Download as pdf or txt
Download as pdf or txt
You are on page 1of 43

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ማውጫ
ምዕራፍ አንድ ሃይማኖት ........................................................................ 8
1.1 ሃይማኖት ምንድን ነው? .......................................................................... 8
1.1.1 የሃይማኖት ትርጉም ........................................................................................... 8
1.1.2 የሃይማኖት መገለጫዎች..................................................................................... 8

1.2 የሃይማኖት መሰረት ............................................................................... 11


1.2.1 ሀልዎተ እግዚአብሔር (የፈጣሪ መኖር) ............................................................. 11
1.2.2 ሥልጣን ያላቸው ነገሮች መኖር ........................................................................ 11

1.3 የሃይማኖት አስፈላጊነት .......................................................................... 12


1.4 ሃይማኖትና የሚያምኑ ፍጥረታት............................................................ 15
1.4.1 ሃይማኖት ለእነማን ያስፈልጋል? ....................................................................... 15
1.4.2 ምእመናን ምን አላቸው? ................................................................................... 15
1.4.3 ሀይማኖት እንዴትና መቼ ተጀመረ .................................................................... 16

1.5 የክርስትና ሃይማኖት ባህርያት ................................................................ 17


1.6 ፈጣሪን ማመን....................................................................................... 19
1.7 አስማተ አምላክ (የአምላክ ስሞች) ............................................................ 19
1.8 የእግዚአብሔር ባህርያት .......................................................................... 20
ምዕራፍ ሁለት ሥነ ፍጥረት ................................................................... 22
2.1 መግቢያ ............................................................................................... 22
2.1.1 ትርጉም ......................................................................................................... 23
2.1.2 የፍጥረታት ዓላማ .......................................................................................... 23
2.1.3 የፍጥረታት የአፈጣጠር መንገድ ...................................................................... 23
2.1.4 ፈጣሪ እና ፍጡር ........................................................................................... 24

2.2 የስድስቱ ቀን ፍጥረታት ........................................................................ 25


ትምህርተ ሃይማኖት

2.2.1 የፍጥረታት ብዛት እና አቆጣጠር ..................................................................... 25


2.2.2 የዕለተ እሁድ ፍጥረታት ................................................................................. 26
2.2.3 የዕለተ ሰኞ ፍጥረታት .................................................................................... 33
2.2.4 የዕለተ ማክሰኞ ፍጥረታት .............................................................................. 34
2.2.5 የዕለተ ረብዕ ፍጥረታት .................................................................................. 35
2.2.6 የዕለተ ሐሙስ ፍጥረታት ............................................................................... 37
2.2.7 የዕለተ አርብ ፍጥረታት .................................................................................. 37
2.2.8 የሰው ልጅ ..................................................................................................... 38

ምዕራፍ ሦስት አዕማደ ምሥጢር ........................................................... 43


3.1 የምሥጢር ትርጉም .............................................................................. 43
3.2 የምሥጢር ዓይነት................................................................................ 43
3.3 አዕማደ ምሥጢር ትርጓሜ .................................................................... 44
3.4 የአማዕደ ምሥጢራት አከፋፈል ............................................................. 45
3.5 መግቢያ ለአምሥቱ አዕማደ ምሥጢራት ................................................ 45
ምዕራፍ አራት ምስጢረ ሥላሴ............................................................... 48
4.1 የሥላሴ ቃል ትርጉም ........................................................................... 48
4.2 ምሥጢራዊ ትርጉም ............................................................................. 48
4.3 ምሥጢረ ሥላሴ በብሉይና በሀዲስ ኪዳን................................................ 54
4.4 ምስጢረ ሥላሴን የሚያስረዱ ምሳሌዎች................................................. 55
4.5 ምሥጢረ ሥላሴ በቅዱሳን አበው ........................................................... 56
ምዕራፍ አምስት ምስጢረ ሥጋዌ ........................................................... 59
5.1 የቃሉ ትርጉም ...................................................................................... 59
5.2 የሰው ልጅ ተፈጥሮ ፣ ክብር ፣ ውድቀት እና የተሰጠው ተስፋ ................ 60
5.3 ምሥጢረ ተዋሕዶ ................................................................................ 62
5.4 የወልደ እግዚአብሔር (የአምላክ) ሁለት ልደታት ..................................... 65

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 1 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

5.5 ነገረ ሥጋዌ በመፅሀፍ ቅዱስ (በብሉይ እና በሐዲስ ኪዳን) ....................... 71


5.6 ምሥጢረ ሥጋዌ በአዋልድ መጻሕፍት (በቅዱሳን አበው አንደበት) ........... 74
5.7 በምሥጢረ ሥጋዌ መናፍቃን የሚያነሷቸው ጥያቄዎች ........................... 76
ምዕራፍ ስድስት ነገረ ማርያም......................................................... 80
6.1 ትርጓሜና ትንቢት................................................................................. 80
6.1.1 ትርጓሜ .............................................................................................. 80
6.1.2 ስመ ድንግል ማርያም ትርጓሜ ........................................................... 81
6.1.3 ስለ ወላዲተ አምላክ የተነገሩ ትንቢቶች ................................................ 82
6.2 የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ታሪክ እና ምሥጢራዊ ትንታኔ... 83
6.2.1 የዘር ሀረግ ......................................................................................... 83
6.2.2 ወደ ቤተ መቅደስ መግባት እና ተያያዥ ፈተናዎቹ ............................... 86
6.2.2.1 አንዲት የመባሏ ምስጢር............................................................................. 88

6.2.3 ጸሎተ እግዝእትነ ማርያም (የእመቤታችን የማርያም ፀሎት) .................. 89


የመለማመጃ ጥያቄ ........................................................................... 92
6.3 ክብረ ቅድስት ድንግል ማርያም ከነገረ ድህነት ጋር ያለው ምስጢራዊ ትስስር 93
6.3.1 ብሰራተ ቅዱስ ገብርኤል መልአክ......................................................... 93
6.3.2 የቅድስት ኤልሳቤጥ ቃለ ውዳሴ ........................................................... 93
6.3.3 እመቤታችን ድንግል ማርያም የአዳም በደልና የኃጢአት ውርስ (ጥንተ አብሶ)
የለባትም ....................................................................................................... 94
6.3.4 አምስቱ የእመቤታችን ሀዘናት ............................................... 95
6.3.5 የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት .............................. 96
6.3.6 ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርም ስግደት እንደሚገባ ................... 96
የመለማመጃ ጥያቄ ........................................................................................ 97
6.4 የእመቤታችን ታሪካዊ ምሳሌዎች እና እመቤታችን በሊቃውንት አንደበት ... 98

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 2 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

6.4.1 እመቤታችንና ምሳሌዎቿ ...................................................... 98


6.4.1.1 የማክሰኞ እርሻ (ገራህተ ሰሉስ) ......................................................... 98
6.4.1.2 የያእቆብ መሰላል (ሰዋሰወ ያዕቆብ) ..................................................... 98
6.4.3 የኢያሱ የምስክር ሐውልት ( ሐውልተ ስምዕ ዘኢያሱ) .......................... 99
6.4.4 የጌድዮን ፀምር (ፀምር ዘጌድዮን) ........................................................100
6.4.2 እመቤታችን በሊቃውንት አንዳበት .....................................................101
የመለማመጃ ጥያቄ ......................................................................................103
ምዕራፍ ሰባት ምሥጢረ ጥምቀት......................................................... 105
7.1 ትርጉም .............................................................................................105
7.2 የምሥጢረ ጥምቀት አጀማመር............................................................106
7.3 የጥምቀት ምሳሌዎች .........................................................................107
7.4 የጌታችን ጥምቀት ...............................................................................109
የጥምቀት አይነት ........................................................................................113
የህፃናት ጥምቀት ........................................................................................114
7.5 በምሥጢረ ጥምቀት ዙርያ የሚነሱ አንዳንድ የመናፍቃን ጥያቄዎች .......115
ምዕራፍ ስምንት ምስጢረ ቁርባን ........................................................ 117
8.1 መግቢያ .............................................................................................117
8.2 የምስጢረ ቁርባን ምሳሌዎች ................................................................119
8.3 የምስጢረ ቁርባን አመሰራረት...............................................................120
8.4 ስለ ምስጢረ ቁርባን የአበው ምስክርነት ................................................122
8.5 በምስጢረ ቁርባን ላይ የሚነሱ የመናፍቃን ጥያቄዎች ............................123
ምዕራፍ ዘጠኝ ምስጢረ ትንሳኤ ሙታን ................................................. 125
9.1 ትርጉም .............................................................................................125
9.2 ትንሳኤ ሙታን በመጽሐፍ ቅዱስ.........................................................125

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 3 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

9.3 የትንሳኤ ሙታን ምሳሌ ......................................................................127


9.4 የምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን አመሰራረት ...............................................128
9.5 የሰው አነሳስ (ዳግም መፅዓት) ..............................................................135
9.6 በምስጢረ ትንሳኤ ሙታን ላይ የሚነሱ አንዳንድ የምናፈቃን ጥያቄዎች ..137
ምዕራፍ አስር ቅድስና ........................................................................ 139
10.1 የቅድስና ትርጉም አከፋፈልና የቅዱሳን መለያ ጠባያት .........................139
10.1.1 የቅድስና አከፋፈል ...........................................................................139
ሀ. የባሕርይ ቅድስና ................................................................................................. 139
ለ የጸጋ ቅድስና ........................................................................................................ 140

i. የቅዱሳን መለያ ጠባያት .........................................................................140


10.2. የበዓላት ምንነት ................................................................................141
10.2.1 የብሉይ ኪዳን በዐላት .......................................................................142
10.2.2 የጌታ በዓላት ...................................................................................142
10.2.3 የእመቤታችን በዓላት .....................................................................144
10.2.4 የቅዱሳን መላዕክት በዓላት .............................................................145
10.2.5 የሌሎች ቅዱሳን በዓላት .................................................................145
10.2.6 ሀገራዊ በዓላት ..............................................................................146
10.2.7 በዓላትን የማክበር ጥቅም ...............................................................147
10.3 ቅዱሳን ንዋያት .................................................................................148
10.3.1 ለመዝሙር አገልግሎት የሚውሉ ንዋያት..........................................148
10.3.2 ለሥርዓተ ቅዳሴ የሚያገለግሉና ሌሎች ንዋያት ..................................151
10.4 ቅዱሳን መካናት ...................................................................... 160
10.4.1 እግዚአብሔር አምላካችን ታላላቅ ስራዎች የሰራባቸው ቦታዎች፡- ............... 160
10.4.2 ቅዱሳን መካናት በዓለም .............................................................................. 162
10.4.3 ቅዱሳን መካናት በኢትዮጲያ .......................................................................... 163

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 4 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

10.4.4 ለቅዱሳን መካናት መደረግ ያለበት ጥንቃቄ .................................................... 164

10.5 ቅዱሳን ሰዎች ......................................................................... 164


1 የቅዱሳን ሕይወት .................................................................................164
2 የቅዱሳን ሰዎች አሰያየም .......................................................................167
. መዓረጋተ ቅዱሳን...................................................................................169
የቅዱሳን ቃል ኪዳን ....................................................................................173
i. የቅዱሳን ክብር .................................................................................................... 173
ii. የቅዱሳን መታሰቢያቸው ................................................................................... 175
iii. የቅዱሳን ገድልና የገድል መጽሐፍት ................................................................. 175
iv. በዓላተ ቅዱሳን ................................................................................................ 176

የቅዱሳን አማላጅነት....................................................................................176
10.6 ቅዱሳን ሥዕላት .................................................................... 181
1 የቅዱሳን ሥዕላት አጠቃላይ ገፅታ ..........................................................182
1.1 በዘመነ ብሉይ ................................................................................................. 182
1.2 በዘመነ ሐዲስ .................................................................................................. 182

2 የቅዱሳን ሥዕላት አጀማመር ..................................................................184


2.1 የሥዕለ ሥላሴ አጀማመርና ምንጮች................................................................ 184
2.2 የሥዕለ ክርስቶስ አጀማመርና ምንጮች ............................................................. 187
2.3 የሥዕለ ማርያም አጀማመርና ምንጮች ............................................................. 192

2.4 የቅዱሳን ሥዕሎች የአሳሳል ዘዬ (ደንቦች) .............................................194


2.5 ቅዱሳን ሥዕላትና ቤተ ክርስቲያን ........................................................197
2.5.1 በሥዕል ፊት መስገድ ................................................................................... 197
2.5.2 ቤተ ክርስቲያን ለምን በቅዱሳት ሥዕላት ትሞላለች) ...................................... 197

10.7 ቅዱሳን መላእክት ................................................................. 198


1 የመላእክት ሥነ ፍጥረት ........................................................................198

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 5 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

2 የመላእክት ባሕርይ................................................................................201
ሀ. የመላእክት አገልግሎት ...........................................................................201
ለ. የመላእክት ስልጣንና ክብር ......................................................................203
ሐ ሰባቱ ሊቃነ መላእክት .............................................................................204
ዋቢ መጻሕፍት ............................................................................. 210

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 6 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

መግቢያ

የሰው ልጅ በህይወት ዘመኑ ውስጥ ከእግዚአብሔር አምላኩ ከተቀበለው ወይም ከተሰጠው


አንዱ ሀይማኖት ነው፡፡ ይኸውም የእግዚአብሔርን ፈጣሪነት የእርሱን ፍጡርነትን አውቆ
ለፈጣሪው ለእግዚአብሔር የሚገባ አምልኮትን ለእርሱ ደግሞ የተመቸና የተገባ ህይወት
እንዲኖረው የሚያደርገው ነው፡፡ በመሆኑም የሰው ልጅ የሃይማኖት ጥቅምና አስፈላጊነት
አውቆ የተፈጠረበትን አላማ ለማሳካት እንዲችልና በሃይማኖት የጠነከረ በምግባር የጎለመሰ
እንዲሆን የሃይማኖትን ትምህርት አስቀድሞ ሊያውቅና ሊረዳ ያስፈልጋል፡፡ ምክንያቱም
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረን ሀይማኖት መሰረት ናትና፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 7 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

ምዕራፍ አንድ ሃይማኖት

1.1 ሃይማኖት ምንድን ነው?


1.1.1 የሃይማኖት ትርጉም

ሃይማኖት የሚለው ቃል “ሀይመነ” ከሚለው የግዕዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ማመን መታምን ማለት
ነው፡፡ በሀይማኖት የምናምነውም ሆነ የምንታመነው እግዚአብሔርን ነው፡፡

ሃይማኖት ማመን ነው ስንል በአይነ ስጋ አይቶ በስጋ ጆሮ ሰምቶ በልብ አስቦ በስሜት ህዋሳት አድምጦ
ሊመረምሩት የማይቻለውን በርህቀት (ሩቅ በመሆን) እና በርቀት (በረቂቅነት) ያለውን ይሆናል ይደረጋል
ብሎ መቀበል ነው ምክንያቱም ሀይማኖት የሚቀበሉት ነውና፡፡

ሃይማኖት መታምን ነው ስንል ይሆናል ፣ ይደረጋል ብሎ በእምነት የተቀበሉትን እንዲሆን ፣ እንዲደረግ ፣


እንዲፈጸም ተግባራዊ ምላሽ መስጠት ማለት ነው፡፡

ከላይ ከተመለከትነው የሃይማኖት ትርጉም በተጨማሪ፡-

1. ሀይማኖት የፍጡርና ፈጣሪ የሆነ እግዚአብሔር የሚገናኙበት ረቂቅ መንገድ ነው፡፡ ኤር 6፤16
2. ሀይማኖት ልዑል እግዚአብሔር ሰውን ለማዳን ያደረገው ጉዞ (ፍኖተ እግዚአብሔር) ነው፡፡ ዘፍ 3፤1

1.1.2 የሃይማኖት መገለጫዎች


ሀ. የሚቀበሉት ነው

ሀይማኖት አምነው የሚቀበሉት እንጂ አውቀው የሚቀበሉት ወይም የሚያምኑት አይደለም፡፡ ከአመኑና
ከተቀበሉ በኃላ ግን ለማወቅና በራሱ ወሰን ለመመርመር ስልጣን መቀበል ይቻላል፡፡

‹‹ሁላችን የእግዚአብሔርን ልጅ በማመንና በማወቅ ወደሚገኝ አንድነት…›› ኤፌ4፤13

ይህ ጥቅስ ማመን ከማወቅ በፊት መሆን እንዳለበት ያስረዳል፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 8 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

ዝም ብለን የምንቀበለው ለምንድን ነው)

1.እምነት ከስሜት በላይ ስለሆነ

ስሜት በህዋሳት ልናረጋግጠው የምንችለው ነው፡፡ እግዚአብሔር ደግሞ መንፈስ ነው (ዮሀ 4፤24) መንፈስን
ደግሞ በስሜት ልንረዳው አንችልምና ለመረዳትም አቅምና እውቀት አይኖረንምና ሀይማኖትን አምነን
እንቀበላልን እንጂ በእውቀት ውስጥ ሆነን አንቀበልም፡፡

2. ከአእምሮ (ከዕውቀት) በላይ ስለሆነ

ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ 12፤3 ‹‹እንደ ባለ አእምሮ እንዲያስብ እንጂ ማሰብ ከሚገባው አልፎ በትዕቢት
እንዳያስብ ከመካከላችሁ ላለው ለእያንዳንዱ በተሰጠኝ ጸጋ እናገራለሁ፡፡ አስተምራለሁ፤ እመክራለሁ›› ይህ
ጥቅስ የሚያመለክተው ለአእምሮ ወሰን ሲኖረው ለእግዚአብሔር ግን ወሰን የለውም ስለዚህ ሰው
የማይቻለውን ነገር ሊያደርግ ቢፈልግ አይቻለውምና በእምነት መቀበል ይኖርበታል፡፡

ለ. በተስፋ የሚረዱት ነው

‹‹ተስፋ ለሚያደርጉት ሀይማኖት የተረዳች ናት…..›› ዕብ 11፤1 ሰው ተስፋ ከሌለው አያምንም ካላመነ
ደግሞ ተስፋ አይኖረውም፡፡ ወደፊት ተስፋ የምናደርገውን ዘላለማዊ ህይወትና እግዚአብሔር የሚያወርሰንን
መንግስት የምናረጋግጠው በሀይማኖት ብቻ ነው፡፡ የእግዚአብሔር ረድኤትና ፀጋ ፣ ጥበቃና ቸርነትን አምነን
የምንጠቀመው በተስፋ ነው፡፡

በተስፋ የምንጠብቃቸው ብዙ ነገሮች አሉ፡- ከዘላለማዊ ህይወትና ከመንግስተ ሰማያት በፊት የእግዚአብሔርን
እርዳታ ለስጋዊም ሆነ ለሰማያዊ ህይወታችን ስንፈልግ በፀሎት ጠይቀን የምንጠብቀው በተስፋ ነው፡፡

ሐ. በፍቅር የሚገለጥ ነው

ሀይማኖት የድህነተ ስጋ የድህነተ ነፍስ መንገድ ነው፡፡ የጎሰቆለ ባሪያችንን አድሶ ፣ የተገፈፍነውን ፀጋ
መልሶ ፣ በስጋ በነፍስ ያዳነን ደግሞ በተዋህዶ የከበረ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡
እርሱም የተገለጠው ከፍቅር የተነሳ ነው፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 9 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

‹‹በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ህይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን
እስኪሰጥ ድረስ አለሙን እንዲሁ ወዶአልና›› ዮሐ 3፤16

መ. በስራ የሚተረጎም ነው

አንድ ሰው ይሆናል ይደረጋል ያለውን የሚገልጠው በራሱ ህይወት ወይንም በሌላ ሰው ላይ ነው፡፡ በሌላው
ሰው ላይ የሚያደርገው በፍቅር የሚገለጥ ሲሆን በስራ የሚተረጎመው ብለን የምንገልፀው የመታመን ዋናው
መገለጫ የሆነና በስራ በመጀመር የሚሰራ ነው፡፡

ሠ. የማናየውን የምናይበት ረቂቅ መሳሪያ ነው

እምነት ዝም ብለን የምንቀበለው በተስፋ የምንረዳው በፍቅር የምንገልጠው እና በስራ የምንተረጉመው ነው፡፡
ይህም በመራቅ ወይም በረቂቅነት በዐይነ ስጋ የማይታዩትን ለማየት ያበቃናል፡፡

ለምሳሌ፡- ለነብየ እግዚአብሔር ኢሳያስና ለያዕቆብ እግዚአብሔር አምላክ ለእነርሱ ማየት በሚገባቸው መልኩ
ተገልጦ ታይቶአቸዋል፡፡ ኢሳ 6፤6 ዘፍ 20፤13፡፡

ረ. እግዚአብሔርን ደስ የምናሰኝበት ነው

እግዚአሔርን ደስ ማሰኘት የምንችለው በእምነትና አምንን በምንሰራቸው በጎ ተግባራት ነው፡፡ ሮማዊው መቶ


አለቃ ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ደስ ያሰኘውና ያስደነቀው በእምነቱ ነበር፡፡ መቶ አለቃው
የብላቴናውን መታመም ተናግሮ ጌታችን መጥቼ ልፈውሰው ቢለው ‹‹ጌታ ሆይ በቤቴ ጣራ ከታች ልትገባ
አይገባኝም ነገር ግን ቃል ብቻ ተናግር ብላቴናዬም ይፈወሳል›› በማለት እምነቱን ገልፆአል፤ ጌታችንም
‹‹እውነት እላችኋለሁ በእስራኤልስ ስንኳ እንዲህ ያለ ታላቅ እምነት አላገኘሁም›› ሲል አደነቀው፡፡ ማቴ
8፤5-10፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 10 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

1.2 የሃይማኖት መሰረት


1.2.1 ሀልዎተ እግዚአብሔር (የፈጣሪ መኖር)

ሀልዎት የግዕዝ ቃል ሲሆን “ሀለወ” ከሚለው ግስ የወጣ ነው ትርጉሙም መኖር ወይም ህልውና ማለት
ነው፡፡ ስለዚህ ሀለዎተ እግዚአብሔር ስንል የእግዚአብሔር መኖር ማለት ነው፡፡ የእግዚአብሔርን መኖር
ለማወቅ እና ለመረዳት ቁልፉ እምነት ነው ከእምነት ያልተነሳ ሰው በፍፁም ወደ እግዚአብሔር ሊደርስ
አይቻለውም፡፡ ፈጣሪ እናውቀው ዘንድ የሚያግዙንን ብዙ ነገሮችን ሰጥቶናል እንድናውቀው አጋዥ አድርጎ
ከሰጠን ውስጥ ስነፍጥረት ፣ ህሊና ፣ የሰው ልጅ የተፈጥሮ ዝንባሌ እና ቃለ እግዚአብሔር ናቸው፡፡

1.2.2 ሥልጣን ያላቸው ነገሮች መኖር


ሀ. የቤተክርስቲያንን ትውፊት
ሰው የቤተክርስቲያንን ስልጣን ከአወቀና እውነቱን ከተረዳ ሀይማኖቱን መመስከር ይችላል ያለ ቤተክርስቲያን
ትውፊት መፅሐፍ ቅዱስንም መቀበል አይቻልም ምክንያቱም መፅሐፍ ቅዱስ ከአንዱ ወደ ሌላው እየተላለፈ
በየጊዜው እየተፃፈ ከኖረ በኋላ በመናፍቃን መነሳት ምክንያት በቀኖና የተደነገገውና ለዚህ የበቃው በትውፊት
ነው፡፡

ትውፊት እውነትን የመናገር ብቃት ያለው የእምነት መሰረት ነው ስለዚህ ትውፊት የመጻህፍትና
የእውነትም ምንጭ ስለሆነ መሰረት ሀይማኖት ለመሆን ስልጣን አለው፡፡ ትውፊትን አሁን አግኝተን
መጠቀም የምንችለው ደግሞ ከመምህራንና ከሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ ‹‹በሐዋርያትና በነብያት
መሰረት ላይ ታንፃችኋል የማዕዘኑ ራስ ድንጋይ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው›› ኤፌ2፤20፡፡ ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን
የምታስተምረውን የሚሰማ እና የሚሰራ ሁሉ ታላቅ የእምነት መሰረት አለው፡፡
ለ. ቅዱስ መጽሐፍ
መጽሐፍ ቅዱስ የእምነት መሰረት ያሰኘው እውነቱን የሚናገርና መለኮታዊ ስልጣን ያለው መጽሀፍ ነው፡፡
ይህንንም ስልጣን የሰጠው ራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡

‹‹መጽሐፍትን ካላመናችሁ ግን ቃሌን እንዴት ታምናላችሁ?›› ዮሐ 5፤46

የእርሱን ትንሳኤ ባለማመን ወደ ኤማሁስ ጉዞ የጀመሩትን ሁለቱን ደቀ መዛሙርትንም ያሳምናቸው


ቅዱሳት መጻህፍትን በመተርጎም ነበር፡፡ ሉቃ24፤13

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 11 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

ስለዚህ የቤተክርስቲያንን ትውፊትና ቅዱሳት መጻህፍት እውነቱን በመናገር የተገለጡ ለእምነታችን


መሰረትነት ስልጣን ያላቸው መሆናቸውን በመገንዘብ ወደ ቅዱሳን መጻሐፍት ሰዎች ሁሉ እንዲመለሱ
ማሳሰብ ይገባናል፡፡

1.3 የሃይማኖት አስፈላጊነት


እግዚአብሔር ወደ ሰው ፤ ሰውም ወደ እግዚአብሔር የሚያደርገው ጉዞ ሀይማኖት ይባላል፡፡ እግዚአብሔርን
በሀይማኖት እናየዋለን በጸሎት እናነጋግረዋለን በዚህ አለም ሳለ ስለእግዚአብሔር የሆነውን ሁሉ
የምናስተውለው በሃይማኖት ብቻ ነው፡፡ ያለ ሀይማኖትም እግዚአብሔርን ደስ ማሰኝት አይቻልም፡፡
ዕብ11፤6፡፡

ሀይማኖት - ለስጋም ፣ ለነፍስም ጠቃሚ ነው

ለስጋ
ያለስጋ ነፍስ አትቆምምና መጀመሪያ ለስጋ እንደሚያስፈልጋት እንመለከታለን፡፡ ሀይማኖት ለስጋ ጠቀሜታ
አለው ስንል ለማንኛውም ምድራዊ ህይወታችን ለማለት ነው፡፡ ሰው በሀይማኖት ቢኖር፡-

ሀ. ሰላም ያገኛል
በዚህ አለም የሚኖር ሰው ሁሉ ሰላምን ይሻል፣ ይፈልጋል ሊያገኛት ግን አይችልም ምክንያቱም ሰላምን
እነርሱ የሚፈልጉት በመጠጥ ቤት ፣ በገንዘብ በመሳሰሉት ነውና በእነዚህ ነገሮች ሰላምን የሚመስል

አእምሮን በማታለል ሰላም ሊገኝ ይችላል፡፡ ነገር ግን ከህሊና ክስ ማምለጥ አይቻልም፡፡ ሰው በሀይማኖት
ከኖረ ያለፈ በደሉን በንስሐ አስተሰርዮ ከእግዚአብሔር ስለሚያገኝ ፍጹም ሰላም ያገኛል ከእርሱ የምናገኝው
ሰላም ከአለም እንደምናገኝው አይደለም፡፡

‹‹ሰላምን እተውላችኋለሁ ፤ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ ፤ እኔ የምሰጣችሁ አለም እንደሚሰጥ አይደለም›› ዮሐ


14፤27 ይህም ሰላም ፍጹም ልዩ ነውና፡፡

እግዚአብሔር በሃይማኖት እስከተከተልነው ድረስ በአካሄዳችንም ደስ ካሰኘነው ከጠላቶቻችሁ ጋር ሁሉ


በሰላም እንድንኖር ያስችለናል፡፡ ጠቢቡ ሰለሞን ‹‹የሰው አካሄድ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘው እንደሆነ
በእርሱና በጠላቶቹ መካከል ስንኳ ሰላምን ያደርጋል›› እንዳለ ምሳሌ16፤7፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 12 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

ለ. በረከተ ስጋን ያገኛል


የበረከተ ስጋ መጀመሪያው ልጅ ነው፡፡ እግዚአብሔር ፍጥረታትን ከፈጠረ በኃላ የሰጣቸው የመጀመሪያ
በረከት ልጁ ነውና፡፡ ለአብርሀም የበረከት ቃልኪዳን የገባለት በልጁ ነው ዕብ 11፤17፡፡
ለሌሎችም አበው እንዲሁ የእግዚአብሔር ትልቁ በረከትና ስጦታ ልጅ ነው የሚባለው ለወደድናቸው የተባረከ
ልጅ በመስጠቱ ብቻ ሳይሆን አለሙንም ለማዳን የሰጠው የባህርይ ልጁን ስለሆነ ነው፡፡ በሀይማኖት በረከት
ስጋን ያገኙት ብዙዎች ናቸው ለአብነት ያህል እፍኝ ከማትሞላ ዱቄት ጋግራ ለነብዩ በመስጠት በበረከት
የኖረችው የሰራፕታዋ ሴት 1ኛ ነገ 11፤1 እንዲሁም ነብዩ ዳንኤልና ሰልስቱ ደቂቅ በሀይማኖታቸው
ምክንያት በስጋዊ እውቀት አስር እጅ ፍጹም በልጠው ተገኝተዋል፡፡ ዳን1፤1-20፡፡
ሐ. ድህነተ ስጋን ያስገኛል
በተለያየ ምክንያት ከመጣው ደዌ ሁሉ ሰው በሀይማኖት ብቻ ሊድን ይችላል ጌታችን በመዋዕለ ስጋዌው
ተገልጦ በሚያስተምርበት ወቅት ብዙ ድውያነ ስጋን ፈውሶል ይሁን እንጂ እነርሱን ያዳናቸው በእምነታቸው
እንደሆነ ሁሉ ሰው ዋጋ ሊከፍለው ድህነት ሊያደርግለት የሚገባው በሀይማኖት እንደሆነ አስተምሮአል፡፡
‹‹በርጤሜዎስ እምነትህ አድኖሃል›› ሉቃ 18፤42፡፡

‹‹ተሻግረውም ወደ ጌንሴሬጥ ምድር መጡ የዚያ ቦታ ሰዎችም ባወቁት ጊዜ በዙሪያው ወዳለ አገር


ሁሉ ላኩ ህመምተኞችንም ሁሉ ወደ እርሱ አመጡ የልብሱንም ጫፍ ብቻ ሊዳስሱ ይለምኑ ነበር
የዳሰሱትም ሁሉ ዳኑ›› ማቴ14፤34-36

ይህን የመሰለ ተረፈ ደዌ የሌለበት ድህነት ስጋ የሚገኘው በሃይማኖት ነው፡፡ ባለመድሃኒቶች ቢያድኑም
ደዌውን ፈጽመው አያስለቅቁትም ቢያስለቅቁትም ሌላውን የሰውነት ክፍል ጎድተው ነው፡፡ ፍጹም የሆነ
ድህነተ ስጋን ማግኘት የሚቻለው በሀይማኖት ነው፡፡
መ. ከመከራ ስጋ ይጠብቃል
‹‹ከእናንተ ማንም ነፍሰ ገዳይ ወይም ሌባ ወይም ክፉ አድራጊ እንደሚሆን ወይም በሌሎች ጉዳይ
እንደሚገባ ሆኖ መከራን አይቀበል ክርስቲያን እንደሚሆን ግን መከራን ቢቀበል ስለዚህ ስም
እግዚአብሔርን ያመስግን እንጂ አይፈር›› 1ኛ ጴጥ 4፤15

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 13 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

በመጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔርን በማመናቸው ከመከራ ስጋ የተጠበቁ ሰዎች ብዙ ናቸው፡፡ ከእነዚህ


በድንጋይ ተወግራ በእሳት ተቃጥላ ከመሞት የዳነችው ሶስና ወደ እሳት ተጥለው የልብሳቸው እራፊ እንኳን
ያልተነካባቸው ሠልስቱ ደቂቅ ወደ አናብስት ጉድጎድ ተጥሎ የተጠበቀው ዳንኤል ሁሉም እንዲሞቱ አዋጅ
ተፈርዶባቸው በአስቴር ትዕዛዝ ጾመው እና ጸልየው ሞታቸው ወደ ህይወት፤ ሀዘናቸው በደስታ
የተለወጠላቸው በሀይማኖት ነው፡፡

ለነፍስ
ጌታችን በወንጌል ‹‹ሰው አለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጎድል ምን ይጠቅመዋል?›› ማቴ 16፤26
እንዳለ ዋናው የሀይማኖት ጥቅም ወይም አስፈላጊነት ለነፍስ ነው፡፡ ይህንንም በሁለት ነጥቦች እንመልከት
ሀ. ድህነተ ነፍስ
ለድህነተ ነፍስ የመጀመሪያው በር ሀይማኖት ነው፡፡ ጌታችን ‹‹እኔ የበጎች በር ነኝ›› ዮሐ 10፤7 ‹‹እኔ
መንገድና እውነት ህይወት ነኝ›› ዮሐ 14፤6 ‹‹በእርሱ የሚያምን አይፈረድበትም ፤ በማያምን ግን በአንዱ
በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል›› ዮሐ 3፤18፡፡ እያለ አስተምሯል፡፡
የሐዋርያትም ትምህርት እንደጌታችን ነበረ ያለ ሀይማኖት ድህነት እንደማይገኝ አስረግረጠው ተናግረዋል፡፡
ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ሲላስ የእስር ቤቱን ዘበኛ ‹‹በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን አንተና ቤተሰቦችህም
ትድናላችሁ›› ሐዋ 16፤31 ያሉት ለዚህ ማስረጃ ነው፡፡ ሰው ለድህነተ ነፍስ በዚህ ምድር በሚያደርገው
ጉዞም በረከተ ነፍስን እያገኘ የሚቆየው በሀይማኖት ነው፡፡
ለ. ክብረ ነፍስ
ሰው በሀይማኖት ከኖረ ክብረ ነፍስን ያስገኛል፡፡ ይህም ከመዳን በኃላ ከተጋድሎ የተነሳ የሚሰጥ ክብር ሲሆን
ክብሩ በምድርም የሚገባቸውን ያህል ሊሰጣቸው ይችላል፡፡ ይህንን ጌታ በዘሪው ምሳሌ ላይ ‹‹አንዱም መቶ
፣ አንዱንም ስልሳ ፣ አንዱም ሰላሳ ያደርጋል (ያፈራል)›› ሲል ማቴ 13፤23፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ቅዱሳን
በክብረ ነፍስ ከብረው በፀጋ በትሩፋት በልፅገው የሚበላለጡ እንደሆነ ሲናገር ‹‹የፀሐይ ክብር አንድ ነው ፣
የጨረቃም ክብር ሌላ ነው ፣ የከዋክብትም ክብር ሌላ ነው ፣ በክብር አንዱ ኮከብ ከሌላው ኮከብ ይለያልና››
1ኛ ቆሮ 15፣41 ይህንም ክብራቸውን የምናቀው (የምንገነዘበው) በሚሰጣቸው ፀጋ ነው፡፡ ይህም አንደ
ሀይማኖት ፅናትና እንደ ተጋድሎ የሚሰጥ ነው፡፡
ጌታችን ይህን ሲናገር ‹‹እውነት እላችኋለሁ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ ይህን ተራራ
ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል›› ማቴ 17፤20 ብሎአል፡፡ በዚህ ፀጋ በክብረ ነፍስ የከበሩ
የእግዚአብሔር ወዳጆች ድውያንን ፈውሰዋል ፣ ሙታንንም አስነስተዋል ፣ ብዙ ተአምራትን አድርገዋል፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 14 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

1.4 ሃይማኖትና የሚያምኑ ፍጥረታት

1.4.1 ሃይማኖት ለእነማን ያስፈልጋል?


ሀይማኖት የሚያስፈልጋቸው ስሙን ቀድሰው ክብሩን ወርሰው ለመኖር ለተፈጠሩ ፍጥረታት ብቻ ነው፡፡
ሌሎች ለአንክሮ ለተዘክሮ ለምግበ ስጋ የተፈጠሩ ናቸው፡፡ ስሙን ቀድሰው ክብሩን የሚወርሱ ደግሞ ሰውና
መላዕክት ብቻ ናቸው፡፡ እነዚህ ሁለቱ ፍጥረታት ግዕዛነ አእምሮ የተሰጣቸው ሲሆኑ አሁንም በማመስገን
ላይ ያሉና የተለየ ግንኙነት ያላቸው ናቸው፡፡

እነዚህ ፍጥረታት ከሌሎቹ የሚለዩበት ነገሮች ቢኖራቸውም ዋነኞቹ ግን ሁለት ናቸው፡፡ ከእነዚህም
የመጀመሪያውም ግዕዛነ አእምሮ ወይንም እውቀት የተሰጣቸው መሆኑ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ መላዕክት
ፍፁም የማይሞቱ ፣ ሰው ደግሞ የማትሞት ነፍስ ያላቸው መሆናቸው ነው ስለዚህ የዘለአለም ህይወት
ተስፈኞች ናቸውና ከእግዚአብሔር ጋር በመጣላት ወደ ሲኦል ገሀነም እንዳይወርዱ ሀይማኖትና ምግባር
ያስፈልጋቸዋል፡፡ ሀይማኖት እንዲኖራቸው ያደረገውም ሞት የማያሸንፈው ባህሪ ይዘው መገኘታቸው ነው
የሰው ሞትም የነፍስን ከስጋ መለየት እንጂ የነፍስ መጥፋት አያመለክትም፡፡

1.4.2 ምእመናን ምን አላቸው?


ሀ. ነፃ ፍቃድ

ፈጣሪ ለፍጥረታት ከሰጠው ልዩ ፀጋ ውስጥ የመጀመሪያው ነፃ ፈቃድ ነው፡፡ ፈጣሪ ነፃ ፈቃዳችንን


ተጠቅመን እንድናመልከው እንጂ በግድ እንድናመልከው አላደረገንም፡፡ ሰው ወዶ ፈቅዶ ነው ለአንድ ነገር
ተገዥ የሚሆነው ሰው በተሰጠው በነፃ ፈቃድ አውቆ ቤተ ክርስቲያን መሄድ አለመሄድ፤ ፈጣሪውን
እግዚአብሔርን ማመን አለማመን፤ መጾም አለመጾም፤ መጸለይ አለመጸለይ ወዘተ ማድረግ ይችላል፡፡

ለ. ምርጫ

በነፃ ፈቃድ ይጠቅመናል የምንለውን መርጠን እንድንሰራ መብቱ ተሰጥቶናል ሌላ ቀርቶ ፈጣሪንም
እስከአለማምለክ ቃሉንም እስካለመስማት ድረስ ሰው መምራጥ ይችላል፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 15 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

ሐ. ኃላፊነት

የመጨረሻው ደግሞ ነፃ ፈቃዱን ተጠቅሞ መርጦ ለወሰነው ውሳኔ ተጠያቂው ወይም ሀላፊነት የሚወስደው
ራሱ ነው፡፡ ሰው ቃለእግዚአብሔርን ላለመስማት ወስኖ በኋላ አልሰማሁምና አይፈረድብኝም የማለት መብት
የለውም፡፡ ቤተ ክርስቶያን የህይወት መንገድ ከፈጣሪ የምታገናኝ የሰማይ ደጅ መሆኗን አምናለሁ እያለ ወደ
ቤተ ክርስቲያን ያልመጣ ሰው እግዚአብሔርን የሸሸ ራሱ ስለሆነ በህይወቱም ችግር ቢደርስበት ራሱ ተጠያቂ
ይሆናል፡፡ ት.ኤር 31፤34

1.4.3 ሀይማኖት እንዴትና መቼ ተጀመረ


ሀይማኖት ፈጣሪ አለማት ልዑል እግዚአብሔር የመፍጠር ስራውን በጀመረበት በዕለተ እሁድ
ስምንት ፍጥረታትን ፈጥሯል፡፡ ከእነዚህም ስምንት ፍጥረታት መካከል ቅዱሳን መላዕክት ይገኙበታል፡፡
ሲፈጠሩ ብሩህ አዕምሮ ተሰጣቸው ፤ መላዕክት በተሰጣቸው እውቀት ተጠቅመው መፈጠራቸውን
እንዲያውቁ ስለረዳቸው ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር ብለው ፈጣሪያቸውን አመስግነዋል፡፡ ኢዮ 38፤7
ኢሳ 6፤3፡፡
ከዚህ የምንረዳውና የምንገነዘበው ነገር ቢኖር ቅዱሳን መላዕክት ፍጥረት ያለ ፈጣሪ ስራ ያለአሰሪ ሊገኝ
እንደማይችል ማመናቸውና ፍጥረታትን ካለመኖር ወደመኖር አምጥቶ ለፈጠረ እግዚአብሔር ምስጋናና
አምልኮት እንደሚገባ መረዳታቸውን ነው፡፡ ይሁን እንጂ ከመላዕክት በነገድ ከፍ ብሎ ሳጥናኤል አፈጣጠሩን
ተመልክቶ ‹ለተገኙትና ለተፈጠሩት ሁሉ አስገኝና ሰሪያቸው ለተፈጠሩትም ፈጣሪያቸው እኔ ነኝ› በማለት
ክህደትን በመጀመር በአለመ መላዕክት ዘንድ ክፍፍልን ፈጥሯል ፤ ይሁንና ፀንቶ ያፀና እየተባለ የሚጠራው
መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ‹‹የፈጠረንን አምላክ እስክናገኝ ድረስ በያለንበት እንፅና›› በማለት በቀደመው
እምነታቸው በመፅናት የአምልኮ ምስጋናን ከማቅረብ አልተከለከሉም በመሆኑም ከዚህ የምንረዳው ነገር
ቢኖር ቅዱሳን መላዕክት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መርቶ ያደረሳቸው ሀይማኖት ነው፡፡ ት.ኢሳ 14፤12-
16
በሰው ልጆች ሀይማኖት የተጀመረው ከመጀመሪያው ፍጥረት አዳም ጀምሮ ነው ዘፍ 3፤1፡፡ እግዚአብሔር
ከፈጠራቸው ፍጥረታት መካከል ሀይማኖት ያላቸው ሰውና መላዕክት ናቸው፡፡ ሀይማኖት እንዲኖራቸው
ያሰገደደበት ምክንያት፡-
ሀ. ስሙን ቀድሰው ክብሩን እንዲወርሱ የተፈጠሩ በመሆናቸው
ለ. እውቀት ያላቸው አሁንም በማመስገን ላይ ያሉና ከፈጣሪ ጋር የተለየ ግንኙነት ያላቸው በመሆናቸው

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 16 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

ሐ. መላዕክት ፍፁም የማይሞቱ ፣ ሰው ደግሞ የማትሞት ነፍስ አላቸው፡፡ ሁለቱም ፍጥረታት የዘላለም
ህይወት ተካፋዮች በመሆናቸው ነው፡፡

ሰው ያለ ሃይማኖት መኖር ይችላልን?


ሰው የሚያምነው ነገር ሳይኖር ሊኖር አይችልም እግዚአብሔርን እንኳን ባያምን የሚያምንበት የራሱ ነገር
ይኖረዋል፡፡
ለምሳሌ፡- ለፍጥረታት ፈጣሪ የለውም በልማድ የተገኘ ነው እንኳን ብሎ የሚያሰበውን ጉልበቱን ወይም
እውቀቱን ነው፡፡ ይህም በእውቀቱ ወይንም በጉልበቱ ማምለክ ማለት ነው፡፡ ጉልበታቸውን ያመልኩ ከነበሩት
ውስጥ ጎልያድ ተጠቃሽ ነው፡፡
ከቤተ ክርስቲያንም አንፃር አንድ ሰው ከሀይማኖት ወጣ የሚባለው ወልድ ዋህድ ብሎ ከማመንና ከሙሉ
ትምህርተ ሀይማኖቷ ሲለይ ነው፡፡ በአጭር ቃል ያለ ኦክስጅን መኖር እንደማይቻለው ያለ ሀይማኖት መኖር
አይችልም፡፡ ኦክስጂን የሚጠቀሙ ሁሉ ስለኦክስጂን ላያውቁ ይችላሉ እነዚህም ሰዎች ስለሚያምኑት ላያውቁ
ይችላሉ እንጂ የሚያምኑት የለም ማለት ግን ከባድ ነው፡፡

የክርስትና ሃይማኖት
የክርስትና እምነት የምንለው በወንጌል ማመን ነው፡፡ ወንጌል ደግሞ የምትናገረው የጌታችን የኢየሱስ
ክርስቶስ ሕይወቱን፣ አኗኗሩን፣ ተአምራቱንና ስራውን ሁሉ ነው፡፡

1.5 የክርስትና ሃይማኖት ባህርያት


ሀ. የመገለጥ ሀይማኖት ነው
ክርስትና እንደአብርሃም በፍኖተ አእምሮ ፣ እንደሙሴም ከእርሱ በመጠራት ሳይሆን አምላክ ሰው ሆኖ
እንደተገለጠ የሚያስተምር ነው፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹እግዚአብሔርንም የመምሰል ምስጢር ያለጥርጥር ታላቅ ነው ፣ በስጋ የተገለጠ ፣


በመንፈስ የፀደቀ ፣ ለመላእክት የታየ ፣ በአህዛብ የተሰበከ ፣ በአለም የታመነ ፣ በክብር ያረገ›› 1ኛ ጢሞ
3፤16 በማለት በመገለጥና በመታየት ላይ እንደሚያጠነጥን አስረድቶል፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 17 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

‹‹የአማልክት አምልክ እግዚአብሔር በፅዮን ይታያል›› መዝ 83፤7 ያለው ሰው ሆኖ ይመጣል ይገለፃል


ለማለት እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡
መገለጥ የምንለው ስጋ አዳምን ተዋህዶ ሰው ሆኖ መታየቱ ነው፡፡ ስለዚህ የክርስትና ሀይማኖት የመገለጥ
ሀይማኖት ነው የምንለው በእርሱ ሰው መሆን የተመሰረተ በሐዋርያት ትምህርት ስብከት የታነፀ ማለት
ነው፡፡ በአጭር ቃል የመገለጥ ሀይማኖት ማለት ከሰዎች የተገኘ ሳይሆን ከራሱ ከእግዚአብሔር አንድ ጊዜ
ብቻ የተገኘ ሀይማኖት ማለት ነው፡፡

‹‹ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠ ሀይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኳችሁ


እፅፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ›› ይሁዳ 1፤3

ለ. ልዩ ነው
1. እምነቱ በአንድ አምላክ ከማመን በላይ ነው በቀድሞው ዘመንም ሆነ በአሁኑ ዘመን የሚኖሩ ብዙ
ፈላስፎች በአንድ አምላክ መኖር ያምናሉ፡፡ የክርስትና ሃይማኖታችንም ከአህዛብ ተለይታ በአንድ አምላክ
የማመኗን ያህል ከአይሁድም ተለይታ በሦስት ገፅ አካላት ታምናለች፡፡ ይህም ‹‹አንድነቱ ሶስትነቱ
የማይከፈለው ፣ ሶስትነቱም አንድነቱን የማይጠቀልለው›› ማለት ነው፡፡
2. ስላሴ በስልጣን ስሩያን ብለን ከማመናችን የተነሳ በተለየ አካሉ ሰው ሆኖ ለተገለጠው አምላክ ማንነት
የምንሰጠው ፍፁም ልዩ ነው፡፡ ‹‹አንተ የህያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ›› ይህም የባህርይ አምላክ ነህ የሚል
ነው፡፡ ይህም የቤተክርስቲያን መሰረት ነው፡፡

ሐ. በር ነው
ወደ ገነት መግቢያው በር ፣ ጽድቅና ድህነትም ማግኛው አንድ ብቻ ነው፡፡ ሰው ሆኖ በተገለጠው በክርስቶስ
ማመን ያለዚህ መንገድ ህግን ቢፈፅሙ ምግባር ትሩፋት ቢሰሩ ሊድኑ አይችሉም፡፡

‹‹በሩ እኔ ነኝ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል ይገባልም ይወጣልም መሰማሪያም


ያገኛል›› ዮሀ 10፤9

በክርስቶስ አምኖ ሳይጠመቅ ስጋውን ሳይበላ ደሙን ሳይጠጣ ምስጥራትን ሳይፈፅም ማንም ሊፀድቅ
አይችልም፡፡ ክርስትና ብቸኛና ጠባብ የፅድቅ በር ናት፡፡ ሉቃ 13፤24

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 18 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

1.6 ፈጣሪን ማመን


የመጀመሪያው ሰው ፣ የሚታየውና የማይታየው አለም ከምን ተገኘ? ሰማይና ምድርስ እንዴት ፀኑ?
እንደእውነቱ ከሆነ ተመራማሪዎቹ በአዝጋሚ ለውጥ ተገኘ የሚሉት የመጀመሪያው ነገር ከምን ተገኘ
የሚሉት የመጀመሪያው ነገር ከምን ተገኘ? ክረምትና በጋ ፣ ብርሀንና ጨለማ ፣ ዘሩና መከሩ ፣ ቀንና
ሌሊቱ እነዚህና ሌሎችም ጥያቄዎች ማንሳት ይቻላል እነዚህ ሁሉ ወደ አንድ ነገር ያመራሉ፡፡ ‹‹አንድ
ሀይል›› የሚለው የብዙ ፈላስፋዎች አስተሳሰብ ያመጣው ከእነዚህና መሰል ጥያቄዎች ማምለጥ
አለመቻላቸው ነው፡፡
ሰው ባያምንም ሊቆጣጠረው የማይችል በራሱ ጥበብም ያላወቀው አንድ ሀይል እንዳለ ፍጥረት ሁሉ
ይስማማል ይህ የፍጥረት ሁሉ ጌታና ፈጣሪ መኖሩ የታወቀና የተረጋገጠባቸው ወይም መኖሩን እንድንቀበል
የሚያስገድዱን ማስረጃዎች አሉ፡፡
1. ስነ ፍጥረት
2. የህሊና ምስክርነት
3. የሰው ልጅ የተፈጥሮ ዝንባሌ
4. መፅሀፍ ቅዱስ

1.7 አስማተ አምላክ (የአምላክ ስሞች)


ስም - በቁም ከባህርይና ከግብር የሚወጣ ቦታን ፣ አካል ፣ ህይወት ያለው ማናቸውም ሁሉ በክፍሉ፣
በአካሉ፣ በአይነቱ ፣ በመልኩ ፣ በነገዱ ፣ በዘሩና በአባቱ ዘመድ ተለይቶ የሚጠራበት የሚታወቅበት ማለት
ነው፡፡ ስም በአራት አበይት ክፍሎች ይከፈላል፡፡ እነርሱም የተፀውኦ፣ የግብር፣ የባህርይ እና የተቀብኦ ስም
ናቸው፡፡

1) የተፀውኦ ስም፡- የመጠሪያ ስም ማለት ነው፡፡ ይህ ስም ከሌላው ሰው ተለይተው የሚጠሩበት ስም


ነው፡፡ በተጨማሪም በሌላ የሚሰጥ ወይም በራስ የሚመረጥ ነው፡፡ ለምሳሌ አበበ፡፡
2) የተቀብኦ ስም፡- ይህ ሰውየው ከኖረ ከጊዜ በኋላ በሰዎች የሚሰጥለ፣ በሽረት እና በሞት የሚቀር ስም
ነው፡፡ ለምሳሌ ጳጳስ፣ ሻለቃ፡፡
3) የግብር ስም ፡- ጠባይን አመልን የሚያመለክት ስም ነው፡፡ ይህም ከጊዜ በኋላ የመጣን ወይም የሆነን
ጠባይ በመመልከት በሌላ የምሰጥ ነው፡፡ ለምሳሌ ያዕቆብ- ተረከዝ የዥ፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 19 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

4) የባሕርይ(የባሕርይ ግብር) ስም ፡- በሌላ ያልተሰጡ በነበረበት ዘመን ሁሉ ያለውን በሕርይ


የሚያመለክቱ ናቸው፡፡ የአምላክ ስሞች ባህርይውን እና ከባሕርይው ተነስቶ የሚሰራውን ግብር
የሚያመለክቱ ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡ ነገር ግን ስሞቹ ባሕርይውን ጠንቅቀው የገልጻሉ ማለት
አይደለም፡፡ የእግዚአብሔርን ባሕርይ ጠንቅቆ የሚረዳ ሕሊና እና አከናውኖ የሚገልጽ ቃልም
ስለሌለ፡፡ ከእግዚአብሔር የባሕርይ(የባሕርይ ግብር) ስሞች ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡
1. እግዚአብሔር - ቃሉ እግዚአ እና ብሔር ከሚሉ ሁለት የግዕዝ ቃል የተወሰደ ነው ትርጉሙም የአለም
ገዢ ፣ የአለም ጌታ ፣ አለምን ፈጥሮ የሚገዛ ፣ የአለም ንጉስ ማለት ነው፡፡ እንደ ቤተ ክርስቲያን
ሊቃውንት አገላለጽ ከሆነ እግዚአብሔር “እግዚአብሔር ነኝ” ሲል የገለጠው ከሙሴ በኋላ ነው፡፡ ዘዳ
6፤2-3
2. ይሖዋ/ያህዌ - ይሖዋ እብራይስጥ፣ ያህዌ ግእዝ ሲሆን ትርጉሙም ያለና የሚኖር ማለት ነው፡፡
እግዚአብሔር አምላክ የነበረ፣ ያለና የሚኖር መሆኑን የሚየመለክት ነው፡፡ ዘፀ 3፤14፣ ራዕ 1፤4፡፡
3. አልፋና ኦሜጋ - የግሪክ ቃል ነው ቅዱስ ኢሳይያስ እንደገለፀው ‹‹እኔ ፊተኛ ነኝ ፣ እኔም ኃለኛ ነኝ››
የሚለው ቃል የዚህ ትርጉም ነው፡፡ በራእይም ‹‹የነበረውና ያለው የመጣውና የሚመጣው ሁሉን የሚገዛ
እግዚአብሔር አምላክ አልፋና ኦሜጋ እኔ ነኝ›› በማለት በዚሁ ስም ተገልፆአል፡፡ ኢሳ 44፤6፣ ራዕ 1፤8፣
22፤13፡፡
4. ኤልሻዳይ - የዕብራይስጥ ቃል ነው ትርጉሙ ሁሉን ቻይ፣ ሁሉን ያዥ ማለት ነው፡፡ ዘፍ 17፤1፣ ዘጸ
6፤3

1.8 የእግዚአብሔር ባህርያት


የቅዱሳት መፅሐፍት ስለ እግዚአብሔር መኖር በብዛት ከመጻፉም በላይ ስለ እርሱ የተሰጡ ባህርዩን
የሚገልፁ ቅፅል ስሞች አሉት እነርሱም የሚከተሉት ናቸው፡፡

1. ቅዱስ፡- እግዚአብሔር ቅዱስ ነው፡፡ እርሱ ራሱ ‹‹እኔ ቅዱስ እንደሆንኩ እናንተም ቅዱሳን ሁኑ›› ሲል
ተናግሯል ዘሌ 19፣2 ኢሳ 6፣3፡፡

2. ጻድቅ፡- እግዚአብሔር በሁሉ እውነተኛ ነው፡፡ በእውነተኛነቱ ለሁሉ በትክክል ይፈርዳል


1ኛ ሳሙ 2፤2 2ኛጢሞ 4፤8፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 20 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

ዮሐንስ አቡቀለምሲስ (በራዕዩ 16፣7) ‹‹አዎን አቤቱ ሁሉን የምትገዛ እግዚአብሔር ሆይ ፍርድህ እውነተኛና
ጽድቅ ነው›› ብሏል
3. አምላከ አማልክት (የአማልክት አምላክ) ፡- እግዚአብሔር አምላክነቱ የባህሪው ነው፡፡ የሰዎች አማልክት
መባል ግን ፀጋ ነው፡፡ የፀጋ አማልክት የሚባሉትም የእግዚአብሔርን ቃል ህዝቡን የሚያስተምሩ መምህራን
ካህናት ናቸው እንጂ ጣኦታት አይደሉም መዝ 81፤6፣ ዮሐ 10፣34
4. የጌቶች ጌታ፡- እግዚአብሔር ጌትነቱ የባህሪው ነው የሰዎች ጌቶች መባል ግን የፀጋ ነው ጌቶች
የሚባሉትም መምህራን ናቸው፡፡ ስለእግዚአብሔር የባህርይ ጌትነት ነብዩ ዳዊት ‹‹እግዚአብሔር እግዚእ
አስተርአየ ለነ›› ይላል መዝ 117፣27፣ ዮሐ 20፣28፡፡
5. ሁሉን ቻይ፡- ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር ፈፅሞ የለም ሁሉን ማድረግ ይችላል እግዚአብሔር ራሱ
ለአብርሐም ‹‹ሁሉን ቻይ ነኝ (ኤልሻዳይ)›› ነኝ ብሎ ገልፆለታል፡፡ ዘፍ17፣1 ሉቃ1፣37
6. ሁሉን አዋቂ፡- እግዚአብሔር ሁሉን ነገር ከመሆኑ በፊት ያውቃል ነገሮች ሁሉ ለመታሰባቸው ፣
ከመሰረታቸው በፊት ያውቃቸው፡፡ መዝ 138፤1-5፣ ዮሐ 2፤5፣ ኤር 17፤10፡፡
7. ዘላለማዊ እግዚአብሔር በዘመናት አይወሰንም፡- ከዘመን በፊት ነበር ፣ ዘመናትንም አሳልፎ ይኖራል፡፡
መዝ 89፤1-2 በጠቅላላ እግዚአብሔር መጀመሪያና መጨረሻ የለውም ራሱ መጀመሪያ መጨረሻ ነውና፡፡
በእርሱ ዘንድ ለውጥ የለም፡፡ ኢሳ 44፤6፡፡

የመለማመጃ ጥያቄዎች
1. ሃይማኖት ማለት ምን ማለት ነው)
2. ሃይማኖት በተስፋ የሚረዱት ነው ሲባል ምን ማለት ነው)
3. ሃይማኖት ለምን ያስፈልጋል)
4. የክርስትና ሀይማኖት ልዩ ባህሪያት ምንድን ናቸው)
5. የአማላካችን የልዑል እግዚአብሔር ባሕርያቱ ምን ምን ናቸው)
6. አልፋና ኦሜጋ ምን ማለት ነው)
7. የሃይማኖት አስፈላጊነት ምንድን ነው)
8. የክርስትና ሀይማኖት ልዩ ነው ስንል ምን ማለታችን ነው)
9. የአምላክ ስሞችን ከነትርጓሜያቸው ዘርዝሩ)
10. የሰው ልጅ ነጻ ፍቃድ ፣ ምርጫና ኃላፊነት ተሰጥቶታል ስንል ምን ማለታችን ነው)

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 21 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

ምዕራፍ ሁለት ሥነ ፍጥረት


2.1 መግቢያ

ልዑል እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን እንዲሁም በእርሱ ውስጥ የሚገኙትን ነገሮች ሁሉ ከምንም ወይም
ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣበትን ማለትም የፈጠረበትን ያፈጣጠር ታሪክ በዝርዝር የሚያስረዳ ትምህርት
ሥነ ፍጥረት ይባላል፡፡

እግዚአብሔር በመጀመርያ ቀን ሰማይን ምድርንና ብርሃንን ፈጠረ፡፡

በሁለተኛውም ቀን ከበላይና ከበታች ያለውን ውኃ የሚለይ ጠፈርን ፈጠረ ጠፈሩንም ሰማይ ብሎ ጠራው፡፡

በሦስተኛው ቀን ከሰማይ በታች ያለው ውሃ ተከማችቶ ባሕር እንዲባልና ውሃው አንድ ቦታ ሲከማች
የተገለጸው ደረቅ ቦታ ደግሞ ምድር እዲባል ወስኖ ዘርና ፍሬ የሚያፈሩ ዛፎችና ሳሮችን በምድር ላይ
እንዲበቅሉ አዘዘ፡፡ እንዲሁም ኾነ፡፡

በአራተኛው ቀን ዕለታትን ሳምንታትን ወሮችንና ዓመቶችን እንዲለዩ ተብሎ ፀሐይ ጨረቃና ከዋክብት
ተፈጠሩ፡፡

በአምስተኛው ቀን አዕዋፍና የባሕር ውስጥ ተንቀሳቃሾች እንዲሁም ዓሣዎች ተፈጠሩ፡፡

በስድስተኛው ቀን አራዊት እንስሳትና ሰው ተፈጠሩ፡፡

የሚታዩትንና የማይታዩትን ፍጥረቶች ኹሉ እግዚአብሔር በቃሉ እንደፈጠራቸው ቅዱሳት መጻሕፍት


ይመሰክራሉ፡፡ አፈጣጠሩም ከምንም ነው እንጂ የሰው ልጆች ነገር ለመፈልሰፍ አንዱን ንጥረ ነገር በማሻሻል
ወይም አንዱን ከሌላው ጋር በማቀላቀል የሚያከናውናት ዓይነት ሥራ አይደለም ስለዚህ ነው ነቢዩ ዳዊት
‹‹በእግዚአብሔር ቃል ሰማያት ተፈጠሩ የሰማይ ሰራዊት ኹሉ በአፉ እስትንፋስ … እርሱ ስለተናገረ ኾነዋል
እርሱም ስላዘዘ ጸንተዋል›› መዝ 33፤7-9፡፡

እንዲሁም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ዕብራውያን በላከው መልእክቱም ‹‹ዓለም በእግዚአብሔር አንድ
ቃል እንደተፈጠረ የምናውቀው በእምነት ነው የምናየው ነገር ሁሉ ከምንም እንደተገኘ በእምነት
እናስተውላለን፡፡›› ዕብ 11፤3፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 22 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

እግዚአብሔር ፍጥረቱን ሲፈጥር ለእርሱ ምንም የሚያስፈልገው ነገር ኖሮት አይደልም፡፡ በመለኮት ክብሩ
ብቻውን መኖር ሲችል የደግነት ባሕርዩ ኹሉን ፈጠረ፡፡

2.1.1 ትርጉም

ሥነ ፍጥረት ማለት የሁለት ቃላት ጥምር ሲሆን እነርሱም ‹‹ሥነ›› እና ‹‹ፍጥረት›› ናቸው፡፡

‹‹ሥነ›› ማለት ‹‹ሠናይ›› ከሚል የግዕዝ ግስ የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ያማረ ማለት ነው፡፡ በዚህም
መሰረት ሥነ ፍጥረት ማለት የተዋበ ያማረ ፍጥረት ማለት ነው፡፡

‹‹ሥነ›› ማለት ‹‹ተንስአ›› ከሚል የግዕዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተስማማ ማለት ነው፡፡ በዚህም
መሰረት ሥነ ፍጥረት ማለት የተስማማ የተግባባ ፍጥረት ማለት ነው፡፡ ስያሜው ሊሰጥ የቻለው አራቱ
ባሕርያተ ሥጋ እርስ በእርሳቸው የሚቃረኑ ሲሆኑ በእግዚአብሔር ጥበብና ኃይል ተስማምተው
መኖራቸውን ለማመልከት ነው፡፡

2.1.2 የፍጥረታት ዓላማ

ልዑል እግዚአብሔር ይህን ዓለም የፈጠረበት ዓላማ ፍጥረታትም የተፈጠሩበት እንደዚህ ነው፡፡ ከሀያ ሁለቱ
ፍጥረታት መካከል ሁለቱ ሕያዋን ሲሆኑ ሀያዎቹ ግን አላፊዎች ናቸው ሁለቱ ሰው እና መላእክት ናቸው፡፡
የእነርሱ የመፈጠር ዓላማ ስሙን ቀድሰው ክብሩን እንዲወርሱ ሲሆን ሌሎቹ ፍጥረታት ግን ልንበላቸው
ልንጠጣቸው ልንሰራባቸው ልንማርባቸው ተፈጥረዋል፡፡

 እንጠጣው ዘንድ ውሃ ወተት …. ወዘተ


 እንጓዝበት ዘንድ ፈረሱን በቅሎውን …. ወዘተ
 እንማርባቸው ዘንድ ፀሐይ እሳት ውሃ ወዘተ እነዚህ በባህርያቸው አንድነት ሦስትነት አላቸው በእነዚህ
የሥላሴን አንድነት እና ሦስትነት እንማርባቸዋለን

2.1.3 የፍጥረታት የአፈጣጠር መንገድ


ወደፊት በየቦታቸው እንደምንመለከተው እግዚአብሔር ፍጥረታትን በሁለት መንገድ ፈጥሯዋቸል፡፡
የመጀመሪያው ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣቸው ናቸው፡፡ ሁለተኛው ከተፈጠረው የተፈጠሩ ናቸው፡፡
እነዚህም እምኀበ አልቦ ኀበ ቦ እና ግብር እም ግብር ተብሎ ይጠራሉ፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 23 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

1. እምኀበ አልቦ ኀበ ቦ
እግዚአብሔር ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ እንደፈጠረ በዕብራውያን 11 ቁ 3 ‹‹ዓለሞች በእግዚአብሔር
ቃል እንደ ተዘጋጀ ስለዚህም የሚታየው ነገር ከሚታዩት እንዳልሆነ በእምነት እናስተውላለን›› በሌላም ስፍራ
‹‹የሌለውን እንዳለ አድርጎ በሚጠራ›› ሮሜ 4 ቁ 17 ተብሏል፡፡ በእነዚህ ጥቅሶች ላይ ‹‹የሚታየው ነገር
ከሚታዩት እንዳልሆነ›› እና ‹‹የሌለውን እንዳለ›› የሚሉት ቃላት እምኀበ አልቦ ኀበ ቦ መፍጠሩን ያስረዳሉ፡፡
እምኀበ አልቦ ኀበ ቦ በሌላ ስሙ ‹‹ጥንተ ተፈጥሮ›› ይባላል፡፡

2. ግብር እም ግብር
ከተፈጠረ ነገር የተፈጠሩ ከሚባሉት ውስጥ ለምሳሌ የሰው ሥጋ ከአፈር የአዕዋፍ ደግሞ ከውኃ
መፈጠራቸው ምሳሌ ይሆናል፡፡ ዘፍ 1፤20 ዘፍ 2፤7፡፡

የፍጥረታት አገኛኛታቸው

ሥነ ፍጥረት አገኛኘታቸው በሦስት መንገድ ነው፡፡

1. በአርምሞ (በዝምታ) ልዑል እግዚአብሔር በአርምሞ (በዝምታ) የፈጠራቸው ፍጥረታት በዕለተ እሁድ
የተፈጠሩ መሬት ፣ ውሃ ፣ ነፋስ ፣ እሳት ፣ ጨለማ ፣ ሰባቱ ሰማያት እና መላዕክት ናቸው፡፡
2. በነቢብ (በመናገር) ልዑል እግዚአብሔር በነቢብ (በመናገር) የፈጠራቸው ፍጥረታት ከእለተ እሁድ
ስምንተኛ ፍጥረት ብርሃን አንስቶ እስከ ዓርብ ሦስተኛ ፍጥረት ድረስ ያሉትን ፍጥረታት በመናገር
ፈጠራቸው፡፡ ለምሳሌ ብርሃን ጠፈር ዕፅዋት እንስሳት … ወዘተ
3. በገቢር (በመስራት) ልዑል እግዚአብሔር በገቢር (በመስራት) የፈጠራቸው ፍጥረታት ብዛት አንድ ነው
እርሱም የሰው ልጅ ነው፡፡ እግዚአብሔር ከፈጠራቸው ፍጥረታት እንደ ሰው የከበረ ፍጡር የለም ከዙፋኑ
ወርዶ ከመሬት ጭቃ የሰውን ልጅ በእጁ ፈጥሮታልና፡፡ ዘፍ 1፤26፡፡

2.1.4 ፈጣሪ እና ፍጡር

እግዚአብሔር ዓለም ሳይፈጠር እንደዛሬ ሁሉ አንድነቱ ሦስትነቱን ሳይጠቀልል ሦስትነቱ አንድነቱን


ሳይለያይ ሲሰለስ ሲቀደስ ይኖር ነበር፡፡ ‹‹እንዘ አሃዱ ሰለስቱ ወእንዘ ሰለስቱ አሃዱ›› አንዱ ሲሆኑ ሦስት
ሦስት ሲሆኑ አንድ እንዲል፡፡ ዓለም ሳይፈጠር ማን ያመሰግነው ነበር ቢሉ በገዛ ባህሪው ይመሰገን ነበር፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 24 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

እግዚአብሔር ይህን ዓለም ለመፍጠሩ ግን የጎደለበት ኖሮ ይሞላልኛል ጥቅም አገኝ ብሎ አይደለም


ይቅርታዬንና ክብሬን እሰጣቸው ዘንድ ነው እንጂ የምጠቀምባቸው ኖሮ ከእነሱ እጠቀም ብዬ
አልፈጠርኳቸውም ብሏል፡፡ (መጽሐፈ ቀሌሜንጦስ)

ሰው የሆነ እንደሆነ ግን ልሰወር ባለ ጊዜ አጥር ቅጥር መጋረጃ ልገለጽም ባለ ጊዜ መብራት አብሩልኝ


ግለጡልኝ ይላል፡፡ እርሱ ግን ይህን ሁሉ አያሻውም ልሰወር ባለ ጊዜ ራሱን በራሱ ይሰውራል ልገለጽ ባለ
ጊዜ ራሱን በራሱ ይገልጻል ፡፡

ዳግመኛም የሰው ባህርይ መራብ መጠማት ስለሆነ የሚባለው የሚጠጣው ነገርን ይሻል፡፡ እርሱ ግን ይህን
ሁሉ አይሻም፡፡

2.2 የስድስቱ ቀን ፍጥረታት

ልዑል እግዚአብሔር ይህንን ዓለም የፈጠረው በስድስት ቀናት ነው፡፡ በዘመነ ዮሐንስ በወርሃ መጋቢት 29
ቀን ልዑል እግዚአብሔር 22ቱን ፍጥረታት መፍጠር ጀመረ፡፡ በሚያዝያ 5 ቀን ፍጥረታትን መፍጠር
አቆመ፡፡ ይህ ቀን እንዴት ሊታወቅ ይቻላል ቢሉ በባህረ ሃሳብ ስሌት መሰረት ነው፡፡

2.2.1 የፍጥረታት ብዛት እና አቆጣጠር

ልዑል እግዚአብሔር ከእለተ እሁድ እስከ እለተ ዓርብ ድረስ የፈጠራቸው ፍጥረታት እያንዳንዱ ቢቆጠሩ
ፍጡር ተናግሮ አይፈጽመውም ነበር ነገር ግን ብዙውን አንድ ወገን እያደረጉ ቢቆጥሩ 22 ይሆናል፡፡ ይህም
ምሳሌነቱ የሀያ ሁለቱ አርስተ አበው ነው፡፡ እነርሱም፡- አዳም ፣ ሴት ፣ ሄኖስ ፣ ቃይና ፣ መላልኤል ፣
ያሬድ ፣ ማቱሳላ ፣ ላሜህ ፣ ኖህ ፣ ሴም ፣ አርፋክሳድ ፣ ሳላ ፣ ኤቦር ፣ ፋሌቅ ፣ ረግው ፣ ሴሩሕ ፣
ናኮር ፣ ታራ ፣ አብርሃም ፣ ይስሐቅ እና ያዕቆብ ናቸው፡፡

እነዚህ 22ቱ ሥነ ፍጥረታት የሚባሉት በዝርዝር

1ኛ በዕለተ እሁድ የተፈጠሩ ፍጥረታት ብዛት ስምንት ናቸው፡፡

2ኛ በዕለተ ሰኞ የተፈጠሩ ብዛት አንድ ነው፡፡

3ኛ በዕለተ ማክሰኞ የተፈጠሩ ፍጥረታት ብዛት ሦስት ናቸው፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 25 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

4ኛ በዕለተ ረቡዕ (ሮብ) የተፈጠሩ ፍጥረታት ብዛት ሦስት ናቸው፡፡

5ኛ በዕለተ ሐሙስ የተፈጠሩ ፍጥረታት ብዛት ሦስት ናቸው፡፡

6ኛ በዕለተ ዓርብ የተፈጠሩ ፍጥረታት ብዛት አራት ናቸው፡፡

እነዚህ ከላይ ልዑል እግዚአብሔር ከእሁድ አንስቶ እስከ አርብ ድረስ የፈጠራቸው ፍጥረታት ናቸው፡፡
ከእነዚህ ራሳቸውን ችለው የሚንቀሳቀሱ አሉ ልዑል እግዚአብሔር ካልፈቀደ በቀር የማይንቀሳቀሱም አሉ፡፡

2.2.2 የዕለተ እሁድ ፍጥረታት

እግዚአብሔር አምላክ በመጀመርያው ቀን እሑድ ስምንት ፍጥረትን ፈጥሮአል፡፡ እነርሱም ነፋስ ፣ እሳት ፣
ውኃ ፣ መሬት ፣ ጨለማ ፣ መላእክት ፣ ብሩህ ሰማይና ብርሃን ናቸው፡፡ በዚህ ክፍል እያንዳንዱን
ፍጥረታት በዝርዝር እንመለከታልን፡፡

1 አራቱ ባሕርያተ ሥጋ

እግዚአብሔር እሑድ ቀን በመጀመርያው ሰዓት ሌሊት አራቱ ባሕርያተ ሥጋን ፈጠረ፡፡ አራቱ ባህርያተ
ሥጋ የሚባሉት ነፋስ ፣ እሳት ፣ ውኃና መሬት ናቸው፡፡ አራቱ ባህርያተ ሥጋ ሦስት ግብር (ጠባይ)
እንዲኖራቸው አድርጎ ነው የፈጠራቸው፡፡ ይኸውም በባሕርዬ አንድነት ሦስትነት እንዳለ እወቁ ማለቱ ነው፡፡

 የእሳት ግብሩ (ጠባዩ) ማቃጠል ብሩህነት ደረቅነት ነው፡፡


 የነፋስ ግብሩ (ጠባዩ) ርጥብነት ማቃጠልና ጨለማነት ነው፡፡
 የውኃ ግብሩ (ጠባዩ) ብሩህነት ርጥብነትና ቀዝቃዛነት ነው፡፡
 የመሬት ግብሩ (ጠባዩ) ደረቅነት ጨለማነትና ቀዝቃዛነት ነው፡፡

አራቱ ባሕርያተ ሥጋ ለምን አራት ሆኑ

አራቱ ባሕርያተ ሥጋ አራት የሆኑበት ምክንያት በባሕርዩ አራት ነገሮች እንዳሉት ለማመልከት ነው እኒህም
ባለጠግነት ርኀሩህነት ከሃሊነት እና ፈታሒነት ናቸው፡፡

 ባለጠግነቱ በመሬት ይመሰላል፡፡


 ርኀሩኀነቱ በውኃ ይመሰላል፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 26 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

 ከሃሊነቱ በእሳት ይመሰላል፡፡


 ፈታሒነቱ በነፋስ ይመሰላል፡፡

 ባለጠግነቱ በመሬት መመሰሉ እንደምን ነው ቢሉ?

ስለ ባለጠግነቱ ‹‹ለሚጠሩት ሁሉ ባለጠጋ ነው›› ሮሜ 10፤12 እንዲል፡፡ ባለጠጋ እግዚአብሔር ሁሉን


እንዲያስገኝ እንዲሁም መሬትም የምንበላውን የምንጠጣውንና የምንለብሰውን ታስገኛለች፡፡ ‹‹እግዚአብሔርም
በጎ ነገርን ይሰጣል ምድራችንም ፍሬዋን ትሰጣለች›› መዝ 84፤12

ልዑል እግዚአብሔር ባለጠጋ ነኝ ሲል መሬትን ፈጠረ ሀብት ሁሉ ከመሬት ይገኛልና ሌላው ደግሞ መሬት
ሁሉን ቻይ ናት የፈጠረውን ፍጥረት ሁሉ ችላ ትኖራለች እንደዚሁም ሁሉ ልዑል እግዚዘብሔር ሁሉን
ችሎ ታግሶ ለሁሉ ሀብቱን ሰጥቶ ይኖራል፡፡

 ርኀሩኀነቱ በውኃ መመሰሉ እንደምን ነው ቢሉ?

ውኃ ያደፈውን እንደሚያነጻና እንደሚያጠራ ሁሉ እግዚአብሔርም ኃጢአተኛውን ማረኝ ብሎ ቢቀርበው


ሁሉንም የሚቀበል በመሆኑ ነው ርኀሩኀነቱ በውሃ የተመሰለው፡፡ ‹‹እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ እንደ
ምህረትህን ብዛት መተላለፌን ደምስስ፡፡ ከበደሌም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ›› እንዲል ዳዊት መዝ 50፤1፡፡

 ከሃሊነቱ በእሳት መመሰሉ እንደምን ነው ቢሉ?

ከሃሊነት ማለት ቻይነት ማለት ነው፡፡ እሳት በተነሳ ጊዜ ገደልና ባሕር ካልከለከለው በስተቀር ሁሉን
ማጥፋት ይቻለዋል፡፡ እግዚአብሔርም ቸርነቱ ካልከለከለው በቀር ሁሉን ማጥፋት ይቻለዋል፡፡
‹‹ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም›› ሉቃ 1፤37፡፡

 ፈታሒነቱ በነፋስ መመሰሉ እንደምን ነው ቢሉ?

ፈታሒነቱ (ፍርዱ) በነፋስ መመሰሉ ገበሬ አዝመራውን አጭዶ ከአውድማው ላይ ወቅቶ በመንሽ ባነሳው
ጊዜ በነፋስ ኃይል ፍሬ ከገለባው ገለባውም ከፍሬ ይለያል፡፡ ልዑል እግዚአብሔርም በፍርዱ ጻድቃንን ከኃጣን
ኃጣንን ከጻድቃን ይለያል፡፡ ‹‹መንሹም በእጁ ነው አውድማውንም ፈጽሞ ያጠራል ስንዴውንም በጎተራ
ይከታል ገለባውን ግን በማይጠፋ እሳት ያቃጥለዋል›› ሉቃ 3፤17

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 27 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

ልዑል እግዚአብሔር እነዚህን አራቱ ባህርያተ ሥጋን በአንዴ በሙላት (በብዛት) አልፈጠራቸውም ጥቂት
እሳት ጥቂት መሬት ጥቂት ነፋስ ጥቂት ውሃ ፈጥሮ ብዙ ተባዙ ብሎ በቃሉ ቢያዛቸው በዝተው ተባዝተው
ህሊና እግዚአብሔር የመጠነላቸው ድረስ ደርሰው ቆመዋል፡፡ በከሃሊነቱ ፀንተው ራሳቸውን ያዙ፡፡
እግዚአብሔር ካዘዘው ቅንጣት ታክል አልጨመሩም አልቀነሱም፡፡

አምላካችን እነዚህን ከላይ የተዘረዘሩት ግብር ይዘው የፈጠራቸው ፍጥረታት አንዱ ከአንዱ ጋር ቢጣሉ
ያስታርቃቸዋል በእነዚህ ባሕርያቸው

 እሳት በውዕየቱ (በማቃጠሉ) (በሙቀቱ) ከነፋስ በብሩህነቱ (በብርሃናዊነቱ) ከውሃ በይቡስነቱ ከመሬት
አዋህዶ አስማምቶ ትቶታል፡፡
 ውሃን በብሩህነቱ (በብርሃናዊነቱ) ከእሳት በቆሪርነቱ (በቀዝቃዛነቱ) ከነፋስ በርጡቡነቱ (በርጥብነቱ)
ከመሬት አስማምቶታል፡፡
 መሬትም በይቡስነቱ (በደረቅነቱ) ከእሳት በጽሉምነቱ (በጨለማነቱ) ከነፋስ በርጡቡነቱ (በርጥበቱ) ከውሃ
እንዲህ አድርጎ አስማምቶታል፡፡

በተጨማሪም እነዚህ አራቱ ባህርያተ ሥጋ እርስ በእርሳቸው እንዲሸናነፉ አድርጎ ነው የፈጠራቸው ይህም
እንዲህ ነው እሳት ውሃን ያጠፋዋል ውሃ ደግሞ እሳትን ያጠፋዋል፡፡ እንዲሁም ነፋስ መሬትን ይበትነዋል
መሬት ደግሞ ነፋስን ይገድበዋል፡፡

1 ጨለማ

ልዑል እግዚአብሔር በዕለተ እሁድ ከፈጠራቸው ፍጥረታት መካከል ጨለማ በአምስተኛ ደረጃ የተፈጠረ
ነው የተፈጠረውም በዝምታ ነው ስለምን በዝምታ ፈጠረ ቢሉ የሚሰማ በሌለበት መናገር አይረባምና ሲል
ነው፡፡ ሌላው የሚሰሙ መላዕክት አልፈጠረም እና በዝምታ ጨለማን ፈጠረ፡፡ ይህ ጨለማ በዚህ ዘመን
ካለው ጨለማ ጋር የሚወዳደር አይደለም ይህ ጨለማ በውስጡ ምንም አይነት ብርሃን የለውም ድቅድቅ
ጨለማ ነበር ታዲያ አሁን ያ ጨለማ የት ሄደ ያሉ እንደሆነ አስቀድሞ ዲያቢሎስ በበደለ ጊዜ ተጠቅልሎ
ወደ ሲኦል ወርዶበታል፡፡ ስለምን ጨለማን ፈጠረ ያሉ እንደሆነ ባትፈልጉኝ ባትመረምሩኝ አልገኝም ሲል
ጨለማን ፈጠረ፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 28 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

2 ሰባቱ ሰማያት

ሰባቱ ሰማያት በሌላ አጠራር ብሩህ ሰማይ በመባል ይታወቃል፡፡ አጠራሩ ቀና ብለን ከምንመለከተው ሰማይ
(ጠፈር) የተለዩ ሰባቱ ሰማያትን ለማመልከት ያገለግላል፡፡ ሰማያት ሰባት ስለመሆናቸው ‹‹የሰማይ ምጥቀቱ
ሳይታይ ሰባቱ ሰማያት ሳይቆጠሩ›› ዕዝ 4፤4

የሰባቱ ሰማያት ዝርዝር ከላይ ወደ ታች

በግዕዝ በዕብራይስጥ

ጽርሐ አርያም ዊሎን


መንበረ መንግስት ረቂዕ
ሰማይ ውዱድ ሻሓቅ
ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ዝቡል
ኢዮር ምዖን
ራማ ምኮን
ኤረር ዓርቦት

የሰባቱ ሰማያት አፈጣጠራቸው

ሀ. ጽርሐ አርያም

ከሰማያት ሁሉ በላይ ናት፡፡ ከእርሷ በላይ ሌላ ሰማይ የለም፡፡ ዳርዋና መጨረሻዋን የሚያውቅ እግዚአብሔር
ብቻ ነው፡፡ ጽርሐ አርያም በመንበረ ስብሐት ላይ እንደ ጠፈር ሆና ተፈጥራለች፡፡

ለ. መንበረ መንግሥት (መንበረ ስብሐት)

መንበረ መንግሥት መንበረ ብርሃን ፣ መንበረ ስብሐት እና መንበረ ጸባዖት የተባሉ ሌሎች ስሞች አላት፡፡
አሰራሯም እንደ ቤተ መቅደስ ነው፡፡ በዚህች ሰማይ ላይ ሥላሴ ለጻድቃን ለሰማዕታት እና ለመላእክት
በዘፈቀደ ሁነው ይታዩበታል፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 29 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

በዘፈቀደ ሁነው ይታዩበታል ሲባል ለምሳሌ ለነቢዩ ኢሳይያስ እግዚአብሔር በአዳራሽ እንደተቀመጠ ንጉስ
ሆኖ ተገልጦለታል፡፡ ‹‹ንጉስ ኦዝያን በሞተበት ዓመት እግዚአብሔር በረጅምና ከፍ ባለ ዙፋን ተቀምጦ
አየሁት የልብሱም ዘርፍ መቅደሱን ሞልቶት ነበር›› ኢሳ 6፤1

ሐ. ሰማይ ውዱድ

ሰማይ ውዱድ በኪሩቤል ጀርባ ላይ የተዘረጋ ሆኖ ለመንበረ መንግስት እንደ አዳራሽ ወለል ነው፡፡በሌላ
አገላለጽ መንበረ መንግስት እንደ ዙፋን የተዘረጋበት ሰማይ ነው፡፡ ‹‹ከእንስሶች (ኪሩቤል) ራስ በላይ
የሚያስፈራ በረዶ የሚመስል የጠፍር አምሳያ በራሳቸው ላይ ተዘርግቶ ነበር›› ሕዝ ምዕ 1 ቁ 22፡፡

መ. ኢየሩሳሌም ሰማያዊት

ኢየሩሳሌም ሰማያዊት አሠራሯ እንደ ቤተ መቅደስ ያለ ነው፡፡ አስራ ሁለት ደጆች አሏት፡፡ ብርሃኗ ከሌሎች
ሰማያት ልዩና የተዋበ ነው፡፡ አዕማዶቿ የብርሃን ክዳኗ የብርሃን መርገፏ የብርሃን የሆነላት ሰማይ ናት፡፡
በሰባት የእሳት መጋረጃና በሰባት የእሳት አጥር የታጠረች ናት፡፡

በጉኖቿም የአስራ ሁለቱ ሐዋርያት ስም በመድረኳም የአስራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል ስም በምሶሶዋ
የጻድቃንና የሰማዕታት ስም ተጽፎበታል፡፡

ኢየሩሳሌም ሰማያዊት በውስጧ ቁመቷም ወርዷም እኩል የሆነ ከብርሃን ተሰራች ‹‹ታቦር ዘዶር›› የምትባል
የእመቤታችን ምሳሌ የሆነች ታቦት የተቀመጠባት ሰማይ ናት፡፡ ‹‹ታቦት ዘዶር እንተ ይእቲ እግዝትነ
ማርያም›› እንዲል አባ ሕርያቆስ

‹‹የላይኛይቱ ኢየሩሳሌም ግን በነጻነት የምትኖር ናት እርሷም እናታችን ናት›› ገላ 4፤26፡፡ ‹‹በኢየሩሳሌም


አትማሉ የንጉስ ከተማ ናትና›› ማቴ 5፤34፡፡ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት በኋላ ጻድቃን የሚወርሷት መንግስተ
ሰማያት ይህች ናት፡፡

ከዚህ በታች የተቀሩት ሦስቱ ከተሞች ዓለመ መላእክት (የመላእክት ከተሞች) ይባላሉ፡፡

ሠ. ኢዮር

ረ. ራማ

ሰ. ኤረር ናቸው፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 30 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

እነዚህ የመላእክት ሃገር ሦስቱም ቁመታቸው ወርዳቸው አንድ ዓይነት ነው፡፡

እነዚህን ሦስት የመላእክት ከተሞች ሲፈጥር ከላይ ከሰማይ ውዱድ አስከ ጽርሐ አርያም ድረስ እርሱ ባወቀ
ዘግቶታል እነዚህን ግን ሲሰራ ውስጥ ለውስጥ እንዲገናኙ ግን ወደ ላይ ከሰማይ ውዱድ እስከ ጽርሐ
አርያም ያለውን የሚያሳይ ምንም መስኮት አልሰራላቸውም ብቻ ወጥ ድፍን አርጎ ሰርቷቸዋል ስለምን ቢባል
በቀጣይነት የሚፈጥራቸው ፍጥረታት በነዚህ ሰማያት ያሉ መላእክት ምሥጢሩን እንዳያዩ ነው፡፡ ሌላው
እርሱ ሲሰራ አግዘነዋል ብለው እንዳይስቱ ነው፡፡

3 መላእክት
 አፈጣጠራቸው

መላእክት በእለተ ዕሁድ የተፈጠሩ ፍጥረታት ናቸው፡፡ መላእክትን በመቶ ነገድ በአስር አለቃ በአስር ከተማ
በሦስቱ ሰማያት ፈጥሮ አስፍሮአቸዋል፡፡ መላእክት ከምንም ነገር የተፈጠሩ ሲሆን አንዳድ ወገኖች የዳዊት
መዝሙርን በመጥቀስ መዝ 10፤3 ከእሳት እና ከነፋስ ተፈጠሩ ይላሉ፡፡ ዳዊት ያለው ተልዕኳቸውን
ለማመልከት ነው፡፡ ነፋስ ፈጣን ነው መላእክትም በተልዕኳቸው ፈጣኖች ናቸው፡፡ እሳት ረቂቅ ነው
መላእክትም ረቂቃን ናቸው፡፡ ‹‹መላእክቱን መንፈስ የሚያደርግ አገልጋዮቹንም የእሳት ነበልባል›› መዝ
103፤4

 አሰፋፈራቸው

እግዚአብሔር መላእክትን ከፈጠራቸው በኋላ በሦስቱ የመላእክት ከተሞች በኢዮር በራማና በኤረር በከተማ
አሥር በነገድ መቶ አድርጉ አስፍሯቸዋል፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 31 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

የመላእክት ከተማ አለቃ ነገድ ስማቸው


ከተሞች
ኢዮር 1 ሳጥናኤል 10 አጋእዝት
2 ኪሩብ 10 ኪሩቤል
3 ሱራፊ 10 ሱራፌል
4 ቅድስ ሚካኤል 10 ኃይላት
ራማ 5 ቅዱስ ገብርኤል 10 አርባብ
6 ቅዱስ ሩፋኤል 10 መናብርት
7 ቅዱስ ሰርኤል 10 ሥልጣናት
ኤረር 8 ሰደክያል 10 መኳንንት
9 ሰላታኤል 10 ሊቃናት
10 አናንያል 10 መላእክት

4 ብርሃን

ብርሃን በዕለተ እሁድ በስተመጨረሻ በስምንተኛነት የፈጠረው ፍጥረት ነው፡፡ ብርሃን የተፈጠረው በመናገር
ነው፡፡ በዚህም በዕለቱ ብቸኛው በነቢብ የተፈጠረ ፍጥረት ነው፡፡ ብርሃን በነቢብ (በመናገር) ከተፈጠረበት
ምክንያት አንዱ የሚሰሙ (ሰማዕያን) መላእክት የተፈጠሩ ስለሆነ ብርሃንን በመናገር ፈጠረው፡፡

ታሪኩም እንዲህ ነው እግዚአብሔር አምላክ መላእክትን ከፈጠረ በኋላ ተሰወራቸው ከዚህም በኋላ መላእክት
በተፈጥሮአቸው ፈጣሪያቸውን መመርመር ጀመሩ አንዱ የአንዱን ትንፋሽ በተሰማሙ ጊዜ ከየት መጣህ
ማን ፈጠረህ በማለት እርስ በእርሳቸው መጠያየቅ ጀመሩ ፤ ማን ፈጠረን በማለት መመራመር ጀመሩ፡፡ ያን
ጊዜ ሳጥናኤል ከሁሉ በላይ ነበርና ቀና ብሎ ቢያይ ሁሉ ከሱ በታች ናቸው ከዚያም እኔ ፈጠርኳችሁ አለ
ያን ጊዜ መላእክቱ አንተማ አልፈጠርከንም አንተ አኛን ከፈጠርክ እኛ ደግሞ ከኛ በታች ያሉትን ፈጥረናል
ማለት ነው አሉት፡፡ ያን ጊዜ እግዚአብሔር በዙፋኑ ሆኖ ቢገለጥ ሰባቱ ሰማያት ተናወጠ መላእክቱ እጅግ
ተረበሹ ተንቀጠቀጡ ያን ጊዜ ቅዱስ ገብርኤል ‹‹ንቁም በበሕላዌነ እስከ ንረክቦ አምላክነ›› የፈጠረን እራሱ
እስኪገለጥ ባለንበት እንጽና ብሎ መላእክትን አረጋጋ ያን ጊዜ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሁሉን መላእክት
እያቀፈ ይጠይቃቸው ጀመር ማን ፈጠራችሁ ይህ ሁሉ ሰማይ የኔ ቤት ነው ማን እዚህ አስገባችሁ ብሎ

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 32 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

ጠየቃቸው እነርሱም ይህን ሁሉ አንተ ታውቅ እንደሆነ እኛ አናውቅም አሉት ያን ጊዜ ብርሃን ይሁን ብሎ
አዘዘ ወድያው በስተምስራቅ ተፈጥሮ የነበረ እንደ ምንጭ እየፈሰሰ እየጎረፈ ሁሉ ዓለማትን አጥለቀለቀ፡፡

እግዚአብሔር ብርሃንን ስለምን ፈጠረ ቢሉ ብትሹኝ (ብትፈልጉኝ) ብትመረምሩኝ እገኛለው ሲል ነው፡፡

በዚህ ዕለት አምላካችን እነዚህን ስምንት ፍጥረታት ፈጥሮአል እሁድ ማለት አሃደ ከሚል የግእዝ ግስ
የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም አንድ አደረገ ማለት ነው፡፡ ሥነ ፍጥረት አንድ ተብሎ የጀመረው በዚህ ቀን
ስለሆነ የተሰጠ ስያሜ ነው፡፡

2.2.3 የዕለተ ሰኞ ፍጥረታት

እግዚአብሔር ሰኞ ዕለት እሁድ የፈጠረውን ውኃ ለሦስት ከፍሎ አንዱን እጅ ውኃ ከኤረር በታች አሰፈረው፡፡
ስሙንም ሐኖስ አለው፡፡ ይህንን ብጥብጥ ውኃ ባቢል በሚባል ነፋስ ተሸካሚነት ከጠፍር በላይ አሰፈረው፡፡
ሁለተኛውን እጅ ከሐኖስ በታች አሰፈረው ስሙንም ጠፈር አለው፡፡ ይህም የረጋ ውሃ ነው፡፡ ሦስተኛውን
እጅ ደግሞ በዚህ በምድር አሰፈረው ስሙንም ውቅያኖስ አለው፡፡ ሌላው እግዚአብሔር ጠፈርን የፈጠረው
የሰው ልጅ ጠፈርን እያየ ሰማያዊ ርስት እንዳለው እዲያውቅ እና ተስፋ እንዲያደርግ እንዲሁም በዕለተ
ረቡዕ ለሚፈጥራቸው ለፀሐይ ለጨረቃ ለከዋክብት ማህደር መመላለሻ እንዲሆኑ ነው፡፡

እግዚአብሔር በዕለተ ሰኞ እነዚህን ከላይ የተዘረዘሩትን ካዘጋጀ በኋላ በመቀጠል ምድር የተበጠበጠ እርጎ
መስላ ነበር፡፡ እናም ያንን ማስታካከል ጀመረ መሬትን ለያት ውሃውን ወደታች መሬትን ወደ ላይ አወጣት
እንደ አይብና እንደ አጓት ለይቶአቸዋል ከዚያም ለውሃው ውስጥ መንገድ ሰርቶ ትቶታል፡፡ ምድር ግን
ተራራውን ኮረብታውን የምትወልድ አስክትሆን ድረስ አግዝፎ አወፍሮ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ከሰሜን
እስከ ደቡብ ጎዝጉዞ ዘርግቶ አንጥፎ ከውሃ በላይ እንደ መርከብ አጽንቶታል፡፡ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር
ምድርን ዙርያዋን ሁለት እጅ አድርጎ ከፈላት የወዲያኛውን አንዱን እጅ ናጌብ አለው፡፡ የወዲያኛውን
ሁለተኛውን እጅ አድማስ አለው፡፡ በናጌብ እና በአድማስ መካከል ያለውን ጉድጓድ ውሃ ሞልቶበት ውቅያኖስ
አለው፡፡ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር ታላቁን ተራራ በታላላቁ ሚዛን ታናናሹ ተራራ በታናናሹ ሚዛን
ይመዘን ብሎ አዘዘው ያን ጊዜ ሁሉም በሚዛኑ ተመዝኖ ደጋው ያደላድል ቆላው ይጉደል ወንዙ ይከፈል
ብሎ አዘዘው ከዚያም እግዚአብሔር ከዚህ ከመሬት በታች ያሉትን ፍጥረታት ለእሳት ለነፋስ ለበርባኖስ
ለጨለማ ስድስት በምስራቅ ስድስት በምዕራብ ስድስት በሰሜን ስድስት በደቡብ በአጠቃላይ ሀያ አራት
መስኮት አወጣላቸው በእነዚህም በእነዚህም ሁለት ሁለት መላእክት ሰይፍ እያስያዘ ጠባቂ አቁሞአል፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 33 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

በመቀጠልም እግዚአብሔር ከእሳት በታች ያሉትን ነፋሳት አስራ ሁለት አለቆች አደረገላቸው ፤ አራቱን
አለቆች ነፋሳተ ምሕረት ስምንቱ አለቆች ነፋሳተ መዓት ናቸው፡፡ በሁለቱ ነፋሳተ መዓት መሐከል አንድ
አንድ ነፋሳተ ምህረት እያደረገ ሰርቶአቸዋል፡፡ በመቀጠልም አስራ ሁለቱን የእሳት አለቆች ከአስራ ሁለቱ
መስኮቶች አስራ ሁለቱን የነፋሳት አለቆች ከአስራ ሁለቱ መስኮቶች ወጥተው ምድር እንዲያደርቋት አዘዘ ያን
ጊዜ እነዚህ የእሳት እና የነፋሳት አለቆች ከየመስኮታቸው ወጥተው ምድርን የምስራቁ ወደ ምዕራቡ የሰሜኑ
ወደ ደቡቡ ወዲያ ወዲህ ቢመላለሱ ተራራው ኮረብታው ረጋ ፀና ዲንጋዩ በብረት የሚቆፈር ሆነ ምድር ግን
ገና በእግዚአብሔር ቃል ዘር የሚወድቅባት ናትና እጅግም በጣም አልደረቀችም በጣምም አልረጠበችም፡፡
ውሃ ምጥጥ አድርጋ ነበር ልክ እንደ ግንቦት እንደ ሰኔ ማሳ ያማረች የለሰለሰች ሆነች፡፡ ሌላው ደግሞ
ከምድር ጋር ተቀላቅሎ የነበረውን ውሃ በሦስት እጅ ከፍሎ አንዱን እጅ ከውቅያኖስ ቀላቀለው ሁለተኛውን
እጅ ከምድር በታች አደረገው ሦስተኛውን ደግሞ በምድር ላይ ባሕር ወንዝ ሐይቅ ኩሬ አደረገው፡፡ ለምድር
ሦስት ስም አላት ከውሃ ሳትለይ ፀብር (ጭቃ) ደርቃ ስትፍታታ መሬት ከውሃ ከተለየች በኃላ አፈር ትቢያ
ትባላለች፡፡

የዕለተ ሰኞ ፍጥረታት እነዚህ ናቸው፡፡ ሰኞ (ሰኑይ) ማለት ሁለት ማለት ነው፡፡ እንግዲህ በሁለተኛው ቀን
ዘጠኝ ፍጥረታት ደርሰዋል፡፡ ሰኞ ማለት ለፍጥረታት ሁለተኛ ለቀመር ሰባተኛ ለፀሐይ ስድስተኛ ማለት
ነው፡፡

2.2.4 የዕለተ ማክሰኞ ፍጥረታት

እግዚአብሔር በዕለተ ማክሰኞ (ስሉስ) የፈጠራቸው ፍጥረታት ብዛት ሦስት ናቸው፡፡ እነርሱም

1. በምሳር የሚፈለጡ (የሚቆረጡ)


2. በማጭድ የሚታጨዱ (አዝእርት)
3. በእጅ የሚለቀሙ (አትክልት)

ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ገነትን በምስራቅ አቅጣጫ ዘፍ 2፤8 ብሔረ ሕያዋንን በሰሜን አቅጣጫ ብሔረ
ብጹአንን በደቡብ አቅጣጫ መሬትን በመሐል ሲዖልን በምዕራብ አቅጣጫ እነዚህን አምስት አለማት አዘጋጀ፡፡
ምድርም ከተደላደለች በኋላ ጉበት መስላ ቢያያት ‹‹ምድር ዘር የሚሰጥ ሣርና ቡቃያ ውጣ›› ብሎ ከላይ
የዘረዘርናቸውን የዕለቱን ሦስት ፍጥረታት ፈጥሯል፡፡ በመቀጠልም እግዚአብሔር በገነት ውስጥ ብዙ ዕፆችን
አበቀለ ከእነሱም መካከል ዕፀ ሕይወትን በመሐል ገነት አበቀለ ይህች ዕፀ ሕይወት በጣም ረጅም ቁመት

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 34 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

ፍሬዋ ደግሞ እንደ ሮማን ፍሬ ተነባብሮ ከታች እስከ ላይ ድረስ የሞት ነበረች፡፡ ከዚችም ከዕፀ ሕይወት ስር
ማየ ሕይወት አወጣ ማየ ሕይወት ከወተት ሰባት እጥፍ ትነጻለች ከማር ከስኳር ሰባት እጥፍ ትጣፍጣለች፡፡
በዚህች ዕፀ ሕይወት በአራቱም መአዘን አራቱን ዓብይ ዕፅዋት አኖረ፡፡ ከዚያም አራቱን ዓብይ አፍላጋት
(ወንዞች) አወጣ የነዚህም ስማቸው ግዮን ፣ ኤፍራጥስ ፣ ኤፌሶንና ጤግሮስ ይባላሉ፡፡ እነዚህም ገነትን
ወዲያ እና ወዲህ እንደ መስቀል ተመላልሰው ያጠጥዋታል፡፡ ይህች እለት በእመቤታችን ትመሰላለች፡፡ ያለ
ዘር ስላፈራች እነዚህን ሁሉ ፍጥረት ስላስገኘች፡፡

የዕለተ ማክሰኞ ፍጥረታት እነዚህ ናቸው፡፡ ማክሰኞ (ስሉስ) ማለት ለፍጥረታት ሦስተኛ ለቀመር አንደኛ
ለፀሐይ ሰባተኛ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት ፍጥረታት አስራ ሁለት ደርሰዋል፡፡

2.2.5 የዕለተ ረብዕ ፍጥረታት

እግዚአብሔር በዕለተ ረቡዕ የፈጠረው ፍጥረት ብዛት ሦስት ናቸው፡፡ እነርሱም ፀሐይ ጨረቃ ከዋክብት
ናቸው፡፡ እግዚአብሔር እነዚህን ፍጥረታት ከምን ፈጠራቸው ቢሉ ፀሐይን ከእሳት እና ከነፋስ አደረገ ይህም
ይታወቅ ዘንድ በእሳትነቷ ትሞቃለች በነፋስነቷ ትሔዳለች፡፡ የተቀሩትን ደግሞ ከውሃና ከነፋስ ፈጥሯቿል
ይህም ይታወቅ ዘንድ በውሃነታቸው ይቀዘቅዛሉ በነፋስነታቸው ይሔዳሉ፡፡

ከዚህም ሌላ እግዚአብሔር በዕለተ ሰኞ በሰራው ጠፍር ላይ በሦስት ኬክሮስ በሦስት መዓረግ ዝቅ አድርጎ
በምስራቅ በኩል ጨረቃን በምዕራብ በኩል ፀሐይን ፈጥሯል፡፡ ለፀሐይ መዓልቱን (ቀኑን) ለጨረቃ ሌሊቱን
አስገዛ፡፡ ይህን ማድረጉ ለፍጥረቱ አስቦ ነው ሀያ አራቱንም ሰዓት ፀሐይ ብትገዛ ፍጥረት በሙቀት ብዛት
በቀለጠ ነበር እንደገና ሀያ አራቱንም ሰዓት ለጨረቃ ቢያስገዛት ፍጥረት በቅዝቃዜ በውርጭ ባለቀ ነበር ፤
ሁሉም ተቻችለው እንዲኖሩ አደረጋቸው፡፡ ለፀሐይና ለጨረቃ ቀንና ሌሊቱን ካስከዛ ለከዋክብትስ ምንን አስገዛ
ቢሉ አራቱን ወቅቶች ነው፡፡ እነዚህም ክረም በጋ ፀደይ መፀው ናቸው፡፡ መዝ 135፤8-9 ከዋክብት አራት
አለቆች አሏቸው እነዚህም፡-

1. ምልክኤል
2. ሕልሜልሜሊክ
3. ምልኤል
4. ናርኤል ናቸው፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 35 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

1. መፀው (ናርኤል)

ከመስከረም 26 እስከ ታህሳስ 25 ድረስ ያለው ወቅት መፀው ይባላል፡፡ በመፀው ሰልጥኖ የነበረው ቁር
ወረታች ተቀብሮ የከረመው ሙቀት ወደ ላይ ሲል ከታች ሙቀት ከላይ ዝናብ ሲመታው አዝዕርት አትክልት
ዕፅዋት ያድጋሉ ይገዝፋሉ ያብባሉ በዚህ ወቅት ደግሞ ናርኤል ይመግበዋል (ይገዛዋል)፡፡

2. ሀጋይ (ምልኤል

ከታህሳስ 26 እስከ መጋቢት 25 ድረስ ያለው ወቅት ሀጋይ ይባላል፡፡ በሀጋይ ሰልጥኖ የነበረው ብርድ ፈጽሞ
ሲጠፋ ተቀብሮ የነበረው ሙቀት ሲወጣ ከሙቀቱ ፅናት የተነሳ አዝዕርት አትክልት ይደርቃሉ ታጭደው
ተወቅተው በጎተራ ይገባሉ በዚህ ወቅት ምልኤል ይመግበዋል (ይገዛዋል)፡፡

3. ፀደይ (ምልክኤል)

ከመጋቢት 26 እስከ ሰኔ 25 ድረስ ያለው ወቅት ፀደይ ይባላል፡፡ በፀደይ ሰልጥኖ የነበረው ሙቀት ወደ ታች
ተቀብሮ የነበረው ብርድ ወደ ላይ ሲወጣ ከላይ ሙቀቱ ከታች ቅዝቃዜ ሲመታው ምድር ትረሰርሳለች፡፡
በዚህ ወቅት ደግሞ ምልክኤል ይመግበዋል (ይገዛዋል)፡፡

4. ክረምት (ህልሜልሜሌክ)

ከሰኔ 26 እስከ መስከረም 25 ድረስ ያለው ወቅት ክረምት ይባላል፡፡ በክረምት የፀሐዩ ሙቀት ይጠፋል
ከውሃው ብዛት ከምንጩ ጽናት የተነሳ ምድር ፈረስ ፈረስ ናድ ናድ ትላለች፡፡ በዚህ ወቅት ህልሜልሜሌክ
ይመግበዋል (ይገዛዋል)፡፡

እነዚህ የከዋክብት አለቆች እነዚህን ወቅቶች እንደዚህ እያደረጉ ይመግባሉ (ይገዛሉ) ግን የቀን አገዛዛቸው
እያንዳንዱን ስንቆጥር ዘጠና ቀን ነው፡፡ ከጳጉሜ አምስቱን ቀን አንድ አንድ ሲጨመርላቸው ዘጠና አንድ ቀን
ይመጣል፡፡

እነዚህ የዕለተ ረቡዕ ፍጥረታት ናቸው፡፡ ረቡዕ ማለት ለፍጥረት አራተኛ ለቀመር ሁለተኛ ለፀሐይ አንደኛ
ማለት ነው፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 36 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

2.2.6 የዕለተ ሐሙስ ፍጥረታት

እግዚአብሔር በዕለተ ሐሙስ ምን ፍጥረት ፈጠረ ቢሉ በዕለተ ሐሙስ ባህር ሕያውን (ሕይወት ያላቸው)
ፍጥረታትን (እንስሳትን) ታስገኝ ብሎ አዘዘ በዛን ጊዜ ሦስት ፍጥረታትን ባሕር አስገኘች፡፡ እነዚህም፡-

1) በእግር የሚሽከረከሩ
2) በክንፍ የሚበሩ
3) በደረት የሚሳቡ

እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት ፍጥረታት በባሕር (በውቅያኖስ) ተወስነው የሚኖሩ በደመ ነፍስ ሕያዋን የሆኑ
ፍጥረታት ናቸው፡፡ አፈጣጠራቸውም ከአራት ባሕያርተ ሥጋ ነው፡፡ በሐሙስ ፍጥረት ደመ ነፍስ የሌላት
ባህር በደመ ነፍስ ሕያዋን ሆኑ ፍጥረታት ማስገኘቷ ጌታም ፍትወት እንስሳዊት ከሌለባት ከእመቤታችን
የመገኘቱ ምሳሌ ነው፡፡

የዕለተ ሐሙስ ፍጥረታት ምሳሌነታቸው

1. ሲፈጠሩ በርረው ከውኃ ወደ የብስ የወጡ የኢጥቃንን፡፡


2. ካባህር የቀሩ የጥሙቃን፡፡
3. በባህር እና በየብስ የሚላለሱ ወደ ጽድቅና ኃጢአት የሚመላሱ ሰዎች ምሳሌ ነው፡፡

የዕለተ ሐሙስ ፍጥረታት እነዚህ ሲሆኑ ሐሙስ ማለት አምስተኛ ዕለት ማለት ነው፡፡ ለፍጥረታት
አምስተኛ ለቀመር ሦስተኛ ለፀሐይ ሁለተኛ ማለት ነው፡፡

2.2.7 የዕለተ አርብ ፍጥረታት

እግዚአብሔር በዕለተ አርብ የፈጠራቸው ፍጥረታት አራት ናቸው፡፡ በዕለተ ሐሙስ ባህርን እንዳዘዘ ሁሉ
በዕለተ አርብ ደግሞ መሬት(የብስን) ሕያዋን(ሕይወት ያላቸውን) ፍጥረታ በየወገኑ ታወጣ ዘንድ አዘዛት
መሬትም ሦስቱን ፍጥረታት በየወገኑ አስገኘች፡፡ እነርሱም፡-

1. በእግር የሚሽከረከሩ
2. በክንፍ የሚበሩ
3. በደረት የሚሳቡና

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 37 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

4. ሰው ናቸው፡፡

እግዚአብሔር እነዚህን ፍጥረታት ሲፈጥር ሴት እና ወንድ እያደረገ ፈጥሮአቸዋል፡፡ እነዚህ ከላይ


የተዘረዘሩት ፍጥረታት በዕለተ ሐሙስ ከተፈጠሩት በምን ይለያሉ ቢሉ ሐሙስ የተፈጠሩት ከባህር ነውና
ከባህር ወጥተው ፀሐይ ቢመታቸውታ ቢውሉ ቢያድሩ ይሞታሉ ያልቃሉ፡፡ እንዲሁም በዕለተ አርብ
የተፈጠሩት ደግሞ በባህር ውስጥ ገብተው ቢውሉ ቢያድሩ ቅዝቃዜ ብርድ ሲፈጃቸው ይሞታሉ፡፡
በግብራቸው (በነዚህ ባህርያቸው) ይለያያሉ ማለት ነው፡፡

በዚህ ዕለት በስተመጨረሻ በአራተኝነት እግዚአብሔር እንዲህ አለ ‹‹ኑ እንውረድ ሰውን እንደ መልካችን
እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር አለ፡፡›› ዘፍ 1፤25 ሥላሴ እስካሁን ድረስ ያሉትን ፍጥረት የፈጠሩት በዝምታ
በመናገር ነበር አሁን ግን ከሰማይ ወርደው በእጃቸው አክብረው አዳምን ፈጠሩት፡፡ አዳም የተፈጠረው
ከአራቱ ባህርያተ ሥጋ እና ከሦስቱ ባህርያተ ነፍስ ነው፡፡

አርብ ማለት ለፍጥረት ስድስተኛ ለቀመር ደግሞ ሦስተኛ ቀን ማለት ነው፡፡

2.2.8 የሰው ልጅ

ሰው ማለት ሰብ ከሚል የግዕዝ ግስ የተወሰደ ሲሆን ትርጉሙም ሰባት ማለት ነው፡፡ ሰባት የተባለበት
ምክንያት ሰው ከሰባት ነገሮች የተፈጠረ ስለሆነ ነው፡፡ እነዚህም ባህርያት ከአራቱ ባህርያተ ሥጋ ከሦስቱ
ባህርያተ ነፍስ ናቸው፡፡

አራቱ ባህርያተ ሥጋ
 መሬት
 እሳት
 ነፋስ
 ውሃ ናቸው፡፡

ሶስቱ ባህርያተ ነፍስ

 ሕያዊት
 ልባዊት
 ነባቢት

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 38 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

በአጠቃላይ ሰው ከእነዚህ የተፈጠረ ፍጡር ነው፡፡

አዳም እና ሔዋን

አዳም ማለት እጅግ የልረዘመ እጅግም ያላጠረ መካከለኛ ይህ ቀረ የማይባል መልከመልካም ማለት ነው፡፡
ሔዋን አዳም ስም ሲያወጣላት አጥንትሽ ካጥንቴ ስጋሽ ከስጋዮ ይቼ ከወንድ ተገኝታለች ስም ሴት ትባል
አላት ቆይቶ የሕያዋን ሁሉ እናት ናትና ሔዋን ትባል አላት፡፡

የሰው አፈጣጠር ከእሱ ቀደም ብለው ከተፈጠሩት ፍጥረታት ይለያል ይከብራል፡፡ ዘፍ 1፤25 ‹‹ኑ እንውረድ
ሰውን እንደመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር›› ብለው ሥላሴ ተናግረው ሰውን በመልካቸው እንደ
ምሳሌያቸው ፈጠሩ ፤ ሰው መልኩ ሥላሴን ይመስላል፡፡ በሚያዚያ 5 ቀን በዕለተ አርብ በ4 ሰዓት አዳም
ተፈጠረ፡፡ አዳም የተፈጠረበት ቦታ ኤልዳ በምትባል በማዕከላዊ ምድር ተፈጠረ፡፡ ከተፈጠረ በኋላ በአርባኛው
ቀን ወደ ኤዶም ገነት ገባ፡፡ አዳም ከተፈጠረ ከስምንት ቀን በኋላ ሔዋን ጎኑ ተፈጠረች፡፡ እግዚአብሔር
ሔዋንን ሲፈጥራት በአዳም ላይ እንቅልፍ ጥሎበት ከግራ ጎኑ አንድ አጥንት ወስዶ ነው፡፡ ሐዋን በተፈጠረች
በሰማንያኛው ቀን ወደ ኤዶም ገነት ገባች፡፡ አዳም የተፈጠረው የ30 አመት ጎልማሣ ሲሆን ሔዋን ደግሞ
ስትፈጠር የ15 አመት ቆንጆ ነበረች፡፡ አዳምና ሔዋን በኤዶም ገነት ውስጥ የኖሩት ለ7 አመት ከ3 ወር
ነው፡፡

የአዳም እና ሔዋን አወዳደቅ

አዳምና ሔዋን ወደ ገነት የገቡት አዳም በተፈጠ በ40 ቀን በመላእክት አጃቢነት ሔዋንም በተፈጠረች በ80
ቀን እንዲሁም መላእክት አጃቢነት ወደ ኤዶም ገነት ገብተው ይኖሩ ነበር፡፡ ልዑል እግዚአብሔር በኤዶም
ገነት 3 ዕፆችን አስቀምጦ ነበር፡፡ አንዱን ብላ ፣ አንዱን አትብላ ብሎት አንዱን ደግሞ ሰውሮት (ብላም
አትብላም አላለውም) ነበር፡፡ ብላ ያለው በኤደን ገነት ያሉትን ዕፅዋት ሁላ ሲሆን ፤ አትብላ ያለው ደግሞ
ዕፀ በለስን ነው ፤ ሦስተኛው ልዑል እግዚአብሔር የሰወረው ዕፀ ሕይወትን ነው አዳም አትብላ ያለውን ዕፅ
ሳይበላ ትዕዛዙን ጠብቆ ቢሆን ኖሮ ከዕፀ ሕይወት በልቶ ታድሶ ኢየሩሳሌም በገባ ነበር፡፡ ልዑል እግዚአብሔር
አዳምን ዕፀ በለስን አትብላ ያለው የእርሱን ገዢነት የነርሱን ተገዢነት ለማሳወቅ ነው፡፡

እግዚአብሔር አምላክ አዳምን የአራዊት ሁሉ ጌታ አድርጎ ሹሞት ነበር፡፡ እንዲህም ሆኖ ተሳስበው ከአዳም
ዘንድ እየመጡ ይባረኩ ነበር፡፡ እርሱም ለእያንዳንዳቸ ስም ያወጣላቸው ነበር፡፡

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 39 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

ከዕለታት አንድ ቀን እንስሳት አራዊት ሁሉ እንደልማዳቸው ተሰብስበው ሔደው አርደህ ብላን አልበህ ጠጣን
አሉት ፤ እርሱም ምን አጥቼ ጌታዬ ሁሉን ብላ ሁሉን ጠጣ ብሎ ሰጥቶኛል ካንድ ዕፅ በስተቀር የከለከለኝ
የለም፡፡ እናንተስ ባላችሁበት ያብዛችሁ ያርባችሁ ብሎ አሰናበታቸው፡፡ ዲያብሎስም ከመንገድ ጠብቆ
የትደርሠው እንደመጡ ጠየቃቸው እነርሱም ከጌታቸው ከአዳም ዘንድ እንደ ሆነ ነገሩት፡፡ እርሱም እንዴት
ነው አላቸው እነርሱም ነገሩት፡፡ እግዚአብሔር በገነት ያሉትን ነገሮች እንዲመገብ እፀ በለስን እንዳይበላና
እርሱን ከበላ የሞት ሞትን እንደሚሞት ነግሮታል አሉት፡፡ ዲያቢሎስ ይህን ሲሠማ አዳምን የሚያስትበትን
መንገድ መፈለግ ጀመረ ያን ጊዜ እባብ እየተቻኮለች መጣች እርሱ ባለበት መንገድም ስታልፍ ዲያቢሎስ
ወዴት እንደምትሄድ ጠየቃት እርሷም ጌታዬ አዳም ዘንድ ነው የምሄደው አለችው፡፡ ዲያቢሎስም እባብን
አብሬሽ ልሂድ አላት በዛን ጊዜ እባብ ፈቀደችለት አብረውም ሲሄዱ ዲያቢሎስ እንዲህ አላት ‹‹እባብን እስከ
ገነት ተራራ ድረስ ልዘልሽ አንቺ ደግሞ ከዚያ በኋላ ታዝይኛለሽ›› ብሎ አዘላት በዛን ጊዜ ዲያቢሎስ እባብን
አዝላ ጉዞ ጀመሩ፡፡ ከገነት ተራራ ከታች ሲደርሱ በይ በተራሽ እዘይኝ ብሎ ከገነት በር ሲደርሱ ውረድ ባለች
ጊዜ እንደ ቅቤ ቀልጦ በሰውነቷ ተዋሃዳት፡፡

ተዋሃዳት የሚለው

ዲያቢሎስ ቀደም ብሎ እባብን ሲያናግራ አልተስማሙም ነበር እርሷ መልከመልካም አቋም እንደ ግመል
አይነት ነበረች እርሱ ደግሞ መልከ ጥፉ ነበር፡፡ በተነጋገሩ ሰዓት ምን ይላት ነበር እዘይኝ እና እርሱ ዘንድ
ስንቀርብን የኔ ንግግር ያንቺ ደግሞ መልክ ይሻላል ሲላት ነበር ፤ ያን ነውን በስተመጨረሻ ተግባራዊ
ያደረገው፡፡

 ከዚያም በኋላ ዲያቢሎስ ከእባብ ተዋህዶ ወደ አዳም ቀረቡ፡፡ አዳምንም አዳም ሆይ የሠማይ የምድር ገዢ
ባለው ጊዜ አዳም ተቆጣው እኔ የምድር እንጂ የሠማይ ገዢ አይደለሁም አለው፡፡ ያን ጊዜ ዲያቢሎስ አዳም
ነገሩን አዳም እንዳልተቀበለው ባወቀ ጊዜ ዲያቢሎስ አዳምን ጠየቀው አጋርህ ሔዋን ወዴት ናት አለው፡፡ እዛ
አለችልህ ብሎ አሳየው ያን ጊዜ ዲያቢሎስ ወደ ሔዋን ሲሄድ ሔዋን ሆይ የሰማይና የምድር ንግስት አላት
ያን ጊዜ ሔዋን በሐሴት ተዋጠች ፤ ነገሩን እንደተቀበለችው አውቆ ለይቼ የጠየቅኋት እንደሆነ
ታውቅብኛለች ብሎ በገነት ካለው ዕፅ ሁሉ አትብሉ ያላችሁ ለምን ነው አላት፡፡ እሷም አረ በገነት ያሉትን
ሁሉ ዕፅ እንበላለን ነገር ግን ዕፀ በለስን እንዳንበላ አዞናል አለችው፡፡ ያን ጊዜ ዲያቢሎስ እንዴት አላት፡፡
እርሱን በበላችሁ ጊዜ የሞት ሞት ትሞታላችሁ ብሎናል አለችው፡፡ ዲያቢሎስም እናንተ ሞኝ ምግብ ከመቼ

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 40 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

ጀምሮ ነው የሚገለው ብትበሉ እኮ እንደርሱ አምላክ ትሆናላችሁ ለዛ ነው አላት ፤ ግን ስትበሉ እኩል


መጌጉረስ አለባችሁ አላት፡፡
 ከዚያን በኋላ ሔዋን በለሱን ቆርጣ አዳም በመጣ ጊዜ ይህን የበላን እንደሆነ አምላክ እንሆናለን አለችሁ፡፡
አዳም ግን ይህን በበላችሁ ጊዜ የሞት ሞት ትሞታላችሁ ብሎን የለም የጌታችን ትእዛዝ ማፍረስ ይሆንብን
የለምን አላት፡፡ አሁን ከዚህ ብንበላ የሞት ሞት ሆኖ ነው ይልቅስ እንብላ ብላ ወተወተችው ከዚያ በግራ
እጅዋ ለእርሷ በቀኝ እጅዋ ለርሱ በአንድላይ በሉት፡፡ በዚህን ጊዜ ለብሰውት የነበረ የብርሃን ልብሳቸው
ተገፈፈ፡፡ በዚያን ጊዜ አይናቸው ተከፈተ እርስ በእርስ እርቃናቸውን ስለሆኑ ተፈራርተው ተደበቁ፡፡
ከዚያ በኋላ ልዑል እግዚአብሔር አዳምን ይጎበኘው ዘንድ በመጣ ሰዓት ከቦታው አጣው አዳም አዳም ብሎ
በጠራው ሰዓት አቤት እዚህ ነኝ አለው ልዑል እግዚአብሔርም አዳም ተደብቆ ስለነበር አትብላ ያልኩህን ዕፅ
በላህ እንዴት አለው፡፡ አዳምም አዎን ይህቺ እረዳት ትሁንህ ብለህ የሠጠኸኝ ሴት አሣሣተችን አለው፡፡
የዚያን ጊዜ ሔዋንም ይህች እባብ አሣተችኝ አለች፡፡ ልዑል እግዚአብሔርም ከዚያም በአዳም ላይ ትንቢትን
ተናገረ አዳም ክፉና ደጉን ሊያውቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ አለ፡፡ ዘፍ 3፤22፡፡ ከዚያም በኋላ ከእባብ ጀምሮ
እርግማንን ጀመረ፡፡

 እባብንም፡- አንቺ በደረትሽ የምትሣቢ ሁኚ ፤ በአንተና በሴቲቱ መካከል ፀብን አደርጋለሁ፡፡ ከእርሷ
የሚወለደው አንተን አናት አናትህን ይበልህ ፤ አንተም ሽኮና ሽኮናውን ትላለህ አለው፡፡ ዘፍ 3፤15
 በሔዋን ላይ፡- አንቺ በለሲቱን እንዳደማሽ ያንቺም ደም ይፈሳል ከባልሽ በታች ሁኝ ባልሽ ይግዛሽ፡፡ ዛሬ
በየወሩ ሴቶች የሚፈሳቸው የወር አበባ ኋላም አርግዘው በጭንቀት ወልደው እንደገና ህመማቸውን ረስተው
ወደ ቦታቸው መመለሳቸው ከዚያ የተነሳ ነው፡፡ ዘፍ 3፤16
 አዳም፡- አንተ ሚስትህን እንደሰማህ ዘወትር ከእርሷ ትዕዛዝ አትውጣ ምድር እሾህ አሜኬላ ታብቅል ብሎ
ረገመው፡፡ የሞት ሞትን ትቀምሳለህ አለው፡፡ ዘፍ 3፤17

ከዚያም በኋላ ልዑል እግዚአብሔር አዳም እና ሔዋንን የቆዳ ልብስ አልብሶ ከገነት አስወጣቸው፡፡ ገነትንም
በኪሩቤል መላዕክ ጠባቂ አስቆመለት፡፡ አዳምንም ከገነት በስተምስራቅ በደብረ ቅዱስ በተባለ ተራራ
አስቀመጠው፡፡ ከዚያም አዳምንም አምላኩ ይቅር ይለው ዘንድ ሱባኤ ያዘ የዚያን ጊዜ የያዘው ሱባኤ 41 ቀን
ነበር በ38ኛ ቀን ዲያቢሎስ በመላዕክት ተመስሎ አዳምን ፀሎትህ ተሰምቶአልና ተከትለኸኝ ወደ ገነት
ትገባለህ አለው፡፡ አዳም የሱባኤው ቀን ስላልተገባደደ ተጠራጠረው ያን ጊዜ ዲያቢሎስ እንዳወቀ ገብቶ
አዳምን ደሞ አንተ አትሰማም ብሎ ወደ ሔዋን ሄደ ሔዋን ጸሎታችሁ ተሠምቷል ኑ እንሒድ ባላት ሰዓት

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 41 ትምህርት ክፍል


ትምህርተ ሃይማኖት

ከሱባኤው ወጣች ያን ጊዜ አዳም በጣም አዘነ መላዕኩ ገብርኤል ከዚህ በፊት እንዳትለያት ብሎት ነበርና
ዲያብሎስን ተከትለው ወደ ገነት ጉዞ ጀመሩ ያን ጊዜ ገነት በር ላይ በደረሱ ጊዜ ዲያቢሎስ ማንነቱን
ገለጠላቸው ወዲያው ድንጋይ አንስቶ አዳምን ፈነከተው አዳምም አለቀሰ ከዚያም በኋላ ዕለት ዕለት
የሚመገበው በገነት ያሉ አዋፋት የሚያመጡለት ፍራፍሬ ነበር፡፡ ያንን ፍራፍሬ ተፈንክቶ ከፈሰሰው ደም
ጋር ለወሰ መስዋትንም አቀረበ፡፡ ያን ጊዜ ልዑል እግዚአብሔር ለአዳም ቃል ኪዳን ገባለት ከአምስት ቀን
በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሀለው አለው፡፡ ነገር ግን ድጋሚ ያንተን ደም መስዋዕት አድርገህ አታቅርብ
እንሠሣትን በመስዋትነት እንዲያቀርብ ነገረው፡፡

የመለማመጃ ጥያቄዎች

1. ሥነ ፍጥረት ማለት ምን ማለት ነው)


2. ልዑል እግዚአብሔር ፍጥረታትን ስለምን ፈጠረ)
3. ፍጥረታት ከፈጣሪ በምን ይለያሉ)
4. ልዑል እግኢብሔር ፍጥረታትን በስንት መንገድ ፈጠረ በዝርዝር ጻፉ)
5. ልዑል እግዚአብሔር ፍጥረታትን የፈጠረበትን ዓላማ በዝርዝር ጻፉ)
6. በእለተ እሁድ የተፈጠሩ ፍጥረታትን ዘርዝሩ
7. በእለተ ሰኞ የተፈጠሩ ፍጥረታትን ዘርዝሩ
8. በእለተ ማክሰኞ የተፈጠሩ ፍጥረታትን ዘርዝሩ
9. በእለተ ረብዕ የተፈጠሩ ፍጥረታትን ዘርዝሩ
10. በእለተ ሐሙስ የተፈጠሩ ፍጥረታትን ዘርዝሩ
11. በእለተ አርብ የተፈጠሩ ፍጥረታትን ዘርዝሩ
12. አዳምና ሔዋን በየት ተፈጠሩ)
13. አዳምና ሔዋን በተፈጠሩ በስንተኛው ቀን ወደ ኤደን ገነት ገቡ)
14. ለአዳምና ሔዋን ለውድቀታቸው ምክንያቱ ምን ነበር)
15. እግዚአብሔር አምላክ አዳምንና ሔዋንን ምን ብሎ ረገማቸው)

የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት ገፅ 42 ትምህርት ክፍል

You might also like