Professional Documents
Culture Documents
Fikad Asetat
Fikad Asetat
አቀራረብ መመሪያ/የተሻሻለው
ይደረጋል፡፡
3.1.2 ከላይ በተራ ቁጥር 3.1.1 የተጠቀሰው ቢኖርም በዚህ
መመሪያ ክፍል ሁለት አንቀጽ 2.4 ንዑስ አንቀጽ 2.4.2
መሠረት ወደ 3ኛ በጀት ዓመት የተዛወረውን የአንድ ዓመት
እረፍት ፈቃድ ሙሉ በሙሉ በገንዘብ ተለውጦ እንዲሰጠው
የመጠየቅ መብት ያለው ሲሆን አሰሪው መ/ቤቱም
የሠራተኛውን የዓመት እረፍት ፈቃድ ጥያቄውን ተቀብሎ
ማስተናገድ ይኖርበታል፡፡
በስራ ጫና ምክንያትም ወደ 3ኛው የበጀት ዓመት
የተዛወረውን የአንድ ዓመት የዓመት እረፍት
ፈቃድ በገንዘብ ተለውጦ የሚሰጠው ይሆናል ፡፡
ሆኖም ግን ከስራ ጫና ውጭ ወደ 3ኛው የበጀት
ዓመቱ የተዛወረ የዓመት ዕረፍት ፈቃድ ወደ
ገንዘብ ተቀይሮ እንዲሰጥ አይደረግም፡፡
3.1.3 አገልግሎቱ የተቋረጠ የመንግስት ሠራተኛ የዓመት
እረፍት ፈቃዱ ለአንድ ወይም ለሁለት ተከታታይ የበጀት ዓመት
በመንግሥት ሥራ ምክንያት በመ/ቤቱ የበላይ ኃላፊ ወደ
ሁለተኛው ወይም ሶስተኛ የበጀት ዓመት የተላለፈ ከሆነ
የዓመት እረፍት ፈቃዱ ሙሉ በሙሉ በገንዘብ ተቀይሮ ለራሱ
ወይም ለተተኪዎች እንዲሰጥ ይደረጋል፡፡ ሆኖም ሥራውን በገዛ
ፈቃዱ ለቆ ወደ ሌላ የሲቪል ሰርቪስ መ/ቤት የተቀጠረ
ሠራተኛ
ከሆነ ግን ፈቃዱን በገንዘብ ተቀይሮ የሚሰጠው የዓመት እረፍት ፈቃድ
ጉዳዮች፡-
4.2.1 ሕክምናውን የሰጠው ተቋም የራስጌና የግርጌ
ማህተም ማድረግ፣
4.2.2 የታካሚው ስም ከነአያቱ ፣ለሕክምና የቀረበበት ቀን የተደረገ
የሕክምና ዓይነት፣ የተሰጠ የሕክምና ፈቃድ ካለ በፊደልና በአሃዝ
ይገለፃል፡፡
4.2.3 የህክምና ማስረጃው በህክምና ተቋሙ የበላይ ኃላፊ ወይም
ህክምናውን በሰጠው ባለሙያ የተፈረመ መሆን ይኖርበታል፡፡
4.2.4 የማስረጃው የፕሮቶኮል ቁጥርና ቀን የተሟላ ሊሆን ይገባል፣
4.2.5 የሕክምና ማስረጃው ስርዝ ድልዝ የሌለበት መሆን አለበት፡
ክፍል አምስት
የሕመም ፈቃድ
5.1 የሕመም ፈቃድ
5.1.1 ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ በሕመም ምክንያት ሥራ
መሥራት ያልቻለ እንደሆነ ደመወዝ የሚከፈልበት የሕመም ፈቃድ
ይሰጠዋል፡፡
1. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) መሠረት የሙከራ ጊዜውን ላጠናቀቀ
የመንግሥት ሠራተኛ የሚሰጥ የሕመም ፈቃድ በተከታታይ ወይም በተለያየ ጊዜ
ቢወስድም ሕመሙ ከደረሰበት የመጀመሪያ ቀን አንስቶ ባለው አስራ ሁለት ወር
ጊዜ ውስጥ ከስምንት ወር ወይም በአራት ዓመት ውስጥ ከአሥራ ሁለት ወር
አይበልጥም፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) መሠረት የሚሰጥ የሕመም ፈቃድ
ለመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ከሙሉ ደመወዝ ጋር እና ለሚቀጥሉት
ሁለት ወራት ከግማሽ ደመወዝ ጋር ይሆናል፡፡
3. በንዑስ ቁጥር /2/ ሥር የተገለፀው ቢኖርም የኢች. አይ.ቪ/ኤድስ
ህሙማን የሆኑ ሠራተኞች ለ8 ወራት ሙሉ ደመወዝና ለቀሪዎች
አራት ወራት ደግሞ ግማሽ ደመወዝ እንዲከፈላቸው ይደረጋል፣
4. የሙከራ ጊዜውን ያላጠናቀቀ የመንግሥት ሠራተኛ ከታመመ የህክምና
ማስረጃ የሚቀርብበት የአንድ ወር የሕመም ፈቃድ ከደመወዝ ጋር
ይሰጠዋል፡፡
5. ማንኛውም የመንግሥት ሠራተኛ ሲታመም፣
ሀ) ከአቅም በላይ የሆነ ምክንያት ካላጋጠመው በስተቀር
በተቻለ ፍጥነት መታመሙን ለመሥሪያ ቤቱ ማሳወቅ
አለበት፣
ለ) በተከታታይ ከሦስት ቀናት ወይም በአንድ የበጀት ዓመት
ውስጥ ከስድስት ቀናት በላይ በሕመሙ ምክንያት ከሥራ
የቀረ እንደሆነ ለመታመሙ የሕክምና ማስረጃ ማቅረብ
አለበት፡፡
6. የሙከራ ጊዜውን ያጠናቀቀ የመንግስት ሠራተኛ በዓመት
ፈቃድ ላይ እያለ መታመሙን የሚያረጋግጥ የህክምና ማስረጃ
ካቀረበ የዓመት ፈቃዱ ተቋርጦ የሕመም ፈቃድ ይሰጠዋል፡፡
7. በንዑስ ቁጥር (6) መሠረት የተቋረጠው የዓመት ፈቃድ
የሕመም ፈቃዱ እንደተጠናቀቀ እንዲቀጥል ይደረጋል፡፡
ክፍል ስድስት
ልዩ ልዩ ጉዳዮች
6.1 የህክምና ማስረጃ ተቀባይነት ሊኖረው የሚችለው
በቅድሚያ የመንግስት ሰራተኛው በሚሰራበት የስራ ቦታ
አቅራቢያ ከሚገኝ የመንግስት የህክምና ተቋም ሪፈር
ተደርጎ ወደ መንግስት ከፍተኛ የህክምና ተቋም ህክምና
አገልግሎት
6.2 በዚህ መመሪያ ውስጥ ያልተካተቱ ፈቃዶች
በመንግሥት መ/ቤቶች ተቀባይነት አይኖራቸውም፡፡
6.3 የጤና ባለሙያዎች ለሚሰጧቸው የህክምና ፈቃድ
ማስረጃዎች በጋራም ሆነ በተናጠል ተጠያቂነት አለባቸው፣
6.4 ከሙያው ሥነ-ምግባር ውጭ ተገቢ ያልሆነ የህክምና
ማስረጃ መስጠት ተጠያቂ ያደርጋል፡፡
6.5 የመንግሥት መ/ቤቶች የሚቀርቡላቸውን የህክምና
ማስረጃዎች ትክክለኛነት የማጣራት ኃላፊነት አለባቸው፡፡
6.6 የሚሰጠው የሕክምና ፈቃድ ተከታታይና ቅዳሜና እሁድን
እንዲሁም ሌሎች የበዓላት ቀናትን ያካትታል፡፡
6.7 ታካሚዎች የሚያቀርቡት የህክምና ማስረጃ የሰራተኛው
የቅርብ ሀላፊ ካየው በኋላ በክልል በሰው ኃብት አስተዳደር
ዳይሮክተሬት በሜትሮፖሊታን ከተሞች፣በዞን፣ በወረዳ፣ በመካከለኛ
ከተማ በአንስተኛ ከተማ፣ በክ/ከተማና በሌሎች ከተማ
አስተዳደሮች ደግሞ በሰው ኃብት አስተዳደር ሠራተኞች
አማካኝነት ተረጋግጦ ከሠራተኛው የግል ማህደር እንዲቀመጥ
ይደረጋል፡፡
6.8 በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር
253/2010 አንቀጽ 96 ንዑስ አንቀጽ 2 መሠረት ይህን
መመሪያ የመለወጥ፣ የማሻሻል ወይም በሥራ ላይ በሚውልበት
ጊዜ ማብራሪያ ወይም ትርጉም የመስጠት ኃላፊነት የሲቪል
ሰርቪስ ኮሚሽን ነው፡
6.9 በሰኔ ወር 2011 ዓ/ም ወጥቶ በሥራ ላይ የነበረው የፈቃድ
አሰጣጥና ማስረጃ አቀራረብ መመሪያና ይህንን አስመልክቶ
የተላለፉ ሰርኩላሮች በዚህ መመሪያ ተተክተዋል፡፡
6.10 ይህን መመሪያ በተዛባ መልኩ ወይም ያለአግባብ
የሚያስፈጽም ማንኛውም አካል ወይም የስራ ኃላፊ አግባብ
ባለው ህግ ተጠያቂ ይሆናል
6.11 በዚህ መመሪያ አሰራር ላይ የሚኖር ቅሬታ በስራ ላይ
ባለው የቅሬታአቀራረብ ሥርዓት መሰረት ተፈፃሚ
ይሆናል::
6.12 ይህ መመሪያ ከፀደቀበት ህዳር/ 2013 ዓ/ም ጀምሮ
የፀና ነው፡
ሙሉቀን አየሁ
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን
ኮሚሽነር
ህዳር/2013ዓ.ም
ባህር ዳር
ተቀጽላ-1
የሠራተኞች የዓመት ፈቃድ መጠየቂያ ቅጽ፣
ሀ/ ፈቃድ ጠያቂ፣
ስም የአገልግሎት ዘመን ቀደምሲል
ለመ/ቤቱ ባቀረብኩት የዓመት እረፍት ፈቃድ መውጫ
ፕሮግራም መሠረት ከ ዓ.ም የዓመት እረፍት ፈቃዴ ከ
ዓ/ም እስከ ዓ.ም ድረስ ለ-------ቀናት
የሙሉ ቀን/የግማሽ ቀን ፈቃድ እንዲሰጠኝ እጠይቃለሁ፡፡
ለስራ ብፈለግ በ-------------------
ከተማ------------------------- ቀበሌ
----------------------- ስልክ ቁጥር አድራሻ
የምገኝ መሆኔን እገልፃለሁ፡፡
የጠያቂው ፊርማ ቀን
ለ/ ፈቃድ ሰጪ
ሠራተኛው ያቀረቡት የዓመት እረፍት ፈቃድ ጥያቄ አስቀድመው
ባሣወቁት ፕሮግራም መሠረት ስለሆነ ከ ቀን ዓ.ም
ጀምሮ የ ቀን የዓመት እረፍት የሙሉ ቀን/የግማሽ ቀን
ፈቃዳቸው እንዲሰጣቸው ተስማምቻለሁ፡፡
የቅርብ ኃላፊ /ሂደት መሪ/አስተባባሪ ስም ፊርማ
ቀን
ሐ/ ሠራተኛው ያቀረቡት የዓመት እረፍት ፈቃድ ጥያቄ
አስቀድመው ባሣወቁት ፕሮግራም መሠረት ቢሆንም የሥራ
ሂደቱ ካለበት ወቅታዊና አስቸኳይ ሥራ አኳያ የዓመት እረፍት
ፍቃዳቸውን መጠቀም ስለማይችሉ በዚህ የበጀት ዓመት
ወደ-----------------
ወር/----------------ዓ.ም እንዲዛወርላቸው
ወስኛለሁ፡፡
የቅርብ ኃላፊ /ሂደት መሪ/አስተባባሪ ስም ፊርማ
ቀን
መ/ ሠራተኛው ያቀረቡት የዓመት እረፍት ፈቃድ ጥያቄ
አስቀድመው ባሣወቁት ፕሮግራም መሠረት ቢሆንም የሥራ
ክፍሉ ካለበት ወቅታዊና አስቸኳይ ሥራ አኳያ የዓመት እረፍት
ፍቃዳቸውን መጠቀም ስለማይችሉ ወደ ሚቀጥለው የበጀት
አመት ቢዛወርላቸው የሚል የውሳኔ አስተያየት አለኝ፡፡
የቅርብ ኃላፊ/ሂደት መሪ/አስተባባሪ ስም ፊርማ
ቀን
ሠ/ የሠራተኛው የዓመት እረፍተ ፈቃድ መውጫ ጊዜ
ወደሚቀጥለው የበጀት ዓመት እንዲራዘም ወስኛለሁ፡፡
የመ/ቤት ኃላፊ/ም/ኃላፊ/ ተወካይ ስም ፊርማ
ቀን
ረ/ በሰው ኃብት ልማት ሥራ አመራር ደጋፊ የሥራ ሂደት
የሚሞላ
ሠራተኛው አስቀድመው ባሳወቁት ፕሮግራም መሠረት
ያቀረቡት ጥያቄ ስለሆነ ከ እስከ ዓ.ም ጀምሮ ከ
ዓ.ም ፈቃዳቸው ቀን------- የተሰጣቸው ሲሆን
ፈቃዳቸውን እንደጨረሱ
በ-------------------------------ቀን
--------------------- ዓ.ም በምድብ የስራ
ቦታቸው ላይ ይገኛሉ፡፡
ጠቅላላ ያላቸው የዓመት ፈቃድ የተወሰደ
ቀሪ
የ201
የ201
የ2ዐ1
ጠቅላላ ያላቸው መሆኑን
እንገልፃለን፡፡
ያዘጋጀው የ/ሀ/ል/ስ/አ/ ደጋፊ ሥራ ሂደት ባለሙያ ስም ፊርማ
ተቀጽላ-2
ቁጥር
---------------------
ቀን
--------------------------
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
የ ቢሮ/ኮሚሽን/ጽ/ቤት/ኤጀንሲ/ባለስልጣን/መምሪያ
የሠራተኞች የዓመት እረፍት ፈቃድ መውጫ ፕሮግራም ማሻሻያ ቅጽ
እኔ አቶ/ወ/ሮ/ወ/ሪት የተባልኩ የዚሁ መ/ቤት ባልደረባ
ሀ/በ
ምክንያት ቀደም ሲል ባቀረብኩት ፕሮግም መሠረት የዓመት
እረፍት ፈቃዴን መጠቀም ስላልቻልኩ በዚሁ በጀት ዓመትከ
ቀን ዓ.ም ጀምሮ መጠቀም እንድችል የፕሮግራም
ሽግሽግ እንዲደረግልኝ እጠይቃለሁ፡፡
የሠራተኛው/ዋ/ ስም ፊርማ ቀን
ለ/ ያቀረቡትን ችግር ከግምት ውስጥ በማስገባት የዓመት
እረፍት ፈቃድ መውጫ ፕሮግራም ማሻሻያውን ተቀብየዋለሁ፡፡
የቅ/ኃላፊ/የስ/ሂ መሪ/አስተባባሪ ስም ፊርማ
ቀን
ሐ/ በ
የቅርብ ኃላፊ/የስ/ሂ/መሪ/አስ/
ስም ……………….
ፊርማ ……………………..
ቀን ……………………..
የሰው ኃብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት/ቡድን
ስም…………………………………..
ፊርማ …………………………..
ቀን ………………………..
አመሰግናለሁ!!