Download as pptx, pdf, or txt
Download as pptx, pdf, or txt
You are on page 1of 25

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ (ኢምገ)

የኤሌክትሮኒክ ግብይት ስርአትና ደንብ


የሥልጠና ፕሮግራም

2013 ዓ .ም.
የምርት ገበያዉ የህግ ማዕቀፍ
• የምርት ገበያዉ የህግ ማዕቀፍ እና አላማዎች
• የምርት ገበያዉ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 550/1999 የተቋቋመ
ድርጅት ነው፡፡
• የምርት ገበያዉ የተቋቋመዉ በአዋጁ አንቀጽ 6 ሥር የተዘረዘሩትን በርካታ ዓላማዎችን
መሠረት በማድረግ ሲሆን ከዓላማዎቹም ውስጥ፡
የአምራቾችን፣ የገዢዎችን፣ አቅራቢዎችንና ፍላጎት በማርካትና የኢትዮጵያ አነስተኛ አምራቾች
የገበያ ተሳትፎን በማሳደግ ዉጤታማ፣ ግልጽ አሠራርን የተከተለና በሥርዓት የሚመራ
የግብይት ሥርዓት መፍጠር፤
በምርት ገበያው የሚደረጉ ግብይቶች ካልተገደቡ ድርጊቶችና የህግ ጥሰቶች የራቁ በማድረግ
የምርት ገበያውን የግብይት ስረአት እና የግብይቶችን ጤናማነት ማስጠበቅ እንዲሁም
ተገበያዮች በምርት ገበያው ላይ በሚካሄዱ ግብይቶች ላይ እምነት እንዲኖራቸው ማድረግ፤
የምርት ደረጃ ምስክር ወረቀትንና ዋስትና ያለዉ የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ መሠረት በማድረግ
ግብይት ማካሄድ፤
ግዴታን ባለመወጣት የሚያጋጥሙ አደጋዎችን ለመቀነስ በምርት ገበያዉ የሚከናወኑ
ግብይቶችን ክፍያና ርክክብ የመፈጸም፤ እና
ወቅታዊ የገበያ መረጃዎችን ለህዝቡ ማቅረብ የሚሉት ይገኙበታል ፡፡
• በምርት ገበያው የማቋቋሚያ አዋጅ አንቀጽ 6 ዉስጥ የተቀመጡትን ዓላማዎች
ለመተግበር እንዲረዳ የምርት ገበያዉ አሰራር የሚመራበትን ዝርዝር ደንብ አዉጥቶ
በየጊዜው አስፈላጊው ማሻሻያ እየተደረገበት በሥራ ላይ ይገኛል፡፡
የምርት ገበያው ደንብ የምርት ገበያዉ ስራ አመራር፣ ስለምርት ገበያ አባልነት፣
ስለተገበያዮች፣ ስለማከማቻ መጋዘን፣ ክፍያና ርክክብ፣ የገበያ መረጃ ስርጭት፣
ስለዲሲፕሊን እና አፈጻጸም፣ ቁጥጥር እንዲሁም ሌሎች ከግብይት ጋር ተያያዥነት
ያላቸው ጉዳዮች የሚመሩበትን ዝርዝር ህግ አስቀምጧል፡፡
የግብይት ስርዓት

በምርት ገበያው የሚደረግ ግብይት ምርት ገበያው በሚወስነው አኳኋንና የጊዜ ሰሌዳ
መሠረት
 በመገበያያ መድረክ ድምጽን በማስተጋባት ወይም
 በኤሌክትሮኒክ ግብይት መድረክ ላይ ተወዳዳሪነትን በሚጋብዝ ሁኔታ ይካሄዳል፡፡
(አንቀጽ 5.1፣ 5.3)

•የኤሌክትሮኒክ የግብይት፡- የኤሌክትሮኒክ ግብይት የምርት ገበያው በሚያዘጋጀዉ


የኤሌክትሮኒክ መገበያያ እና በሚወስነው ጊዜ መሠረት በኤሌክትሮኒክ የግብይት ስርዓት
ተወዳዳሪነትን በሚጋብዝ ሁኔታ ይካሄዳል፡፡ (አንቀጽ 5.1፣ 5.3)
 በምርት ገበያው በ2 መንገድ በኤሌክትሮኒክስ አማካኝነት ግብይት ይፈጸማል፡-
•1. ኢትሬድ (e-Trade): በዚህኛው የመገበያያ መንገድ እንደ ሰሊጥ፣ አኩሪ አተር፣
ቦሎቄና የመሳሰሉት የቅባትና ጥራጥሬ እህሎች ናቸው፡፡
•2. የኤልክትሮኒክስ ጨረታ (eauction): በዚህኛው መንገድ የቡና ምርት
የሚገበያይበት ሲስተም ነው፡፡
የኤሌክትሮኒክ የግብይት ክፍለ ጊዜያት

• የኤሌክትሮኒክ የግብይት ክፍለ ጊዜ የሚከተሉትን ያካትታል፤ (አንቀጽ 5.2.3)


ቅድመ መክፈቻ የግብይት ክፍለ ጊዜ - ትዕዛዝ ማስገባት ይጀመራል፣ የገቡ ትዕዛዞች
መሰረዝ ይቻላል፣ ግብይት አይፈቀድም፤
መሰረዝ የማይቻልበት ቅድመ መክፈቻ ክፍለ ጊዜ - ትዕዛዝ ማስገባት ይቻላል
ነገርግን ትዕዛዝ መሰረዝ ወይም ማሻሻል አይቻልም፣ ግብይት አይፈቀድም፣
ክፍት የግብይት ክፍለ ጊዜ – የተላኩ ትዕዛዞች የሚዛመዱበት የግብይት ክፍለ ጊዜ
ነው፣ በዚህ ክፍለጊዜ ትእዛዙ ከመፈጸሙ በፊት ትእዛዝ ማስገባት፣ ማሻሻል እና
መሰረዝ ይቻላል፣
ዝግ የግብይት ክፍለ ጊዜ – ትዕዛዝ ማስገባት፣ ማሻሻል ወይም መሰረዝ
የማይቻልበት ዝግ የግብይት ክፍለ ጊዜ ነው፣
ማጠናቀቂያ እና መሰናጃ ክፍለ ጊዜ – ግብይቱ ከተጠናቀቀ/ካበቃ በኋላ ገበያው
ዝግ ሆኖ የሚቆይበት እና አባላትም ትዕዛዝ ማስገባት፣ ማሻሻል፣ ማየት ወይም
መሰረዝ የማይችሉበት ጊዜ ነው፡፡ በዚህ ጊዜ ምርት ገበያው የተለያዩ የቢሮ
ስራዎችን ማጠናቀቅና እስከ እለት ድረስ ብቻ የሚጸና ትእዛዝ ከሲስተም ማውጣት
የመሳሰሉትን የጥገና ስራዎች ያከናውናል፡፡
ወደ ኤልክትሮኒክስ ግብይት መድረክ የመግባት ፈቃድ

• የተፈቀደላቸው ሰዎች ብቻ አባላትን ወክለው ወደ ኤሌክትኖኒክ መገበያያ መድረክ መግባት ይችላሉ፡፡


ማንኛውም ሰው ኤሌክትኖኒክ ግብይት ተወካይ መሆን የሚችለው በግብይት ፈጻሚነት ዕውቅና ካገኘ፣ በምርት ግብይት
በኤሌክትኖኒክ ግብይትና ምርት ገበያው በሚጠይቃቸው ሌሎች የብቃት ማረጋገጫ ስልጠናዎች የወሰደና ፈተናውን በሚገባ
ያለፈ እና በአባሉ የተሰጠ የሹመት ደብዳቤ ካቀረበና ይህም በምርት ገበያው ከጸደቀ ነው፡

የኤሌክትሮኒክ ግብይት ተርሚናል የሥራ ማከናወኛ መሣሪያ ተጠቃሚን መለየት (አንቀጽ 5.3.3)
እያንዳንዱ ተጠቃሚ የራሱ መለያ ቁጥር ይኖረዋል፡፡ የኤሌክትሮኒክ ግብይት ተወካይ እና የራሱን መመሪያ
የሚያስገባ ደንበኛ የተጠቃሚ መለያ ምዝገባ ሁልጊዜ የጸና እና ትክክለኛ መሆኑን ማረጋገጥ የአባሉ ኃላፊነት
ነው፡፡
 እያንዳንዱ የኤሌክትሮኒክ የግብይት ተወካይ ኤሌክትሮኒክ የግብይት
መድረኩን ለመጠቀም ልዩ መለያ ቁጥር እና የይለፍ ቃል (Password)
መጠቀም አለበት፡፡
 የኤሌክትሮኒክ ግብይት ተወካይ ከተጠቃሚው ውጭ ሌላ ሰው የእሱን
መለያ ቁጥር እና የይለፍ ቃል (Password) ተጠቅሞ ትዕዛዝ ወይም
መመሪያ እንዲያስገባ መፍቀድ የለበትም፡፡
 የኤሌክትሮኒክ ግብይት ተወካይ የሚጠቀምበትን የይለፍ ቃል (Password)
ለማንኛውም ሰው (ለምሳሌ ለስራ ባልደረባ ፣ ለቤተሰብ አባላት)
ማሳወቅ የለበትም፡፡
 የኤሌክትሮኒክ ግብይት ተወካይ የሚጠቀምበትን የይለፍ ቃል (Password)
ሌሎች ሰዎች ሊያዩት በሚችሉበት ቦታ ማስቀመጥ የለበትም፡፡
 የኤሌክትሮኒክ ግብይት ተወካይ የሚጠቀምበትን የይለፍ ቃል
(Password) ሌሎች ሰዎች አውቀውት ሊሆን ይችላል ብሎ ስጋት
ካደረበት ለግብይት ስርዓት ቁጥጥር ክፍል ለአባላት ሁኔታውን
በማሳወቅ የመለያ ቁጥሩን ማስቀየር አለበት ፡፡
የኤሌክትሮኒክ ግብይት ድጋፍ (አንቀጽ 5.3.4)
• የምርት ገበያው ኤሌክትሮኒክ የግብይት ስርዓት ቁጥጥር ክፍል ለአባላት እና
ኤሌክትሮኒክ የግብይት ተወካዮች ድጋፍ እና ለሚከሰቱ ችግሮችም መፍትሄ
ይሰጣል፡፡ ምርት ገበያው በተወሰነ ጊዜ ለዚሁ ጉዳይ በተመደበ ስልክ ወይም
በሌላ የኤሌክትሮኒክ መንገድ ድጋፍ ሊሰጥ ይችላል፡፡

የግብይት ደንቦች

የግብይት ክፍለ ጊዜ መክፈቻ እና መዝጊያ ጥሪ (አንቀጽ 5.4.1 እና 5.4.2) ፤


ምርት ገበያው እያንዳንዱ የኤልክትሮኒክ ግብይት ክፍለጊዜ መቼ
እንደሚከፈት እና መቼ እንደሚዘጋ በየጊዜው በቅድሚያ ያሳውቃል፡፡
ፋንተም ትዕዛዝ ወይም መመሪያ (አንቀጽ 5.3.5)

 ፋንተም ትዕዛዝ ወይም መመሪያ ማለት 1) የምርት ገበያው የግብይት ስርዓት በጉድለት
ወይም በብልሽት የገባው መረጃ (ለምሳሌ ያህል ውል፣ መጠን ወይም ዋጋ)
ከኤሌክትሮኒክ የግብይት ተወካይ እውቅና ውጭ በምርት ገበያው የግብይት
ስርዓት ወይም አገልግሎት ላይ በተከሰተ ጉድለት ወይም ብልሽት ምክንያት ሲቀየር
ነው::

 ምርት ገበያው የግብይት ስርዓት ውስጥ ፋንተም ትዕዛዝ/ መመሪያ መግባቱ


ወይም እየገባ ስለመሆኑ ወይም ስለመፈፀሙ አሳማኝ ምክንያት ሲኖር
ምርት ገበያ ለጉዳት የተጋለጡ ግብይቶችን በተመለከተ ግብይት መዝጋት፣
የሽያጭ እና የግዥ ትዕዛዞችን መሠረዝ እና/ወይም አዲስ የሚገቡ የሽያጭ
እና የግዥ ትዕዛዞችን ማገድን ጨምሮ አስፈላጊውን እርምጃ ይወስዳል፡፡

 በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ በፋንተም ትዕዛዝ/መመሪያ ምክንያት


የተፈጸሙ ግብይቶች ከዕለታዊ የዋጋ ተመን ውጪ ተፈጽመው ከሆነ ምርት
ገበያው ግብይቶቹ እንደሚሰረዙ ወዲያውኑ ማሳወቅ አለበት፡፡ በዚህ
መሰረት ለተሰረዘ ግብይት የምርት ገበያው ምንም አይነት ተጠያቂነት
ወይም ለግብይት ተሳታፊዎች ኃላፊነት የለበትም፡፡
 በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ በፋንተም ትዕዛዝ/መመሪያ
ምክንያት የተፈጸሙ ግብይቶች በዕለታዊ የዋጋ ገደብ ውስጥ
የተፈጸሙ ቢሆንም የምርት ገበያውን ህልውናና ጤናማ
አሰራር አደጋ ላይ የሚጥሉ ከሆነ ምርት ገበያው ግብይቶቹን
መሰረዝ አለበት፡፡

 በምርት ገበያው የግብይት መድረክ የተፈጸመ ፋንተም


ትዕዛዝ/መመሪያ ካልተሰረዘ ከፋንተም ትዕዛዝ ተቃራኒውን
የያዘው ተገበያይ ምርት ገበያውን ተጠያቂ ሊያደርገው
አይችልም፡፡ ካለፈቃዱ በፋንተም ትዕዛዝ ምክንያት ለተገበያየ
ሰው ምርት ገበያው ተጠያቂ ይሆናል፡፡ ለዚህ ሰው የምርት
ገበያው ተጠያቂነት በተሸጠበት ዋጋ እና ሊሸጥ ይችልበት
የነበረው ዋጋ መካከል ያለውን የዋጋ ልዩነት ብቻ መሆን
አለበት፡፡
በኤሌክትሮኒክ የግብይት መድረክ የሽያጭ እና የግዥ ጥያቄ (አንቀጽ 5.5.2)

 ትዕዛዝ፡- ማለት በምርት ገበያው ግብይት መድረክ ላይ የምርት ገበያው ውል ለመግዛት


ወይም ለመሸጥ የግብይት ተወካይ የሚያስተላልፈው የግዥ ወይም የሽያጭ ጥያቄ ነው፡፡
(አንቀጽ 1.1.6 የኢ.ም.ገ የግብይት ተዋኒያን የስነምግባር መመሪያ)

•ትዕዛዝ ማስገባት
• በምርት ገበያው የኤሌክትሮኒክ ግብይት ማካሄድ የሚቻለው በተፈቀዱ
የኤሌትሮኒክስ ግብይት ስራ ማከናወኛ መሳሪያዎች አማካኝነት ብቻ ነው፡፡
• መመሪያ ወይም ትዕዛዝ ወደ ኤሌክትሮኒክ መገበያያ መድረክ ማስገባት የሚችለው
በምርት ገበያው የሚዘጋጀው የተጠቃሚ መለያ ቁጥር የተሰጠው ሰው ብቻ
ነው፡፡
• መመሪያ ወይም ትዕዛዝ ለማስገባት ቢያንስ የሚከተሉት መረጃዎች
ያስፈልጋሉ፡የተሰጠ መለያ ቁጥር፤የአባል መለያ ቁጥር፤ዋጋ፣ ብዛት፣ የግብይት
አይነት (የገዥ ወይም የሻጭ)፤ የሚጸናበት ጊዜ፤የቀርብበት ቦታ፤ እና የምርት
መረጃ ናቸው፡፡
የኤሌክትሮኒክ የግብይት ተወካይ የተቀበለው መመሪያ በቀጥታ ወደ
ኤሌክትሮኒክ የግብይት መድረክ ማስገባት የማይቻል ከሆነ መመሪያውን እና
የተመደበለትን ሂሳብ፣ ቀን፣ መመሪያው የተሰጠበትን ጊዜ ጨምሮ
የተሰጠውን መመሪያ በጽሁፍ መያዝ አለበት፡፡ መመሪያው መፈጸሚያው
ጊዜ ሲደርስ ወደ ኤሌክትሮኒክ የግብይት ስርዓት ውስጥ መግባት አለበት፡፡

ትእዛዝ የሚጸናበት ጊዜ (አንቀጽ 5.5.2.2)


 እስከሚሰረዝ ድረስ የሚጸና ትዕዛዝ ፡በተወሰነ ጊዜ ውስጥ ካልተፈጸመ ወይም
ትእዛዙ ከእለቱ የዋጋ ገደብ ውጪ በመሆኑ ምክንያት ካልተሰረዘ ሲስተሙ
ትእዛዙን ከምን ያህል ቀናት በኋላ መሰረዝ እንዳለበት የምርት ገበያው
ይወስናል፡፡
 ምርት ገበያው እስከ እለት ድረስ ብቻ የሚጸና ትዕዛዝ የሚቆይበትን ከፍተኛውን
ቀን ይወስናል፡፡ ይህ ትዕዛዝ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ሳይፈጸም ከቀረ ወይም
ትዕዛዙ ከእለቱ የዋጋ ገደብ ውጪ ከሆነ ትዕዛዙን ሲስተሙ ይሰርዘዋል፡፡”
ግብይቶች (አንቀጽ 5.5.3፣ 5.5.4)

 ኤሌክትሮኒክ የግብይት መድረክ ከተሳታፊዎች ማንነት በስተቀር


የተፈጸሙ ግብይቶችን ዝርዝር መረጃ በሙሉ ለተገበያዮች
እንዲታይ ያደርጋል፡፡
 የግብይት ተወካዮች ምርት ገበያው ቅጥር ግቢ ስለመገኘት (አንቀጽ 5.5.6)
የግብይት ተወካይ ወይም መመሪያ ማስገባት የተፈቀደለት ደንበኛ
ሊሳተፍበት ያሰበው ግብይት የመጀመሪያ የግብይት ክፈለ ጊዜ ከመከፈቱ
ከግማሽ ሰዓት አስቀድሞ በምርት ገበያው ቅጥር ግቢ ውስጥ በአካል መገኘት
ለግብይት የሚያገለግሉ የአባል ደንበኛ አቋም (MCP) እና የመሳሰሉትን
የቅድመ ዘግጅት መረጃ መውሰድ አለበት።
መመሪያ የማጽደቅ ቅደም ተከተል (አንቀጽ 5.5.9)

ሀ. የደንበኞች መመሪያ የሚጸድቅበት የቀደምትነት መስፈርት ጊዜ ነው ፡፡


 ለዚህም ሲባል አባላት የደንበኞቻቸውን መመሪያ በትእዛዝ መቀበያ ቅጽ ላይ
በጽሁፍ መዝገበው መያዝ አለባቸው (ይህም ከ10 አመት ላላነሰ ጊዜ መቀመጥ
አለበት) (አንቀጽ 2.5.1.1 የኢ.ም.ገ የግብይት ተዋኒያን የስነምግባር መመሪያ )፡፡

 በመመዝገቢያ ቅጹ ላይየሚመዘገቡት መረጃዎች የሚከተሉትን ሊይዝ ይችላል፡-


የደንበኛ መለያ ቁጥር፣ የመገበያያ ዋጋ፣ የግብይት አይነት (ግዥ ወይም ሽያጭ)፣
የሚጸናበት ጊዜና የመመሪያው አይነት፣ የግብይቱ አይነት እና መመሪያው
የተሰጠበት ትክክለኛ ጊዜ ናቸው፡፡ ይህንንም ምርት ገበያው በተወሰነ ጊዜ
አፈጻጸሙን ኦዲት ሊያደርግ ይችላል፡፡

• ለ. ኤሌክትሮኒክ የግብይት ተወካይ የራሱን መመሪያ የማስገባት መብት የሌለውን
ደንበኛ መመሪያ በተቀበለበት ቅደም ተከተል ወደ ኤሌክትሮኒክ የግብይት መድረክ
ያስገባል፡፡ በቂ እና ተገቢነት ባለው ምክንያት ወዲያው ወደ ኤሌክትሮኒክ የግብይት
መድረክ መግባት ያልቻለ መመሪያ ወደ ሲስተሙ በተቻለ ፍጥነት በቀረበበት ቅደም
ተከተል መሰረት መግባት አለበት፡፡
• ሐ. ከላይ የተቀመጠው ጠቅላላ ድንጋጌ ቢኖርም አባላት በእጃቸው ያሉትን
መመሪያዎች በሙሉ ሳያስገቡ የራሳቸውን ትዕዛዝ ወደ ኤሌክትሮኒክ የግብይት
መድረክ ማስገባት አይችሉም፡፡

• የግብይት ደንቦች

 ግብይት የሚገዙ አዋጆች፣ መመርያዎች እና ደንቦች በሙሉ ተፋጻሚነት ይኖራቸዋል፡፡


 ምርት ገበያዉ የሚያወጣቸዉ የአባልነት መስፈርቶች ማሟላት / በማደስ
ለአባልነት ብቁ መሆን እንዲሁም
 የአባልም ሆነ የደንበኛ ህጋዊ እና የታደሰ ንግድ ፍቃድ ይዞ ለግብይት ዝግጁ
መሆን አስፈላጊ ነው፡፡
ግብይትና የግብይት መድረክ አሰራሮች
 የምርት ገበያው አባላት ወይም አባል ያልሆኑ ቀጥታ ተገበያዮች በራሳቸው
ወይም ግብይቱን በተመለከተ በተፈቀደለት ተወካያቸው አማካኝነት ግብይት
ማከናወን ይችላሉ፡፡
ማንኛውም አባል ግብይትን በተመለከተ እስከ 4 በሚደረሱ በተፈቀደላቸው
የግብይት ተወካዮች የመወከል መብት አለው፡፡ ሆኖም በአንድ ግብይት ላይ
ተሳትፎ የሚያደርጉ የግብይት ተወካዮች ቁጥር በተመለከተ ምርት ገበያው
የሚወሰን ይሆናል፡፡ ( አንቀጽ 2.3.1 የኢ.ም.ገ የግብይት ተዋኒያን የስነምግባር
መመሪያ)
ማንኛውም አባል ያልሆነ ቀጥታ ተገበያይ በ2 የግብይት ተወካዮች የመወከል
መብት አለው፡፡ ሆኖም በአንድ ግብይት ላይ መሳተፍ የሚችለው በ1 ተወካይ
ብቻ ነው፡፡ ( አንቀጽ 2.3.2 የኢ.ም.ገ የግብይት ተዋኒያን የስነምግባር
መመሪያ )
አባሉ ወይም አባል ያልሆነው ቀጥታ ተገበያይ የታገደ ከሆነ የግብይት ተወካዩ
ወደግብይት መደረኩ መግባት የለበትም፡፡ (አንቀጽ 2.3.3 የኢ.ም.ገ የግብይት
ተዋኒያን የስነምግባር መመሪያ )

የግብይት ተወካይ ሊሳተፍ ያሰበው ግብይት ከመከፈቱ ግማሽ ሰዓት አስቀድሞ


በምርት ገበያው ግቢ ውስጥ በአካል መገኘት አለበት፡፡

ተገበያዮች ወደ ግብይት መድረኩ በመገቡበት ወቅት የመገበያያ ኩፖን


(ቶከን)፣ ጃኬታቸውን (ጋዎን) በመልበስ፣ የመግቢያ ባጃቸውን በሚታይ ቦታ
ላይ ማንጠልጠል አለባቸው (አንቀጽ 2.4.3.1 (መ) የኢ.ም.ገ የግብይት ተዋኒያን
የስነምግባር መመሪያ )
በምርት ገበያው የመገበያየት መብት
• በምርት ገበያው የመገበያየት መብት ያላቸው አባላት እና አባል ያልሆኑ
ቀጥታ ተገበያዮች ብቻ ናቸው፡፡
1. አባላት፡-የሚባሉት የምርት ገበያውን የአባልነት መቀመጫ በጨረታ
በማሸነፍ ተገቢውን ክፍያ እና የአባልነት ቅድመ ሁኔታዎች በማሟላት
በምርት ገበያው ቅድመ እውቅና አግኝተው በምርት ገበያው ባለስልጣን
መ/ቤት እውቅና የተሰጣቸው ድርጅቶች ወይምግለሰቦች ናቸው፡፡
2. 2. አባል ያልሆኑ ቀጥታ ተገበያዮች፡- በምርት ገበያው ደንብ መሰረት
አባል ያልሆኑ ቀጥታ ተገበያይ መሆን የሚችሉት አባል ወይም ደንበኛ
ሳይሆኑ ገዢ ወይም ሻጭ ብቻ በመሆን ለራሳቸው ብቻ የተላያዩ ምርት
የሚገበያዩ አቅራቢዎች፣ ላኪዎች፥ አነስተኛ ግብርና አምራቾች፥
አቀናባሪዎች እና በንግድ ላይ የተሰማሩ አምራቾች ናቸው፡፡
በተለየ ሁኔታ በሌላ ህግ ካልተደነገገ በስተቀር ማንኛውም አባል ወይም
አባል ያልሆኑ ቀጥታ ተገበያይ በምርት ገበያው መገበያየት የሚችለው በገዢ
ወይም በሻጭ ወገን ብቻ ነው፡፡
ግዴታዎች

• ማንኛውም አባል በማናቸውም ጊዜ ለዚህ ደንብ ተገዢ መሆኑና የተፈቀደላቸው


ተወካዮቹም ለዚህ ደንብ እና ለሌሎች የምርት ገበያው ደንቦች ተገዢ መሆናቸውን
ማረጋገጥ ይኖርበታል።
• ማንኛውም አባል የተፈቀደለት ተወካዩ የዚህን ደንብ ማንኛውንም ድንጋጌ የሚተላለፍ
ድርጊት መፈጸሙን እንዳወቀ ወዲያውኑ ለምርት ገበያው ማስታወቅ ይኖርበታል፡፡”
• ማንኛውም አባል የምርት ገበያው ኮሚቴ ወይም ሠራተኞች ሥራቸውን በሚያከናውኑበት
ጊዜ የመተባበር ግዴታ አለበት።
• ማንኛውም አባል ሀሰት ወይም አሳሳች መሆኑን የሚያውቀውን ወይም በምክንያታዊነት
ሊያውቅ የሚገባውን መረጃ ለምርት ገበያው መስጠት የለበትም።
• ማንኛውም አባል በተመደበለት የምርት ገበያ የመገበያያ ሥርዐት በመጠቀም
ለሚያስተላልፈው ትዕዛዝ ሁሉ ኃላፊ ነው። በዚህ መሰረት ለተፈጸመው ግብይትም ተዋዋይ
ወገን ይሆናል።
የዲስፕሊን ጥፋቶች

የምርት ገበያዉን ደንብ እና መመሪያዎችን እንዲሁም አግባብነት ያላቸዉን


ሌሎች ሕጎችን በአግባቡ አለመተግበርና አክብሮ አለመንቀሳቀስ እና ግዴታዎች
በአግባቡ አለመወጣት ወይም የተከለከሉ ተግባራትን መፈጸም በምርት ገበያው
ደንብ መሰረት የጥፋቶቹን ክብደት ግምት ውስጥ በማስገባት በዲሲፕሊን
የሚያስቀጣ ይሆናል።

የቅጣት አይነት (ወሰን)፡- እንደ ጥፋቱ ክብደትና ድግግሞሽ ሆኖ የምርት


ገበያው የስራ አፈጻጸም ኮሚቴ ከቃል ማስጠንቀቂያ ጀምሮ ከግብይት እስከ
ማገድ የሚደርስ ቅጣት ሊያስተላልፉ ይችላሉ፡፡

ከላይ የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ አንድ የግብይት ተወካይ በ6 ወር ጊዜ


ውስጥ ለ3 ጊዜ እና ከዛ በላይ ጥፋት አጥፍቶ ከተገኘ ጥፋቱን የፈጸመው
የግብይት ተወካይ እስከ 1 አመት ለሚደርስ ጊዜ ግብይት እንዳይሳተፉ ሊታገዱ
ይችላሉ፡፡ ( አንቀጽ 15.3.3.4 የተሻሻለው የምርት ገበያ ህግ ቁ. 13/2012)
የተከለከሉ ተግባራት

ማንኛውም አባል እና የግብይት ተወካይ ከሌላ ግለሰብ ጋር ባለው ቅርበት የተነሳ የተገለፁለትን
ትዕዛዞች ለሚመለከተው የምርት ገበያ ወይም ለባለስልጣን ሰራተኛ ካልሆነ በስተቀር መግለፅ
የለበትም፡፡
አባል ወይም የግብይት ተወካይ ከማንኛውም ትዕዛዝ/ መመሪያ ወይም ውል ጋር በተያያዘ ለሌላ
ሰው ወይም በሌላ ሰው ስም ሲሰራ ማታለል፣ በሀሰት ሪፓርት ማድረግ፣ ሆነ ብሎ ማጭበርበር፣
የራስን ጥቅም ማስቀደም ማስገደድ፣ አሳሳች መሆን፣ምርትን ከገበያ ማስወገድ፣ የተሳሳተ መረጃ
ማሰራጨት፣ የውስጥ አዋቂ መረጃ ተጠቅሞ ግብይት መፈጸም እና የምርት ተፈላጊነት ላይ
ሰውሰራሽ ተጽዕኖ ማድረግ የለበትም፡፡
በመገበያያ መድረኩ ላይ ተንቀሳቃሽ የመገናኛ መሣሪያዎችን (ለምሳሌ ስልክ) መያዝ
በምርት ገበያው ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚደረጉ ግብይቶች በአግባቡ እንዳይከናወኑ ሊያደርግ
በሚችል ሁኔታ መንቀሳቀስ
ተገበያዮች ወደ ግብይት መድረክ ከገቡ በኃላ እርስ በራሳቸው መነጋገር ክልክል ነው(አንቀጽ 5.3.1.5
የደ.ቁ. 12/2012)
 በምርት ገበያው የተዘጋጀ የመለያ ባጅ ሁል ጊዜ በግልፅ በሚታይ ቦታ ላይ ሳያንጠለጥል ወደ
መገበያያ መድረኩ መግባት የተከለከለ ነው። (አንቀጽ 5.3.1.3 (ሐ) የደ.ቁ. 12/2012)
አባላት፣ አባል ያልሆኑ ቀጥታ ተገበያዮች፣ የመድረክ ተወካዮች እንዲሁም
ደንበኞች የምርት ገበያውን ደንብ እና ሌሎች አግባብ ያላቸውን ህጎች በመጣስ
ጥፋቶችን ሲፈጽሙ ተፈጸሙ የተባሉት ጥፋቶች በምርት ገበያው የህግ
ማስከበሪያ መምሪያ ሰራተኞች ከተመረመሩ በሓላ የዲሲፕሊን እርምጃ
እንዲወሰድባቸው ለምርት ገበያው የግብይት አፈጻጸም ኮሚቴ ይቀርባሉ፡፡

አባላት፣ አባል ያልሆኑ ቀጥታ ተገበያዮች፣ የመድረክ ተወካዮች እንዲሁም


ደንነበኞች የህግ ጥሰቶችን በተመለከተ ለሚደረጉ ምርመራዎች ሲጠየቁ
ለምርት ገበያው አስፈላጊውን ድጋፍ መስጠት ማለትም ሰነድ ማቅረብ፣
ጥያቄዎችን መመለስ እና/ወይም በአካል ቀርቦ ማስረዳት፣ ድጋፉን እንደተጠየቀ
ወዲያውኑ መፈጸም አለባቸው፡፡

የግብይት አፈጻጸም ኮሚቴ በደንቡ ላይ የሚፈጸሙ ጥሰቶችን መርምሮ


የዲሲፕሊን እርምጃ ይወስዳል፡፡የምርት ገበያው የህግ ማስከበር መምሪያም
የቅጣት ውሳኔው እንዲፈጸም ያደርጋል፡፡
የይግባኝ መብት

15.4.5 የይግባኝ መብት


የምርት ገበያው የዲሲፕሊን ጥፋቶችን አስመልክቶ በሰጠው ውሳኔ ቅር የተሰኘ አባል አባል
ያልሆነ ቀጥታ ተገበያይ፣ የመድረክ ተወካይ ውሳኔው በተሰጠ አንድ ወር ጊዜ ውስጥ ይግባኙን
መጀመሪያ ለምርት ገበያው ቦርድ ማቅረብ አለበት፡፡ ቦርዱ አቤቱታውን ከመረመረ በኋላ
በግብይት አፈጻጸም ኮሚቴ በድጋሚ እንዲታይ ሊመራው ወይም እራሱ ውሳኔ ሊሰጥበት
ይችላል፡፡ ( 15.4.5.1)

ምርት ገበያው በሰጠው ማናቸውም የዲሲፕሊን ውሳኔ ላይ የምርት ገበያው አባል


ለባለስልጣኑ ይግባኝ ለማቅረብ ይችላል፡፡ (15.4.5.2)
ቦርዱ በሚቀርብለት ጥያቄ መሰረት የይግባኝ ሂደት እስኪጠናቀቅ ድረስ የምርት ገበያው
ውሳኔ ታግዶ እንዲቆይ ትእዛዝ ለመስጠት ይችላል፡፡ (15.4.5.3)
የግልግል/የሽምግልና ዳኝነት
የዕርቅ ሙከራው ያልተሳካ ከሆነ አስታራቂው ወይም አስታራቂዎች ተከራካሪ ወገኖች
ስላለመታረቃቸው መግለጫ በማዘጋጀት የግልግል ዳኝነት ሥርዓት ሂደቱ እንዲጀመር
ጉዳዩን ለግልግል ዳኝነት ይመሩታል፡፡
ተከራካሪ ወገኖች የግልግል ዳኝነቱ ሥራውን በተቀላጠፈ ሁኔታ እንዲያካሂድና እንዲወስን
ማንኛውንም አስፈላጊ ነገር መፈፀም አለባቸው። (16.1.24.1)
ተከራካሪ ወገኖች የመጨረሻ እና ይግባኝ የማይባልበትን የግልግል ዳኝነቱን ውሳኔ ማክበር
አለባቸው። (16.1.24.2)
አመሰግናለሁ !!

You might also like