Criminal Power Point

You might also like

Download as pptx, pdf, or txt
Download as pptx, pdf, or txt
You are on page 1of 45

እ”"D” ÅI“ S׋G<

መግቢያ
 መንግሥት የህብረተሰብን ሠላምና ፀጥታ እንዲሁም የግለሰብን መብትና
ነፃነት የማስከበር ሃላፊነት አለው፡፡ ይሄንን ሃላፊነት ህገ መንግስቱ
በሚፈቅደው እና በሚያዘው መሠረት ተገባራዊ ለማድረግ አስፈላጊ
እርምጃዎችን ይወስዳል፡፡ ከእነዚህ እርምጃዎች አንዱ የወንጀል ህግ
መደንገግ እና ይህንን ህግ የተላለፉ ሰዎች ወደ ህግ ማቅረብ ይጨምራል፡፡
 የወንጀል ህጉ ዓላማና ግብ በሕገ መንግስቱ ላይ የደነገጉትን የሰብአዊና
ዲሞክራሲያዊ መብቶች በማስከበር ዙሪያ ከፍተኛ ሚና አለው እያንዳንዱ
ዜጋ ወይም የመንግስት አካል በህገ መንግስቱ ላይ የተጣለውን ግዴታ
ካልተወጣ እና ከጣሰ የወንጀል ህጉ አስፈላጊውን ምላሽ ይሰጣል፡፡
 በወንጀል ህግ ድንጋጌዎች ንፁህ ግለሰቦች ሣይጐዱ የመንግስትና የህዝብ
ጥቅም ሣይስተጓገሎል ጥፋተኞች እንዲቀጡና ከጥፋታቸው እንዲማሩ
ማድረግ የመንግስት ሃላፊነት ነው፡፡
የወንጀል ህግ አላማ
 ለጥቅላላው ጥቅም ሲባል የአገሪቱን መንግስት፤ህዝቦቹን፤ ነዋሪዎቹን
ሰላም፤ ደህነነት፤ሥርዓት፤መብትና ጥቅም መተበቅና ማረጋገጥ ነው፡፡
(የወንጀል ሕግ አንቀፅ 1)
የወንጀል ሕግ ግብ

የወንጀል ሕግ ግብ

የሰዎችን እና ንበረታቸውን መከላከል/


ደህነነት
መቅጣት/ ማስተማር/
መጠበቅ/protection/ deterrence/ punishment/ rehabilitation/
የወንጀል ሕግ ከፍትሐብሔር ሕግ የሚለይባቸው
ነገሮች
ወንጀል ፍትሐብሔር
ቅጣት እስራት፤ የግዴታ ካሳ/ገንዘብ/ ቅጣቶች
ስራ፤የገንዘብ መቀጮ
ተከራካሪ ወገኖች መንግስ/የህዝብ ጥቅም መንግስት እና ግለሰብ ወይም
ወክሎ/ እና ግለሰቦች በሁለት ግለሰቦች መካከል
ማስረጃ ምዘና ያለጥርጥር ጥፋተኝነት የተሻለ ማስረጃ ማለትም 50 +1
መረጋገጥ አለበት/Beyond
reasonable doubt/
የወንጀል ትርጉም

ወንጀል ምንድነው ? ፤

የተሻሻለውን የኢፌዲሪ ወንጀል ህግ አዋጅ ቁጥር 414/97 አንቀፅ 23 (1)

የሚከተለውን ተደንግጎ ይገኛል ፡

“ሕገ-ወጥነቱና አስቀጪነቱ በህግ የተደነገገውን ድርጊት መፈጸም ወንጀል ነው”


ድርጊት ( ACT ) ምንድን ነው ?
 ድርጊት ማለት ፡-
 አድርግ የተባለውን ነገር አለማድረግ / omission /
 ሕግ እንድታደርግ ወይም እንድትፈፅም የሚያስገድድህን ድርጊት አለመፈፀም
ማለት ነው ፡፡ለምሳሌ፡-
 ወንጀልን ለመፈፀም የተደረገውን መሰናዳት ወይም ሙከራ ፣ፍፃሜን ያገኘ ወንጀል አለማሳወቅ አንቀፅ 39.
 በሞት ወይም በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት የሚያስቀጣ ወንጀል መፈፀሙን/የወንጀለኛውን ለሚመለከተው አለማሳወቅ አንቀፅ

443.
 ምስክርነት ተጠርቶ አለመቅረብ አንቀፅ 448
 በአደጋ ላይ የሚገኝ ሰውን አለመርዳት አንቀፅ 575.

 አታድርግ የተባለውን ነገር ማድረግ / commission /


 በሕግ እንዳታደርግ ወይም እንዳትፈፅም የሚከለክለውን ድርጊት መፈፀም
ወይም ማደረግ ማለት ነው፡፡
ወንጀል ተፈፅሟል ለማለት መሟላት ያለባቸው መሰረታዊ ሁኔታዎች
 የኢፌዲሪ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ አንቀፅ 23(2) እንደሚያስቀምጠው አንድ ወንጀል ተፈፅሟል የሚባለው
ወንጀሉን የሚያቀቁሙት 3 መሰረታዊ ነገሮች ተሟልተው ሲገኙ ብቻ ነው ፡፡ እነዚህም፡-

ወንጀል

ሕጋዊ ፍሬ ነገር ግዙፋዊ ፍሬ ነገር


ሞራላዊ ፍሬ ነገር

ቀጥታ ሀሳብ

ተዘዋዋሪ ሀሳብ

ከባድ ቸልተኝነት

ቀላል ቸልተኝነት
1. ህጋዊ ፍሬ ነገር [ Legal element ]
ህጋዊ ፍሬ ነገር ማለት አንድን ድርጊት ወንጀል ነው ለማለት በመጀመሪያ ደረጃ
ድርጊቱ እንዳይፈፀም ያስቀጣል ወይም ያስጠይቃል ወይም ይሄ ድርጊት ወንጀል
ነው የሚል የተፃፈ ወይም የተደነገገ ድርጊት ወይም የተፃፈ ህግ ሲኖር ነው ፡፡

2. ግዙፋዊ ፍሬ ነገር [material element /act]


በወንጀል ህግ አንድ ድርጊት በህግ ያስጠይቃል የተባለው ድርጊት በህግ መደንገጉ
ብቻ በሕግ አያስጠይቅም ፤ ያ ያስጠይቃል የተባለውን ድርጊት በተግባር መፈፀም
አለበት ወይም ተፈፅሞ ሲገኝ ነው ፡፡
3. ሞራላዊ ፍሬ ነገር ( moral element )
 ሞራላዊ ፍሬ ነገር የሚያሳያው ወንጀሉ ሲፈፀም የወንጀል ፈፃሚው
ፍላጎት እና አስተሳሰብ ምን እንደነበረ የሚያሳይ ፍሬ ነገር ነው ፡፡
ማለትም ድርጊቱን የፈፀመው ስው አስቦና አውቆ ነው ወይስ ሳያስብ
ወይም ከአቅም በላይ በሆነ ሁኔታ ወይም በቸልተኝነት ነው ድርጊቱን
የፈፀመው ብሎ የሚያረጋግጥልን ፍሬ ነገር ነው ፡፡
 በመሆኑም ሞራላዊ ፍሬ ነገር በሚከተሉት 4 መገለጫዎች ሊረጋገጥ
ወይም ሊፈፀም ይችላል ፡፡ እነሱም፡-
ሀ. በቀጥታ ሀሳብ [ Direct intention )
 አድራጊው ሰው ድርጊቱን የሚያመጣውን ውጤት አውቆ እና ፍልጎ
የሚያስቀጣን ድርጊት በራሱ ፍላጎት ሲሰራ ወይም ሲፈፅም::
ለ. በተዘዋዋሪ ሀሳብ [ Indirect intention ]
 ድርጊቱን ህገ ወጥና ሊያስቀጣ የሚችል ውጤት ሊያስከትል
እንደሚችል እያወቀ ፤ይሁንና የሆነ ይሁን ብሎ ድርጊቱን የፈፀመ
ከሆነ::
ለምሳሌ፡- X በቀጠሮ ሰዓት ለመድረስ ከፍጥነት ገደብ በላይ በእግረኞች
የሚጨናነቅ መንገድ መሆኑንና እግረኛ ሊገጭ እንደሚችል እያወቀ ከነዳ
በዚህ መሀል እግረኛ ቢገጭ በተዘዋዋሪ (Indirect intention )
የነበረው መሆኑን ያሳያል፡፡
ሐ. ከባድ ቸልተኝነት( gross negligence )
 ድርጊቱ ሊያመጣ የሚችለውን ውጤት እያወቀ አይድርስም በሚል
ግምት ወይም ባለማመዛዘን የሰራ እንደሆነ በከባድ ቸለልተኝነት
ያስጠይቃል ፡፡

ለምሳሌ፡- A መኪና እየነዳ አብሮት ያለው B በጣም እየፈጠንክ ነው


ቀስ ብለህ ንዳ ሲለው A አይዞህ እኔ እኮ ጎበዝ ሹፌር ነኝ አያሳስብህ
ብሎት ሲጓዙ ሰው ቢገጩ A በከባድ ቸልተኝነት ይጠየቃል::
መ. ቀላል ቸልተኝነት ( simple negligence )
 ድርጊቱ በወንጀል የሚያስቀጣ ውጤት ሊያስከትል እንደሚችል ማወቅ
እያለበት ወይም እየተቻለ ባለመገመት ወይም ባለማሰብ የሚፈፀም
ከሆነ ድርጊቱ በቀላል ቸለልተኝነት እንደሚያስጠይቅ በህጉ ተገልፃዋል ፡፡

ለምሳሌ፡- X ጥይት የሌለው ሽጉጥ እንደያዘ አስቦ ቢተኩስ እና ሰው

ቢጎዳ በቀላል ቸልተኝነት ይጠየቃል ምክንያቱም ሽጉጥ ገዳይ

ከሚባሉት መሳሪያዎች የሚመደብ በመሆኑ ልዩ ጥንቃቄ ይፈልጋል

ይህንን ባለመወጣቱ ይጠየቃል፡፡


የወንጀል ዓይነቶች
 ወንጀሎች ባላቸው የአፈፃፀም ደረጃ በ2 ከፍለን ማስቀመጥ እንችላለን
፡፡ እነሱም ፡-
ሀ/ ሙሉ ለሙሉ የተፈፀመ ወንጀል
 ወንጀሉ ሙሉ ለሙሉ ግቡን ሲያደርስ ወይም የታለመለት
ዓላማ ሲያሳካ ወንጀሉ ሙሉ ለሙሉ የተፈፀመ ወንጀል
እንለዋለን፤
 ወንጀል ፈፃሚው ወንጀልን ለመፈፀም የተነሳበትን ፍላጎት
ሲያሳካ ሙሉ ለመሉ የተፈፀመ ወንጀል ይባላል፤
ለ/ ሙከራ ወንጀል (የወንጀልህግቁጥር 27)
 አንድ ሰው ወንጀል የማድረግ ሃሳብ ኖሮት ድርጊቱን ለማከናወን ይጀምርና ሳይሳካለት
ሲቀር ነው፡፡ ወይም ድርጊቱ የታለመለትን ግብ ሳይመታ ሲቀር በሙከራ ላይ ያለ
ወንጀል ይባላል ወይም በሌላ አገላለፅ ማንኛውም ሰው ወንጀልን ለማድረግ ጀምሮ፡-

 የወንጀሉን ድርጊት እስከ መጨረሻው ካልተከታተለ፣

 የወንጀሉን ድርጊት እስከ መጨረሻ ለመከታተል ካልቻለ፣


 የወንጀሉን ድርጊት እስከ መጨረሻው ተከታትሎ ውጤት ያላገኘ እንደሆነ ማለት ነው፡፡
የወንጀል ክስ የሚቀርብባቸው ሁኔታዎች
 አንድ የወንጀል ድርጊት ላይ ክስ የማቅረብ መብት የተሰጠው ለዐቃቤ

ህግ መሆኑን የወንጀል ሕግ አንቀፅ 211(1) ይደነግጋል፡፡ የክስ

አቤቱታው ለዐቃቤ ህግ የሚቀርብባቸው በዋናነት ሁለት መንገዶች

ሲሆን እነዚህም በግል ተበዳይ በሚቀርብ አቤቱታ ወይም ተቋማት

በሚሆኑ ጊዜ በተቋሙ ውክልና የተሰጠው የሕግ ባለሙያ ነው፡፡


 አንድ ወንጀል የተበዳዩን ብቻ ሳይሆን የጠቅላላውን ሕብረተሰብ ጥቅምና ደህንነት

የሚመለከት በመሆኑ የወንጀል ክስ የማቅረብ መብት ያለው በመንግስት ስም ዐቃቤ ሕግ

ስለሆነ በግል ከሳሽነት የወንጀል ክስ ሊቀርብ አይችልም፡፡ ነገርግን አንዳንድ ቀለል ያለ

ወንጀሎች ከሕብረተሰቡ ጥቅምና ደህንነት ይልቅ የተበዳዩን ግለሰብ ጥቅምና ደህንነት

የሚመለከቱ በመሆናቸው የሕጉ ልዩ ክፍል በተለይ በሚደነግገው መሰረት እንደዚህ

ያለውን ክስ የግል ተበዳዩ ወይም ስለ እርሱ ሆኖ የመክሰስ መብት ያለው ሰው የክስ

አቤቱታውን ካላቀረበ በቀርበ ዐቃቤ ሕግም ቢሆን ክስ ሊቀርብ አይችልም፡፡ ዐቃቤ ህግ

በግል አቤቱታው መሰረት ጉዳዩን አጣርቶ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ክስ ያቀርባል፡፡ የግል

አቤቱታ የሚያስፈልጋቸው ወንጀሎችም የግል አቤቱታ ካልቀረበባቸው በቀር ለማቅረብ

አይቻልም፡፡
 በመንግስት መስሪቤቶች ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ክስ የሚቀርበው
በዐቃቤ ህግ ነው፡፡ በመሆኑም በእነዚህ ተቋማት የሚገኙ የሕግ
ባለሙያዎች የወንጀል ጉዳይ ሲገጥም የሰነድ ሆነ የሰው ማስረጃዎች ካሉ
እነዚህን በማጠናከር አቤቱታውን ለፓሊስ በማቅረብ ፓሊስም
መዝገቡን ለዐቃቤ ህግ በማስተላለፍ መዝገቡ እንዲደራጅ በማድረግ ክስ
ይመሰርታል፡፡በዐቃቤ ህግ ክስ ከተመሰረተ በኋላ የተቋሙ የህግ
ባለሙያዎች ቀጣይ ስራ መዝገቡ የደረሰበትን ደረጃ መከታተል ብቻ
ይሆናል፡፡
የሙስና ወንጀሎች
የሙስና ወንጀል ምንነት
 የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣው አዋጅ ቁጥር 881/2007 በአንቀፅ 4(2) ላይ

የተሰጠው ትርጓሜ ስናይ “ማንኛውም የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ሠራተኛ


በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የማይገባ ጥቅም ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት
ወይም በሌላ ሰው መብት ወይም ጥቅም ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ በተሰጠው ኃላፊነት
ወይም ተግባር ማድረግ የሚገባውን እንዳያደርግ ወይም ማድረግ የማይገባውን እንዲያደርግ
ከሌላ ሰው ላይ ጥቅም የተቀበለ ወይም የጠየቀ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ ለራሱ ወይም
ለሌላ ሰው ጥቅም ለማስገኘት የተሰጠውን ስልጣን ወይም የህዝብ አደራ ያላግባብ የተገለገለ
እንደሆነ ………..በሙስና ወንጀል ፈፃሚነት ተጠያቂ ይሆናል” በማለት በግልፅ ይደነግጋል፡፡

 ከላይ የተሰጠው ትርጉም ዘርዝረን ስንመለከት

ሀ/ የመንግስት ሠራተኛ ማነው ?


 በመንግስት መ/ቤት ወይም በመንግስት የልማት ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥሮ፣
ተሾሞ፣ ተመድቦ ወይም በህዝብ ተመርጦ ሥራውን የሚያከናውን ሰው
ሲሆን የሥራ አመራር ቦርድ አባልን ይጨምራል፡፡ [አዋጅ ቁጥር 881/2007
አንቀፅ 2(2)]
ለ/ የማይገባ ጥቅም ምንድን ነው ?
 ለመንግስት ሠራተኛው ደሞወዝና በህግ የተፈቀደ ጥቅም ተገቢ ጥቅም ሲሆን
ከዚህ ውጭ የሚገኝ ማንኛውም ጥቅም የማይገባ ጥቅም ስለሆነ በሙስና
ወንጀል ያስጠይቃል ፡፡ [አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 2(14)]
ሐ/ ጥቅም ምንድነው ?
 አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 2(13)] እንደሚከተለው ተርጉሞታል:-
 ገንዘብ፣ ዋጋ ያለው ማንኛውም ንብረት፣ ሥጦታ፣
 ብድር፣ ክፍያ፣ ወረታ ወይም ኮሚሸን፣
 ማንኛውም ሹመት፣ ቅጥር ወይም ውል፣
 ከወንጀል፣ ከፍታብሔር ክስ፣ ከችሎታ ማጣት፣
 ድክመት ማዳን፣ አገልግሎት፣ ወይም ውለታ፣
 ከብድር፣ ከግዴታ፣ ወይም ከእዳ ነፃ ማድረግ ፣
 ማናቸውንም መብት፣ተግባር መፈፀም ወይም አለመፈፀም
 ከተዘረዘሩት ውጭ ሌላ ማንኛውን ጥቅምን ያካትታል፡፡
በተቋማችን የሚታዩ የሙስና ወንጀሎች እና የሕግ ድንጋጌዎቻቸው
1.በግዢ ላይ የሚፈፀሙ የሙስና ወንጀሎች
 የሙስና ወንጀል አዋጅ 881/2007 አንቀፅ 13 እንደሚደነግገው ማንኛውም የመንግስት

ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሰራተኛ የማይገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለማስገኘት በግዥ ወይም
በሽያጭ ወይም በሚያከናውናቸው ተግባራት ማናቸውንም ጥቅም ያገኘ ወይም የወሰደ እንደነገሩ
ሁኔታ ከ1 ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት እና እስከ 3000 ብር የቀላል የገንዘብ መቀጮ
ወይም ከ 10ዓመት የማይበልጥ ፅኑ እስራት እና ከ100 ሺህ ብር የማይበልጥ የገንዘብ ቅጣት
እንደሚያስከትል ነው፡፡
 የተወሰደውን ወይም የተገኘውን ጥቅም በፍ/ብሄር ከሶ የማስመለሱ ተግባር የተጠበቀ መሆኑን

ማንም ልብ ሊለው ይገባል፡፡በድርጅታችን በግዥ ክፍል የሚስተዋሉ በፕሮፎርማ ግዥ ግዜ


የማጭበርበር ድርጊት በዚህ ድንጋጌ ስር የሚያስጠይቅ በመሆኑ ልንጠነቀቅ ይገባል፡፡
2. ሰነዶችን ማጥፋት ወይም ጉዳት ማድረስ
 ማንም ሰው የሌላውን ሰው መብት ወይም ጥቅም ለመጉዳት ወይም ለራሱ ወይም ሌላውን ለመጥቀም
የድርጅቱ ሰነድ ላይ ጉዳት ማድረስ፤መቅደድ ፤ማጥፋት ፤ጥቅም ላይ እንዳይውል ማድረግ ወይም
መውሰድ ተግባር የተፈፀመ እንደሆነ የፈፀመው አካል ከ3- 10 ዓመት ፅኑ እስራት እና ከ10ሺ እስከ
70ሺ የሚደርስ መቀጮ እንደሚቀጣ እንዲሁም ወንጀሉ የተፈፀመው ሰነዶቹን
እንዲያዘጋጀት፣እንዲመዘግብ፣እንዲጠብቅ ወይም እንዲሰጥ የተመደበ ሠራተኛ ከሆነ ከ 7-25
አመት የሚደርስ ፅኑ እስራት እና ከ25ሺ እስከ 100ሺ የሚደርስ መቀጮ ይቀጣል በማለት በአወጅ
ቁ.881/2007 አንቀፅ 24 ላይ በግልፅ ተደንግጓል፡፡
 በመሆኑም የሰራተኞችን ወይም የደንበኛን ፋይሎችን መደበቅና ማጥፋት በዚህ ድንጋጌ መሰረት
የሚያስቀጣ መሆኑን ልንገነዘብ ይገባል፡፡
3. ሰነዶችን አስመስሎ ማዘጋጀት ወይም ወደ ሀሰት መለወጥ
 ማንም ሰው የሌላውን መብት ወይም ጥቅም ለመጉዳት ወይም እራሱን ለመጥቀም በማሰብ
ሃሰተኛ ፅሁፍ ማዘጋጀት፤የሌላውን ሰው ፊርማ አስመስሎ መፈረም ፤የእውነተኛን ፅሁፍን ይዘት
አሃዝ ፍሬ ነገር እና ዝርዝር መግለጫን በሙሉና በከፊል መለወጥ እስከ 10 ዓመት እስራት እና
እስከ 30ሺ መቀጮ እንደሚያስቀጣ የሙስና ወንጀሎች አዋጅ 881/2007 አንቀፅ 23 ላይ
እና በወንጀል ህጉ አንቀፅ 375 ተደንግጉዋል፡፡
 በዋነኝነት በድርጅታችን የመልካም አስተዳደር ዕቅድ ውይይት ግዜ የተነሱ ኔጌቲቭ የነበረውን
ፖዘቲቭ ማድረግ፤ሰንድ በመሰረዝ ማጭበርበር፤ተገልጋይ የማይጠቀምበትን ዕቃ በማጋነን
በግምት ውስጥ በማካተትና ደንበኛውን በማስከፈል የተረፈውን ዕቃ ከድርጅቱ በህጋዊ መንገድ
ወጭ በማድረግ ለራስ ጥቅም ማዋል እና ለሌሎችም ተገልጋዮች ከተቋሙ እውቅና ውጭ
በማስከፈል መስራት፤የእቃ መጠየቂያ ሰነዶችን በኦርጅናል እና የተከፈለበትን ቀን ወደ ኋላ ባሉት
ዓመታት በመሙላት ማጭበርበር እና የመሳሰሉት የሰነድ ማጭበርበር ወንጀል በዚህ ድንጋጌ ስር
የሚያስቀጡ ናቸው፡፡
4. ያለአግባብ ፍቃድ መስጠት ወይም ማፅደቅ
 ማንኛወም የተቋሙ ኃላፊ ውይም ሰራተኛ በህግ ሊሰጥ የማይችል የስራ ፍቀድ
የሰጠ ወይም ያፀደቀ እንደ ነገሩ ሁኔታ እስከ 10 ዓመት ፅኑ እስራትና
ከ30ሺ ብር በማይበልጥ መቀጮ ያስቀጣል ይላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ፍቃዱ
የተሰጠው ወይም የፀደቀው በቸልተኝነት ቢሆን እንኳን በቀላል እስራት እና
መቀጮ እንደሚቀጣ አዋጅ 881/2007 አንቀፅ 20 ላይ ይደነግጋል፡፡
 ማንኛውም ሰራተኛ ይሁን ኃላፊ የሥራ ፍቃድ ሲሰጥ ይሁን ሲያፀድቅ ወንጀል
ለመስራት ባያስብ እንኳን በቸልተኝነት ተገቢ ያልሆነ የሥራ ፍቃድ ከሰጠ
ወይም ካፀደቀ ከተጠያቂነት የማያመልጥ በመሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ
ያስፈልጋል፡፡
5. ያላግባብ ጉዳይ ማንጓተት
 አወጅ ቁ.881/2007 አንቀፅ 18 እንደሚደነግገው ማንኛውም የመንግስት ወይም
ህዝባዊ ድርጅት ሠራተኛ በሥራው ምክንያት ከቀረበለት ጉዳይ ጋር በተገናኘ ጥቅም
ለማግኘት ወይም ሌላውን ለመጥቀም ወይም ለመጉዳት ከሕግ፣ ከሥራ ፣ መመርያ
ወይም ከተቀመጠው አሰራር ውጭ ያለበቂ ምክንያት ባለጉዳይን ያዘገየ ፣ ያሰለቸ እና
ያጉላላ እንደሆነ እስከ 5 ዓመት እስራት እና 5 ሺ ብር ያልበለጠ መቀጮ እንደሚቀጣ
ነው፡፡
 በመስሪያ ቤታችን የሚስተዋለው ወረፋ አስጠባቂ ወረፋን የማዛባት ተግባር ፣
ከተቀመጠው የመስተንግዶ ስታንዳርድ በላይ በማቆየት ባለጉዳይን ማማረር ፣
የመብራት ብልሽት ሲኖር ያለበቂ ምክንያት በወቅቱ አለማስተካከል ፣ የግብዓት እጥረት
ሰበብ በማድረግ ፍትሃዊ መስተንግዶ አለማካሄድ ፣ ተገልጋይ ግልፅ መረጃ እንዳይኖረው
በማድረግ ሰበብ አስባብ እያበዙ ማጉላላት እና መሰል ድርጊቶች ከላይ በተጠቀሰው
ድንጋጌ መሰረት የሚያስጠይቅ መሆኑን ከግንዘቤ ውስጥ ልናስገባ ይገባል ፡፡
6. በህገወጥ መንገድ ገንዘብ መሰብሰብ
 የሙስና ወንጀሎች አዋጅ 881/2007 በአንቀጽ 17 ላይ የማይገባ ጥቅም ለማግኘት

በማሰብ ሊከፈል የማይገባ መሆኑን እያወቀ የገቢ ጥቅም እንዲሰበሰብ ያዘዘ እንደሆነ

እስከ 10 ዓመት እስራት እና እስከ 30 ሺ መቀጮ እንደሚያስቀጣ ያስቀምጣል፡፡


 ከዚህ ጋር በተገናኘ በአንዳንድ የመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች በትራንስፎርመር ላይ ያልተገባ

ድርጊትን በመፈፀም የመብራት አገልግሎት እንዲቋረጥ በማድረግና ለማስተካከል ከፍተኛ

ገንዘብ የማሰባሰብ ስራ፤ ግምትን በማጋነን ደንበኛውን ዋጋ እንቀንሳለን በሚል

በመደራደር ጉቦ እንዲከፍል ማግባባት፤ ፊውዝ በመንቀል ሓይል መቆራረጥ እንዲከሰት

በማድረግ ለጥገና ገንዘብ ማስከፈል፤ የመሳሰሉት የወንጀል ተግባራት የሚሰሩ አካላት

በዚህ ድንጋጌ መሰረት በሙስና ወንጀል ሊያስጠይቅ እንደሚችል ልብ ሊባል ይገባል፡፡


7.የእምነት ማጉደል ተግባር
 የሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 31 ላይ ማኛውም የመንግስት ወይም

ህዝባዊ ድርጅት ሰራተኛ ተገቢ ያልሆነ ብልፅግና ለራሱ ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት

በማሰብ በአደራ የተሰጠውን ዋጋ ያለውን ነገር ወይም ጥሬ ገንዘብ በሙሉ ወይም በከፊል ለራሱ ያደረገ

እንደሆነ እስከ 7 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት እና 10ሺህ የገንዘብ መቀጮ ያስቀጣል ይላል፡፡

 በመስ/ቤቱ የውስጥ ኦዲት በተለያየ ግዜ በየሪጅኖች እና ዲስትሪክቶች በሚያደርገው የኦዲት ስራ

በርካታ የገንዘብ ነክ ሥራ ጋር በተገናኘ የተቀጠሩ ሠራተኞች የገንዘብ ጉድለት ሲፈፅሙ ይስተዋላል ፡፡

በጉድለት የሚረጋገጠው ገንዘብ ቀላል የማይባል እና የድርጅቱን የገንዘብ ዓቅም የሚፈታተን ነው፡፡

ይህን በተቻለ መጠን ለመቅረፍ እንዲቻል በገንዘብ ነክ የሚቀጠሩ ሰራተኞች በሚቀጠሩበት ጊዜ በቂ

የሆነ ዋስ እንዲያቀርቡ ማድረግ እና በሥራ ላይም አስፈላጊውን ክትትል በማደረግ የቅድመ መከላከል

ሥራ መስራት ተገቢ ነው፡፡


8. ጉቦ መቀበል(አንቀፅ 10)
 ማንኛውም የመንግስት ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሰራተኛ ለራሱ ወይም

ለሌላ ሰው ጥቅም እንዲሰጥ የጠየቀ፤የተቀበለ ወይም የተስፋ ቃል


የተቀበለ ከሆነ እንደነገሩ ሁኔታ ከ1 አመት እስከ 10 አመት የሚደርስ
እስራት እንዲሁም ከ3 ሺ ብር እስከ 40ሺ ብር ድረስ የሚደርስ
የገንዘብ መቀጮ ይቀጣል፡፡
ምንጩ ያልታወቀ ንብረትና ገንዘብ (የሙስና ወንጀሎች አዋጅቁ.
881/2007 አንቀፅ 21)
ማንኛውም የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ሠራተኛ የሆነ ወይም የነበረ ሰው፡-
 ሀ. የኑሮ ደረጃው አሁን ባለበት ወይም አስቀድሞ በነበረበት የመንግስት ወይም
ህዝባዊ ድርጅት ሥራ ወይም በሌላ መንገድ ከሚያገኘው ወይም ሲያገኘው ከነበረው
ህጋዊ ገቢ የበለጠ እንደሆነ፤
 ለ. ያለው ንብረት ወይምገንዘብ ምንጭ አሁን ባለበት ወይም አስቀድሞ
በነበረበት የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ሥራ ወይም በሌላ መንገድ
ከሚያገኘው ወይም ሲያገኝ ከነበረው ህጋዊ ገቢ ጋር የማይመጣጠን እንደሆነ፤
ምንጩ ያልታወቀ የቀጠለ…
 የዚህ ዓይነቱ የኑሮ ደረጃ እንዴት ሊኖረው እንደቻለ ወይም ያለው ንብረት ወይም
ገንዘቡ በእጁ ሊገባ እንደቻለ ለፍ/ቤት ካላስረዳ በስተቀር የንብረቱ ወይም የገንዘብ
ምንጩ መወረስ ወይም ለባለቤቱ መመለስ እንደተጠበቀ ሆኖ በቀላል እስራት እና
በመቀጮ፤ ወይም ነገሩ ከባድ ሲሆን ከ5 ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት እና ከ5
ሺብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል፡፡
 በመሆኑም ሀብትን ማሳወቅና ማስመዝገብ (የሀብት ማሳወቂያና ማስመዝገቢያ አዋጅ
668/2002) የመንግሥት አሠራርን በግልጽነትና በተጠያቂነት ላይ ለመመስረት
አስፈላጊ ከመሆኑም በላይ ሀብት ማሳወቅና ማስመዝገብ ሙስናና ብልሹ አሠራርን
ለመከላከልና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው አለው፡፡
በተቋማችን የሚታዩ ሌሎች ወንጀሎች እና የሕግ ድንጋጌዎቻቸው

1.የስርቆት ተግባራት
 ማንም ሰው የማይገባውን ሃብትና ንብረት ለማግኘት በማሰብ ንብረትነቱ የድርጅቱ የሆነውን
የማይንቀሳቀስ እና የሚንቀሳቀስ ንብረት የወሰደ ወይም ከራሱ ንብረት ጋር የቀላቀለ እንደሆነ
እስከ 5 ዓመት ድረስ በፅኑ እስራት የሚያስቀጣ መሆኑን ይደነግጋል፡፡ከዚህ ጋር በተገናኘ አንድ
ሰው ለፈፀመው ድርጊት በወንጀል ተቀጣ ማለት ከፍ/ብሄር ነፃ ነው ማለት አይደለም ፡፡
የወንጀል ቅጣቱ እንደተጠበቀ ሆኖ የወሰደውን ንብረት በፍ/ብሄር ተከሶ እንዲመለስ
ይደረጋል፡፡
 ከቆጣሪ ውጭ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማግኘት የኃይል ስርቆት መፈፀም ጋር በተገናኘ ለራስ ወይም
ለሌላ አካል ጥቅም ለማስገኘት የኃይል ማሰራጫ ላይ ወይም ሌላ ሰው ከዘረጋው መስመር
ኤሌክትሪክ ኃይል በመውሰድ የማይገባ ጥቅም ያገኘ እንደሆነ እስከ 5 ዓመት የሚደርስ እስራት
ወይም 20ሺ ብር መቀጮ እንደሚያስከትል የኢነርጂ አዋጅ ቁጥር 810/2006 በአንቀፅ
28 ላይ ተደንግጓል፡፡
2. በሐሰተኛ ሰነድ መገልገል
 በሃሰት በተዘጋጀ ሰነዶቸ ወይም ወደ ሃሰት በተለወጠ ሰነድ እያወቀ መገልገል እንደ
ወንጀል ክብደቱ ታይቶ እስከ 10 ዓመት እንደሚያስቀጣ የወንጀል ህጉ 378
ላይ በግልፅ ተቀምጧል፡፡በየትኛውም መስሪያ ቤት በተጨባጭ የሚስተዋሉ
የሃሰተኛ የት/ት ማስረጃ ሰነድ መጠቀም በዚህ ድንጋጌ መሰረት ያስጠይቃል፡፡
3. የተቋሙን ንብረት ያለአግባብ መገልገል/ማባከን
 ማንኛውም ሰው ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት
በአደራ የተሰጡትን ወይም የተረከበውን የመንግስት ወይም የህዝብ ንብረት
አሳልፎ የሰጠ፣የጣለ፣የሸጠ፣የለወጠ፣ያስያዘ እና ጉዳት እንዲደርስባቸው ያደረገ
እንደሆነ እስከ 5 ዓመት በሚደርስ እስራት ይቀጣል(የወንጀል ሕግ አንቀፅ
677)፡፡በመስሪያ ቤታችን የሚስተዋለው እንደ የሥራ መሳርያ
ማከራየት፤የድርጅቱን ዕቃ መሸጥ በዚህ ድንጋጌ መሰረት ያስጠይቃል፡፡
 ምንም እንኳን ድርጊቱ በቸልተኛነት የተፈፀመ ቢሆንም እስከ አንድ አመት
በሚደርስ እስራት እንደሚያስቀጣ ልብ ልንል ይገባል፡፡
4.የሥራ ኃላፊነትን ባለመወጣት የሚፈፀም ወንጀል
 ማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ የሥራ ግዴታ ተግባሩን በአግባቡ ሳይፈፀም
በመቅረቱ በመንግስት ፤በህብረተሰቡ ወይም በግለሰብ ጥቅም ላይ ጉዳት ያደረሰ
ከሆነ ከ1000 ብር በማይበልጥ መቀጮ ወይም ከስድስት ወር በማይበልጥ
ቀላል እስራት ያስቀጣል በማለት የወንጀል ሕጉ በአንቀፅ 420 ላይ ይደነግጋል፡፡
 ከዚህ ጋር በተያያዘ ብዙ ግዜ የድርጅታችን የጥገና ክፍሎች የኤሌክትሪክ መስመር
ተበጥሶ መውደቁን እየተነገራቸው በአፋጣኝ አስፈላጊውን ጥገና ባለማድረጋቸው
በስው እና ንብረት ላይ አደጋ ሲደርስ ይስተዋላል፡፡ሌላችም ክፍሎች እንዲሁ
የስራ ድርሻቸውን በአግባቡ ባለመወጣት በድርጅታችን ላይ ጉዳት ሲደረስ
ይስተዋላል፡፡ለምሳሌ ሆን ብሎ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚዎችን በወቅቱ ቢል
እንዳይከፍሉ ማዘግየት እና ሌሎች የስራ ኃላፊነትን በአግባቡ አለመወጣት በዚህ
ድንጋጌ ሰር የሚያስጠይቅ መሆኑን ሁሉም ልብ ሊለው ይገባል፡፡
5. ለፍትህ እርዳታ መስጠትን እምቢ ማለት
 ማንም ሰው በምስክርነት ወይም በተከሳሽነት ወይም በልዩ አዋቂ ምስክርነት ማስረጃ እንዲያቀረብ
ታዞ ሳያቀርብ የቀረ ፤ ምስክርነት ቃሉን እንዲሰጥ በህግ መሰረት ተጠርቶ ሳይሰጥ የቀረ እንደሆነ
ከሁለት ወር በማይበልጥ እስራት ወይም ከ1000ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል በማለት
የወንጀል ህጉ በአንቀፅ 448 ላይ ይደነግጋል፡፡

 ማንም ሰው በቂ ምክንያት ሳይኖረው በህግ ወይም በሙያው ደንቦችን ለህዝብ ደህንነት ወይም ሰላም
ሲባል ወንጀሎችን ለሚመለከታቸው ባለስልጣናት አለማስታወቅ ከ1000 በማይበልጥ መቀጮ
ወይም ከ6ወር በማይበልጥ እስራት ያስቀጣል በማለት የወንጀል ህጉ በአንቀፅ 443 ላይ ይደነግጋል፡፡
 ማንኛውም ሰው ከመንግስት ስራ ጋር በተያያዘ ሁኔታ በሕግ በተፈቀደው
ወይም ከፍርድ ቤት በተሰጠ ትዕዛዝ መሰረት በመንግስት ሠራተኛ
ሲጠየቅ ቀርቦ ለማስረዳት ተገቢውን መልስ ለመስጠት ፣ሰነዶችን
ለማቅረብ ወይም ለማስመርመር እምቢተኛ ከሆነ ወይም ያልተባበረ
እንደሆነ ወይም በማናቸውም ሌላ መንገድ የመንግስትን ሥራ ያደናቀፈ
እንደሆነ ከ5 ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ወይም በመቀጮ
ይቀጣል በማለት የወንጀል ህጉ በአንቀፅ 338 ላይ በግልፅ
ያስቀምጣል፡፡
6.በኤሌክትሪክ መስመር ላይ ጉዳት ማድረስ
 ማንኛውም ሰው በባለ ፍቃዱ የተገጠመለትን የኤሌክትሪክ ቆጣሪ ያሰናከለ ወይም
እንዲሰናከል የፈቀደ ወይም የኤሌክትሪክ ፍጆታን እንዳይመዘገብ ያደረገ እንደሆነ
እስከ 5 ዓመት በእስራት እንደሚያስቀጣ የኢነርጂ አዋጅ 810 /2006 አቀንፅ
29 ይደነግጋል፡፡
 ማንኛውም ሰው የራሱ ያልሆነውን ዕቃ፣ መሳርያ፣ ንብረት ላይ ጉዳት በማድረስ
ዋጋ ያሳጣ ወይም እንዳያገለግል ያደረገ እንደሆነ እስከ 3 ዓመት የሚደርስ እስራት
ወይም በመቀጮ የሚያስቀጣ ሲሆን የወደመው ንብረት የቴሌ ወይም የመብራት
ሃይል የተዘረጋ መስመር ከሆነ እስከ 10 ዓመት ፅኑ እስራት እንደሚያስቀጣ
የወንጀል ህጉ አንቀፅ 690(2) ይደነግጋል፡፡
የሕግ ሰውነት የተሰጣቸው ድርጅቶች በወንጀል ሕግ ተጠያቂ
የሚሆኑበት አግባበብ

 የወንጀል ሕጉ አንቀጽ በአንቀጽ 23(3) ላይ ምንም እንኳን በመርህ ደረጃ


ወንጀልን ለማቋቋም ሦስት መሠረታዊ ፍሬ ነገሮች (ሕጋዊ፣ ግዙፋዊ እና ሞራላዊ
ፍሬ ነገሮች) በአንድነት ተሟልተው መገኘት ያለባቸው ቢሆንም የሕግ ሰውነት
የተሰጠው ድርጅት በወንጀል ተጠያቂ ሊሆን የሚችል ስለመሆኑ አስቀምጧል፡፡
 ሆኖም የሕግ ሰውነት የተሰጠው ድርጅት በወንጀል ተጠያቂ ሊሆኑ የሚችሉት
በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 34 የተመለከቱት ነጥቦች ግምት ውስጥ ገብተው ነው፡፡
እነዚህም፡-
◦ የወንጀል ተጠያቂነቱ የሚመለከተው ማንኛውም ድርጅት ሳይሆን የሕግ ሰውነት
የተሰጠው ድርጅት ነው፡፡
◦ የሕግ ሰውነት የተሰጠው ድርጅት በወንጀል ሊጠየቅ የሚችለው በወንጀል ሕጉ ልዩ
ክፍል በግልጽ ተደንግጎ በሚገኝበት ጊዜ ብቻ ነው፡፡
◦ የሕግ ሰውነት የተሰጠው ድርጅቶች በወንጀል ተጠያቂ ቢሆኑም ጥፋተኛ ሆነው
ሲገኙ ሊጣልባቸው የሚችለው ዋና ቅጣት መቀጮ ነው፡፡ በእርግጥ ተጨማሪ
ቅጣቶች ሊጣሉባቸው ይችላሉ፡፡በመሆኑም ከዋና ቅጣቶች በተደራቢ አስፈላጊ
ሆኖ ሲገኝ ድርጅቶች እንዲዘጉ፣ እንዲታገዱ ወይም እንዲፈርሱ ሊወሰን ይችላል፡፡
◦ የሕግ የሰውነት የተሰጣቸው ድርጅቶች መጠየቃቸው ድርጊቱን በቀጥታ የፈፀሙት
ሰዎች ያለባቸውን የወንጀል ተጠያቂነት አያስቀርም፡፡
የወንጀል ይርጋ (የወንጀል ሕግ አንቀፅ 217፣218)
 የሞት ፍርድ ወይም ዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት የሚያስቀጣ ከሆነ ከ25
ዓመት፤
 ከ10 ዓመት በላይ እስከ 25 ዓመት ሊደርስ የሚችል ፅኑ እስራት
የሚያስቀጣ ከሆነ 20ዓመት፤
 ከ5 ዓመት በላይ እስከ 10ዓመት ሊደርስ የሚችል ፅኑ እስራት
የሚያስቀጣ 10 ዓመት፤
 ከ5ዓመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል 10 ዓመት፤
 ከ1 ዓመት በላይ በቀላል እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል 5 ዓመት፤
 እስከ 1 ዓመት በቀላል እስራት የሚያስቀጣ ወይም በገንዘብ መቀጮ
ብቻ ሊያስቀጣ የሚችል ወንጀል 3 ዓመት
 የግል አቤቱታ መቅረብ ያለበት ተበዳዩ የወንጀሉን ድርጊት ወይም
የወንጀል አድራጊውን ማንነት ካወቀበት ቀን ጀምሮ እስከ 3 ወር ባለው
ጊዜ ውስጥ ብቻ ነው (የወንጀል ሕግ ቁጥር 213)፡፡ ነገርግን
በማንኛውም ሁኔታ በግል አቤቱታ ብቻ የሚያስቀጣ ማንኛውም
የወንጀል ክስ የይርጋ ዘመን 2 ዓመት ብቻ ነው (የወንጀል ሕግ ቁጥር
218)፡፡

You might also like