Download as pptx, pdf, or txt
Download as pptx, pdf, or txt
You are on page 1of 42

በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራስየዊ ሪፓብልክ የቴክኒክና

ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኤጀንሲ

ሀገር አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት


አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች የደረጃ እድገት
እንዲሁም
የዲኖችና ምክትል ዲኖች ምልመላና ምደባ
አፈፃፀም መመሪያ

ታህሳስ 2005 ዓ .ም
አዲስ አበባ
የመመሪያው ይዘት
•መግብያ
•የደረጃ እድገት አስፈላጊነት
•ትርጉም
•የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና አሰልጣኞችና እንስትራክተሮች ፕሮፋይል
•የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ዲኖች እና ምክትል ዲኖች ፕሮፋይል
•የተቋማት ዲኖች እና ምክትል ዲኖች ምልመላና አመዳደብ
•የተቋማት ዲኖች እና ምክትል ዲኖች ምልመላ መስፈርት
•የሥልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች ምልመላና አመዳደብ
•የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ዲኖች እና ምክትል ዲኖች ለደረጃ እድገት ለመወዳደር ሊያሟሉ
የሚገባቸው መስፈርቶች
•አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች ለደረጃ እድገት ለመቅረብ ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች
•በየደረጃው የሚፈጸም የደረጃ እድገት ሥርዓት
•የዲኖችና ምክትል ዲኖች የደረጃ እድገት አፈፃጸም
•የአቤቱታ እና ቅሬታ አቀራራብ ህደት
•ልዩ ልዩ ሁኔታዎች
መግብያ

 የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ስትራቴጂ አጠቃላይ አላማ በሀገሪቷ ብቃት፤ ተነሳሽነትና የፈጠራ
ክህሎት ያለው የሰው ሀይል በመፍጠር ድህነትን ማስወገድና ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋጽኦ
ማድረግ ነው፣፣ ይህም የሚተገበረው በሁሉም የኢኮኖሚ ዘርፎች ፍላጎት ላይ የተመሰረተና ከፍተኛ ጥራት
ያለው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና በመስጠት እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና
ተቋማት አዳድስና ምርጥ ቴክኖሎጂዎችን በመቅዳትና ወደ እንዱስትሪው በማስተላለፍ እንዱስትሪውን
በተለይም የጥቃቅንና አነስተኛ እንተርፕራይዞችን ምርትና አገልግሎት በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪነቱን
ማሳደግ እንዲችሉ በማድረግ ነው፣፣

04/22/2024 3
የቀጠለ ….

 ከላይ የተጠቀሱትን ቁልፍ ተግባራት ለመፈፀም ወሳኙን ድርሻ የሚጫወቱት አሰልጣኞች መሆናቸው እሙን
ነው፣፣ በመሆኑም አሰልጣኞችና እንስትራክተሮች እንዲሁም ዲኖችና ምክትል ዲኖች ጥራትና ብቃት
ያለውን ሥልጠና በመስጠት ሙያዊና ሀገራዊ ሀላፊነታቸውን እነዲወጡ ተገቢውን የማትጊያና
የጥቅማጥቅም እንዲሁም ተከታታይነት ያለው የደረጃ እድገት ሥርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል፣፣ በዚህ
መሰረት በሀገር አቀፍ ደረጃ ተጠንቶ የፀደቀውን የደመወዝ ስኬል የአፈፃጸም መመሪያ የሲቪል ሰርቪስ
ሚኒስቴር በቁጥር ሲሰሚ/ጠ10/9/241 ታህሳስ 11 ቀን 2004 ዓ.ም ለትምህርት ሚኒስቴር በጽሁፍ
ያሳወቀውን መነሻ በማድረግ ይህ የደረጃ እድገት አፈፃፀም መመሪያ ተዘገጅቷል፣፣

04/22/2024 4
የቀጠለ

•በመሆኑም አሰልጣኞችና እንስትራክተሮች እንዲሁም ዲኖችና ምክትል ዲኖች ሠልጣኞችን የማሰልጠን ብቃታቸውና
ያስመዘገቡት ተጨባጭ ውጤት በየጊዜው እየተገመገመ በጀማሪ አሰልጣኝነት፤ በረዳት አሰልጣኝነት፤በአሰልጣኝነት፤
በከፍተኛ አሰልጣኝነት፤ በጀማሪ ኢንስትራክተርነት፤ በረዳት ኢንስትራክተርነት፤ በኢንስትራክተርነት፤ በከፍተኛ
ኢንስትራክተርነት፤ በመሪ ኢንስትራክተርነት እና ዋና ኢንስትራክተርነት በተቀመጠው ደረጃ መመደብ እንዲችሉ የእድገት
መሰላሉ ተቀምጦላቸዋል፣፣ ይህ የእድገት መሰላል አስፈላጊውን ውጤት እንዲየስገኝ አሰልጣኞችና ኢንስትራክተርነት የሥራ
ውጤታቸውን እየተገነዘቡ ሥልጠናውን በብቃት በመምራት ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ሠልጣኞችን በማፍራት የእድገት
መሰላሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እና የተጣለባቸውን ኃላፊነት በተገቢው መንገድ እንዲወጡ ለማድረግ የሚየስችል ተገቢው
የሥራ አፈፃጸም ግምገማ ሥርዓትም ተዘርግቷል፣፣
የቀጠለ

•የሥራ አፈፃጸም ግምገማው አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች እንዲሁም ዲኖችና


ምክትል ዲኖች በሚሰጡት ሥልጠና ጥራትና በሚያበቁአቸው ሠልጣኞች
ብዛትና አራቱን ማእቀፎች መሠረት በማድረግ ለኢንዱስትሪው
ኤክስቴንሽን በሚሰጡት አገልግሎትና በሚገኘው ውጤት ጭምር የእድገቱ
ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል የሚረዳ ከመሆኑም ባሻገር ለመደበኛ
ደመወዝ ጭማሪ፤ ለዝውውር፤ ለምደባ፤ በችሎታ ማነስ ለሚደረግ ስንብትና
ለዲሲፕሊን እርምጃ አወሳሰድም ጭምር ያገለግላል፣፣ ስለሆነም ለግምገማ
መስፈርትነት በተቀመጡት ነጥቦች ላይ በመመርኮዝ ምዘናውን በተጨባጭ
መረጃ ላይ በመንተራስ እንዲከናወን ማድረግ ይጠበቃል፣፣
ክፍል አንድ
1.1. የደረጃ እድገት አስፈላጊነት

ይህ “ሀገር አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች የደረጃ ችድገት
እንዲሁም የዲኖችና ምክትል ዲኖች ምልመላና ምደባ አፈፃፀም መመሪያ ”ውጤት ተኮር ሥልጠና ሥርዓቱን በሚገባ
ወደ ተግባር በመለወጥ የስትራቴጂው ቁልፍ ግቦች መሳካት እንዲችሉ፤ በአሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች ልማት ረገድ
ያለው ሥራ ወሳኝ በመሆኑ ይህ መመሪያ የተቋማት አሰልጣኞች ማትጊያ ሥርዓትን ለመተግበር እንዲያስችል ተደርጎ
በሀገር አቀፍ ደረጃ /ወጥ በሆነ መልኩ/ ተግባራዊ እንዲሆን ተዘገጅተዋል፣፣
የቀጠለ

1.2. ትርጉም
 ዲን ማለት ብቃቱ በሙያ ምዘና የተረጋገጠ፤ የመንግስትን ፖሊስና ስትራቴጂ ለመተግበር ቁርጠኝነት
ያለው፤ በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ካሉት የኤ ደረጃ ወይም የቢ ደረጃ
አሰልጣኞች መካካል በክልሉ ወይም ከተማ አስተዳደሩ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና
ኮሚሽን/ኤጀንሲ/ቢሮ ተወዳድሮ የሚመደብ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋምን
በበላይነት የሚመራ ኃላፊ ነው፡፡
 ምክትል ዲን ማለት ብቃቱ በሙያ ምዘና የተረጋገጠና የመንግስትን ፖሊሲና ስትራቴጂ ለመተግበር
ቁርጠኝነት ያለው ከቢ ደረጃ ወይም ከኤ ደረጃ አሰልጣኝ መካከል አብዛኛው ስልጠና ከሚሰጥባቸው
የሙያ ዘርፎች ተወዳድሮ የሚመደብ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋም የውጤት ተኮር
ስልጠና የሥራ ሂደትና የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን የሥራ ሂደትን በበለቤትነት
የሚመራና በምክትል ዲንነት ደረጃ የሚመደብ ማለት ነው፣፣

04/22/2024 8
የቀጠለ

 ግንበር ቀደም አሰልጣኝ/ኢንስትራክተር ማለት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ስትራቴጂ እና


ውጤት ተኮር ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ሥርዓትን በሚገባ ተገንዚቦ እራሱ ተዋናይ ሆኖ
ሌሎች እንዲከተሉት በማድረግ ለተግባራዊነቱ በቁርጠኝነት የሚታገል እና ተጨባጭ ውጤት
ማስመዝገብ የቻለ አሰልጣኝ/ኢንስትራክተር ማለት ነው፡፡
 የደረጃ እድገት ማለት ለአሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች የደመወዝ ለውጥሊያስገኝ የሚችል ከአንድ
የስራ ደረጃ ወደ ሌላ የሥራ ደረጃ የሚደረግ ለውጥ/ሽግግር ማለት ነው፡፡
 ክልል ማለት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብልክ ህገ መንግስት አንቀጽ 47/1 መሰረት
በክልልነት የታወቁት ሲሆኑ የአዲስ አበባና የድሬደዋ ከተማ አስተዳደርንም ይጨምራል፡፡

04/22/2024 9
የቀጠለ

 የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኤጀንሲ/ኮሚሽን/ቢሮ ማለት በክልሉ ወይም ከተማ አስተዳደሩ


ህጋዊ እውቅና አግኝቶ የተቋቋመ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠናን በበላይነት የሚያስተባብርና
የሚመራ አካል ነው፡፡
 ተቋም ማለት በተለያዩ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና የሙያ መስኮችና የሥልጠና ደረጃዎች
ሠልጣኞችን ተቀብሎ ሥልጠና የሚሰጥና የሚያበቃ የማሰልጠኛ የቋም ነው፡፡
 የዘርፍ አስተባባሪዎች ማለት በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ውስጥ የሚሰጡ ተመሳሳይነት
ያላቸውን የሥልጠና መስኮች በውጤት ተኮር ስልጠና በመምራት በጋራ አቅደው እንዲሰሩ
የሚያስተባብሩ አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች ማለት ነው፡፡

04/22/2024 10
የቀጠለ

 አሰልጣኝ/ኢንትራክተር ማለት በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋም ውስጥ ከሚሰጡት


ሙያዎች ውስጥ በአንዱ የሥልጠና መስክ ህጋዊ ከሆነ ዩኒቨርሲቲ በድግሪ/በሁለተኛ ድግሪ ወይም
ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋም በደረጃ III፤ በደረጃ IV፤ በደረጃ V ሥልጠናውን
አጠናቆና ሥልጠናውን ባጠነቀቀበት ሙያ እንደተገቢነቱ በደረጃ I፤ በደረጃ II ፤ በደረጃ III ፤ በደረጃ
IV እና በደረጃ V ተመዝኖ የሙያ ብቃቱ የተረጋገጠ የማሰልጠንና የማብቃት ሥራ ላይ የተሰማራ
ባለሙያ ሲሆን የተቋማት ኃላፊዎችንም ይጨምራል፡፡
 ባለድርሻ አካላት ማለት በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ሥርዓት ውስጥ ጉልህ ሚና ያላቸው
እንደ መንግስታዊ አካላት፤ የልማት ድርጅቶች፤ ማሰልጠኛ ተቋሞች እንዲሁም የአሰሪና የሰራተኛ
ማህበራት ተወካዮችና የመሳሰሉትን ያጠቃልላል፡፡

04/22/2024 11
1.3. የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች ፕሮፋይል
1.3.1. C-ደረጃ አሰልጣኝ

•በደረጃ III፤ በደረጃ IV ወይም በደረጃ IV ሥልጠናውን አጠናቆ ሥልጠናውን ባጠነቀቀበት ሙያ


በደረጃ I፤ በደረጃ II ፤ በደረጃ III ፤ በደረጃ IV እና በደረጃ V ተመዝኖ የሙያ ብቃቱ የተረጋገጠ

•የማሰልጠን ስነ ዘዴ ስልጠና ወስዶ በጥሩ ስነ ምግባር ሥልጠናውን ያጠናቀቀ

1.3.2. B- ደረጃ እንስትራክተር


•የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና በሚሰጥባቸው ሙያዎች ከተወቀ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ድግሪ ሥልጠናውን
ያጠነቀቀ
•የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና በሚሰጥበት ሙያ የና ሥልጠናውን ባጠናቀቀበት ሙያ በደረጃ I፤ በደረጃ II ፤
በደረጃ III ፤ በደረጃ IV እና ወይም በደረጃ V ተመዝኖ የሙያ ብቃቱ የተረጋገጠ
•የማሰልጠን ስነ ዘዴ ስልጠና ወስዶ በጥሩ ስነ ምግባር ሥልጠናውን ያጠናቀቀ
1.3.3. A-ደረጃ ኢኒስትራክተር

•የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና በሚሰጥባቸው ሙያዎች ከተወቀ ዩኒቨርሲቲ በሁለተኛ ድግሪ


ሥልጠናውን ያጠነቀቀ
•ሥልጠናውን ባጠናቀቀበት የሙያ ዘርፍ በሙያው በደረጃ I፤ በደረጃ II ፤ በደረጃ III ፤ በደረጃ IV እና ወይም
በደረጃ V ተመዝኖ የሙያ ብቃቱ የተረጋገጠ
•የማሰልጠን ስነ ዘዴ ስልጠና ወስዶ በጥሩ ስነ ምግባር ሥልጠናውን ያጠናቀቀ

1.4. የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ዲኖች እና ምክትል ዲኖች ፕሮፋይል

1.4.1. የዲኖች ፕሮፋይል


 በኤ ደረጃ በኢንስትራክተርነትና ከዚያ በላይ ወይም በቢ ደረጃ ከፍተኛ ኢንስትራክተርና ከዚያ በላይ ያለውን
የአሰልጣኝነት ፕሮፋይል የሚያሟሉ
 በአሰልጣኝነት ቆይታቸው ከፍተኛ የሥራ አፈፃፀም ያላቸው

 የዉጤት ተኮር ሥልጠና ሥርዓትንለመተግበር የሚያስችል በፌዴራል ወይም በክልል/ከተማ አስተዳደር ደረጃ
የተዘጋጀውን/የሚዘጋጀውን የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና አመራር የወሰዱ/ለመውሰድ ዝግጁ የሆኑ
1.4.2. የምክትል ዲኖች ፕሮፋይል

 ለምክትል ዲንነት የሚወዳደሩ አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች ደጋፊ ሞጁሎች/Empowerment Courses/


ከሚያሰለጥኑ አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች በስተቀር በተቋሙ በሚገኙ አብዛኛው ሥልጠና በሚሰጥባቸው
ሙያዎች የሚያሰለጥኑ ሆነው በኤ - ደረጃ በኢንስትራክትና ከዚያ በላይ ወይም በቢ- ደረጃ በረዳት
ኢንስትራክተርነትና ከዚያ በላይ ያለውን የአሰልጣኝነትና የኢንስትራክተርነት ፕሮፋይል የሚያሟሉ
 በአሰልጣኝነት ቆይታቸው ከፍተኛ የሥራ አፈፃፀም ያላቸው

 የዉጤት ተኮር ሥልጠና ሥርዓትንለመተግበር የሚያስችል በፌዴራል ወይም በክልል/ከተማ አስተዳደር


ደረጃ የተዘጋጀውን/የሚዘጋጀውን የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና አመራር የወሰዱ/ለመውሰድ ዝግጁ
የሆኑ

04/22/2024 14
1.5. የተቋም ዲኖች እና ምክትል ዲኖች ምልመላ እና አመዳደብ

 የተቋም ዲኖችና ምክትል ዲኖች ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና አሰልጣኞች መካከል


የሚመለመሉት በዚህ መመሪያ በተዘጋጀው መመልመያ መስፈርት መሰረት ሲሆን በክልሉ ወይም
ከተማ አስተዳደሩ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኮሚሽን/ቢሮ/ኤጀንሲ ደረጃ በሚቋቋም
መልማይ ኮሚቴ ወይም በክልሉ ወይም በከተማ አስተዳደሩ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና
ኮሚሽን/ቢሮ/ኤጀንሲ ህጋዊ ውክልና በሚሰጠው አካል አማካኝነት ተከናውኖ ለክልሉ ወይም
ከተማ አስተዳደሩ ኮሚሽን/ቢሮ/ኤጀንሲ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኃላፊ ቀርቦ
ይፀድቃል፡፡

04/22/2024 15
ከላይ የተቀመጠው የዲኖች እና ምክትል ዲኖች ፕሮፋይል እንደተጠበቀ ሆኖ ለምልመላ ዕጩ ሆነው የሚቀርቡት
ዲኖች ወይም ምክትል ዲኖች በተጨማሪ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ መሆን አላባቸው፡፡

1.5.1. በተቀመጠው መስፈርት መሰረት የተቋም ዲን ለመሆን የሚያስችል ብቃት ያላቸው፣ አመለካከታቸው የጠራና
የመንግስትን ፖሊሲና ስትራቴጂ ለመተግበር ቁርጠኛ የሆኑ

1.5.2. ግንበር ቀደም አሰልጣኝ/ኢንስትራክተር በመሆን አርአያ ሆነው ሌሎች ግንበር ቀደም እንዲሆኑ ያደረጉ

1.5.3. ራሳቸውን ከኪራይ ሰብሳቢነት ያፀዱና ኪራይ ሰብሳቦዎችን በፅኑ የሚታጋሉ

1.5.4. በሚያሰለጥኑበት ሙያ ልዩ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ሠልጣኞች ድጋፍ በማድረግ የጎላ አስተዋፅኦ ያደረጉ

1.5.5. የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋም ያለበትን የክልል/የአከባቢውን የሥራ ቋንቋ የሚችሉ መሆን
አለባቸው፡፡

04/22/2024 16
1.6. የዲኖችና ምክትል ዲኖች ምልመላ መስፈርት

1.6.1. የ18 ወራት ሥራ አፈፃፀም 30%

1.6.2. የትምህርት ደረጃ 10%

1.6.3. የሥራ ልምድ/አገልግሎት/ 10%

1.6.4. ፈተና/የፅሑፍ፣የቃል/ 35%

1.6.5. በክልሉ/ከተማ አስተዳደሩ ቴ/ሙ/ት/ሥ/ ኮሚሽን/ቢሮ/ኤጀንሲ ኃላፊ የሚሞላ 15%


1.7. የሥልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች ምልመላና አመዳደብ

የተቋማት የሥልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች ምልመላና ምደባ በተመለከተ በተቋሙ ውስጥ


በአርፉ ካሉ አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች መካከል ተወዳድረው የሚመደቡ ሆነው
ቀጥሎ ያለውን መስፈርት ማሟላት አለባቸው፡፡

1.7.1. የ18 ወራት ሥራ አፈፃፀም 30%

1.7.2. የትምህርት ደረጃ 10%

1.7.3. የሥራ ልምድ/አገልግሎት/ 10%

1.7.4. ፈተና/የፅሑፍ፣የቃል/35%

1.6.5. በተቋሙ ማኔጅመንት ኮሚቴ የሚሞላ 15%


1.8. ዲኖች እና ምክትል ዲኖች ለደረጃ ኝድገት ለመወዳደር ሊያሟሉ የሚገባቸው
መስፈርቶች

 የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ዲኖችና ንክትል ዲኖች


አሰልጣኞችን/ኢንስትራክተሮችን እና የተቋሙን ማህበረሰብ በማስተባበር፣ የሥራ ዕቅድ
የማዘገጀት፣ የማስፈፀም፣ ክትትልና ድጋፍ የማድረግ ና ፣ የመገምገም ተግባሮችን ለማከነወን
እንዲሁም በአከባቢው ካሉ ባለድርሻ አካላት /Stake Holders/ እንዲሁም ከጥቃቅንና አነስተኛ
ተቋማት ጋር ጤናማ ግንኙነት በመፍጠር ተግበር ተኮር የትብብር ሥልጠና ደረጃውን በጠበቃ
ሁኔታ እንዲሰጥና የበቁ ሠልጣኞችን አፍርተው/ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን
ለእንዱስትሪው/ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት በማቅረብ የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማቱን ተወዳዳሪነት
የማረጋገጥ ከፍተኛ ኃላፊነት የሚጣልባቸው ናቸው፡፡
 በመሆኑም ይህንን የዲኖችና ምክትል ዲኖች ሰፊ የአመራርና የማስተባበር ብቃታቸውን በመለካት
ሌሎች አሰልጣኞች ከአንድ ደረጃ ወደ ቀጣዩ ደረጃ ለማደግ በሚመዘኑበት መስፈርት መሰረት
የደረጃ እድገታቸው ተፈፃሚ ይሆናል፡፡

04/22/2024 19
1.9. አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች ለደረጃ እድገት ለመቅረብ መሟላት ያለባቸው
መስፈርቶች
1.9. 1. የሲ ደረጃ አሰልጣኞች ለደረጃ እድገት ለመቅረብ መሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች
ተ. የውድድር ደረጃ ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች

በጀማሪ አሰልጣኝነት ቢያንስ 2 ዓመት ያገለገለ

የ2 ዓመት አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም አማካይ ውጤት 65% እና በላይ የሆነ


በቆይተው ካሰለጠናቸው ሠልጣኞች መካከል ቢያንስ እንደሀገር ለዓመቱ
ከጀማሪ አሰልጣኝነት ወደ ረዳት
1 አሰልጣኝነት የተቀመጠውን በምዘና የማብቃት ግብ በአቨሬጁ/አማካይ ያሟላ
በቆይታው ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ድጋፍ በመስጠት በምዘና
እንዲበቁ ማድረግና በተሻሻላ የአሰራር ስልት ሀብት እንዲያፈሩ ያደረገ፣
የትብብር ሥልጠናን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ያደረገ

04/22/2024 20
የቀጠለ

ተ. የውድድር ደረጃ ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች


በረዳትአሰልጣኝነት ቢያንስ ሁለት /2/ ዓመት ያገለገለ

የ2 ዓመት አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም አማካይ ውጤት 70% እና በላይ የሆነ

በቆይተው ካሰለጠናቸው ሠልጣኞች መካከል ቢያንስ እንደሀገር ለዓመቱ የተቀመጠውን


ከረዳት አሰልጣኝነት ወደ
2 አሰልጣኝነት በምዘና የማብቃት ግብ በአቨሬጁ/አማካይ ያሟላ

በቆይታው ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ድጋፍ በመስጠት በምዘና እንዲበቁ


ማድረግና በተሻሻላ የአሰራር ስልት ሀብት እንዲያፈሩ ያደረገ፣

የትብብር ሥልጠናን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ያደረገ


የቀጠለ
ተ. የውድድር ደረጃ ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች

በአሰልጣኝነት ሦስት/3/ ዓመት ያገለገለ

የ3ዓመት አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም አማካይ ውጤት 75% እና በላይ የሆነ

በቆይተው ካሰለጠናቸው ሠልጣኞች መካከል ቢያንስ እንደሀገር ለዓመቱ

ከአሰልጣኝነት ወደ ከፍተኛ የተቀመጠውን በምዘና የማብቃት ግብ በአቨሬጁ/አማካይ ያሟላ


3 አሰልጣኝነት

በዘርፉ ለሚገኙ ጀማሪና ረዳት አሠልጣኞች ተከታታይ ሙያዊ ድጋፍ ያደረገ

በሙያው ቢያንስ አንድ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝን በመደገፍ ሀብት


እንዲያፈሩ ያደረገ

የትብብር ሥልጠናን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ያደረገ


1.9. 2. የቢ ደረጃ አሰልጣኞች ና ኢንስትራክተሮች ለደረጃ እድገት ለመቅረብ መሟላት የሚገባቸው
መስፈርቶች

ተ. የውድድር ደረጃ ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች



በጀማሪ ኢንስትራክተርነት ቢያንስ 2 ዓመት ያገለገለ

የ2 ዓመት አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም አማካይ ውጤት 75% እና በላይ የሆነ

በቆይተው ካሰለጠናቸው ሠልጣኞች መካከል ቢያንስ እንደሀገር ለዓመቱ


የተቀመጠውን በምዘና የማብቃት ግብ በአቨሬጁ/አማካይ ያሟላ
ከጀማሪ ኢንስትራክተርነት ወደ ረዳት
1 ኢንስትራክተርነት

ቢያንስ አንድ ቴክኖሎጂ በመኮረጅ ለጥ/አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ አሸጋግሮ ሀብት


እንዲያፈሩ ያደረገ

ለሲ- ደረጃ አሰልጣኞች ተከታታይ ሙያዊ ድጋፍ ያደረገ


የትብብር ሥልጠናን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ያደረገ
የቀጠለ

ተ.ቁ የውድድር ደረጃ ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች

በረዳት ኢንስትራክተርነት ቢያንስ 2 ዓመት ያገለገለ

የ2 ዓመት አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም አማካይ ውጤት 80% እና በላይ


የሆነ

በቆይተው ካሰለጠናቸው ሠልጣኞች መካከል ቢያንስ እንደሀገር ለዓመቱ


2
ከረዳት ኢንስትራክተርነት ወደ የተቀመጠውን በምዘና የማብቃት ግብ በአቨሬጁ/አማካይ ያሟላ
ኢንስትራክተርነት
ቢያንስ አንድ ቴክኖሎጂ በመኮረጅ ለጥ/አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ አሸጋግሮ
ሀብት እንዲያፈሩ ያደረገ

ለሲ- ደረጃ አሰልጣኞች ተከታታይ ሙያዊ ድጋፍ ያደረገ

የትብብር ሥልጠናን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ያደረገ

04/22/2024 24
የቀጠለ

ተ.ቁ የውድድር ደረጃ ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች

በኢንስትራክተርነት ቢያንስ 3 ዓመት ያገለገለ

የ3ዓመት አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም አማካይ ውጤት 85% እና በላይ የሆነ

በዘርፉ ለሚገኙ አሠልጣኞች፣ ኢንስትራክተሮችና ረዳት ኢንስትራክተሮች


ተከታታይ ሙያዊ ዲጋፍ ያደረገ
ከኢንስትራክተርነት ወደ መሪ
3 ኢንስትራክተርነት በቆይተው ካሰለጠናቸው ሠልጣኞች መካከል ቢያንስ እንደሀገር ለዓመቱ
የተቀመጠውን በምዘና የማብቃት ግብ በአቨሬጁ/አማካይ ያሟላ

በትኩረት ዘርፎች ችግር ፈቺ የሆኑ ቢያንስ 3 ምርጥ ቴክኖሎጂዎችን በመኮረጅ


ለጥ/አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ አሸጋግሮ ሀብት እንዲያፈሩ ያደረገ

የትብብር ሥልጠናን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ያደረገ

04/22/2024 25
የቀጠለ

ተ.ቁ የውድድር ደረጃ ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች


በከፍተኛ ኢንስትራክተርነት 4 ዓመት ያገለገለ

የ4ዓመት አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም አማካይ ውጤት 85% እና በላይ የሆነ

በዘርፉ ለሚገኙ አሠልጣኞች፣ ኢንስትራክተሮችና ረዳት ኢንስትራክተሮች


ተከታታይ ሙያዊ ዲጋፍ ያደረገ

በቆይተው ካሰለጠናቸው ሠልጣኞች መካከል ቢያንስ እንደሀገር ለዓመቱ


ከከፍተኛ ኢንስትራክተርነት ወደ የተቀመጠውን በምዘና የማብቃት ግብ በአቨሬጁ/አማካይ ያሟላ
4 መሪ ኢንስትራክተርነት

በትኩረት ዘርፎች ችግር ፈቺ የሆኑ ቢያንስ 3 ምርጥ ቴክኖሎጂዎችን


በመኮረጅ ለጥ/አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች አሸጋግሮ ሀብት እንዲያፈሩ ያደረገ

በዘርፉ በስሩ ለሚገኙ አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች ተከታታይ ሙያዊ


ድጋፍ የሰጠ
የትብብር ሥልጠናን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ያደረገ
04/22/2024 26
1.9.3. የኤ-ደረጃ ኢንስትራክተሮች ለደረጃ እድገት ለመቅረብ ሊያሟሉ የሚገባቸው
ተ.ቁ የውድድርመስፈርቶች
ደረጃ ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች
በኢንስትራክተርነት ለ3 ዓመት ያገለገለ

የ3 ዓመት አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም አማካይ ውጤት 90% እና በላይ የሆነ

በዘርፉ ለሚገኙ የሲ- ደረጃ አሠልጣኞች እና የቢ- ደረጃ ኢንስትራክተሮች


ተከታታይ ሙያዊ ዲጋፍ ያደረገ
ከኢንስትራክተርነት ወደ ከፍተኛ በቆይተው ካሰለጠናቸው ሠልጣኞች መካከል ቢያንስ እንደሀገር ለዓመቱ
1 ኢንስትራክተርነት
የተቀመጠውን በምዘና የማብቃት ግብ በአቨሬጁ/አማካይ ያሟላ

በትኩረት ዘርፎች ችግር ፈቺ የሆኑ ቢያንስ 3 ምርጥ ቴክኖሎጂዎችን


በመኮረጅ/በማሻሻል ለጥ/አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች አሸጋግሮ ሀብት
እንዲያፈሩ ያደረገ
የትብብር ሥልጠናን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ያደረገ

04/22/2024 27
የቀጠለ

ተ. የውድድር ደረጃ ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች



በከፍተኛ ኢንስትራክተርነት 4 ዓመት ያገለገለ

የ4 ዓመት አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም አማካይ ውጤት 95% እና በላይ የሆነ


በዘርፉ ለሚገኙ አሠልጣኞች ኢንስትራክተሮች ተከታታይ ሙያዊ ዲጋፍ
ያደረገ
ከከፍተኛ ኢንስትራክተርነት ወደ መሪ በቆይተው ካሰለጠናቸው ሠልጣኞች መካከል ቢያንስ እንደሀገር ለዓመቱ
2 ኢንስትራክተርነት
የተቀመጠውን በምዘና የማብቃት ግብ በአቨሬጁ/አማካይ ያሟላ

በትኩረት ዘርፎች ችግር ፈቺ የሆኑ ቢያንስ 4 ምርጥ ቴክኖሎጂዎችን


በመኮረጅ/በማሻሻል ለጥ/አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች አሸጋግሮ ሀብት እንዲያፈሩ
ያደረገ
የትብብር ሥልጠናን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ያደረገ
የቀጠለ

ተ.ቁ የውድድር ደረጃ ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች

በመሪ ኢንስትራክተርነት 4 ዓመት ያገለገለ


የ4 ዓመት አጠቃላይ የስራ አፈፃፀም አማካይ ውጤት 95% እና በላይ የሆነ

በዘርፉ ለሚገኙ የሲ፣ የቢ እና የኤ ደረጃ አሠልጣኞች/ ኢንስትራክተሮች


ተከታታይ ሙያዊ ዲጋፍ ያደረገ

በቆይተው ካሰለጠናቸው ሠልጣኞች መካከል ቢያንስ እንደሀገር ለዓመቱ


ከመሪ ኢንስትራክተርነት ወደ ዋና የተቀመጠውን በምዘና የማብቃት ግብ በአቨሬጁ/አማካይ ያሟላ
3 ኢንስትራክተርነት

የህብረተሰቡን የኑሮ ደረጃ ሊያስለውጡ የሚችሉ 4 እና በላይ ቴክኖሎጂዎችን


በመኮረጅና በማሻሻል ለጥ/አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ለህብረተሰቡ
በማስተላለፍ በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በህብረተሰቡ ላይ ካፈረው
ሀብት አንፃር አመርቂና ተጨባጭ ለውጥ ያመጣ

የትብብር ሥልጠናን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ያደረገ


1.9.4. የአሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች የደሞዝ ደረጃ ዕድገት አሰጣጥ ሂደት

 የአሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች የደሞዝ ደረጃ እድገት አሰጣጥ ሂደት ዓይነቶች እንደሚከተለው ይሆናል፡፡

1.9.4.1. ከአንድ ደረጃ ወደሚቀጥለው የደረጃ ተዋረድ አምዳዊ እድገት/Vertical Career/ የሚሰጠው
ለየደረጃው በተቀመጡት የማቆያ ጊዜያትና በተገኙት የሥራ የግምገማ ውጤቶች ላይ ተመስርቶ የሚከናወን
ይሆናል፡፡

1.9.4.2. የጎናዊ የእርከን ደሞዝ ጭማሪ/Horizontal Career/ የሚሰጠው አጠቃላይ የመንግስት ሠራተኞች
እርከን ጭማሪ በሚለቀቅበት ጊዜ ይሆናል፡፡

1.9.4.2.1. ከጥር 1 እስከ ሰኔ 30 መካከል አዲስ ለሚቀጠሩ ወይም በደረጃ ዕድገት ሁለት እርከንና በላይ ያገኙ
ወይም በዲሲፕሊን ከደረጃ ዝቅ ያሉ አሰልጣኞች መደበኛ የደሞዝ ጭማሪ የሚያገኙት ከሐምሌ 1
ቀን ጀምሮ ነው፡፡

1.9.4.2. በሐምሌ 1 እና ታህሳስ 30 መካከል አዲስ የተቀጠሩ ወይም በደረጃ እድገት ከሁለት እርከንና ከዚያ
በላይ ያገኙ ወይም በዲሲፕሊን ከደረጃ ዝቅ ያሉ አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች መደበኛ ጭማር
የሚያገኙበት ከጥር 1 ጀምሮ ይሆናል፡፡

04/22/2024 30
1.9.4.3. የትምህርት ማሻሻያ የደሞዝ ዕድገት ጭማሪ አሰጣጥ

 የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ደመወዝ አከፋፈል በሀገር ውስጥ እውቅና ካላቸው ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እና
የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ኢንስቲትዩት እንዲሁም ከሀገር ውጪ ትምህርታቸውን አሻሽለው
ለሚመለሱ አሰልጣኞች ከዚህ በታች በተቀመጠው ሰንጠረዥ መሰረት የሚፈፀም ይሆናል፡፡

ከትምህርት ማሻሻል በኋላ የሚደርሱበት አዲሱ


ተ.ቁ ከትምህርት ማሻሻል በፊት የነበሩበት ደረጃ ምርመራ
ደረጃ

1 የ C- ጀማሪ አሰልጣኝ B - ጀማሪ ኢንስትራክተር


2 የ C- ረዳት አሰልጣኝ B- ጀማሪ ኢንስትራክተር
3 የ C- አሰልጣኝ B-ረዳት ኢንስትራክተር በተቋሙ ፍላጎትና ዕቅድ
መሰረት ወደ ከፍተኛ
4 የ C- ከፍተኛ አሰልጣኝ B-ኢንስትራክተር ትምህርት ተቋም ተልከው
ትምህርታቸውን አሻሽለው
5 የ B- ጀማሪ ኢንስትራክተር A-ኢንስትራክተር ሲመለሱ በሙያው
6 የ B- ረዳት ኢንስትራክተር A-ኢንስትራክተር በሚጠበቀው ደረጃ በሚዘና
ብቃታቸውን ማረጋገጥ
7 የ B- ኢንስትራክተር A-ኢንስትራክተር ይጠበቅባቸዋል፡፡
8 የ B- ከፍተኛ ኢንስትራክተር A- ከፍተኛ ኢንስትራክተር
9 የ B- መሪ ኢንስትራክተር A- መሪ ኢንስትራክተር

04/22/2024 31
1.10. በየደረጃው የሚፈፀም የደረጃ እድገት ሥርዓት

የአሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች የደረጃ እድገት በተቋም የደረጃ ዕድገት ኮሚቴ ተቋቁሞ ለደረጃ እድገት የሚቀርቡ
አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች ውድድሩ በተቋም ደረጃ ከተከናወነ በኋላ ተግባራዊ የሚሆነው በተቋሙ ማኔጅመንት
ታይቶ ለተቋሙ ቦርድ ሲፀድቅ ነው፡፡

1.10.1. የአሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች የደረጃ ዕድገት ኮሚቴ አባላት


የተቋም የውጤት ተኮር ሥልጠና ምክትል ዲን ------------------ ሰብሳቢ
የተቋም ቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንዱስትሩ ኤክስቴንሽን ም/ዲን --- አባል
የአሰልጣኙ ዲፓርትመንት ተጠሪ --------------------------------- አባል
የመምህራን ተወካይ ----------------------------------------------- አባል
የሰው ሀይል አስተዳደር የሥ/ሂደት ባለቤት ------------------------ ፀሓፊ
የሰው ሀይል አስተዳደር የሥ/ሂደት አንድ ባለሙያ ------------------ አባል
የሴት አሰልጣኞች ተወካይ ------------------------------------------ አባል
1.10.2. የአሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች የደረጃ እድገት ኮሚቴ ተግባርና ኀላፊነት

•በዘመኑ ለደረጃ እድገት የሚቀርቡ አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች ለደረጃ እድገቱ ከመቅራባቸው በፊት
ያከናወኗቸውን ተጨባጭ ተግባራት የሚገልፅ ዝርዝር መረጃ በየተቋሙ በሚመለከተው ምክትል ዲን አማካኝነት
ለኮሚቴው ይቀርባል፡፡

•ተቋሙ በየዘመኑ ለደረጃ እድገት ውድድር የሚቀርቡትን አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች በዝርዝራቸው ለይተው
በግልፅ ማስታወቂያ ያሳውቃል፡፡ በሥራ ምክንያት በአካባቢው የሌሉ አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች ቢኖሩ
ማረጃቸውን የተቋሙ የሰው ኃይል አስተዳደር ለኮሚቴው ይቀርባል፡፡

•የቀረበው መረጃ ተአማኒነቱን ኮሚቴው ያረጋግጣል፡፡

•ኮሚቴው ተገቢ ቃለጉባኤ በመያዝ ለደረጃ እድገቱ የተቀመጠውን መስፈርት ያሟሉትን በየደረጀው የዕድገት መሰላል
መሠረት አጣርቶ ከአስፈላጊ ማስረጃ ጋር ለተቋሙ ማኔጅመንት ያስተላልፋል፡፡

•የተቋሙ ማኔጅመንት ከደረጃ እድገት ኮሚቴ የቀረበለትን ዝርዝር መረጃ ካጣራና ከገመገማ በኋላ ለተቋሙ ቦርድ
አቅርቦ ያፀድቃል፡፡
1.11. የዲኖች እና ምክትል ዲኖች የደረጃ እድገት አፈፃፀም

ዲኖች እና ምክትል ዲኖች በአሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች የደረጃ እድገት መሰላል በደረሱበት ደረጃ ላይ ደረጃው
የሚያስገኝላቸውን ደመወዝ ያገኛሉ፣ በሚያሰዩት ተጨባጭ ጥረትና ውጤት እንዲሁም በቆይታቸው ወቅት ለዓመቱ
የተቀመጠውን የሙያ ብቃት ምዘና ግብ አማካይ ያሟሉ በአሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች የደረጃ እድገት መሰላል
መሰረት ወደሚቀጥለው ደረጃ ያድጋሉ፡፡

1.11.1. የተቋም ምክትል ዲኖች እና ሥልጠና ዘርፍ አስተባባሪዎች የደረጃ እድገት አፈፃፀም

የተቋም ምክትል ዲኖችና ሥልጠና ዘርፍ አስተባባሪዎች የደረጃ እድገት ኮሚቴ አባል ሆነው ዕድገቱ የሚመለከታቸው
ከሆነ ከኮሚቴው አባልነት ወጥተው በሌሎች የኮሚቴው አባላት እድገታቸው እንዲታይ ይደረጋል፡፡

04/22/2024 34
1.12. የአቤቱታ እና ቅሬታ አቀራራብ ሂደት

1.12.1. አሠልጣኞችና ኢንስትራክተሮች በየደረጀው ባለ የደረጃ እድገታቸው አፈፃፀም ላይ ቅሬታ ካላቸው


አቤቱታቸውን በሲቪለ ሰርቪስ የቅሬታ አቀራራብ አሰራር መሰረት በየደረጀው ላሉ የሚመለከታቸው አካላት
ቀርቦ በተገቢው መረጃ ላይ ተመስርቶ ውሳኔ እንዲያገኝ ይደረጋል፡፡

በዚህም መሠረት፣

ሀ. የቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜን በተመለከተ

 ቅር የተሰኙ አሰልጣኞችና ጉዳዩን ለቅርብ አለቃ ወይም ለሚመለከተው ኋላፊ በማቅረብ ውይይት
ኢንስትራክተሮች በተደረገበት ቀን ጀምሮ በአስር የሥራ ቀናት ውስጥ ማመልከቻቸውን ለመስሪያ ቤቱ የቅሬታ
አጣሪ ኮሚቴ ማቅረብ ይገባቸዋል፡፡

 ከፍ ሲል በተወሰነው የጊዜ ገደብ ውስጥ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት የቅሬታውን ማመልከቻ ሊያቀርብ ያልቻለ
ከሆነ ከአቅም በላይ የሆነው ምክንያት በተወገደ በአስር የሥራ ቀናት ውስጥ ማመልከቻውን ሊያቀርብ ይችላል፡፡

04/22/2024 35
ለ. ቅሬታ ማጣራት
የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ

የቅሬታ ማመልከቻውንና አግባብ ያለቸውን ማስረጃዎች በመመርመር፣

ጉዳዩ የሚመለከታቸውን ሁሉ በማነጋገር

አግባብነት ያላቸው ህጎች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎችና የአሰራር ልምዶችን በማገነዘብ የቀረበለትን


ቅሬታ ያጣራል፡፡ የምርመራውን ውጤትና የውሳኔ ሀሳብ የያዘ ሪፖርት ለተቋሙ የበላይ አመራር
ከአንድ ወር ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ በማቅረብ ያስወስናል፡፡ የበላይ አመራሩም የኮሚቴውን ውሳኔ
የማፅደቅ ወይም በቂ ምክንያት ሲኖረው የተለየ ውሳኔ የመስጠት ወይም ኮሚቴው እንደገና ጉዳዩን
እንዲያጣራ ማዘዝ ይችላል፡፡

1.12.2. አቤቱታው የአስተዳደራዊ አፈፃፀም ችግር የሚኖረው ሆኖ ከተገኛ ደረጃውን በመጠበቅ


እስከ ክልሉ የመልካም አስተዳደርና ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ልቀርብ ይችላል፡፡
1.13. ልዩ ልዩ ሁኔታዎች

 አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች ከማሰልጠን ሥራ መደብ በራሳቸው ፍላጎት ወደ ቴ/ሙ/ት/ሥ/


ጽ/ቤት/ቢሮ/ኮሚሽን/ኤጀንሲ ተመድበው ከሰሩ በዚያ ደረጃ የሚሰጠው ግምገማ በተቋም ውስጥ ከሚከናወኑ
ተግባራት ጋር ተመሳሳይነት ስለሌለው ምዘናው ለደረጃ እድገት ውድድር አይያዝላቸውም፡፡

 የእያንዳንዱ የአሰልጣኝና ኢንስትራክተር የደረጃ እድገት የራሱ የቆይታ ጊዜ ያለው ስለሆነ አሰልጣኞች
/ኢንስትራክተሮች በደረሱበት ደረጃ የቆይታ ጊዜአቸውን ሳያሟሉ በተለያዩ ምክንያቶች ከሥራ ገበታቸው
ተለይተው ቆይተው ሲመለሱ መጀመሪያ ከሥራ ገበታቸው ከመሄዳቸው በፊት በነበሩበት ደረጃ ተመልሰው የቆይታ
ጊዜያቸውን ጠብቃውና ተገምግመው የደረጃ እድገት ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡

 አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች በጤና ችግር ምክንያት በማሰልጠን ሥራ ሊቀጥሉ ካልቻሉ ይኻው በሀኪም ቦርድ
ሲረጋገጥ የቴ/ሙ/ት/ሥ/ጽ/ቤት/ቢሮ/ኮሚሽን/ኤጀንሲ ቀርቦ በሌላ ሥራ መደብ ቦታ ካለ በቋሚነት ወይም
በጊዜያዊነት ተዘውረው እንዲሰሩ ሊያደርግ ይችላል፡፡ ከዚህ በኋላ የደረጃ እድገቱም የሚታይላቸው ከህመሙ
ተሽሎኣቸው ወደ አሰልጣኝነት ወይም ኢንስትራክተርነት የሥራ መደብ ተመልሰው ሲመደቡና ዕድገቱ የሚፈልጋውን
የቆይታ ጊዜ ሲያሟሉ የእድገቱ ተጠቃሚ ይሆናሉ፡፡
የቀጠለ

 አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች በራሳቸው ፍላጎት ወደ ሌላ መሥሪያ ቤት ከተዛወሩና ከተወሰነ ጊዜ ቆይታ በኋላ ወደ


አሰልጣኝነት ሙያ ለመመለስ ጥያቄ ቢያቀርቡ የሰለጠኑበት ሙያ በተቋሙ ውስጥ ሥልጠና የሚሰጥበት ከሆነና
የአሰልጣኝ እጥረት ካለ በሥራ ላይ በነበሩበት ወቅት ሲሰጡ የነበሩት ሥልጠና ውጤታማ መሆኑ ተጣርቶና በጀት
መኖሩ ተረጋግጦ ወደ ሥራ ተመልሰው ሊመደቡ ይችላሉ፡፡ ሲመለሱም ቀደም ስል በነበረበት የሙያ ደረጃ ይሆናል፡፡
ነገር ግን የትምህርት ደረጃ ለውጥ የሚመጣ ከሆነ የቀድሞ አገልግሎትና የሙያ ደረጃ ተገናዝቦ በሚመጥነው ደረጃ
ይመደባሉ፡፡

 አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች ከአንድ ደረጃ ወደሚቀጥለው ደረጃ ለማደግ በሚያደርጉት ሂደት በመጀመሪያው
የእድገት ውድድር ከወደቁ በ2ኛ ጊዜ ለውድድር ለመቅረብ የተከታዩን አንድ አመት ሁለት የግምገማ ውጤት
በማካተት ባሉበት ደረጃ ለአንድ ጊዜ ብቻ ይሆናል፡፡ ወደሚቀጥለው ደረጃ ካለፉ ለሚቀጥለው ደረጃ ዕድገት
የሚቀርቡት ዕድገቱን ካገኙበት ቀን ጀምሮ የመቆያ ጊዜ ጠብቆ ይሆናል፡፡
የቀጠለ

ይህም በአሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች የደረጃ እድገት ሂደት ውስጥ ለአንድ ጊዜ ብቻ ሊሰጥ የሚችል ዕድል ይሆናል፡፡
በተጨማሪም ካሉት ደረጃዎች በአንዱ ላይ ብቻ የሚሰጥ ዕድል ሆኖ በሌለው ደረጃ ላይ በድጋሚ የዚህ አይነቱ ዕድል
ተጠቃሚ ሊሆኑ አይችሉም፡፡ የዚህ ዓይነት ሁኔታ ሲያጋጥም የማቆያ ጊዜኣቸውን እየጠበቁ ለእድገት የሚቀርቡ
ይሆናል፡፡ ተወዳድረው ካላለፉ ባሉበት ደረጃ የተሰጣቸውን የቆይታ ጊዜ ጠብቀው ሊቀርቡ ይችላሉ ማለት ነው፡፡

ለዲኖችና ም/ዲኖች አሠልጣኞችና ኢንስትራክተሮች የሚሰጥ የደረጃ ዕድገት ለሥራ ረስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች
ባለሙያዎችን ለመሳብና ለማናቃቃት ከሚደረጉ የአበል ክፍያዎች እና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች ጋር ግንኙነት
አይኖረውም፡፡

04/22/2024 39
የቀጠለ

 የአሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች የደረጃ አሰጣጥ በአሰልጣኞችና ኢንስተራክተሮች መካከል የሚደረግ ውድድር


ሳይሆን በተቀመጠው የመመዘኛ መስፈርት ስታንዳርድ በሆነ መለኪያ የሚመዘኑበት ወይም የሚለኩበትና
የተቀመጠውን ስታንዳርድ መለኪያ ሲያሟሉ ለዕድገት የሚቀርቡበት ሂደት ነው፡፡

 የአሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች ለደረጃ እድገት የሚወዳደሩት ከተቀጠሩበት ቀን ጀምሮ የቆይታ ጊዜያቸውን


ሲያሟሉ ሆኖ የደረጃ እድገት ውድድሩ የሚካሄደው በየአመቱ ሓምሌ እና ጥር ወር ነው፡፡ የግምገማ
ማጠናቃቂያና የደረጃ እድገት ማግኛ ወቅት በየተቋሙ የግምገማ ጊዜ ከሓምሌ 1 እስከ ሰኔ 30 ሲሆን አሰልጣኞችና
ኢንስትራክተሮችም በደረሱባቸው ደረጃ ካላቸው ቆይታ አኳያ ይሆናል፡፡

 በዲሲፕሊን ጉዳዮች ላይ የሚሰጡ ውሳኔዎች የመንግስት ሠራተኞች የዲሲፕሊን አፈፃፀም ደንብን መሠረት
በማድረግ የሚፈፀም ይሆናል፡፡

 ለሙያ ብቃት ምዘና የተሰጠ ማስረጃ የሚያገለግለው የልህቀት ማዕከሉ ለወሰነው የቆይታ ጊዜ ብቻ ነው፡፡

04/22/2024 40
የቀጠለ

 የማህበረሰብ ክህሎት ማሰልጠኛ ማዕከላት በገበያ ፍላጎት ላይ በመመርኮዝ የደረጃ I እና II እንዲሁም አጫጭር
ሥልጠናዎችን በመስጠት በርካታ ስራ አጥ ዜጎችን አብቅቶ ወደ ስራ ለማሰማራት የሚያግዙ ማዕከላት ሆነው
በሲ- ደረጃ ከፍተኛ አሰልጣኝ የሚመሩ ይሆናሉ፡፡

 ዲኖች እና ምክትል ዲኖች በየጊዜው የሚያስመዘግቡት የስራ አፈፃፀም ውጤት ከከፍተኛ ነጥብ በታች ሆኖ
ከተገኛ በኃላፊነት ሊቀጥሉ አይችሉም፡፡

 ለደረጃ እድገት የሚቀርቡ አሰልጣኞችና ኢንስትራክተሮች አገልግሎት የሚያዘው በመንግስት ተቋም ውስጥ
በአሰልጣኝነት ያገለገሉበት ጊዜ ብቻ ታሳቢ ተደርጎ ይሆናል፡፡

 በግል ተቋማት፣ መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማት ወይንም በቢሮ በመስራት የተገኛ የስራ ልምድ በተቋም ውስጥ
ለሚደረግ የደረጃ እድገት ውድድር አይያዝም፡፡ እንዲሁም በተለያየ ምክንያት ከሥራ ቦታ የተለየበት ጊዜ ወይም
ለትምህርትና ሥልጠና ተብሎ ከ3 ወር በላይ የተሰጠ ፍቃድ ለደረጃ እድገት የቆይታ ጊዜ ታሳቢ አይሆንም፡፡

04/22/2024 41
04/22/2024 42

You might also like