳንድ የውስጥ
አለመረጋጋቶች የውጭ ሀገራት ተፅዕኖና የኮሮና ወረርሺኝ የኢንዱስትሪ ዘርፉ አንዱና ዋነኛው ተጎጂ ዘርፍ
ቢሆንም የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ፓርኮቹ የራሳቸዉን የተለያዩ
ወጪዎችን በራሳቸዉ የሚሸፍኑበትን መንገድ በማመቻቸት እና አላስፈላጊ ወጪዎችን በመቀነስ እንዲሁም የተለያዩ
የገበያ አማራጮችንን ለባለሃብቶች በማፈላላግ በችግር ዉስጥም ቢሆን ትርፍ ማምጣት ችሏል፡፡

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ባለፉት ሰባት አመታት 13 ኢንዱስትሪ ፓርኮችን በማልማት ወደ ኦፕሬሽን
ለማስተላለፍ ችሏል፡፡ በሂደቱም ከ 78 ሺ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች ቀጥተኛ የስራ እድል መፍጠር የቻለ ሲሆን ከወጪ ንግድ
839.77 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ማግኘት ተችሏል ይህና ሌሎች በዚህ ሰነድ ያልተጠቀሱ የኮርፖሬሽኑ ስኬቶች ሃገራችን
ኢትዮጵያን በቅርብ ጊዜ የአፍሪካ የማኑፋክቸሪንግ ማዕከል ያደርጋታል።

ሃገራዊ ሁኔታን በሚመለከት በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል የተከሰተው ጦርነት በፓርክ ልማትና አስተዳደር ስራ፣
በውጭ ቀጥተኛ መዋዕለ ንዋይ ፍሰት እንዲሁም በኮርፖሬሽመኑ ፓርኮች ላይ የበኩሉን ተጽዕኖ የሚያሳድር
ከመሆኑም በላይ በተጨባጭ በኮርፖሬሽኑ ንብረት ላይ የመውደም ያጋጠመ ሲሆን ይህንን ሁኔታ ለመቀልበስ
በሚያስችል አግባብ በፓርክ ውስጥ ገብተው እያለሙ ለሚገኙ ባለሃብቶች ልዩ ልዩ ድጋፎችን በማድረግ
ባለሐብቶች በሙሉ አቅማቸው ማምረት እንዲችሉ ማድረግ ይገባል፡፡

ከዚህ ጋር ተያይዞ አንጻራዊ ሰላም ባለባቸው ፓርኮች ውስጥ ከፍተኛ የመዋዕለ ንዋይ ፍሰት እንዲኖር በትኩረት
መስራት፣ ሁሉንም የኮርፖሬሽኑን ሼዶችና የለማ መሬት በሙሉ አቅም ማስያዝ እንዲቻል ማድረግ ተገቢ
ይሆናል፡፡ከአሁናዊ ሃገራዊ ሁኔታ ጋር በተገናኘ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ላይ ጥቃት እንዳይደረስ አስፈላጊውን
የአደጋ መከላከል ስራ በመስራትና በፓርክ ውስጥ ያሉ ባለሃብቶች በሙሉ አቅማቸው በልዩ ትኩረት
እንዲያመርቱ ለማድረግ በቂ ጥበቃና የፓርክ ደህንነት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ይደረጋል፡፡

በኮርፖሬሽኑ ኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት አስተዳደር ላይ የይገባኛል ጥያቄ የሚያሳድረው የስራ መጓተት
በኮርፖሬሽኑ ውጤታማነትና ተወዳዳሪነት ላይ ከፍተኛ ጫና የሚያሳድር በመሆኑ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ
11
አካላት ጋር ጠንካራ ግንኙነት የሚፈጠርበትን አሠራር የሚዘረጋ ሲሆን ይህንንም እውን ለማድረግ የባለድርሻ
አካላት የግንኙነት አግባብ የሚመራበት ስልት ተዘጋጅቶ ይሰራል፡፡ በሌላ በኩል በዓለም አቀፍ ደረጃ የኮሮና
ቫይርስ ተጽዕኖ በኢንዱስትሪ ፓርክ ልማትና አስተዳደር ስራ ላይ የበኩሉን ማህበራዊ ተጽዕኖ ያሳደረ ሲሆን
በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ለሚሰሩ ባለሃብቶች የብቁ ሰራተኞች አቅርቦት ችግር ብሎም በፓርኮች ውስጥ
ባሉ ሠራተኞችና ባለሃብቶች መካከል የሚፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት እንዲቻል ብሎም
የባለሐብቶችን ጥያቄ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት እንዲቻል የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሠጣጥ እንዲያድግ
ይደረጋል፡፡

ኮርፖሬሽኑ ለኢኮ-ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚሰራ በመሆኑ ከተፈጥሮ ካባቢና ፓርክ በሚለማበት አካባቢ ከሚገኝ
ማህበረሰብ ጋር ተስማሚ እንዲሆን ተደርጎ የሚሠራ ይሆናል፡፡ በዚህም ኮርፖሬሽኑ በሚያለማቸውና
በሚያስተዳድራቸው ፓርኮች ቀጣነት ያለው አረንጓዴ ኢንዱስትሪ ልማት ለማካሄድ እንዲቻል በደረቅና ፈሳሽ
ማጣሪያ ስራ ላይ ከፍተኛ መዋለ ንዋይ በማፍሰስ ከማህበራዊና ተፈጥሯአዊ ከባቢ ጋር ተስማሚ የሆነ የፓርክ
ልማት ስራ እንዲከናወን ይደረጋል፡፡

በሌላ በኩል አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ዓለም በደረሰበት የቴክኖሎጅ ዓቅም መራመድ የኮርፖሬሽኑን
ተወዳዳሪነትና ተመራጭነት ለማሳደግ ከማገዙም በላይ የኮርፖሬሽኑን አገልግሎት በዘመናዊ አሠራር ታግዞ
በማቀላጠፍ አጠቃላይ የኮርፖሬሽኑን የመረጃ አያያዝና አስተዳደር እንዲሁም የመዋዕለ ንዋይ ፍሰቱን
በቴክኖሎጅ ታግዞ መስራት አስፈላጊ ነው፡፡

ከዚህ በላይ የተጠቀሱትን አሁናዊ ነባራዊ ሁኔታዎች በመቋቋም ኮርፖሬሽኑ ለጠቅላላ ሃገራዊ ምርት (GDP)
ተኪ ምርት በማምረት ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡ በዚህም መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር እንዲመጣ
ከማድረግም ባሻገር እንደ ሃገር በዓለም አቀፍ ደረጃ በኢንዱስትሪ ግብዓት ዙሪያ እያጋጠመ ያለውን እጥረት
በመሸፈን ረገድ መልካም ስራዎችን በመስራት ላይ ነው፡፡

በሌላ በኩል በኮርፖሬሽኑ ፓርክ ልማትና አስተዳደር እንቅስቃሴ ውስጥ አዳዲስ የኢንዱስትሪ ከተሞች
እየተገነቡ ከተሜነት እንዲስፋፋ ከማገዙም በላይ የስራ እድል ፈጠራን በማሳደግ የዜጎች ኢኮኖሚያዊ
ተጠቃሚነት እንዲያድግ፣ የውጭ ምንዛሬ ጫና እንዲቀንስ በማድረግ ብሎም የቴክኖሎጅ ሽግግርን እውን
በማድረግ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው፡፡ በዚህም ኮርፖሬሽኑ ምርጥ አልሚና አስተዳዳሪ ለመሆን እየሰራ ያለ
የመንግስት የልማት ድርጅት ነው፡፡

12
3. የዋና ዋና ግቦች ዒላማዎች አፈፃፀም
ግብ 1፡ የሀገራዊ ኢንዱስትሪያል ፓርኮች ስፓሻል ማስተር ፕላንን መሰረት ባደረገ መልኩ የኢንዱስትሪያል ፓርኮች
ልማትን ማፋጠን፤
በኢንዱስትሪ ፓርኮች ያልተጠናቀቁ ግንባታዎችን ማጠናቀቅ

በበጀት ዓመቱ በተለያዩ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የማስተካከያ ስራዎችን ለማከናወን ታቅዶ የነበረ ሲሆን
አፈጻጸማቸው እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

የሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክ የውሃና ፍሳሽ ማጣሪያ ሲቪል ስራዎች አንዲሁም ሌሎች በፓርኩ ውስጥ መጠናቀቅ
የሚገባቸው እና ማስተካከያ የሚያስፈልጋቸው ስራዎች በአሁኑ ወቅት ያሉበትን ደረጃ የውሃና ፍሳሽ ማጣሪያ
ሲቪል ስራዎች ጋር በተገናኘ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ገጠማ ስራ ለማከናወን የሚያስችል የግንባታ እቃዎችን ከቀረጥ
ነጻ ተጠቃሚነት ጋር በተያያዘ የነበሩ ችግሮች የተፈቱ በመሆናቸው ስራ ተቋራጩ በቅርቡ ወደ ሳይት ተመልሶ በነፋስ
ምክንያት የተጎዱ ሼዶችን የመጠገን እንዲሁም የፍሳሽ ማጣሪያ ቀሪ ስራዎች የመሳሰለሉትን በማከናወን ላይ
ይገኛል፡፡ በአጠቃላይ በበጀት አመቱ 10.6% ለማከናወን ታቅዶ 3.35% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙ ሲታይ 31.6%
ይሆናል፡፡ ለአፈፃፀም ማነስ ምክንያት ከሚጠቀሱት አንዱ ከቀረጥ ነፃ ገቢ የእቃዎች መዘግየት እንዲሁም ከወቅታዊ
ሃገራዊ የፀጥታ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ረዘም ላሉ ወራት ስራ ተቋራጩ በሳይት ላይ ተመልሶ ሥራዉን ማከናወን
ያልቻለ በመሆኑ ነው፡፡

በሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የፍሳሽና ውሃ ማጣሪያዎች የእርማትና ማስተካከያ እንዲሁም የአጠቃላይ የፓርኩን
ደህንነት በተሟላ ሁኔታ መጠበቅ የሚያስችል የ CCTV እና ተያያዥ ስራዎች ሙሉ ለሙሉ ተጠናቀው የርክክብ
ሂደቱ ተፈጻሚ ሆኗል፡፡ የፍሳሽ ማጣሪያ (ZLD) ማስተካከያ ስራዎችን በተመለከተ አማካሪውንና ስራ ተቋራጩን
ያካተተ የፍሳሽ ማጣሪያ ውጤታማነት እንዲከታተል በተቋቋመው ቡድን አማካኝነት ቀደም ሲል የተያዙ ስራዎች
ኮንትራቱ በሚፈቅደው አግባብ መሰረት የማስተካከያ ስራዎቹ ተግባራዊ እየተደረጉ ይገኛሉ፡፡ የማስተካከያ ስራዎቹ
የደረሱበት ደረጃ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት በጥልቀት በሳይት ላይ የተገመገመ ሲሆን በቀጣይ
የጊዜ ገደብ በማስቀመጥ ወደ ትግበራ ለመግባት ክትትል በመደረግ ላይ ይገኛል፡፡ በውሃ ማጣሪያው ላይ ያሉ
ችግሮችን ለመፍታት እንዲያስችል ከተለያዩ የስራ ክፍሎች ባለሙያዎችን ያካተተ ኮሚቴ ተቋቁሞ ሪፖርት የቀረበ
ሲሆን በዚሁ መሰረት ለአማካሪው ተልኮ አማካሪው በስራ ተቋራጩ በኩል ምላሸ እንዲሰጥበት የተጠየቀ ቢሆንም
እስካሁን በስራ ተቋራጩ የቀረበ ምላሽ የለም ሆኖም ግን በአማካሪው በኩል ጥቂት ማስተካከያ በማድረግ አሁን
ያለውን ውሃ ማጣሪያ አገልግሎት እንዲሰጥ ማድረግ እንደሚቻል በተሰጠው ምክረ ሃሳብ መሰረት ለስራ ተቋራጩ
ትእዛዝ የተሰጠ በመሆኑ በዚሁ ላይ ጥብቅ ክትትል ማድረግ ይህ የማይሳካ ከሆነ ከውለታው ላይ ተገቢው ገንዘብ
ተቀናሽ የሚደረግ ይሆናል፡፡ በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ ውስጥ ሥራውን 100% ለማከናወን ታቅዶ 45% ተከናውኗል፡፡
ለአፈፃፀሙ ማነስ ምክንያት የማስተካከያ ሥራዎቹን ተቋራጩ በኩል በሚፈለገው ፍጥነት አለመከናወኑ ነው፡፡

በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርከ ከፍሳሽ ማጣሪያ ፣ Electric Fence & CCTV Camera ገጠማ፣ የጎርፍ መከላከያ እና
ተያያዥ ስራዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ መጠናቀቅ የሚገባቸው እንዲሁም የማስተካከያ እና የእርማት ስራ
13
የሚያስፈልጋቸው ስራዎች በተቋራጩ ሥራ መዘግየት ነው፡፡ የፍሳሽ ማጣሪያውን ቀሪ ስራዎችን የማጠናቀቅ እና
የ Test እና Commisioning ስራ ፣ የሎሪ ፓርኪንግ ፤ የጎርፍ መውረጃ ትቦ (የቦክስ ከልቨርት) ፣ ሁለት ቦታዎች ላይ
አጥር የመዝጋት ስራ፣ የጥበቃ ቤት አንዲሁም የክሊኒክ ቆሻሻ ማቃጠያ ቦታ ግንባታ ተጠናቋል፡፡ STP ቴስት እና
ኮሚሽኒንግ ሂደት የተጠናቆ ኦፕሬሽን ተጀመረ ሲሆን የርክክብ ሂደቱን ለማከናወን የማስተካከያ ስራዎች ዝርዝር
ለቀማ ስራ በተቋቋመው ኮሚቴ አማካኝነት ተጠናቋል፡፡በአሁኑ ወቅት የ ETP test and commissioning ስራ
ተጀምሯል ከዚህም ጋር ተያይዞ ወደ ማህበረሰቡ ይለቀቅ ነበረውን ፍሳሽ ማስቆም ተችሏል፡፡ ስለሆነም ኮንተራክተሩ
ስራውን በሚፈለገው ፍጥነት እንዲያጠናቅቅ በቀጣይ ጥብቅ ክትትል የሚደረግ ይሆናል፡፡ Electric Fence & CCTV
Camera ገጠማ ስራን በተመለከተ ከውጭ ከሚገቡ የግንባታ እቃዎች ጋር በተያያዘ የነበረው ችግር መፍትሄ ያገኘ
በመሆኑ በቀጣይ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል በዚህም በበጀት ዓመቱ 100% ለማከናወን ታቅዶ
56.5% ተከናውኗል፡፡ ለአፈፃፀም ማነስ የስራ ተቋራጩ ደካማ አፈፃፀም አንዲሁም የስራ መጓተትና ከውጭ የሚገቡ
የግንባታ እቃዎች በወቅቱ አለመድረስ በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

የድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክን በተመለከተ የፍሳሽ ማጣሪያ ቀሪ ስራ፣ የ CCTV ገጠማና የአስፋልት መንገድ
ማስተካከያ እንዲሁም የጊዜያዊ ውሃ አቅርቦት ግንባታ ስራዎች በበጀት አመቱ ትኩረት ተሰጥቶ ክትትል
ከሚደረግባቸው ስራዎች በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ በዚህም መሰረት ከፕሮጀክቱ አፈጻጸም ጋር በተያያዘ
በፕሮጀክቱ በመገኘት አፈጻጸሙ የተገመገመ ሲሆን የአስፓልት የማስተካከያ ስራ እንዲሁም የአውቶብስ ማቆሚያ
ስራው ከጥቂት ማስተካከያ ስራዎች በስተቀር የተጠናቀቀ ሲሆን የሮድ ማርኪንግ እና አንዳንድ የማጠቃለያ ስራዎች
ብቻ ይቀራሉ፡፡ የዘላቂ ውሃ አቅርቦት ግንባታ ጋር ተያይዞ የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ እንዲሁም የፓይፕ ዝርጋታ ስራ
የተከናወነ እና በስራ ተቋራጩ በኩል የቴስት ስራ በመከናወን ላይ በመሆኑ በቅርቡ ለፓርኩ ውሃ ማድረስ የሚቻልበት
ሁኔታ ላይ ይገኛል፡፡ የ CCTV ገጠማ እና የፍሳሽ ማጣሪያ ቀሪ ስራዎችን በተመለከተ ከስራ ተቋራጩ ጋር ክፍያን
በተመለከተ የነበረው ተመሳሳይ ጥያቄ ምለሽ ያገኘ በመሆኑ ቀሪ ስራዎቹን ለማጠናቀቅ ጥብቅ ክትትል በመደረግ
ላይ ይገኛል፡፡ ሆኖም ግን በቅርቡ አማካሪው በተገኘበት አጠቃላይ ቀሪ ስራዎቹን የማጠናቀቅ ሂደትን በተመለከተ
በተደረገ ውይይት ለስራ ተቋራጩ በጊዜ ገደብ ስራውን እንዲያጠናቅቅ ማሳሰቢያ ተሰጠው ሲሆን ይህ የማይሳካ
ከሆነ ግን ወደ ቀጣይ እርምጃ የሚገባ መሆኑን መግባባታ ላይ ተደርሷል፡፡ በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ 100%
ለማከናወን ታቅዶ የነበረ ሲሆን 52% ተከናውኗል አፈፃፀሙ ሲታይ 52% ይሆናል፡፡ ለአፈፃፀም ማነስ የስራ ተቋራጩ
ደካማ አፈፃፀም አንዲሁም የስራ መጓተትና ከውጭ የሚገቡ የግንባታ እቃዎች በወቅቱ አለመድረስ በዋናነት
የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

የደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ የጎርፍ መከላከያ ስራን በተመለከተ አማካሪው በተገኘበት ከስራ ተቋራጩ ጋር
በተደረገው ውይይት መሰረት በስራ በስራ ተቋራጩ የሚሰራውን የማስተካከያ ዲዛይን በአጭር ጊዜ ውስጥ
እንዲጠናቀቅ አቅጣጫ በተቀመጠው መሰረት ስራ ተቋራጩ የዲዛይን ማስተካከያ ስራውን አጠናቆ የግንባታ
ስራውን ጀምሯል፡፡ የ CCTV እና የዋና በር week electric system ማስተካከያ ስራን ለማጠናቀቅ ከውጭ ለግንባታ
የሚገቡ እቃዎች ጋር ተያይዞ ያለው ችግር የተፈታ በመሆኑ በቀጣይ ቀሪ ስራው የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡ በአጠቃላይ
በበጀት ዓመቱ ውስጥ 100% ለማከናወን ታቅዶ 86.5% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙ ሲታይ 86.5% ይሆናል፡፡ለአፈፃፀም
14
ማነስ የስራ ተቋራጩ ደካማ አፈፃፀም አንዲሁም ከውጭ የሚገቡ የግንባታ እቃዎች በወቅቱ አለመድረስ በዋናነት
የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

በባህርዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ አብዛኛው የግንባታ ሥራዎች በዕቅዱ መሠረት የተከናወኑና የተሻለ አፈፃፀም ያለው
ፓርክ ሲሆን በበበጀት ዓመቱ የአንድ ማዕከል አገለግሎት ህንፃ የአጥር ግንባታው ተጠናቋል፡፡ እንዲሁም ከ CCTV እና
የዋና መንገዶች ግንባታ ጋር የተያያዙ መጠነኛ የእርማትና የማስተካከያ ሥራዎች የተሰሩ ሲሆን በቀጣይ
የማስተካከያ ስራዎቹን በማጠናቀቅ ወደ ርክክብ የሚገባ ይሆናል፡፡

የደብረ ብርሃን እና ባህር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርኮች ፍሳሽ ማጣሪያ ግንባታን በተመለከተ ስራው በሚጠበቀው ፍጥነት
ማከናወን ያልተቻለ ሲሆን ለዚህም እንደ ዋና ምክንያት ሆኖ ሲቀርብ የነበረውን በፍላጎት መግለጫው ውስጥ ተካቶ
የነበረውን BOQ(የግንባታ ዝርዝር መስፈርት የያዘ ሰነድ) ችግር ለመፍታት የተቋቋመው ኮሚቴ ባቀረበው የውሳኔ
ሃሳብ መሰረት የማሻሻያ ውል የተፈረመ ቢሆንም የቅድመ ክፍያ ዋስትና ማስያዣ ሥራ ተቋራጩ በውሉ መሰረት
ማስያዝ ያለመቻሉን ተከትሎ የውል ማሻሻያ ለማድረግ ጥረት የተደረገ ቢሆንም ከውል አንፃር የሚያስኬድ ሆኖ
ባለመገኘቱ ቅድመ ክፍያ ያልተከፈለ መሆኑ ስራ ተቋራጩ ከሚያነሳው የፋይናንስ እጥረት ጋር ተያይዞ አሁንም
ድረስ ስራውን በሚፈለገው ፍጥነት ላለመከናወኑ ምክንያት ሆኑአል፡፡ በዚህም ያለው አፈጻጸም ከግንባታ ጊዜው
አንጻር ሲታይ በጣም ዝቅተኛ የሚባል ነው፡፡ ይህንንም ተከትሎ ከስራ ተቋራጩ ጋር ውይይት ተደርጎ ስራ ተቋራጩ
ያሉበትን ችግር እንዲፈታ እና ውሉ በሚጠይቀው መሰረት የቅድመ ክፍያ ዋስትናውን በማስገባት ስራውን
በሚፈለገው ፍጥነት እንዲያከናውን ለማድረግ በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል፡፡ በሁለቱም(የደብረ ብርሃን እና ባህር ዳር )
ኢንዱስትሪ ፓርኮች የበፈር፣ የፕሪ ትሪትመንትታንክ፣ የተጣራ ውሃ ማጠራቀሚያ እንዲሁም አብዛኛው የኮንክሪት
ስራ የተጀመረበት ሁኔታ ይታያል፡፡ በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ ውስጥ በባህር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ 70% ለማከናወን
ታቅዶ 15.01% የተከናወነ ሲሆን በደብረብርሃንም በተመሳሳይ 70% ታቅዶ 13.3% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙ ሲታይ
ለባህርዳር 15.01% ሲሆን ደብረብርሃን ደግሞ 13.8% ይሆናል፡፡ ለአፈፃፀም ማነስ የስራ ተቋራጩ ደካማ አፈፃፀም
ስራውን በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ ያለው ተነሳሽነት በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

የኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ ፍሳሽ ማጣሪያ ግንባታን በተመለከተ በበጀት ዓመቱ 50% ለማከናወን ታቅዶ የነበረ
ቢሆንም ስራውን በተያዘለት ጊዜ ማከናወን አልተቻለም፡፡ ለዚህም እንደ ዋና ምክንያት የሚጠቀሰው ሥራ
ተቋራጩ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ አለመግባቱ እንዲሁም የዲዛይን ሥራውን አለማጠናቀቁ ሲሆን ከወቅታዊ ሃገራዊ
ችግር ጋር በተያያዘም ስራ ተቋራጩ ስራ አቆሞ የነበረ መሆኑ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡በአሁኑ ወቅት በዋናነት የቅድመ
ክፍያ ዋስትና ማስያዣ ሥራ ተቋራጩ በውሉ መሰረት ማስያዝ ያለመቻሉን ተከትሎ የውል ማሻሻያ ለማድረግ
ጥረት የተደረገ ቢሆንም ከውል አንፃር የሚያስኬድ ሆኖ ባለመገኘቱ ቅድመ ክፍያ ያልተከፈለ መሆኑ ከፋይናንስ
እጥረት ጋር ተያይዞ አሁንም ድረስ ስራ ተቋራጩ ስራውን በሚፈለገው ፍጥነት እንዳያከናውን ምክንያት ሆኑአል፡፡
በዚህም ምክንያት ያለው አፈጻጸም ከግንባታ ጊዜው አንጻር ሲታይ በጣም ዝቅተኛ የሚባል ነው፡፡ ይህንንም ተከትሎ
ስራ ተቋራጩ ያሉበትን ችግሮች እንዲፈታ እና ውሉ በሚጠይቀው መሰረት ዋስትና እንዲያስይዝ እና ስራውን
በሚፈለገው ፍጥነት እንዲያከናውን ተደጋጋሚ የሆነ የስራ ትእዛዝ የተሰጠው ሲሆን በአሁኑ ወቅትም በአማካሪው
15
እንዲሁም በኮርፖሬሽኑ በኩል የመጀመሪያ የስራ መዘግየት የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እንዲደርሰው ተደርጓል፡፡ይህንኑ
ተከትሎ በቀጣይ ውል ወደ ማቋረጥ የሚገባ ይሆናል፡፡

የኮምቦልቻ እና ጅማ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን የመጨረሻ ርክክብ ማድረግ በተመለከተ ስራ ተቋራጩ ቀሪ


የማስተካከያ ስራዎቹን ባለማጠናቀቁ ያልተከናወነ በመሆኑ በእቅድ ክለሳ ወቅት ማሻሻያ ተደርጎበት
ደብረብርሃንንም ጨምሮ በአመቱ መጨረሻ ላይ እንዲከናወን የተወሰነ ሲሆን በዚህም የጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክ
የመጨረሻ ርክክብ እንዲደረግ በአማካሪው በኩል ጥያቄ ተጠይቋል፡፡ ነገር ግን አሁንም በፓርኩ ውስጥ ያልተጠናቀቁ
ስራዎች በመኖራቸውን አማካሪው እንዲያውቀው ተደርጓል፡፡በቀጣይ አስፈላጊው ማስተካከያ እነዲደረግ በማድረግ
ርክክቡ የሚከናወን ይሆናል፡፡

የአዲስ ኢንዱስትሪ ፓርክ የአጥር እና የዋና በር ግንባታን በተመለከተ በበጀት ዓመቱ 100% ለማከናወን የታቀደ ሲሆን
80.75% ተከናውኗል፡፡አፈፃፀሙ ሲታይ 80.75% ሲሆን የተጨማሪ ስራ ጥያቄው የፀደቀ በመሆኑ ስራ ተቋራጩ
በቀጣይ ቀሪ ስራዎቹን ለማጠናቀቅ ስራውን በሙሉ አቅሙ እንዲያከናውን ክትትል የሚደረግ ይሆናል፡፡ ለአፈፃፀሙ
ማነስ ያገጠመው የለውጥ ስራ እንደምክንያት የሚጠቀስ ነው፡፡

በቦሌ ለሚ ምዕራፍ ሁለት እና ቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን በተመለከተ በፓርኮቹ ያልተጠናቀቁ የግንባታና
ከመሰረተ ልማት ጋር የተያያዙ ስራዎች በኮሚቴ በጋራ ተለይተው ክትትል እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡ በዚህም በቦሌ
ለሚ 100% ታቅዶ 67% እንዲሁም በቂሊንጦ 100% ታቅዶ 79.5% ተከናውኗል አፈፃፀሙ ሲታይ በቅደም ተከተል
67% እና 79.5% ይሆናል፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በሁለቱ ኢንዱስትሪ ፓርኮች የፍሣሽ ማጣሪያን በተመለከተ ምንም
አይነት የማዘጋጃ ቤታዊና የኢንዱስትሪ ፍሣሽ ባለመኖሩ ምክንያት የፍተሻና ሙከራ ስራውን ለማከናወን አስቸጋሪ
አድርጎታል፡፡ ይህንን ለመፍታት እንዲቻል ከአዲስ አበባ ውሃና ፍሣሽ ባለሥልጣን ጋር የተጀመረውን የጋራ መግባቢያ
ስምምነት ማጠናቀቅ ትኩረት የሚፈልግ ስራ ሆኗል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የኤሌክትሪክ መስመርና ዕቃዎች እንዲሁም
የውሃ መስመርና ፓምፕ ስቴሽኖችን በተመለከተ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ዘላቂ ኤሌክትሪክ ሃይል ያልተገናኘ በመሆኑ
የርክክብ ሂደቱን ማከናወን ያልተቻለ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት የሙከራ እና ፍተሻ የሚያስፈልጋቸው ስራዎችን
በተመለከተ በውሉ መሰረት ለማከናወን በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ በአጠቃላይ ቀሪ እና የማስተካከያ ስራዎችን
በተመለከተ ርክክብ ለመፈፀም ይረዳ ዘንድ አጠቃላይ የስራውን ውጤታማነት አንዲገመግም የተቋቋመው ኮሚቴ
የተሰራውን ስራ፣ ቀሪ ስራዎቹ እንዲሁም ከውል ላይ የሚቀነሱ ስራዎች ተገምግመው የተጠናቀቁ ሲሆን ይህንኑ
ተግባራዊ ለማድረግ ተደጋጋሚ ውይይቶች በማድረግ በአጭር ጊዜ ውስጥ መፍትሄ እንዲያገኝ ጥብቅ ክትትል
እየተደረገበት ይገኛል፡፡

በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ ቀደም ሲል የተጀመሩ የግንባታ ሥራዎችን ማጠናቀቅን በተመለከተ
በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ 7% ለማከናወን ታቅዶ 5.2% ተፈጽሟል፡፡ አፈፃፀሙ ሲታይ 74.2% ይሆናል፡፡ ከዚህ
በተጨማሪ ግንባታቸዉ ተጠናቀዉ የማስተካከያ ስራ እና ርክክብ መፈጸም ከሚያስፈልጋቸዉ ፕሮጀክቶች ዉስጥ የ
G+2 Business Incubation ceneter ህንጻ የመጀመሪያ ደረጃ ርክክብን መፈጸም ተችሏል፡፡ ከተያዙት የግንባታ ዕቅዶች

16
መካከል የፓርኩን ወሰን ለማስከበር የሚያስችል አጥር ለመገንባት ከይገባኛል ነፃ በሆኑ ቦታዎች ላይ 3 ኪ.ሜ የሚጠጋ
ቦታ ላይ የአጥር ስራዉ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ርክክብ የተፈጸመ ሲሆን አስፈላጊ በሆኑ ቦታዎች ላይ ጥበቃ ማማዎች
እንዲገነቡ ተደርጓል፡፡ በተጨማሪም በቀሪ ቦታዎች ላይ የኮንክሪት ፖል የማቆም ስራ የተከናወነ ቢሆንም በአካባቢዉ
ባለዉ የጸጥታ ችግር እንዲሁም ስራ ተቋራጩ ለአጥር ግንባታ የሚያስፈልገዉን ማቴሪያል አቅርቦ ግንባታዉን
ባለማከናወኑ ምክንያት የአፈጻጸም ማነስ ተስተዉሏል፡፡ የኢንኩቤሽን ሴንተር ህንጻን ግንባታ የሲቪል ስራ መሰረታዊ
በሚባል ደረጃ የተጠናቀቀ ቢሆንም የህንጻዉን የመጀመሪያ ደረጃ ርክክብ ለመፈጸም የሚያስፈልጉ የመብራት፤ ዉሃ
እና ዳታ ኔትወርኪንግ ስራዎች ከማጠናቀቅ አንጻር የስራ ተቋራጩ አፈጻጸም ማነስ ታይቶበት የነበረ በመሆኑ ውል
ለማቋረጥ የአንድ ወር ውል ማቋረጥን የተመለከተ ማሳሰቢያ በተሰጠው መሰረት ወደ ስራ የገባ ሲሆን በስራ
ተቋራጩ ጥያቄ መሰረትም የ 21 ቀን ማራዘሚያ ተሠጥቶት ስራውን ከማጠናቀቅ አንፃር የተሻለ አፈፃፀም ያሳየ
ሲሆን የ MCIT Head Quarter ህንጻን በተመለከተ ለስራ ተቋራጩ ተመሳሳይ ውል ለማቋረጥ የአንድ ወር ውል
ማቋረጥን የተመለከተ ማሳሰቢያ ተሰጥቶት የነበረ ቢሆንም ስራውን በተሠጠው የጊዜ ገደብ ማከናወን ባለመቻሉ
ውሉ ተቋርጧል፡፡

በ ICT ፓርክ የመሠረተ ልማት ግንባታና ላንድስኬፒንግ ስራዎችን ለማከናወን የግዥ ሂደት ላይ የነበረ ሲሆን
የቴክኒካል ግምገማው እንዲሁም የዋጋ ጥናቱ በኮሚቴ ተሰርቶ/ተጠንቶ ሪፖርት ቀርቧል፡፡ሆኖም ግን እስካሁን የግዥ
ሂደቱ ባለመጠናቁ እና ውል ያልተገባ በመሆኑ ስራውን በተያዘለት እቅድ መሰረት ማከናወን አልተቻለም፡፡

የቦሌ ለሚ አንድ ኢንዱስትሪ ፓርክ ቀሪ ያልተጠናቀቀ የአጥር ስራ ለማከናወን 38% ዕቅድ ተይዞ 8% የተከናወነ
ሲሆን አፈፃፀሙም 21.05% ነዉ፡፡ ለአፈፃፀም ማነስ እንደዋና ምክንያት የሚጠቀሰዉ የወሰን ማስከበር ችግር
መፍትሄ ላይ ባለመደረሱ ነዉ፡፡ ስለሆነም ችግሩን ለመቅረፍ ካሳ የተከፈላቸዉን ዝርዝር መረጃ ከክፍለ ከተማ
አደራጅቶ ለመያዝ እና ወሰን የማስከበር ስራ ለማከናወን በወረዳው በኩል ኮሚቴ ተዋቅሮ ብዙ ጥረቶች ቢደረጉም
መፍትሄ ላይ ባለመደረሱ ስራዉ በተደጋጋሚ በመስተጓጎሉ ነዉ፡፡ በቀጣይም ችግሩን ለመፍታት ከሚመለከታቸዉ ጋር
ጥረት የሚደረግ ይሆናል፡፡ በሌላ በኩል ግንባታቸውን ለሚጀምሩ አዳዲስ ኢንዱስትሪ ፓርኮች የተለያዩ የዝግጅት
ስራዎች ለማከናወን በተያዘዉ ዕቅድ መሰረት ለአይሻ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚደረገዉን የዉሃ አቅርቦት በተመለከተ
ከዚህ በፊት የተደረገዉን የሃይድሮሎጂካል ጥናት መነሻ በማድረግ የዉሃ አቅርቦት ስራዉ በምን መልኩ መከናወን
እንዳለበት የሚያሳይ ረቅቅ ሰነድ ተዘጋጅቶ በዋና ስራ አስፈፃሚ በኩል ዉሳኔ እንዲሰጥበት ቀርቧል፡፡ ለዚህም
አፈፃፀሙም 100% ነዉ፡፡

ለኢንዱስትሪ ፓርኮች መሬት ዝግጅት ከክልልና ከተሞች ጋር ውይይት በማድረግ ስምምነት ላይ መድረስ እና ይዞታ
የማስጠበቅ ስራዎችን ማከናወን፤

የቦሌ ለሚ ምዕራፍ አንድ አጥር ግንባታ ስራ በይገባኛል ጥያቄ ምክንያት ያልታጠረ ቦታ ሳይት በመሄድ X, Y
Coordinate መረጃ ተሰብስቦ በፕላን የማመላከት ስራ ተሰርቷል፡፡ በዚህ መሰረት የአጥር ስራ ለማስቀጠል ካሳ ክፍያ
የተፈፀመበትን መረጃ ተጣርቶ እንዲሰጥ በሚል ለለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ደብዳቤ በተጠየቀው መሰረት ኢንዱስትሪ

17
ፓርክ ውስጥ ካሳ ክፍያ ቅሬታ ያላቸው ተሺዎች በተመለከተ የለሚ ኩራ/ወረዳ ከፍተኛ የሰራ ሀላፊዎች አመራሮች
እና የኮርፖሬሽኑ ሀላፊዎቸው እንዲሁም የአርሶ አደር ተወካዮች በተገኙበት ውይይት የተደረገ ሲሆን በዚህ መሰረት
ሰርተፍኬት ካላቸው መረጃ ተጣርቶ መስተናገድ እንደሚችሉ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ በዚህ መሰረት የካሳ ክፍያ
ሰርተፊኬት ያቀረቡ 70 የሚሆኑ የልማት ተነሺዎች ለሚ ኩራ ክ/ከተማ ለቦሌ ክ/ከተማ የካሳ ክፍያ መረጃ እንዲጣራ
በደብዳቤ በጠየቁት መሰረት ቦሌ ክፍለ ከተማ ፋይናንስ በአጠቃላይ ሰርተፊኬት ያቀረቡ 70 ተነሺዎች ውስጥ 46
ሰነዳቸው ወደ ፋይናንስ ያልተላከና ያልተከፈላቸው መሆኑን ለለሚ ኩራ ክ/ከተማ በደብዳቤ አሳውቀዋል ቀሪዎቹን
የማጣራት ስራ እንዲሰራ ክትትል እየተደረገ ነው፡፡

ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ በአዳማ ሁናን ኢንዱስትሪ ፓርክ 122 ሄክታር መሬት መረጃ እንዲያዝና ከክልሉ በጀት
እንዲያዝ ክትትል ማድረግ ስራን ለማከናወን ከከተማው ከንቲባ ጋር በተደረገው ውይይት ኮርፖሬሽኑ በቅድሚያ
በባዶ ቦታው ላይ ግንባታ ካልጀመረ የተነሺዎችን መረጃ ለመሰብሰብ እንደሚቸገሩ ገልፀዋል፤ በመሆኑም ቦታውን
በጊዜያዊ አጥር ለማሳጠር ጨረታ ወጥቶ ስራ ተቋራጭ ተለይቶ ውሉ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡

የመሰረተ ልማት መስመር ዝርጋታ የሚያልፍባቸው ቦታዎችን ወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ ቦሌ ለሚ ኢ/ፓርክ
የኤሌክትሪክ ሀይል ማሰራጫ ጣቢያ ይዞታ ውስጥ ያሉ ቤቶች ካሳ ክፍያ በድጋሚ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል
ከክፍለ ከተማው ጋር ተነጋግረው ክፍያ እንዲፈፅሙ በተወሰነው መሰረት የ 40 ተነሺዎች ካሳ ክፍያ ተፈፅሟል፡፡
የቀሪ 14 ተነሺዎችን አስመልክቶ ከይዞታቸው ውጪ መሆናቸውን በመግልፅ ለመክፈል እንደሚቸገሩ ለክፍለ
ከተማው አሳውቀዋል፡፡ ሆኖም የልማት ስራው መደናቀፍ ስለሌለበት ከመመሪያው አንፃር ለቀሪዎቹ ካሳ ክፍያው
ስለሚፈፀምበት ሁኔታ መግባባት ላይ በመድረስ ችግሩን ለመፍታት ክትትል እየተደረገ ነው፡፡

ለቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የኤሌክትሪክ መስመሩ የሚያለፍበት ከሀይል
ማሰራጫ ጣቢያ እስከ ፓርኩ ድረስ ቦታ ከይገባኛል ጥያቄ ነፃ ለማድረግ ኤሌክትሪክ መስመሩ የአዲስ አበባ ከተማ
መንገዶች ባለስልጠና በሚያስገነባው መንገድ ውስጥ እንዲካተት ተደረጎ ከመንገዱ ወጪ ያለው ቀሪ 500 ሜትር
ያህል የኤሌክትሪክ መስመር የሚያልፍበት ቦታ የልኬት ስራ ተከናውኖ የካሳ ግምት ክፍያውን ኮርፖሬሽናችን
እንዲከፍል ክፍለ ከተማው ባሳወቀው መሰረት ለተነሺዎቹ የካሳ ክፍያው እየተከናወነ ይገኛል፡፡

የቦሌ ለሚ ምዕራፍ አንድ የውሀ መስመር ዝርጋታ 600 ሜትር ካሳ ክፍያ እንዲፈጸም ለገንዘብ ሚኒስቴር ተጠይቆ
ብር 17,562,030.00 ተፈቅዶ ክፍያው ለቦሌ ክፍለ ከተማ በአካውንታቸው ገቢ በተደረገው መሰረት ክፍያ ለ 14 አርሶ
አደር ተነሺዎቸ ሙሉ በሙሉ ተከናውኖ የውሀ መስመር ዝርጋታ ስራው እየተከናወነ ይገኛል፡፡ በተጨማሪ ከቦሌ ለሚ
ዘላቂ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ በጥናት ከተለየው 1.5 ኪ.ሜ ውስጥ ከይዞታችን ውጪ የሚገኘው ይገባኛል
ጥያቄ ያለበት 500 ሜትር ቦታ በተመለከተ መስመሩ በ 8 ሜትር ስፋት ልኬት ቢጠናቀቅም ይዞታቸውን
የሚነካባቸው አርሶ አደሮች ሙሉ በሙሉ ይዞታቸው እንዲለካላቸው እና ካሳ እንዲከፈላቸው በሚል ጥያቄ
ባቀረቡት መሰረት ክፍለ ከተማው በተደጋጋሚ ከማህበረሰቡ ጋር ውይይት ቢያደርግም የማሳመን ስራ ባለመሳካቱ
ኮርፖሬሽኑ ልማቱ መደናቀፍ ስለሌለበትና ከ 8 ሜትር ውጪ የሚገኘውን ቦታንም ለልዩ ልዩ አገልግሎት መጠቀም

18
እንደሚቻል ግምት ውስጥ በማስገባት ካሳ ክፍያውን ለመፈፀም ስምምተታችን ለክፍለ ከተማው በደብዳቤ ተገልፆ
ለተነሺዎቹ የካሳ ክፍያው በኮርፖሬሽኑ በኩል እየተፈፀመ ይገኛል፡፡

በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ በ 7.5 ሄክታር መሬት በተገኘ ተለዋጭ መሬት ላይ የሚገኙ ነዋሪዎች ለካሳ ክፍያ
የሚሆን በጀት እንዲፈቀድ ክትትል ማድረግና ምትክ እንዲያገኙ ለማደረግ ክፍለ ከተማው ከዚህ ቀደም በተለዋጭ
መሬት ላይ ለሚገኙ ነዋሪዎች የካሳ ክፍያ እና ምትክ ቦታ የወሰዱት ባለይዞታዎች መረጃ በማጣራት ለቀሪ ተነሺዎች
የካሳ ክፍያ በጀት ለመያዝ እና ምትክ ቦታ ለማዘጋጀት ተግባር በተወሰነ ደረጃ የመረጃ ማጣራት ስራው ተጀምሯል፡፡
ነገር ግን የአመራሮች እና ባለሙያዎች በየጊዜው ስራው በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ አልተቻልም፡፡ በዚህም
መሠረት በበጀት ዓመቱ 100% ለማጠናቀቅ ታቅዶ 35% ተከናውኗል፡፡

በአሶሳ ከተማ ለኢንዱስትሪ ፓርክ የሚውል 100 ሄክታር ተለዋጭ መሬት በከተማ አስተዳደሩ በኩል ከማንኛውም
ይገባኛል ጥያቄ ነፃ ተደርጎ በቀጣይ ለሚከናወን የልማት ተግባር ዝግጁ ሆኗል፡፡ በዚህም መሠረት በበጀት ዓመቱ 100
ሄከታር ነፃ ለማድረግ ታቅዶ 100 ሄክታር ነፃ የተደረገ ሲሆን የዕቅዱ አፈፃፀም 100% ይሆናል፡፡

በኢንዱስትሪ ፓርኮች ለግል ኢንዱስትሪ ፓርክ አልሚና ኢንተርፕራይዞች ቦታ በማጥናት ርክክብ መፈፀም፤

ኮርፖሬሽኑ ባለማቸው ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ በማስተር ፕላኑና ሽንሻኖ ጥናት የለማ መሬት ለባለሀብቶች
ለመመደብ እንዲቻል በአስራ ሁለት ወራት የባለሀብቶች ጥያቄ በቀረበው መሰረት ለመስራት በዕቅድ ተይዞ በአይ ሲ
ቲ ፓርክ ለ 2 ባለሀብት፣ በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ ለ 3 ባለሀብት እንዲሁም በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ለ 2
ባለሀብት ቦታ የመመደብ ስራ የተከናወነ ሲሆን ይህም 100% አፈፃፀም አሳይቷል፡፡ በተጨማሪም ለአይ ሲ ቲ ፓርክ
በዘላቂነት የሚያገለግል 230 KV ሀይል ማከፋፈያ ጣቢያ የሚሆን 6 ሄክታር ቦታ በጥናት በመለየት በፕላን ፎርማት
ተዘጋጅቶ ወደ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል በደብዳቤ ተልኳል፡፡

ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ስፓሻል ፕላን ጥናት ሰነድ ወደ ተግባር እንዲገባ የዝግጅት ስራዎች ማጠናቀቅ፤

የአገራዊ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ስፓሻል ፕላን ጥናትን በተመለከተ በየክልሉ ላሉ 84 አመራሮች ግንዛቤ ማስጨበጫ
መድረክ ለመፍጠር እንዲቻል ዝርዝር ፕሮፖዛል ተዘጋጅቶ ስልጠናውን በማከናወን ከስልጠናው የሚገኙ ግብዓቶችን
ማካተትና ፕላኑ በሚመለከተው አካል እንዲጸድቅ ለማድረግ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም አሁን ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር
በተያያዘ እልተከናወነም፡፡ የአሰልጣኞች ስልጠና ለኮርፖሬሽኑ ሰራተኞች ተሰጥቶ በቀጣይ በየክልሉ በመሔድ
የግንዛቤ እና ስልጠና ለመስጠት ዝርዝር ፕሮግራም ተዘጋጅቷል፡፡ እንዲሁም ጥናቱን ለማስፈፀም እንዲቻል መነሻ
ሰነድ ለማዘጋጀ ታቅዶ የስፓሻል ፕላኑ ማስፈጸሚያ የአፈጻጸም ፕላን ረቂቅ ሰነድ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡

19
በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ መሠረት ልማት ማሟላት
ጊዜያዊ የኤሌክትሪክ ሀይል ማቅረብ

በኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ ካርቪኮ ለተባለው የግል አልሚ ተጨማሪ 16 ሜጋዋት ጊዜያዊ የኤሌክትሪክ ኃይል
ለማቅረብ በባለፈው የበጀት ዓመት 40% የኃይል አቅርቦት ስራው የተከናወነ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ የ Check Survey እና
285 የኮንክሪት ፖል መትከያ ጉድጓድ ቁፋሮ ስራዎች ተጠናቋል፡፡ ኮንክሪት ፖሎች ሳይት ላይ የደረሱ ሲሆን ከ 285
ኮንክሪት ፖሎች ውስጥ 272 ኮንክሪት ፖሎች ተተክለዋል፡፡ በተጨማሪም በ 145 ኮንክሪት ፖሎች ላይ cross arm
ገጠማ ስራ ተከናውኗል፡፡ በባለሐበቱ በኩል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባቀረበው ስፔሲፊኬሽን መሠረት
ከውጭ አገር ግዥ ተፈፅሞ የቀረቡ የ top pole accessories ሳይት ላይ ደርሰው፤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
በ top pole accessories ያቀረበውን አስተያየት መሰረት በማድረግ የማስተካከያ ስራው ተከናውኖ ርክክብ ተፈፅሟል፡፡
ለባለሀብቱ ተጨማሪ 16 ሜጋዋት ጊዜያዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የታቀደ ሲሆን በ 2014 በጀት ዓመት 60%
ክንውን እንዲኖረው ታቅዶ 50.22% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 83.7% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛ ምክንያቶች
የኮንክሪት ፖሎች ተከላ ለማከናወን የ ROW ችግር ፣በሀገሪቱ በነበረው ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ስራውን ለመፈፀም
አስቸጋሪ መሆን እንዲሁም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል ስራውን በፍጥነት አለመከናወኑ ነው፡፡

በቦሌ ለሚ ሁለት ኢንዱስትሪ ፓርክ ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል እስኪሟላ ድረስ ሻንግቴክስ ለተባለ የግል ባለሀብት 1.2
ሜጋዋት ጊዜያዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 927,749.36 የዋጋ ግምት ቀርቦ
ክፍያው ተከናውኗል፡፡ ባለሀብቱ ያቀረበውን ትራንስፎርመር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል ፍተሻ ስራ
ተከናውኖ የኤሌክትሪክ መስመሩ ኢነርጃይዝ ሆኗል፡፡ ለባለሀብቱም የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲቀርብ የታቀደ ቢሆንም
ከታቀደበት ጊዜ አስቀድሞ የተጠየቀው የኤሌክትሪክ ኃይል ቀርቧል፡፡ በበጀት ዓመቱ 100% ለማጠናቀቅ ታቅዶ 100%
ተፈፅሟል፡፡ ከዕቅዱ በፊት ስራው ሊከናወን የቻለበት ዋነኛው ምክንያት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር
በጉዳዩ ላይ ውይይትና ጥብቅ ክትትል በማድረግ ለባለሀብቱ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲቀርብ በመደረጉ ነው፡፡

የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ 10 ሜጋዋት ጊዚያዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማሟላት ኮንክሪት ፖሎች
ተመርተው ፍተሻና ሙከራ የተከናወነ ሲሆን ተጨማሪ 25 ኮንክሪት ፖሎች ተተክለዋል፡፡ በተተከሉ ኮንክሪት ፖሎች
ላይ Cros-arm እና Insulators ተገጥመዋል፡፡ 11 ኮንክሪት ፖሎች በሚተከሉበት ቦታ ላይ የ GPS ኮኦርዲኔት በመውሰድ
በካርታ ላይ ተመላክቷል፡፡ ይህ እደተጠበቀ ሆኖ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ቀሪ 11 ኮንክሪት ፖሎች ለመትከል
በይገባኛል ጥያቄ ምክንያት በሰብስቴሽኑ ውስጥ የሚገኘውን የካሳ ክፍያ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል
ባለመፈፀሙ የኮንክሪት ፖል ተከላ ስራው ሊከናወን አልቻለም፡፡ ለሚ ኩራ ክ/ከተማ በሰብስቴሸኑ የሚገኙ
ባለይዞታዎች መረጃ አደራጅቶ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያቀረበ ቢሆንም የቀረበው መረጃ መጀመርያ ከነበሩት
7 ባለይዞታዎች በአሁኑ ጊዜ ከ 40 በላይ ባለይዞታዎች መረጃ በመቅረቡ ምክንያት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
ክፍያውን መፈፀም እንደሚቸገር ገልፆ ጥናቱ በጋራ እንዲከናወን ለክ/ከተማው ጥያቄ አቅርቧል፡፡ በዚህም መሰረት
የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ኮሚቴ በማዋቀር ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለሙያ ጋር ውይይት በማድረግ ተጨማሪ
የሰነድ ማጣራት ስራ ለማከናወን መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የካሳ ክፍያው ከጊዜ ወደ
20
ጊዜ የሚያሳየውን ውስብስብነትና በኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ላይ እያሳደረ የሚገኘውን ጫና ግምት ውስጥ በማስገባት
ሰነድ ከቀረበላቸው ባለይዞታዎች ውስጥ ድርጅቱ የተሟላ ሰነድ ቀርቧል ብሎ ላመነባቸው 40 ባለይዞታዎች
ክፍያውን ፈፅሟል፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ ለሚ ኩራ ክ/ከተማ ቀደም ሲል ለሶፍሌት ኩባንያ ኤሌክትሪክ ማከፋፈያ
መስመር ለተተከለበት መሬት የተፈፀመ የካሳ ክፍያ ሰነድ እንዲቀርብለት በጠየቀው መሰረት መረጃው ቀርቦለታል፡፡
የኤሌክትሪክ መስመሩ ከ ICT ፓርክ አጥር ሊገነባ ወደ ታቀደው አዲስ ሰብስቴሽን እንዲራዘም ለኢትዮጵያ
ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጥያቄ ቀርቦ ለዚሁ ማራዘሚያ የዋጋ ግምቱ ተሰርቶ ከፍያ እንዲፈፀም ለኮርፖሬሽኑ
ቀርቧል፡፡ በ 2014 በጀት ዓመት በ 12 ወራት ውስጥ 23% ለማድረስ በተያዘው እቅድ መሰረት 14.8% ተከናውኗል፡፡
አፈፃፀሙም 64.4% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛ ምክንያቶቸ የኮንክሪት ፖሎችና ተያያዥ የኤሌክትሪክ ዕቃዎች
አቅርቦት መዘግየት፣ በ EEU በኩል የኤሌክትሪክ መስመሩ የሚዘረጋበት አቅጣጫ የተደረገ ተደጋጋሚ ለውጥ፣ የቅየሳ
መዘግየት እንደተጠበቁ ሆነው በዋነኛነት 11 ኮንክሪት ፖሎች ለመትከል በቦሌ አራብሳ ሰብስቴሽን ውስጥ የሚገኙ
ባለይዞታዎች በቅድሚያ የካሳ ክፍያ ካልተከፈለ ፖሎቹን ማስተከል እንደማይችሉ በመግለፃቸው እንዲሁም
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ክፍያውን በሚፈለገው ፍጥነት አለመፈፀሙ ናቸው፡፡

ለሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክ 10 ሜጋዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የመካከለኛ ቮልቴጅ ማከፋፈያ መስመር
ዝርጋታ፣ ፍተሻና ሙከራ ስራ ተጠናቋል:: በፓርኩ ውስጥ የኤሌክትሪክ ኬብል ዝርጋታ ስራ የተከናወነ ሲሆን
የሰብስቴሽን ወጪ ላይ የዕቃዎች ገጠማ፣ ፍተሻና ሙከራ ተከናውኗል፡፡ በፓርኩ ውስጥ የሚገኙት RMUs
ከመገጠማቸው በፊት በሀገር ውስጥ ፍተሻ ለማከናወን አማካሪ፣ ኮርፖሬሽኑ፣ የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ አገልግሎት
እና የስራ ተቋራጩ ባለሙያዎች በተገኙበት መካኒካል ፍተሻና ቪዥዋል ኢንስፔክሽን ተከናውኗል፡፡ በ 2014 በጀት
ዓመት 30% ክንውን እንዲኖረው ታቅዶ 20.5% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 68.33% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛ
ምክንያት በሀገሪቱ የነበረው የፀጥታ ችግርና በስራ ተቋራጩ በኩል ተርሚኔሽን ኪት ወደ ሀገር ውስጥ በሚፈለገው
ፍጥነት አለማስገባት እና ስራ ተቋራጩ በሼዶች ውስጥ ለሚገጠሙ ትራንስፎርመሮች በጸደቀው ቴክኒካል
ስፔሲፊኬሽን መሰረት ፋይናንሻል ፕሮፖዛል በሚጠበቀው ፍጥነት አለማቅረቡ ነው፡፡

ለአይሻ ኢንዱስትሪ ፓርክ ጊዜያዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የቅድመ ዝግጅት ስራ ለማከናወን በተያዘው ዕቅድ
መሰረት በኢትዮጵያ ኤሌሌትሪክ አገልግሎት በኩል የአዋጭነት ጥናት ተከናውኖ ሁለት አማራጮች ቀርበዋል፡፡
አንደኛው አማራጭ ከአይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ውስጥ 120 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው ሲሆን
በማመንጫው ውስጥ ባለ 230/33 KV ፓወር ትራንስፎርመር፤ ስዊችጊር እና ተዛማጅ የማስፋፊያ ስራዎችን
በማከናወን መጠቀም እንደሚቻልና ምንም ጭነት ያልጫነ እና በኮሚሽኒንግ ላይ ያለ ሲሆን ከፓርኩ በ 14 ኪ.ሜ
ርቀት ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ሁለተኛው አማራጭ ከአይሻ የባቡር ትራክሽን ሰብስቴሽን ጣቢያ ውስጥ 230/33 KV ፓወር
ትራንስፎርመር፤ ስዊችጊር እና ተዛማጅ የማስፋፊያ ስራዎችን በማከናወን አሁን ባለው ሁኔታ እስከ 176 ሜጋዋት
መጫን እንደሚቻል የሚታሰብ ሲሆን ከፓርኩ በ 18 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ከቴክኒካል አዋጭነት አንጻር
አማራጭ አንድ ተመራጭ ነው፡፡ በ 2014 በጀት ዓመት 20% ክንውን እንዲኖረው ታቅዶ 20% ተከናውኗል፡፡
አፈፃፀሙም 100% ነው፡፡

21
ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት፤

የሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዘላቂ ኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ከዋናው ሰብስቴሽን ጋር በ 33 ኪቮ Underground Cable
ለማገናኘትና መስመሩ የሚያልፍበትን ኮሪደር ለመምረጥ የልኬት እና የ GPS ኮርዲኔት ስራ ተከናውኗል፡፡ የሲቪል
ስራውን በስራ ተቋራጭ ለማሰራት የጨረታ ሰነድ አየር ላይ እንዲውል ተደርጓል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ
አገልግሎት ለሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የኬብል ትሬንች ግንባታ እና የኬብል ዝርጋታ ስራ ለማከናወን ኮርፖሬሽኑ
ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ 2012 በጀት ዓመት 101 ሚሊዮን ብር ክፍያ የፈፀመ ቢሆንም የኬብል ትሬንች
ሲቪል ስራውን ማከናወን እንደማይችል ገልፆ ስራውን አቋርጦታል፡፡ ኮርፖሬሽኑም ወደ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ
አገልግሎት አካውንት ገቢ የተደረገውን የገንዘብ መጠን ብር 101,981,438.78 ተመላሽ እንዲደረግልን ጥያቄ ቀርቦ
ነበር፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ የኮርፖሬሽኑና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አመራሮች መካከል በተደረገ
ውይይት መሰረት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሲቪል ስራውን እንደሚያከናውን ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡
በዚህም መሠረት የኬብል ትሬንች የሲቪል ስራውን የሚሰራ ቡድን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል
በማዋቀር የዲዛይን እና BOQ (Bill of Quantity) ዝግጅት ተጠናቆ ጨረታ ወጥቷል፡፡ በዚህም መሠረት የጨረታ ሰነድ
የገዙ ተጫራቾችን የቴክኒካል እና የፋይናንሽያል ግምገማ ተከናውኖ ተጠናቋል፡፡ የኬብል አቅርቦትን በተመለከተ ከ 57
ኪ.ሜ ውስጥ 10 ኪ.ሜ የሚሆን ኬብል የተመረተ ሲሆን አስፈላጊውን ሙከራና ፍተሻ ተደርጎ ተጠናቋል፡፡ በመሆኑም
ለሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል በ underground Cable ተደራሽ ለማድረግ በበጀት አመቱ 24%
ክንውን እንዲኖረው ታቅዶ 15.6% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 65% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛ ምክንያት
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የሲቪል ግንባታ ስራውን ለመጀመር የሐሳብ ለውጥ መኖር፣ በድጋሚ
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል ስራውን ለመጀመር ስምምነት ላይ ቢደረስም የጨረታ ሂደት መዘግየት
እንዲሁም በድርጅቱ በኩል ይሟላል የተባለው ኬብል አቅርቦት በሚፈለገው ፍጥነት አለመቅረቡ ናቸው፡፡

በቦሌ ለሚ ሁለት ኢንዱስትሪ ፓርክ ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በጋራ
በመሆን የልኬት ስራ ተከናውኗል፡፡ መስመሩ በሚያልፍበት ኮሪደር ላይ የሚገኙ የይገባኛል ጥያቄዎች ተለይተው
በክ/ከተማ አስተዳደሩ የዋጋ ግምት ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ በቀረበውን የካሳ ክፍያ ላይ ክ/ከተማው ከማህበረሰቡ ጋር
ውይይት ያደረገ ቢሆንም የጋራ መግባባት ላይ አልተደረሰም፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ ስራ ተቋራጭ ተመርጦ የሲቪል
ስራው የተጀመረ ሲሆን ቁፋሮ 1,163 ሜትር፣ የኮንክሪት ስራ 340 ሜትር ተከናውኗል፡፡ በተጨማሪም የግንባታ ፍቃድ
ለማግኘት በዲዛይኑ መሰረት መካተት ያለባቸውን ኮኦርዲኔቶች፣መስመሩ የሚያልፍባቸው የሼዶች ቁጥር
እንዲሁም አስፈላጊ መግለጫዎችን በማካተት ኮርፖሬሽኑ ለአዲስ አበባ ከተማ ግንባታ ፈቃድ እና ቁጥጥር
ባለስልጣን መረጃዎችን አደራጅቶ ያቀረበ ሲሆን ኤሌክትሪክ መስመሩ የሚያልፍበት ኮሪደር ላይ ያሉትን የካሳ ክፍያ
ጥያቄዎች ለመፍታት ኮርፖሬሽኑ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የክፍለ ከተማ አስተዳደሩና የሚመለከታቸው
የአርሶ አደር ተወካዮች በተገኙበት ውይይት ተካሂዷል፡፡ በዚህም መሠረት የክፍለ ከተማ አስተዳደሩ የካሳ ክፍያ የዋጋ
ግምት ለኮርፖሬሽኑ አቅርቧል፡፡ በተጨማሪም የኬብል አቅርቦትን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
የብሔራዊ ባንክ እና ንግድ ባንክ ፍቃድ አግኝቶ ለአቅራቢው ድርጅት ቅድመ ክፍያ ተከፍሏል፡፡ ለቦሌ ለሚ ሁለት
ኢንዱስትሪ ፓርክ ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ ለማድረግ በበጀት አመቱ 95% ክንውን እንዲኖረው ታቅዶ
22
48.8% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 51.36% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛ ምክንያት የይገባኛል ጥያቄዎች በባለድርሻ
አካላት ምላሽ አለማገኘታቸው ስራው እንዲቆም ምክንያት ሆኗል፡፡

ለቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የኬብል ትሬንች መስሪያ በቂ ቦታ ተመርጧል፡፡
የኬብል ትሬንች ዲዛይን ተሻሽሎ እንዲቀርብ በተደረሰው ስምምነት መሰረት የተሻሻለውን ዲዛይን ለአዲስ አበባ
ከተማ ግንባታ ፈቃድ እና ቁጥጥር ባለስልጣን ቀርቦ የግንባታ ፈቃድ ተገኝቷል፡፡ ስራ ተቋራጭ ተመርጦ የሲቪል
ስራው የተጀመረ ሲሆን የቁፋሮ ስራ 940 ሜትር፣ የኮንክሪት ስራ 648 ሜትር ተከናውኗል፡፡ በተጨማሪም የኬብል
አቅርቦትን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የብሄራዊ ባንክ እና የንግድ ባንክ ፍቃድ አግኝቶ
ለአቅራቢው ቅድመ ክፍያ ከፍሏል፡፡ በበጀት አመቱ 95 % ክንውን እንዲኖረው ታቅዶ 56.8 % ተከናውኗል፡፡
አፈፃፀሙም 59.78 % ነው፡፡ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛ ምክንያቶች የትሬንች ግንባታውን ለማካሄድ በተመረጠው ቦታ
ላይ የሚገኝ የአርሶ አደር ይዞታ የይገባኛል ጥያቄ ዘግየቶ የተፈታ በመሆኑና በግንባታው ላይ የ Box እና Pipe Culvert
ዲዛይኖች አለመፅደቅ ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው፡፡

በቦሌ ለሚ I ኢንዱስትሪ ፓርክ ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ በተመለከተ በኢተዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
በኩል ዝርዝር ዲዛይን፣ ውስጥ ለውስጥ ከተዘረጋው ነባሩ መስመር ጋር የሚገናኝበትን ቦታ እና ከሰብስቴሽን
ከሚመጣው 33KV መስመር ጋር ለማጣጣም 33/15KV (15MVA) ትራንስፎርመርና የኢንስታሌሽን ስራዎችን
በማካተት የዋጋ ግምት ተዘጋጅቶ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የቀረበ ሲሆን የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ
ፓርክ ምዕራፍ አንድ ከተገነባው 134 ሜጋ ዋት ሰብስቴሽን የኤሌክትሪክ ኃይል ያገኝ ዘንድ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ
አገልግሎት በኩል የትራንስፎርመር ግዥው እንዲፈፀምና የኢንስታሌሽን ስራውም በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ
አገልግሎት በኩል እንዲከናወን የውሳኔ ሐሳብ ለኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ ቀርቧል፡፡ ለቦሌ ለሚ I ኢንዱስትሪ
ፓርክ ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ ለማድረግ በበጀት አመቱ 15% ክንውን እንዲኖረው ታቅዶ 3.2%
ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 21.3% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛ ምክንያት ባለ 33/15 ኪ.ቮ የትራንስፎርመር አቅራቢ
ውሳኔ አለማግኘቱ፣ የሲቪል ስራው የይገባኛል ጥያቄዎች በባለድርሻ አካላት በኩል ምላሽ አለመሰጠቱ የሲቪል
ስራው እንዲቆም ምክንያት ሆኗል፡፡

ለኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ 60 ሜጋዋት ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል
ማስተላለፊያ መስመር 407 ኪ.ሜ ዝርጋታ እና የሰብስቴሽን ግንባታ በሂደት ላይ የሚገኝ ሲሆን በባለፈው የበጀት
ዓመት 60% የግንባታ ስራው ተጠናቋል፡፡ የከፍተኛ ቮልቴጅ ተሸካሚ መስመር ዝርጋታ፣ የፋውንዴሽን ዝግጅት፣
የታወሮች ተከላ እንዲሁም የ Insulator fixing ስራዎች ተከናውኗል፡፡ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ
መስመር ዝርጋታ እና የሰብስቴሽን ግንባታ በሚመለከት በሀገሪቱ በነበረው ወቅታዊ የፀጥታ ችግር ምክንያት ስርቆት
እና ጉዳት ያጋጠማቸውን ዕቃዎች ለመለየት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል የዳሰሳ ጥናት ተከናውኗል፡፡ ከባህር
ዳር እስከ ወልዲያ የከፍተኛ ቮልቴጅ ማሰተላላፍያ መስመር ግንባታ ስራ ተጀምሯል፡፡ ለኢንዱስትሪ ፓርኩ ዘላቂ
የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ ለማድረግ በ 2014 በጀት ዓመቱ 28% ክንውን እንዲኖረው ታቅዶ 13% ተከናውኗል፡፡
አፈፃፀሙም 46.43% ነው፡፡ ለአፈፃፀም ማነስ ዋነኛው ምክንያት በሀገሪቱ በነበረው ወቅታዊ የፀጥታ ችግር
23
ምክንያት ስርቆት እና ጉዳት ያጋጠማቸውን ዕቃዎች ለመለየት የዳሰሳ ጥናት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል
ለማከናወን ረዘም ያለ ጊዜ ሊወስድ መቻሉ እና ስራ ተቋራጮቹ ቶሎ ወደ ስራ አለመመለስ ናቸው፡፡

ለኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ 200 ሜጋ ዋት ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማሟላትና ወደ ቀጣይ
የትግበራ ምዕራፍ ለመሸጋገር እንዲያስችል ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተጠንቶ በቀረበው የ 200
ሜጋዋት ሰብስቴሽንና 230 ኪ.ቮ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የቴክኒካል አዋጭነት ጥናት ላይ ውይይት ተካሂዶ
የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ በኮርፖሬሽኑና ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መካከል የሰብስቴሽን ግንባታ እና
ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ የማማከር ስምምነት ተፈርሟል፡፡ በዚህም መሰረት በኢትዮጵያ
ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል የሰብስቴሽንና ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዲዛይን፣ ስፔሲፊኬሽን፣
BOQ እና የጨረታ ሰነድ ዝግጀት ተጠናቋል፡፡ ዲዛይኑን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ውይይት
የተደረገ ሲሆን በኮርፖሬሽኑ ለተነሱ ቴክኒካል ጥያቄዎች ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ የሰብስቴሽኑ ግንባታ እና ኤሌክትሪክ
ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ለማከናወን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከስራ ተቋራጭ ጋር ውል እንዲገባ
ኮርፖሬሽኑ ወጪውን እንዲሸፍን መግባባት ላይ ተደሷል፡፡ ኮርፖሬሽኑና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
የተስማሙበትን ለሰብስቴሽን ግንባታ የሚውል መሬት በፓርኩ ቅጥር ግቢ ውስጥ ተመርጧል፤ የሰርቨይንግ ስራም
ተከናውኗል፡፡ የፕሮጀክቱን ፋይናንሻል ስምምነት ሰነድ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተዘጋጅቶ የቀረበ ሲሆን
የኮርፖሬሽኑ የህግ አገልግሎት መምሪያ ሐሳብ በማካተት ሰነዱ እንዲዳብር ከተደረገ በኋላ አቅጣጫ እንዲሰጥበት
ለኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ ቀርቧል፡፡ በአጠቃላይ የሰብስቴሽን ግንባታ እና ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል
ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ ስራው በ 2014 በጀት ዓመት 30% ለማድረስ ታቅዶ 16% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙ
53.3% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋና ዋና ምክንያቶች ከስራ ተቋራጭ ጋር ውል መግባት ያለበት ባለድርሻ አካል
ለመለየት ረዘም ያለ ጊዜ መውሰዱ እና የፋይናንሻል ስምምነት ሰነድ ዝግጅትና መፈራረም አቅጣጫ አለመሰጠቱ
ናቸው፡፡

በኢንዱስትሪ ፓርኮች የቴሌኮም መሰረተ ልማትን ማሟላት

ለባህር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ ከኢትዮ ቴሌኮም ስቴሽን እስከ ኢንዱስትሪ ፓርኩ ድረስ የፋይበር ኬብል ዝርጋታ
ለማከናወን የሲቪል ስራ ተጀምሮ ከ 93 የቴሌኮም ማንሆሎች ውስጥ 80 ተጠናቋል፡፡ በተጨማሪም የ 5 ማንሆል
ፒት ግንባታ፣ 8 ኪ.ሜ የዳክት ቁፋሮ እና 4.4 ኪ.ሜ የፒቪሲ ቱቦ ዝርጋታ ተከናውኗል፡፡ ለኢንዱስትሪ ፓርኩ
የቴሌኮም አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ የታቀደ ሲሆን በ 2014 በጀት ዓመት 5% ክንውን እንዲኖረው ታቅዶ 3.78%
ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 75.6% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛ ምክንያት በኢትዮ ቴሌኮም በኩል የፋይበር ኬብል
ዝርጋታ ስራ በፍጥነት አለመከናወኑ እና የይገባኛል ጥያቄ አለመፈታት ናቸው፡፡

ለሰመራ ኢንዱስትሪ ፓርክ የቴሌኮም መሰረተ ልማት ለማሟላት በባለፈው የበጀት ዓመት 30% የቴሌኮም መሰረተ
ልማት አቅርቦት ስራ ተጠናቋል፡፡ 150 የቴሌኮም ፖሎች ተከላ እና 7.5 ኪ.ሜ የፋይበር ኬብል ዝርጋታ ስራ
ተከናውኗል፡፡ በፓርኩ ውስጥ የፋይበር ኬብል ዝርጋታ እንዲሁም በሼዶች ውስጥ የፋይበር እና ኮፐር ኬብል ዝርጋታ

24
ስራዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል፡፡ ስራ ተቋራጩ በኢትዮ ቴሌኮም በኩል በ HLD እና MSAN ስፔሲፊኬሽን ላይ
የተሰጡትን አስተያየቶች አካቶ እንዲያቀርብ በአማካሪው በኩል ትዕዛዝ ቀርቧል፡፡ በ 2014 በጀት ዓመት 70% ክንውን
እንዲኖረው ታቅዶ 50% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 71.43% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛ ምክንያት ስራ ተቋራጩ
በዲዛይን ማፀደቅ ሂደት ላይ በኢትዮ ቴሌኮም በኩል የቀረቡ አስተያየቶችን ተቀብሎ በሚፈለገው ፍጥነት
አለማቅረቡ እና ስራ ተቋራጩ ሳይት ላይ በመገኘት ስራዎችን በሚፈለገው ፍጥነት አለማጠናቀቁ ናቸው፡፡

ለአይሻ ኢንዱስትሪ ፓርክ የቴሌኮም መሰረተ ልማት እንዲሟላ የቅድመ ዝግጅት ሥራ እንዲከናወን በተያዘው ዕቅድ
መሰረት በኢትዮ ቴሌኮም በኩል የአዋጭነት ጥናት ተከናውኖ ለፓርኩ የሚያስፈልገው የቴሌኮም መሰረተ ልማት
ከፓርኩ በ 17.69 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ከሚገኝ የቴሌኮም መሰረተ ልማት ሟሟላት እንደሚቻል ተረጋግጧል፡፡ በ 2014
በጀት ዓመት 20% ክንውን እንዲኖረው ታቅዶ 20% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 100% ነው፡፡

ለኢንዱስትሪ ፓርኮች ጥራቱ የተረጋገጠ ዉሃ እንዲሟላ ማድረግ

የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውሃ አርቅቦትን በዘላቂነት ለማሟላት የሲቪል ስራ 2.34% ለማከናወን ዕቅድ ተይዞ
1.24% ተከናውኗል፡፡ ይህም አፈፀፀሙን 52.99% ያደርገዋል ፡፡ እንዲሁም ለዚሁ ዉሃ አቅርቦት የኤሌክትሮሜካኒካል
ስራ ለማከናወን 45% ታቀዶ የነበረ ሲሆን 14% ተከናውኗል፡፡ ይህም አፈፃፀሙ 31.11% ነዉ፡፡ ለሲቪል ስራ አፈፃፀም
ማነስ እንደዋነኛ ምክንያት የሚጠቀሰው በይገባኛል ጥያቄ ምክንያት ስራዉ በተደጋጋሚ መስተጓጎሉ እና የህግ
ማስከበር ስራዉ በተወሰኑ ግንባታ ቦታዎች ላይ ባለመከናወኑ ነዉ፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ ለቦሌ-ለሚ ምእራፍ 1
ኢንዱስትሪ ፓርክ ከጉድጓድ ቁጥር 4 ,በቀን 2,016 ኩብ.ሜትር ውሃ (35 ሊትር /ሰከንድ) እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በቦሌ ለሚ አንድ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዉስጥ ጉድጓዱ በመደርመሱ ምክንያት ከአገልግሎት ዉጪ
የሆነዉን ጉድጓድ ቁጥር 5 ምትክ ጉድጓድ ለማስቆፈር አማካሪዉ ባስቀመጠዉ ምክረ ሃሳብ መሰረት የማኔጅመንት
ዉሳኔ አግኝቶ ተተኪ የጉድጓድ ቁፋሮ ለማከናወን 100% ዕቅድ ተይዞ የነበረ ሲሆን ከዚህም ውስጥ 65% ተከናውኗል፡፡
ይህም አፈፃፀሙን 84.61% ነዉ፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ እንደዋነኛ ምክንያት የሚጠቀሰው ስራ ተቋራጩ የዋጋ ግምት
አስገብቶ በፀደቀለት እና ወደ ስራ ለመግባት ታሳቢ በተደረገዉ ጊዜ ሰሌዳ መሰረት ወደ ስራ ለመግባት ፍቃደኛ
አለመሆኑ ነዉ። ስለሆነም ችግሩን ለመፍታት በድጋሚ በአጭር ጊዜ ዉስጥ የስራ ተቋራጭ ግዥ ለመፈፀም የቅድመ
ዝግጅት ስራ ተከናዉኖ ዉሳኔ እንዲሰጥበት ለኮርፖሬሽኑ ማኔጅመንት ቀርቦ ዉሳኔ ተሰጥቶበታል፡፡ ስለሆነም በዚሁ
ለሚመለከተዉ ክፍል የጨረታ ሰነድ ተዘጋጅቶ ለግዥ አፅዳቂ ኮሚቴ ቀርቧል፡፡

ለአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዘላቂ ውሃ ለማቅረብ ECO (Engineering Corporation of Oromia) በኩል የጥናት እና
ዲዛይን ስራ እንዲከናወን በተያዘዉ ዕቅድ መሰረት 100% ለማከናወን ታቅዶ 80% የተከናወነ ሲሆን ይህም
አፈፃፀሙን 80% ያደርገዋል። ለአፈፃፀም ማነስ እንደምክንያት የሚጠቀሰዉ አማካሪዉ በተቀመጠዉ የጊዜ ሰሌዳ
መሰረት የታቀደዉን ያህል ባለማከናወኑ ነዉ፡፡ ሌላዉ የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ጊዜያዊ ዉሃ አቅርቦት ሲሆን 100%
ለማከናወን ዕቅድ ተይዞ 10% ተከናዉኗል፡፡ አፈፃፀሙም 10% ነዉ፡፡ ለአፈፃፀም ማነስ ምክንያት የስራ ተቋራጩ
አፈፃፀም ዝቅተኛ መሆን ነዉ፡፡
25
በድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ የዘላቂ ውሃ አቅርቦት ለማረጋገጥ የጥልቅ ውሃ ጉድጓድ ከፓርኩ ከ 8 ኪ.ሜትር ላይ
ተቆፍሮ እና ዉሃ መስመር ዘርግቶ የዉሃ አቅርቦቱን ተደራሽ ለማድረግ 62.14% ለማከናወን ታቅዶ 48.5% የተከናወነ
ሲሆን፣ ይህም አፈፃፀሙ 78.04% ነዉ። ለአፈፃፀም ማነስ ምክንያት የይገባኛል ጥያቄ ሙሉ በሙሉ አለመፈታትና
ስራ ተቋራጩ አፈፃፀም ማነስ ነዉ፡፡ በተጨማሪም በድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዙሪያ ለሚኖሩ ነዋሪዎች ኮርፖሬሽኑ
ከውሃ አቅርቦቱ ተጠቃሚ ለማድረግ ቃል በገባላቸው መሰረት ከዉሃ አቅርቦቱ ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል ሰነድ
በማዘጋጀት ለኮርፖሬሽኑ ማኔጅመንት ቀርቧል፡፡ በዚህም ከተያዘዉ 100% ዕቅድ 75% የተከናወነ ሲሆን፣ ይህም
አፈፃፀሙን 75% ያደርገዋል፡፡ ለአፈፃፀም ማነስ ምክንያት ለስራዉ በቀረበዉ ፕሮፖዛል ላይ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር
ስምምነት ላይ ሳይደረስ በመቆየቱ ነዉ፡፡ በመሆኑም በአሁኑ ሰዓት ስምምነት ላይ ተደርሶ ስራዉ መከናወን
ስለሚቻልበት ሁኔታ ክትትል በመደረግ ላይ ነዉ፡፡

በአዳማና ድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርኮች የከርሰ ምድር ውሃ በአግባቡ እና ከብክነት በፀዳ መልኩ ለመጠቀም እንዲቻል
ኮርፖሬሽኑ የዝናብ ዉሃ ማቆሪያ (Water harvesting structure) ቀሪ ስራዎችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ዝግጁ
ለማድረግ በሁለቱም ኢንዱስትሪ ፓርኮች የዝናብ ዉሃ ማቆሪያ ቀሪ ስራ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ የድሬዳዋ
ኢንዱስትሪ ፓርክ የዝናብ ዉሃ ማቆሪያ ቀሪ ስራ በማከናወን ለአገልግሎት ዝግጁ ሲሆን የአዳማ የዝናብ ዉሃ
ማቆሪያ ቀሪ ስራ የስራ ተቋራጩ አፈፃፀም በማነሱ አልተከናወነም፡፡ በመሆኑም በሁለቱም ኢንዱስትሪ ፓርኮች ቀሪ
የዝናብ ዉሃ ማቆሪያ ስራ ለማጠናቀቅ የተያዘዉ ዕቅድ በድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተጠናቀቀ ሲሆን አፈፃፀሙን
50% ያደርገዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ፓርኮች መዳረሻና ተለዋጭ መንገድ ግንባታ መከታተልእና ማስፈፀም

በተለያዩ ከተሞች የተገነቡትን የኢንዱስትሪ ፓርኮች በመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽ በማድረግ ውጤታማ እና
ፈጣን የሆነ የትራንስፓርት አገልግሎት እንዲኖር ለማድረግ ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር እና ከአዲስ አበባ
ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ጋር በመሆን ለፓርኮቹ የመዳረሻ መንገድ ግንባታዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡

በበጀት ዓመቱ ለኢንዱስትሪ ፓርኮቹ የመዳረሻ መንገድ ግንባታ ለማከናወን ከተያዙት ውስጥ የኮምቦልቻ
ኢንዱስትሪ ፓርክ ተደራሽ ከሚደረገው የ 3.28 ኪ.ሜትር የመዳረሻ መንገድ የቀሪ 2.55 ኪ.ሜትር ግንባታ ዉስጥ ቀሪ
ዉስን የማጠናቀቂያ ስራዎችን ለማጠናቀቅ 11.75% ዕቅድ ተይዞ 11.75% የተከናወነ ሲሆን ይህም አፈፀፀሙን 100%
ያደርገዋል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአስተዳደር መስሪያ ቤቱ በኩል ግንባታው የሚከናወነው የደብረብርሀን ኢንዱስትሪ ፓርክን
ተደራሽ የሚያደርገው የደብረብርሃን-ደነባ-ጅሁር የ 110 ኪ.ሜትር መንገድ ሲሆን፣ በበጀት ዓመቱ ከደብረ ብርሃን
ከተማ እስከ ኢንዱስትሪ ፓርኩ ድረስ ያለውን የ 6 ኪ.ሜትር መዳረሻ መንገድ እና የፓርኩን የመኪና ማቆሚያ
26
ግንባታ ለማከናወን 26% ዕቅድ ተይዞ 26% የተከናወነ ሲሆን አፈፃፀሙም 100% ነዉ፡፡ በዚህም ወሰን የማስከበር ስራ፣
ካሳ ክፍያ እንዲፈፀም እና በግንባታ ክልል ዉስጥ ያሉ ንብረቶችን የማስነሳት ስራና የታቀደዉ ግንባታ እንዲከናወን
ከሚመለከታቸዉ ጋር በመሰራቱ የተያዘዉ ዕቅድ ሊከናወን ተችሏል፡፡ የነበረዉ የመንገዱ ጊዜአዊ ችግር ታሳቢ
በማድረግ ለተጠቃሚ ምቹ ለማድረግ ከአስተዳደር መ/ቤቱ ጋር በተደረገ መግባባት እስከ ደብረብርሃን ኢንዱስትሪ
ፓርክ ድረስ ያለውን የ 6 ኪ.ሜትር መንገድ ጥገና ተከናዉኗል፡፡ በተጨማሪም የፓርኩን መኪና ማቆሚያ ግንባታ
በተመለከተ መንገዱን በሚያማክረዉ አማካሪ ድርጅት በኩል የመጨረሻ ደረጃ ዲዛይንና የግንባታ ዋጋ ተጠናቋል፡፡
ከመዳረሻ መንገዱ ወደ ኢንዱስትሪ ፓርኩ የሚመጣዉን የጎርፍ ፍሳሽ ለፓርኩ ስጋት እንዳይሆን ለማስቻል፣
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የመንገድ ግንባታውን የሚያማክረው አማካሪ ድርጅት እና የኮርፖሬሽኑ
ተወካዮች እንዲሁም የፓርኩን ግንባታ ካከናወነው የስራ ተቋራጭ እና አማካሪ ድርጅት በተገኙበት የጋራ የመስክ
ዳሰሳ እና የውይይት መድረክ ተካሂዶ የጎርፍ ፍሳሹ ከፓርኩ ጋር በተናበበ መልኩ መሄድ እንዳለበት መግባባት ተደርሶ
በዚሁ አግባብ እየተከናወነ ይገኛል፡፡

በሁለቱም ኢንዱስትሪ ፓርኮች (ኮምቦልቻና ደብረ-ብርሃን) መዳረሻ መንገድ ግንባታ ለማከናወን እንዲቻል በተያዘዉ
የቅንጅት ዕቅድ መሰረት በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር በኩል በተዘጋጀዉ የጋራ ግምገማ መድረክ እንዲሁም
የመስክ ላይ ክትትልና ድጋፍ መርሃ ግብር ኮርፖሬሽናችን እና ሌሎች የሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት
በጋራ የመስክ ምልከታና ዉይይት በማድረግ ለችግሮቹ መፍትሄ ላይ ለመድረስና ምቹ ሁኔታ ለማምጣት በትኩረት
ተሰርቷል፡፡

የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የ 3 ኪ.ሜትር የመዳረሻ መንገድ ግንባታ በሚቀጥለዉ 2015 ዓ.ም በጀት ዓመት ለመንገድ
ግንባታዉ የሚሆን በጀት እንዲያዝና ቅድመ ዝግጅት ስራ እንዲከናወን ለማድረግ በተያዘዉ የክትትል ዕቅድ መሰረት
ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር መ/ቤት ጋር መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ በዚህም መሰረት የተያዘዉ ዕቅድ ሙሉ
በሙሉ ተከናዉኗል፡፡

በተመሳሳይ የይገባኛል ጥያቄ ባለመፈታቱ ምክንያት ግንባታው ያልተጠናቀቀው የድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ
መዳረሻ መንገድ በተመለከተ ግንባታዉን ማከናወን እንዲቻል በመስተዳደሩ በኩል ከይገባኛል ነፃ እንዲሆን ክትትል
እየተደረገ ሲሆን በከተማ አስተዳደሩ በኩል ካሳ ክፍያ ለተፈፀመባቸዉ ከፊል ንብረቶችን የማስነሳት እና ግምት
ላልተሰራላቸዉ ንብረቶች የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ በዚሁ አግባብ የግምት ስራ በመሰራት
ላይ ሲሆን ከከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጋር በመሆን በገንዘብ
ሚኒስቴር በኩል ለቀሪ ግንባታዉ አስፈላጊዉ በጀት እንዲያዝ ለማድረግ ባደርግነዉ ክትትል በጀቱ የተፈቀደ
ስለመሆኑ ከአስተዳደር መ/ቤቱ ማወቅ ችለናል፡፡ በዚህም የግንባታ ቦታዉን ከይገባኛል ነፃ ለማድረግ 100% ዕቅድ
ተይዞ 40% የተከናወነ ሲሆን አፈፃፀሙም 40% ነዉ፡፡ ለአፈፃፀም ማነስ ምክንያት ወሰን ለማስከበር፤ ንብረቶችን
ለማስነሳትና የካሳ ክፍያ እና በጀት ለማስፈቀድ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እና በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
በኩል ከታሰበዉ ጊዜ በላይ ጊዜ በመዉሰዱ ነዉ፡፡ እንዲሁም የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ አጎራባች ለሚኖሩ ነዋሪዎች

27
ከተለዋጭ መንገድ ግንባታ ጋር ተያያዥ ቀሪ ስራዎች እንዲጠናቀቁ ክትትል ማድረግ በተመለከተ 4% ዕቅድ ተይዞ
4% የተከናወነ ሲሆን አፈፃፀሙም 100% ነዉ፡፡

በተጨማሪም በቦሌ ለሚ 1 ኢንዱስትሪ ፓርክ ዙሪያ ከሚገነቡ እና ለነዋሪዎች የመዳረሻ አገልግሎትን የሚሰጡ
መንገዶች በአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን በኩል እንዲከናወን በተደረሰዉ መግባባት መሰረት በፓርኩ አራቱም
አቅጣጫ የሚገነቡ መንገዶች ያሉበትን ደረጃ ከባለስልጣን መሥሪያ ቤቱ ጋር በጋራ በመነጋገር በፕላን
የመለየት፣ከፓርኩ ጋር የማናበብ እና የማጣጣም ስራ ተከናውኗል፡፡ እንዲሁም ለፕሮጀክቶች በተያዘዉ የግንባታ
መርሃ ግብር መሰረት ስራዉ እንዲጀመር የጋራ ስምምነት ላይ ለመድረስ የሚያስችል አንድ ረቂቅ ሰነድ ተዘጋጅቷል፡፡
በዚህም አፈፃፀሙን 100% ያደርገዋል፡፡ በተመሳሳይ በዚህ ረቂቅ ሰነድ ላይ የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ
ፓርክ እና የቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክን ተደራሽ የሚያደርጉ መንገዶችን ሰነዱ ላይ እንዲካተት ተደርጓል፡፡ ከነዚሁ
ፓርኮቹን ተደራሽ ከሚያደርጉ የመዳረሻ መንገዶች መካከል አራብሳ - አይሲቲ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 10%
ዲዛይን እና ግንባታ እንዲከናወን ክትትል ማድረግ በተመለከተ 10% ለማከናወን ዕቅድ ተይዞ 10% የተከናወነ ሲሆን
አፈፃፀሙን 100% ያደርገዋል፡፡ ለዚህም ስራ ፓርኩን በ over pass የሚያልፍ የመንገዱን ድልድይ ዲዛይንና ይህንኑ
መንገድ ከፓርኩ የመሰረተ ልማት መስመሮች ጋር የማናበብና ማጣጣም ስራ ተከናዉኗል፡፡ በቀጣይም አሁን ላይ
የገጠመዉ የወሰን ማስከበር ችግር በከተማ አስተዳደሩ በኩል እንዲፈታ ከሚመለከታቸዉ የወረዳና ክፍለ ከተማ
አመራር ጋር ክትትል የሚደረግ ይሆናል፡፡

1.9 የኤሌክትሪክ ኃይልና ቴሌኮም የርክክብ ስራዎች

የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ኤሌክትሪክ እና ቴሌኮም መስመሮችና ተያያዥ ዕቃዎች የማስተካከያ ስራዎችን
በተመለከተ ስራ ተቋራጩ በፓምፕ ስቴሽን እና ደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ያልተጠናቀቁ የፋይበርና ኮፐር ኬብሎች
ዝርጋታ ስራዎችን አጠናቋል፡፡ የፍሳሽ ማጣሪያው የፋይበር እና ኮፐር ኬብሎች ዝርጋታ ስራ 100% ተከናውኗል፡፡ 600
ሜትር የመካከለኛ ቮልቴጅ ኬብል ትሬንች እንዲፀዳ ተደርጓል፤ በ 40 ማንሆሎች ላይ የማስተካከያ ስራ ተሰርቷል፡፡
የፋይበር ኬብል እና ቴሌኮም ዕቃዎች ማስተካከያ ስራዎች ለማከናወን የሚያስፈልጉ ዕቃዎች ከድሬዳዋ ኢንዱስትሪ
ፓርክ ወደ አዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ለማጓጓዝ እና ከውጭ ሀገር ተገዝተው በመጡ ዕቃዎች ላይ የከስተምስ ድጋፍ
እንዲደረግለት ስራ ተቋራጩ በጠየቀው መሰረት ድጋፍ ተደርጎለታል፡፡ የፍሳሽ ማጣሪያ ETP ኤሌክትሪክ ኃይል
ለማገናኘት ዕቃዎች ግዥ በኮርፖሬሽኑ በኩል ተከናውኖ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል ተገጥመዋል፤
የኢነርጂ ቆጣሪ ተገጥሟል፤ ለ ETP ኤሌክትሪክ ኃይል ቀርቧል አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡ ቀሪ ያልተጠናቀቁ
የአውቶማቲክ አላርም ኮንትሮልና የ CCTV ስራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ በ 2014 በጀት ዓመት የርክክብ ስራዎቹ
8.5% ክንውን እንዲኖር ታቅዶ 6.98% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙ 82% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛ ምክንያት
የቴሌኮም ዕቃዎች ዝውውር መዘግየት፣ ስራ ተቋራጩ በቂ ባለሞያዎችን ሳይት ላይ አለመመደብና የመካከለኛ
ቮልቴጅ እና ቴሌኮም ዕቃዎች ላይ የማስተካከያ ስራዎች በሚፈለገው ፍጥነት አለማከናወን ሲሆን በዚህም
ምክንያት የርክክብ ስራው በተቀመጠው መርሀ ግብር እንዳይጠናቀቅ ምክንያት ሆኗል፡፡

28
የድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ ኤሌክትሪክ እና ቴሌኮም መስመሮችና ተያያዥ ዕቃዎች ማስተካከያ ስራዎች
ለማፋጠን እንዲረዳ ቀሪ ስራዎች ተለይተው ማጠናቀቅ ስለሚቻልበት ሁኔታ ከባለድርሻ አካለት ጋር ተከታታይ
ውይይቶች ተደርገዋል፡፡ በዚህ መሰረት የቴሌኮም መስመሮችና ተያያዥ ዕቃዎች ማስተካከያ ስራዎች በመከናወን
ላይ ናቸው፡፡ በዳታ ሴንተር ውስጥ የኮርስዊች ኮንፊገሬሽን ስራዎች እና የሼዶች ራውተር ኮንፊገሬሽን ተከናውኗል፡፡
እንዲሁም የፋይበር እና ኮፐር ኬብሎች ፍተሻና ሙከራ ስራ በኢትዮ ቴሌኮም በኩል ተከናውኗል፡፡ ፋይበር ኬብሎች
ችግር እንደሌለባቸው በፍተሻና ሙከራ ጊዜ ተረጋግጧል፤ በተወሰኑ የኮፐር ኬብሎች ላይ ችግሮች የተስተዋሉ ሲሆን
እንዲስተካከሉ በተሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ስራ ተቋራጩ የፋይበርና ኮፐር ኬብሎች ማንሆሎች እንዲሁም የኮፐር
ኬብሎች ማስተካከያ ስራ አጠናቋል፡፡ እንዲሁም ኢትዮ ቴሌኮም ሁሉም የቴሌኮም ፓኔሎች Grounding System
እንዲኖራቸው በሰጠው አስተያየት መሰረት ስራ ተቋራጩ አስተያየቶቹን አስተካክሎ አጠናቋል፡፡ የኢንዱስትሪ
ፓርኩ እሳት አደጋ መከታተያ እና መቆጣጠሪያ ላይ በፋይበር ኬብል አማካኝነት ከዳታ ሴንተር ጋር የመገናኘት፣
ፍተሻና ሙከራ ተጠናቋል፡፡ ስራ ተቋራጩ የመካከለኛ ቮልቴጅ ማንሆሎችና ኬብል ትሬንች የማፅዳትና ኬብሎችን
የማስተካከል ስራ ጀምሮ የነበረ ቢሆንም ባለሙያዎቹ ወደ ዉሃ አቅርቦት ስራ በማዛወራቸው ምክንያት የተሰጡትን
አስተያየቶች የማስተካከል ስራው ቆሟል፡፡ የኤሌክትሪክ እና ቴሌኮም መስመሮችና ተያያዥ ዕቃዎች የመጨረሻ
ደረጃ ርክክብ እንዲጠናቀቅ ለአማካሪ ድርጅቱ ተጠይቋል፡፡ አማካሪውም የቴሌኮም መስመሮችና ተያያዥ ዕቃዎች
የመጨረሻ ደረጃ ርክክብ ማከናወን አስፈላጊነትና አስቸኳይነት በመጥቀስ ስራ ተቋራጩ በአጭር ጊዜ ውስጥ
የርክክብ ዕቅድና መርሀግብር እንዲያቀርብና ርክክቡ እንዲጠናቀቅ ትእዛዝ ሰጥቷል፡፡ ስራ ተቋራጩ ባሉያዎቹን ወደ
ሳይት እንዲመልሳቸውና የመጨረሻ ደረጃ ርክክቡ እንዲጀምር ውይይት የተደረገ ሲሆን የቴሌኮም ርክክብ
ለማጠናቀቅ ከውጭ ሀገር ባለሙያ አስመጥቷል፡፡ የኢንዱስትሪ ፓርኩ ኤሌክትሪክና ቴሌኮም ማከፋፈያ መስመሮችና
ዕቃዎች ርክክብ በ 2014 በጀት 32.5% ለማድረስ ታቅዶ 25.4% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙ 73% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ
ዋነኛ ምክንያቶች የቴሌኮም ዕቃዎች አቅርቦት መዘግየት፣ የስራ ተቋራጩ ባለሙያዎች ሳይት ላይ አለመኖር፣ ስራ
ተቋራጩ ዋና ትኩረቱን ወደ ኢንዱስትሪ ፓርኩ ዘላቂ የዉሃ አቅርቦት ላይ ማድረጉና ሙሉ የሰው ኃይሉ ወደዚህ ስራ
በማሰማራቱ በኤሌክትሪክ መስመሮችና ተያያዥ ዕቃዎች ማስተካከያና ርክክብ በሚፈለገው ፍጥነት አለማከናወን
ናቸው፡፡

ለደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ የኤሌክትሪክ እና ቴሌኮም ስራዎች ርክክብ ለማከናወን የመካከለኛ ቮልቴጅ
የኤሌክትሪክ ሲስተም ማስተካከያ ስራ እንዲሁም የቴሌኮም Weak current System ፍተሻና ሙከራ ስራዎች
ተከናውኗል፤ የቴሌኮም መስመሮችና ተያያዥ እቃዎች ርክክብ ለመፈፀም በኢትዮ ቴሌኮም በኩል የራውተሮች እና
ኮር ስዊቾች ሙከራና ፍተሻ ስራ ተከናውኗል፡፡ በተጨማሪም ከኢትዮ ቴሌኮም ስቴሽን እስከ ኢንዱስትሪ ፓርኩ
ድረስ ያለው ቀሪ የፋይበር ኬብል ዝርጋታ ስራ በኢትዮ ቴሌኮም በኩል ተከናውኗል፤ የፍተሻ ስራውም ተጠናቋል፡፡
ለስልጠና የሚያስፈልጉ ሁሉም ሰነዶች በስራ ተቋራጩ ተዘጋጅተው ቀርበዋል፡፡ በ 2014 በጀት ዓመት 13.3% ክንውን
እንዲኖር ታቅዶ 8.534% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 64.16% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛ ምክንያት ስራ ተቋራጩ
በወቅቱ ባለሙያ አለመመደብ፣ የጊዜ ሰሌዳ በሚፈለገው ፍጥነት አለማሳወቁ፣ የማስተካከያ ስራዎችን በፍጥነት
አለማጠናቀቁ እና ሳይት በመገኘት ስራዎችን ማከናወን አለመቻሉ ናቸው፡፡

29
የባህር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ መካከለኛ ቮልቴጅ ማከፋፈያ ዕቃዎችና መስመር ዝርጋታ በተመለከተ ኮርፖሬሽኑ፣
አማካሪው እንዲሁም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በተገኙበት የመጨረሻ ደረጃ ርክክብ ተከናውኗል፡፡
የቴሌኮም መስመሮችና ተያያዥ ዕቃዎች ፍተሻና ሙከራ እንደሁም ርክክብ በተመለከተ በመጀመሪያ ደረጃ ርክክብ
ወቅት የተሰጡትን አስተያየቶች በስራ ተቋራጩ በኩል ተስተካክለዋል፤አማካሪው በተገኘበትም ተረጋግጧል፡፡ ይህ
እንደተጠበቀ ሆኖ ስራ ተቋራጩ የ Access Control ስልጠና ለኮርፖሬሽኑ ባለሙያዎች እንዲሰጥ ተደርጓል፡፡
የቴሌኮም ዕቃዎችን ርክክብ ለማድረግ አስፈላጊ የሆኑ ዶክመንቶች በኢትዮ ቴሌኮም ፀድቋል፡፡ የ Weak Current
System የመጨረሻ ርክክብ አማካሪው በተገኘበት ተከናውኗል፡፡ በ 2014 በጀት ዓመት 100% ክንውን እንዲኖረው
ታቅዶ 84% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 84% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛ ምክንያት ስራ ተቋራጩ የርክክብ ሰነድ
በኢትዮ ቴሌኮም በኩል የተሰጠውን አስተያየት መሰረት አስተካክሎ በሚፈለገው ፍጥነት አለማቅረቡ ነው፡፡

የቦሌ ለሚ II ኢንዱስትሪ ፓርክ የኤሌክትሪክ መስመሮችና ተያያዥ እቃዎች ርክክብ ለማከናወን በቀረበው ዲዛይን፣
ስፔስፊኬሽንና BOQ መሠረት ስለመሰራቱ የፊዚካል ኢንስፔክሽን ስራዎች በ RMU፣ Compact transformers፣ ኬብል
እና የመንገድ መብራት ላይ ተከናውኖ ተጠናቋል፡፡ በፊዚካል ኢንስፔክሽኑ መሰረት መስተካከል የሚገባቸው ስራዎች
ስራ ተቋራጩ እንዲያውቀው የተደረገ ሲሆን የ earthing ስራ እየተከናወነ ነው፡፡ በተጨማሪም ለሙከራና ፍተሻ
የሚያስፈልግ 2 ሜጋዋት ጊዜያዊ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲቀርብ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠይቆ የዋጋ
ግምት የቀረበ ሲሆን ክፍያም ተፈፅሟል፡፡ በዚህም መሠረት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ምስራቅ ሪጅን
በኩል ስራው ተጀምሯል፡፡ የቴሌኮም ርክክብን በተመለከተ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመሆን ሁለቱም MSAN ርክክብ
ተጠናቋል፡፡ በበጀት አመቱ 82.5% ክንውን እንዲኖረው ታቅዶ 39.5% ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 47.87% ነው፡፡
ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛ ምክንያቶች ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል አለመቅረቡ፣ በፊዚካል ፍተሻ ወቅት የተገኙ
ማስተካከያ የሚፈልጉ ስራዎች በስራ ተቋራጭ በኩል በሚገባው ፍጥነት አለመከናወን እንዲሁም ስራ ተቋራጩ
የርክክብ መርሀግብር በፍጥነት አለማቅረብ የርክክብ ስራው እንዲዘገይ ሆኗል፡፡

በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ የቴሌኮም እንዲሁም የኤሌክትሪክ መስመሮችን ርክክብ ለማከናወን በቀረበው ዲዛይን፣
ስፔስፊኬሽንና BOQ ስለመሰራቱ ለማረጋገጥ በመካከለኛ ቮልቴጅ እቃዎች ላይ የፊዚካል ኢንስፔክሽን ስራ
ተከናውኗል፡፡ በፊዚካል ኢንስፔክሽን ወቅት ማስተካከያ የሚፈልጉ ዝርዝር ስራዎች ተለይተው ለስራ ተቋራጩ
በቀርበው መሰረት የማስተካከያ ስራዎቹ ተከናውነዋል፡፡ ለኢንዱስትሪ ፓርኩ ጊዜያዊ የኤሌክትሪክ ኃይል በ 33 ኪሎ
ቮልት ከፓርኩ በቅርብ ርቀት ከሚገኘው ቂሊንጦ ሰብስቴሽን በአየር ላይ (over head) በመዘርጋት በመካከለኛ ቮልቴጅ
እቃዎች አና ኬብሎች ላይ ፍተሻ እና ሙከራ ለማከናወን ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ
አገልግሎት ጊዜያዊ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት መስመር ዝርጋታ ለማከናወን ለኮርፖሬሽኑ ያቀረበውን የዋጋ
ግምት ክፍያ ተፈፅሟል፤ የመስመር ዝርጋታ ስራውም በሂደት ላይ ነው፡፡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ
አገልግሎት፣ አማካሪ ድርጅቱ እና ኮርፖሬሽኑ ባለሙያዎች በተገኙበት ስራ ተቋራጩ የመካከለኛ ቮልቴጅ ኬብሎች
ፍተሻና ሙከራ እያከናወነ ይገኛል፡፡ በበጀት አመቱ የርክክብ ስራው 82.5% ክንውን እንዲኖረው ታቅዶ 44.75%
ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙም 54.24% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋነኛው ምክንያት ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል አለመኖር፣

30
ጊዜያዊ የኤሌክትሪክ አቅርቦት መዘግየት እና በኤሌክትሪክ መስመሮችና ተያያዥ ዕቃዎች ላይ ፍተሻና ሙከራ
ስራዎች በሚፈለገው ፍጥነት አለመከናወን ናቸው፡፡

ግብ 2፡ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የስራ እድል ፈጠራና ውጤታማነትን ማሳደግ፤

የስራ እድል ፈጠራ በኢንዱሰትሪ ፓርኮች ልማት ከተቀመጡ ዋና ዋና ተልዕኮዎች ውስጥ አንዱ ሲሆን
በኢንዱስትሪ ፓርኮች በጀት ዓመቱ ለ 74,200 ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ በአጠቃላይ ለ 55,266 ስራ ዕድል

የተፈጠረ ሲሆን አፈጻጸሙ 74.5% ይሆናል፡፡ በበጀት ዓመቱ ውስጥ 4,373 የሚሆኑ ሰራተኞች ከአንዱ ድርጅት ወደ

ሌላው ድርጅት የተመደቡ (reallocated) የተደረጉ ናቸው፡፡ በበጀት ዓመቱ ውስጥ በ AGOA በተፈጠረው ተጽዕኖ
ምክንያት ኩባንያዎች በመልቀቃቸው (ሀዋሳ) እና በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት ምክንያት ኩባንያዎች ለተወሰነ
ጊዜ ስራ በማቆማቸው፣ ጥቅማ ጥቅም ማነስ፣ ደመወዝ ማነስ እና መኖሪያ ቤት አቅርቦት ችግር ምክንያት ከኢንዱስትሪ
ፓርኮች በአጠቃላይ 51,591 ሰራተኞች የለቀቁ ሲሆን የሰራተኞች የመልቀቅ ምጣኔን ለመቀነስ እና የስራ ዕድል ፈጠራ እና
ምርታማነትን ለማሳደግ ከሰራተኞች መብት እና ጥቅማ ጥቅም ጋር ተያይዞ የሚታዩ ችግሮች ከባለሀብቶች እና

ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል እየተሰራም ነው፡፡ በአጠቃላይ ወደ ኦፕሬሽን በገቡ ኢንዱስትሪ

ፓርኮች እስካሁን ለ 67,815 (ወንድ 9,281 እና ሴት 58,534) ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከፋብሪካ

ሰራተኞች (Operators) ውጪ በሌሎች የስራ ዘርፎች (ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች፣ ጥበቃ፣ ግሪነሪ፣ ፅዳት፣ OSS፣ ሾፌሮች
እና ረዳቶቻቸው፣ ግንባታ፣ ምግብ አቅራቢዎች፣ የቀን ሠራተኞች ወይም የጉልበት ሠራተኞች እና ሌሎች ጭምር)

የተፈጠረው ስራ ዕድል 9,407 ሲሆን በአጠቃላይ እስከ ሰኔ ወር 2014 ዓ.ም ድረስ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ለ 77,222 ዜጎች

ስራ ዕድል ተፈጥሯለ፡፡ አፈፃፀሙም 84.8% ነው፡፡በኢንፎርሜሽን ኮምዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ በበጀት አመቱ አዲስ

የተፈጠረው የስራ እድል ወንድ 1385 እና ሴት 538 በድምሩ 1923 የስራ ዕድል የተፈጠረ ሲሆን በበጀት አመቱ

በመደበኛነት ወንድ 191 እና ሴት 321 በድምሩ 512 ሰራተኞች ከስራ ለቀዋል፡፡ አሁን በአጠቃላይ በመደበኛነት ወንድ 1917

እና ሴት 766 በድምሩ 2,683 ሰራተኞች በቀጥተኛ መንገድ በተፈጠረ ስራ እድል በፓርኩ ውስጥ በስራ ላይ ይገኛሉ፡፡

ሠንጠረዥ 1፡- በበጀት ዓመቱ የተፈጠረ የስራ ዕድል እና የለቀቁ ሰራተኞች

31
በበጀት ዓመቱ የተፈጠረ የስራ ዕድል እና የለቀቁ ሰራተኞች እስከ ሰኔ 30 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ስራ ላይ የሚገኙ ሰራተኞች

የበጀት Reall ሌሎች


የኢ/ፓርኮች ዓመቱ ocate አፈጻጸም የተፈጠረ ጠቅላላ
ተ.ቁ ስም ዕቅድ ወንድ ሴት ድምር d በመቶኛ የለቀቁ ወንድ ሴት ድምር የስራ ዕድል ድምር
1,948
1 ሀዋሳ 28,000 2,357 16,239 18,596 3,694 66% 17,548 4,230 25,580 29,810 31,758

2 ቦሌ ለሚ 20,300 2,095 16,607 18,702 3 92% 15,224 2,301 19,268 21,569 2,583 24,152
3 ኮምቦልቻ 3,500 316 1,827 2,143 166 61% 3,513 243 1,785 2,028 1,010 3,038
4 አዳማ 10,900 858 7655 8,513 382 78% 8614 642 6,166 6,808 993 7,801

5 ድሬዳዋ 3,852 958 2,305 3,263 112 85% 2,347 929 765 1,694 785 2,479
6 ጅማ 400 36 204 240 - 14% 1,368 43 197 240 46 286

7 ደብረብርሃን 2,958 136 2228 2,364 16 80% 1303 170 2,488 2,658 445 3,103

8 ባህርዳር 2,080 12 218 230 - 11% 631 23 706 729 409 1,138

9 ቂሊንጦ 766 - - - - - 50 62 98 160 510 670

10 አ/ኢ/መንደር 1244 411 804 1,215 - 98% 993 638 1,481 2,119 27 2,146

11 ሠመራ 200 - - - - - - - - - 651 651

12 አይሲቲ ፓርክ 1000 1385 538 1923 - 100% 512 1917 766 2683 962 3645
8,564 48,625 57,189 52,103 59,300 10,369 80,867
ድምር 75,200 4,373 57.08% 9,281
70,498
በበጀት ዐመቱ ከዕቅዳቸው አንጻር ቦሌ ለሚ እና አዲስ ኢንዱስትሪ የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው ሲሆን በጅማ፣ ባህርዳር አና
ቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ከዕቅዳቸው አንጻር በጣም ዝቅተኛ በመሆኑ ከኩባንያዎች ወደ ሙሉ የማምረት አቅም
እንዲመጡ ድጋፍ እና ክትትል ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡

በኢንዱስትሪ ፓርኮች ኩባንያዎች ድርጅታቸውን በሚዘጉበት ወይም ሰራተኛ በሚቀንሱበት ወቅት ሰራተኞች ስራ እንዳያጡ
በሌሎች ኩባንያዎች ውስጥ እንዲቀጥሩ (reallocated) የተደረገ ሲሆን በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ 4,373 ሰራተኞች reallocated
የተደረጉ ሲሆን ከፍተኛ reallocated የተደረገው በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ (3,694) ነው፡፡
በኢንዱሰትሪ ፓርኮች ሰራተኞችን ለመቅጠር ብዙ ጥረቶች የተደረገ ቢሆንም በተለያዩ ምክንያቶች የሚለቀው ሰራተኛ
መጨመር፣ በኩባንያዎች በራሳቸው ምክንያት፣ በ AGOA እና በሌሎችም ምክንያት ፋብሪካዎችን የመዝጋት እና ሰራተኞችን
የመቀነስ የተከሰተ ሲሆን በዚህም ፡ -

 በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ PVH (ሼድ ቁጥር 1 እና ሼድ 29)፣ Ontex እና KGG ሼድ በመለቀቅ ሂደት ላይ
በመሆናቸው እንዲሁም Best እና Everest ደግሞ ያላቸውን ሼድ በመቀነሳቸው እና ሌሎች ኩባንያዎችም ሼዶችን
ለመልቀቅ ጥያቄ ያቀረቡ በመሆናቸው የከሰተ ሲሆን
 በተጨማሪም በኢንዱስትሪ ፓርኩ እንደ Indochine፣ Hidramani፣ Best እና Everest ኩባንያዎች ደግሞ ከፍተኛ ቁጥር
ያለው የሰው ኃይል ቀንሰዋል፡፡
 በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ Soufflet እና CGCOC ድርጅቶች ኮንስትራክሽን ላይ የነበሩ ሰራተኞች በመቀነሳቸው
እንዲሁም New Wide ሠራተኛ በመበተናቸው፣
 በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ Antex የተባለ ድርጅት 3 ሼዶችን ለመመለስ በሂደት ላይ የሚገኝ በመሆኑ
 በጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክ Huajian የተባለው ድርጅት ፓርኩን የለቀቀ በመሆኑ ሠራተኞችን መበተናቸው ምክንያት
የሠራተኛ መቀነስ አሳይቷል፡፡
32
 እንዲሁም ኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ በነበረው ጦርነቱ ምክንያት ባለሀብቶች ስራ በማቆማቸው ስራ ዕድል ፈጠራ
ላይ አሉታዊ ተጽእኖ መፍጠር ችሏል፡፡

በ 2014 ዓ.ም የበጀት ዓመቱ ስራ ዕድል ፈጠራ ከ 2013 ዓ.ም ተመሳሳይ ወቅት (56,236) ጋር ሲነጻጸር በ 970 ዝቅ ያለ ነው፡፡
በሌላ በኩል የሰራተኞች ስራ መልቀቅ ከባለፈው ተመሳሳይ ወቅት (41,542) ጋር ሲነጻጸር በ 10,049 ከፍ ያለ ነው፡፡
የስራ እድል ፈጠራ ጥረታችንን አጠናክረን ማስቀጠል፤ ለሰራተኛ መልቀቅ ዋና ምክንያት የሆኑትን እንደ መኖሪያ ቤት አቅርቦት
እና አነስተኛ ደመወዝ ወለል ውሳኔ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መስራት ጠይቃል፡፡ በሌላ በኩል ወደ ምርት ተግባር
ያልገቡ የፋብሪካ ሼዶችና የለማ መሬት ወደ ግንባታ እንዲገቡ በማስቻል የስራ እድል ፈጠራውን ማጠናከር ልዩ ትኩረት
የሚሰጠው ሲሆን ይህንንም ለማስፈጸም ከባለድርሻ አካላት ጋር የተቀናጀ ስራ ማከናወን ትኩረት የሚሰጠው ይሆናል፡፡
ግራፍ 1፡- በበጀት ዓመቱ ውስጥ ስራ ዕድል ፈጠራ እና የሰራተኞች ስራ መልቀቅ

74,200
ዕቅድ አፈጻጸመም የለቀቁ

55,266
51,591
74.5%
28,000

20,300
18,702
18,596
17,548

15,224

10,900
8,614
8,513

3,852
3,500
3,513

3,263

2,958
2,347

2,364
2,143

2,080
1,368

1,303

1,244
1,215
993
766
631
400
240

230

200
50
0

0
0
ሀዋ
ሳ ሚ ቻ
ዳማ ዳ
ዋ ማ
ርሃ
ን ዳር ንጦ ንደ
ር ራ
ለ ቦል አ ሬ ጅ ር ሊ ሠ

ቦሌ ኮ
ም ድ ረብ ባህ ቂ /መ

ደ /ኢ

ከማኑፋክቸሪንግ የስራ ባህሪ አንፃር እስከ 2.5 ቀጥተኛ ያልሆነ የስራ ዕድል እንደሚፈጠር ስለሚታመን በኢንዱስትሪ
ፓርኮች ከፈጠሩት ቀጥተኛ የስራ ዕድል (77,222) አንፃር ሲታይ ወደ 200 ሺህ የሚጠጋ ቀጥተኛ ያልሆነ የስራ ዕድል
ተፈጥሯል፡፡
1.1. በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚገኙ ኩባንያዎች የተፈጠ ስራ ዕድል በዝርዝር
1.1.1. በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የኩባንያዎች የስራ ዕድል ፈጠራ
በበጀት ዓመቱ ውስጥ ለ 28,000 ዜጎች ስራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ ለ 18,596 ዜጎች መፍጠር የተቻለ ሲሆን 17,548
ሰራተኞች ደግሞ ስራ ለቀዋል፡፡ በሌሎች የስራ ዘርፎች ለ 1,948 ስራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡ በኢንዱስትሪ ፓርኩ
ምርትማነት ስራ ላይ በቀጥታ ለሚሳተፉ ለ 29,810 ኦፕሬተሮች የስራ እድል የተፈጠረ ሲሆን በአጠቃላይ
በኢንዱስትሪ ፓርኩ 31,758 ሰራተኞች ስራ ላይ ይገኛሉ፡፡ በመሆኑ ካለፈው ዓመት የሥራ ዕድል ፈጠራ አንፃር
ሲታይ 3209 መቀነስ ያሳየ በመሆኑ በሥራ ላይ ያሉትን ኩባንያዎች መበደገፍና አድስ ባለሃብት እንዲገባ
በ Indochine Apparel Ltd፣ Best International Garment PLC፣ Hela Indochine Appareal LTD፣ Silver Spark እና
Everest የተሻለ የስራ ዕድል የፈጠሩ ኩባንያዎች ሲሆኑ Chargeurs Fashion፣ ITL Apparel labels፣ Jas Holding
Garment እና Quadrant Apparel እስካሁን ፈጠሩት ስራ ዕድል በጣም ዝቅተኛ በመሆኑ ትኩረት የሚፈልግ ጉዳይ
ነው፡፡

33
HIP Yearly job creati on STATUS
total # of workers Hired Resigned
3 13
171 254 284 1,067 1,7971,035
713 974 1,387 705 1,056 1,498
20 20 726 586 16,006
260 2,387
1,010
124 324 480
375 389
680 1,504 4,0441,248 2 18,596
1,3291,918 840
154 20 800 1,558 111 1,083 727
815
132
4946
700 941 904 2194 37
111 325 2599 3015 29843
805 1693
11922514 41841767
225
- 884 783
3
0- 0- 0-
t s i a k l y IC x e t t i L g a ) s L
jo H le ed r l
an p ar Ta r e s en es ir IT in as ts s
In
V n an ge be te EP te in in re ld b ld le TA
P
x ti v i r
ar m s n
ch ch ve
B N en TO
Te Ar u a C h
d a
I s d r a er en O o go
m o am
i v
C d
o d E
u Su S
H
ar
m
Se
P Q H ili In s
J In ng JA G
S a a P
el Ji (J
H G
JP

1.1.2. በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ የኩባንያዎች የስራ ዕድል ፈጠራ


በኢንዱስትሪ ፓርኩ ለ 20,300 ዜጎች ስራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ ለ 18,778 ዜጎች መፍጠር የተቻለ ሲሆን 15,226
ሰራተኞች ደግሞ ስራ ለቀዋል፡፡ በሌሎች የስራ ዘርፎች ለ 2,583 ስራ ዕድል የተፈጠረ ሲሆን በአጠቃላይ በኢንዱስትሪ
ፓርኩ 24,152 ሰራተኞች ስራ ላይ ይገኛሉ፡፡ በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ Jay Jay Garment PLC፣ Shints ETP እና Ashton
ከፍተኛውን የሰው ኃይል የቀጠሩ ኩባንያዎች ሲሆኑ ከዚህ በላይ ክትትል እና ድጋፍ ቢደረግላቸው ከዚህ በላይ ስራ
ዕድል መፍጠር የሚችሉ መሆኑ የሚያሳይ ነው፡፡ በሌለ በኩል Lyu shoutao, Vestis, Arvind እና Anega Energies
የተባሉት ድርጅቶች ሙሉ በሙሉ ስራ እንዲገቡ መደገፍ ይገባል፡፡

BLIP YEARLY JOB CREATION STATUS


100% 5 6 -
90% 2,920 699
483 977 2,575 12 15,224
80% 781 335 4,483
70% 1,960 4,153 68
60% 712 3,297 2,951
221 18,702
50% 996 17
40% 909 82
30% 1,442 3,936
8,888
20% 388 853 929 5,356 60 2,133 21,569
10% 660 452 1,751
0% -
.
nd ti
s ay ao p
ew nt
s EI on
I t
ex ga L
vi s J t r to n i K t B
G
ffle t ne TA
A
r V
e y o u e p Sh sh u ng A TO
Ja Sh Ev To
A So a
u Sh
Ly

total # of workers Hired Resigned

34
1.1.3. በኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ የኩባንያዎች የስራ ዕድል ፈጠራ
በኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ በበጀት ዓመቱ ለ 3,500 አዲስ የስራ ዕድል ለመፍጠር ዕቅድ ተይዞ ለ 2,143 ሰራተኞች
የስራ ዕድል የተፈጠረ ሲሆን 3,513 ሰራተኞች ለቀዋል፡፡ በኢንዱስትሪ ፓርኩ Fuanlai Textile እና Trybus Bridgtex
የተሻለ ስራ ዕድል ፈጠሩ ቢሆንም Carvico እና Pungkook ከዚህ በላይ ስራ ዕድል መፍጠር እንዲችሉ ክትትልና
አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ስለሆነም በተቀመጠው የማበረታቻው ቅድመ ሁኔታ መሰረት
ኩባንያዎችን ክትትል ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

KIP YEARLY JOB CREATION STATUS


100%
8
80% 39 548 700
2257 3513
60%
313 865
40% 2143
98 926
20% 534 704 2028
0%
692
Carvico Ethiopia Pungkook Trybus Bridgtex Fuanlai Textile Total
Ethiopia PLC PLC Ethiopia

total # of workers Hired Resigned

1.1.4. በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የኩባንያዎች የስራ ዕድል ፈጠራ


በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ እስካሁን በምርት ስራ ላይ በቀጥታ ለሚሳተፉ 6,808 ኦፕሬተሮች የሥራ ዕድል
የተፈጠረ ሲሆን በተጨማሪም ለ 993 ለሚሆኑ ዜጎች ኢንዱስትሪ ፓርኩ ውስጥ ባሉ ኩባንያዎች አማካኝነት በቀን
ሰራተኝነት፣ በጥበቃ እና በተለያዩ የስራ መስኮች የስራ ዕድል ተፈጥሮላቸዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ውስጥ ለ 10,900 ዜጎች
ስራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ ለ 8,513 ሰራተኞች የስራ ዕድል የተፈጠረ ሲሆን 8,614 የሚሆኑ ሰራተኞች ኢንዱስትሪ
ፓርኩን ለቀዋል፡፡

በኢንዱሰትሪ ፓርኩ ቻርተር ቬንቸር፣ ኤግል ፓክ፣ ዋይ ኬኬ እና የተወሰኑ የአንቴክስ ሼዶች ወደ ስራ ያለገቡ በመሆኑ
የስራ አድል ፈጠራ ላይ ተፅእኖ የፈጠረ በመሆኑ ኩባንያዎች በመደገፍ እንዲገቡ እና ለመልቀቅ ፍላጎት ባላቸው ላይ
መተካት አስፈላጊ ነው፡፡

35
AIP Yearly JOB CREATION STATUS
100%
90% 11
1,008 1,499 5,294
80% 5,294
70%
60% 61 1,606
50% 4,759
40% 4,759 2,339
30%
20% 1,706 6,524
10% 3,735 27 1,057
0%
Antex Jotun Sunshine Kingdom Total

total # of workers Hired Resined

1.1.5. በድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ የኩባንያዎች የስራ ዕድል ፈጠራ


በድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ ምርታማነት ስራ ላይ በቀጥታ ለሚሳተፉ ለ 1,694 ኦፕሬተሮች የስራ ዕድል የተፈጠረ
ሲሆን በተጨማሪም ለ 785 ለሚሆኑ ዜጎች ኢንዱስትሪ ፓርኩ ውስጥ ባሉ ኩባንያዎች አማካኝነት በቀን
ሰራተኝነት በጥበቃ እና በተለያዩ የስራ መስኮች የስራ ዕድል የተፈጠረላቸው ሲሆን በኢንዱስትሪ ፓርኩ WFP
ተባለው ድርጅት በሌሎች ስራ ዘርፎች ለ 254 (32%) ዜጎች ስራ ዕድል በመፍጠር ድርሻ ይኖረዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ
ውስጥ ለ 3,263 ሰዎች የስራ ዕድል የተፈጠረ ሲሆን 2,347 ሰራተኞች ደግሞ ስራ የለቀቁ ናቸው፡፡

ኤስ ኤንድ ዲ የተባለ ድርጅት የፋብሪካ ሼዱን ለመጋዝንነት እየተጠቀመበት በመሆኑ ዝቅተኛ የስራ እድል
እንዲፈጥር ያደረገው በመሆኑ በመደገፍ ወደ ምርት እንዲገባ ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡ በበጀት ዓመቱ ውስጥ
902,476.00 ዶላር ሽያጭ አከናውኗል፡፡ ኢል አውቶ የተባለው ኩባንያ ሥራ ለመጀመር ዝግጁ እየሆነ በመሆኑ የስራ
አድል ፈጠራ ላይ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡

DDIP Yearly Job Creation Sratus


100% 0 0
90%
226 614 2347
80% 1507
70%
60% 664
50% 359 7 904 3263
40% 1442
30%
20%
10% 222 396 815 254 1694
0%
HAN PLAST S&D Andrea Shoes Wuxi #1 WFP Total

total # of workers Hired Resined

36
1.1.6. በደብረብርሀን ኢነዱስትሪ ፓርክ የኩባንያዎች የስራ ዕድል ፈጠራ
በደብረብርሀን ኢንዱስትሪ ፓርክ ምርት ስራ ላይ በቀጥታ ለሚሳተፉ ለ 2,658 ኦፕሬተሮች የስራ ዕድል የተፈጠረ
ሲሆን በተጨማሪም ለ 436 ለሚሆኑ ዜጎች ኢንዱስትሪ ፓርኩ ውስጥ ባሉ ኩባንያዎች አማካኝነት በቀን
ሰራተኝነት በጥበቃ እና በተለያዩ የስራ መስኮች የስራ ዕድል ተፈጥሮላቸዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ውስጥ ለ 2,364 ሰዎች
የስራ ዕድል የተፈጠረ ሲሆን 1,303 ሰራተኞች ደግሞ ስራ የለቀቁ ናቸው፡፡

DBIP Yearly JOB CREATION STATUS


100% 97 1,303
80% 1,142
64 1,481
60%
1,562 3,050
40% 7
20%
1,277 46 1,335 2,658
0%
EK Kintt Wear PLC Boortmalt Shangcheng Total
ethi.apparal manf.
PLC
total # of workers Hired Resisned

1.1.7. በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ የኩባንያዎች የስራ ዕድል ፈጠራ


በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ በበጀት ዓመቱ ውስጥ ለ 766 ሰዎች አዲስ የስራ ዕድል ለመፍጠር የታቀደ ቢሆንም የፌስ ማስክ
ፍላጎት ከግዜ ወደ ግዜ እየቀነሰ በመምጣቱ ድርጅቶቹ አዲስ የሥራ ዕድል መፍጠር አልቻሉም፡፡ በአሁኑ ጊዜ በርካታ ሰው
በመከተቡና የፌስማስክ አጠቃቀሙም ቀደም ሲል ከነበረው አኳያ በመቀነሱ ኩባንያዎች ተጨማሪ ሠራተኞች መቅጠር
አልቻሉም፡፡ ኢንዱስትሪ ፓርኩ ለ 160 ኦፕሬተሮች እና 510 ደግሞ በተለያዩ የስራ መስኮች ለተሰማሩ ዜጎች በአጠቃላይ እስካሁን
ለ 670 ዜጎች የስራ ዕድል የተፈጠረ ሲሆን በወሩ 50 ሰራተኞች ስራቸውን ለቀዋል፡፡

እስከ ሰኔ ወር 2014 መጨረሻ ስራ ላይ


ተ.ቁ የድርጅቶች ስም የሚገኙ (Operators) ምርመራ
1 Royal Medical 48
2 The New Mellinnium 48
3 TKBD Medical Supplies 17
4 Glocare pharm 47
ድምር 160

1.1.8. ጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የኩባንያዎች የስራ ዕድል ፈጠራ


አክሻይ ጄይን የተባለው ኩባንያ በጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክ አንድ ሼድ ተከራይቶ የአቨካዶ ዘይት በመምረት ሂደት ላይ
የሚገኝ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ለ 240 ዜጎች የስራ ዕድል ፈጥሯል፡፡ ድርጅቱ ምርቱን ለውጭ ሀገር ኤክስፖርት
የሚያደርግ በመሆኑ ክትትል እና አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ አስፈላጊ ሲሆን Huajian የተባለ ድርጅት ስራ
በማቆሙ 1,368 ሰራተኞች ስራ ለቀዋል፡፡

37
እስከ ሰኔ ወር 2014 መጨረሻ ስራ ላይ
ተ.ቁ የድርጅቶች ስም የሚገኙ (Operators) ምርመራ
1 Akshay Jain 240
ድምር 240

1.1.9. ባህርዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ የኩባንያው የስራ ዕድል ፈጠራ


Hoplun ኩባንያ እስከ ሰኔ 2014 ዓ.ም ድረስ ለ 729 የአካባቢው ነዋሪዎች የስራ ዕድል የፈጠረ ቀጥተኛ ቢሆንም ድርጅቱ
ተጨማሪ ሼዶችን ወደ ስራ በማስገባት የምርት መጀመር ሂደት ላይ ባለመሆኑ ኢንዱስትሪ ፓርኩ ለኩባንያው ተጨማሪ
ድጋፍ በማድረግ ወደ ምርት ሂደት እንዲገባ ማስቻል ይጠበቅበታል፡፡ በተጨማሪም ለ 409 ዜጎች በሌሎች የስራ ዘርፎች
በኢንዱስትሪ ፓርኩ ስራ የተፈጠረላቸው ሲሆን በአጠቃላይ ለ 1,138 ሰዎች በስራ ላየ ይገኛሉ፡፡ በበጀት ዓመቱ ውስጥ
ለ 230 ዜጎች ብቻ ስራ ዕድል መፍጠር የተቻለ ሲሆን 631 የሚሆኑ ሰራተኞች ደግሞ ስራ ለቀዋል፡፡
አዲስ የተፈጠረ በወሩ ስራ እስከ ሰኔ ወር 2014 መጨረሻ ስራ ላይ
ተ.ቁ የድርጅቶች ስም ሰራ ዕድል የለቀቁ የሚገኙ (Operators) ምርመራ
1 Hop Lun - - 729
ድምር - - 729

1.1.10. አዲስ ኢንዱስትሪ መንደር


በኢንዱስትሪ መንደሩ ለ 1,244 ዜጎች ስራ ዕድል ለመፍጠር ታቅዶ ለ 1,215 ዜጎች የተፈጠረ ሲሆን በበጀት ዓመቱ 993
ሰራተኞች ስራቸውን ለቀዋል፡፡ በሌሎች ስራ ዘርፎች ለ 27 ዜጎች ስራ ዕድል የተፈጠረ ሲሆን በአጠቃላይ በአሁኑ ጊዜ
ባሉት አስራ አራት ኩባንያዎች ለ 2,119 ሰዎች የስራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡ ድርጅቶቹ በሙሉ አቅመማቸው
እንዲያመርቱ ከፍተኛ ድጋፍ እና ክትትል ይጠይቃል፡፡

AIV Yearly Job creation Status


41 17 0 8 45 73 0 14 993
80% 77 49 34 70 103 146 162 45 113 280 119
126 177 35 1215
40% 24 114 50 21 286 6
207 113 385 257 63 325
0% 18 76 106 301 220 21 2119

on
l t
pt ds tr
y
ra af
t h cy e d al al
em ta en es ot ar ot
a l tt
ris m ce
tar us
a m cr
n Lu g d ez T
el C
o C ar on it In
d T ri
o fi a n T
Z a G C P
e T E
le ed S
ta
ic s ir B
fr ni D
A Yo

Total Hired Resigned

1.2. የሰራተኞችን ስራ የመልቀቅ ምጣኔ ለመቀነስ የተከናወኑ ስራዎች


የኢንዱስትሪ ፓርክ የፋብሪካ የሰራተኞች ስራ የመልቀቅ ምጣኔን ለመቀነስ ሠራተኞች የመኖሪያ ቤት አቅርቦት
ችግር ዋነኛው ተግዳሮት በመሆኑ ይህንኑ ለመቅረፍ ኮርፖሬሽኑ ኮርነርስቶን ዴቨሎፕመንት ከተባለ ኩባንያ ጋር
የውል ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን ስምምነቱም በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የፋብሪካ ሰራተኞች መኖርያነት

38
የሚያገለግል አስራ ሶስት የ Dormitory ህንጻዎችን ገንብቶ ለፋብሪካ ሰራተኞች መኖሪያነት ለማዋል በእንቅስቃሴ
ላይ ይገኛል፡፡ እንዲሁም በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ Antex Textile PLC የተባለ ድርጅት ለሠራተኞች መኖሪያ
ቤት ለማቅረብ ፍላጎትን ያቀረበ ሲሆን ግንባተ አልጀመረም፡፡
በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ Shints ETP Garment የተባለ ኩባንያ የሰራተኞች መኖሪያ ቤት ግንባታ አጠናክሮ
የቀጠለ ሲሆን ባለፉት ሁለት ዓመታት ጀምሮ 2,707 የሚሆኑ ሰራተኞች በህንፃዎች በመኖር ላይ የሚገኝ ሲሆን
በሌሎች ኢንዱስትሪ ፓርኮችም የሠራተኞችን የመኖርያ ቤት ችግር ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡

በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ በሚገኙ አምራች ድርጅቶች ተቀጥረው የሚሰሩትን ሰራተኞች የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል
የህብረት ስራ ማህበር (Worker’s Cooperative) ህጋዊ እውቅና ኖሮት እንዲቋቋም የተደረገ ሲሆን ራሱን በራሱ የመምራትና
ሙሉ በሙሉ የማስተዳደር አቅም እስኪፈጥር ድረስ የማደራጀት፣ የመስሪያ ቦታና ቁሳቁስ ድጋፍ ከኢንዱስትሪ ፓርኩ እንዲሁም
ለመነሻ ካፒታል በአይ ዲ ኤች (IDH) በኩል ብር 1,451,325.44 ድጋፍ ተደርጓል፡፡ በዚሁ መሠረት ማህበሩ ስድስት ሠራተኞች
ሲኖሩት እነሱም አንድ ሥራ አስኪያጅ፣ አንድ ሴክሬታሪ፣ አንድ የግዢ፣ አንድ የሂሣብ ሠራተኛ እንዲሁም ሁለት የሽያጭ ባለሙያ
ናቸው፡፡ የመስሪያና ማከፋፈያ ቦታ በኢንዱስትሪ ፓርኩ በኩል የተመቻቸ ሲሆን ኅብረት ሥራ ማህበሩ በህዳር ወደ ሥራ ገብቶ
ለተጠቃሚዎች የዳቦ ዱቄት፣ ስኳር፣ ፓስታ፣ዘይት እና ማካሮኒ ግብዓቶች ለአባላት የማከፋፈል ስራ ይገኛል፡፡ የሠራተኞች
የኅብረት ስራ ማህበር (Workers Cooperative) በዓመቱ ውስጥ 6,000 የፓርኩ ሰራተኞችን ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ
እስካሁን 4549(ወ =1282 እና ሴ = 3,267) ሠራተኞች የሕብረት ስራ ማህበሩ አባል ሆነው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እየሆኑ
ይገኛሉ፡፡ ይህም አፈጻጸሙ 75.8% ነው፡፡ የባለሀብቶች የፋይናንሺያል ድጋፍ አለማድረግ እና የአባላት ዝቅተኛ የኢኮኖሚ አቅም
የማህበሩ የፋይናንሺያል ዘላቂነትና አዳዲስ አባላት ማፍራት ላይ መሰረታዊ ችግር እየፈጠረ ይገኛል፡፡ ችግሩን በዘላቂነት
ለመፍታት ይቻል ዘንድ ከተለያዩ አጋር አካላት (ከሚመለከታቸው የመንግስት የልማት ድርጅቶች፣ የመንግስት ተቋማት፣
መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት እና በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ከሚሰሩ ባለሃብቶች) ጋር ውይይት ለማድረግ የተቻለ ሲሆን
በዚህም ከ 16 ተቋማት 21 ግለሰቦች ተሳታፊ ሆነው ውይይት የተደረገ ቢሆንም ካለው ችግር አኳያ ውይይቱ በቀጣይነት በትኩረት
መሰራት ይኖርበታል፡፡

በአጠቃላይ በኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚደረጉ ማህበራዊ ድጋፍ እና አቅም ግንባታ ስልጠና ዙሪያ የተከናወኑ ስራዎች
የሰራተኞችን ስራ መልቀቅ ምጣኔው ከመቀነስ አንጻር ትልቅ ሚና ይኖረዋል፡፡

ግብ 3፡ የወጪ ንግድ ገቢን ማሳደግ

ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ከለሙበት አንዱና ዋናው ዓላማ ስትራቴጅካዊ ተኪ ምርቶችን በማምረት የአገር ውስጥ ፍላጎትን
በማሟላትና የውጭ ምንዛሬ ጫና መቀነስ ሲሆን ይህን ግብ ለማሳካት የሜንቴናስ ወርከ ሾፖችን የማደራጀት፣ ጥገናዎችን
የማከናወን፣ የኤሌክትሪክ፣ ውሀ፣ ቴሌኮም እና የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስፈላጊ ግብዓቶችን ለማሟላት ጥረት ተደርጓል፡፡
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ጥገና እና ዎርክሾፕ ለማቋቋም የሚያስችል የ Maintenance Operation Procedure እና Setting-up a
Workshop ሰነድ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኝ በመሆኑ ቀጣይ ዎርክሾፕ ለማቋቋም ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል፡፡ በበጀት ዓመቱ
ውስጥ ጥገና ስራዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ዎርክሾፕ በ 7 ኢንዱስትሪ ፓርኮች በማቋቋም ስራ ላይ ለማዋል ታቅዶ በ 3
ኢንዱስትሪ ፓርኮች (ቦሌ ለሚ፣ ኮምቦልቻ እና ሀዋሳ) አበረታች ስራዎች እየተከናወኑ የሚገኙ ሲሆን አፈጻጸሙ 43% ብቻ ነው፡፡
ባህርዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ የዎርክሾፕ ግንባታ የተጠናቀቀ ሲሆን መለዋወጫ ማሟላት ላይ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል፡፡ አዳማ

39
መለዋወጫ ዕቃዎች ማሟላት ጠጀመረ ቢሆንም ገና ብዙ የሚቀረው ሲሆን እና ድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ መለዋወጫ ዕቃዎች ግዥ
በተወሰነ ደረጃ ማከናወን ተችሏል፡፡ በተጨማሪም ዎርክሾፕ በማቋቋም ሂደት ላይ ያጋጠመውን ችግር እና መልካም ተሞክሮዎች ላይ
ያተኮረ ውይይት በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከስምንት ኢንዱስትሪ ፓርኮች የተወጣጡ ባለሙያዎች እና ኃላፊዎች የተሳተፉ ሲሆን
ለሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች ለሚገጥማቸው ችግር አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ችግር ፈቺ የሆነ 11 አባላት ያሉት የባለሙያ ቡድን
ለማቋቋም ተችሏል፡፡

በበጀት ዓመቱ ውስጥ በባለሀብቶች የሚቀርቡ የፋሲሊቲ እና የጥገና ጥያቄዎችን 100% ምላሽ ለመስጠት ታቅዶ ከቀረቡት 241
የጥገና ጥያቄዎች ለ 2,169 ምላሽ ሲሆን አፈጻጸሙ 88% ነው፡፡ ከቀረቡት ጥያቄዎች 292 የጥገና ጥያቄዎች በተጠየቀው ጊዜ ምላሽ
ያላገኙ ሲሆን ለጥገና የሚያስፈልጉ በቂ መለዋወጫ መሳሪያዎች ባለመሟላታቸው እና የጥገና ዎርክ ሾፕ ባለመኖሩ ከዕቅዱ በታች
መፈጸም ተችሏል፡፡ ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እና ጥገና አንፃር ኮርፖሬሽኑ ሊመራበት ወይም ሊፈፅመው የሚችለውን ተግባር
በሚመለከት በኮርፖሬሽኑ ደረጃ የጥናት ቡድን ተቋቁሞ የጥናት ሰነድ በቀረበው መሠረት በኢንዱስትሪ ፓርኮች ደረጃ አደረጃጀቱን
የመፈተሽ፣ የማይጠገኑ ሰራዎችን የሚያከናውን አውት ሶርስንግ ሰራዎችን የመለየት፣ ልምድ ያላቸው ባለሙያዎችን የማሰባሰብ ስራ
ለማከናወን ጥረት እየተደረገ ስለሆነ ለዚህም ኢነርጂ ጥናት እና አቅርቦት መምሪያ በልማት ዘርፍ ስር የነበረው ወደ ኢንዱስትሪ ፓርኮች
ኦፕሬሽን ዘርፍ እንዲጠቃለል ተደርጓል፡፡ በኢንዱስትሪ ፓርኮች የተከናወኑ በሜካኒካል፣ በኤሌክትሪካል፣ በሳኒተሪ፣ በኮንስትራክሽን፣
በእሳት አደጋ መከላከያ መሳሪያዎች፣ ቴሌኮም እና ኢቲፒ የጥገና ስራዎች ከዚህ በታች በሠንጠረዥ ቀርቧል፡፡

ሠንጠረዥ 2፡- ዝርዝር የተከናወኑ የጥገና ስራዎች

የቀረቡ የጥገና ጥያቄዎች አፈጸጸም


ተ.ቁ የቀረቡ የጥገና ዓይነት ብዛት የተጠገኑ ብዛት ያልተጠገኑ ብዛት በመቶኛ
1 የውሃ ሲስተም 275 234 41 85%
2 ሜካኒካል ሲስተም 253 197 56 78%
3 ኤሌክትሪካል ሲስተም 573 516 57 90%
4 ሳኒታሪ ሲስተም 518 453 65 87%
5 የእሳት አደጋ መከላከል 424 396 28 93%
6 ግንባታ 333 296 37 89%
7 ቴሌኮም 85 77 8 91%
ድምር 2,461 2,169 292 88%

2.2. የኤሌክትሪክ፣ የውሃ እና የቴሌኮም አገልግሎቶች በጥራት ማቅረብ

2.2.1. የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት


በበጀት ዓመቱ ውስጥ የኃይል አቅርቦት በኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ሳይቆራረጥ እንዲቀርብ የቅድመ ጥንቃቄና
በኢንዱስትሪ ፓርኮች አቅም ሊከናወኑ የሚችሉ የጥገና ስራዎችን በማከናወን አገልግሎቱን ለማሻሻል ጥረት
ተደርጓል፡፡ የአዲስ ኢንዱስትሪ መንደር የኤሌክትሪክ መስመር ለአደጋ ተጋላጭነት ለመቀነስ እና ዘላቂ መፍትሄ
እንዲያገኝ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በደብዳቤ በማሳወቅ መንገድ አቋርጠው የሚያልፉት
የኤሌክትሪክ መስመሮች በመሬት ውስጥ እንዲያልፉ እና የእንጨት የኤሌክትሪክ ፖሎችን ወደ Concrete Pole
ዝርጋታ ለማስጀመር ጥረት እየተደረገ የሚገኝ ቢሆንም ስራውን ለማስጀመር ከሚገባው በላይ ጊዜ ወስዷል፡፡

40
በተጨማሪም በየኢንዱስትሪ ፓርኮቹ የተቋቋሙት የሜንትናንስ ቡድን የሚገጥሙትን ችግሮች በመፍታት እና
የ Preventive ስራዎች ተከናውነዋል፡፡
ሠንጠረዥ 4፡- በበጀት ዓመቱ በኢ/ፓርኮች ያጋጠመ የኃይል መቆራረጥ ችግር
የኃይል መቆራረጥ
ተ.ቁ ኢንዱስትሪ ፓርክ ስም በቀን በሰዓት በደቂቃ
1 ሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ 2 26 132
2 ቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ 9 5 20
3 አዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ 28 25 111
4 ባህርዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ 5 12 42
5 ቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ 3 47 -
6 ኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ 10 33 40
7 ደብረብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ 3 41 12
8 አዲስ ኢንዱስትሪ መንደር 7 - -
9 ድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ - 38 37
ድምር 67 227 394

በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ ውሰጥ በ 9 ኢንዱስትሪ ፓርኮች ለ 67 ቀን ከ 227 ሰዓት ከ 394 ደቂቃ (ለ 76 ቀናት ከ 17

ሰዓት ከ 57 ደቂቃ) የኃይል መቆራረጥ ችግር ተከስቷል፡፡ በእነዚህ ቀናት ውስጥ በካምፓኒዎች ምርታማነት ላይም

ሆነ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ ግምት ውስጥ ያስገባ መፍትሄ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን

ሊሰጠው የሚገባ ሲሆን በአጠቃላይ የአቅርቦቱ አፈጻጸሙ 99% ይሆናል፡፡

2.2.2. የውሃ አቅርቦት


በበጀት ዓመቱ ውስጥ በኢንዱስትሪ ፓርኮች የመጠጥ ውሃ አገልግሎት ሳይቋረጥ በጥራት ለማቅረብ እና
የባለሀብቶችን የምርት ሂደት እንዳይስተጓጉል የተጣራ ውሃ በማቅረብና የጥገና ስራዎች በመስራት በስምንት
ኢንዱስትሪ ፓርኮች 1,707,563 ሜ 3 ውሃ የቀረበ ሲሆን የውሃ አቅርቦቱ በሚቋረጥበት ወቅት ድርጅቶች ሳይቸገሩ
ከሌላ ቦታ እንዲያቀርቡ የተደረገበት ሁኔታ በመኖሩ አገልግሎቱ ሙሉ በሙሉ በተጀመረባቸው ኢንዱስትሪ ፓርኮች
(ሀዋሳ፣ ቦሌ ለሚ፣ ኮምቦልቻ፣ ደብረብርሃን እና ባህርዳር) በበጀት ዓመቱ ውስጥ የመቆራረጥ ችግር በመኖሩ
የአቅርቦቱ አፈጻጸም 98% ይሆናል፡፡ የውሃ አቅርቦት ችግር ባለባቸው ኢንዱስትሪ ፓርኮች ፓርኮች (አዳማ እና
ድሬዳዋ) በቦቴ እንደሚያቀርቡ ይታወቃል፡፡ በዚህም በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ለመጠጥ ውሃ አቅርቦት 244,178.21
ብር፣ ድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ 52,499.58 ብር እና አዳማ ኢንዱስትሪፓርክ 454,299.11 ብር ከሶስቱ ኢንዱስትሪ
ፓርኮች 750,976.90 ብር ወጪ ሆኗዋል፡፡ በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የውሃ አቅርቦት ችግርን ለመቅረፍ
በኢንዱስትሪ ፓርኩ ውስጥ አንድ ጉድጓድ ተቆፍሮ ውሃ የተገኘ ቢሆንም የዝግጀት እና ተከላ በመዘግየቱ ምክንያት
ውሃውን መጠቀም አልተቻለም፡፡ ስለሆነም ቀጣይ ስራዎች በጊዜ እንዲጠናቀቁ ክትትል ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በሌላ
በኩል በድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ የውሃ አቅርቦት አበረታች ውጤት የተገኘ ሲሆን ቀሪ መጠናቀቅ የሚገባቸውን
በማጠናቀቅ ሙሉ በሙሉ አገልግሎቱ እንዲጀምር ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡ የውሃ አቅርቦት ችግር ምክንያት
ባለሀብቶች ከፍተኛ ችግር ላይ በመሆናቸው የሼድ ኪራይ ክፍያም ለመክፈል እንደሚቸገሩ በመግለፅ ላይ ናቸው፡፡
41
በኮርፖሬሽኑ በኩል ውሃ ለማቅረብ ጥረት እየተደረገ ቢሆንም በተያዘው ዕቅድ መሰረት ማጠናቀቅ ባለመቻሉ
ቀጣይ ትኩረት የሚያስፈልገው ተግባር ነው፡፡ በበጀት ዓመቱ ውስጥ ዝርዝር የውሃ አቅርቦት መጠን እንደሚከተለው
በሠንጠረዥ ቀርቧል፡፡

ሠንጠረዥ 3፡- የበጀት ዓመቱ ውሃ አቅርቦት


ተ.ቁ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ስም የውሃ አቅርቦት በሜ 3
1 ሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ 1,130,661
2 ቦሌ ለሚ ኢንዱስት ፓርክ 310,983
3 ኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ 96,692
4 ደብረብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ 134,994
5 ባህርዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ 16,911
6 አዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ 2,780.88
7 ጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክ 8,053.00
8 ቂሊንጦ 6,488
ድምር 1,707,563

2.2.3. የቴሌኮም አገልግሎት


በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ አስተማማኝ የሆነ የቴሌኮም አገልግሎት በአግባቡ እንዲቀርብ የውስጥ
ሜንቴናንስ ስራዎችን በማከናወንና ከኢትዮ - ቴሌኮም ጋር በጋራ በመስራት የቴሌኮም አገልግሎት በጥራት
ለማቅረብ ጥረት ተደርጓል፡፡ በዘጠኝ ወራት ውስጥ የቴሌኮም አገልግሎቱ ባለሀብቶችን ለችግር የሚያጋልጥ
ባለመከሰቱ የአቅርቦቱ አፈጻጸም 100% ይሆናል፡፡

2.3. የአንድ ማዕከል አገልግሎት አሰጣጥ


በአንድ ማዕከል አገልግሎት ዙርያ የሚታዩትን ችግሮች ለመቅረፍ ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን እና ከኮርፖሬሽኑ
ከፍተኛ አመራር ደረጃ ውይይት የተካሄደ ሲሆን በውይይቱም በማዕከሉ የአገልግሎት አሰጣጥ እና ቅንጅታዊ አሰራር
ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበት መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ደረጃ የአንድ ማዕከል
አገልግሎት አሰጣጥ እንዲሻሻል አገልግሎቱን ከሚሰጡ ተቋማት ጋር የጋራ ውይይቶችን በማድረግ በኢንዱስትሪ
ፓርኮቹ ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር የተያያዙ ችግሮችን ለመፍታት ጥረት ተደርጓል፡፡ ለአንድ ማዕከል አገልግሎት ሰጪ
ተቋማት ቢሮ ማዘጋጀት እና የቢሮ ቁሳቁሶችን የማሟላት ስራ በቅርቡ ወደ ስራ በገቡ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ቢሮ
የማመቻቸት እና የቢሮ ዕቃዎችን የማሟላት ስራዎች ተከናውኗል፡፡

በኢንዱስትሪ ፓርኮች አገልግሎት አሰጣጥ ዙርያ ባለፉት ወራት በሰባት ኢንዱስትሪ ፓርኮች በሚገኙ 38
ኩባንያዎች ላይ በኢንዱስትሪ ፓርኩ እና በባለድርሻ አካላት በሚሰጡ አገልግሎቶች ዙርያ የባለሀብቱን እርካታ
በመለካት አንድ የጥናት ሰነድ የተከናወነ ሲሆን ጥናት የተካሄደባቸው ኢንዱትሪ ፓርኮች እንዲደርሳቸው ተደርጓል፡፡
42
በጥናት ሰነዱ እንደሚያመላክተው አጠቃላይ ባለሀብቶቹ በኢንዱስትሪ ፓርኮች በሚቀርቡት አገልግሎቶች ላይ
73% መርካታቸውን የገለጹ ቢሆንም በተለይ በሰራተኞች የመልቀቅ ምጠኔ፣ በውሃ አቅርቦት፣ የጥገና አገልግሎት
ጥራት ማነስ እና በብሄራዊ ባንክ FDI ላይ ባወጣው መመርያ ላይ ቅሬታ እንዳላቸው ያሳያል፡፡ ስለሆነም በጥናት
ውጤት መሰረት ኢንዱስትሪ ፓርኮች በተነሱት ችግሮች ዙርያ ባለሀብቶችን ለማርካት መስራት ይጠበቅባቸዋል፡፡
በኢንዱስትሪ ፓርኮቹ የባንክ አገልግሎት ለማሻሻል የግል ባንኮች አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ለማድረግ
ከኮርፖሬሽኑ ከኦሮሚያ ኅብረት ስራ ባንክ እና የአዋሽ ባንክ ጋር የተፈጠመው የውል ስምምነት እንደሚከተለው
በዝርዝር ቀርቧል፡፡

ሠንጠረዥ 4፡- በበጀት ዓመቱ በባንኮች የተከራየ ቢሮ

ተ.ቁ ኢንዱስትሪ ፓርክ ስም ውሉን የፈረመ የባንክ ስም ስፋት በሜ 2 ምርመራ


አዋሽ ባንክ 90.19
1 አዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ
ኦሮሚያ ኅብረት ስራ ባንክ 58.6
2 ድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ አዋሽ ባንክ 92
“ 112.36 በሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች የርክክብ
3 ሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ
ኦሮሚያ ኅብረት ስራ ባንክ 42 ስራ ተሰርቷል፡፡ የ Awash Bank 79.66
“ 140.57 ሜ 2 ስፋት ያለው ውል ቢፈርምም
4 ቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ
ኦሮሚያ ኅብረት ስራ ባንክ 140.57 ርክክብ አድርጎ ወደ ወደ ስራ ባለመግባቱ
5 ኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ አዋሽ ባንክ 138.25 termination ደብዳቤ እንዲደርስ ተደርጎ
6 ቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ “ 112 ንግድ ባንክ እንዲወስድ ተደርጓል፡፡
7 ደብረብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 134.5
8 ባህርዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ አዋሽ ባንክ 91
ድምር - 1,152.04

2.4. ቀጥተኛ የኤክስፖርት አፈጻጸም


ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶች በስፋት እንዲመረቱ እና ጥራታቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በማስቻል የውጭ
ምንዛሬ አቅምን ማሳደግ ኮርፖሬሽኑ የተቋቋመበት ዋና ዓላማ አንዱ እንደሆነ የሚታወቅ ሲሆን በ በጀት ዓመቱ ውስጥ
በኢንዱስትሪ ፓርኮች በሚከናወኑ የምርት አቅም እና ውጤታማነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት ለማከናወን የተለያዩ
ስራዎች ተሰርቷል፡፡ በበጀት ዓመቱ ውስጥ ከ 9 ኢንዱስትሪ ፓርኮች 212,255,619.46 አሜሪካን ዶላር የሚያወጣ
ምርት እንዲመረት ታቅዶ 179,493,664.69 የአሜሪካን ዶላር የሚያወጣ ምርት በማምረት ኤክስፖርት እንዲደረግ
ክትትል እና አስፈላጊውን ድጋፍ የተደረገ ሲሆን የወጪ ንግድ አፈጻጸሙ ከዕቅዱ አንጻር 84.5% ነው፡፡
 ለዕቅዱ መነሻ የነበረው የኢንዱስትሪ ፓርኮች ሰራተኞች መርታማነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ
መምጣቱ፣ ኩባንያዎች ከገዢዎች ትዕዛዝ በስፋት በማግኘት ላይ በመሆናቸው እና ኩባንያዎች የፋብሪካ
ሼዶችን የመጠቀም አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ታሳቢ ተደርጎ የነበረ ቢሆንም በሀገራችን
በተከሰተው ግጭት አማካይነት የገዥዎች ትዕዛዝ በየጊዜው እየቀነሰ እና እየተሰረዘ መምጣቱ እና
ከመስከረም ወር 2014 ዓ.ም የአሜሪካ መንግስት የኢትዮጵያን ከቀረጥ ነፃ ጥቅም ለማስቀረት የጊዜ ገደብ
በማስቀመጡ እያንዳንዱ ኩባንያዎች ቢዝነሳቸውን (በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚገኘው PVH) ለመዝጋት
ተገዷል፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ ኩባንያዎች እያመረቱ ያሉት ከዕግዱ በፊት የተሰጣቸውን ትዕዛዝ ለማሟላት
መሆኑ እና ገዢዎች ትዕዛዝ ሊቀንስ ስለሚችል በመንግስት በኩል ልዩ ትኩረት እና ድጋፍ ሊሰጥ እንደሚገባ

43
የሚያመላክት ነው፡፡ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ በትራንሽን፣ በአፍሪኮም፣ እና በኢማጃክ፣ በበጀት
አመቱ ከውጭ ንግድ ገቢ 16,847,464.81 የአሜሪካን ዶላር ማግኘት ተችሏል፡፡

ሠንጠረዥ 4፡- በበጀት ዓመቱ ውስጥ የኢ/ፓርኮች የኤክስፖርት አፈጻጸም

ተ.ቁ ኢንዱስትሪ ፓርክ ኤክስፖርት ዕቅድ አፈጻጸም አፈጻጸም በመቶኛ


1 ሀዋሳ ኢ/ፓርክ 113,310,623.00 90,634,612.00 80%
2 ቦሌ ለሚ ኢ/ፓርክ 57,467,765.00 51,145,193.00 89%
3 ኮምቦልቻ ኢ/ፓርክ 10,099,638.33 9,877,485.07 98%
4 አዳማ ኢ/ፓርክ 15,894,123.00 15,832,114.71 99%
5 ድሬዳዋ ኢ/ፓርክ 7,588,929.70 5,154,396.00 68%
6 ባህርዳር ኢ/ፓርክ 1,962,596.57 572,200.00 29%
7 ደብረብርሃን ኢ/ፓርክ 2,729,923.86 2,323,684.00 85%
8 አዲስ ኢ/መንደር 1,487,920.00 1,953,979.91 100%+
9 ጅማ ኢ/ፓርክ 1,714,100.00 2,000,000.00 100%+
10 ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ 33,636,491.74 16,847,464.81 50.08%
ድምር 212,255,619.46 179,493,664.69 84.5%
2.

አብዛኛዎቹ ኢንዱስትሪ ፓርኮች የኤክስፖርት አፈፃፀም የተሻለ ቢሆንም ባህርዳር፣ ጅማ እና የደብረብርሃን ኢንዱስትሪ
ፓርኮች ሌሎች ድርጅቶች ወደ ስራ ባለመግባታቸው እና ሼድ አጠቀቃም ላይ ዝቅተኛ በመሆኑ የኤክስፖርት
አፈጻጸማቸው ከዕቅዱ አንጻር ዝቅተኛ ነው፡፡ በቀጣይ ሌሎች ድርጅቶችን ወደ ስራ ማስገባት እና የድርጅቶች ሼድ
አጠቃቀም (Shed Utilization) ላይ በትኩረት መስራት ያስፈልጋል፡፡ በአጠቃላይ በ 2014 ዓ.ም የበጀት ዓመቱ ኤክስፖርት
ምርት መጠን ከ 2013 ዓ.ም ተመሳሳይ ወቅት (181,692,971.81) ጋር ሲነጻጸር በ 2,199,308.19 ዶላር ዝቅ ያለ ነው፡፡

ግራፍ 2፡- ቀጥተኛ የበጀት ዓመቱ ኤክስፖርት አፈጻጸም

212,255,619.
An n u a l E xp o r t Pe r fo r ma n c e

179,493,664.
46
ዕቅድ አፈጻጸም 84.5%
69
113,310,623.0
90,634,612.00

57,467,765.00
51,145,193.00
0

15,894,123.00
15,832,114.71
10,099,638.33
9,877,485.07

7,588,929.70
5,154,396.00

2,729,923.86
2,323,684.00

2,000,000.00
1,962,596.57

1,953,979.91

1,714,100.00
1,487,920.00
572,200.00

ሀዋሳ ቦሌ ለሚ ኮ ምቦ ል ቻ አዳማ ድሬዳ ዋ ባ ህር ዳ ር ደብ ረብ ርሃ ን አ/ ጅማ ድምር


ኢ/
መን ደር

አብዛኛዎቹ ኢንዱስትሪ ፓርኮች የኤክስፖርት አፈፃፀም የተሻለ ቢሆንም የአዳማ እና ባህርዳር ኢንዱስትሪ
ፓርኮች የኤክስፖርት አፈጻጸም በጣም ዝቅተኛ በመሆኑ በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶት መስራት ያስፈልጋል፡፡

44
የሀዋሳ ኢ/ፓርክ ኩባንያዎች የኤክስፖርት አፈፃፀም

Export in USD
90,634,612
JPG(JP Garments) 746,373
2,009,975
JAS 3,008,822
133,993
Sumbiri 3,998,760
7,491,753
Jiangsu (KGG) 181,278
2,206,760
Indochine 17,532,268
6,395,733
Ontex 138,083
5,203,734
Centery 1,217,081
8,900,887
Siliver spark 6,436,197
5,094,492
Isabela 4,173,754
232,631
Arvined 1,989,376
8,544,497
PVH 4,998,165
- 20,000,000 40,000,000 60,000,000 80,000,000 100,000,000

በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የበጀት ዓመቱ የኤክስፖርት አፈፃፀም 90,634,612.00 (80%) ሲሆን Indochine Apparel Ltd፣
JP Textile(Ethiopia)፣ Tal Garment PLC፣ Siliver Spark፣ PVH Manufacturing PLC፣ Hela Indochine እና Best በአንፃራዊ
የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው ናቸው፡፡ እንዲሁም (ITL Apparel Labelling Solution PLC እና Ontex Hygienic Disposal PLC)
አነስተኛ አፈጻጸም ያሳዩ ኩባንያዎች ናቸው፡፡ ምንም እንኩዋን የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የ AGOA ተጽዕኖ ከኩባንያዎች
መልቀቅ አንጻር ከፍተኛ ቢሆንም የበጀት ዓመቱ የኤክስፖርት አፈጻጸሙ አበረታች መሆኑን ያሳያል፡፡ ነገር ግን ይህን
አፈጻጸም ለማስቀጠል የተለቀቁ ሼዶቸን የማስያዝ እና የተያዙት ሼዶችንም ድጋፍ በማድረግ የተሻለ ስራ መስራት
ይጠይቀል፡፡

የቦሌ ለሚ ኢ/ፓርክ ኩባንያዎች የኤክስፖርት አፈፃፀም

45
BLIP Yearly Export in USD
Total 51,145,193
Shangtex 344,859
Ashton 4,031,087
Shints 8,317,177
Top new 1,027,291
Evertop 2,750,427
Lyu shoutao 2,478,179
Jay Jay 28,180,890
Vestis 238,663
Arvind 3,776,621
- 10,000,000 20,000,000 30,000,000 40,000,000 50,000,000 60,000,000

በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ የበጀት ዓመቱ የኤክስፖርት አፈፃፀም 51,145,193.00 (89%) ሲሆን Jay Jay፣ Shints፣
Ashoton እና Arvind Lifestyle Apparel Manufacturing PLC በበጀት ዓመቱ ውስጥ የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው ኩባንያዎች
ናቸው፡፡ በቦሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ የኤክስፖርት አፈጻጸማቸው አነስተኛ የሆኑ ኩባንያዎችን እንደ Vestis ኩባንያዎች
ክትትል እና ድጋፍ ማድረግ ይጠይቃል፡፡

የኮምቦልቻ ኢ/ፓርክ ኩባንያዎች የኤክስፖርት አፈፃፀም

KIP Yearly Export in USD

Total 9,877,484

Fuanlai Textile Ethiopia 557,435

Trybus Bridgtex PLC 585,654

Pungkook Ethiopia PLC 1,012,642

Carvico Ethiopia 7,721,753

- 2,000,000 4,000,000 6,000,000 8,000,000 10,000,000 12,000,000

ከላይ በቻርቱ እንሚያሳየው በኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ የበጀት ዓመቱ የኤክስፖርት አፈጻጸም 9,877,484.00
(98%) ነው፡፡ በአካባቢው በነበረው ጦርነት ምክልያት ስራ ያቆሙ ድርጅቶች በአፈጣኝ እንዲጀምሩ በኮርፖሬሽኑ
በኩል ከፍተኛ ስራ የተሰራ ከመሆኑም ባሻገር ለኩባንያዎቹ የሰባት ወር የሼድ ኪራይ ማበረታቻ ያደረገ ሲሆን
ኩባንያዎቹ በተዘጉበት ወቅት ለነበረው የሼድ ኪራይ የእፎይታ ግዜ በመስጠት እና ለተጨማሪ አራት ወራት ደግሞ
ከጦርነቱ በፊት የነበራቸውን የሰው ሀይል እንዲቀጥሩ በተቀመጠው ቅድመ ሁኔታ መሰረት እየታየ ተፈጻሚ የሚሆን

46
ነው፡፡ በአጠቃላይ ኮርፖሬሽኑ የኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ ወደ ቀድሞ የማምረት አቅሙ እንዲመለስ ከፍተኛ
ጥረት እያደረገ ነው፡፡

የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ኩባንያዎች የኤክስፖርት አፈፃፀም

AIP Yearly Export in USD

Total 15,832,114.71

kingdom 4,458,617.63

Sunshine 1,548,154.57

Antex 9,825,342.51

0.00 5,000,000.00 10,000,000.00 15,000,000.00 20,000,000.00

የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የኤክስፖርት አፈፃፀም 15,832,115.00 (99%) ሲሆን ኢንዱስትሪ ፓርኩ ከዚህ የተሻለ አፈጻጸም
እንዲኖር ሌሎች ድርጅቶች ኤክስፖርት ማድረግ እንዲጀምሩ ክትትል እና አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
በተጨማሪም አገልግሎት ላይ ያልሆኑ የፋብሪካ ሼዶች ወደ ስራ እንዲገቡ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

የድሬዳዋ ኢ/ፓርክ ኩባንያዎች የኤክስፖርት አፈፃፀም

የድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ አፈፃፀም ከዕቅዱ አንፃር 5,154,396.00 (68%) ሲሆን አጠቃላይ ከሼድ መያዝ አቅም
አንፃር ሲታይ ገና ብዙ ስራ የሚጠይቅ ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ Wuxi No. 1 Cotton ከአጠቃላይ ኤክስፖርቱ 75%
ኤክስፖርት አድርጓል፡፡

DDIP Yearly Export in USD

Total 5,154,396

Wuxi #1 4,165,374

Andrea Shoes 575,272

HAN PLAST 413,750

- 1,000,000 2,000,000 3,000,000 4,000,000 5,000,000 6,000,000

የደብረብርሃን ኢ/ፓርክ ኩባንያዎች የኤክስፖርት አፈፃፀም

የኩባንያ ስም የኢንዱስትሪ ፓርኩ ስም እሰከ ሰኔ ኤክስፖርት በአሜሪካን ዶላር


47
1 EK ደብረ ብርሀን ኢ/ፓርክ 2,323,684.00

በደብረብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ እስካሁን ሼድ ከተከራዩት ኩባንያዎች EK KNITTING PLC ብቻ ኤክስፖርት


(2,323,684.00) የተደረገ ሲሆን አፈጻጸሙ 85% ይሆናል፡፡ በቅርቡ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የገባው Shangcheng
የተባለው ኩባንያ በአፋጣኝ ወደ ምርት እንዲገባ ኢንዱስትሪ ፓርኩ ክትትል እና ድጋፍ ሊያደርግ ይገባል፡፡

የጅማ ኢ/ፓርክ ኩባንያዎች የኤክስፖርት አፈፃፀም

የኩባንያ ስም የኢንዱስትሪ ፓርኩ ስም እሰከ ሰኔ ኤክስፖርት በአሜሪካን ዶላር


2 Akshay ጅማ ኢ/ፓርክ 2,000,000.00

በጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክ እስካሁን ሼድ ከተከራዩት ኩባንያዎች (Akshay Jian) በአጠቃላይ ኤክስፖርት (2,000,000.00
ዶላር) የተደረገ ሲሆን አፈጻጸሙ ከ 100% በላይ ነው፡፡

የአዲስ ኢ/መንደር ኩባንያዎች የኤክስፖርት አፈፃፀም

በአዲስ ኢንዱስትሪ መንደር Africa Cotton PLC 552,123.77፣ Yonis Garment PLC 82,259.35፣ Pittards Production
Manufacturing PLC 1,272,825.81 እና Trio Craft PLC 34,328.84 እና የተባለ ድርጅት 12,442.14 (በ indirect) በአጠቃላይ
1,953,979.91 የአሜሪካን ዶላር ኤክስፖርት ማድረግ የቻሉ ሲሆን አፈጻጸሙ ከ 100% በላይ ይሆናል፡፡ ሌሎች
ኩባንያዎችም ኤክስፖርት የማድረግ አቅማቸውን በማሳደግ የኤክስፖርት ስራን እንዲጀምሩ ክትትል እና አስፈላጊውን
ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

AIV Yearly Export in USD

Total 1,953,979.91

Tamera 12,442.14

Trio craft plc 34,328.84

Pittards 1,272,825.81

Yonis Garment 82,259.35

Africa Cotton PLC 552,123.77

- 500,000.00 1,000,000.00 1,500,000.00 2,000,000.00 2,500,000.00

የባህርዳር ኢ/ፓርክ ኩባንያዎች የኤክስፖርት አፈፃፀም

የኩባንያ ስም የኢንዱስትሪ ፓርኩ ስም እሰከ ሰኔ ኤክስፖርት በአሜሪካን ዶላር


1 Hop Lun ባህርዳር ኢ/ፓርክ 572,200.00

48
በጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክ እስካሁን ሼድ ከተከራዩት ኩባንያ (Hop Lun) በአጠቃላይ ኤክስፖርት (572,200.00) የተደረገ
ሲሆን አፈጻጸሙ 29% ይሆናል፡፡

በአጠቃላይ የመቐለ ኢንዱስትሪ ፓርክ ሳያካትት ወደ ኦፕሬሽን በገቡ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ምርት ከገቡ ጊዜ
አንስቶ የኤክስፖርት አፈጻጸም እስከ ሰኔ ወር 2014 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ የባለፈው 2013 ዓ.ም ተኪ ምርቶች ሽያጭ
ጭምር 914,835,812.38 የአሜሪካን ዶላር የሚያወጣ ምርት እንዲመረት ክትትል እና አስፈላጊውን ድጋፍ
ተደርጓል፡፡

2.5. የባለሀብቶች የሼድ የማስያዝ እና አጠቃቀም


 ሼድ የማስያዝ
በኢንዱስትሪ ፓርኮች እስካሁን ባለው ሂደት የግንባታ ስራቸው ተጠናቆ ለምርት ስራ ከተዘጋጁ ሼዶች
177 ናቸው፡፡ በመቐለ ኢንዱስትሪ ፓርክ የተያዙ ሼዶች እና ሼድ አጠቃቀም ከወቅታዊ ጉዳይ ጋር ተያይዞ
ያለበት ሁኔታ ባለመታወቁ በሌሎች ኢንዱስትሪ ፓርኮች 136 ሼዶች በባለሀብቶች ተይዘዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ
ውስጥ አዲስ 14 ያልተያዙ ሼዶችን ውል በመፈረም ወደ ስራ ለማስገባት ታቅዶ 13 ድርጅቶች ውል
የፈረሙ ሲሆን አፈጻጸሙ 93% ነው፡፡ በአጠቃላይ የሼዶች የመስያዝ ምጣኔ (Occupancy Rate) እስከ ሰኔ
ወር 2014 ዓ.ም መጨረሻ 95% ለማድረስ ታቅዶ የመቐለ ኢ/ፓርክ የተያዙ ሼዶች ያለበት ሁኔታ
ባለመታወቁ 15 ሼዶችን ሳይጨምር ከ 162 ሼዶች የተያዙ ሼዶች 136 ሲሆን አፈጻጸሙ 83.3% ይሆናል፡፡

ሠንጠረዥ 7፡- ዝርዝር የሼዶች Occupancy እና Utilization Rate


መቀለን ጨምሮ በአጠቃላይ መቐለን ሳይጨምር የተከራዩ ሼዶች Occupancy Rate (በ
ተ.ቁ. ኢንዱስትሪፓርክ የተገነቡ ሼዶች ብዛት አጠቃላይ ሼዶች ብዛት %) ምርመራ
1 ቦሌ ለሚ 24 24 24 100
2 ሀዋሳ 52 52 48 92.3
3 መቐለ 15 --- --- ---
4 ኮምቦልቻ 9 9 9 100
5 አዳማ 19 19 17 89
6 ድሬዳዋ 15 15 7 47
7 ጅማ 9 9 1 11.11
8 ባህርዳር 8 8 8 100
9 ደብረብርሀን 8 8 8 100
10 ሠመራ 8 8 4 50
11 አ/ኢ/መንደር 10 10 10 100
ድምር 177 162 136 83.3%

 ሼድ አጠቃቀም

በመቐለ ኢንዱስትሪ ፓርክ ሼድ አጠቃቀም ሳይጨምር በሌሎች ኢንዱስትሪ ፓርኮች ሼዶችን የምርት ስራ
ላይ የማዋል ምጣኔን በኪራይ ከተላለፈው 716,740 ሜ 2 መካከል 602,750 ሜ 2 ለምርት ስራ የዋሉ ሲሆን

49
ቀሪዎቹ 113,990 ሜ 2 በባለሀብቶች በተሟላ መልኩ ለምርት ስራ እየዋሉ ባለመሆናቸው የሼዶች የመጠቀም
ምጣኔ (Shed Utilization Rate) 84% እንዲሆን አድርጎታል፡፡ በዚህም ወደ ኦፕሬሽን በገቡ ኢንዱስትሪ ፓርኮች
ሼዶችን የተረከቡ ባለሀብቶች በተወሰኑት ሼዶች ላይ ብቻ የሚሰሩ ሲሆን በቀጣይ በትኩረት መስራት
ያስፈልጋል፡፡

ሠንጠረዥ 8፡- ሼድ አጠቃቀም


Ips Current used area production storage office canteen free on construction utilization rate
BLIP 165,000 81,402 45,619 10,756 - 21,723 5,500 84%
HIP 352,740 213,780 82,200 11,240 22,065 23,455 93%
AIP 66,500 43,308 10,692 12,500 81%
BDIP 44,000 9,793 4,942 1,452 37%
DBIP 27,500 17,072 5,557 1,739 3,132 165,000 89%
DDIP 14,000 8,340 660 200 4,800 66%
KIP 44,000 28,933 15,067 66%
JIP 3,000 3,000 100%
Total 716,740 405,628 149,670 25,387 22,065 80,677 84%

2.6. የባለሀብቶች የለማ መሬት አጠቃቀም


በኢንዱስትሪ ፓርኮች የለማ መሬት ለባለሀብቶች ለማስተላለፍ የቦሌ ለሚ እና ቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርኮች የተወሰኑ
ባለሀብቶች ቦታ ተረክበው ወደ ግንባታ ስራ የገቡ ሲሆን ውል ፈጽመው ግንባታ ያልጀመሩት ድርጅቶች ወደ ስራ

እንዲገቡ ክትትል እየተደረገ ይገኛል፡፡ በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ ሶስት የለማ መሬት በንዑስ ሊዝ ውል የወሰዱ

ድርጅቶች (የኢትዮጵያ መድሀኒት ፋብሪካ፣ ዘንዲ የህክም፣ ፕራይም ፖእንት እና ዘ ኒው ሚሊኒየም ወርልድ ሜዲካል

ዲቫይስ ማኑፋክቸሪንግ የተባሉ ድርጅቶች ቦታ በመረከብ የግንበታ ሂደት ላይ የሚገኙ ሲሆን ሌሎች ድርጅቶች

የግንባታ ስራ እንዲጀምሩ ክትትል እና ድጋፍ ተደርጓል፡፡ እንዲሁም በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ LR Ethiopia

የተባለው ድርጅት ግንባታ ለመጀመር መሬት ርክክብ አድርጓል፡፡

ሠንጠረዥ 9፡- የለማ መሬት Occupancy እና Utilization Rate


በባለሀብቶች የተያዘ/ውል በባለሀብቱ ግንባታ
በሊዝ የተከራየ የለማ የተፈረመ የለማ መሬት የተጀመረበት የለማ ውል ከተፈረመው ስራ
ተ.ቁ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ስም የለማ መሬት በሄክ መሬት በሄክ በሄክታር መሬት በሄክ የተጀመረበት የለማ መሬት በ(%)
1 ቦሌ ለሚ 2 109 21.25 19.49 19.75 93
2 ቂሊንጦ 173 27.35 15.80 5.7 20.80
3 ኮምቦልቻ 10.79 - - - -
4 አዳማ 5 - - - -
5 ድሬዳዋ 48 - - - -
6 ባህርዳር 23 - - - -
7 ደ/ብርሃን 35 - - - -
8 ጅማ 4.6 4 - - -
ድምር 408.39 52.5 12.85% 25.45 48.47%

በደብረብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ Leasable land for Industry 24 ሄክታር እና Leasable Land for commercial 11
ሄክታር በአጠቃላይ 35 ሄክታር ሲሆን በኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ በአጠቃላይ የለማ መሬት 10.79 ሄክታር ነው፡፡

50
2.7. በኢንዱስትሪ ፓርኮች ኦፕሬሽን ውል ስምምነቶችን ማስተዳደር
በኢንዱስትሪ ፓርኮች ለማምረቻ ሼድ እና ለቢሮ አገልግሎት የኪራይ ውል የፈጸሙ ባለሀብቶች እና አገልግሎት
ሰጪ ተቋማት በገቡት ውል መሰረት እየሰሩ መሆናቸውን በሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች ክትትል የተደረገ ሲሆን
በውሉ መሰረት በማይፈጽሙት ላይ እንዲያሻሽሉ የማሳሰብ እና እርምጃ የመውሰድ ስራዎች ተሰርቷል፡፡ በበጀት
ዓመቱ ውስጥ በ 4 ኢንዱስትሪ ፓርኮች ሼዶችን በመከራየት ውል የፈጸሙ ባለሀብቶች እና አገልግሎት ሰጪ
ተቋማት ውል ማደስና የውል ማሻሻያ ስራዎች ለማከናወን የታቅደ በሶስት ኢንዱስትሪ ፓርኮች (በሀዋሳ፣ ድሬዳዋ፣
ጅማ፣ ቂሊንጦ፣ ሠመራ፣ በቦሌ ለሚ እና በአዲስ ኢንዱስትሪ መንደር) ለተለያዩ ድርጅቶች የውል ማሻሻያ እና
እድሳት የተደረገላቸው ሲሆን አፈጻጸሙ ከ 100% በላይ ነው፡፡ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ለማምረቻ ሼድ፣ ለ Residential
እና ለቢሮ አገልግሎት የኪራይ ውል የፈጸሙ ባለሀብቶች እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በገቡት ውል መሰረት እየሰሩ
መሆናቸውን በሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች ክትትል እየተደረገ ሲሆን ዝርዝሩ አባሪ 2 ላይ ተያይዟል፡፡

በ Pipeline ውስጥ ያሉ ድርጅቶች በለማ መሬት (Akshay Jian & Golden፣ Safaricom፣ Yellen Pharmaceutical፣
Afian PLC፣ Green Base እና Dimtros KAMPOURIS (KAMBOTES))፣ በሼድ (Tamira Techno፣ Gulf Ingot፣ እና AET
Manufacturing PLC) እና በቢሮ (Coop Bank እና Awash Insurance) ድርጅቶች ናቸው፡፡ በሀዋሳ እና ድሬዳዋ
ኢንዱስትሪ ፓርኮች የመኖሪያ ቤት (residential) የተገነቡ ሲሆን እስካሁን የተከራዩ እና የልተከራዩ ቤቶች
እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

ሠንጠረዥ 10፡- የተያዙና ያልተያዙ Residential በ 2 ቱ ኢ/ፓርኮች

ሀ) ሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ


የተያዘ/ያልተያ ስቱዲዮ ዶርሚተሪ ባለ 1 መኝታ ባለ 3 መኝታ
የተያዘ/Occupied/ 143 141 74 46
ያልተያዘ/Vacant/ 13 29 26 4
ድምር 156 170 100 50
ለ) ድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ
የተያዘ/Occupied/ - - 2 2
ያልተያዘ/Vacant/ 77 89 98 48
ድምር 77 89 100 50

ግብ 4፡ ለሀገር ውስጥ ገበያ ስራቴጂካዊ ምርቶችን በማቅረብ የውጭ ምንዛሬ ጫናን መቀነስ /Import
subsitiution

በበጀት ዓመቱ ውስጥ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን የሚተኩ (Import Substitution) ላይ ባለሀብቶች ካመረቱት ምርት
138,962,649.87 የአሜሪካ ዶላር የሚያወጣ ምርት ለሀገር ውስጥ ገበያ እንዲቀርብ በማድረግ የውጭ ምንዛሬ ጫና
ለመቀነስ ታቅዶ ባለሀብቶች በሀገር ውስጥ ምርታቸውን የሚሸጡበት መንገድ በመመቻቸቱ የሀገር ውስጥ ምርት
ሽያጭ በከፍተኛ ሁኔታ ጭማሬ ያሳየ ሲሆን 6,106,750,749.48 ብር የሚያወጣ የተለያዩ ምርቶች ለሀገር ውስጥ
እንዲቀርቡ የሚያስችሉ ስራዎች ተሰርቷል፡፡ ለእነዚህ ምርቶች ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ይወጣ የነበረ
127,963,866.82 የአሜሪካን ዶላር ለማዳን ተችሏል፡፡ በዚህም አጠቃላይ አፈጻጸሙ 92% ሲሆን በሀዋሳ ኢንዱስትሪ

51
ፓርክ (22%) እና ቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ (18%) አፈጻጸማቸው ከዕቅዱ አንጻር ዝቅተኛ በመሆኑ ክትትል እና
አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡

ሠንጠረዥ 11፡- በበጀት ዓመቱ ሀገር ውስጥ የተሸጡ ምርቶች አፈጻጸም


በሀገር ውስጥ የተሸጠ ሀገር ውስጥ የተሸጠ ምርት በወቅቱ አፈጻጸም
ተ.ቁ. ኢንዱስትሪ ፓርኮች ስም የበጀት ዓመቱ ዕቅድ የምርት መጠን በብር ምንዛሬ ወደ ዶላር ሲቀየር በመቶኛ
1 ሀዋሳ ኢ/ፓርክ 2,450,960.00 141,852,275.00 521,914.09 22%
2 ቦሌ ለሚ ኢ/ፓርክ 56,420,481.64 2,774,591,932.00 56,640,188.00 100%+
3 አዳማ ኢ/ፓርክ 2,117,800.50 148,706,084.55 2,880,784.28 100%+
4 ድሬዳዋ ኢ/ፓርክ 11,297,075.00 384,917,990.00 7,934,802.45 76%
5 ደብረብርሃን ኢ/ፓርክ 49,339,807.64 1,904,723,421.45 44,282,544.00 90%
6 ቂሊንጦ ኢ/ፓርክ 3,863,641.67 38,102,509.48 695,154.00 18%
7 አዲስ ኢ/መንድር 9,909,325.00 556,856,537.00 11,441,073.00 100%+
8 ጅማ ኢ/ፓርክ 3,563,559.00 157,000,000.00 3,567,407.00 100%
ድምር 138,962,649.87 6,106,750,749.48 127,963,866.82 92%

ግራፍ 3፡- የተኪ ምርቶች አፈጻጸም

138,962,650
An n u a l I mp o r t s u b s ti t u ti o n

127,963,866
92%

.45
.82
ዕቅድ አፈጻጸም
56,640,188.00
56,420,481.64

49,339,807.64
44,282,544.00

11,441,073.00
11,297,075.00

9,909,325.00
7,934,802.45

3,863,641.67

3,563,559.00
3,567,407.00
2,880,784.28
2,450,960.00

2,117,800.50

695,154.00
521,914.09

ሀዋሳ ቦሌ ለሚ አዳማ ድሬዳ ዋ ደብ ረብ ርሃ ን ቂሊን ጦ አ/ ጅማ ድምር


ኢ/
መን ድር

ግብ 5፡ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያሉ ድርጅቶችን እና የሀገር ውስጥ አምራቾች መሀል ያለውን


ትስስር ማጠናከር እና ማሳደግ

በኢንዱስትሪ ፓርኮች በምርት ስራ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች ከሀገር ውስጥ ግብዓት አቅራቢዎች ጋር በማስተሳሰር
የሀገር ውስጥ አምራቾችን አቅም ለማጎልበት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማምጣት የተለያዩ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡
በኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚገኙ ኩባንያዎች የሚያስፈልጋቸውን የጥሬ ዕቃዎች አቅርቦት ዳሰሳ በማድረግ ዝርዝር
የያዘ ሰነድ በማዘጋጀት ትስስር ለመፍጠር ታቅዶ አፈጻጸሙ 100% ነው፡፡

52
በበጀት ዓመቱ ውስጥ 353 ለሚሆኑ ሀገር ውስጥ ምርት አቅራቢዎች በኢንዱስትሪ ፓርኮች ከተሰማሩ ጋር

በግብዓት አቅርቦት ትስስር ለመፍጠር ታቅዶ ከ 662 የሀገር ውስጥ ድርጅቶች ጋር ትስስር የተፈጠረ ሲሆን

አፈጻጸሙ ከ 100% በላይ ነው፡፡ በሌላ በኩል እስካሁን በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚገኘው Soufflet የተባለ

ብቅል አምራች ድርጅት ከ 48,067 ገበሬዎች፣ በደብረብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ Boortmalt የተባለው ድርጅት

ከ 32,500 ገበሬዎች እና በጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክ Akshay Jian የተባለ ድርጅት ከ 15,000 ገበሬዎች ጋር ትስስር

በመፍጠር በአጠቃላይ ከ 95,567 ገበሬዎች ጋር ትስስር ተፈጥሯል፡፡ በበጀት ዓመቱ ውስጥ 49,646,651.00

የአሜሪካን ዶላር የሚያወጣ ምርት ትስስር ከተፈጠረላቸው የሀገር ውስጥ ድርጅቶች ግብዓት እንዲያቀርቡ ታቅዶ

3,447,428,392.00 ብር የሚያወጣ የግብዓት ትስስር በመፍጠር በወቅቱ የምዛሬ ዋጋ ሲቀየር 69,851,184.22 የሚሆን

የአሜሪካን ዶላር ለኢንዱስትሪ ፓርኮች አምራቾች ቀርቧል፡፡ በዚህም ከዕቅዱ አኳያ አፈጻጸሙ ከ 100% በላይ

ሲሆን ለኢንዱስትሪ ፓርኮች ድርጅቶች ከተለያዩ የሀገር ውስጥ የግብዓት አቅራቢዎች የቀረቡ ዕቃዎች በዋናነት

ካርቶኖች፣ ማሸጊያዎች፣ ገብስ፣ ጥሬ ቆዳ፣ የስቴሽነሪ ዕቃዎች ናቸው፡፡

ሠንጠረዥ 12፡- ከሀገር ውስጥ ምርት አምራቾች ጋር የማስተሳሰር ስራ

የ 12 ወራት ዕቅድ ለኩባንያዎች የቀረበ ግብዓት የግብዓት መጠን በወቅቱ ምንዛሬ


ተ.ቁ ኢንዱስትሪ ፓርክ ስም በአሜሪካን ዶላር በብር ሲተመን ወደ ዶላር ሲቀየር አፈጻጸም ምርመራ
1 ሀዋሳ ኢ/ፓርክ 863,273.00 22,796,604.00 498,620.00 58%

2 ቦሌ ለሚ ኢ/ፓርክ 16,267,612 2,625,059,183 51,794,943.00 100%+

3 ኮምቦልቻ ኢ/ፓርክ 38,428.00 918,308.00 19,787.00 51%

4 አዳማ ኢ/ፓርክ 103,282.00 8,654,297.00 173,233.00 100%+

5 ደብረብርሃን ኢ/ፓርክ 31,555,556.00 700,000,000.00 15,555,556.00 49%

6 ቂሊንጦ ኢ/ፓርክ 18,500.00 - - -


7 ጅማ ኢ/ፓርክ 608,000.00 90,000,000.00 1,809,045.22 100%+
ድምር 49,646,651.00 3,447,428,392.00 69,851,184.22 100%+

በኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚገኙ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችን ሊሰጥ የሚገባ ድጋፍን የሚመለከት ጥናት ሰነድ ለማዘጋጀት ታቅዶ
ሰነዱ መጠናቀቁ ቀጣይ ለተግባራዊነቱ ክትትል የሚደረግ ይሆናል፡፡
ግራፍ 4፡- የተኪ ምርቶች አፈጻጸም

53
69,851,184.22
An n u a l L in k a g e PE R FOR M AN CE

ዕቅድ አፈጻጸም 100%+

51,794,943.00

49,646,651
31,555,556
15,555,556.00
16,267,612

1,809,045.22
498,620.00

173,233.00
19,787.00
863,273

608,000
103,282
38,428

18,500
0.00
ሀ ዋ ሳ ኢ / ፓ ርክ ቦሌ ለሚ ኮ ምቦ ል ቻ አዳማ ደብ ረብ ርሃ ን ቂሊን ጦ ጅ ማ ኢ / ፓ ርክ ድምር
ኢ / ፓ ርክ ኢ / ፓ ርክ ኢ / ፓ ርክ ኢ / ፓ ርክ ኢ / ፓ ርክ

በኢንዱስትሪ ፓርኮች በምርት ስራ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች ከሀገር ውስጥ ግብዓት አቅራቢዎች ጋር በማስተሳሰር
የሀገር ውስጥ አምራቾችን አቅም ለማጎልበትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማምጣት የተለያዩ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡
በዚሁ መሠረት በኢንዱስትሪ ፓርኮች ኩባንያዎች የሚያስፈልጋቸውን የጥሬ ዕቃዎች አቅርቦት ዳሰሳ በማድረግ
ዝርዝር የያዘ ሰነድ በማዘጋጀት ትስስር ለመፍጠር ታቅዶ ሰነዱ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡ በ 2014 በጀት ዓመት በበበጀት
ዓመቱ 35,678,151.16 የአሜሪካን ዶላር የሚያወጣ ምርት ትስስር ከተፈጠረላቸው የሀገር ውስጥ የግብዓት
አቅራቢዎች እንዲቀርብ ለማድረግ ታቅዶ 34,158,862.02 የአሜሪካን ዶላር (በብር 1,599,163,464.14) የሚያወጣ
ግብዓት በኢንዱስትሪ ፓርክ ዉስጥ ለሚገኙ አምራቾች ቀርቧል፡፡ በዚህም ከዕቅዱ አኳያ አፈጻጸሙ 95.74% በላይ
ሲሆን በኢንዱስትሪ ፓርክ ዉስጥ ለሚገኙ ድርጅቶች ከተለያዩ የሀገር ውስጥ የግብዓት ዓቅራቢዎች የቀረቡ
ግባዓቶች በዋናነት ካርቶኖች፣ ማሸጊያዎች፣ ማቅለሚያ፣ ገብስ፣ ጥሬ ቆዳ፣ የእስቴሽነሪ ዕቃዎች እና የመሳሰሉት
ናቸዉ፡፡

በ 2014 በጀት ዓመት በ 9 ወሩ በኮርፖሬሽኑ ስር የሚተዳደሩ 5 ኢንዱስትሪ ፓርኮች (ሀዋሳ፤ ቦሌ ለሚ፤ ኮምቦልቻ፤
ደብረ ብርሃን እና አዳማ) የሚገኙ ድርጅቶች 313 የሚሆኑ የሀገር ውስጥ አምራቾችና ድርጅቶች ጋር ትስስር
ተፈጥረዋል፡፡ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ትስስሩን ከፈጠሩ 20 ድርጅቶች ዉስጥ በሀዋሳ 9፤ ቦሌ ለሚ 6፤ በኮምቦልቻ 2፤
በደብረ ብርሃን 2 እና በአዳማ 2 ድርጅቶች ናቸዉ፡፡ በሌላ በኩል እስካሁን በተፈጠረው ትስስር በቦሌ ለሚ
ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚገኘው Soufflet የተባለ ብቅል አምራች ድርጅት ከ 46,836 ገበሬዎች ጋር ትስስር የፈጠረ
ሲሆን በደብረብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ Boortmalt የተባለው ድርጅት ከ 27,500 ገበሬዎች ጋር ትስስር በመፍጠር
በአጠቃላይ ከ 74,336 አርሶ አደሮች ትስስር ተፈጥሯል፡፡

ግብ 6፡ የኢኮ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ልማት ዘላቂነትን ማረጋገጥ

የፍሳሽ ማጣሪያ ግንባታ ሥራዎች

54
የኢንዱስትሪ ፓርክ ልማትን ዘለቄታዊ ማድረግ አንዱ ግብ ሲሆን በበጀት ዓመቱየሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የፍሳሽ
ማጣሪያ የማስተካከያና ቀሪ ሥራዎች ማጠናቀቅ 43% ለማከናወን ታቅዶ 21% ተከናውኗል፣ የአዳማ ኢንዱስትሪ
ፓርክ ከፍሳሽ ማጣሪያ ጋር የተያያዙ ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ 28% ለማከናወን በዕቅድ ተይዞ 21% ተከናውኗል፣
አፈፃፀሙም 75% ነው፡፡ የድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ የፍሳሽ ማጣሪያ የማስተካከያና ቀሪ ሥራዎች ማጠናቀቅ 15%
ለማከናወን ታቅዶ 6% የተከናወነ ሲሆን አፈፃፀሙም 40% ነው፡፡ ቦሌ ለሚ ምዕራፍ 2 ፍሳሽ ማጣሪያና ቀሪ
የማስተካከያ ሥራዎች ማጠናቀቅ 85% ለማከናወን ታቅዶ 65% ተከናውኗል፣ አፈፃፀሙም 76.4% ነው፡፡ ቂሊንጦ
ኢንዱስትሪ ፓርክ ፍሳሽ ማጣሪያና ቀሪ የማስተካከያ ሥራዎች ለማጠናቀቅ በበጀት ዓመቱውስጥ 85% ለማከናወን
ታቅዶ 72.5% ተከናውኗል፣ አፈፃፀሙም 85.2%% ነው፡፡

በተጨማሪም በበጀት ዓመቱውስጥ በባህርዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ የፍሳሽ ማጣሪያና ቀሪ የማስተካከያ ሥራዎች
ማጠናቀቅ በተመለከተ 40% ለማከናወን ታቅዶ 14.5% የተከናወነ ሲሆን በደብረብርሃን በተመሳሳይ 35% ታቅዶ 11%
ተከናውኗል፡፡ አፈፃፀሙ ለባህርዳር 36.2% ሲሆን ደብረብርሃን 31.4% ይሆናል፡፡ የኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ ፍሳሽ
ማጣሪያ ግንባታን በተመለከተ በበጀት ዓመቱ 15% ለማከናወን ታቅዶ የነበረ ቢሆንም ስራውን በተያዘለት ጊዜ
ማከናወን አልተቻለም፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ ዋና ምክንያት ሥራ ተቋራጩ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ አለመግባቱ
እንዲሁም የዲዛይን ሥራውን አለማጠናቀቁ ሲሆን ከወቅታዊ ሃገራዊ የፀጥታ ችግር ልላኛው ምክንያት ነው፡፡

ፍሳሽ እና ደረቅ ቆሻሻን የማጣራትና የማስወገድ ስራን በተመለከተ

የኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት አንዱ እና ዋናው ዓላማ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎችን በአንድ ቦታ በማሰባሰብ
የሀብት አጠቃቀም ውጤታማነትን ከማረጋገጥ ባለፈ ከኢንዱስትሪዎች በጠጣር፣ በፍሳሽ ወይም በጋስ መልክ
በመለቀቅ በአካባቢ እና በማህበረሰብ ላይ ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉ ችግሮችን መቆጣጠር ሲሆን ከነዚህም ውስጥ
የኢንዱስትሪ ፍሳሽን በማከም እና በማጣራት ጥቅም ላይ እንዲውል ማስቻል ብክለትም ከማሰቀረት ባሻገር
የተፈጥሮ ሃብትን ለመቆጠብ ትልቅ ፋይዳ የሚኖረው ተግባር ነው፡፡ በ 9 ወራቱ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚመነጭ 88
ቶን ስለጅ በረጲ ደረቅ ቆሻሻ ጣቢያ ለማስወገድ ታቅዶ 211 ቶን ስለጅ የተወገደ ሲሆን አፈፃፀሙ ከዕቅዱ አንፃር
በፐርሰንት ስገመገም ከ 100 በላይ ነው፡፡

ፍሳሽ ቆሻሻ ማጣራትን በተመለከተ በ 9 ወራቱ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች 1,484,636 ሜ 3 ፍሳሽ ለማጣራት የታቀደ
ሲሆን 1,206,797.39 ሜ 3 ፍሳሽ የተጣራ ሲሆን በፐርሰንት ስገመገም 81.3 ነው፡፡ እንዲሁም ከሀዋሳ ኢንዱስት ፓርክ
የዜሮ ሊኪውድ ማጣሪያ 954,450 ሜ 3 የተጣራ ውሃ ጥቅም ላይ ለማዋል የታቀደ ሲሆን 764,546 ሜ 3 ውሃ
የተጣራ ጥቅም ላይ እንዲውል የተደረገ ሲሆንህ አፈፃፀሙም በፐርሰንት ስገመገም 80 ነው፡፡

ደረቅ ቆሻሻ ማስወገድን በተመለከተ በኢንዱስትሪ ፓርኮች በበበጀት ዓመቱ 9,928.99 ሜ 3 ደረቅ ቆሻሻ ከሰባት
ኢ/ፓርኮች ለማስወገድ እቅድ ተይዞ 10,772.68 ሜ 3 በአግባቡ ተወግዶል፡፡ አፈፃፀሙም ከዕቅዱ አንፃር ስገመገም
ከ 100 በላይ ነው፡፡

55
የአረንጓዴ ልማት ስራዎች

በአረንጓዴ ልማት ስራዎች በተመለከተ ኮርፖሬሽኑ ባስገነባቸው 12 ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የአረንጓዴ ልማት
እንክብካቤ፣ አያያዥ እና ሌሎች ቴክኒካል ድጋፎች ተደርጓል፡፡ በኢንዱስትሪ ፓርኮች የችግኝ ጣቢያ በማቋቋም
ተጨማሪ ገቢ ለማግኘት የሚያስችል የችግኝ ጣቢያ በ 3 ኢንዱስትሪ ፓርኮች (በቦሌ ለሚ፣ ደብረ ብርሃን እና
በባህርዳር እንዱስትሪ ፓርኮች) የተጀመረ ሲሆን ከዚሁ ጋር በተያያዘ ባለድርሻ አካል ማለትም የአካባቢ እና የደን
ምርምር ማዕከልን የሙያ ድጋፍ እንዲያደርግልን በተጠየቀው መሰረት ከአካባቢ እና ደን ምርምር ለተለያዩ የዛፍ
ዝርያዎች የዘር ድጋፍ ለኮርፖሬሽኑ ተደርጓል፡፡

በአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሩ በበበጀት ዓመቱ 1,000,000 ችግኞችን ለመትከል የታቀደ ሲሆን 785,305 ችግኞች
በፐርሰንት 78.53 የተተከለ ሲሆን ከተተከለው ውስጥ 528,834 የፀደቀ ችግኝ በመሆኑ አፈፃፀሙ በፐርሰንት
85.60%ነው፡፡

ግብ 7. የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች አገልግሎት ወደ ምክር እና ስልጠና የልዕቀት ተቋም ትራንስፎርም


በማድረግ በዛም ከአገልግሎት የሚገኘውን ገቢ ማሳደግ

የምክር እና ስልጠና አገልግሎት ገቢ

በበጀት ዓመቱውስጥ በተለያየ ዘርፍ በድምሩ 74 ፕሮፖዛሎችን ለደንበኞት ያቀረበ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 24
ፕሮፖዛሎች በግልጽ ጨረታ የተወዳደርንባቸው እንዲሁም 54 ፕሮፖዛሎች ድርጅቱ በቀጥታ በደንበኞች ተጋብዞ
ያቀረባቸው ናቸው፡፡ ለደንበኞች ቀርበው ውጤታቸው ከታወቁ 24 ፕሮፖዛሎች ውስጥ 23 በደንበኛ ዘንድ
ተቀባይነት አግኝተው የኮንትራት ውል የተፈረመባቸው ሲሆን የፕሮጀክቶቹ ጠቅላላ ዋጋ ብር 10,924,713.05 ነው፡፡

በ 2014 በጀት ዓመት በበጀት ዓመቱ ውስጥ አጠቃላይ ገቢ ብር 30,257,867.48 (ከኦፕሬሽን ብር 26,060,000
እንዲሁም ከፋሲሊቲ ብር 3,657,867.48) ይገኛል ተብሎ የታቀደ ሲሆን የተገኘው ገቢ ብር 24,383,900.60
(ከኦፕሬሽን ብር 21,698,534.03 ከፋሲሊቲ ኪራይ ብር 3,366,002.00) ነው፡፡ የአጠቃላይ የገቢ ዕቅድ አፈጻጸም
80.59% ነው፡፡

በበጀት ዓመቱ ውስጥ ከኦፕሬሽን (ከምክርና ከሥልጠና አገልግሎት) ይገኛል ተብሎ የታቀደው የገቢ መጠን ብር
26,060,000 ሲሆን የተገኘው ገቢ ብር 21,698,534.03 (ከምክር አገልግሎት ብር 20,964,689.05 ፣ከስልጠና
አገልግሎት ብር 733,844.98) ነው፡፡የኦፕሬሽን (ምክርና ስልጠና) አፈጻጸም ከእቅዱ አንጻር 83.26% ፡፡

56
በበጀት ዓመቱውስጥ ከፋሲሊቲ ኪራይ ይገኛል ተብሎ የታቀደው የኪራይ ገቢ ብር 3,366,002.00 ሲሆን የተገኘው
ገቢ ብር 3,139,860.00 በመሆኑ ክንውኑ የዕቅዱ 93.28% ሆኗል፡፡ አፈጻጸሙ ከዕቅድ በታች የሆነው የህንፃው እድሳት
ባለመጠናቀቁ በበጀት ዓመቱ ውስጥ ለማከራየት ታቅደው የነበሩ ክፍሎች ባለመከራየታቸው ነው፡፡

በበጀት ዓመቱውስጥ ለኦፕሬሽን እና ለአስተዳደራዊ አገልግሎቶች የታቀደው አጠቃላይ የወጪ በጀት ብር


19,685,086.25 ሲሆን ለእነዚሁ ሥራዎች የተደረገው አጠቃላይ የወጪ መጠን ብር 19,817,290.16 ነው፡፡ አፈጻጸሙ
ከዕቅዱ ጋር ሲነጻጸር 100.67% ነው፤የወጪ አፈጻጸሙ ከዕቅዱ ከፍ ብሎ የታየው በበጀት ዓመቱ ውስጥ ለኦፕሬሽን
የወጡ ወጪዎች ከፍ በማለቱ ነው፡፡ ለበበጀት ዓመቱ የታቀደው የትርፍ መጠን ከታክስ በፊት ብር 10,572,781.23
ሲሆን የተገኘው አፈጻጸም የሚያሳየው ብር 4,440,147.17 ነው፡፡ ስለሆነም አፈጻጸሙ ከዕቅዱ ጋር ሲነጻጸር 42%
ነው፡፡

ግብ 8፡ የኮርፖሬሽኑን ትርፋማነት ዘላቂ እንዲሆን ማድረግ

ኮርፖሬሽኑን ትርፋማነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ ያለመ ሲሆን የሀገሪቱን ኢኮኖሚ በስራ እድል ፈጠራ እና የውጭ
ምንዛሬ ግኝት ከሚያደርገው ድጋፍ ባለፈ እንደ ኮርፖሬሽን ደግሞ በተለያዮ የቢዝነስ መስኮች ላይ በመሰማራት
እንዲሁም ወጪ ቆጣቢ አሰራሮችን በማጥናትና በመተግበር ትርፋማነትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ ያለመ ነው፡፡ በበጀት
ዓመቱ ብር 101,137 ሚሊዮን ብር ትርፍ ለማግኘት የታቀደ ሲሆን በ 9 ወራት ውስጥ ትርፍ 79 ሚሊዮን ብር ማግኘት
ተችሏል፡፡

ከሼዶች ኪራይ ፣ ከለማ መሬት እና ኮርፖሬሽኑ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች ገቢን በአግባቡ መሰብሰብ

በ 2014 በበበጀት ዓመቱ ከሼዶች ኪራይ፣ ከለማ መሬት ኪራይ ፣ ከምክር እና ስልጠና አገልግሎት ፣ ከቢዝነስ ልማት
ስራዎች እና ሌሎች ገቢዎች ብር 998,313,358.30 ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ ብር 791,417,371.95 ገቢ በመሆኑ
አፈጻጸሙ የእቅዱን 79.27% ሆኗል፡፡

የገቢ አማራጮችን ማስፋትና ትርፋማነትን ማረጋገጥ

በመጀመሪያ በበበጀት ዓመቱ የበጀት ዓመት ውስጥ የኮርፖሬሽኑን የገቢ ምንጮችን ለማስፋፋት እና ትርፋማነትን
ለማረጋገጥ ወደ ኦፕሬሽን በገቡ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ተጨማሪ የገቢ ምንጮችን በመለየት የኢንዱስትሪ ፓርኮች
የመደበኛ ወጪያቸውን 30% እንዲሸፍኑ የሚያስችል ሰነድ ተዘጋጅቶ በሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ጋር
ውይይት ተድርጎበት ተፈጻሚ እንዲሆን ለሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች ተልኮ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል፡፡

በ 9 ወራት ውስጥ ለ 8 የኢንዱስትሪ ፓርኮች ከተለቀቀላቸው መደበኛ በጀት የተጠቀሙት 283,582,041.40 ብር


ሲሆን በዕቅድ ከተያዘው 30% በጀት በድምሩ 61,419,721.75 ከተጨማሪ የገቢ ምንጮች የተገኘ የገቢ መጠን
7,771,788.27 ብር በመሆኑ ከተጠቀሙት 30% በጀት ጋር ሲነፃፀር አፈፃፀሙ 12.65% ነው፡፡ ለአፈፃፀሙ ማነስ
ምክንያቶች በሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የፍሳሽ ማጣሪያ ክፍያ ከፍተኛ በመሆኑ፣ እንዲሁም በበጀት ዓመቱ አዲስ

57
የተመረጡ የገቢ ምንጮችን ወደ ስራ ለማስገባትና ተግባራዊ ለማድረግ ጊዜ የወሰዱ በመሆኑ እና የኢንዱስትሪ
ፓርኮች ከዚህ በፊት የተመረጡ የገቢ ምንጮች ላይ ሙሉ አቅማቸውን ተጠቅመው ስራ ላይ ማዋል ባለመቻላቸው
ነው፡፡

በአዋጭነት ጥናት የተደገፉ አዳዲስ የቢዝነስ ሃሳቦችን በመለየት 3 የአዋጭነት ጥናት ለመሥራት ታቅዶ ለቢዝነስ
ልማት በተለየው መሬት ላይ ሊሰሩ የሚችሉ የቢዝነስ አይነቶችን በቦሌ ለሚ እና ቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርኮች
ሊሰሩ የሚችሉ ወደ 30 /ሰላሳ/ የሚደርሱ የቢዝነስ አማራጮች የተለዩ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ በተመረጡ ዘርፎች
በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ስራ ሊገቡ የሚያስችሉትን በመለየት የቅድመ አዋጭነት ዳሰሳ Pre-Feasibility/ Preliminary
Scanning ስራ ተጠናቆ 3 /ሶስት/ የአዋጭነት ጥናቶች /Feasibility Study/ ቢዝነስ ሃሳቦችን የፍልውሃ አገልግሎት፣
የመዝናኛ አገልግሎት ለመስጠት እንዲሁም የችግኝ መትከል አዋጭነት ጥናቶችን ማከናወን የተቻለ በመሆነ
አፈፃፀሙ 100% ሆኗል፡፡

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን እና የሚያስተዳድራቸው የኢንዱስትሪ ፓርኮች ወጪ ቆጣቢ አሰራርን


እንዲከተሉ ለማድረግ የሚያስችል የ 3 ፓርኮችን (ቦሌ ለሚ፣ ሃዋሳ እና አዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን) ከፍተኛ ወጪ
የሚያስወጧቸውን ተግባራት መለየት በመቻሉ ክንውኑ 100% ሆኗል፡፡ በተጨማሪም አማራጭ ሃሳቦችን በማቅረብ
ፓርኮቹ ወጪያቸውን በመቀነስ ትርፋማ እንዲሆኑ የሚያስችሉ መፍትሄዎችን በማማከር በተያዘው ዕቅድ መሠረት
100% ተከናውኗል፡፡

የኢንዱስትሪ ኮንሰልተንሲ እና ስልጠና አገልግሎት የሚሰጥባቸው መስኮችን/ዘርፎች መለየትን በሚመለከት የቦሌ


ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ የኢንዱስትሪ ኮንሰልተንሲ እና ስልጠና አገልግሎት የሚሰጥባቸውን መስኮች በተለይም ATP
(i.e Laboratory Test Service, Water Treatment service (the treatment plant treats under capacity), Lab
Accreditations), በቀዳሚነት የተለዩ ሲሆን እነዚህንም ቶሎ ወደ ስራ ለማስገባት የቅድመ አዋጭነት ዳሰሳ ስራዎች
Pre-Feasibility/ Preliminary Scanning በተለይም ከተስማሚነት ምዘና፣ ከ Ethiopian National Accreditation
Association አስፈላጊ መስፈርቶችና የዕውቅና ሰርቲፊኬት ለማግኘት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰራ ይገኛል፡፡

ለከርፖሬሽኑ ለተለያዩ የሥራ ክፍሎች፣ ለባለሀብቶችና 83 የሕግ አስተያየቶችና የምክር ድጋፍ ለመስጠት ታቅዶ 95
የተሰጠ ሲሆን አፈፃፀሙ 100%+ ነው፡፡ ለኮርፖሬሽኑ ልዩ ልዩ አገልግሎት የሚውሉ የተጠኑ ሞዴል ረቂቅ ውሎችን
በማዘጋጀት፤ ተዘጋጅተው የቀረቡት ላይ አስተያየት ከመስጠት አንፃር 61 ውሎችን ለማዘጋጀት ታቅዶ 80 ውሎች
በመዘጋጀታቸው አፈፃፀሙ 100%+ ነው፡፡ የፍርድ ቤት ጉዳዮችን ከመከታተል አንፃር በወሩ ፍርድ ቤት በሚሰጠው
ቀጠሮ መሰረት በሃያ አምስት ጉዳዮች ላይ ክትትል ተደርጓል፡፡ ስምንት የመግባቢያ ስምምነት ሠነድ ለማዘጋጀት
ታቅዶ አስራ አንድ የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ በመዘጋጀቱ አፈፃፀሙ 100%+ ነው፡፡ በተጨማሪም ሶስት ህግ ነክ
ስልጠና ለመስጠት በዕቅድ በተያዘው መሠረት በመከናወኑ አፈፃፀሙ 100% ሆኗል፡፡ ኮርፖሬሽኑ በሌሎች የፍትሕ
አካላት ዘንድ ጉዳዮች በመከታተል የኮርፖሬሽኑን ጥቅም ማስጠበቅ የእርምት እርምጃ ላይ አስፈላጊው ሥራ
ተከናውኗል፡፡

58
ግብ 9፡ ኮርፖሬሽኑን በሀገር ውስጥና በአለምአቀፍ ደረጃ ተመራጭ እና ተወዳዳሪ ማድረግ
ስምንት /8/ ባለሃብቶች በኢንቨስትመንት ተሳታፊ እንዲሆኑ በታቀደው መሠረት፤ በድሬዳዋ ኢ/ፓ (አንድ ባለ 11000
ካሬ ሜትር የፋብሪካ ሼድ) አንድ የሀገር ውስጥ ባለሀብት ኤላውቶ የመኪና አምራች ድርጅት/Elauto Engineering)፤
በቦሌ ለሚ 2 ኢ/ፓርክ (1.89 ሄክታር የለማ መሬት) የውጭ ባለሀብት /Dimitrios Kampouris ኢንቨስት ለማድረግ
ከኮርፖሬሽኑ ጋር ውል ተፈራርመዋል፡፡ በዚህም ከዕቅዱ አንፃር የተከናወነ ሁለት /2/ ሲሆን አፈፃፀሙ 25% ነው፡፡

ኮርፖሬሽኑ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች በተለያዩ ዘዴዎች ማስተዋወቅን አስመልክቶ በኢትዮጵያ የሚገኙ የተለያዩ
ሀገራት አምባሳደሮችን እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቦችን በመያዝ የተመረጡ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እንዲጎበኙ
እና በዘርፉ ለውጭ ሀገር ባለሀብቶች ስለተዘጋጁ ማበረታቻዎች ገለፃ በማድረግ ኢንቨስትመንቱን ማስተዋወቅ
የተቻለ ሲሆን የአፍሪካ ልማት ባንክ ግሩፕ በምክትል ፕሬዝዳንት የተመራ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ልዑክ የተመረጡ
ኢንዱስትሪ ፓርኮችን የጎበኙ ሲሆን የሳፋሪኮም ከፍተኛ ኃላፊዎችን፣ የቢዝነስ የኢንተርፕራይዝ ልማት አና የቴክኒክ
አባላትን ያካተተ ቡድን በአይሲቲ ፓርክ በመገኘት የመስክ ላይ ጉብኝት አከናውነዋል፡፡

በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚገኙ የሀገር ውስጥ እና ዓለም ዓቀፍ አምራቾችን በኮርፖሬሽኑ ማህበራዊ ሚዲያ
ላይ #በኢትዮጵያ የተሰራ_Made in Ethiopia በሚል ቀጣይነት ባለው መልኩ ማስተዋወቅ ታቅዶ ከ 18 በላይ በሆኑ
ኩባንያዎች፣ የ Jotun ቀለም፣ አንቴክስ ቴክስታይል አዳማ ፣ ሰን ሻይን አፓረል በአዳማ፣ ሃን ፕላስት (በፎቶና
በቪዲዮ) ድሬዳዋ፣ Royal Medical Textile (በፎቶና በቪዲዮ)፣ New Millennium በቪዲዮ ቂሊንጦ፣ EK Ethiopia
Knitted Manufacturing Plc. ደብረ ብርሃን፣ የኢንዶቺን አፓረል ፒኤልሲ ሀዋሳ፣ ጄይ ጄይ ጋርመንት በቦሌ ለሚ፣ የ JP
ቴክስታይል፣ አዲስ ኢንዲስትሪ መንደር የአፍሪካ ኮተንስ ፒ ኢል ሲ በመተዋወቁ አፈፃፀሙ 100% ሆኗል፡፡

የኮሙኒኬሽን ስራዎችን በተመረጡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ላይ የሚዲያ ቱር በማዘጋጀት የዜና እና የፕሮግራም ሽፋን
እንዲኖራቸው ለማድረግ በተያዘው ዕቅድ ከ 18 በላይ የሚዲያ ተቋማት እና ከ 35 በላይ የመገናኛ ብዙሀን
ባለሙያዎች የተሳተፉበት 3 ዙር የሚዲያ ቱሮችን በማዘጋጀት ኮርፖሬሽኑን በስፋት ለማስተዋወቅ ሀዋሳ፣ አዳማ፣
በኮምቦልቻ እና ደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርኮች ጉብኝት ተደርጎ ኮርፖሬሽኑን በስፋት ለማስተዋወቅ በመቻሉ
አፈፃፀሙ 100%+ ሆኗል፡፡

ግብ 10:- በሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ መሰል ተቋማት እና የልማት አጋር ድርጅቶች ጋር ቅንጅታዊ
አስራር ማሳደግ

ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር ትስስር መፍጠር


በ 2014 በጀት ዓመት በ 9 ወራቱ ተቋማቱን በመለየት እና የመግባቢያ 2 ሰነድ /MOU ለማዘጋጀት ታቅዶ የሰነድ ስራ
በመዘጋጀቱ አፈጻጸሙ 100% ሆኗል፡፡ በቀጣይ ከተለዩት ተቋማት ጋር ውይይት በማድረግ የመግባቢያ ሰነዱን
ለመፈራረም የመግባቢያ ሰነድ ስምምነት ስራ በሂደት ላይ ይገኛል፡፡

59
ከተለያዩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማትና የትምህርት ማዕከላት ጋር የተለያዩ ተግባራት የተከናወኑ
ሲሆን DAB ከተሰኘ የምክር አገልግሎት ሰጪ ተቋም ጋር በተደረገ ግንኙነት ከጾታ ትንኮሳ ጋር ተያይዞ እየተካሄደ
ባለው ጥናት 235 የኢንዱስትሪ ፓርኩ ሰራተኞች እንዲሳተፉ ተደርጓል፡፡ በተጨማሪም ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ መስከረም
2014 ዓ.ም 64 ተመራቂ ተማሪዎች በኢንዱስትሪ ፓርኩ ውስጥ በሚገኙ ኩባንያዎች ውስጥ የሥራ ዕድል እንዲያገኙ
የሊንኬጅ ሥራ የተሰራ ሲሆን ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከሐረማያ ዩኒቨርስቲ 4 የመጀመሪያ ዲግሪ
ተማሪዎች በኢንተርን ሺፕ ፕሮግራም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ 1 የሁለተኛ ዲግሪ በኤክስተርን ሺፕ ፕሮግራም
እንዲሁም ለሦስተኛ ዲግሪ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 2 ተማሪዎች በኢንዱስትሪ ፓርኩ ጥናትና ምርምር በማድረግ
ላይ ይገኛሉ፡፡ በኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ በወሩ ውስጥ 39 የወሎ ዩኒቨርሲቲ ኢንቫይሮመንታል ሄልዝ
ተማሪዎች በኢንዱስትሪ ፓርኩ ግቢ ውስጥ የተግባር ልምምድ እንዲያደርጉ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል
ተደርጓል፡፡
በኮርፖሬሽኑ ልማት አጋር ድርጅቶች የሚያስፈልገውን የቴክኒክና ገንዘብ ድጋፍ ዳሰሳ ማድረግና ቅንጅት መፍጠር
በኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ዘርፍ በኩል ከልማት ድርጅቶች ጋር በመሆን የቤት አቅርቦት ስትራቴጂ ሰነድ በማዘጋጀት
ለመንግስት ለውሳኔ እንዲቀርብ ማድረግ 1% በተጠና ሰነድ ብዛት የተያዘ ሲሆን በታቀደው መሠረት ተከናውኗል፤
አፈጻጸሙም 100% ነው፡፡ በተጨማሪም ከአይሻ ከተማ አስተዳደር ጋር ለ 900 ሄክታር የሚሆን የመሬት መረከቢያና
ለሶስተኛ ወገን ማስተላለፊያ መግባቢያ ስምምነት ለመፈረም የታቀደ ቢሆንም በዕቅዱ መሠረት ማከናወን
አልተቻለም ሆኖም የመግባቢያ ስምምነት ተፈርሞ እንዲላክልን ለሶማሌ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ከተማ ልማትና
ኮንስትራክሽን ቢሮ በደብዳቤ ተጠይቋል፡፡
በበበጀት ዓመቱ ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት (ከሐረማያ ዩኒቨርስቲ 4 የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች
በኢንተርን ሺፕ ፕሮግራም፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ 1 የሁለተኛ ዲግሪ በኤክስተርን ሺፕ ፕሮግራም እንዲሁም
ለሦስተኛ ዲግሪ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 2 ተማሪዎች) በኢንዱስትሪ ፓርኩ ጥናት እና ምርምር በማድረግ ላይ
ይገኛሉ፡፡ በኮምቦልቻ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ 39 የወሎ ዩኒቨርሲቲ Environmental Health ተማሪዎች
በኢንዱስትሪ ፓርኩ ግቢ ውስጥ የተግባር ልምምድ እንዲያደርጉ አስፈላጊውን ድጋፍ እና ክትትል ተደርጓል፡፡ የአምቦ
ዩኒቨርሲቲ መስከረም 2014 ዓ.ም ላይ የሚመረቁ 73 ተማሪዎች በኢንዱስትሪ ፓርኩ ውስጥ በሚገኙ ኩባንያዎች
ውስጥ የሥራ ዐድል እንዲያገኙ የሊንኬጅ ሥራ ተሰርቷል፡፡

ከልማት አጋር ድርጅቶች የቴክኒክና የገንዘብ ድጋፍ እንዲገኝ ማድረግ

ከራሽያ ኢምባሲ፣ IFC, GIZ እና Purpose Black ውይይት ተደርጓል፡፡ ሆኖም ግን ተጨማሪ ባለመለየታችን ውይይት
ማካሄድ አልቻልንም፡፡ ምክንያቱም አንዳንድ ከረጂ ድርጅቶች የሚያስፈልጉ ድጋፎችን በተመለከተ ፕሮፖዛል
እያዘጋጀን በመሆኑና ስናጠናቅቅ ከረጂ ድርጅቶች ጋር ውይይት ለማድረግ በማሰብ ነው፡፡

በተለያዩ መስኮች ከተሰማሩ የልማት ድርጅቶች፣ ኤምባሲዎች እና የቢዝነስ ፎረሞች ላይ ውይይት ማድረግ

60
የአፍሪካ ልማት ባንክ October 13/2021 ባዘጋጀው ‘’Virtual Business Opportunities Seminar’’፣ 4 ኛው ዓለም ዓቀፍ
የንግድ ትርዒት /Ethiopia Plast Print Pack and Ethiopia Agro Food/ በስካይ ላይት ሆቴል ፣ አምራች
ኢንዱስትሪዎች የተሳተፉበት 4 ኛው ኤግዚቢሽንና ባዛር በኤግዚቢሽን ማዕከል እና 4th Edition of the ET Real
Estate and Home Expo on January 1, 2022 በሂልተን ሆቴል ተሳትፎ ተደርጓል፡፡ በዚህም ኮርፖሬሽናችን
ሊሳተፍባቸው ሊሰራባቸው የሚችሉ ሞዳሊቲዎች ልምድ የተቀሰመበት ሲሆን ይበልጥ በማዳበርና ለኮርፖሬሽኑ
ትርፋማነት ይረዳ ዘንድ ተጨማሪ ግብዓቶችን በማሟላት ሰነድ እያዘጋጀን እንገኛለን፡፡

ኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሉባቸውን ችግሮች በመለየት ከልማት አጋር ድርጅቶች ድጋፍ ማሰባሰብ

ቦሌ ለሚ እና ቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሉባቸውን ችግሮች መለየት የተቻለ ቢሆንም ከልማት ድርጅቶች
ድጋፍ ለማግኘት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት ባለመጠናቀቁ ድጋፍ አልተገኘም ሆኖም ድጋፉን ለማግኘት
የሚያስችል ፕሮፖዛል በማጠናቀቅ ለረጂ ድርጅቶች በማቅረብ በ 3 ኛው ሩብ ዓመት ድጋፍ ማሰባሰብ ታስቧል፡፡

ከልማት አጋር ድርጅቶች ጋር ቅንጅታዊ አሰራርን ማሳደግ

በበበጀት ዓመቱ በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ኢትዮ - ኮሪያን ቴክስታይል ቴክኖ ፓርክ የተሰኘ የልማት አጋር
ድርጅት ለጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ስራዎች የሚያግዝ 1.058 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚያወጣ የስልጠና እና
የተለያዩ ጥናቶች ለማካሄድ የሚውሉ ክፍሎች አስፈላጊ በሆኑ ዕቃዎች Furnish ለማደረግ የስምምነት ሰነድ
ተዘጋጅቶ ወደ ስራ ለመግባት በሂደት ላይ ይገኛል፡፡

 ከ DSW ጋር የተለያዩ ድጋፎች እንዲደረጉና ሥልጠናዎች እንዲሰጡ ውይይት ተደርጓል፡፡


 የሸማቾች ኅብረት ሥራ ማህበርን ለማቋቋም የሚያስችል የመነሻ ካፒታል ማግኘት ላይ IDH የሚባለው
ግብረ-ሰናይ ድርጅት 36,000.00 ዩሮ ለመደገፍ ተስማምቶ የኮንቲራት ውል ተፈርሟል፡፡
 DAB ከተሰኘ የምክር አገልግሎት ሰጪ ተቋም ጋር በተደረገ ግንኙነት ከፆታ ትንኮሳ ጋር ተያይዞ እየተካሄደ
ባለው ጥናት 235 ሰራተኞች ሲሳተፉ የማስተባበር ሥራ ተሰርቷል፡፡
 ከአፍሪካ ህብረት በኢንቨስትመንት ኮሚሽን እና GIZ ጋባዥነት የመጡ 7 እንግዶችን በመቀበል ፓርኩን
እንዲጎበኙ ተደርጓል፡፡
 ከሩሲያ ኢምባሲ ለመጡ አምባሳደሩን ጨምሮ ጉብኝት ላይ ለተገኙ 10 እንግዶች ስለ ፓርኩ ገለፃ
ተደርጎላቻው ፓርኩን እንዲጎበኙ የማስተባበር ስራ ተሰርቷል፡፡
ዕውቅ ከሆኑ ዓለም አቀፍ የኢንዱስትሪ ፓርክ አልሚዎች እና አስተዳዳሪዎች ጋር ግንኙነት መፍጠር

ሁለት ዕውቅ የሆኑ ዓለም ዓቀፍ የኢንዱስትሪ ፓርክ አልሚና አስተዳዳሪዎችን (Suzhou Industrial Parks in China
እና Changchun Economic & Technological Development Zone in China) ጋር በቢዝነስ ልማት ዙሪያ ግንኙነት
ለመፍጠር የሚያስችል ጥያቄ ቀርቦ ምላሽ እየተጠበቀ ነው፡፡ አማራጭ ሌሎች አልሚና አስተዳዳሪዎችን ማፈላለግ
61
ላይም ይሠራል፡፡ በ በበበጀት ዓመቱ ዓመቱ የመግባቢያ ስምምነት ማዘጋጀት በቁጥር ሶስት /3/ ዕቅድ የተያዘ
ቢሆንም ዘጠኝ /9/ በመዘጋጀቱ አፈፃፀሙ 100%+ ነው፡፡

በአለም አቀፍ ደረጃ የምክር አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶችን መለየትና ምርጥ ተሞክሮ መቀመር

ተሞክሮ ለመውሰድ ድርጅቶችን መለየትና ማጥናት በ በበበጀት ዓመቱ አንድ የጥናት ሰነድ ለማዘጋጀት ታቅዶ
ተሞክሮ የሚወሰድባቸው ድርጅቶችን ሥራ ተጀምሮ ክንውኑ 10% ሲሆን ለአፈጻጸሙ ማነስ እንደ ችግር የታየው
በተመሳሳይ የሥራ መስክ የተሰማራ ድርጅቶች አለማግኘት ነው፡፡

4. ኮርፖሬት ገቨርናንስ እና ፋይናንስ


4.1. ኮርፖሬት ገቨርናንስ
የቦርድ አመራር አፈጻጸም

በበጀት ዓመቱ በአዲስ መልክ የተዋቀው የቦርድ አመራር የኮርፖሬሽኑን መጀመሪያ ለበበበጀት ዓመቱ ዓመት ሪፖርት
በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል፡፡

የስጋት አስተዳደር

በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን መምሪያው በአደረጃጀት ተደግፎና የሠው ኃይሉን በማሟላት ወደ ስራ እንዲገባ
ከመደረጉ ባሻገር ከብሔራዊ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ጋር በጥምረት ሥራዎችን ለመከወን እንቅስቃሴ እየተደረገ
ይገኛል፡፡

የውስጥ ኦዲት ስራዎች

የፋይናንስና ሕጋዊነት የኦዲት በተያዘው ዕቅድ መሠረት የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ቅ/ፅ/ቤት የ 2012 በጀት ዓመት
ሒሳብ (ከሐምሌ 1/2011 ዓ.ም - ሰኔ 30/2012 ዓ.ም) የፋይናንስና ሕጋዊነት ኦዲት ቀሪ 30% ስራው ተጠናቋል፡፡
የድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ ቅ/ፅ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት ሂሳብ (ከሐምሌ 1/2012 ዓ.ም - ሰኔ 30/2013 ዓ.ም)
የፋይናንስና ሕጋዊነት ኦዲት ስራ በተጨማሪም የተወዳዳሪነትና ሥራ ፈጠራ ፕሮጀክት ፅ/ቤት (CJCP) የ 2013 በጀት
ዓመት የ 6 ወራት ሒሳብ (ከጥር 1/2013 ዓ.ም - ሰኔ 30/2013 ዓ.ም) ስራው ተጠናቆ ሪፖርት የቀረበ በመሆኑ ክንውኑ
100% ሆኗል፡፡

የክዋኔ ኦዲት በተያዘው ዕቅድ መሠረት በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ቅ/ፅ/ቤት የ 2012 በጀት ዓመት የንብረት አስተዳደር
የክዋኔ ኦዲት ቀሪ 30% ስራ፣ የ 2012 በጀት ዓመት የግዥ አፈፃፀም የክዋኔ ኦዲት ቀሪ 30% ስራ፣ የ 2012 በጀት ዓመት
የሰው ሃብት አስተዳደር ስራዎች አፈፃፀም ቀሪ 30% ስራ፣ በ 2013 በጀት ዓመት ከሼዶች ኪራይና ከሌሎች ምንጮች
የሚገኘውን የገቢ አሰባሰብና የውል ስምምነት አፈፃፀም ስራው ሥራው ተጠናቆ ሪፖርት ቀርቧል ክንውኑም 100%
ሲሆን በዋናው መ/ቤት የሰው ሃብት አስተዳደር የ 2013 በጀት ዓመት ቅጥር፣ የደረጃ ዕድገት፣ ዝውውርና ስንብት
አፈፃፀም ላይ የክዋኔ ኦዲት ስራው ተጠናቋል፡፡ የድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ ቅ/ፅ/ቤት የ 2013 በጀት ዓመት የሰው
62
ሃብት አስተዳደር ስራዎች አፈፃፀም፣ የ 2013 በጀት ዓመት የግዥ አፈፃፀም፣ የ 2013 በጀት ዓመት የንብረት
አስተዳደር የክዋኔ ኦዲት ስራው ተጠናቆ ሪፖርት የተዘጋጀ በመሆኑ ክንወኑ 100% ነው፡፡

የክትትል ኦዲት ዕቅድ በተያዘው መሠረት በኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ፓርክ (ICT Park) ከ 2009 እስከ
2013 በጀት ዓመት 1 ኛ ሩብ ዓመት ድረስ በፌደራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት በቀረበው የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት መሰረት
በተገኙ የኦዲት ግኝቶች ላይ የማስተካከያ/የእርምት እርምጃ መወሰዱን በተመለከተ የክትትል ኦዲት ስራው ተጠናቆ
ሪፖርት በመቅረቡ ክንወኑ 100% ነው፡፡ በውጭ ኦዲት በሚቀርበው የኮርፖሬሽኑ የ 2011 በጀት ዓመት የፋይናንስና
ሕጋዊነት ኦዲት ሪፖርት መሰረት በኦዲት ግኝቶች ላይ የማስተካከያ/ የእርምት እርምጃ መወሰዱን በተመለከተ
የውጭ ኦዲቱ ባለመጠናቀቁና ሪፖርት ባለመቅረቡ የክትትል ኦዲቱ አልተከናወነም፡፡
በሌላ በኩል የክትትል ኦዲት በተያዘለት ዕቅድ በ 2013 በጀት ዓመት የዋና መ/ቤት እና የቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች የንብረት
ቆጠራ ሪፖርት መሰረት የማስተካከያ ወይም የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ ለማድረግ እና መወሰዱን ለማረጋገጥ
የክትትል ኦዲት እየተከናወነ የሚገኝ በመሆኑ ያለበት ደረጃ 75% ነው፡፡ በውጭ ኦዲት በቀረበው የተወዳዳሪነትና
ሥራ ፈጠራ ፕሮጀክት ፅ/ቤት (CJCP) የ 2013 በጀት ዓመት የፋይናንስና ሕጋዊነት ኦዲት ሪፖርት የኦዲት ግኝቶች
መሰረት የማስተካከያ/የእርምት እርምጃ መወሰዱን ለማረጋገጥ የክትትል ኦዲት ስራው ተጠናቆ ሪፖርት በመቅረቡ
ክንውኑ 100% ሆኗል፡፡

የኮርፖሬት ማኀበራዊ ኃላፊነት

በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተፈጠረ ግጭት ለተጎዱና ለተፈናቀሉ የህብረተሰብ ክፍሎች አንደ ኮርፖሬሽን ድጋፍ
ተደርጓል፡፡ በዚህም መሠረት በአፋር/ሰመራ፣ ደብረ ብርሃን፣ ሸዋሮቢት፣ ኮምቦልቻ 30 ሚሊዮን የሚጠጋ ብር ድጋፍ
የተደረገ ሲሆን የድጋፍ ዓይነቶች ብርድልብስ፣ የመመገቢያ ቁሳቁስ፣ የዳቦ ዱቄት፣ስኳር፣ መኮሮኒ፣ ፓስታ፣ የምግብ
ዘይት፣ ውሃ፣ የገላ ሳሙና፣ የልብስ ሳሙና፣ የሴቶች የንጽህና መጠበቂያ ናቸው፡፡ ለሀገር ድንበር ስዋደቁ ለተጎዱ
የመከላከያ ሠራዊት አባላት በማቆያቸው ቂሊንጦ ኢ/ፓ በመገኘት 1.4 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ብር የእራት
ፕሮግራም በማዘጋጀት የመመገብ ስራ ተሰርቷል፡፡ በተጨማሪ 378 የኮርፖሬሽኑ ሠራተኞች ለጀግና መከላከያ
ሠራዊታችን ደም ለግሳዋል፡፡
ከኮርፖሬት ማህበራዊ ኃላፊነት ትግበራ ጋር በተያያዘ የሚያጋጥሙ መሰረታዊ ችግሮች እና ተግባሩን ውጤታማ
ለማድረግ ልንከተላቸው ስለሚገቡ መሰረታዊ ሂደቶች በቦሌ ለሚ እና ደብረብርሀን ኢንዱስትሪ ፓርኮች የቴክኒክ
ድጋፍ ተደርጓል፡፡ በዚሁ መሰረት ኢንዱስትሪ ፓርኮች የኮርፖሬት ማህበራዊ ኮሚቴ አቋቁመው ትኩረት የሚሹ
ተፅዕኖዎችን በመለየት፣ አጋር እና ባለ ድርሻ አካላትን በማሳተፍ ተግባሩ ትኩረት ተሰጥቶት መሰራት እንዳለበት
ግንዛቤ ተፈጥሮዋል፡፡
በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ በሚገኙ አምራች ድርጅቶች ተቀጥረው የሚሰሩትን ሰራተኞች የኑሮ ሁኔታ
በማሻሻል የተረጋጋና ውጤታማ የስራ ህይወት እንዲኖራቸው ለማስቻል የሚያግዝ የሰራተኞች ራስ አገዝ የህብረት
ስራ ማህበር (worker cooperative) ህጋዊ እውቅና ኖሮት እንዲቋቋም ተደርጓል፡፡ ማህበሩ ራሱን በራሱ
እንዲያስተዳድር ህጋዊ ተደርጎ የተቋቋመ ሲሆን ራሱን በራሱ የመምራትና ሙሉ የማስተዳደር አቅም እስኪፈጥር
63
ድረስ የማደራጀት፣ የመስሪያ ቦታና ቁሳቁስ ድጋፍ ከኢንዱስትሪ ፓርኩ እንዲሁም ለመነሻ ካፒታል በአይ ዲ
ኤች/IDH በኩል ድጋፍ እንዲያገኝ የመግባቢያ ስምምነት ተፈርሟል፡፡
በዚህም መሰረት ከ 3,200 (ሶስት ሺ ሁለት መቶ በላይ) መስራች አባላት የተመዘገቡና አስፈላጊውን የመመስረቻ
ሰነዶች፣ መተዳደሪያ ደንብ፣ የአዋጭነት ጥናትና የስራ እቅድ እንዲሟላ ተደርጓል፡፡ ማህበሩ የአጭር፣ የመካከለኛና
የረጅም ጊዜ የስራ እቅድ ያለው ሲሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ የሰራተኞችን አቅም ያገናዘበ የመሰረታዊ ፍጆታ
ምርቶችን እና የሴቶች የንፅህና መጠበቂያ ግብዓቶችን በጠመጣጣኝ ዋጋ የማቅረብ እቅድ እንዲኖረው ተደርጓል፡፡
የስራ ማስጀመሪያ ብሩ እንዲለቀቅም ከአይ ዲ ኤች/IDH አስተባባሪ ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን ብሩ ገቢ ሲደረግ
በእቅዱ መሰረት ስራ የሚጀምር ይሆናል፡፡

ዲስክሎዠር
በመደበኛነት መረጃ ለሚፈልጉ ተቋማት በኢንዱስተሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዕቅድና ክትትል መምሪያ
ወቅታዊ ሪፖርቶችን በየሩብ ዓመቱ የሚላክ ሲሆን ለመገናኛ ብዙሀንም ብሎም መረጃ ለሚፈልጉ ከተለያዩ
የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በተገቢው መንገድ ፋይናንስ ነክ የሆኑና ፋይናንስ ነክ ያልሆኑ መረጃዎችን ተደራሽ
የማድረግ ሥራ ተከናውኗል፡፡

4.2. የኮርፖሬት ፋይናንስ አፈጻጸም

የውጭ ኦዲትና የ IFRS ትግበራ አፈፃፀም ደረጃ

ዓለም ዓቀፍ የፋይናንስ ስርዓት /IFRS/ ተግባራዊ ስለመደረጉ አሁን ላይ ያለበት ሁኔታ እና ደረጃን በሚመለከት፡- -
እስከ 2010 ያለው ሂሳብ በ /IFRS/ ተዘግቶ በውጪ ኦዲት ተመርምሯል -ከ 2011 ጀምሮ ያለው በ /IFRS/ ተሰርቷል፡፡

በሂሣብ ማስመርመር ሂደት ያሉ ችግሮችና መወሰድ ያለባቸው እርምጃዎች

በሂሣብ ማስመርመር ሂደት ላይ ምንም ችግር ባይገጥመንም የኮርፖረሽኑን የሂሳብ ሪፖርቶች በኢንተርፕራይዝ
ሪሶርስ ፕላኒግ የማውጣት ሥራው እንዲፋጠን በቁርጠኝነት ለበጀት ዓመቱ ሪፖርት ሊሠራ ይገባል፡፡

የብድር መጠንና የአከፋፈል ሁኔታ

ኮርፖሬሽኑ ብድር የለበትም

4.3. የሪፎርምና የሰው ሃይል አቅም ግንባታ ስራዎች

ሪፎርም ስራዎች አፈጻጸም


በበጀት ዓመቱ በበበጀት ዓመቱ ማሻሻያ የተደረገባቸው የሰው ሃብት አስተዳደር መመሪያ ተዘጋጅቶ ለማስጸደቅ
የቀረበ ሲሆን አፈፅፀሙ 90% ነው፡፡ የሥራ መሪዎች መተዳደሪያ ደንብ፣ የኮርፖሬሽኑ ብድር መመሪያ እና የጥቅማ
ጥቅም ፓኬጅ መመሪያ ረቂቅ ለማስጸደቅ ቀርቧል፡፡ የባንክ ብድር መመሪያ ተዘጋጅቶ የፀደቀ ተግባራዊ ሆኗል፡፡የሰው

64
ሃብት አስተዳደር ስርአትን ለማዘመን ኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒንግን (ERP) ትግበራ የተከናወነ ሲሆን
አፈፃፀሙም 100% ነው፡፡

የአቅም ግንባታ ስራዎች /ለአመራርና ሠራተኞች/


የአቅም ክፍተት የሚያሟሉ ከመምሪያዎች ፍላጐት መሠረት ያደረገ 4/አራት/ ስልጠናዎች የተሰጡ ሲሆን እነሱም፡-
 የአቅም ክፍተት የሚያሟሉ ከመምሪያዎች ፍላጐት መሠረት ያደረገ /አንድ/ IFRS ስልጠና ለቅርንጫፍ
ኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ለዋናው መ/ቤት ሠራተኞች እና የስራ ኃላፊዎች በአጠቃላይ 17 ሰራተኞች
ተሰጥቷል፡፡
 ERP/ኢንተርፕራይዝ ሪሶር ፕላኒን/ ስልጠና ከኢንዱስትሪ ፓርክ እና ከዋናው መ/ቤት ለተውጣጡ ለ 52
ለፋይናንስ እና አስተዳደር ሠራተኞች እና የስራ መሪዎች ተሰጥቷል፡፡
 ጀንደር ሚኒስትሪሚንግ ስልተጠና ከቅርን|ጫፍ ኢንዱስትረሪ ፓርኮች እና ከዋናው መ/ቤት ለተውጣቱ 25
ሠራተኞች ተሰጥቷል፡፡

የሠራተኛ ሁኔታ በጾታ የቋሚ /ኮንትራት/ጊዜያዊ

በ በበበጀት ዓመቱ አዲስ የተቀጠሩ ሰራተኞች ወንድ 107 እና ሴት 31 በድምሩ 138 በዚህም መሰረት የዋናው መስሪያ
ቤትን ጨምሮ በኢንዱስትሪ ፓርኮች የኮርፖሬሽኑ አጠቃላይ የሰው ኃይል ሁኔታ በ 2013 በጀት ዓመትመጨረሻ
ከነበረበት 877 በያዝነው በጀት ዓመት 6 ወራት ውስጥ 959 ደርሷል፡፡ በኮርፖሬሽኑ የሚገኙ ሠራተኞች ጾታን
በተመለከተ ወንድ 695 እና ሴት 264 በድምር 959 ነዉ፡፡ በአሁኑ ወቅት በኮርፖሬሽኑ በኮንትራት ያሉ ሠራተኞች
ሴት 6፣ ወንድ 8 በአጠቃላይ 14 ሠራተኞች ይገኛሉ፡፡

4.3. ዘርፈ ብዙ ሥራዎች

በስርዓተ ፆታና በኤች.አይ.ቪ ኤድስ ዙሪያ ከፌዴራል ኤችአይቪ/ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽ/ቤት ጋር
በመነጋገር በጥር ወር ከ 6 የተለያዩ ፓርኮች አራት አራት (4) (4) ሰው በመምረጥ ለ 28 የፓርክ ሰራተኞች
የአቻ ለአቻ ስልጠና ተሰጥል፡፡
ኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ኮርፖሬሽን እና CJC (የተወዳዳሪነትና ሥራ ፈጠራ ፕሮጀክት ማ/ጽ/ቤት) ጋር
በመተባበር የሥርዓተ ፆታ ፖሊሲዎች፣ የሥርዓተ-ፆታ ልዩነትን ለማቃለል፣ ፍትሃዊ ክፍያ ለመፍጠር እና ፆታዊ
ትንኮሳዎችን ለመከላከል በሥርዓተ-ፆታ ላይ የተመሠረተ ጥናት ዋናው መ/ቤትን ጨምሮ በ(በበበጀት ዓመቱ
) 6 ኢንዱስትሪ ፓርኮች እንዲደረግ ክትትል ድጋፍ ተደርጓል፡፡
ኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ኮርፖሬሽን እና CJC (የተወዳዳሪነትና ሥራ ፈጠራ ፕሮጀክት ማ/ጽ/ቤት) ጋር
በመተባበር በማዶ ኢንተርናሽናል ሆቴል 21 ለሚሆኑ ሠራተኞች ከሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች በማውጣጣት
"የ Gender Mainstreaming" የአሰልጣኞች ስልጠና እንዲወስዱ ተደርጓል፡፡

4.4. የሙያ ደህንነትና ጤንነት


65
የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎችን መከላከልና መቆጣጠር

በኮርፖሬሽኑ ስር የሚገኙ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ከእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች ለመከላከልና የአደጋ ስጋት ቅነሳ
ዝግጁነት ተግባራትን በመፈፀም የፓርኩን አደጋ የመቋቋም አቅም ለማሳደግና አደጋዎች ቢከሰቱ በፍጥነት በቁጥጥር
ስር ለማዋል በሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርክ የቅድመ አደጋ መከላከል ስራ ተከናወኗል፡፡ በበጀት ዓመቱ በኮርፖሬሽኑ
በተለያዩ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ባሉ ኩባንያዎች ተቀጥረው ለሚሰሩ ሰራተኞች በእሳት እና ድንገተኛ አደጋዎች
መከላከል እና መቆጣጠር ዙሪያ ለሰራተኞች ስልጠና እና ግንዛቤ የመስጠት ሥራ ተከናውኗል፡፡ በዚህ መሠረት
በኮርፖሬሽኑ ለ 9,817.00 ሠራተኞች ስልጠና ግንዛቤ ለመስጠት ታቅዶ ለ 11,411 ሠራተኞች በመሰጠቱ ክንውኑ 100%
+ ነዉ፡፡ በተጨማሪምበሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ለ 35,000 ማህበረሰብ ክፍል ተደራሽ የሆነ ራዲዮ ጣቢያ በመጠቀም
የቅድመ አደጋ የጥንቃቄ መልዕክቶችን የማስተላለፍ ስራ ተሰርቷል፡፡

በኢንዱስትሪ ፓርኮች የጤና አጠባበቅ ስራዎች

በኮርፖሬሽኑ ወና መ/ቤትና በሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች የጤና አጠባበቅ ስራዎችን በተመለከተ በበበጀት ዓመቱ
ከአቅራቢያ የሚገኙ ጤና ተቋማት ጋር በመተባበር የኮቪድ-19 መከላከያ ክትባት ለ 22,830 ሠራተኞች መሰጠት
ተችሏል፡፡ እንዲሁም በሁሉም ኢንዱስት ፓርኮች በኮቪድ 19 ዙሪያ ለ 70,027.00 ሠራተኞች ግንዛቤ ለመስጠት
የታቀደ ሲሆን ለ 69,235.00 ሠራተኞች በመሰጠቱ አፈፃፀሙ ከዕቅዱ አንፃር በፐርሰንት ስገመገም ከ 98.87% በላይ
ነው:: የተለያዩ ተለላፊ በሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ዙሪያ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ በኮርፖሬሽኑ በበጀት
ዓመቱ ለ 11,299 ሠራኞች ለመስጠት ታቅዶ ለ 9,949 ሠራተኞች ግንዛቤ የተሰጠ ሲሆን አፈፃፀሙ ከዕቅ አንፃር
በፐርሰንት 88 ነው፡፡ የመጀመሪያ ዕርዳታ አሰጣጥን በሚመለከት የአሰልጣኞች ስልጠና ከሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች
የተውጣጡ 20 የቅድመ ሆስፒታል እና አንቡላንስ አገልግሎት ባለሙያዎች በብሄራዊ ቀይ መስቀል አማካይነት
በኮፖሬሽኑ ወጪ ስልጠና ወስደው የአሰልጣኝነት Certificate ወስዶ በማሰልጠን ላይ ናቸው፡፡ የጤና አጠባበቅ ስልጠና
በየጊዜው በመሰጠቱ ሠራተኞች ከተላላፊ በሽታዎች አስቀድሞ ራሳቸውን በመከላከል ስራቸው ላይ ውጤታማ
እንዲሆኑ የሚረዳ ነው፡፡
በበጀት ዓመቱ ውስጥ በ 6 ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ (ሀዋሳ፣ ደብረብርሃን፣ ኮምቦልቻ፣ ድሬዳዋ፣ ባህርዳር እና
አዳማ) ለ 611 ሰራተኞች በስራ ቦታ የተከሰቱ ድንገተኛ አደጋዎች የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ ተሰጥቷል፡፡ ከነዚህም
ውስጥ 511 የሪፈራል አምቡላንስ አገልግሎት ተሰጥቷቸው በአቅራቢያ ወደሚገኝ የጤና ተቋም እንዲሄዱ በማድረግ
አስፈላጊውን ህክምና አግኝተዋል፡፡ በአጣቃላይ በኢንዱስትሪ ፓርኮች ለአደጋ ስጋት መንስኤዎች እና ለሚከሰቱ
አደጋዎች 100% ፈጣን ምላሽ እንዲያገኙ ታቅዶ በበበጀት ዓመቱ ውስጥ ሊከሰቱ የሚችሉ ችግሮች እና አደጋዎች
ከባለድርሻ አካላት በመሆን ምላሽ እንዲያገኙ እና ክትትል የማድረግ ስራዎች ተሰርቷል፡፡

5. የበጀት ዓመቱ ሪፖርት በሠንጠረዥ

66
የኮርፖሬሽኑ ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ከላይ የተጠቀሰውን ይዘት የሚያሟላ ሆኖ የሪፖርቱን ወጥነት
ለመጠበቅ እንዲቻል በሰንጠረዥ አፈጻጸሞች ከዚህ በታች የተመለከቱት እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡
ኦፐሬሽን
ምርት/አገልግሎት በዓይነት( በመጠንና በዋጋ)
የ 2014 በጀት ዓመት በበበጀት ዓመቱ
ተ.ቁ /የአገልግሎት ዓይነት መለኪያ
ዕቅድ ክንውን
1 Sheds Shed no 177 135
8,970.81
2 One Stop Service (OSS) Square meter -

3 Residential Square meter - 2,163.01


540.55 (total
4 Land Lease Square hectar 61.42 (sub-leased)
available area)
Consultancy and
5 ቁጥር (ሰው ወር) 260 164.73
Training
6 Water Service M3 1,099,609.58 1,099,609.58
7 ETP/STP M3 1,193,860.50 951,219.30
8 Others - -

የትርፍ (ታክስ በፊት)፣

ያለፈው ተመሳሳይ ጊዜ ክንውን


የትርፍ መጠን በአገልግሎት የትርፍ (ታክስ በፊት)(በሚሊዮን ብር) (በሚሊዮን በመቶኛ
ተ.ቁ
ዓይነት ብር)
ዕቅድ አፈጻጸም %
ከሼድ ኪራይ ፣ ከፓርኮች 101,137,983 79,004,184.13 ትርፍ 78 (77.5) ከ 100% በላይ
አገልግሎት፣ ከምክርና ስልጠና ትርፍ በበበጀት ዓመቱ ሚሊዮን እድገት
1 አገልግሎት ገቢ ከኦፕሬሽን፣ በበጀት ኪሳራ
አስተዳደር እና ሌሎች ወጪዎች ዓመቱ
ተቀናንሶ

የውጭ ምንዛሪ ግኝት ዕቅድ አፈጻጸም በ 2014 በጀት ዓመት

ተ.ቁ ኢንዱስትሪ ፓርክ ኤክስፖርት ዕቅድ አፈጻጸም አፈጻጸም በመቶኛ


1 ሀዋሳ 80,510,623.00 71,662,490.00 89%
2 ቦሌ ለሚ 40,667,765.00 37,906,749.30 93.20%
3 ኮምቦልቻ 6,099,638.33 7,387,152.07 100%+
4 አዳማ 10,181,923.00 11,125,370.00 100%+
5 ድሬዳዋ 5,388,929.70 4,674,246.70 86.70%
6 ደብረብርሃን 1,895,761.00 1,430,246.00 75.40%
7 አዲስ ኢ/መንደር 1,087,920.00 971,128.00 89.30%
67
8 ባህርዳር 1,062,200.00 572,200.00 53.86%
9 ቂሊንጦ 0 0 -
10 ጅማ 914,100.00 680,675.00 74.50%
ድምር 147,808,860.03 136,410,257.07 92.28828166
11 አይ ሲ ቲ ፓርክ 23,373,586.39 16,356,004.46 69.97644344
ድምር 171,182,446.42 152,766,261.53 89.2417796

ኮርፖሬት ገቨርናንስ

የሥራ አመራር ቦርድ በበበጀት ዓመቱ የተደረጉ ስብሰባዎች

ተ.ቁ የስብሰባ ቀን የስብሰባው ዋና ዋና አጀንዳዎች በስብሰባ ያልተገኙ አባላት ስም


1 መጋቢት 23  አጀንዳ 1.የተቋም ትውውቅ የለም
የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት
ኮርፖሬሽን የእስካሁን ጉዞ የፋይናስ
ቁመና እንዲሁም የህግ መሰረቶች፤
 የኢንዱስትሪ ፓርኮች ሥራ አመራር
ቦርድ ጽ/ቤት መቋቋም፤
 የኢንዱስትሪ ፓርኮች 2014 የቀሪ 6
ወራት የተከለሰ ዕቅድ ገምግሞ

ኮርፖሬት ማኀበራዊ ኃላፊነት

ክንውን /በሺህ ብር/


የድጋፍ ዓይነት
ተ.ቁ ዕቅድ በገንዘ
በዓይነት

ብርድልብስ፣ የመመገቢያ ቁሳቁስ፣ የዳቦ
አፋር/ሰመራ፣ ደብረ
30 ሚሊዮን የሚጠጋ ዱቄት፣ስኳር፣ መኮሮኒ፣ ፓስታ፣የምግብ ዘይት፣ ውሃ፣
1 ብርሃን፣ ሸዋሮቢት፣
ብር የገላ ሳሙና፣ የልብስ ሳሙና፣ የሴቶች የንጽህና
ኮምቦልቻ፣
መጠበቂያ፣
1.4 ሚሊዮን የሚጠጋ ለተጎዱ የመከላከያ አባላት በማቆያቸው በመገኘት
2 ቂሊንጦ ኢ/ፓ የእራት ፕሮግራም በማዘጋጀት የመመገብ ስራ
ብር
3 ደም ልገሳ 378 ሠራተኞች ደም ለግሳዋል

ኮርፖሬት ፋይናንስ

68
ኮርፖሬሽኑን ሂሣብ መዘጋትና ማስመርመር ሁኔታ

ተ.ቁ የሂሣብ መዝጋትና ማስመርመር የበጀት ዓመት መግለጫ


የ 2011 በጀት ሂሳብ
የ 2011፣ 2012 እና 2013 በጀት ዓመት ሂሳብ
1 የተዘጋ ሂሣብ የ 2012 በጀት ሂሳብ
ተዘግቷል
የ 2013 በጀት ሂሳብ
2 በመዘጋት ላይ ያለ - -
በመጀመሪያ በበበጀት ዓመቱ ዓመት የ 2011
3 በመርመር ላይ ያለ 2011 በጀት ዓመት ሂሳብ በጀት ዓመት ሂሳብ ኦዲት እንዲደረግ ለኦዲት
ሰርቪስ ተልኳል
የ 2010 በጀት ዓመት ሂሳብ ተመርምሮ
4 የተመረመረ 2010 በጀት ዓመት ሂሳብ
አልቋል

የሀገር ውስጥ ብድር ክፍያ ሁኔታ (በሚሊዮን ብር)

ብድሩ ጠቅላላ
የአበዳሪው ባንክ/ እስካሁን ቀሪ የብድር መጠን
ተ.ቁ ተወሰደበት ብድር ዕቅድ ክንውን በመቶኛ
ተቋም ስም የተከፈለ (ሚሊዮን)
ቀን/ዓ.ም መጠን
የለም የለም የለም

ማስታወሻ፤ የብድር ዉል የሚፈፀመው ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በመሆኑ መረጃው በእኛ ተቋም አይገኝም፡፡

የውጭ ሀገር ብድር ክፍያ (በሚሊዮን USD)

ጠቅላ
የአበዳሪው ብድሩ
ላ እስካሁን ቀሪ የብድር መጠን
ተ.ቁ ባንክ/ ተቋም ተወሰደበት ዕቅድ ክንውን በመቶኛ
ብድር የተከፈለ (ሚሊዮን)
ስም ቀን/ዓ.ም
መጠን
የለም የለም የለም

ማስታወሻ፤ የብድር ውል የሚፈፀመው ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በመሆኑ መረጃው በእኛ ተቋም አይገኝም፡፡
የሪፎርም ስራዎች አፈጻጸም

በዕቅድ የተያዙ ዋና ዋና የሪፎርም በበበበጀት ዓመቱ ዓመቱ የተከናወኑ አፈጻጸ የተገኘ ውጤት
ሥራዎች ሥራዎች ም
በመቶኛ
የሰራተኞች ደንብ ልብስና ብራንዲንግ 100%
ስራዎች
ዲጂታል የሰራተኞች የአቴንደንሰስ 100% የተሻለ የመግቢያና መውጫ ሰዓት
መቆጣጠረያ ስረዓት የማክበር ባህል እንዲተገበር
ተችሏል፡፡
ማሻሻያ የተደረገባቸው የሰው ሃብት 90%
አስተዳደር መመሪያ፣ የሥራ መሪዎች
መተዳደሪያ ደንብ፣ የኮርፖሬሽኑ ብድር
69
መመሪያ እና የጥቅማቅጥም ፓኬጅ
የኮርፖሬሽኑን የአሰራር ሥርዓት መመሪያ ረቂቅ ለማስጸደቅ ቀርቧል፡፡
የሚያግዙ እና የሚያቀላጥፉ የሰው ሃብት አስተዳደር ስርአትን 100% የዘመነ አሠራር በመተግበሩ የሰው
መመሪያዎችን ማሻሻያ ማጠናቀቅና ለማዘመን ኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ኃይል የሥራ ጊዜና ቅልጥፍናን
ማስፀደቅ፤እንዲሁም አዲስ ፕላኒንግን (ERP) መተግበር መጨመር
መመሪያዎችን ማዘጋጀት፤
የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒንግን (ERP) 50% በሰው ሃብት አስተዳደር (ERP)
ላይ ያጋጠሙ የሰራተኞች የአቅም ሙሉ በሙሉ ትግበራ ላይ
ክፍተቶች በመለየት የሥራ ላይ ሥልጠና በመዋሉ የአሠራር ቅልጥፍናን
መስጠት ጨምሯል

በተጀመረው የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ 100%


ፕላኒንግን (ERP) ስርዓት ላይ ያልተካተቱ በትግበራ ላይ ያለውን ክፍተት
የሰው ሀብት አስተዳደር ተግባራት ላይ በማየት ተከታታይ ሥልጠና
ማስፋፊያ እንዲደረግላቸው ማስፈለጉ
ለሚመለከተው አካል በማቅረብ ዘመናዊ
አሰራርን መተግበር፤
የባንክ ብድር መመሪያ ተዘጋጅቶ ፀድቆ 100% የሠራተኛውን ፍላጎት ማርካት፣
ተግባራዊ እንዲሆን ለቅርንጫፍ ፅ/ቤት የሥራ ተነሳሽነትን መጨመር
እና ለሁሉም የስራ ክፍሎች ተልኳል
የኮርፖሬሽኑን የሰው ሀብት ብቁ የአቅም ክፍተት የሚሞሉ ፍላጎትን 71.4%
በሆነ መንገድ ማደራጀት፤ መሰረት ያደረገ በበጀት ዓመቱ 18
ሥልጠና እንዲሰጡ ማመቻቸት ላይ 5
ሥልጠናዎች በመሰጠቱ
በሶሻል ኮሚቴ ማዋቀር 100% የሰራተኞችን ማህበራዊ
ግንኙነቶች ማጠናከር
የኮርፖሬሽኑን ተቋማዊ የስራ ባህል የሶሻል ኮሚቴው የሚመራበት 100%
የሚያሻሽሉ አዳዲስ አሰራሮችን መተዳደሪያ ደንብ ማዘጋጀት፤
መተግበር፤ የቁልፍ አፈጻጸም ውጤት አመልካቾችን 100%
መሰረት ያደረገ የሥራ አፈጻጸም ምዘና
መመሪያ ማዘጋጀት
አፈጻጸምን ለመለካት የሚያስችሉ 100%
መመዘኛ ቅጾችን ማዘጋጀት

ለአመራርና ሠራተኛ የተሰጠ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች

ተቁ የሥልጠና ዓይነት/በዋና ዋና ጥቅል ርዕሱ አፈጻጸም

70
(management, finance, technic and others) ዕቅድ ወ ሴ ድምር በ%
1 የበጀት ዝግጅትና አስተዳደር ለአራት ቀናት፤ 4 0 4 4 100
የግራውንድ ዋተር ኢንቨስቲጌሽን ለአምስት ቀናት
9 2 11 11 100+
2 በዋናው መ/ቤት፤
ኢሞሽናል ኢንተለጀንስ ለሶስት ቀናት
6 4 10 10 100+
3 በኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች አገልግሎት፣
የውስጥ ኦዲት ቁጥር ለ 10 ቀናት በኢትዮጵያ
5 1 6 6 120
4 ስራ አመራር ኢንስቲትዩት
ድምር 24 7 31 31 100+
ማስታወሻ፡ በበጀት ዓመቱ ዓመቱ የታቀደ የሥልጠና ብዛት 7 ሲሆን የተሰጠ ሥልጠና 4 አፈፃፀሙ 57% ነዉ፡፡
በስራ ላይ ያለ የሰው ሀይል
የቅጥር ሁኔታ አፈጻጸም
ወንድ ሴት ድምር
ቋሚ 695 264 959
ኮንትራት 8 6 14
ጊዜያዊ - - -
ድምር 703 270 973

በበጀት ዓመቱ የተፈጠሩ እና የለቀቁ ሰራተኞች


ሌሎች
የኢንዱስትሪ ፓርኩ የበጀት ዓመቱ አፈጻጸም መደበኛ የተፈጠረ ጠቅላላ
ተ.ቁ ወንድ ሴት ድምር የለቀቁ ወንድ ሴት
ስም ዕቅድ በመቶኛ ድምር የስራ ድምር
ዕድል
1 ሀዋሳ 20,351 2,228 13,896 16,124 79.20% 20,468 2,475 22,399 24,874 6,187 31,061
+
2 ቦሌ ለሚ 13,819 1,766 12,232 13,998 100% 11,027 2,175 18,503 20,678 2,583 23,261
3 ኮምቦልቻ 1,955 171 1,254 1,425 72.80% 2,933 180 1,745 1,925 1,076 3,001
4 አዳማ 8,714 787 7,134 7,921 90.80% 7,609 633 6,097 6,730 998 7,728
5 ድሬዳዋ 2,702 686 1,407 2,093 77.50% 1,831 1,112 692 1,804 541 2,345
6 ደብረብርሃን 1,934 108 881 989 51.10% 895 112 1476 1588 447 2,035
7 ጅማ 170 0 0 0 0 1,368 30 124 154 15 169
8 አ/ኢ/መንደር 914 345 603 948 100%+ 770 653 1,434 2,087 25 2,112
9 ቂሊንጦ 381 13 53 66 17.00% 26 67 112 179 448 627
10 ባህርዳር 1,130 12 218 230 20.40% 622 55 706 761 362 1,123
11 ሠመራ 0 0 0 0 0 0 0 0 0 356 356
12 አይሲቲ ፓርክ 700 189 307 498 71.14286 431 743 596 1339 959 2,298

ድምር 52,770 6,305 37,985 44,292 84 47,980 8,235 53,884 62,119 13,997 76,116

6. ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና የተወሰዱ የመፍትሄ እርምጃዎች

71
በበበበጀት ዓመቱ ዓመቱ በአፈፃፀም ሂደት ዉስጥ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች

 የቦታ ይዞታ ይገባኛል ጥያቄ በሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች በሚባል ደረጃ ወሠንን ለማስከበር
የሚያስችሉ የአጥር ግንባታ ሥራ ለማከናወን፣ የውሃ መስመር ዝርጋታ ሥራ፣ የኤሌክትሪክ
መስመሮችን ለመዘርጋት፣ ለባለሐብት ርክክብ የሚፈፀምባቸው ቦታዎች፣ መዳረሻ መንገድ
ግንባታዎችና በአጠቃላይ ኮርፖሬሽኑ በሕጋዊ አግባብ በተረከባቸው ቦታዎች ከይዞታ ይገባኛል ጥያቄ
ጋር በተያያዘ በርካታ ጥያቄዎች ተነስተዋል፡፡ በዚሁ መሠረት በዕቅድ የተያዙ ሥራዎችን ለማከናወን
አሉታዊ የሆኑ ተፅዕኖ አሣድሯል፡፡
 በሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች ከ AGOA ጋር በተያያዘ በባለሀብቶች ላይ ከፍተኛ ስጋት የፈጠረ በመሆኑ
አንዳንድ ድርጅቶች በዚህ ምክንያት ከኢንዱስትሪ ፓርክ ስራ የማቆምና ሌሎችም የተለየ መፍትሄ
በመንግስት በኩል ካልተቀመጠ ቀጣይነታቸው ላይ ስጋት እንዳለባቸው በመግለጽ ላይ መሆናቸው ትልቅ
ስጋት ፈጥሯል፣
 በኢንዱስትሪ ፓርኮች አጎራባች ለሚኖሩ ነዋሪዎች ወደ ከተማ የሚወጡበት አማራጭ መንገድ
ያልተሰራላቸው እንዲሁም የአጥር ሥራው ባለመጠናቀቁ የፀጥታ ችግር፣
 በኢንዱስትሪ ፓርክ የፍሳሽ ማጣሪያ ግንባታዎች በመካሄድ ላይ ቢሆንም ከመሬት ይገባኛልና ከካሳ
ክፍያ ጋር በተያያዘ ችግሮች ስላለተፈቱ በውለታው መሰረትና በሚፈለገው ፍጥነት እየተካሄደ
አለመሆኑና ከግዜያዊ የቆሻሻ ማጠራቀሚያዎች ጋር የተያያዙ ችግሮች፤
 በሀገር ውስጥና አለምአቀፍ የተዘጋጁ ሁነቶች በኮሮና እንዲሁም በሀገሪቷ ወቅታዊ የፀጥታ ችግር
ምክንያት በመራዘማቸው ለመሳተፍ አለመቻልና ልምድ ያለመቅሰም፤
 የ 2014 በጀት በወቅቱ አለመጽደቅ ምክንያት ግዥዎችን በተያዘው ዕቅድ ለመፈጸም፣
 በኢንዱስትሪ ፓርኮች ከፍተኛ የሰራተኞች ፍልሰት፤
 የድርጅቱ አሰራር ለማዘመን የ ERP ሶፍትዌር ቢተገበርም የተለያዩ ስራዎቸን ለመስራት በሚፈለግበትና
መረጃ በሚጠየቅበት ጊዜ በሚፈለገው መጠንና ወቅቱን የጠበቀ ሪፖርት አለማድረስ፤
 በገበያ ላይ የሲሚንቶ እጥረት መከሰት በፓርኩ ውስጥ ያሉ ግንባታዎች በሚፈለገው ልክ እንዳይሰሩ
አርጓቸዋል፤
 በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ እንደ ስርቆት ያሉ የደህንነት ስጋቶች መበራከት፤
 የስራ ተቋራጮች አቅም ማነስ፤
 የገበያ ዋጋ አለመረጋጋት፤
 በአንዳንድ ኢንዱስትሪ ፓርኮች በመብራትና የቴሌኮም አቅርቦት መቆራረጥና የፋይበር መስመር
በመቆረጡ ምክንያት ከፍተኛ የሆነ የኢንተርኔት መቆራረጥ ፣ እንዲሁም መረጃ መበላሸት (Data
Corruption) መከሰት፣የመረጃ ፍሰት ችግር ፈጥሯል፡፡
72
በበበጀት ዓመቱ የተወሰዱ የመፍትሄ እርምጃዎች

 በሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ የአካባቢና የከተማ አስተዳደር አካላት ጋር
ውይይቶችን በማካሄድ የጋራ ዕቅዶችን በማዘጋጀት ችግሩ እንዲፈታ ጥረት ተደርጓል፤
 በቀጣይ ነፃ በሚደረጉ መሬቶች ላይ በጊዜያዊም ቢሆን አጥር ግንባታዎችን ለየኢንዱስትሪ ፓርኮች
ኃላፊነት ተሠጥቶ እንዲታጠር ተደርጓል፣
 ከዚሁ በተጨማሪ ቀደም ሲል በኮርፖሬሽኑ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በኢንዱስትሪ ፓርኮች
አጠቃላይ ልማት ላይ መሰረታዊ ለውጥ የሚያመጡት አነስተኛ ወጪ የሚያስከትሉ የካሣ ጥያቄዎችን
ምላሽ ለመስጠት ከሚመለከተቻዉ የፌዴራል፤ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፤ ከክፍለ ከተማ እና ወረዳ
ጋር ዉይይት ተደርጓል፤
 ስራዎች በተቀመጠላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ሁሉም የሚመለከታቸው ክፍሎች በፍጥነት ምላሽ
እንዲሰጡ ክትትል በማድረግ በተወሰነ መልኩ ችግሮችን መቅረፍ ተችሏል፤
 የኮርፖሬሽኑ አወቃቀር ኮርፖሬሽኑ ካለው ራዕይ እና አገራዊ ኃላፊነት እንዲሁም ጊዜውን ባማከለ መልኩ
ማዋቀር ተችሏል፤
 ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የተለያዩ የታቀዱ ሥራዎችን በታቀደላቸው ጊዜ ለማከናወን የመግባቢያ
ሰነድ መፈራረም ተችሏል፤
 የሚመለከታቸው ኃላፊዎች በስራቸው የሚገኙ ሠራተኞች በሙሉ የሚጠሩባቸውን ስልጠናዎች
እንዲሳተፉ ተድርጓል፤
 በኮርፖሬሽኑ ውስጥ ለሚተገበሩ አዳዲስ አሰራሮች ለሰራተኞች ተገቢውን ስልጠና በመስጠትና
ለተግባራዊነቱ ክትትል ተደርጓል፣
 ስለኮሮና (ኮቪድ 19) ክትባት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መረሃግብር በማዘጋጀት ሰራተኞች እንዲከተቡ
ማድረግ ተችሏል፤
 በገበያ ላይ የሲሚንቶ እጥረት ስለተከሰተ በፓርኩ ውስጥ ላሉ ግንባታ ለሚገነቡ ባለሀብቶች
ከሚመለከታቸው ሲሚንቶ አምራቾች ጋር በመወያየት ሲሚንቶ በአግባቡ እንዲያገኙ
ለማድረግከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ዉይይቶች ተጀምሯል፤
 የኢንተርኔት አገልግሎት መቆራረጥ ቅሬታን በሚመለከት ለኢትዮቴሌኮም ደብደቤ መፃፍና
ከሚመለከታቸው የስራ ኃላፊዎች ጋር መነጋገር፤በተጨማሪም ከኢትዮ-ቴሌኮም የቴክኒክ (ጥገና) ቡድን
በፓርኮች ውስጥ በሚሰጣቸው የአንድ ማዕከል ቢሮ ውስጥ ገብቶ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርጓል

7. ትኩረት የሚሹና ድጋፍ የሚፈልጉ ጉዳዮች


 በሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች ከ AGOA ጋር በተያያዘ በባለሀብቶች ላይ ከፍተኛ ስጋት የፈጠረ በመሆኑ
ይህንን ችግር ለመፍታት ሌሎች የገበያ አማራጮችን በመፈለግና በማመቻቸት ድጋፍ ማድረግ፣
73
 በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ የሚከሰተውን ከወሰን ማስከበር ጋር እና የካሳ ክፍያን በሚመለከት በተያያዘ
የአካባቢና የከተማ አስተዳደር አካላት ጋር ውይይቶችን በማካሄድ ድጋፍ እንዲደረግና የልማት ተነሺዎችን
የማሳመንና ግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ ላይ ተገቢውን እገዛና ድጋፍ ማድረግ፣
 ከመሠረተ-ልማት ግንባታና አቅርቦት እጥረትና መቆራረጥ ጋር በተያያዘ አገልግሎቱን ከሚሰጡ ተቋማት
ጋር ቅንጅታዊ አሰራርን በመፍጠርና በመወያየት በሁሉም ኢንዱስትሪ ፓርኮች የአገልግሎት ክፍተትን
የተፈጠሩ ችግሮችን መቅረፍ፣
 የተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማስተዋወቅና ኢንቨስተሮችን በመሳብ የተሻለ የገቢ
አማራጮችንና ኢንቨስትመንት ለመሳብ ድጋፍና ክትትል ማድረግ፣

74

You might also like